Telegram Web Link
#MinistryofRevenue

" የግብር ክሊራንስ " የምስክር ወረቀት የብድር መከልከያ ምክንያት መሆን የለበትም ሲል የገቢዎች ሚኒስትር ማሳሰቢያ ሰጠ።

የገቢዎች ሚኒስቴር ባንኮች የግብር ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ይዘው ለብድር ለሚቀርቡ ደንበኞች የተለመደውን የብድር አገልግሎት እንዳይከለክሉ ማሳሰቢያ መስጠቱ ተመላክቷል።

ሚኒስቴሩ በቅርቡ በሚሰጠው የምስክር ወረቀት ላይ የተቀመጠው የታክስ ቅድሚያ መብት ድንጋጌ የብድር አሰጣጥ ሂደቱን የሚቀይር አዲስ መብት አለመሆኑን በማስታወቅ፣ ባንኮች የምስክር ወረቀቱን ተቀባይነት እንደሌለው ሊያስቡ እንደማይገባ አስታውቋል።

የገቢዎች ሚኒስትር ለብሔራዊ ባንክ እና ለሁሉም ባንኮች በሚል በፃፈዉ ደብዳቤ ላይ እንደተመላከተዉ ግብር ክሊራንስ የምስክር ወረቀት የሚሰጠው ግብር ከፋዩ በሕጉ መሠረት የተጣለበትን ታክስ የመክፈል ግዴታ ሲወጣ መሆኑን ገልጿል።

በተጨማሪም፣ ለታክስ ባለስልጣኑ በቅድሚያ መከፈል እንዳለባቸውና በየትኛውም ህግ ወይም ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ክፍያዎች መሆናቸው በግልጽ ተቀምጧል።

ሚኒስቴሩ እየተሰጠ ባለው የታክስ ክሊራንስ የምስክር ወረቀት ላይ የሰፈረው የቅድሚያ መብት ድንጋጌ፣ ከላይ የተጠቀሰውን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ድንጋጌ ለማካተት እንጂ፣ ለባለስልጣኑ ሌላ አዲስ ልዩ መብት ለመስጠት እንዳልሆነ አብራርቷል።

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የካፒታል ጋዜጣ ነው።

@tikvahethiopia
372👏29🤔14🥰11🙏7😭5😡2😢1
“የ9 ጤና ባለሙያዎች ሕይወት አልፏል። 7ቱ ከአርሲ፣ ሁለቱ ከባሌ ናቸው” - የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ

➡️ “የተጎዱት ወደ 8 ይደርሳሉ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አራት ናቸው። በአጠቃላይ 28 ባለሙያዎች ተሳፍረው ነበር” - ዞን ጤና ቢሮ

ከኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ተውጣጥተው ለትምህርት ወደ ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ሲጓዙ በነበሩ ጤና ባለሙያዎች በመኪና አደጋ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የክልሉና የዞኑ ጤና ቢሮ ባለስልጣናት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የኦሮሚያ ክልል ጤና ቢሮ ምክትል ኃላፊ ዶ/ር ተስፋዬ ከበበው ፣ “የመኪና አደጋ ነው የደረሰው፤ የዘጠኝ ጤና ባለሙያዎች ሕይወት አልፏል። 7ቱ ከአርሲ፣ ሁለቱ ከባሌ ናቸው” ሲሉ ሰማሁት ያሉትን መረጃ ነግረውናል።

አደጋው የደረሰው ጤና ባለሙያዎቹ ለፈተና ወደ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ እየተጓዙ በነበረበት ወቅት መሆኑንም አስረድተዋል።

ተጨማሪ ማብራሪያ የጠየቅናቸው የአርሲ ዞን ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን ሐምዲኖ፣ ጤና ባለሙያዎቹ ለትምህርት (ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ ለኢንትራንስ ፈተና) ወደ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በኮንትራት መኪና እየሄዱ እንደነበር፤ ብዙዎቹ ከአርሲ እንደሆኑና ወለንጪቲ አካባቢ ሲደርሱ አደጋው እንዳጋጣማቸው አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ ሞትና የጉዳት መጠን የደረሰባቸው ስንት ናቸው? ብሎ ሲጠይቃቸውም፣ “የሞቱት 7 ናቸው፤ ሦስት ወንድና አራት ሴት። የተጎዱት ወደ ስምንት ይደርሳሉ፤ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው አራት ናቸው” ብለዋል።

በመኪናው በአጠቃላይ 28 ሰዎች ተሳፍረው እንደነበር፣ ሁሉም ከተለያዩ ወረዳዎች የተውጣጡ ጤና ባለሙያዎች እንደነበሩ ገልጸው፣ “ሁሉም የጤና ጣቢያ ሠራተኞች ናቸው” ነው ያሉት።

ከተሳፋሪውቹ መካከል፣ “በ4ቱ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፤ አራቱ ታክመው ወጥተዋል” ያሉት ኃላፊው፣ አሰላና አዳማ ሆስፒታሎች ህክምና እየተከታሀሉ ያሉ ጤና ባለሙያዎች መኖራቸውንም ጠቁመዋል። 

አደጋው የደረሰው ከአዳማ ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲጓዙ ወለንጪቲ እንደደረሱ ትላንት ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ/ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ገደማ መሆኑንም ገልጸዋል።

አደጋው የተከሰተው፣ ከሀረርጌ ወደ አዳማ በርበሬ ጭኖ ሲጓዝ የነበረ አይሱዚና ባለሙያዎቹን የጫነው ተሽከርካሪ ተጋጭተው መሆኑም አቶ ሱልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

በጉዳቱ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማቸው አስረድተው፣ “የመኪና አደጋ በጣም እየበዛ ነው፤ ትራንስፓርትና ሎጂስቲክስ ቢሮዎች በደንብ መስራት አለባቸው። በየቀኑ የሰው ሕይወት እየጠፋ ነው፤ ንብረት ላይም ውድመት እየተደረሰ ነው፤ ጥንቃቄ ያስፈልጋል” ሲሉ አሳስበበዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
😭751362💔64😢32🕊16🙏7👏5🥰4😱3😡2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸው የይዘት አካባቢዎች ይፋ አድርጓል።

የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡ 

1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ

ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ኬሚስትሪ፣
- ፊዝክስና ባዮሎጂ

ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ታሪክ፣
- ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።

2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡

3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡

5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ ይገባል፡፡

#EAES

@tikvahethiopia
1.03K😭87🤔71👏47😡31🙏30🕊11🥰10😢8😱2
#SafaricomEthiopia

ሚሊየነር ለመሆን ተዘጋጅተዋል?
የሳፋሪኮምን የበሽ ጥቅልን በM-PESA በመግዛት የማሸነፍ ዕድላችንን በእጥፍ እናሳድግ።

ይህ ዕድል እንዳያመልጥዎ!

ለተጨማሪ መረጃ በቴሌግራም ያግኙን፥
https://www.tg-me.com/MPesaETCustomerCare

#MPESASafaricom #MPESAEthiopia
48🙏5😭5😡2😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " በክልሉ አድማ ብተናና መደበኛ ፖሊስ እየተወሰደ ያለዉ የሃይል እርምጃዉ ቀጥሎ ከብት በመጠበቅ ላይ የነበሩ 2 ንፁሃን አርሶአደሮች ተገድለዋል " - ነዋሪዎች ➡️ " ' የሃይል እርምጃ ተወስዶ ሁለት አርሶአደሮች ተገድለዋል ' የሚባለው ፍፁም የዉሸት መረጃ ነዉ። ሽፍቶችን ለመያዝ እየተደረገ ባለዉ ኦፕሬሽን እስካሁን የሞተ ሰዉ የለም " - የጋሞ ዞን ፖሊስ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል…
" የሶስት ወጣቶች በመንግስት የፀጥታ ሃይል መገደላቸው ዳግም በአከባቢው ዉጥረት እንዲነግስ ምክንያት ሆኗል " - የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል አቶ አብርሃም አሞሼ

የዘይሴ ብሔረሰብ በአሁኑ ወቅት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ስር የሚተዳደር ሲሆን እራስን በራስ ለማስተዳደር ባነሳዉ ጥያቄ መነሻ ባለፉት ዓመታት ለተለያዩ ችግሮች ተዳርጎ መቆየቱን ‎በኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ም/ ቤት አባልና የዘይሴ ብሔረሰብ ተወካይ አቶ አብረሃም አሞሼ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

" ‎የዘይሴ ብሔረሰብ ህዳር 29/1987 ዓ/ም የኢፌዴሪ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ከመሰረቱና ሕገ መንግስቱን ካፀደቁ ብሔረሰቦች መካከል አንዱ ቢሆንም እራሱን በራሱ የሚያስተዳድርበት መዋቅር የሌለው በመሆኑ ቋንቋ፣ ባህሉና ማንነቱ እየተበረዘ መምጣቱን ተከትሎ እራሱን በራሱ ለማስተዳደር የመዋቅር ጥያቄ ላለፉት 30 ዓመታት እየጠየቀ ቆይቷል " ብለዋል።

‎በተለያዩ ምክንያቶች የብሔረሰቡ ጥያቄ በአግባቡ ሳይመለስ መቆየቱን ተከትሎ ለተከታታይ ዓመታት ለመንግስት ጥያቄ ሲያቀርብ የቆየዉ የዘይሴ ብሔረሰብ በ6ኛዉ ዙር ሀገራዊ ምርጫ የኢዜማ ፓርቲን በሙሉ ድምፅ በመምረጡ በገዢዉ ፓርቲ ልዩ ልዩ ተፅእኖዎች ሲደረጉበት መቆየቱን ገልጸዋል።

‎በተለይም በአካባቢዉ ባለፉት ሁለት ዓመታት የኢዜማ አመራሮች እና አባላት ያለአግባብ መታሰራቸውንና ከስራም ጭምር መባረራቸዉ እንዲሁም በርካታ አርሶአደሮች ከቀያቸው መሰደዳቸውን በመግለፅ ይህ ድርጊት በአሁኑ ወቅትም መቀጠሉን አስታውቀዋል።

" ‎በጥቅምት መግቢያ የብሔረሰቡ ተወላጅ የሆኑ ሶስት ወጣቶች በመንግስት የፀጥታ ሃይሎች መገደላቸውን ተከትሎ በአከባቢው ውጥረት እንዲነግስ ምክንያት ሆኗል " ያሉት አቶ አብረሃም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህን መረጃ በሰጡበት ዕለትም በአከባቢው ውጥረት መንገሱንና የኢዜማ አመራሮችና አባላት መታሰራቸውን ተናግረዋል።

‎ይህን ተከትሎም ፦
- ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር
- ለብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት፣
- ሰላም ሚንስትር፣
- ለፍትህ ሚንስትር፣
- ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድና ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ደብዳቤ መፃፋቸዉንና ለችግሩ ዘላቂ መፍትሔ እንዲበጅለት መጠየቃቸውን አስረድተዋል።

‎ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአርባምንጭ ኮንሶ የሚወስደዉ መንገድ በአከባቢው ባለዉ አለመረጋጋት ስጋት ተዘግቶ መዋሉን አሽከርካሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የተናገሩ ሲሆን ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ጋሞ ዞን ፖሊስ አዛዥ እንዲሁም ወደ አርባምንጭ ዙሪያ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ደዉሎ የነበረ ቢሆንም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሳይሳካ ቀርቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa

@tikvahethiopia
161😭68🙏9😡7👏6🕊1
TIKVAH-ETHIOPIA
" የሰላምና የዕርቅ ዕድል ቅድሚያ እንዲሰጠው ጉባኤው የበኩሉን ጥረት ማድረግ ይገባዋል " - ቅዱስነታቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የቅዱስ ሲኖዶስ ዓቢይ ጉባኤ መጀመሩን አስመልክቶ መልዕክት አስተላልፈዋል። በዚህም መልዕክታቸው የርስ በርስ ግጭቶች ቆመው ግጭቶች በውይይት እና በድርድር እንዲፈቱ…
#Update

ቅዱስ ሲኖዶስ የአህጉረ ስብከት ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት ምደባ ውሳኔ አሳለፈ።

1. የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ቶማስ የአዊና የመተከል አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከትን ደርበው የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከትን እንዲመሩና እንዲይዙ ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

2. የደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት የከሚሴ የደቡብ ወሎ ልዩ ዞን  የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ ደርበው እንዲመሩ ምልዓተ ጉባኤው  ወስኗል፡፡

3. የምሥራቅ ወለጋንና የሆሮ ጉድሩን ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ጳጳስ ሀገረ ስብከታቸውን እንደያዙ  ደርበው እንዲመሩ የቅዱስ ሲኖዶስ  ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

4. ብፁዕ አቡነ ኤውስጣቴዎስ  የአሉባቦር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ  የምዕራብ ወለጋና ደርበው እንዲመሩ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ወስኗል፡፡

ውሳኔዎቹ የተወሰኑት አሁን ላይ በተደራቢ እንዲመሩ የተያዙት አህጉረ ስብከት በዘላቂነት ሊቃነ ጳጳሳት ተመድበው እስከፈታ ድረስ የተወሰነ ውሳኔ መሆኑን ቅዱስ ሲኖዶስ አሳውቋል። #EOTCTV

@tikvahethiopia
345🙏33🕊26😡23😭12🤔10🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update አቶ ታዬ ደንደአ ወደ ማረሚያ ቤት እንዲወርዱ ፍርድ ቤት አዘዘ። የቀድሞ የሰላም ሚኒስትር ዴዔታ አቶ ታዬ ደንደአ የዋስትና መብታቸው ተነስቶ ጉዳያቸውን ማረሚያ ሆነው እንዲከታተሉ ዛሬ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሰጥቷል። ፖሊስ አቶ ታዬን ዛሬ ፍርድ ቤት አቅርቧል። አቃቤ ህግ ከዚህ ቀደም የተዘጉ ሁለት ክሶችን ጨምሮ መዝገቡ በፍርድ ቤቱ እንዲቀሳቀስ ጠይቋል። አቶ ታየ ደንደአ…
#ችሎት

በእስር ላይ የሚገኙ የቀድሞ ሰላም ሚንስትር ዴኤታ አቶ ታዬ ደንዳአ ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ።

አቶ ታዬ " ህገወጥ የጦር መሣሪያ መያዝ፤ ጠላትን ማገዝ እና በጉልበት ህገመንግስት ለመናድ ከሚሰሩ ቡድን ጋር መተባበር " በሚሉት ወንጀሎች ነው ተጠርጥረው የታሰሩት ሲሉ የህግ ጥበቃቸው አቶ አበራ ንጉስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

አቶ ታዬ ዳንዳአ ተጠርጥረው በተከሰሱበት ወንጀል በዋስ መብት ከተለቀቁ ከተወሰን ወራት በኃላ ዳግም ግንቦት 25 ቀን 2017 ዓ.ም ታስረው በቂልንጦ ማረምያ ቤት ይገኛሉ።

በተጠረጠሩበት ወንጀሎች የመጨረሻ ውሳኔ ለመስጠት ልደታ ፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፀረ ሽብር ችሎት ሀምሌ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጥሮ ሰጥቶ ነበር።

የአቶ ታዬ መዝገብ ተመርምሮ ዛሬ ውሳኔ ለመስጠት ቢቀጥርም ፍርድ ቤቱ በተደራራብ ስራዎች መዝገቡን አጣርቶ ውሳኔ ለመስጠት ግዜ አለማግኘቱን ገልፆ ተለዋጭ ቀጠሮ  ገልፆል።

በዛሬው ችሎት ከሳሽ አቃቢህግ እንዳልቀርበ ጠበቃቸው አቶ አበራ ተናግረዋል።

የአቶ ታዬ ዳንዳአ ጠበቃ አቶ አበራ ንጉስ ደንበኛቸው ከዚህ ቀደም ታስረው ባሉበት የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እንደደረሰባቸው ለፍርድ  ቤቱ አቤቱታ አቅርበው በጉዳዩ ላይ ትዛዝ አለመሰጠቱን ፤ እንዲሁም  ከሁለት ወር ቆይታ በኃላ መዝገባቸው ተመርምሮ አለማለቁ ቅር እንዳሰኛቸው ለችሎቱ ማስረዳታቸውን ገልፀዋል።

ሆኖም የፌዴራል ልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፀረ ሽብር ወንጀል ችሎት ውሳኔ ለመስጠት ለጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል ሲሉ አቶ አበራ ንጉስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
381😢119😡60😭29💔22🕊14🙏13🥰2
#ሀዋሳ

" ባልተገባ መልኩ ተይዘዋል " ያላቸውን የመንግሥት ቤቶች በማስለቀቅ ለከተማ ነዋሪዎች ማስተላለፍ ጀምራለሁ ሲል የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር አሳወቀ።

ከተማ አስተዳደሩ ይህን ያለው በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ ነው።

የግል ቤት ኖሯቸው በመንግሥት ቤት ውስጥ የሚኖሩትን በማስለቀቅ ለሚገባቸው የከተማው ነዋሪዎች አስረክባለሁ ብሏል።

በቅርቡ የተሾሙት አዲስ ከንቲባ አቶ ተክሌ ጆምባ " በተለያዩ አጋጣሚዎች በከተማዋ የሚገኙ የመንግሥት ቤቶች የመንግሥት ቤት  ወደማይገባቸው ግለሰቦች ተዘዋውሯል " ያሉ ሲሆን " በተለይ የግል ቤት ኖሮአቸው በመንግሥት ቤት የሚኖሩ ግለሰቦችን ቤት በመረከብ ለሚገባቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ለማስተላለፍ ዝግጅት ተደርጓል " ሲሉ ገልጸዋል።

" የክልሉ መንግሥት ይህ ተፈፃሚ እንዲሆን አቅጣጫ አስቀምጧል ፤ የከተማው አስተዳደርም ለተፈፃሚነቱ በቁርጠኝነት ይሰራል " ብለዋል።

ከተማ አስተዳደሩ ፦
- ይህ ቤቶችን የማስለቀቅ ስራ በምን አግባበ እንደሚመራ፣
- ከመቼ ተጀምሮ ተፈጻሚ እንደሚሆን፣
- ስንት ቤቶች ባልተገቡ ሰዎች እንደተያዙ በይፋ  ያለው ነገር የለም።

@tikvahethiopia
260👏69😭19🤔13😡7🕊6😢4🙏2
የገቢዎች ሚኒስቴር የደመወዝ ስኬል መሸጋገሪያ ሰንጠረዥ ይፋ ተደርጓል።

የደሞዝ ስኬሉን ትክክለኛነት ቲክቫህ ከፌደራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን አረጋግጧል።

በ13 ደረጃዎች የተከፈለውን የደሞዝ ስኬል ከተያያዘው ፋይል ላይ ይመልከቱ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
304😡131😭55👏27🙏21🤔18😢11😱9🥰4💔4
2025/10/24 01:40:01
Back to Top
HTML Embed Code: