Telegram Web Link
TIKVAH-ETHIOPIA
“የ9 ጤና ባለሙያዎች ሕይወት አልፏል። 7ቱ ከአርሲ፣ ሁለቱ ከባሌ ናቸው” - የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ➡️ “የተጎዱት ወደ 8 ይደርሳሉ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አራት ናቸው። በአጠቃላይ 28 ባለሙያዎች ተሳፍረው ነበር” - ዞን ጤና ቢሮ ከኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ተውጣጥተው ለትምህርት ወደ ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሲጓዙ በነበሩ ጤና ባለሙያዎች በመኪና አደጋ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የክልሉና የዞኑ…
" አሽከርካሪዎች በተለይ ኦላንጪቲ ከተማን ለጉዞ በሚያቋርጡበት ወቅት ጥንቃቄ አድርጉ " - ዋና ኢንስፔክተር ስለሽ ባይ

ከትላንት በስቲያ ለሊት በምስራቅ ሸዋ ዞን ቦሳት ወረዳ ልዩ ስሙ " ጋር " የተባለ ስፍራ በደረሰው የትራፊክ አደጋ 7 የጤና ባለሙያዎችን ጨምሮ 9 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል።

አደጋው ከአዳማ ወደ መታሃራ ሲጓዝ የነበረ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከአይሱዙ መኪና ጋር በመጋጨቱ ነበር የደረሰው።

ከዚሁ አደጋ ጋር በተያያዘ የቦሰት ወረዳ የትራፊክ ደህንነት አስተባባሪ ዋና ኢንስፔክተር ስለሽ ባይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል የአደጋው መንስኤ አሽከርካሪው ከተገቢው በላይ በፍጥነት ማሽከርከር በተለይም በምሽት መጓዝ ነው።

" መንገዱን በውል ለማያውቁት ከፍተኛ የትራክፊክ ፍሰት ስለሚያስተናግድ ጥንቃቄ ማድረግ ግዴታ ነው " ሲሉ አሳስበዋል።

በአደጋው ከሞቱት 9 ሰዎች መካከል ሰባቱ የህክምና ባለሙያዎች ሲሆኑ በአርሲ ዞን አግልግሎት ላይ የነበሩ እና ለሞያ አቅም ግንባታ እና ለፈተና ወደ ሀሮማያ ዩኒቨርስቲ ስጓዙ የነበሩ እንደሆኑ ይታወሳል።

ሶስት ከባድ የአካል ጉዳት እና አምስት ቀላል የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ስዎች  በአዳማ እና ቦሳት ሆስፒታል በህክምና ላይ ይገኛሉ።

ኢንስፔክተር ስለሽ ባይ አደጋው የደረሰበት አካባቢ የከባድ ተሽከርካሪዎች መተላለፊያ መሆኑን በመጠቆም የህዝብ ማመላለሻ አሽከርካሪዎች በተለይ ኦላንጪቲ ከተማን ለጉዞ በሚያቋርጡበት ወቅት ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ

@tikvahethiopia
477😢285😭79💔25🙏20🕊16🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የስምረት ፓርቲ መስራች ጉባኤ አቶ ጌታቸው ረዳ የፓርቲው ፕሬዝደንት አድርጎ መረጠ።

አቶ ነጋ አሰፋ ደግሞ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንት አድርጎ መርጧል።

አቶ ሃፍቱ ኪሮስ ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሁም ሰብለ አሰፋ የፓርቲው ፅህፈት ቤት ኃላፊ ሆነዋል።

ለማእከላዊ ኮሚቴ ከመረጣቸው 31 አባላት ውስጥ ፦

1. አቶ ጌታቸው ረዳ
2. ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ሂወት
3. ወ/ሮ ኣልማዝ ገ/ፃድቕ
4. አቶ ብርሃነ ገ/የሱስ
5. አቶ ሃፍቱ ኪሮስ
6. ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ
7. አቶ ነጋ ኣሰፋ

የፓርቲው ስራ አስፈፃሚ አድርጓቸዋል።

- አቶ ሙላት ገ/ስላሴ
- አቶ ጠዓመ ዓረዶም
- ዶ/ር ሺሻይ ኣማረ 
- ወ/ሮ ኬሪያ ኢብራሂም
- አቶ ፀጋይ ገ/ተኽለ
- ዶ/ር ርእየ ኢሳያስ 
- አቶ ገ/ሚካኤል እኑን
- አቶ ዮናስ ሃይለ
- አቶ ተስፋኣለም ይሕደጎ
- አቶ ኤርሚያስ ኣባቡ
- አቶ ስላስ ሃፍቱ
- አቶ ፀጋይ ፃዲቕ
- አቶ የማነ ንጉስ
- አቶ ሃፍቱ ወ/ንስአ
- አቶ ደስታ ግርማይ 
- አቶ ወ/ሰንበት ተ/ኪሮስ
- አቶ መብራት ስዩም
- ዶ/ር ዮናስ ገ/ሄር
- ዶ/ር ከላሊ ኣድሀና
- ቀሺ በሪሁ ሓዱሽ
- አቶ ተዘራ ጌታሁን
- አቶ ፍፁም ለገሰ
- ወ/ሮ ኣስኳል ገብረ
- አቶ ፀጋይ ገ/ጂወርጊስ

ደግሞ የፓርቲው የማእከላይ ኮሚቴ አድርጎ በመምረጥ የአንድ ቀን ጉባኤውን ማምሻውን አጠናቋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
1.12K😡168🤔78😭39🕊32🙏18😢9👏8💔8🥰3
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሾፌሩ ምንም ጉዳት ሳይደርስበት ከተገለበጠው ተሽከርካሪ ውስጥ ወጥቷል ! " ዛሬ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ አረዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ሶር አምባ ሆቴል ፊት ለፊት ከቀኑ 6:45 ሠዓት ላይ የትራፊክ አደጋ የአጋጠመ ሲሆን በአደጋው በንብረት ላይ መጠነኛ ጉዳት ከመድረሱ በስተቀር በሠው ላይ የደረሰ ጉዳት የለም። አደጋው በደረሰበት ሰዓት መኪናውን እያሽከረከረ የነበረዉ ሾፌር ምንም…
" ተአምር ነው ! "

ተሽከርካሪው 150 ሜትር ርዝማኔ ያለው ገደል ገብቶ አርሶ አደር ግቢ ውስጥ ቢያርፍም ከቀላል ጉዳት ውጪ ያጋጠመ ከባድ ጉዳትና ሞት የለም።

በትግራይ ክልል የሚገኘው የጥንታዊው አቡነ አረጋዊ ገዳም ዝክር በየዓመቱ የአገር ውስጥና ከውጭ የሚመጡ ምእመናን በተገኙነት ጥቅምት 14 ነው የሚከበረው።

ታዲያ በ" ቶዮታ " ተሽከርካሪ ባለቤቱ እራሱን ጨምሮ 5 ሰዎች ጭኖ ዓመታዊው የአቡነ አረጋዊ ገዳም ለመሳለም በመጓዝ ላይ እያለ ተሽከርካሪው መንገድ ስቶ ተንሸራቶ ገደል ይገባል።

ተሽከርካሪው የገባበት ገደል ርዝማኔው 150 ሜትር ነው ብለዋል የአይን እማኞች።

ተሽከርካሪው መንገድ ስቶ ወደ ገደል ከተወረወረ በኃላ በፎቶው እንደሚታየው ወደ አንድ አርሶ አደር ቤት ግቢ ገብቶ ተዘቅዝቆ አርፏል።

ከአስፈሪ ገደል ተወርውሮ በሚታየው መልኩ ያረፈው ተሽከርካሪ በአርሶ አደር ቅጥር ግቢ ከነበሩት ሰዎችና እንስሳት ላይ አንድ ቀላል ጉዳት ከማድረሱ ውጪ የተከሰተ ከባድ ጉዳትና ሞት የለም።

ክስቱቱን ለሰሙት " ተአምር " ያስባለ እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ቤተሰብ አባል ገልጾልናል።

አሽከርካሪዎች ለማሽከርከር በሚያዳግቱና ተዳፋት በሆኑ መንገዶች ላይ ሲያሽከረክሩ እርጋታና ማስተዋል ሊለያቸው አይገባም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia
3.9K🙏1.25K😱123🤔68🕊61👏47💔35😡20🥰17😭11😢3
#SafaricomEthiopia
#MPESASafaricom

እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉💵

ባሳለፍነው ጥቅምት 10 በነበረን የስምንተኛ ዙር ዕድለኞች ዕጣ አወጣጥ መሰረት የ1,000,000 ብር እድለኛ ከሻሸመኔ እንዲሁም የ100,000 ብር እድለኛ ደግሞ ከጅጅጋ ሆነዋል!

ማን ያውቃል ቀጣይ እርስዎ ሊሆኑ ይችላሉ! የበሽ ጥቅል እየገዛን እንንበሽበሽ! 🥳🎉🎉

ሌሎች የ100ብር አሸናፊዎች #Besh100Winner በመጠቀም ኮሜንት ላይ ወይም story ላይ ሳፋሪኮም ኢትዮጽያን ታግ በማድረግ ያሳውቁን።

📲 የM-PESA መተግበሪያን አሁኑኑ ያውርዱ፡ https://onelink.to/ewsb22

የቴሌግራም ቦታችን👉🏽 https://www.tg-me.com/official_safaricomet_bot

ወደ *777*0# ይደውሉ ወይም በM-PESA የበሽ ጥቅል ይግዙ!

#furtheraheadtogether
#Besh100Winner
149😡11😱6🙏6😢5💔4🤔2
" ድርጊቱና አሳፋሪና ከሙያው ስነምግባር የወጣ ነው። የትኛውም ሰው ከሙያ ባህሪው የወጣ ነገር ሲሰራ በሕግ ይጠየቃል "- ስልጤ ዞን ፖሊስ

➡️ " እምቢታ ካለም ሴትዮዋን በሕግ መጠየቅ ይቻል ነበር። ይህን አለመከተሉ የፓሊስ አባሉ ችግር ነው። በቁጥጥር ስር ውሎ ታስሯል! "

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በስልጤ ዞን ምስራቅ ስልጢ ወረዳ ገርቢ በር ከተማ አንድ የፖሊስ አባል አንዲት እናት ለሽያጭ ያቀረበችውን ጎመን በእግሩ በመበታተን ከጥቅም ውጭ ማድረጉና ይህችውን እናት ማመናጨቁ በርካቶችን በብርቱ አስቆጥቷል።

የፖሊስ አባሉ ለሽያጭ የቀረበውን ጎመን በእግሩ ሲበታትነው የሚያሳይ ቪዲዮ በገሃድ የተሰራጨ ሲሆን፣ ይህንኑ አስነዋሪ ድርጊት የተመለከቱና በቦታው የነበሩ ነዋሪዎች " ከፖሊስ የማይጠበቅ፣ የእናትን እና የስራን ክብር የጣሰ ተግርባር በመሆኑ ፖሊሱ በሕግ ሊጠየቅ ይገባል " ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፥ በጉዳዩ ዙሪያ የስልጤ ዞን ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኮማንደር ኑረዲን አብደላን አነጋግሯል።

ኮማንደር ኑረዲን ነገሩ መከሰቱን አረጋግጠዋል።

የፖሊስ አባሉ ድርጊቱን መፈጸሙን ገልጸው፣ " ድርጊቱ አሳፋሪና ከሙያው ስነምግባር የወጣ ነው። የትኛውም ሰው ከሙያ ባህሪው የወጣ ነገር ሲሰራ በሕግ የሚጠየቅበት አግባብ አለ " ነው ያሉት።

" መደረግ የሌለበት ነው፥ ለዚህ የሚያበቃም አይደለም፥ ጤናማ በሆነ መንገድ ማንሳት፣ እምቢታ ካለም ሴትዮዋን በሕግ መጠየቅ ይቻል ነበር። ይህን አለመከተሉ የፓሊስ አባሉ ችግር ነው። በቁጥጥር ስር ውሎ ታስሯል " ሲሉም አክለዋል።

" ቦታው ቁልቁለት ስለሆነ ለሰው ደህንነት ሲባል ሌላ የገበያ ቦታ ተቀይሯል። ግን እዛ ቦታ ላይ መጥተው ይቀመጣሉ (ነጋዴዎች) ወደ ተፈቀደው ቦታ እንዲሄዱ ለማድረግ ፖሊሶች በቦታው ይመደባሉ "ሲሉ አስረድተው፥ ድርጊቱ የተፈጸመው ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ/ም በዚሁ በተከለከለ ቦታ ቁጭ ብላ በነበረች ሴት መሆኑን ገልጸዋል።

ለገበያ ከተፈቀደው ቦታ ሰዎቹን ያነሷቸው ሌሎች የከተማው አካላት ጭምር እንደሆኑ፥ ፖሊስም በቦታው እንደሚመደብ ኮማንደሩ አስረድተዋል።

ፖሊስ ድርጊቱ የተፈጸመባትን እናት ቀርቦ ያደረገላት ድጋፍ አለ ? ስነ ልቦነዋ እንዳይጎዳስ ምን ተደረገላት ? ለሚለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ፥ " ፖሊስ፥ ሌሎች የማህበረሰብ አካላትም ድጋፍ ለማድረግ ጥረት እያደረጉ ነው " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
1.43K😡531😭126👏110💔72🙏48😢20🕊18😱13🤔10🥰5
የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ምዝገባ ነገ እሁድ ልዩ በሆነ መልኩ እንዳለ ሰምተዋል?

ለፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ለመመዝገብ አስበው ጊዜ እና ሰዓት አልመቻች ብሎዎታል? ተማሪዎችስ ከትምህርት ሰዓት ውጭ ለመመዝገብ? እንግዲያው ነገ ጥቅምት 16 በልዩ ሁኔታ በሁሉም የምዝገባ ጣቢያዎች አገልግሎት ስለምንሰጥ በአቅራቢያዎ በሚገኝ የምዝገባ ጣቢያ በመሔድ ይመዝገቡ።

ለተጨማሪ መረጃ id.gov.et ይጎብኙ ወይም 9779 ይደውሉ።

#ፋይዳለኢትዮጵያ #ፋይዳለሁሉም #ፋይዳምዝገባ
138😡18🤔17🕊4🥰3
" በስልጠና ማጠናቀቂያ ወቅት ያገኙት ሰርተፍኬት በዩኒቨርሲቲው ለመማር በሚወዳደሩበት ወቅት 10 በመቶ ውጤት እንዲኖረው እናደርጋለን "- የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር (ኢመደአ) ከአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በ2017 ዓ/ም የክረምት መርሃ ግብር በሳይበር ደህንነትና ተያያዥ ዘርፎች ያሰለጠናቸውን 629 ታዳጊ ወጣቶችን በዛሬው ዕለት አስመረቋል።

ታዳጊዎቹ በክረምት መርሃ ግብር የሰለጠኑት ፦
- በሳይበር ደህንነት፣
- በቴክኖሎጂ ልማት፣
- በኢምቤድድ ሲስተም፣ እና በኤሮስፔስ ዘርፎች ነው።

ላለፉት ሦስት አመታት አዲስ አበባ ላይ ብቻ ሲካሄድ የቆየው የስልጠና መርሃ ግብር፤ በ2017 ዓ/ም ከባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ለመጀመሪያ ጊዜ 76 ልጆች ሰልጥነው መመረቅ መቻላቸው ተገልጿል።

ስልጠናውን የተከታተሉት ታዳጊዎች ከኢለመንተሪ፣ ሃይስኩል እና ዩኒቨርሲቲ የተወጣጡ ናቸው ።

ታዳጊዎቹ ስልጠናቸውን ከኢንሳ በተጨማሪ  በአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ (AASTU) ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በማጠናቀቂያው ወቅት የተሰጣቸው ሰርተፍኬት በዩኒቨርሲቲው ትምህርት ለመከታተል በሚወዳደሩበት ወቅት የመቁረጫው ነጥብ ዝቅ እንደሚያደረግላቸው የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጀ እንግዳ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

የአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ደረጀ እንግዳ በዝርዝር ምን አሉ ?

" ግቢ ውስጥ በቆዩበት ጊዜ በተለያዩ ዘርፎች ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ቆይተዋል ስልጠናውን ኮርስ በመስጠት ብቻ ሳይሆን ችግሮቻችንን በመንገር ችግሮችን መፍታት ከመቻላቸውም በላይ ፕሮዳክቶችን ይዘው መጥተዋል።

የራሳቸው የሆነ የተለያዩ ችግሮችን መፍታት እና መሸጥ የሚችሉ ፕሮዳክቶችን ይዘው ወጥተዋል።

እኛ ፈተና ፈትነን ተማሪዎችን የምንቀበል መሆኑ ይታወቃል ፈተና ፈትነን ስንቀበል የ 12 ውጤት እና የመግቢያ ፈተና ውጤት ነው የምናየው።

በእዚህ ስልጠና ከመላው የኢትዮጵያ አካባቢዎች መጥተው በግቢያችን ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ ተማሪዎች የወሰዱት ሰርተፍኬት በግቢያችን ለመማር በሚያመለክቱበት ወቅት ቫልዩ ይኖረዋል።

ከእዚህ ቀደም ስናወዳድር 50 በመቶ 12 ክፍል ውጤት 50 በመቶ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ውጤት እንመለከት ነበር አሁን 10 በመቶ በስልጠና ማጠናቀቂያው ወቅት ያገኙትን ሰርተፍኬት እንዲይዝ  እናደርጋለን።

አንድ ላይ ተደምሮ ከመቶ ሲያዝ የመቁረጫ ነጥብ ላይ ባመጡት ቁጥር ዝቅ ያደረግላቸዋል ፣ ልዩ ኮታ ይሰጣቸዋል ማለት ነው ።

ይህንን እድል አምናም ሰጥተናል ዘንድሮ ከገቡ መካከልም ይህንን እድል ያገኙ አሉ በሚቀጥለው አመትም ይህ ይቀጥላል።

ሁለተኛ እዚህ ስልጠናቸውን የተከታተሉ ተማሪዎች የተለያዩ ፕሮዳክቶችን አውጥተዋል እኛ ዩኒቨርሲቲ ውስጥ የኢንዱስትሪያል ኢኖቬሽን እና ኢንኩቤሽን ሃብ ሰርተናል ይህ ሃብ ወደ 189 ስታርታፖችን መቀበል ይችላል።

እነዚህ ስታርታፖች ከተለያዩ ቦታ እና ዩንቨርሲቲዎች የተወጣጡ ሊሆኑ ይችላሉ ነገር ግን ሜድ ኢን ኢትዮጵያ ምርቶች ያላቸው እና መሸጫ ቦታ ያጡ ሰዎችን የምናሰባስብበት ቦታ ነው።

ይህንን ስፔስ (ቦታ) ስልጠናውን ለተከታተሉ ሰዎች ለሰሯቸው ምርቶች (ፕሮዳክቶች) እናቀርባለን።

የምናቀርበው በሁለት አይነት መንገድ ነው አቅሙ ኖሯቸው በራሳችን እንቀጥል ካሉ የተወሰነ ኪራይ እናስከፍላለን ፣ምንም አቅም የለንም የሚሉ ካሉ ከተለያዩ ባለሃብቶች እና ከዩኒቨርሲቲውም አንድ ላይ አድርገን ድጋፍ በማድረግ ምርታቸው ወደ ገበያ እንዲወጣ እና ስራ ፈጣሪ እንዲሆን ድጋፍ እናደርጋለን " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
310😡21🙏5🤔3🕊2🥰1😱1
የስንዴ ምርት አቀነባባሪ አምራቾች ለረጅም ጊዜ ሲያቀርቡት የነበረው ቅሬታ መፈታቱ ተገለጸ።

ለብዙ ጊዜ በገቢዎች ሚኒስቴር እና በስንዴ አቀነባባሪዎች አጨቃጫቂ የነበረው የታክስ ጉዳይ መፍትሄ አግኝቷል።

የገቢዎች ሚኒስቴር ጥቅምት 4 ቀን 2018 ባሰራጨው ሰርኩላር የስንዴ ምርት አቀነባባሪ አምራቾች ለስንዴ ግዢ የሚፈጸም ክፍያ ላይ የነበራቸው ተደጋጋሚ ቅሬታ ላይ የገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔ መሰጠቱን ገልጿል።

ከገንዘብ ሚኒስቴር በዶ/ር እዮብ ተካልኝ (የቀድሞ ሚኒስትር ዴኤታ) የተፈረመውና ለገቢዎች ሚኒስቴር የተላከው ደብዳቤ ጉዳዩ ለብዙ ጊዜ ለአምራቹ ኢንዱስትሪ እና ለሻጭ ጫና እየፈጠረ መሆኑንን በመጥቀስ ብዙ ጥያቄዎች ይቀርቡበት እንደነበር አንስቷል።

በገንዘብ ሚኒስቴር የተጻፈው ደብዳቤ ምን ውሳኔዎችን አሳለፈ ?

- ደብዳቤው፥ ለስንዴ ግዥ የሚፈፀም ክፍያ ላይ የቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት (Witholding tax) ተፈጻሚ እንዳይሆን መወሰኑን ይገልጻል።

- የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ደርሷቸው፤ በታክስ ውሳኔ ቅሬታ አጣሪ ጽ/ቤት በሂደት ላይ ያሉ እና በቀጣይ የታክሱን ትክክለኛነት ለማጣራት በሚደረጉ የኦዲት ሥራዎችም ላይ ውሳኔው ተፈጻሚ እንዲሆን ያዛል።

- የግብይት ሥርዓቱ ወደ ዘመናዊነት ተቀይሮ ትክክለኛ የግዥ ደረሰኝ ማግኘት እስኪቻል ድረስ የስንዴ ግዢ በግዥ ማረጋገጫ (Purchase vouchern የተፈጸመ ግብይት ከሆነ የገንዘብ መጠን ሳይገድበው የተፈጸመው ክፍያ ለስንዴ ሻጩ በባንክ የተላለፈ መሆኑ፣ የስንዴ ዱቄቱ በስታንዳርዱ መሠረት ስለመመረቱ እየተረጋገጠ ገቢውን ለማመንጨት የወጣው ወጪ ተቀባይነት እንዲኖረው የሚያስችል ሥርዓት በታክስ ባለስልጣኑ በኩል እንዲዘረጋ መወሰኑን ይጠቅሳል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የደብዳቤውን ትክክለኛነት ከገቢዎች ሚኒስቴር ማረጋገጥ ችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia
490🙏41🕊16😢10🤔7😭7🥰4😱4
2025/10/26 02:29:31
Back to Top
HTML Embed Code: