Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert #Tigray #Afar " ኃላቀሩ ቡድን የፌደራል መንግስትን ወደ ግጭት ለማስገባት በዓፋር በኩል ትንኮሳዎች ፈፅሟል ይህንንም የአዛዡና ጌታውን ሻዕብያ አጀንዳ ለማስፈፀም የተደረገ ነው " - አቶ ጌታቸው ረዳ ጥቂት የትግራይ ኃይል አመራሮች በሻዕብያ ትእዛዝ ሰጪነት በፌደራል መንግስት ላይ ትንኮሳ እንደጀመሩና ይህን ትንኮሳ እንዲያቆሙ አቶ ጌታቸው ረዳ አሳሰቡ። የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር…
" የእናቶች ለቅሶ እስካሁን ሊቆም አልቻለም። ያለቅሳሉ እናቶች። ያለው ቁስል አልተሻረም " - አቶ ገብሩ አስራት

➡️ " በጦርነት የሚነግዱ አሉ። በትግራይ ጦርነት በልፅገው የወጡ ፣ በጣም ሃብታሞች ሆነው የወጡ ሰዎች አሉ! "

የቀድሞው የህወሓት ታጋይ እንዲሁን የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት ጉምቱው ፖለቲከኛ አቶ ገብሩ አስራት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ ምን አሉ (ለኤንቢሲ ቴሌቪዥን) ?

" ከጦርነት የሚገኝ ትርፍ የለም።

እልቂት ፣ ጉዳት፣ ውድመት እንጂ ምንም አይነት ትርፍ ከጦርነት አይገኝም።

ማወቅ ያለብን ግን በጦርነት የሚያተርፉ አሉ። ስልጣናቸውን ማስጠበቅ የሚፈልጉ፣ ስልጣናቸውን ከፍ ማድረግ የሚፈልጉ አሉ።

በጦርነት የሚነግዱ አሉ። ይሄ  በግልጽ ታይቷል በትግራይ ጦርነት ወቅት። በትግራይ ጦርነት በልፅገው የወጡ ፣ በጣም ሃብታሞች ሆነው የወጡ ሰዎች አሉ። ሌላው ግን የነበረውን ሃብት ነው የጨረሰው፤ የነበረው ሃብት ተንኮታኮተ ፤ በመቶ ሚሊዮኖች የነበራቸው ኢንቬስተሮች፣ ነጋዴዎች ከስረዋል በዚህ ጦርነት ፤ ፋብሪካቸው ተቃጥሏል ፤ የነበራቸው ሃብት ተሽጦም ለእዳ አይበቃም ተበድረው ስለነበር። ይሄን ያየ ባለሃብት እና ነጋዴ እንደገና ጦርነት ሊል አይፈልግም።

ከዚህ በተጨማሪ በጣም የሚያሳዝነኝ የእናቶች ለቅሶ እስካሁን ሊቆም አልቻለም። ያለቅሳሉ እናቶች። ከእያንዳንዱ ቤተሰብ አንድ ሰው ፣ ከዛም በላይ የሞተበት ነው የትግራይ አካባቢ ሁኔታ። ይሄን መድገም (ጦርነት መፍጠር) ማለት ሀዘኑን፣ ምሬቱን ፣ አሰቃቂ ገጠመኙን መቀጠል ነው የሚሆነው ያለው ቁስል ሳይሽር።

ስለዚህ ይሄን መገንዘብ አለብን። በምንም መንገድ ወጣቱ ፣ ገበሬው ፣ ኤሊቱም ጭምር የሚገርመኝ ኤሊቱ ነው እያዩ ዝም የሚሉት፣ የሃይማኖት አባቶችም እንዲያውም በቅርቡ ኣክሱም ላይ የምግበይን ንግግር ቁጭ ብለው ሲያዳምጡ ነበር ' አንፈልግም ይሄን ጦርነት ' አላሉም የሃይማኖት አባቶች ጳጳሳት ተብለው ' ሰላም ነው የምንፈልገው ' አላሉም ፤ አንዳንዶቹ እንደውም ይሄን የሚመርቁ አሉ ፤ ይሄ እንዲሆን የሚሰሩ አሉ ይሄ ነገር መቆም አለበት።

የትግራይ ኤሊቶች ከቁጥር በላይ ኃይል ያለው  አቅም ያለው ነው፤ ኮኔክሽንም አለው ስለዚህ ይሄን ጦርነት ማስቆም ዋናው ስራ መሆን አለበት።

ይሄን እያልኩ ያለሁት በህወሓት ፣ በሻዕብያ / ፅምዶም የሚድረገውን ብቻ አይደለም በመንግሥትም በኩል መንግሥት ወደ ሰላም እንዲመጣ የመግፋት ጫና ማድረግ ያስፈልጋል። ጉዳቱ የሁላችንም ነው።

እኔ ትግራይ ስለምንቀሳቀስ ስለ ትግራይ አወራው እንጂ የጦርነት ጉዳት በሌላውም በኩል የሚሞተውን እገነዘባለሁ። የሚገድል ሁል ጊዜም ይሞታል ፤ የሚተኩስ ይሞታል፤ የሚያሸንፍውም ሟች ነው። ስለዚህ በሌላም በኩል የሚሰለፈውም ወጣት ነው።

የኤርትራዎቹ ወጣቶች እንደ ምርኮ የተያዘ ሰራዊት ነው። በዛም ቢሆን ያሳስበኛል። በቃ ዘላለም በጦርነት ውስጥ የተከተቱ። የሚያመልጠው አምልጦ የቀረውን ሰብስበው ወደ ጦርነት ነው የሚማግዱት። ይሄ ነገር ማብቃት አለበት ፤ ምንም ጥቅም የለውም። ከሻዕቢያ አመራሮች ውጭ የሚጠቀም ኤርትራዊ የለም።

እነዚህ (ከላይ የተጠቀሱ) ኃይሎች ሁሉ ጦርነት እንዳያደርጉ ጫና የመፍጠር ጉዳይ የዜጋው የኤሊቱ ፣ የነጋዴውም የባለሃብቱም የሁሉም መሆን አለበት። ድምጻቸውን የሚያሰሙበት ጊዜ አሁን ነው። "

#Tigray #Peace

@tikvahethiopia
1.36K🕊209😢69🙏31💔30👏24😡21😭15😱2🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Tigray
#Afar

ህወሓት ዛሬ ከሰዓት በኃላ ባወጣው መግለጫ ፤ የዓፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ " የትግራይ ሰራዊት የዓፋር ክልል ዘልቀው ገብቷል " ሲል ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ ውድቅ አድርጎታል።

ህወሓት የዓፋር መንግስት "ሓራ መሬት " በሚል ስም በአከባቢው እየተንቀሳቐሱ " ትግራይ ያውካሉ " ያላቸውን ታጣቂዎች ቦታ መስጠቱ በፅኑ ተቃውሟል።

" የኢፌዲሪ መንግስት በዓፋር ክልል ሓራ መሬት ያሉ ታጣቂዎችን በመጠቀም ሌላ ዙር ጦርነት እየጋበዝ ነው " ሲል ከሷል። 

" ትላንት ለሊት የድሮን ድብደባ ተፈጽሟል ፤ በድሮን ድብደባው የትግራይ ሰራዊትና የአከባቢው ነዋሪዎች ተጎድተዋል " ብሏል።

ህወሓት የጉዳቱ መጠኑን በቁጥር አላስቀመጠም።

" የድሮን ድብደባው የፕሪቶሪያ ስምምነት ሙሉ በሙሉ የሚጥስና የከፋ አደጋ የሚያስከትል ተግባር ነው " ሲልም አክሏል።

" የአህጉራዊ አደራዳሪ አገራት ዝምታን ተከትሎ የኢፌዲሪ መንግስት የፕሪቶሪያ ስምምነት እንዳይፈፀም እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል " ያለው ህወሓት "  አሁን የድሮን ድብደባ በማካሄድ ስምምነቱን በግልፅ ጥሶታል ሲል " ስሞታ አቅርቧል።

" የኢትዮጵያ መንግስት አሁንም ያሉ ልዩነቶች በሰላማዊ ፖለቲካዊ  ውይይት እንዲፈታ " ሲል ጥሪ አቅርቧል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
551🕊136😡62😭29👏10🤔8🙏8😱7😢4🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray #Afar ህወሓት ዛሬ ከሰዓት በኃላ ባወጣው መግለጫ ፤ የዓፋር ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የኮሙኒኬሽን ቢሮ " የትግራይ ሰራዊት የዓፋር ክልል ዘልቀው ገብቷል " ሲል ጥቅምት 27/2018 ዓ.ም የሰጠውን መግለጫ ውድቅ አድርጎታል። ህወሓት የዓፋር መንግስት "ሓራ መሬት " በሚል ስም በአከባቢው እየተንቀሳቐሱ " ትግራይ ያውካሉ " ያላቸውን ታጣቂዎች ቦታ መስጠቱ በፅኑ ተቃውሟል። " የኢፌዲሪ…
" ኃላቀሩ ቡድን የወሰደው እርምጃ የትግራይና የዓፋር ህዝቦች የጀመሩት መልካም ዝምድና የሚያበላሽ የአጥፍቶ ጠፊ ውሳኔ ነው " - ስምረት

ዲምክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ (ስምረት)  " ተስፋ አልባ ኋላቀር ቡድን " ሲል የገለፀው ኃይል " የእርስ በርስ ጦርነት ጥዶ ወደ እልቂት ከማስገባቱ በፊት የለውጥ ኃይሎች ተደራጅተን መመከት አለብን " አለ።

ስምረት ፓርቲ  ባወጣው መግለጫ " ኋላቀር ቡድን " ሲል የገለፀው አካል የፓለቲካ ፓርቲዎች ፣ የሃይማኖት መሪዎች ፣ የአገር ሽማግሌዎችና የዓለም አቀፍ ማሕበረሰብ ተማፅኖ ችላ በማለት ጥቅምት 26/2018 ዓ.ም የሻዕብያ ተልእኮ ለመፈፀም ዓፋር ክልል ዘልቆ በመግባት 6 መንደሮቾ ተቆጣጥሮ ይገኛል ብሏል።

" ድርጊቱና እርምጃው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ከማፍረስ በዘለለ የትግራይና የዓፋር ህዝቦች የጀመሩት መልካም ዝምድና የሚያበላሽ የአጥፍቶ ጠፊ ውሳኔ ነው " ሲል ስምረት ፓርቲ ኮንኗል።

ድርጊቱና የትግራይ ህዝብ ፍላጎትና ዓላማ ሳይሆን የሻዕብያ ትእዛዝ ለመፈፀም የተቃጣ መሆኑ ያብራራው ስምረት ፓርቲ ድርጊቱን አውግዞ ጦርነቱ ለማስቀረት በሰላማዊ መንገድ ትግሉ እንደሚቀጥል አሳውቋል።

" እምቢ በሻዕብያ ወታደራዊ ኮማንድ በሚመራ ስር ሆነን አንዋጋም በሉ " ሲል ስምረት ፓርቲ ለትግራይ ሰራዊት አባላት ጥሪውን አቅርበዋል።

ፓርቲው ለትግራይ ዳያስፓራ ማህበረሰብ ባስተላለፈው መልእክት ደግሞ " ከነዚህ ዕድሜ ልክ ደማችንን መጠው የማይጠግቡ መዥገሮች ለመላቀቅ እጅ ለእጅ ተያይዘን ትግላችን ከፍ እናድርገው " ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
703😡157🕊85👏28🤔23😭15💔7🥰6😱6😢4🙏3
" የፕሮጀክቱ ቁልፍ ስራ ከሆነው የወንዝ ቅልበሳ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአማራ ክልል ጎንደር እና ባሕር ዳር የስራ ጉብኝት አድርገዋል።

በጎንደር በነበራቸው የስራ ጉብኝት የመገጭ የመስኖ ልማት ፕሮጀክት የስራ ሁኔታ መገምገሙን ገልጸዋል።

870 ሄክታር ላይ እንዳረፈ የገለጹት ይኸው ፕሮጀክት 17,000 ሄክታር መሬት በመስኖ አቅርቦት ይሸፍናል ተብሎ እንደሚጠበቅ አመልክተዋል።

" የፕሮጀክቱ ቁልፍ ስራ ከሆነው የወንዝ ቅልበሳ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " የተቀሩት ስራዎችም በተያዘላቸው የጊዜ ሰሌዳ እየተካሄዱ ይገኛሉ " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፥ ከቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸውና ከከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የታደሰውን የፋሲል ጊቢ መርቀዋል።

አጠቃላይ የእድሳት ሥራው ከአንድ አመት በታች የፈጀ እንደሆነ ተገልጿል።

" በእድሳቱ ፦
- በቅርስ ስፍራው ነባሩን ታሪክ በመጠበቅ ውበቱን እና ተደራሽነቱን የማስፋት ስራ ተሰርቷል።
-  የቤተመንግሥቱ የግንባታ መዋቅር ተጠግኗል።
- የእግር መንገዶችን ማሻሻል ስራ ተሰርቷል።
- ቁልፍ የሆኑ ሕንፃዎችን ከዝግባ እና ዋንዛ ባሕላዊ ቁሳቁሶችን በመጠቀም በማደስ የስፍራውን ግለ ወጥ መልክ እና ባሕርይ የመጠበቅ ስራ ተሰርቷል።
- ለጎብኝዎች ምቾት የተሰናዱ አገልግሎት መስጫዎች ተሻሽለዋል።
- አዲስ የቱሪስት ማዕከል ተከፍቷል።
- ዘመናዊ መጸዳጃ ቤቶች፣ የተሻሻሉ የመብራት እና የደኅንነት ሥርዓቶችም ተሰናድተዋል።
- እንደ አፄ ፋሲል፣ አፄ ቀዳማዊ ዮሃንስ እና አፄ ቀዳማዊ ኢያሱ አቢያተ መንግሥት ብሎም ድልድዮች፣ መታጠቢያ ሥፍራዎች፣ ታሪካዊ በሮች ወዘተ ታድሰዋል።
- ከ40,000 ስኴር ሜትር በላይ የአካባቢው ምድር የማስዋብ ሥራ ተሰርቷል " ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ ጣናነሽ የተሰኘችው ጀልባ ሥራ መጀመራ ተገልጿል።

" ጣናነሽ በጣና ውሃ ላይ እየቀዘፈች ባሕር ዳር ከተማን ከጎርጎራ ኤኮ ሎጅ ማገናኘት ጀምራለች " ሲሉ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ገልጸዋል።

ጀልባዋ ከ180 ተጓዦች በላይ የማጓጓዝ አቅም እንዳላት አመልክተዋል።

" ለጉብኝት፣  ለመዝናናት እና አስደማሚውን የጣና ሀይቅ የተፈጥሮ ከባቢ ለመጎብኘት ወደ ጎርጎራ ኤኮ ሎጅ የሚደረገውን ጉዞ የበለጠ ምቹ አድርጋዋለች " ሲሉ አክለዋል።

#PMOEthiopia

@tikvahethiopia
1.74K😡366👏93🕊45😭39🙏33🥰27🤔23😢11
TIKVAH-ETHIOPIA
" ኃላቀሩ ቡድን የወሰደው እርምጃ የትግራይና የዓፋር ህዝቦች የጀመሩት መልካም ዝምድና የሚያበላሽ የአጥፍቶ ጠፊ ውሳኔ ነው " - ስምረት ዲምክራሲያዊ ስምረት ትግራይ ፓርቲ (ስምረት)  " ተስፋ አልባ ኋላቀር ቡድን " ሲል የገለፀው ኃይል " የእርስ በርስ ጦርነት ጥዶ ወደ እልቂት ከማስገባቱ በፊት የለውጥ ኃይሎች ተደራጅተን መመከት አለብን " አለ። ስምረት ፓርቲ  ባወጣው መግለጫ " ኋላቀር ቡድን "…
" ሕዝቡ ' እምቢ ለጦርነት ' ማለት አለበት " - የትግራይ ሙሁራን እና ባለሙያዎች ማሕበር

🚨" ህወሓት እና አንዳንድ የጦር ጀነራሎች የፕሪቶሪያ የተኩስ አቁም ስምምነትን መሰረት በማድረግ ነገሮችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ትግራይን ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ለማስገባት እየፎከሩና የጦርነት ዝግጅት እያደረጉ ነው ! "

የትግራይ ሙሁራን እና ባለሙያዎች ማሕበር (GSTS) በትግራይ ያንዣበበው የጦርነት ዳመና በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ ጥሪ አቀረበ።

ማሕበሩ ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ " የትግራይ ሕዝብ ዋናው ፍላጎት ሰላምና ሰላም ብቻ ነው " ብሏል።

ከጫፍ እስከጫፍ ያለው የትግራይ ህዝብ ጦርነትና የጦርነት ወሬ መስማት አይፈልግም ያለው ማሕበሩ " ህወሓት እና አንዳንድ የጦር ጀነራሎች የፕሪቶሪያ የተኩስ አቁም ስምምነትን መሰረት በማድረግ ነገሮችን በሰላማዊ መንገድ ከመፍታት ይልቅ ትግራይን ወደ ሌላ ዙር ጦርነት ለማስገባት እየፎከሩና የጦርነት ዝግጅት እያደረጉ ነው " ብሏል።

" ሕዝብን የሚመራ አካል ጦርነት ለማስቀረት ይጥራል እንጂ ወደ ጦርነት የሚያመሩ ንግግሮችና ተግባራትን መፈጸም የለበትም " በማለትም የክልሉን ጊዚያዊ አስተዳደርም ወቅሷል።

አሁን በአካባቢው እያንዣበበ ያለውን የጦርነት ድባብን ለማስቀረት ሕዝቡ፣ በትግራይ ሐይሎችና በዓፋር ያሉ የታጠቁ ሐይሎች እንዲሁም የዳያስፖራው ማሕበረሰብ ለሰላም መቆም እንዳለባቸው አሳስቧል።

የማሕበሩ የአመራር አባል የሆኑት ዶ/ር ገብረኪዳን ገ/ስላሴ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጡት ማብራሪያ ምን አሉ ?

" የትግራይ ሕዝብ ፍላጎት ሰላም ነው።

ሁለተኛ ጦርነት እንዳይመጣ እንጸልያለን።

ሆኖም ግን እንደዛ አይነት ጥሪ (የጦርነት ጥሪ) የሚያደርጉ በሁሉም ወገን ካሉ ወጣቱ የዚህ ሰለባ እንዳይሆን፤ ሕዝባችንም በሰራዊት ያሉም አንዱ ሀራ መሬት የሚባል አለ፤ ሌላው ቲዲኤፍ ትግራይ ውስጥ ያለው በመካከላቸው ምንም ወደ ግጭት የሚወስዳቸው ነገር ስለሌለ ወደዛ እንዳይሄዱ፤ እና ወጣቱ የጦርነት ሰለባ እንዳይሆን ጥሪ አድርገናል።

ሕዝቡ ' እምቢ ለጦርነት ' ማለት አለበት።

ያለው ልዩነት የፖለቲካ ልዩነት ነው። በፖለቲካ ውይይት እንዲፈቱት ነው የምንጠይቀው። ከዚህ በተጨማሪ ግን ህብረተሰቡ እራሱ ሕብረተሰቡ ፖለቲከኞች በሚፈጥሩት ግጭት ወደ ጦርነት እንዳይገባ የራሱን ተፅዕኖ ማድረግ አለበት። ለጦርነት ' እምቢ ' ማለት አለበት። " ብለዋል።

#Tigray #Peace

@tikvahethiopia
2K🕊392😡102🙏70😭70👏34🤔34💔21🥰17😢12
#SafaricomEthiopia

2 ቀን ብቻ ቀረው!  ቀጣይ ሚሊየነር ማን ይሆን ?🏆💚 ዛሬዉኑ የበሽ ጥቅልን ይግዙ፤ ሚሊየነር የመሆን እድሎን ያስፉ!

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡
https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን: https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom
#furtheraheadtogether
#besh
61😡5🙏3👏1
ዳሸን ባንክ እስከ 30 ሚሊዮን ብር ሽልማት ያለውን የ"ዳሸን ዕድል" ጨዋታ ይፋ አደረገ

ዳሸን ባንክ በዳሸን ሱፐር አፕ ላይ ብቻ የሚገኝ አዲስ የዲጂታል ሽልማት እና የጨዋታ ተሞክሮ የሆነውን ዳሸን እድልን በይፋ መጀመሩን አሳወቀ።

ይህበአይነቱ ልዩ የሆነው የሱፐር አፕ እድል እስከ 30 ሚሊዮን ብር የሚደርስ ጠቅላላ የሽልማት ገንዘብ ያለው ሲሆን፣ ይህም የዳሸን ሱፐር አፕ ተጠቃሚዎች የባንኩን ዘመናዊ ዲጂታል አገልግሎቶች በመጠቀም አስደሳች ሽልማቶችን የማግኘት ልዩ እድል የሚሰጣቸው ነው።

የዳሸን ዕድል ሎተሪ ደንበኞች እንዲሳተፉ እና እንዲያሸንፉ በአርኪ መንገድ የቀረበ ጨዋታ ነው፡፡ የዳሸን ሱፐር አፕ ተጠቃሚዎች በዕለት ተዕለት በሚያደርጓቸው ዲጂታል ግብይቶች፣ (ማለትም የገንዘብ ዝውውሮችን በማድረግ፣ ሱፐር አፕን በማውረድ እና በመጠቀም፣ ከሌሎች ባንኮች ገንዘብ በመቀበል፣ የንግድ ክፍያዎችን በመፈፀም፣ የአየር ሰዓት በመሙላት እንዲሁም ሌሎች በመተግበሪያው ውስጥ የሚገኙትን የቻት ባንኪንግና የበጀት አገልግሎቶችን) እና ሌሎች አገልግሎቶችን በመጠቀም በቀላሉ "ሳንቲሞችን" መሰብሰብ ይችላሉ፡፡

ደንበኞች ከዚያም የሰበሰቡትን ሳንቲሞች በመጠቀም ስልኮቻቸውን "በማወዛወዝ" እና ከሞባይል ዳታ ፓኬጆች አንስቶ ከ100 ብር እስከ 100,000 ብር የሚደርሱ የኤሌክትሮኒክስ የገንዘብ (e-money) ሽልማቶችን፣ ሳምሰንግ ጋላክሲ ኤስ 23 እና ኤ 54፣  አይፎን 16 ሞዴል ስልኮችን እንዲሁም አዲስ የቢዋይዲ መኪና ሽልማቶችን ማሸነፍ ይችላሉ።

ከጥቅምት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ዳሸን ባንክ በዳሸን ዕድል የማስተዋወቅ ዘመቻው በሺዎች የሚቆጠሩ ሽልማቶችን ለአሸናፊዎች መስጠት ጀምሯል። ይህ የማስተዋወቅ ዘመቻ የዳሸንን ደንበኞች ለመሸለም ብቻ የቀረበ ሳይሆን ደንበኞች በዳሸን ሱፐር መተግበሪያ ላይ የቀረቡትን በርካታ የአገልግሎት አይነቶች እንዲጠቀሙ ለማነሳሳት የተነደፈ ነው።

ዛሬውኑ ይህን አስደሳች ጨዋታ ይቀላቀሉ!

የዳሸን ሱፐር መተግበሪያን ያውርዱ፣ ሳንቲሞችን ማግኘት ይጀምሩ፣ እና በዳሸን ባንክ የዲጂታል ባንክ ሕይወትን የሚቀይሩ ሽልማቶችን ለማሸነፍ እድልዎን ይጠቀሙ።

የዳሸን ባንክ ሱፐር አፕ መተግበሪያ ያውርዱ 👇  https://www.dashensuperapp.com/download
212🙏11😱7🤔4😢4
" ባለፉት ስድስት ወራት የንቁ ደንበኞችን ቁጥር በእጥፍ በማሳደግ 11.1 ሚሊየን መድረስ ችለናል " - ሳፋሪኮም

የሳፋሪኮም ኩባንያ የኢትዮጵያ ክንፍ የሆነው ሳፋሪኮም ቴሌኮሙኒኬሽን ኢትዮጵያ ኃ.የተ.የግ.ማ. የንቁ ደንበኞች ቁጥር 11.1 ሚሊዮን መድረሳቸውን ይፋ ተደርጓል።

ሳፋሪኮም ባለፉት ስድስት ወራት የንቁ ደንበኞቹን ቁጥር በእጥፍ በማሳደግ 11.1 ሚሊየን መድረስ መቻሉን ገልጿል።

ተቋሙ በኬንያ እያሳየው ያለው ቀጣይነት ያለው እድገት ዋነኛው የትርፍ አንቀሳቃሽ ሆኖ ቀጥሏል የተባለ ሲሆን በኢትዮጵያም እያጋጠመው ያለውን ኪሳራ ማጠበብ መቻሉን ተጠቁሟል።

በኢትዮጵያ የደረሰበት ኪሳራም ካለፈው በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ ጋር ሲነጻጸር በ59 በመቶ ቅናሽ አለው ነው የተባለው።

የሳፋሪኮም ዋና ሥራ አስፈፃሚ ፒተር ንዴግዋ " አስቸጋሪ የስራ ሁኔታ ቢኖርም፣ በሁሉም ገበያዎች አውታረ መረባችንን በማስፋት እና በማሳደግ ጠንካራ እድገት አሳይተናል " ብለዋል።

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ የሚሰጠው አገልግሎት ባለፉት ስድስት ወራት 47.9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱ የተገለጸ ሲሆን ይህም ከአንድ ዓመት በፊት ካለው አፈጻጸሙ ጋር ሲነጻጸር በእጥፍ ጭማሪ አለው።

ከአጠቃላይ ትርፉ የሞባይል ዳታ 66.7 በመቶ ሲይዝ የድምፅ 22.1 በመቶ እና የመልእክት ልውውጦች 11.2 በመቶ ይይዛሉ።

የሶስት ወራት ንቁ ደንበኞች ቁጥር በ83.7 በመቶ በመጨመር ወደ 11.2 ሚሊዮን ከፍ ማለቱን እና የአንድ ወር ንቁ ደንበኞች ቁጥር ደግሞ ወደ 8.51 ሚሊዮን ማደጉን ተገልጿል።

ሳፋሪኮም " ከኢትዮጵያ የሚገኘው ገቢ ከ60 በመቶ በላይ አድጓል፣ ይህም በሞባይል ዳታ እና በድምጽ አጠቃቀም መጨመር ምክንያት የመጣ ነው " ብሏል።

ይህም ኩባንያው በኬንያም ሆነ በኢትዮጵያ አፈጻጸሙን ማሻሻሉን ማሳያ መሆኑን ተገልጿል።

ኩባንያው በሃገሪቱ ካሉት የኔትወርክ ማማዎች ውስጥ 1847 የሚሆኑት በራሱ የተገነቡ ሲሆን 1,459 የሚሆኑት ደግሞ በኪራይ የሚጠቀማቸው ናቸው።

በተቋሙ በተገነቡ እና በኪራይ በሚጠቀማቸው የኔትወርክ ማማዎች አማካኝነትም 55 በመቶ የህዝብ ሽፋን (Population coverage) መድረስ መቻሉን አሳውቋል።

ኤም-ፔሳ ኢትዮጵያም ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ 12.3 ቢሊዮን ብር እንቅስቃሴ (ግብይት) እንደተከናወነበት ተገልጿል።

ከተንቀሳቀሰው ገንዘብ በተጨማሪም 3.4 ሚሊዮን የ90 ቀናት ንቁ ተጠቃሚዎችን ማፍራቱን ተጠቁሟል።

ኤም ፔሳ በመላ አገሪቱ ከ30,700 በላይ ደንበኞችን ማፍራቱን ይፋ የተደረገ ሲሆን፤316ቱ የነዳጅ ማደያዎች ናቸው ተብሏል።

በኢትዮጵያ የኤምፔሳ ተጠቃሚዎች ቁጥር ቢጨምርም ካለፈው በጀት አመት ጋር ሲነጻጸር ግን ገቢው በ64.3 በመቶ ቀንሷል ነው የተባለው።

ባለፈው ዓመት፣ የሳፋሪኮም ግሩፕ በሴፕቴምበር 30፣ 2024 መጨረሻ ላይ የስድስት ወራት ያልተጣራ ትርፉን ይፋ ሲያደርግ የኤም-ፔሳ በኢትዮጵያ ገቢ 24.4 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ የነበር ሲሆን የዘንድሮ አመት የኢትዮጵያ የኤም-ፔሳ ገቢ ወደ 8.7 ሚሊዮን የኬንያ ሽልንግ ዝቅ ማለቱን ኩባንያው አሳውቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
372🙏20👏15🕊7🥰5🤔5😡4💔3😭1
#Ethiopia

ባንኮች እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ ማጠናቀቅ ይኖርባቸዋል ተባለ።

ብሔራዊ ባንክ እና የብሔራዊ መታወቂያ በጋራ ባወጡት አዲስ የአተገባበር ሥርዓት መሰረት የፋይናንስ ተቋማት ብሄራዊ ኦፕሬተር በሆነው ኢት-ስዊች በኩል ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰር ሥራ መስራት መጀመራቸው ተገልጿል።

እስካሁን 10 የሚሆኑ የፋይናንስ ተቋማት ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር የማስተሳሰሩን ሥራ ጨርሰዋል ሲባል ሌሎች ባንኮች በሙከራ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።

የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ይለበስ አዲስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለጹት ይህ አሰራር ባንኮች አገልግሎታቸው ቀልጣፋ እንዲሆንና ማዕከላዊ የመረጃ አያያዝ እንዲኖር ያስችላል ሲሉ ገልጸዋል።

አክለውም ትስስሩ ባንኮች ከደንበኞቻቸው ጋር ያላቸውን አገልግሎት ያሳልጥላቸዋል፤ ወጪንም ይቆጥብላቸዋል ነው ያሉት።

የኢት-ስዊች ቺፍ ፖርት ፎልዮ ኦፊሰር (CPO) አቤኔዘር ወንደሰን በበኩላቸው ከዚህ በፊት ደንበኞች አካውንት ሲያወጡ ባንኮች የደንበኛውን መታወቂያ ለማረጋገጥ ሁለት መቶ ብር በአንድ ሰው ክፍያ እንደሚጠበቅባቸው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

በአዲሱ አሰራር ባንኮች ስንት እንደሚከፍሉ ተመን ባይወጣላቸውም ክፍያው ሲወሰን ከሀምሳ ብር እንደማይበልጥና ይህም ባንኮችን ከብዙ ወጪ እንደሚያድናቸው አክለው ተናግረዋል።

ባንኮች እስከ ህዳር አጋማሽ ድረስ ጥምረት አድርገው መጨረስ እንዳለባቸውም ነው አቤኔዘር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩት።

ባንኮቹ ከብሔራዊ መታወቂያ ጋር በቀጥታ ትስስር አይኖራቸውም ሲባል ትስስር የሚኖራቸው በኢት-ስዊች በኩል እንደሆነም ተገልጿል።

ኢት-ስዊች ሁሉንም ባንኮች ያስተሳሰረ ስለሆነ ብሔራዊ መታወቂያ ከኢት-ስዊች ጋር በመቀናጀት ሁሉንም ባንኮች በአንድ ጊዜ ማግኘት ይችላል።

የባንክ አካውንት ሲከፈት ባንኮች የብሔራዊ መታወቂያ ቁጥሩን ወደ ኢትስዊች ልከው ኢት-ስዊች ባንኩ ስለደንበኛው የሚያስፈልገውን መረጃ (KYC) ከብሔራዊ መታወቂያ ተቀብሎ ለባንኮቹ መልሶ ይልካል።

የብሔራዊ መታወቂያ የጣት አሻራን በክፍያ ወቅት እንደ ይለፍ ቃልም መጠቀም እንዲቻል አሁን ላይ የተጀመሩት ትስስሮች እንደሚያግዙም ተጠቅሷል።

ኢት-ስዊች የፋይናንስ ሪፖርቱን በቅርቡ ሲያቀርብ በባለፈው በጀት ዓመት፥ ጠቅላላ ገቢው 2.2 ቢሊዮን ብር መሆኑን ጠቅሶ ከታክስ በፊት 1.42 ቢሊዮን ብር ማትረፉንና ይህም ካለፈው የበጀት ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ34% ጭማሪ ማሳየቱን ገልጿል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ


@tikvahethiopia
867😡284😭51🤔28🕊17💔13👏8🙏6😢4
2025/11/09 02:03:41
Back to Top
HTML Embed Code: