TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ኢትዮጵያ በጣት ከሚቆጠሩ አረጋውያን፣ አፈ ማር ከሆኑ መካሪዎችዋ መካከል አንዱ የሆኑትን፣ ለመወደድ የታደሉትን የዘመናችን ጌጥ አጥታለች።
ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ከመሆኑም በላይ ዕድሜን ከጥበብ ጋር ያዋሐዱ በሁሉ ዘመን አይገኙምና ኀዘናችን ጥልቅ ነው። " - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ፎቶ ፦ ቅዱስነታቸው በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሽኝት ላይ በእምባ ተሞልተው ነበር።
Photo Credit - Ahmed Nega
@tikvahethiopia
ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ከመሆኑም በላይ ዕድሜን ከጥበብ ጋር ያዋሐዱ በሁሉ ዘመን አይገኙምና ኀዘናችን ጥልቅ ነው። " - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ፎቶ ፦ ቅዱስነታቸው በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሽኝት ላይ በእምባ ተሞልተው ነበር።
Photo Credit - Ahmed Nega
@tikvahethiopia
2😭4.02K❤1.26K🙏216💔127🕊78😢53😡21👏16🥰13😱10
" እርቦናል፤ ጠምቶናል ፣ የ8 ወር ደመወዝ አልተከፈለንም። ... በመጠጥ ውሃም ችግር ላይ ወድቀናል፣ እኛ ማንን እንጠይቅ፣ በየጊዜው አመራሮች ይቀያየራሉ፣ ህዝቡ ተቸግሯል " - ሰልፈኞቹ
➡️ " የሀገር ሽማግሌዎች መጥተው ' ለ3 ቀን ታገሱን ' ሲሉ ጠየቁን፣ እኛም አባቶቻችንን ማስከፋት ስላልፈለግን እሺ ብለናቸዋል "
በአፋር ክልል የገዋኔ ወረዳ ዞን 3 ነዋሪዎች ከደመወዝ ጥያቄ እና ከመጠጥ ውሃ ችግር ጋር በተገናኘ በዛሬው እለት ጥቅምት 10/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ ሶስት ሰአት አካባቢ ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ መንገድ በመዝጋት አካሂደዋል።
ሰልፈኞቹ በሰልፉ ላይ ፦
- " ካልተከፈለን አናስተምርም "
- " እኛ የገዋኔ ነዋሪዎች እርቦናል ፤ ጠምቶናል "
- " ለወላጅ አልባ ህጻናት የ8 ወር ደመዝ ይሰጠን " የሚሉ እና ሌሎችም ደምጾችን አሰምተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በሰልፉ ላይ የነበሩ የወረዳ ነዋሪዎችን ስለጉዳዩ ጠይቋል።
ነዋሪዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የገዋኔ ወረዳ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች በ2017 ዓ.ም የ5 ወር ደመወዝ አልተከፈለንም፣ በ2018 ዓ.ም በጀት አመት ደግሞ የሀምሌ፣ የነሀሴ እና የመስከረም ወር አልተከፈለንም። በአጠቃላይ የ8 ወር ማለት ነው።
ይህ የሆነው በወረዳው የፋይናንስ ጽህፈት ቤት ሃለፊ ነው። ሃላፊው ወረዳው ላይ አይኖርም፣ አዲስ አበባ እና አዋሽ እንደሚኖር ነው የሰማነው። ቢሮ ስንሄድ አናገኘውም። ችግሩ የማን እንደሆነም እንኳ ማወቅ አልቻልንም።
ክልሉ እራሱ ጥያቄያችንን ሰምቷል፣ በባለፈው አመት ሲከፍሉን የመቼ፣ የመቼ ወር እንኳ እንደከፈሉ አልነገሩንም።
አልፎ አልፎ ይከፍላሉ፣ እኛን እያዘናጉን ነው፣ በዘንድሮው አመት ችግሮች ይስተካከላሉ ብለን ስንጠብቅ ይሄው መስከረም አልቆ ጥቅምት ላይ ነን፣ እስካሁን ግን የተስተካከለ ነገር የለም።
የመጠጥ ውሃ ችግር በክልሉ እንደአጠቃላይ እንዳለ እናውቃለን፣ ነገር ግን የእኛ የተለየ ነው፣ ይህን የውሃ ችግር ለመቅረፍ በ2012 ዓ.ም ከወረዳዋ 30 ኪሎሜትር እርቀት ላይ ከሚገኝ ቦታ ተቆፍሮ ተሰርቶ ነበር። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ተበላሽቷል፣ ከዛም በኋላ ችግሩ ተበብሶ ቀጥሏል።
አሁን ላይ አንዱን የሮቶ ውሃው ከ250 እስከ 350 ብር እየገዛን ነው፣ ይህንን ራሱ ለመግዛት እንኳ ደመወዛችን እየተሰጠን አይደለም። የገዋኔ ነዋሪ እያየው ያለው ሰቆቃ በጣም ያሳዝናል።
የወረዳዋ ነዋሪዎች አብዛኞቹ ወላጅ አልባ ህፃናት ናቸው። እርዳታ አያገኙም፣ በጣም ችግር ላይ ናቸው፣ ደመወዝ በአግባቡ ቢሰጥ ኖሮ በቤተሰቦቻቹው የጡረታ ገንዘብ ይተዳደሩ ነበር። ይህ ግን አልሆነም።
ከሌላ አካባቢ መጥተው በወረዳዋ በመምህርነት የሚያገለግሉ መምህራኖች ስራቸውን ለቀው ወጥተዋል። በዛሬው እለትም ከትምህርት ቤት ተማሪዎች ተመልሰዋል።
መብላት እና መጠጣት ያልቻለ መምህር እንደት አድርጎ ያስተምራል ? እኛ ማንን እንጠይቅ፣ በየጊዜው አመራሮች ይቀያየራሉ፣ ህዝቡ ተቸግሯል።
ይህን ተከትሎ በዛሬው እለት የወረዳው ነዋሪ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተን ነበር። ሰልፍ የወጡት ወጣቶች በመሃል መንገድ ላይ ደረቅ እንጨት እሳት በመለኮስ ተቃውሞ አሰምተናል። ለተወሰነ ደቂቃም የትኛውም ተሽከርካሪ እንዳይንቀሳቀስ አግደን ነበር። ሰልፍ ላይ እያለን የሀገር ሽማግሌዎች መጥተው ' ለ3 ቀን ታገሱን ' ሲሉ ጠየቁን፣ እኛም አባቶቻችንን ማስከፋት ስላልፈለግን እሺ ብለናቸዋል።
አባቶች በስአቱ ያሉን ' መንገዱን ክፈቱት መኪኖች ይሒዱ፣ ለእኛ ደግሞ የሶስት ቀን እድሜ ስጡን፣ ችግሩን ለመቅረፍ በዚህ ሶስት ቀን እኛ የወረዳውን አስተዳደር እንጠይቅ፣ መፍትሔ ከሌለው ግን ለእናንተ እናሳውቃለን ' ነው ያሉት፣ እነሱን የላካቸው የወረዳው አስተዳደር እንደሆነም ሰምተናል።
ሰልፍ የወጣንበት ዋነኛ ምክንያት ለ8 አመት በመጠጥ ውሃ ችግር ላይ በመሆናችን፣ የመንግስት ሰራተኛው ደግሞ የ8 ወር ደመወዝ ስላልተከፈለው ነው። የጡረታ ደመወዝ የሚያገኙ ህፃናት በርሃብ ውስጥ ስለሆኑ ነው።
ውሃ የምንገዛው በየወሩ ነው። ይህንንም የምናገኘው በመከራ ነው። ውሃውን የሚያመጡት የመንግስት መኪኖች ናቸው። በየጊዜው ጥያቄ ስንጠይቅ መፍትሔ እናመጣለን ነው ወረዳው ምላሹ፣ ዛሬ ደግሞ የሀገር ሽማግሌዎች ሰልፍ ላይ እያለን ለሶስት ቀን እንዲንታገስ ጠይቀውናል፣ ነገር ግን አስቡት እስኪ 8 አመት ለተጠየቀ ጥያቄ በ8 አመት መመለስ ሳይችሉ በሶስት ቀን ይመለሳል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው " ብለዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ከሰጡ መካከል በወረዳው የአመራርነት የስራ ሃላፊነት ያላቸው አንድ አካል ጉዳዩ በቀላሉ እንደማይፈታ እና የፌደራል መንግስት የማህበረሰቡን ችግር ተገንዝቦ መፍትሔ ቢሰጥ የተሻለ እንደሚሆን ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
➡️ " የሀገር ሽማግሌዎች መጥተው ' ለ3 ቀን ታገሱን ' ሲሉ ጠየቁን፣ እኛም አባቶቻችንን ማስከፋት ስላልፈለግን እሺ ብለናቸዋል "
በአፋር ክልል የገዋኔ ወረዳ ዞን 3 ነዋሪዎች ከደመወዝ ጥያቄ እና ከመጠጥ ውሃ ችግር ጋር በተገናኘ በዛሬው እለት ጥቅምት 10/2018 ዓ/ም ከጠዋቱ ሶስት ሰአት አካባቢ ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ መንገድ በመዝጋት አካሂደዋል።
ሰልፈኞቹ በሰልፉ ላይ ፦
- " ካልተከፈለን አናስተምርም "
- " እኛ የገዋኔ ነዋሪዎች እርቦናል ፤ ጠምቶናል "
- " ለወላጅ አልባ ህጻናት የ8 ወር ደመዝ ይሰጠን " የሚሉ እና ሌሎችም ደምጾችን አሰምተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም በሰልፉ ላይ የነበሩ የወረዳ ነዋሪዎችን ስለጉዳዩ ጠይቋል።
ነዋሪዎቹ በዝርዝር ምን አሉ ?
" የገዋኔ ወረዳ ሁሉም የመንግስት ሰራተኞች በ2017 ዓ.ም የ5 ወር ደመወዝ አልተከፈለንም፣ በ2018 ዓ.ም በጀት አመት ደግሞ የሀምሌ፣ የነሀሴ እና የመስከረም ወር አልተከፈለንም። በአጠቃላይ የ8 ወር ማለት ነው።
ይህ የሆነው በወረዳው የፋይናንስ ጽህፈት ቤት ሃለፊ ነው። ሃላፊው ወረዳው ላይ አይኖርም፣ አዲስ አበባ እና አዋሽ እንደሚኖር ነው የሰማነው። ቢሮ ስንሄድ አናገኘውም። ችግሩ የማን እንደሆነም እንኳ ማወቅ አልቻልንም።
ክልሉ እራሱ ጥያቄያችንን ሰምቷል፣ በባለፈው አመት ሲከፍሉን የመቼ፣ የመቼ ወር እንኳ እንደከፈሉ አልነገሩንም።
አልፎ አልፎ ይከፍላሉ፣ እኛን እያዘናጉን ነው፣ በዘንድሮው አመት ችግሮች ይስተካከላሉ ብለን ስንጠብቅ ይሄው መስከረም አልቆ ጥቅምት ላይ ነን፣ እስካሁን ግን የተስተካከለ ነገር የለም።
የመጠጥ ውሃ ችግር በክልሉ እንደአጠቃላይ እንዳለ እናውቃለን፣ ነገር ግን የእኛ የተለየ ነው፣ ይህን የውሃ ችግር ለመቅረፍ በ2012 ዓ.ም ከወረዳዋ 30 ኪሎሜትር እርቀት ላይ ከሚገኝ ቦታ ተቆፍሮ ተሰርቶ ነበር። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ተበላሽቷል፣ ከዛም በኋላ ችግሩ ተበብሶ ቀጥሏል።
አሁን ላይ አንዱን የሮቶ ውሃው ከ250 እስከ 350 ብር እየገዛን ነው፣ ይህንን ራሱ ለመግዛት እንኳ ደመወዛችን እየተሰጠን አይደለም። የገዋኔ ነዋሪ እያየው ያለው ሰቆቃ በጣም ያሳዝናል።
የወረዳዋ ነዋሪዎች አብዛኞቹ ወላጅ አልባ ህፃናት ናቸው። እርዳታ አያገኙም፣ በጣም ችግር ላይ ናቸው፣ ደመወዝ በአግባቡ ቢሰጥ ኖሮ በቤተሰቦቻቹው የጡረታ ገንዘብ ይተዳደሩ ነበር። ይህ ግን አልሆነም።
ከሌላ አካባቢ መጥተው በወረዳዋ በመምህርነት የሚያገለግሉ መምህራኖች ስራቸውን ለቀው ወጥተዋል። በዛሬው እለትም ከትምህርት ቤት ተማሪዎች ተመልሰዋል።
መብላት እና መጠጣት ያልቻለ መምህር እንደት አድርጎ ያስተምራል ? እኛ ማንን እንጠይቅ፣ በየጊዜው አመራሮች ይቀያየራሉ፣ ህዝቡ ተቸግሯል።
ይህን ተከትሎ በዛሬው እለት የወረዳው ነዋሪ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተን ነበር። ሰልፍ የወጡት ወጣቶች በመሃል መንገድ ላይ ደረቅ እንጨት እሳት በመለኮስ ተቃውሞ አሰምተናል። ለተወሰነ ደቂቃም የትኛውም ተሽከርካሪ እንዳይንቀሳቀስ አግደን ነበር። ሰልፍ ላይ እያለን የሀገር ሽማግሌዎች መጥተው ' ለ3 ቀን ታገሱን ' ሲሉ ጠየቁን፣ እኛም አባቶቻችንን ማስከፋት ስላልፈለግን እሺ ብለናቸዋል።
አባቶች በስአቱ ያሉን ' መንገዱን ክፈቱት መኪኖች ይሒዱ፣ ለእኛ ደግሞ የሶስት ቀን እድሜ ስጡን፣ ችግሩን ለመቅረፍ በዚህ ሶስት ቀን እኛ የወረዳውን አስተዳደር እንጠይቅ፣ መፍትሔ ከሌለው ግን ለእናንተ እናሳውቃለን ' ነው ያሉት፣ እነሱን የላካቸው የወረዳው አስተዳደር እንደሆነም ሰምተናል።
ሰልፍ የወጣንበት ዋነኛ ምክንያት ለ8 አመት በመጠጥ ውሃ ችግር ላይ በመሆናችን፣ የመንግስት ሰራተኛው ደግሞ የ8 ወር ደመወዝ ስላልተከፈለው ነው። የጡረታ ደመወዝ የሚያገኙ ህፃናት በርሃብ ውስጥ ስለሆኑ ነው።
ውሃ የምንገዛው በየወሩ ነው። ይህንንም የምናገኘው በመከራ ነው። ውሃውን የሚያመጡት የመንግስት መኪኖች ናቸው። በየጊዜው ጥያቄ ስንጠይቅ መፍትሔ እናመጣለን ነው ወረዳው ምላሹ፣ ዛሬ ደግሞ የሀገር ሽማግሌዎች ሰልፍ ላይ እያለን ለሶስት ቀን እንዲንታገስ ጠይቀውናል፣ ነገር ግን አስቡት እስኪ 8 አመት ለተጠየቀ ጥያቄ በ8 አመት መመለስ ሳይችሉ በሶስት ቀን ይመለሳል ብሎ ማሰብ ከባድ ነው " ብለዋል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ከሰጡ መካከል በወረዳው የአመራርነት የስራ ሃላፊነት ያላቸው አንድ አካል ጉዳዩ በቀላሉ እንደማይፈታ እና የፌደራል መንግስት የማህበረሰቡን ችግር ተገንዝቦ መፍትሔ ቢሰጥ የተሻለ እንደሚሆን ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤978😭309👏35😢23🙏19🕊15💔12😡9🥰8🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Earthquake
ዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ ከዓዲግራት ደቡባዊ ምስራቅ 43 ኪሎሜትር የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ በበርካታ አከባቢዎች ላይ ንዝረት ተሰምቷል።
ከምሽቱ 1:30 የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ መረጃ ያሳያል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ ከተሰማባቸው አካባቢዎች አንዷ የትግራይ መዲና መቐለ ስትሆን ንዝረቱ በተለይም በፎቅ/ህንፃዎች ላይ አስፈሪ ስሜት እንደነበር የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
ከጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ወዲህ ንዝረቱ ትግራይ እና አፋር በርካታ አካባቢዎች ጎልቶ የሚሰማ የተለያየ ልኬት ያለው መሬት መንቀጥቀጥ እየተሰማ ነው።
በተለይ እሁድ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር ክልል የሰው ህይወት ቀጥፎ በርካታ ቤቶችን አፍርሶ ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች ያለመጠለያ እንዲቀሩ አድርጓል። በተመሳሳይ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወምበርታ ወረዳ ቤቶች እንዲፈርሱ ምክንያት ሆኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
ዛሬ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት ላይ ከዓዲግራት ደቡባዊ ምስራቅ 43 ኪሎሜትር የመሬት መንቀጥቀጥ ተከስቶ በበርካታ አከባቢዎች ላይ ንዝረት ተሰምቷል።
ከምሽቱ 1:30 የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ በሬክተር ስኬል 4.5 የተለካ እንደሆነ የአሜሪካ ጂኦሎጂካል ሰርቨይ መረጃ ያሳያል።
የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረቱ ከተሰማባቸው አካባቢዎች አንዷ የትግራይ መዲና መቐለ ስትሆን ንዝረቱ በተለይም በፎቅ/ህንፃዎች ላይ አስፈሪ ስሜት እንደነበር የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።
ከጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ወዲህ ንዝረቱ ትግራይ እና አፋር በርካታ አካባቢዎች ጎልቶ የሚሰማ የተለያየ ልኬት ያለው መሬት መንቀጥቀጥ እየተሰማ ነው።
በተለይ እሁድ ጥቅምት 2/2018 ዓ.ም የተከሰተው በሬክተር ስኬል 5.6 የተለካ የመሬት መንቀጥቀጥ አፋር ክልል የሰው ህይወት ቀጥፎ በርካታ ቤቶችን አፍርሶ ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች ያለመጠለያ እንዲቀሩ አድርጓል። በተመሳሳይ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን አፅቢ ወምበርታ ወረዳ ቤቶች እንዲፈርሱ ምክንያት ሆኗል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤479😭162🙏38😱24🕊22💔16😢15👏10🥰4😡2
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኢትዮጵያ በጣት ከሚቆጠሩ አረጋውያን፣ አፈ ማር ከሆኑ መካሪዎችዋ መካከል አንዱ የሆኑትን፣ ለመወደድ የታደሉትን የዘመናችን ጌጥ አጥታለች። ይህንን የድካም ዓለም መገላገል ለእርሳቸው ዕረፍት ቢሆንም ለአገር ግን ታላቅ ጉዳት ከመሆኑም በላይ ዕድሜን ከጥበብ ጋር ያዋሐዱ በሁሉ ዘመን አይገኙምና ኀዘናችን ጥልቅ ነው። " - ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ…
" ሀገራችንን አላህ ሰላም ያድርግልን። ሀገራችንን አላህ አማን ያድርግልን።
እኛም የምንዋደድ አላህ ያድርገን። የምንከባብር አላህ ያድርገን። የምንረዳዳ አላህ ያድርገን። የምንመካከር አላህ ያድርገን።
ጥላቻን ከውስጣችን አላህ ያጥፋው።
በሃይማኖትም ሆነ በፖለቲካ መገዳደልን፣ መጋጨትን፣ መለያየትን ከሀገራችን ከውስጣችን አላህ ያንሳልን።
እንደ አባቶቻችን ከዛም በበለጠ የምንተባበር ፣ የምንከባበር፣ የምንዋደድ ፣ የምንረዳዳ አላህ ያድረገን። " - ታላቁ አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ
@tikvahethiopia
እኛም የምንዋደድ አላህ ያድርገን። የምንከባብር አላህ ያድርገን። የምንረዳዳ አላህ ያድርገን። የምንመካከር አላህ ያድርገን።
ጥላቻን ከውስጣችን አላህ ያጥፋው።
በሃይማኖትም ሆነ በፖለቲካ መገዳደልን፣ መጋጨትን፣ መለያየትን ከሀገራችን ከውስጣችን አላህ ያንሳልን።
እንደ አባቶቻችን ከዛም በበለጠ የምንተባበር ፣ የምንከባበር፣ የምንዋደድ ፣ የምንረዳዳ አላህ ያድረገን። " - ታላቁ አባት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ
@tikvahethiopia
🙏2.8K❤1.01K😭643💔156🕊115😢61🥰30👏30😡21😱18
ዛሬውኑ የባዮሜትሪክ (የጣት አሻራና የፊት ገጽታ) ምዝገባ ያድርጉ
ውድ ደንበኛችን
ባንካችን አቢሲንያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለደንበኞቹ ቀላል፣ አመቺና ደህንነቱ የተጠበቀ እጅግ ዘመናዊ የወረቀት አልባ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ታዲያ ለዚህ አገልግሎት መሳካት የደንበኞች የጣት አሻራና የፊት ገጽታ ዋነኛ ግብዓት በመሆኑ፣ እርስዎም በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ የባዮሜትሪክ ምዝገባ እንዲያደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን። አንዴ ከተመዘገቡም፣ በየጊዜው ማንነትዎን የሚገልጽ ሰነድ ማቅረብ ሳይጠበቅብዎ፣የሚፈልጉትን የባንካችንን አገልግሎት በጣት አሻራዎ ወይም በፊት ገጽታዎ ብቻ ማግኘት ይችላሉ።
#ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #Paperlessbranchmodel #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
ውድ ደንበኛችን
ባንካችን አቢሲንያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለደንበኞቹ ቀላል፣ አመቺና ደህንነቱ የተጠበቀ እጅግ ዘመናዊ የወረቀት አልባ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። ታዲያ ለዚህ አገልግሎት መሳካት የደንበኞች የጣት አሻራና የፊት ገጽታ ዋነኛ ግብዓት በመሆኑ፣ እርስዎም በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ በመሄድ የባዮሜትሪክ ምዝገባ እንዲያደርጉ በአክብሮት እንጠይቃለን። አንዴ ከተመዘገቡም፣ በየጊዜው ማንነትዎን የሚገልጽ ሰነድ ማቅረብ ሳይጠበቅብዎ፣የሚፈልጉትን የባንካችንን አገልግሎት በጣት አሻራዎ ወይም በፊት ገጽታዎ ብቻ ማግኘት ይችላሉ።
#ወረቀትአልባየባንክአገልግሎት #Paperlessbranchmodel #BanksinEthiopia #AddisAbaba #Ethiopia #የሁሉም_ምርጫ
❤280😡23🙏15🤔8😢5
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#SamiTech
አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech
በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።
ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።
የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech
@sww2844
0928442662 / 0940141114
Telgram : https://www.tg-me.com/samcomptech
አዳዲስ ላፕቶፕች ከአንድ ዓመት ዋስትና ጋር!!
@samcomptech
በጥራት፣ በብራንድና በባትሪ ቆይታ አስተማማኝ የሆኑ የተለያዩ ሞዴል ላፕቶፖች በፈለጉት ስክሪን መጠን፣ ኮር አይ እና ጀነሬሽን አሉን።
ለቢሮዎች፣ ለተማሪዎች፣ ለዲዛይን ባለሙያዎች፣ ለጌመሮች ወ.ዘ.ተ. ሁሉም አሉን።
የዕቃዎች ዋጋ፣ ዓይነት እና አድራሻ ለማግኘት 👉 @samcomptech
@sww2844
0928442662 / 0940141114
Telgram : https://www.tg-me.com/samcomptech
❤109😡12🤔11😭4🥰2
" ባቡሩ የተጋጨው ከዚህ ወደ ጂቡቲ ሲሄድ ሳይሆን ከደወሌ ወደ ሽንሌ እየመጣ ነው አደጋው የደረሰው " - የድሬዳዋ ኮሚኒዩኬሽን
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ወረዳ በደረሰ የባቡር አደጋ እስካሁን ባለው መረጃ 12 ሰዎች መሞታቸውን የድሬዳዋ ከተማ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የሽንሌ ወረዳ አስተዳደር በበኩሉ፣ የሟቾቹን ቁጥር 14 ነው ያለ ሲሆን ከ28 የሚልቁት ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው አሳውቋል።
ወረዳው " አደጋው የደረሰው ከደወሌ መነሻውን አድርጎ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረ የድሬዳዋ ደወሌ የምድር ባቡር ድርጅት የህዝብ ማመላለሻ ባቡር ትላንት ሌሊት 8:00 አካባቢ በሶማሌ ክልል ሺኒሌ ወረዳ አካባቢ አነስተኛ ዳገታማ ስፍራ ላይ የኋለኛው ፉርጎ ተነጥሎ ወደ ኋላ በመመለሱ ለጥገና ከቆመ ሌላ ባቡር ጋር በመጋጨቱ ነው " ብሏል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡት አንድ የድሬዳዋ ከተማ ኮሚኒኬሽን አካል " አደጋው ደርሷል። እስካሁን ባለው መረጃ ወደ 12 የሚሆኑ ሰዎች ሞተዋል። ከባድና ቀላል የአካል ጉዳትም ደርሷል " ብለዋል።
አደጋው የደረሰው ባቡሩ " ወደ ጂቡቲ ሲጓዝ ነው " ሲባል የተስተዋለ ሲሆን፤ የቢሮው አካል ግን " ባቡሩ የተጋጨው ከዚህ ወደ ጂቡቲ ሲሄድ ሳይሆን ከደወሌ ወደ ሽንሌ እየመጣ ነው አደጋው የደረሰው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አደጋው የደረሰበት ትክክለኛ ቦታ ሽንሌ ነው፤ ባቡሩ ከደወሌ ወደ ሽንሌ ከዛ ወደ ድሬዳዋ ነው የሚገባው " ሲሉም አክለው አስረድተዋል። ዝርዝር መረጃውን ወደ ስፍራው የተላኩ አካላት እንዳደረሷቸው እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቃቸው የከተማ አስተዳደሩ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ፣ ጉዳዩን አጣርተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
ለተጨማሪ መረጃ ወደ ሽንሌ ወረዳ ያደረግነው መኩራ ስልክ ባለመነሳቱ ለጊዜው አልተሳካም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን ሽንሌ ወረዳ በደረሰ የባቡር አደጋ እስካሁን ባለው መረጃ 12 ሰዎች መሞታቸውን የድሬዳዋ ከተማ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የሽንሌ ወረዳ አስተዳደር በበኩሉ፣ የሟቾቹን ቁጥር 14 ነው ያለ ሲሆን ከ28 የሚልቁት ደግሞ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው አሳውቋል።
ወረዳው " አደጋው የደረሰው ከደወሌ መነሻውን አድርጎ ወደ ድሬዳዋ በመጓዝ ላይ የነበረ የድሬዳዋ ደወሌ የምድር ባቡር ድርጅት የህዝብ ማመላለሻ ባቡር ትላንት ሌሊት 8:00 አካባቢ በሶማሌ ክልል ሺኒሌ ወረዳ አካባቢ አነስተኛ ዳገታማ ስፍራ ላይ የኋለኛው ፉርጎ ተነጥሎ ወደ ኋላ በመመለሱ ለጥገና ከቆመ ሌላ ባቡር ጋር በመጋጨቱ ነው " ብሏል።
ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን የሰጡት አንድ የድሬዳዋ ከተማ ኮሚኒኬሽን አካል " አደጋው ደርሷል። እስካሁን ባለው መረጃ ወደ 12 የሚሆኑ ሰዎች ሞተዋል። ከባድና ቀላል የአካል ጉዳትም ደርሷል " ብለዋል።
አደጋው የደረሰው ባቡሩ " ወደ ጂቡቲ ሲጓዝ ነው " ሲባል የተስተዋለ ሲሆን፤ የቢሮው አካል ግን " ባቡሩ የተጋጨው ከዚህ ወደ ጂቡቲ ሲሄድ ሳይሆን ከደወሌ ወደ ሽንሌ እየመጣ ነው አደጋው የደረሰው " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
" አደጋው የደረሰበት ትክክለኛ ቦታ ሽንሌ ነው፤ ባቡሩ ከደወሌ ወደ ሽንሌ ከዛ ወደ ድሬዳዋ ነው የሚገባው " ሲሉም አክለው አስረድተዋል። ዝርዝር መረጃውን ወደ ስፍራው የተላኩ አካላት እንዳደረሷቸው እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቃቸው የከተማ አስተዳደሩ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ፈለቀ፣ ጉዳዩን አጣርተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ ገልጸዋል።
ለተጨማሪ መረጃ ወደ ሽንሌ ወረዳ ያደረግነው መኩራ ስልክ ባለመነሳቱ ለጊዜው አልተሳካም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😭882❤729💔66😢44🕊38😱20🤔9🙏8🥰7😡4
#BenishangulGumuz
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ከዘንድሮ ዓመት ጀምሮ የክልሉ የትምህርት ቋንቋ #አማርኛ እንዲሆን እና ሰባት የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች " እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት" እየተሰጡ እንዲቀጥሉ ወስኗል።
" ጊዜያዊ ነው " የተባለው ይህ አሠራር በዚህ ዓመት በቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እና በአንደኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ የሚተገበር ሲሆን በየዓመቱ ወደ ሌሎች የክፍል ደረጃዎች እያደገ እንደሚሄድ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች መኖሪያ የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፤ በክልሉ በሚነገሩ አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ትምህርት መስጠት የጀመረው በ2001 ዓ. ም. ነበር።
የመማር ማስተማሪያ ቋንቋ ሆነው ከሚያገለግሉት አፍ መፍቻዎች መካከል ፦
- ቤኒሻንጉልኛ፣
- ጉምዝኛ፣
- ሽናሽኛ እና ማኦኛ ይገኙበታል።
ኮሞኛ፣ ጓምኛ፣ ኦሮምኛ እና አማርኛም ትምህርት ይሰጥባቸው ከነበሩ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች መካከል ናቸው።
በክልሉ የሚገኙ ተማሪዎች ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ሒሳብ እና የሳይንስ ትምህርት አይነቶችን በእነዚህ ቋንቋዎች የሚማሩ ሲሆን ሰባተኛ ክፍል ላይ የመማር ማስተማሪያ ቋንቋው እንግሊዘኛ ይሆናል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ ላሉ የወረዳ፣ ልዩ ወረዳ ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች በጻፈው ደብዳቤ ከዘንድሮ የ2018 ትምህርት ዘመን አንስቶ ይህ አሠራር መቀየሩን አስታውቋል።
የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ተመስገን ዲሳሳ ውሳኔው መተላለፉን ለቢቢሲ አማርኛ አረጋግጠዋል።
በቢሮ ኃላፊው የተጻፈው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ላለፉት 17 ዓመታት ተግባራዊ ሲሆን የቆየው አሠራር የተቀየረው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ካቢኔ ባለፈው ወር መስከረም 10/2018 ዓ. ም. ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነው።
ከሁለት ሳምንት በፊት በመስከረም 21 ለክልሉ ትምህርት ቢሮ የደረሰው የካቢኔው ውሳኔ የተመሠረተው፤ በ2017 ዓ. ም. በተደረገ ጥናት ላይ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ደብዳቤው፤ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎቹ በመማሪያ ማስተማሪያነት ጥቅም ላይ በሚውሉበት ጊዜ "የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ" ይገልጻል።
ይህ የሆነውም "ከሚያስፈልገው የመምህራን ቁጥር እና ብቃት፣ ከግብአት እና ከሌሎች ችግሮች" ጋር በተያያዘ እንደሆነ ይገልጻል።
የትምህርት ቢሮው ኃላፊው ዶ/ር ተመስገን፤ " መምህራን በቂ አይደሉም፤ እንደውም የሉም ማለት ይቻላል። ያሉትም ላይ የአቅም ማነስ አለ " ሲሉ ተናግረዋል።
" ሕጻናት በራሳቸው ቋንቋ በሚማሩበት ጊዜ አካባቢውን በአግባቡ ይረዳሉ፣ የትምህርት ይዘቱንም ይረዳሉ ተብሎ ይታሰባል " ያሉት ዶ/ር ተመስገን፤ " ይህ ሊሆን የሚችለው ግን ሊያስተምር የሚችል፣ በራሱ ብቁ የሆነ መምህር ሲኖር ነው " ብለዋል።
ቋንቋዎቹን እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ለመስጠት የሚሆን የመምህር እጥረት አለመኖሩን የሚናገሩት ኃላፊው፤ ሒሳብ እና ሌሎች የሳይንስ ትምህርቶችን በአፍ መፍቻ ለማስተማር የተመረቀ መምህር ግን አለመገኘቱን ገልጸዋል።
" ያሉትም ቢሆን በሌላ ከተማሩ በኋላ ሁለት ወር ወይም አንድ ወር ቋንቋ ትርጉም እና ተያያዥ ሥልጠና የወሰዱ ናቸው " ብለዋል።
ይህ ጉዳይ " የተማሪዎች ውጤት ላይም ተጽዕኖ እያሳየ " መምጣቱን አክለዋል።
ቢሮው፤ ይህንን " ችግር ለመፍታት እና የተማሪዎችን የመማር ውጤት ለማሻሻል በ2017 ዓ. ም. ያጠናውን " ጥናት ለክልሉ ካቤኒ እንዳቀረበ ደብዳቤው ያስረዳል።
ካቤኒውም፤ " የክልሉ አቅም እስኪጎለብት እና ያሉ ችግሮች በሂደት እስኪፈቱ ድረስ በክልሉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መማሪያ ማስተማሪያ ቋንቋ አማርኛ እንዲሆን " ወስኗል ተብሏል።
" የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች ደግሞ አንድ አንድ የትምህርት ዓይነት ሆነው ብቻ እንዲቀጥል " ካቢኔው ወስኗል።
የሽግግር ሂደት ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ እየተዘጋጀ ነው ተብሏል።
ዶ/ር ተመስገን በዚህ ዓመት ይህ ውሳኔ መተግበር የሚጀምረው በቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እና በአንደኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ እንደሆነና በሚቀጥለው ዓመት ሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች ይህንን አሠራር መተግበር እንደሚጀምሩ እና በቀጣዮቹ ዓመታት ሌሎቹም የክፍል ደረጃዎች እንደሚቀላቀሉ አብራርተዋል።
ቢሮው ይህንን አካሄድ የመረጠው ከአንደኛ ክፍል አንስቶ በአፍ መፍቻ ቋንቋ እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች ላይ አዲስ አሠራር ላለመተግበር በማሰብ መሆኑንም ገልጸዋል።
አማርኛን በክልሉ የትምህርት ቋንቋነት የመጠቀም አሠራር የሚቀጥለው በአፍ መፍቻ ቋንቋዎቹ ብቁ የሆኑ፣ ፍላጎት ያላቸው ሠልጣኝ እና መምህራን እስከሚዘጋጁ ድረስ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
መረጃ የቢቢሲ አማርኛ ነው።
@tikvahethiopia
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ከዘንድሮ ዓመት ጀምሮ የክልሉ የትምህርት ቋንቋ #አማርኛ እንዲሆን እና ሰባት የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች " እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት" እየተሰጡ እንዲቀጥሉ ወስኗል።
" ጊዜያዊ ነው " የተባለው ይህ አሠራር በዚህ ዓመት በቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እና በአንደኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ የሚተገበር ሲሆን በየዓመቱ ወደ ሌሎች የክፍል ደረጃዎች እያደገ እንደሚሄድ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።
የተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች መኖሪያ የሆነው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ፤ በክልሉ በሚነገሩ አፍ መፍቻ ቋንቋዎች ትምህርት መስጠት የጀመረው በ2001 ዓ. ም. ነበር።
የመማር ማስተማሪያ ቋንቋ ሆነው ከሚያገለግሉት አፍ መፍቻዎች መካከል ፦
- ቤኒሻንጉልኛ፣
- ጉምዝኛ፣
- ሽናሽኛ እና ማኦኛ ይገኙበታል።
ኮሞኛ፣ ጓምኛ፣ ኦሮምኛ እና አማርኛም ትምህርት ይሰጥባቸው ከነበሩ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች መካከል ናቸው።
በክልሉ የሚገኙ ተማሪዎች ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ሒሳብ እና የሳይንስ ትምህርት አይነቶችን በእነዚህ ቋንቋዎች የሚማሩ ሲሆን ሰባተኛ ክፍል ላይ የመማር ማስተማሪያ ቋንቋው እንግሊዘኛ ይሆናል።
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ በክልሉ ላሉ የወረዳ፣ ልዩ ወረዳ ከተማ አስተዳደር መዋቅሮች በጻፈው ደብዳቤ ከዘንድሮ የ2018 ትምህርት ዘመን አንስቶ ይህ አሠራር መቀየሩን አስታውቋል።
የቢሮው ኃላፊ ዶ/ር ተመስገን ዲሳሳ ውሳኔው መተላለፉን ለቢቢሲ አማርኛ አረጋግጠዋል።
በቢሮ ኃላፊው የተጻፈው ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ላለፉት 17 ዓመታት ተግባራዊ ሲሆን የቆየው አሠራር የተቀየረው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግሥት ካቢኔ ባለፈው ወር መስከረም 10/2018 ዓ. ም. ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ነው።
ከሁለት ሳምንት በፊት በመስከረም 21 ለክልሉ ትምህርት ቢሮ የደረሰው የካቢኔው ውሳኔ የተመሠረተው፤ በ2017 ዓ. ም. በተደረገ ጥናት ላይ እንደሆነ ተጠቅሷል።
ደብዳቤው፤ የአፍ መፍቻ ቋንቋዎቹ በመማሪያ ማስተማሪያነት ጥቅም ላይ በሚውሉበት ጊዜ "የሚፈለገውን ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ" ይገልጻል።
ይህ የሆነውም "ከሚያስፈልገው የመምህራን ቁጥር እና ብቃት፣ ከግብአት እና ከሌሎች ችግሮች" ጋር በተያያዘ እንደሆነ ይገልጻል።
የትምህርት ቢሮው ኃላፊው ዶ/ር ተመስገን፤ " መምህራን በቂ አይደሉም፤ እንደውም የሉም ማለት ይቻላል። ያሉትም ላይ የአቅም ማነስ አለ " ሲሉ ተናግረዋል።
" ሕጻናት በራሳቸው ቋንቋ በሚማሩበት ጊዜ አካባቢውን በአግባቡ ይረዳሉ፣ የትምህርት ይዘቱንም ይረዳሉ ተብሎ ይታሰባል " ያሉት ዶ/ር ተመስገን፤ " ይህ ሊሆን የሚችለው ግን ሊያስተምር የሚችል፣ በራሱ ብቁ የሆነ መምህር ሲኖር ነው " ብለዋል።
ቋንቋዎቹን እንደ አንድ የትምህርት ዓይነት ለመስጠት የሚሆን የመምህር እጥረት አለመኖሩን የሚናገሩት ኃላፊው፤ ሒሳብ እና ሌሎች የሳይንስ ትምህርቶችን በአፍ መፍቻ ለማስተማር የተመረቀ መምህር ግን አለመገኘቱን ገልጸዋል።
" ያሉትም ቢሆን በሌላ ከተማሩ በኋላ ሁለት ወር ወይም አንድ ወር ቋንቋ ትርጉም እና ተያያዥ ሥልጠና የወሰዱ ናቸው " ብለዋል።
ይህ ጉዳይ " የተማሪዎች ውጤት ላይም ተጽዕኖ እያሳየ " መምጣቱን አክለዋል።
ቢሮው፤ ይህንን " ችግር ለመፍታት እና የተማሪዎችን የመማር ውጤት ለማሻሻል በ2017 ዓ. ም. ያጠናውን " ጥናት ለክልሉ ካቤኒ እንዳቀረበ ደብዳቤው ያስረዳል።
ካቤኒውም፤ " የክልሉ አቅም እስኪጎለብት እና ያሉ ችግሮች በሂደት እስኪፈቱ ድረስ በክልሉ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት መማሪያ ማስተማሪያ ቋንቋ አማርኛ እንዲሆን " ወስኗል ተብሏል።
" የአፍ መፍቻ ቋንቋዎች ደግሞ አንድ አንድ የትምህርት ዓይነት ሆነው ብቻ እንዲቀጥል " ካቢኔው ወስኗል።
የሽግግር ሂደት ዝርዝር የአፈጻጸም መመሪያ እየተዘጋጀ ነው ተብሏል።
ዶ/ር ተመስገን በዚህ ዓመት ይህ ውሳኔ መተግበር የሚጀምረው በቅድመ መደበኛ (ኬጂ) እና በአንደኛ ክፍል ተማሪዎች ላይ እንደሆነና በሚቀጥለው ዓመት ሁለተኛ ክፍል ተማሪዎች ይህንን አሠራር መተግበር እንደሚጀምሩ እና በቀጣዮቹ ዓመታት ሌሎቹም የክፍል ደረጃዎች እንደሚቀላቀሉ አብራርተዋል።
ቢሮው ይህንን አካሄድ የመረጠው ከአንደኛ ክፍል አንስቶ በአፍ መፍቻ ቋንቋ እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች ላይ አዲስ አሠራር ላለመተግበር በማሰብ መሆኑንም ገልጸዋል።
አማርኛን በክልሉ የትምህርት ቋንቋነት የመጠቀም አሠራር የሚቀጥለው በአፍ መፍቻ ቋንቋዎቹ ብቁ የሆኑ፣ ፍላጎት ያላቸው ሠልጣኝ እና መምህራን እስከሚዘጋጁ ድረስ እንደሆነ ጠቅሰዋል።
መረጃ የቢቢሲ አማርኛ ነው።
@tikvahethiopia
1❤1.99K👏312😡96🙏55😭32🤔29🕊21💔6🥰2😱1😢1