Telegram Web Link
#Coffee

ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ሦስት ወራት ዓመት መላክ ካቀደችው ቡና መጠን 25 በመቶ ቢቀንስም በገቢ ደረጃ ግን 23 በመቶ ጭማሪ ማስመውገብ መቻሉን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለሥልጣን አስታውቋል።

° መላክ የታቀደው - 151,969.41 ቶን ቡና

° የተላከው - 113,542 ቶን ቡና


° ለማግኘት የታቀደው ገቢ  - 622.5 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር

° የተገኘው ገቢ - 762.75 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር


ባለፉት ሦስት ወራት የኢትዮጵያ ቡና በብዛት ወዴት ተላከ ?

#ጀርመን

- በመጠን 20,793.14 ቶን (18% ድርሻ )

- በገቢ 138.18 ሚልዮን የአሜሪካን ዶላር (18% ድርሻ)፤

#ሳዉድ_አረቢያ

- በመጠን 16,088.45 ቶን (14% ድርሻ)

- በገቢ 102.18 ሚልዮን የአሜሪካን ዶላር (13% ድርሻ )

#ቤልጅዬም

- በመጠን 13,910.92 ቶን (12% ድርሻ)

- በገቢ 93.45 ሚልዮን የአሜሪካን ዶላር (12% ድርሻ)

@TikvahethMagazine
39🔥3👎2🤔1
#Update : የባንኩ ሴክተር ለውጭ ባንኮች ክፍት እንደሆነ ብሔራዊ ባንክ ካስታወቀ በኋላ እስካሁን ሁለት የኬንያ ባንኮች ዘርፉን ለመቀላቀል በሂደት ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል።

ባንኮቹ ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ በመመሪያው መሠረት ቅርንጫፎችን ወይም ወኪል ቢሮዎችን መክፈት ወይም በሀገር ውስጥ ባሉ ባንኮች የ40 በመቶ አክሲዮን ድረስ ማግኘት ይችላሉ።

ወደ ኢትዮጵያ ገቢያ ሊገቡ እንደሆነ ከተገለጸላቸው መካከል የኬንያው ብሔራዊ ባንክ አንዱ ሲሆን በስም ካልተጠቀሰ አንድ የኢትዮጵያ ባንክ የ40 በመቶ ድርሻ ሊገዛ ይችላል ተብሏል።

ሌላው የኬንያው ኢኪውቲ ባንክ ሲሆን በኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ለመሰማራት በቅርቡ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ጋር ተወያይቶ ነበር።

@TikvahethMagazine
53👍12🤝5🤬4🕊2
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቴሌግራም

ቴሌግራም አዲስ ባወጣው ማዘመኛ ላይ በ Voice chat ጊዜ ወይም በቪዲዮ ጥሪዎች ጊዜ ተሳታፊዎች የጹሑፍ መልዕክት መላክ እንዲችሉ ገልጿል።

@TikvahethMagazine
65👍29🤣3
ሙሉ ኮከብ ሪልሰቴት  በሲኤምሲ የሚገኝ ከ ስኩል ኦፍ ቱሞሮ ዝቅ ብሎ የሚገኝ እጅግ ዘመናዊ ና ጥራታቸውን የጠበቁ አፓርትመንት ቤቶች ይዘንሎት ቀርበናል
👉ግንባታቸው 100% የተጠናቀቁ  ቅንጡ አፓርታማ ቤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ከባለ 1 መኝታ እስከ ባለ 4 መኝታ የተለያዬ የካሬ አማራጭ የያዘ
👉60% የባንክ ብድር አማራጭ የተዘጋጀላቸው
👉ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ እና በግንባታ ላይ ያሉ።
      
     🔸2 ሊፍት
      🔸️የከርሰ ምድር ውሃ
      🔸️backup ጀነኔተር
    🔸️የ ልጆች መጫወቻ እና አረንጓዴ ስፍራ የተሟላለት 3000 ካሬ ላይ ያረፈ ቅንጡ ኮምፓውንድ አፓርትመንት በኢትዮጵያ ብር ለሽያጭ አቅረበናል።

ባለ 1 መኝታ 82 ካሬ
ባለ 2 መኝታ 96,99, እና 105ካሬ
ባለ 3 መኝታ 120,124 እና 127 ካሬ
ባለ 4 መኝታ 181 ካሬ

60%ባንክ ብድር የተመቻቸላቸው ዲጅታል የተናጥል ካርታ የተዘጋጀላቸው

📣በ መሀል CMC መኖሪያ ቤቶን ይግዙ።

ለበለጠ መረጃ
💁‍♂📞 +2519-21-85-72-39
            +2519-48-74-31-71
17🤣2😢1
በሜሪጆይ ኢትዮጵያ በሐዋሳ ከተማ የተገነባው የኩላሊት እጥበት ማዕከል ተመረቀ።

ሜሪጆይ ኢትዮጵያ  የኩላሊት እጥበት ማዕከል ሐዋሳ ቅርንጫፍ ከ29 ሚሊዬን ብር በላይ በፈጀ ወጪ ተገንብቶ ተመርቋል።

የክልሉ መንግስት 10 ሚሊዮን ብር እና አንድ አንቡላንስ መኪና ድጋፍ ሲያደርግ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር በበኩሉ የ5 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጋቸውን ገልጸዋል።

ማዕከሉ 13 የእጥበት ማሽን ያለው ሲሆን፤ በአንድ ጊዜ 12 ህመምተኞችን ያስተናግዳል ሲባል 10ሺህ ዙር የኩላሊት እጥበት ማከናወን እንደሚችልም ተጠቁሟል።

@TikvahethMagazine
72👍10👎1
#TanaForum

በአፍሪካ ፀጥታና ደህንነት ጉዳዮች ላይ ትኩረት ያደረገው 11ኛው ጣና ፎረም በባህር ዳር እና አዲስ አበባ ከተሞች እንደሚካሄድ ተገለጸ።

የፎረሙ የመጀመሪ ምዕራፍ በባህር ዳር ጥቅምት 14  እንደሚካድ በመግለጽ፤ በፎረሙ በአፍሪካ ቀንድን የሚከታተሉ ልዩ መልዕክተኞች እንደሚወያዩ ገልጸዋል።

የፎረሙ ሁለተኛ ምዕራፍ ጥቅምት 15 እና 16 በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ ጠቁመዋል። (EPA)

@TikvahethMagazine
29🤣15👎4👍1🕊1
BYD ከ115,000 በላይ የኤሌክትሪክ መኪናዎች ላይ ማሻሻያ እንደሚያስፈልጋቸው ገለጸ።

የቻይናው ግዙፉ የኤሌትሪክ መኪኖች አምራች ቢ.ዋይ.ዲ በዲዛይንና በባትሪ ተከላ ችግር ምክንያት ከ115,000 በላይ መኪኖችን ለማሻሻያ ወደ ማምረቻ እንዲመለሱ ጥሪ አቅርቧል።

ይህ ችግር የተገኘባቸው ከ2015 እስከ 2017 የተመረቱ ከ44 ሺ በላይ የታንግ እና ከ2021 እስከ 2022 የተመረቱ ከ71ሺ በላይ የዩዋን ፕሮ ሞዴሎች ላይ መሆኑ ተገልጿል።

በዩዋን ፕሮ ሞዴሎች ላይ ያጋጠመው ችግር ባትሪውን ከውኃ እንዲሁም ሌሎች ቆሻሻዎች ለመሸፈን የተገጠመው መከላከያ (Sealing Gasket) በአግባቡ አለመጥበቁ መሆኑ ተገልጿል።

ይህም ውኃ ወይም ሌሎች ነገሮች ወደ ኤሌክትሪካል ሲስተሙ እንዲገቡ እና ተግባሩን ሊረብሹ ይችላሉ።

ተቋሙ በተደጋጋሚ በምርቶቹ ላይ የማሻሻያ ጥሪ ቢያቀርብም ይህኛው ከእስካሁኖቹ በመጠን ከፍ ያለ ነው ተብሏል።

ኩባንያው ፈጠረ ያለውን ችግሮች ከክፍያ ነፃ እንደሚያስተካክል ተናግሯል።

ተጨማሪ ማንበብ ለምትፈልጉ ምንጮች ከላይ ተያይዘዋል።

@TikvahethMagazine
62🤣44👍5🤔5🔥4😢4👎2
ስለ ቴሌግራም ዳይሬክት ሚሴጅ (DM) ያውቃሉ ?

ቴሌግራም በቅርቡ በተለይ የቻናል ተከታታዮች መልዕክታቸውን በቀጥታ ለቻናል አስተዳዳሪዎች የሚልኩበት Direct Message (DM) የተሰኘ አገልግሎት አስተዋውቋል።

የቻናል ተከታዮች መልዕክት በዚሁ በኩል ሲልኩ የላኩት መልዕክት በቀጥታ ለቻናል አስተዳዳሪዎች የሚደርስ ሲሆን ቀጥታ ንግግር በዚያው በኩል ማድረግ ያስችላል።

የቻናል አስተዳዳሪዎችም የሚመጣላቸውን መልዕክት ለማስተዳደር የሚቀላቸው ሲሆን በተለይ ከተከታዮቻቸው ጋር የሚኖር ግንኙነትን ይበልጥ ያጠናክረዋል።

ይህንን አገልግሎት ለመጠቀም በመጀመሪያ የቻናል አስተዳዳሪዎች መፍቀድ የሚጠበቅባቸው ይሆናል። ፈቃድ በተሰጣቸው ቻናሎች ላይ ዳይሬክት ሚሴጅ ለተጠቃሚው በስተግራ በግርጌ በኩል ባለ 💬 ምልክት ማግኘት ይቻላል።

@TikvahethMagazine
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
65👍11🙏5👎1🕊1
#Oromia: የኦሮሚያ  ክልላዊ መንግስት በዛሬው ዕለት በሞጆ ከተማ በተካሄደው መርሐግብር በሴፍቲኔት ድጋፍ ስር ለቆዩ ዜጎች ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የወጣባቸውን 1945 የውኃ ፖምፕ ሞተሮች ማስረከቡን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ገልጿል።

@TikvahethMagazine
69👎33👍19
#ጥንቃቄ: የጥቅምትና ቀጣይ ወራት ነፍሻማና ደረቅ የአየር ንብረት ለእሳት መከሰትና መባባስ አስተዋጾው ከፍተኛ በመሆኑ ህብረተሰብ እሳትና የእሳት ምንጮችን በሚጠቀም ጊዜ ከወትሮው የተለየ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል። (AMN)

@TikvahethMagazine
👍6734🤔2
ሙሉ ኮከብ ሪልሰቴት  በሲኤምሲ የሚገኝ ከ ስኩል ኦፍ ቱሞሮ ዝቅ ብሎ የሚገኝ እጅግ ዘመናዊ ና ጥራታቸውን የጠበቁ አፓርትመንት ቤቶች ይዘንሎት ቀርበናል
👉ግንባታቸው 100% የተጠናቀቁ  ቅንጡ አፓርታማ ቤቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ከባለ 1 መኝታ እስከ ባለ 4 መኝታ የተለያዬ የካሬ አማራጭ የያዘ
👉60% የባንክ ብድር አማራጭ የተዘጋጀላቸው
👉ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቁ እና በግንባታ ላይ ያሉ።
      
     🔸2 ሊፍት
      🔸️የከርሰ ምድር ውሃ
      🔸️backup ጀነኔተር
    🔸️የ ልጆች መጫወቻ እና አረንጓዴ ስፍራ የተሟላለት 3000 ካሬ ላይ ያረፈ ቅንጡ ኮምፓውንድ አፓርትመንት በኢትዮጵያ ብር ለሽያጭ አቅረበናል።

ባለ 1 መኝታ 82 ካሬ
ባለ 2 መኝታ 96,99, እና 105ካሬ
ባለ 3 መኝታ 120,124 እና 127 ካሬ
ባለ 4 መኝታ 181 ካሬ

60%ባንክ ብድር የተመቻቸላቸው ዲጅታል የተናጥል ካርታ የተዘጋጀላቸው

📣በ መሀል CMC መኖሪያ ቤቶን ይግዙ።

ለበለጠ መረጃ
💁‍♂📞 +2519-21-85-72-39
            +2519-48-74-31-71
11
ይሸጣል ብሎ መለጠፍ ድሮ ቀረ

ያገለገለ እቃዎትን ባሉበት ፎቶ በማንሳት ይሽጡ

ልብ ይበሉ ሁላችንም ቤት አንድ የማንፈልገውና የማንጠቀምበት ያገለገለ እቃ አለ በተቃራኒው ደግሞ ያንን እቃ የሚፈልጉ ግን የት እንደሚገኝ የማያውቁ ሰዎች አሉ።

አላማችን እርሶ የማይጠቀሙበትን ያገለገለ እቃ በቀላሉ ካሉበት ሆነው ፖስት በማስደረግ እንዲሸጡ ማስቻል ሲሆን ያገለገለ እቃ መግዛት ሲፈልጉ ደግሞ በቀጥታ ከእቃው ባለቤት በጥሩ ዋጋ እንዲገዙ ማገዝ ነው።

ስለሆነም እርሶም ቤት አገልግሎት ሳይሰጥ ቦታ ይዞ የተቀመጠ ያገለገለ እቃ ካሎት ፎቶ አንስተው ይላኩልን ወይም በሌሎች ሰወች ፖስት የተደረጉ ያገለገሉ እቃዎችን ፎቶ ፣ አድራሻ ፣ ዋጋ እና የእቃውን ባለቤት ስልክ ቁጥር በ ET Creatives በቀላሉ ያገኛሉ

JOIN 👉 https://www.tg-me.com/ET_Creatives_Family

ET Creatives
47
በፓሪስ ከሚገኝ ሙዚየም በእንቁዎች ያጌጡ ቅርሶች መሰረቃቸው ተገለጸ

ትናንት ማለዳ በፓሪስ ሉቨር ሙዚየም በዋጋ የማይተመኑ የተባሉ ጌጣ ጌጦች ተሰረቁ። የፓሪስ ፖሊስ የሌቦቹን ቡድን ለመያዝ አሰሳ እያደረገ መሆኑ ገልጿል።

የፈረንሳይ አገር ውስጥ ሚኒስትር ላውረንት ኑኔዝ እሁድ ዕለት ማለዳ ሙዚየሙ ለጎብኚዎች ክፍት በሆነ በደቂቃ ውስጥ ጭምብል ያጠለቁ ተጠርጣሪዎች ዘረፋውን ለመፈጸም ደቂቃዎች ብቻ እንደፈጀባቸው ተናግረዋል።

የዘራፊዎቹ ቡድን የሙዚየሙ የመጀመሪያ ፎቅ መስኮት ላይ ለመድረስ ከመኪና ላይ የተዘረጋ መሰላል መጠቀማቸው የተገለፀ ሲሆን፣ ጌጣጌጦቹን ለዕይታ ከተቀመጡበት ሰብረው በማውጣት በአነስተኛ ሞተር ሳይክል አምልጠዋል።

በዘራፊዎቹ የተወሰዱት ጌጣጌጦች የፈረንሳይ ንጉሣውያን ቤተሰቦች ይገለገሉባቸው የነበሩ ናቸው። ባለሥልጣናት ዘጠኝ ጌጣጌጦች መወሰዳቸውን ጨምረው አስታውቀዋል።

አራት ሰዎች በዘረፋው ላይ የተሳተፉ ሲሆን ሁለቱ ወደ ሕንጻው ከገቡ በኋላ ጠባቂዎችን ሲያስፈራሯቸው መሰላል የጫነ መኪና ወደ ሕንጻው የመጀመሪያ ፎቅ መስኮት በመጠጋት መሰላሉን መዘርጋቱን ተገልጿል።

እነዚህን የከበሩ ማዕድናትና የተዋቡ ጌጣ ጌጦችን ሙሉ በሙሉ ለመሸጥ መሞከር በቀላሉ ስለሚታወቅ ሊያጋልጣቸው ስለሚችል ወንጀለኞቹ በቀላሉ በታትኖ ለመሸጥ የሚያመቻቸውን ጌጣጌጦች መርጠዋል ነው የተባለው።

@TikvahethMagazine
41🤣21👏12🔥2
በታቦተ ህጉ ላይ የተሳለቁ አምስት ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ።

በደቡብ ምዕራብ ክልል በካፋ ዞን ዋቻ ከተማ አስተዳደር መስከረም መስከረም 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ተከሳሽ አብረሃም ክፍል በሚል መጠሪያ በተከፈተ የቲክቶክ አካውንት በኦርቶዶክስ እምነትና በታቦተ ህጉ ላይ በመሳለቅ ቪዲዮ በመስራት ያጋሩ 5 ተከሳሾች በህግ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተጣራባቸው ነበር።

ጉዳዩን የተመለከተው የዋቻ ከተማ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ጥቅምት 7 ቀን 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት በአምስቱ ተከሳሾች እያንዳንዳቸዉ ላይ  በአንድ ዓመት ፅኑ እስራትእንዲቀጡ ወስኖባቸዋል

መረጃው የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ነው።

@TikvahethMagazine
👍31784🤣44👏21🤬13🤔9🤝6👎4🙏2
2025/10/21 00:48:50
Back to Top
HTML Embed Code: