Telegram Web Link
በሱዳን ጦርነት ለሚዋጉ የኮሎምቢያ ተዋጊዎች የቦሳሶ ወደብ መሸጋገሪያ መሆኑ ተነገረ።

የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምታስተዳድረው በቦሳሶ የሚገኝ ወታደራዊ ማዘዣ ለተዋጊዎቹ መሸጋገሪያ መሆኑ ተገልጿል።

የቀድሞ የኮሎምቢያ ጦር አባላት ለግለሰባዊ ደህንነት ከተመለመሉ በኋላ ለሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል እንዲዋጉ ይደረጋሉ ተብሏል።

አንድ የኮሎምቢያ ተዋጊ 2600 ዶላር በወር የሚያስገኝለትን ኮንትራት መፈረሙን ገልፆ #በኢትዮጵያ በኩል አድርጎ ወደ ፑንትላንድ ቦሳሶ ወደብ መወሰዱን በኋላም በዳርፉር መስፈሩን ገልጿል።

የቦሳሶ ወደብ መጀመሪያ በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ሲሰራ የፑንትላንድ የባህር ኃይልን ለማሰልጠን ነበር ሲባል አሁን ሙሉ ለሙሉ የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የምትቆጣጠረው ማዘዣ ነው ተብሏል።

ምንም እንኳን የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች በሱዳን ጦርነት ያላትን ተሳተፎ ብትክድም ከሰሞኑ የቦሳሶ ወደብ እንዴት የኮሎምቢያ ተዋጊዎች መሸጋገሪያ እንደሆነና የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እየተጠቀመች እንደሆነ የሚያሳይ የምርመራ ዘገባ ወጥቷል።

ዘ ጋርዲያንና La Silla Vacia የተሰኘ የኮሎምቢያ ጋዜጣ በጉዳዩ ላይ የሰሩትን የምርመራ ሪፖርት ከዚህ ማንበብ ይችላሉ።

@TikvahethMagazine
86😢9🕊9👎4👍3
🤙 ኑሮዎን ፒያሳ ላይ ያድርጉ

➣ ውብ አፓርትመንቶቻችን ለኑሮ ምቹ በሆነችው አዲሲቷ ፒያሳ ላይ እርሰዎን ይጠብቃል

   
     66 ካሬ ባለ 1 መኝታ
                 
➣  40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ  6,072,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 5,313,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
      
              2 መኝታ 75 ካሬ
  
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ
6,900,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 6,037,500 ብር ጠቅላላ ዋጋ

          3 መኝታ 106 ካሬ

➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ 9,752,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

➣100% ለከፈለ  30% ቅናሽ 8,533,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

❗️ልብ ይበሉ ከላይ የተፃፉት አነስተኛ ካሬዎች ለ ምሳሌ ሲሆኑ ከፍ ያለ ካሬ ማግኜት ትችላላችሁ

ለበለጠ መረጃ
         👇
☎️
+251986687513

WhatsApp:- +251986687513
Email:-
[email protected]
16🤔1
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ  መታሰቢያ ሐውልት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጥቅምት 9 ቀን  2018 ዓ.ም ይመረቃል።

ምንጭ : EOTC

@TikvahethMagazine
186🤣13😢5👍4
በጠለፋና በአስገድዶ መድፈር የተከሰሰው ግለሰብ በ15 አመት ጽኑ እስራት ተቀጣ።

በካፋ ዞን በቢጣ ወረዳ ኦጊ ዳኪቲ ቀበሌ የካቲት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ ገበያ ለመገበያየት እየሄደች ያለች የግል ተበዳይን ጠልፎ በመድፈር ወንጀል ተከሶ በ15 ዓመት እስራት መቀጣቱን ወረዳው አስታውቋል።

ተከሳሽ ለጊዜው እጃቸውን ለፖሊስ ካልሰጡ ግብራበሮቹ ጋር በመሆንና ስለታማ ቁስ በእጁ ይዞ በማስፈራራት የጠለፋ ወንጀል በመፈፀም ወደ ጌሻ ወረዳ ሀነቶ ቀበሌ አስገድዶ ስለመውሰዱ ነው ፖሊስ ያስረዳው።

በዚሁ መሠረት የቢጣ ወረዳ ፍርድ ቤት  ጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው የወንጀል ችሎት ተከሳሹ ኤልያስ ቆጭቶ በሁለት ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ15 አመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል።

@TikvahethMagazine
👎4424😢17👏7🤔1🤬1
#Oromia: በኦሮሚያ ክልል በአዲስ መልክ ለተደራጁ የቀበሌ መዋቅሮች 6 ሺህ 800 የሞተር ብስክሌቶች ተከፋፍሏል።

የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ሽመልስ አብዲሳ የሞተር ብስክሌቶቹ በቀበሌ መዋቅር የመንግሥት አገልግሎት ፈጣን፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ የሚሰራውን ሥራ የሚያግዙ በመሆኑ በአግባቡ ለተፈለገው ዓላማ እንዲውሉ አስገንዝበዋል። [OBN]

@TikvahethMagazine
👍66👎6418🤔11
#እንድታውቁት

ከዚህ ቀደም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሳይኖራችሁ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላችሁ ግብር ከፋዮች ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥራችሁን ከፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ጋር በአካል መሔድ ሳይጠበቅባችሁ https://mor-migration.fayda.et  በመጠቀም ማያያዝ የሚቻል መሆኑን የብሔራዊ መታወቂያ አስታውቋል።

እስካሁን በኢትዮጵያ ከ25 ሚሊዮን በላይ ዜጎችን በፋይዳ አገልግሎት መመዝገብ ተችሏል ሲባል ከ91 በላይ ተቋማት ጋርም ትስስር ተፈጥሯል።

@TikvahethMagazine
24👎12👍3😢1
ባለ 15 ወለል የሲኒማ ኮምፕሌክስ በመዲናዋ በዛሬው ዕለት ሥራ መጀመሩን ከንቲባ አዳነች አቤቤ አስታወቁ።

በ24,000 ካ.ሜ ላይ ያረፈው "አዲስ ሲኒማ ኮምፕሌክስ" ባለ አራት ወለል የመኪና ማቆሚያ 592 ህፃናትንና 887 አዋቂዎችን የመያዝ አቅም ያላቸው ሁለት የሲኒማ አዳራሾችን ከሙሉ መገልገያዎች ጋር የያዘ ነው ተብሏል።

ከተማ አስተዳደሩ በቅርብ ጊዜ የህፃናትና ወጣቶች ቴአትርና ሲኒማ ኮምፕሌክስን አስመርቆ እንደነበር ይታወሳል።

@TikvahethMagazine
114👍26👎14🤔14😢3
🤙 ኑሮዎን ፒያሳ ላይ ያድርጉ

➣ ውብ አፓርትመንቶቻችን ለኑሮ ምቹ በሆነችው አዲሲቷ ፒያሳ ላይ እርሰዎን ይጠብቃል

   
     66 ካሬ ባለ 1 መኝታ
                 
➣  40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ  6,072,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 5,313,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ
      
              2 መኝታ 75 ካሬ
  
➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ
6,900,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

100% ለከፈለ 30% ቅናሽ 6,037,500 ብር ጠቅላላ ዋጋ

          3 መኝታ 106 ካሬ

➣ 40% ሲከፍሉ 20% ቅናሽ 9,752,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

➣100% ለከፈለ  30% ቅናሽ 8,533,000 ብር ጠቅላላ ዋጋ

❗️ልብ ይበሉ ከላይ የተፃፉት አነስተኛ ካሬዎች ለ ምሳሌ ሲሆኑ ከፍ ያለ ካሬ ማግኜት ትችላላችሁ

ለበለጠ መረጃ
         👇
☎️
+251986687513

WhatsApp:- +251986687513
Email:-
[email protected]
18👍1
2025/10/22 20:24:15
Back to Top
HTML Embed Code: