Telegram Web Link
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በቀን 24/10/2017 ዓ/ም ባካሄዱት ስብሰባ ላይ የተወሰኑ አበይት ጉዳዮች

@tikvahethsport @kidusyoftahe
😁16252👎29👏26🙏8🔥5😢5😱3👍2🤔1
TIKVAH-SPORT
አንሱ ፋቲ በውሰት ሞናኮን ሊቀላቀል ነው ! ስፔናዊው የባርሴሎና የፊት መስመር ተጨዋች አንሱ ፋቲ በረጅም ጊዜ ውሰት ውል የፈረንሳዩን ክለብ ሞናኮ ለመቀላቀል ተስማምቷል። በተጠናቀቀው የውድድር አመት ለባርሴሎና 11 ጨዋታዎች ብቻ ያደረገው አንሱ ፋቲ ነገ በሞናኮ የህክምና ምርመራውን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። ተጨዋቹ ወደ ሞናኮ ከማቅናቱ በፊት ለባርሴሎና የተጨማሪ አንድ አመት ውል ያራዝማል ተብሎ…
አንሱ ፋቲ በውሰት ሞናኮን ተቀላቀለ !

ስፔናዊው የፊት መስመር ተጨዋች አንሱ ፋቲ በረጅም ጊዜ ውሰት ውል የፈረንሳዩን ክለብ ሞናኮ መቀላቀሉ በይፋ ተገልጿል።

በተጨዋቹ የውሰት ውል ውስጥ ባርሴሎና መጥራት ቢፈልግ 11 ሚልዮን ዩሮ መክፈል የሚያስገድድ አንቀጽ ተካቷል።

በተጠናቀቀው የውድድር አመት ለባርሴሎና 11 ጨዋታዎች ያደረገው አንሱ ፋቲ በቅድሚያ በባርሴሎና እስከ 2028 ውሉን አራዝሟል።

ሞናኮ በዝውውር መስኮቱ ፖል ፖግባ እና ኤሪክ ዳየርን በነፃ ዝውውር እንዲሁም አንሱ ፋቲን በውሰት በማስፈረም ቡድናቸውን አጠናክረዋል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
138👍26😁6🔥2
ጆን ዱራን ወደ ፌነርባቼ ለማምራት ተስማማ !

ኮሎምቢያዊው የፊት መስመር አጥቂ ጆን ዱራን የቱርኩን ክለብ ፌነርባቼ ለመቀላቀል ከስምምነት ደርሷል።

ተጨዋቹ ከአል ነስር ወደ ፌነርባቼ በውሰት የሚያደርገውን ዝውውር ለማጠናቀቅ ከኮሎምቢያ ወደ ቱርክ ለመብረር መዘጋጀቱ ተገልጿል።

ጆን ዱራን ባለፈው ክረምት ከአስቶን ቪላ በ 77 ሚልዮን ዩሮ በአምስት አመት ኮንትራት አል ነስርን መቀላቀሉ ይታወሳል።

የ 22ዓመቱ ጆን ዱራን በሳውዲ አረቢያ ሊግ ባደረጋቸው 18 ጨዋታዎች 12 ጎሎችን ማስቆጠር ችሏል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
103🤔38👍17👎10😁5
ሎሬንዞ ኢንሲኜ ከክለቡ ጋር ተለያየ !

ሎሬንዞ ኢንሲኜ እና ፌዴሪኮ ቤርናዴቺ ከአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከሩ ክለብ ቶሮንቶ ጋር ያላቸው ኮንትራት መቋረጡ ተገልጿል።

ሁለቱም ተጨዋቾች ከክለቡ ጋር ያላቸውን ውል በስምምነት በማቋረጥ አሁን ላይ ከኮንትራት ነፃ መሆናቸው ተነግሯል።

የ 34ዓመቱ ኢንሲኜ በ 2025 ለቶሮንቶ 13 ጨዋታዎች ሲያደርግ አንድ ጎል ሲያስቆጥር ሶስት አመቻችቶ አቀብሏል።

ሎሬንዞ ኢንሲኜ በአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከር ከሊዮኔል ሜሲ በመቀጠል ከፍተኛ ተከፋይ እግርኳስ ተጨዋች ነበር።

በጉዳት እና ቅጣት ያለፉት አራት ጨዋታዎች ያመለጡት ቤርናዴቺ በበኩሉ በ 2025 15 ጨዋታዎች ሲያደርግ አራት ጨዋታዎች አድርጎ ሶስት አመቻችቶ አቀብሏል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
50👍23👏7🔥1😁1
TIKVAH-SPORT
አርሰናል ኬፓን ለማስፈረም ተቃርቧል ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የቼልሲውን ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋን ዝውውር ለማጠናቀቅ ከጫፍ መድረሳቸው ተገልጿል። መድፈኞቹ ኬፓ አሪዛባላጋን የቡድኑ ቁጥር ሁለት ግብ ጠባቂ አድርገው ለማስፈረም እየሰሩ መሆኑ ተዘግቦ እንደነበር ይታወሳል። አርሰናል አሁን ላይ የ 30ዓመቱ ኬፓ አሪዛባላጋ በቼልሲ ያለውን ኮንትራት ማፍረሻ 5 ሚልዮን ፓውንድ በመክፈል ለማስፈረም…
አርሰናል በይፋ ግብ ጠባቂ አስፈረመ !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የቼልሲውን ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ ማስፈረማቸውን በይፋ አስታውቀዋል።

መድፈኞቹ ኬፓ አሪዛባላጋን የቡድኑ ቁጥር ሁለት ግብ ጠባቂ አድርገው በሶስት አመት ኮንትራት ማስፈረማቸው ተገልጿል።

አርሰናል የ 30ዓመቱ ኬፓ አሪዛባላጋ በቼልሲ ያለውን ኮንትራት ማፍረሻ 5 ሚልዮን ፓውንድ በመክፈል አስፈርመዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
👍184😁9048👎16👏5🔥4
TIKVAH-SPORT
አርሰናል በይፋ ግብ ጠባቂ አስፈረመ ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የቼልሲውን ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ ማስፈረማቸውን በይፋ አስታውቀዋል። መድፈኞቹ ኬፓ አሪዛባላጋን የቡድኑ ቁጥር ሁለት ግብ ጠባቂ አድርገው በሶስት አመት ኮንትራት ማስፈረማቸው ተገልጿል። አርሰናል የ 30ዓመቱ ኬፓ አሪዛባላጋ በቼልሲ ያለውን ኮንትራት ማፍረሻ 5 ሚልዮን ፓውንድ በመክፈል አስፈርመዋል። @tikvahethsport    …
“ አርሰናል ዋንጫ ለማሸነፍ ተቃርቧል “ ኬፓ አሪዛባላጋ

አርሰናልን የተቀላቀለው ስፔናዊ ግብ ጠባቂ ኬፓ አሪዛባላጋ በክለቡ ለመስራት መጓጓቱን ከፊርማው በኋላ ተናግሯል።

“ እዚህ በመሆኔ በጣም ደስተኛ ነኝ " ያለው ኬፓ አሪዛባላጋ በቀጣይ በክለቡ ለመስራት ጓጉቻለሁ ቡድኑ ለማሸነፍ ያለውን ምኞት ሰምቻለሁ ብሏል።

አክሎም " አርሰናል ዋንጫ ለማሸነፍ ተቃርቧል " ያለው ኬፓ አሪዛባላጋ በጋራ እንደምናሳካው ባለሙሉ ተስፋ ነኝ ሲል ተደምጧል።

ኬፓ አሪዛባላጋ በአርሰናል ቤት የ 13 ቁጥር ማልያ የማለብስ ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
😁558🔥194121👍26👎10👏3
#Wanawsportswear ✔️

መጠበቁ አብቅቷል ኢትዮጵያውያኖችን በአንድ መድረክ የሚያሰባስበው
#ESFNA2025 በይፋ 📍በ ሲያትል FEDERAL WAY MEMORIAL FIELD ስታዲየም ተጀምሯል!!!

ዋናው ስፖርት እንደ ሁልጊዜውም የወንድማማቾችን መንፈስ ለማድመቅ በዝግጅቱ ታድሟል ይህ ደማቅ ዝግጅት ብቻ አይደለም የሀበሻውያን ወንድማማችነት የሚጠናከርበት ባህል እና ታሪክ የሚቀጥልበት ነው።
⭐️ | ዋናው ስፖርት የሲልቨር ደረጃ ስፖንሰር

ለበለጠ መረጃ
8️⃣2️⃣8️⃣9️⃣

🔗 ማህበራዊ ገጾቻችን🔗
Instagram|Facebook |TikTok |X|Youtub
🔥🔥🔥🔥በኢትዮጵያ የተመረተ🔥🔥🔥🔥
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
26😢2🔥1🥰1
ኤደርሰን ከደጋፊዎች ተቃውሞ ቀረበበት !

ብራዚላዊው የማንችስተር ሲቲ ቁጥር አንድ ግብ ጠባቂ ኤደርሰን ከክለቡ ደጋፊዎች ተቃውሞ እየቀረበበት ይገኛል።

ግብ ጠባቂው ትላንት ምሽት በአል ሂላል ጨዋታ ያሳየውን አቋም ተከትሎ ደጋፊዎቹ መልቀቅ አለበት በማለት ተቃውመዋል።

የክለቡ ደጋፊዎች አሁን ላይ በማህበራዊ ሚዲያዎች “#EdersonOut “ የሚል ዘመቻ ከፍተዋል።

ኤደርሰን በቅርቡ በሚቀጥለው የውድድር ዘመን በማንችስተር ሲቲ ቤት እንደሚቆይ ማረጋገጡ አይዘነጋም።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
😁15963👍25👎17🤔1
#ClubWorldCup 🇺🇸

ሪያል ማድሪድ ዛሬ ምሽት ከጁቬንቱስ ጋር በሚያደርገው ጨዋታ ወሳኝ ተጨዋቾቹ ወደ ሜዳ እንደሚመለሱ ተገልጿል።

በጨዋታው በህመም ያለፉት ጨዋታዎች ያመለጡት የቡድኑ ቁልፍ ተጨዋች ኪሊያን ምባፔ ወደ ሜዳ እንደሚመለስ ይጠበቃል።

የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ኪሊያን ምባፔ “ ጥሩ ጤንነት ላይ ነው " ያሉ ሲሆን ወደ አሰላለፍ የሚመለስበት እድል ሰፊ ነው ብለዋል።

ሎስ ብላንኮዎቹ በውድድሩ ወሳኝ ወቅት ኪሊያን ምባፔ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሁለት የኋላ መስመር ተጨዋቾቻቸው ይመለሳሉ።

ለተጨዋቾች ጠንቅ ከሆነው የ " ACL " ጉዳት የተመለሱት ዳኒ ካርቫል እና ኤደር ሚሊታኦ ከጥሎ ማለፉ በኋላ ቡድኑን ማገልገል ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃሉ።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
145🔥15👍14
በሩብ ፍፃሜው ምን ልንመለከት እንችላለን ?

ሪያል ማድሪድ ዛሬ ምሽት ጁቬንቱስን የሚያሸንፍ ከሆነ በውድድሩ ሩብ ፍፃሜ ታሪካዊ ጨዋታ ልንመለከት እንችላለን።

የሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱስ አሸናፊ በሩብ ፍፃሜው የቦርስያ ዶርትመንድ እና ሞንቴሬይን አሸናፊ ይገጥማሉ።

ሪያል ማድሪድ ጁቬንቱስን አሸንፎ ዶርትመንድ የሚያልፍ ከሆን ሁለቱ ወንድማማቾች ጁድ ቤሊንግሀም እና ጆቤ ቤሊንግሀም ለመጀመሪያ ጊዜ በተቃራኒው ይፋለማሉ።

በሌላ በኩል ሪያል ማድሪድ ጁቬንቱስን አሸንፎ ሞንቴሬይ የሚያልፍ ከሆነ ሰርጂዮ ራሞስ የቀድሞ ክለቡን በተቃራኒው ይገጥማል።

ለሪያል ማድሪድ በወሳኝ ቅፅብት ግብ በማስቆጠር የሚታወቀው ራሞስ የቀድሞ ክለቡን ከውድድሩ ለማሰናበት የሚፋለም ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🔥161108👍31😱9👎5😁5
የጨዋታ አሰላለፍ !

4:00 ሪያል ማድሪድ ከ ጁቬንቱስ

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
🔥4625👍1👎1
#ClubWorldCup 🇺🇸

ጁቬንቱስ ማንችስተር ሲቲን ከገጠመው የቡድን ስብስብ የስድስት ተጨዋቾች ቅያሬ አድርገው ወደ ሜዳ ይገባሉ።

አሰልጣኝ ኢጎር ቱዶር በማንችስተር ሲቲ ጨዋታ በተመለከቱት ነገር ደስተኛ አለመሆናቸውን ተናግረው ነበር።

አሰልጣኙ ከጨዋታው በፊት በሰጡት አስተያየት " ሁሉም ሰው ሪያል ማድሪድን ማሸነፍ ይፈልጋል ማለፍ እንፈልጋለን እምነት አለኝ " ብለዋል።

በሪያል ማድሪድ በኩል ኪሊያን ምባፔ የውድድሩ የመጀመሪያ ጨዋታውን ለማድረግ ተጠባባቂ ወንበር ላይ ተቀምጧል።

በሌላ በኩል ሩዲገር በቋሚነት ሲሰለፍ ዳኒ ካርቫል ከዘጠኝ ወራት በኋላ ቡድኑን ለማገልገል ተጠባባቂ ሆኖ ይጀመራል።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
83👍21👎1
" ሁሉም ጨዋታ እንደ ፍፃሜ ነው " አሎንሶ

የሎስ ብላንኮዎቹ አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ጁቬንቱስ በማንችስተር ሲቲ ቢሸነፍም ቀላል ግምት እንደማይሰጡ ገልጸዋል።

“ ሁሉም ጨዋታዎች እንደ ፍፃሜ ነው ስሜታቸው " ያሉት ዣቢ አሎንሶ " ጁቬንቱስ ያው ጁቬንቱስ ነው የአውሮፓ ታሪካዊ ክለብ ነው " ብለዋል።

የጁቬንቱሱ አሰልጣኝ ኢጎር ቱዶር በበኩላቸው “ ብዙ መሮጥ አለብን ምንም ስህተት መስራት የለብንም በራሳችን ማመን አለብን “ ብለዋል።

“ ጨዋታው ከባድ ነው ሪያል ማድሪድ በዚህ ውድድር ሁልጊዜም ጠንካራ ነው ማለፍ ስለምንፈልግ የቻልነውን እናደርጋለን “ ኢጎር ቱዶር

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
92👍18😁1
#ClubWorldCup 🇺🇸

ሪያል ማድሪድ እና ጁቬንቱ ከዚህ በፊት በ 21 አጋጣሚዎች እርስበርስ ጨዋታቸውን አድርገዋል።

ሪያል ማድሪድ በእርስበርስ ግንኙነታቸው የበላይነቱን ቢወስድም ተቀራራቢ ውጤት ነው ያስመዘገቡት።

በእርስበርስ ግንኙነታቸው ሪያል ማድሪድ አስር ጊዜ ሲያሸንፍ ጁቬንቱስ ዘጠኙን አሸንፏል በቀሪዎቹ አቻ ተለያይተዋል።

ሁለቱ ክለቦች እርስበርስ ለመጨረሻ ጊዜ የተገናኙት 2018 በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሩብ ፍፃሜ አቻ በተለያዩበት ጨዋታ ነበር።

ከእርስበርስ ግንኙነታቸው ትልቅ የሚባለው ጨዋታ ሪያል ማድሪድ አሸናፊ የነበረበት የ 2016/17 ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ነው።

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
77👍13😁1
7 '

ሪያል ማድሪድ 0 - 0 ጁቬንቱስ

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
😁2417👍4🥰2👏2
29 '

ሪያል ማድሪድ 0 - 0 ጁቬንቱስ

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
21
TIKVAH-SPORT
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባላት በቀን 24/10/2017 ዓ/ም ባካሄዱት ስብሰባ ላይ የተወሰኑ አበይት ጉዳዮች @tikvahethsport @kidusyoftahe
#Update

ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ።

የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የሌለው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል " ብሏል።

" ብርቅዬ የክለባችን ተጫዋቾች በጨዋታ ሜዳ የገጠሙትን ሁሉንም ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉ የአደባባይ ምስጥር ነዉ " ሲል ገልጿል።

" ይሁን እንጂ ' የሊግ ካምፓኒ ያወጣውን የፋይናንስ ደንብ አላከበራችሁም ' በሚል በክለቡና በተጫዋቾች ላይ ቅጣት ተጥሎባቸዋል ቢባልም ክለቡ  ያነሳዉ ዋንጫ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ በ48 ክለቦች መካከል የተደረገው መሆኑ ዕሙን ነው " ብሏል።

" የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የታገዱ ተጫዋቾችን አሰልፎ ከሆነ በጥሎ ማለፉ ያሸነፋቸው ክለቦች በሙሉ ፎርፌ አግኝተው ጉዳያቸው እንደገና መታየት አለበት እንደ ማለትም ይሆናል " ብሏል።

" እርስ በርስ የሚጣረሱ ሀሳቦችን በማገናኘት ውጤቱን ለመቀማት መሞከር  ተገቢና ህግን የተከተለ ውሳኔ ነው ብለን አናምንም " ሲል ቦርዱ አሳውቋል።

" ፌዴሬሽኑ ዉሳኔውን ከህግጋቱ ጋር በማገናዘብ እንደገና እንዲያጠነዉ ቅሬታችንን እናሰማለን " ብሏል።

" ህዝባችን በፌደሬሽኑ ውሳኔ የተከፋ ቢሆንም የአፊኒ ባህል ያለው ታላቅ ህዝብ ስለሆነ ክስተቶችን በመረጋጋት መርምሮ በተገቢው እንዲያጠነውና  ሂደቱን  በትዕግሥት እንዲጠባበቅ በአክብሮት እየጠይቃል " ሲል ገልጿል።

" የተነፈግነው ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ጉዳዩን እስከ ፊፋ ገላጋይ ፍርድ ቤት ድረስ በይግባኝ ወስደን ለጉዳዩ  ተገቢው እልባት እስኪሰጥ ድረስ የክለቡ ቦርድ ቁርጠኛ መሆኑን እናረጋግጣለን " ሲል አሳውቋል።

@tikvahethiopia
170😁93👍19🤔10👎6
እረፍት

ሪያል ማድሪድ 0 - 0 ጁቬንቱስ

@Tikvahethsport    @kidusyoftahe
25😁20😱3
2025/07/09 22:00:51
Back to Top
HTML Embed Code: