ፒኤስጂ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል !
በክለቦች አለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ፒኤስጂ ከኢንተር ሚያሚ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግብ ጇ ኔቬዝ 2x ፣ አሽራፍ ሀኪሚ እና አቪሌስ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥረዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ፒኤስጂ ሩብ ፍፃሜውን ሲቀላቀል ኢንተር ሚያሚ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
በጨዋታው የፒኤስጂን ሁለት ግቦች ያስቆጠረው ጇ ኔቬዝ የጨዋታው ኮከብ በመባል መመረጥ ችሏል።
ፒኤስጂ በሩብ ፍፃሜው የባየር ሙኒክ እና ፍላሚንጎን አሸናፊ የሚገጥሙ ይሆናል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
በክለቦች አለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ፒኤስጂ ከኢንተር ሚያሚ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 4ለ0 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የፒኤስጂን የማሸነፊያ ግብ ጇ ኔቬዝ 2x ፣ አሽራፍ ሀኪሚ እና አቪሌስ በራሱ መረብ ላይ አስቆጥረዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ፒኤስጂ ሩብ ፍፃሜውን ሲቀላቀል ኢንተር ሚያሚ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
በጨዋታው የፒኤስጂን ሁለት ግቦች ያስቆጠረው ጇ ኔቬዝ የጨዋታው ኮከብ በመባል መመረጥ ችሏል።
ፒኤስጂ በሩብ ፍፃሜው የባየር ሙኒክ እና ፍላሚንጎን አሸናፊ የሚገጥሙ ይሆናል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ቼልሲ ተጨዋች ለማስፈረም እየጣሩ ነው ! የለንደኑ ክለብ ቼልሲ እና ኒውካስል ዩናይትድ የብራይተኑን የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፔድሮ ለማስፈረም ፉክክር ላይ መሆናቸው ተገልጿል። ብራይተን ለ 23ዓመቱ ብራዚላዊ የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፔድሮ እስካሁን የቀረበ ጥያቄ አለመቀበሉ ተነግሯል። ሁለቱ ክለቦች ተጫዋቹን ወደ ስብሰባቸው ለመቀላቀል ከብራይተን ጋር በንግግር ላይ መሆናቸው ተዘግቧል። ተጨዋቹ…
ቼልሲ ተጨዋች ለማስፈረም ተስማማ !
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፔድሮ ለማስፈረም ከብራይተን ጋር ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
የ 23ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፔድሮ በቼልሲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ቢፈለግም ሰማያዊዎቹን ምርጫው ማድረጉ ተነግሯል።
ቼልሲ ለጇ ፔድሮ ዝውውር 50 ሚልዮን ፓውንድ እንደሚያወጡ ሲገለፅ ተጨዋቹ የስድስት አመት ውል እንደሚፈርም ተዘግቧል።
ተጨዋቹ በውድድር አመቱ ለብራይተን 30 ጨዋታዎች ሲያደርግ 10 የፕርሚየር ሊግ ግቦችን አስቆጥሮ ስድስት አመቻች አቀብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፔድሮ ለማስፈረም ከብራይተን ጋር ከስምምነት መድረሳቸው ተገልጿል።
የ 23ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ጇ ፔድሮ በቼልሲ እና ኒውካስል ዩናይትድ ቢፈለግም ሰማያዊዎቹን ምርጫው ማድረጉ ተነግሯል።
ቼልሲ ለጇ ፔድሮ ዝውውር 50 ሚልዮን ፓውንድ እንደሚያወጡ ሲገለፅ ተጨዋቹ የስድስት አመት ውል እንደሚፈርም ተዘግቧል።
ተጨዋቹ በውድድር አመቱ ለብራይተን 30 ጨዋታዎች ሲያደርግ 10 የፕርሚየር ሊግ ግቦችን አስቆጥሮ ስድስት አመቻች አቀብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
“ የአለም ምርጥ ቡድን ነው የገጠምነው “ ማሼራኖ
የኢንተር ሚያሚው አሰልጣኝ ዣቪየር ማሼራኖ ቡድናቸው ከፒኤስጂ ትልቅ ልዩነት ቢኖረውም ለመፎካከር መሞከሩን ገልጸዋል።
“ የገጠምነው የአለም ምርጡን ቡድን ነው “ ያሉት ማሼራኖ “ አውሮፓ ላይ እነሱን ማቆም የቻለ ክለብ የለም እዚህም የአሸናፊነት ግምቱ የእነሱ ነው “ ብለዋል።
አክለውም “ በሁለቱ ክለቦች መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ቢሆንም ለመፎካከር ሞክረናል በተጨዋቾቼ ኮርቻለሁ “ ብለዋል።
ከውድድሩ ምን እንደተማሩ ጥያቄ የቀረበላቸው አሰልጣኝ ማሼራኖ “ ምንም አላውቅም “ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
“ በሁለተኛው አጋማሽ ትንሽ ጥሩ ተጫውተን በምድቡ ሁለት ትልቅ ቡድኖች ጥለናል አሁን ወደፊት እንቀጥላለን “ ማሼራኖ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የኢንተር ሚያሚው አሰልጣኝ ዣቪየር ማሼራኖ ቡድናቸው ከፒኤስጂ ትልቅ ልዩነት ቢኖረውም ለመፎካከር መሞከሩን ገልጸዋል።
“ የገጠምነው የአለም ምርጡን ቡድን ነው “ ያሉት ማሼራኖ “ አውሮፓ ላይ እነሱን ማቆም የቻለ ክለብ የለም እዚህም የአሸናፊነት ግምቱ የእነሱ ነው “ ብለዋል።
አክለውም “ በሁለቱ ክለቦች መካከል ትልቅ ልዩነት አለ ቢሆንም ለመፎካከር ሞክረናል በተጨዋቾቼ ኮርቻለሁ “ ብለዋል።
ከውድድሩ ምን እንደተማሩ ጥያቄ የቀረበላቸው አሰልጣኝ ማሼራኖ “ ምንም አላውቅም “ ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል።
“ በሁለተኛው አጋማሽ ትንሽ ጥሩ ተጫውተን በምድቡ ሁለት ትልቅ ቡድኖች ጥለናል አሁን ወደፊት እንቀጥላለን “ ማሼራኖ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
“ ጥሩ ጨዋታ አድርገናል “ ኤንሪኬ
የፒኤስጂው ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ቡድናቸው ባስመዘገበው ድል ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
“ ጨዋታውን በጥሩ ሁኔታ ነው የጀመርነው " ያሉት ኤንሪኬ ኳስ ተቆጣጥረናል በቂ የግብ አድልም ፈጥረናል ብለዋል።
አክለውም “ በሁለተኛው አጋማሽ ተቀዛቅዘን ነበር ግብ ሊያስቆጥሩ ይችሉም ነበር ነገርግን ደስተኛ ነኝ “ ሲሉ ተደምጠዋል።
“ በሁሉም ተጨዋቾች ደስተኛ ነኝ ይህ እግርኳስ ነው እንደሁልጊዜው ራሳችንን ማሻሻል አለብን “ ኤንሪኬ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የፒኤስጂው ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ቡድናቸው ባስመዘገበው ድል ደስተኛ መሆናቸውን ገልጸዋል።
“ ጨዋታውን በጥሩ ሁኔታ ነው የጀመርነው " ያሉት ኤንሪኬ ኳስ ተቆጣጥረናል በቂ የግብ አድልም ፈጥረናል ብለዋል።
አክለውም “ በሁለተኛው አጋማሽ ተቀዛቅዘን ነበር ግብ ሊያስቆጥሩ ይችሉም ነበር ነገርግን ደስተኛ ነኝ “ ሲሉ ተደምጠዋል።
“ በሁሉም ተጨዋቾች ደስተኛ ነኝ ይህ እግርኳስ ነው እንደሁልጊዜው ራሳችንን ማሻሻል አለብን “ ኤንሪኬ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
" ሜሲ ድንቅ ጨዋታ ነው ያደረገው “
የኢንተር ሚያሚው ዋና አሰልጣኝ ዣቪየር ማሼራኖ ሊዮኔል ሜሲ በምሽቱ ጨዋታ ማድረግ የሚችለውን ምርጥ ነገር ማሳየቱን ገልጸዋል።
“ ሊዮኔል ሜሲ አስደናቂ ጨዋታ ነው ያደረገው “ ያሉት አሰልጣኙ በሁለተኛው አጋማሽ በነበሩን አጋጣሚዎች እሱ ሊያደርገው የሚችለውን ምርጥ ነገር አይተናል ብለዋል።
“ እሱ አሁን 38 ዓመቱ ነው ነገርግን ሰዎች አሁንም እሱን ለማየት ትኬት መቁረጣቸውን ቀጥለዋል ፤ ይህ እሱ ሊሰጠን የሚችለው ትልቅ ዋጋ ያለው ነገር ነው “ ማሼራኖ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የኢንተር ሚያሚው ዋና አሰልጣኝ ዣቪየር ማሼራኖ ሊዮኔል ሜሲ በምሽቱ ጨዋታ ማድረግ የሚችለውን ምርጥ ነገር ማሳየቱን ገልጸዋል።
“ ሊዮኔል ሜሲ አስደናቂ ጨዋታ ነው ያደረገው “ ያሉት አሰልጣኙ በሁለተኛው አጋማሽ በነበሩን አጋጣሚዎች እሱ ሊያደርገው የሚችለውን ምርጥ ነገር አይተናል ብለዋል።
“ እሱ አሁን 38 ዓመቱ ነው ነገርግን ሰዎች አሁንም እሱን ለማየት ትኬት መቁረጣቸውን ቀጥለዋል ፤ ይህ እሱ ሊሰጠን የሚችለው ትልቅ ዋጋ ያለው ነገር ነው “ ማሼራኖ
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ባየር ሙኒክ ሩብ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል !
በክለቦች አለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ባየር ሙኒክ ከፍላሚንጎ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 4ለ2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የባየር ሙኒክን የማሸነፊያ ግቦች ሀሪ ኬን 2x ፣ ጎሬዝካ እና ፑልጋር ማስቆጠር ችለዋል።
የፍላሚንጎን ግቦች ጆርጂንሆ እና ጌርሰን ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ባየር ሙኒክ ሩብ ፍፃሜውን ሲቀላቀል ፍላሚንጎ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
በሩብ ፍፃሜው ባየር ሙኒክ የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂ ከአምስት ቀናት በኋላ የሚገጥሙ ይሆናል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
በክለቦች አለም ዋንጫ ጥሎ ማለፍ ባየር ሙኒክ ከፍላሚንጎ ጋር ያደረጉትን ጨዋታ 4ለ2 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችለዋል።
የባየር ሙኒክን የማሸነፊያ ግቦች ሀሪ ኬን 2x ፣ ጎሬዝካ እና ፑልጋር ማስቆጠር ችለዋል።
የፍላሚንጎን ግቦች ጆርጂንሆ እና ጌርሰን ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል።
ውጤቱን ተከትሎ ባየር ሙኒክ ሩብ ፍፃሜውን ሲቀላቀል ፍላሚንጎ ከውድድሩ ተሰናብተዋል።
በሩብ ፍፃሜው ባየር ሙኒክ የፈረንሳዩን ክለብ ፒኤስጂ ከአምስት ቀናት በኋላ የሚገጥሙ ይሆናል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ክረምትን በምን ሊያሳልፉ አስበዋል?
Can PlayStation 🎮 መፍትሄ ይዞ ብቅ ብሏል🫴
-Sony
PlayStation 2
PlayStation 3
PlayStation 4
PlayStation 5
-Microsoft
Xbox 360
Xbox one
Xbox one s
Xbox Series
ምርቶችን አዘጋጅቶ እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን! እንግዲያውስ እርሶ በተመችዎት ሰዓት ብቅ በማለት ሱቃችን መጎብኘት ይችላሉ።
እቃዎቻችን 6 ወር ዋስትና ስላለው ያለ ሀሳብ ይዝናኑ።
ለልጅም ሆነ ለአዋቂ የሚሆኑ PlayStation Cidi Game ስላሉን ይደውሉልን።
Tv በተለያየ Brand እና Size እኛ ዘንድ ያገኛሉ።
ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል።
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ።
🤝Thanks for choice!
አድራሻ፡፦
ቁጥር 1፦ መገናኛ
ቁጥር 2፦ ቦሌ
ስልክ፦ 0904658609 ወይም 0910529770
0977349492 ይደውሉ
ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://www.tg-me.com/CanPlaystation
👍Update Your Life
Can PlayStation እና Tv Market
Can PlayStation 🎮 መፍትሄ ይዞ ብቅ ብሏል🫴
-Sony
PlayStation 2
PlayStation 3
PlayStation 4
PlayStation 5
-Microsoft
Xbox 360
Xbox one
Xbox one s
Xbox Series
ምርቶችን አዘጋጅቶ እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን! እንግዲያውስ እርሶ በተመችዎት ሰዓት ብቅ በማለት ሱቃችን መጎብኘት ይችላሉ።
እቃዎቻችን 6 ወር ዋስትና ስላለው ያለ ሀሳብ ይዝናኑ።
ለልጅም ሆነ ለአዋቂ የሚሆኑ PlayStation Cidi Game ስላሉን ይደውሉልን።
Tv በተለያየ Brand እና Size እኛ ዘንድ ያገኛሉ።
ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል።
ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ።
🤝Thanks for choice!
አድራሻ፡፦
ቁጥር 1፦ መገናኛ
ቁጥር 2፦ ቦሌ
ስልክ፦ 0904658609 ወይም 0910529770
0977349492 ይደውሉ
ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://www.tg-me.com/CanPlaystation
👍Update Your Life
Can PlayStation እና Tv Market
Forwarded from Betika Ethiopia Official Channel
ተመላሽ እያደረግን ነው! 🔥
ሽንፈት? አይታሰብም!!!!!
በየቀኑ ለአምስት እድለኞች 500 ብር እየሸለምን ነው።
ውርርዱ ባይሳካም አምስት መቶ ብር የግልዎ ይሆናል። ይወራረዱ!
ቢሸነፉም በተመላሽ ያሸንፉ!
ሽንፈት? አይታሰብም!!!!!
በየቀኑ ለአምስት እድለኞች 500 ብር እየሸለምን ነው።
ውርርዱ ባይሳካም አምስት መቶ ብር የግልዎ ይሆናል። ይወራረዱ!
ቢሸነፉም በተመላሽ ያሸንፉ!
ጋቶች ፓኖም በግብ አግቢነቱ ቀጥሏል !
የዋልያዎቹ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም በ ኢራቅ ሊግ ተከታታተይ ጨዋታዎች ግብ ማስቆጠሩን ቀጥሏል።
ሁሉንም ጨዋታዎች ተሰልፎ እየተጫወተ የሚገኘው ጋቶች አራተኛ የሊግ ጎሉን ለኒው ሮዝ ስፖርት ክለብ አስቆጥሯል።
ጋቶች ፓኖም ትላንት ምሽት ቡድኑን መሪ ያደረገች ግብ ሲያስቆጥር የጨዋታው ኮከብ በመባልም ተመርጧል።
ኒውሮዝ ክለብ ትላንት ምሽት ተጋጣሚውን 4ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ጋቶች ከትላንቱ የሊግ ጨዋታ አስቀድሞ በነበረ የሊግ መርሐ ግብር ቡድኑን አሸናፊ ያደረገ ግብ ሲያስቆጥር በሊጉ የሳምንቱ ምርጥ አስራ አንድ ውስጥ መካተት ችሎ ነበር።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የዋልያዎቹ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም በ ኢራቅ ሊግ ተከታታተይ ጨዋታዎች ግብ ማስቆጠሩን ቀጥሏል።
ሁሉንም ጨዋታዎች ተሰልፎ እየተጫወተ የሚገኘው ጋቶች አራተኛ የሊግ ጎሉን ለኒው ሮዝ ስፖርት ክለብ አስቆጥሯል።
ጋቶች ፓኖም ትላንት ምሽት ቡድኑን መሪ ያደረገች ግብ ሲያስቆጥር የጨዋታው ኮከብ በመባልም ተመርጧል።
ኒውሮዝ ክለብ ትላንት ምሽት ተጋጣሚውን 4ለ1 በሆነ ውጤት ማሸነፍ ችሏል።
ጋቶች ከትላንቱ የሊግ ጨዋታ አስቀድሞ በነበረ የሊግ መርሐ ግብር ቡድኑን አሸናፊ ያደረገ ግብ ሲያስቆጥር በሊጉ የሳምንቱ ምርጥ አስራ አንድ ውስጥ መካተት ችሎ ነበር።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
“ ሜሲ ከእሱ ጋር የሚሄዱ አጋሮች አላገኘም “ ኢብራሂሞቪች
ስዊድናዊው የቀድሞ ተጨዋች ዝላታን ኢብራሂሞቪች ሊዮኔል ሜሲ በትላንቱ ጨዋታ “ የማውቀው ሜሲ አልነበረም “ ሲል ገልጿል።
ሜሲ የማውቀው አልነበረም " ያለው ኢብራሂሞቪች ትክክለኛ ቡድን ብትሰጠው እሱ ያለውን ነገር ጨምሮ ጠንካራ ያደርገዋል ብሏል።
“ ኢንተር ሚያሚ ከሜሲ ጋር ከኳስ ውጪ እንዴት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው እንኳን የማይረዱ ተጨዋቾች እና አሰልጣኞች ነው ያለው “ ሲል ዝላታን ተናግሯል።
አክሎም " የተሸነፈው ሜሲ ሳይሆን ኢንተር ሚያሚ ነው እሱ ከሀውልት ጋር ነው የተጫወተው እውነተኛ የቡድን አጋር ቢያገኝ አንበሳውን ታዩት ነበር።"ብሏል።
" ሜሲ እስካሁን የሚጫወተው እግርኳስ ስለሚወድ ነው እሱ አሁንም 99% የአሁን ተጨዋቾች ማድረግ የማይችሉትን ነገር እያደረገ ነው።" ኢብራሂሞቪች
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ስዊድናዊው የቀድሞ ተጨዋች ዝላታን ኢብራሂሞቪች ሊዮኔል ሜሲ በትላንቱ ጨዋታ “ የማውቀው ሜሲ አልነበረም “ ሲል ገልጿል።
ሜሲ የማውቀው አልነበረም " ያለው ኢብራሂሞቪች ትክክለኛ ቡድን ብትሰጠው እሱ ያለውን ነገር ጨምሮ ጠንካራ ያደርገዋል ብሏል።
“ ኢንተር ሚያሚ ከሜሲ ጋር ከኳስ ውጪ እንዴት መንቀሳቀስ እንዳለባቸው እንኳን የማይረዱ ተጨዋቾች እና አሰልጣኞች ነው ያለው “ ሲል ዝላታን ተናግሯል።
አክሎም " የተሸነፈው ሜሲ ሳይሆን ኢንተር ሚያሚ ነው እሱ ከሀውልት ጋር ነው የተጫወተው እውነተኛ የቡድን አጋር ቢያገኝ አንበሳውን ታዩት ነበር።"ብሏል።
" ሜሲ እስካሁን የሚጫወተው እግርኳስ ስለሚወድ ነው እሱ አሁንም 99% የአሁን ተጨዋቾች ማድረግ የማይችሉትን ነገር እያደረገ ነው።" ኢብራሂሞቪች
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የቪክቶር ዮከሬሽ የስፖርቲንግ ሊስበን ቆይታ ?
የስፖርቲንግ ሊስበኑ ፕሬዝዳንት ፍሬዴሪኮ ቫራንዳዝ ቪክቶር ዮከሬሽ በዚህ ክረምት ክለቡን የሚለቅበት እድል ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።
ስፖርቲንግ ሊስበን አሁን ላይ ተጫዋቹን በውሉ ካለው 100 ሚልዮን ዩሮ ውል ማፍረሻ በታች በሆነ የዝውውር ገንዘብ ለመሸጥ ማሰቡን ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።
“ ይሁን እንጂ በ 60 ሚልዮን ዩሮ እና ተጨማሪ 10 ሚልዮን ክለቡን እንደማይለቅ አረጋግጣለሁ “ ሲሉ ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ማንችስተር ዩናይትድ ለማቲውስ ኩንሀ ያወጣውን 73 ሚልዮን ዩሮ እና ለምቤሞ ያቀረበውን ገንዘብ በመጥቀስ አነፃፅረዋል።
አክለውም “ እነዚህ ሁለት ተጨዋቾች የዮከሬሽን ያህል የገበያ ዋጋም ሆነ ብቃት የላቸውም ብዬ አስባለሁ " ሲሉ ተደምጠዋል።
ቪክቶር ዮከሬሽ የፊት መስመር አጥቂ ለማስፈረም በማፈላለግ ላይ በሚገኘው አርሰናል እየተፈለገ ይገኛል።
በሌላ በኩል ተጨዋቹ የሻምፒየንስ ሊግ ቡድን መቀላቀል ቢፈልግም የማንችስተር ዩናይትዱ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ሊያስፈርሙት ይፈልጋሉ።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የስፖርቲንግ ሊስበኑ ፕሬዝዳንት ፍሬዴሪኮ ቫራንዳዝ ቪክቶር ዮከሬሽ በዚህ ክረምት ክለቡን የሚለቅበት እድል ከፍተኛ መሆኑን ገልፀዋል።
ስፖርቲንግ ሊስበን አሁን ላይ ተጫዋቹን በውሉ ካለው 100 ሚልዮን ዩሮ ውል ማፍረሻ በታች በሆነ የዝውውር ገንዘብ ለመሸጥ ማሰቡን ፕሬዝዳንቱ ጠቁመዋል።
“ ይሁን እንጂ በ 60 ሚልዮን ዩሮ እና ተጨማሪ 10 ሚልዮን ክለቡን እንደማይለቅ አረጋግጣለሁ “ ሲሉ ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል።
ፕሬዝዳንቱ ማንችስተር ዩናይትድ ለማቲውስ ኩንሀ ያወጣውን 73 ሚልዮን ዩሮ እና ለምቤሞ ያቀረበውን ገንዘብ በመጥቀስ አነፃፅረዋል።
አክለውም “ እነዚህ ሁለት ተጨዋቾች የዮከሬሽን ያህል የገበያ ዋጋም ሆነ ብቃት የላቸውም ብዬ አስባለሁ " ሲሉ ተደምጠዋል።
ቪክቶር ዮከሬሽ የፊት መስመር አጥቂ ለማስፈረም በማፈላለግ ላይ በሚገኘው አርሰናል እየተፈለገ ይገኛል።
በሌላ በኩል ተጨዋቹ የሻምፒየንስ ሊግ ቡድን መቀላቀል ቢፈልግም የማንችስተር ዩናይትዱ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም ሊያስፈርሙት ይፈልጋሉ።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ኳንሳህ ባየር ሌቨርኩሰንን ሊቀላቀል ነው ! የጀርመን ቡንደስሊጋው ክለብ ባየር ሌቨርኩሰን የሊቨርፑሉን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጃሬል ኳንሳህ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሰዋል። ባየር ሌቨርኩሰን ተጨዋቹን 40 ሚልዮን ዩሮ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከሊቨርፑል ጋር መስማማታቸው ተገልጿል። ሊቨርፑል በተጨዋቹ ኮንትራት ውስጥ መልሶ መግዛት የሚያስችላቸው አንቀጽ ማካተታቸው ተነግሯል። የ…
ኳንሳህ ለጤና ምርመራ ጀርመን ይገኛል !
የሊቨርፑሉን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጃሬል ኳንሳ ባየር ሌቨርኩሰንን ለመቀላቀል ዛሬ የጤና ምርመራውን ያደርጋል።
ተጨዋቹ አሁን ጀርመን መድረሱ ሲገለፅ በቀጣይ የአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀጉን ስብስብ ይቀላቀላል።
ባየር ሌቨርኩሰን ተጨዋቹን 40 ሚልዮን ዩሮ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከሊቨርፑል ጋር ተስማምተዋል።
ሊቨርፑል ከአንድ አመት በኋላ ተጫዋቹን 70 ሚልዮን ዩሮ በሚጠጋ ክፍያ መልሰው መግዛት የሚያስችላቸው አንቀጽ ያካትታሉ።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የሊቨርፑሉን የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጃሬል ኳንሳ ባየር ሌቨርኩሰንን ለመቀላቀል ዛሬ የጤና ምርመራውን ያደርጋል።
ተጨዋቹ አሁን ጀርመን መድረሱ ሲገለፅ በቀጣይ የአሰልጣኝ ኤሪክ ቴንሀጉን ስብስብ ይቀላቀላል።
ባየር ሌቨርኩሰን ተጨዋቹን 40 ሚልዮን ዩሮ በሚደርስ የዝውውር ሒሳብ ለማስፈረም ከሊቨርፑል ጋር ተስማምተዋል።
ሊቨርፑል ከአንድ አመት በኋላ ተጫዋቹን 70 ሚልዮን ዩሮ በሚጠጋ ክፍያ መልሰው መግዛት የሚያስችላቸው አንቀጽ ያካትታሉ።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ቦታፎጎ አሰልጣኙን አሰናበተ !
ከክለቦች አለም ዋንጫ የተሰናበተው የብራዚሉ ክለብ ቦታፎጎ የቡድኑን ዋና አሰልጣኝ ሬናቶ ፓይቫ ማሰናበታቸውን አስታውቀዋል።
አሰልጣኙ ቦታፎጎን እየመሩ በክለቦች አለም ዋንጫው የሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊውን ፒኤስጂ ማሸነፍ ችለዋል።
ቡድኑ በፓልሜራስ ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ መሆኑን ተከትሎ የክለቡ ባለቤት ጆን ቴክስተር አሰልጣኙን አሰናብተዋል።
አሰልጣኙ በተጨማሪም ቦታፎጎ በኮፓ ሊበርታዶሬስ እና ኮፓ ዶ ብራዚል ቡድናቸው አስራ ስድስት ውስጥ እንዲቀላቀል ረድተዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
ከክለቦች አለም ዋንጫ የተሰናበተው የብራዚሉ ክለብ ቦታፎጎ የቡድኑን ዋና አሰልጣኝ ሬናቶ ፓይቫ ማሰናበታቸውን አስታውቀዋል።
አሰልጣኙ ቦታፎጎን እየመሩ በክለቦች አለም ዋንጫው የሻምፒየንስ ሊግ አሸናፊውን ፒኤስጂ ማሸነፍ ችለዋል።
ቡድኑ በፓልሜራስ ተሸንፎ ከውድድሩ ውጪ መሆኑን ተከትሎ የክለቡ ባለቤት ጆን ቴክስተር አሰልጣኙን አሰናብተዋል።
አሰልጣኙ በተጨማሪም ቦታፎጎ በኮፓ ሊበርታዶሬስ እና ኮፓ ዶ ብራዚል ቡድናቸው አስራ ስድስት ውስጥ እንዲቀላቀል ረድተዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
“ ለተጨዋቾቹ አስፈሪ ቡድኖች አሉ ብዬ ነግሬያለሁ " ጋርዲዮላ
የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አል ሂላል በክለቦች አለም ዋንጫ ከአስፈሪ ቡድኖች አንዱ መሆኑን ተናገረዋል።
“ በዚህ ውድድር ትልቅ አቅም ያላቸው አስፈሪ ቡድኖች አሉ ብዬ ለተጨዋቾቹ ነግሬያለሁ " ያሉት ጋርዲዮላ አል ሂላል ከእነሱ ውስጥ አንዱ ነው ብለዋል።
“ አል ሂላል ተጋጣሚውን የመጉዳት አቅም አለው በፊት አድርገውታል አሁንም ያደርጉታል “ ጋርዲዮላ
ስለ ሳውዲ አረቢያ ሊግ እድገት ያነሱት ፔፕ ጋርዲዮላ " ሊጉ በግልጽ በሚታይ መልኩ እያደገ ነው " ብለዋል።
ማንችስተር ሲቲ ዛሬ ሌሊት 10:00 ሰዓት ከአል ሂላል ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የማንችስተር ሲቲው ዋና አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ አል ሂላል በክለቦች አለም ዋንጫ ከአስፈሪ ቡድኖች አንዱ መሆኑን ተናገረዋል።
“ በዚህ ውድድር ትልቅ አቅም ያላቸው አስፈሪ ቡድኖች አሉ ብዬ ለተጨዋቾቹ ነግሬያለሁ " ያሉት ጋርዲዮላ አል ሂላል ከእነሱ ውስጥ አንዱ ነው ብለዋል።
“ አል ሂላል ተጋጣሚውን የመጉዳት አቅም አለው በፊት አድርገውታል አሁንም ያደርጉታል “ ጋርዲዮላ
ስለ ሳውዲ አረቢያ ሊግ እድገት ያነሱት ፔፕ ጋርዲዮላ " ሊጉ በግልጽ በሚታይ መልኩ እያደገ ነው " ብለዋል።
ማንችስተር ሲቲ ዛሬ ሌሊት 10:00 ሰዓት ከአል ሂላል ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
“ የክለቦች አለም ዋንጫ የደከመ ሀሳብ ነው “ ክሎፕ ጀርመናዊው አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ አዲሱን የክለቦች አለም ዋንጫ ውድድር መጀመር ሀሳብ “ የማይረባ ሀሳብ “ ሲሉ ተችተዋል። “ የክለቦች አለም ዋንጫን የመጀመር ሀሳብ በእግርኳስ ከተተገበሩ ጥሩ ያልሆኑ ውሳኔዎች መካከል የከፋው ነው “ ሲሉ የርገን ክሎፕ ተናግረዋል። ውድድሩ በሚቀጥለው የውድድር አመት “ ተጨዋቾች ገጥሟቸው የማያውቀው ጉዳት…
ጋርዲዮላ የየርገን ክሎፕን ትችት ተጋርተዋል !
የማንችስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የርገን ክሎፕ የክለቦች አለም ዋንጫ ላይ የሰነዘሩትን ትችት እንደሚጋሩ ገልጸዋል።
የርገን ክሎፕ የውድድሩን የመጀመር ሀሳብ “ በእግርኳስ ካየናቸው ጥሩ ያልሆኑ ውሳኔዎች መካከል የከፋው ነው “ ሲሉ ገልፀውት ነበር።
አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በበኩላቸው “ በየርገን ክሎፕ ሀሳብ እስማማለሁ አስተያየቱ አላስገረመኝም እረዳዋለሁ “ ብለዋል።
ፔፕ ጋርዲዮላ አክለውም " ውድድሩ ተጨዋቾቻችንን እና ቀጣይ የውድድር አመታችንን ሊጎዳው ይችላል " ብለዋል።
የሰማያዊዎቹ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በተመሳሳይ ከቀናት በፊት ውድድሩን “ ቀልድ ነው “ ሲሉ ገልፀው ሲጀመር አሜሪካን ለእግርኳስ ትክክለኛ ቦታ አይደለችም ብለዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
የማንችስተር ሲቲው አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ የርገን ክሎፕ የክለቦች አለም ዋንጫ ላይ የሰነዘሩትን ትችት እንደሚጋሩ ገልጸዋል።
የርገን ክሎፕ የውድድሩን የመጀመር ሀሳብ “ በእግርኳስ ካየናቸው ጥሩ ያልሆኑ ውሳኔዎች መካከል የከፋው ነው “ ሲሉ ገልፀውት ነበር።
አሰልጣኝ ፔፕ ጋርዲዮላ በበኩላቸው “ በየርገን ክሎፕ ሀሳብ እስማማለሁ አስተያየቱ አላስገረመኝም እረዳዋለሁ “ ብለዋል።
ፔፕ ጋርዲዮላ አክለውም " ውድድሩ ተጨዋቾቻችንን እና ቀጣይ የውድድር አመታችንን ሊጎዳው ይችላል " ብለዋል።
የሰማያዊዎቹ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካ በተመሳሳይ ከቀናት በፊት ውድድሩን “ ቀልድ ነው “ ሲሉ ገልፀው ሲጀመር አሜሪካን ለእግርኳስ ትክክለኛ ቦታ አይደለችም ብለዋል።
@tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ጋቶች ፓኖም በግብ አግቢነቱ ቀጥሏል ! የዋልያዎቹ የመሐል ሜዳ ተጫዋች ጋቶች ፓኖም በ ኢራቅ ሊግ ተከታታተይ ጨዋታዎች ግብ ማስቆጠሩን ቀጥሏል። ሁሉንም ጨዋታዎች ተሰልፎ እየተጫወተ የሚገኘው ጋቶች አራተኛ የሊግ ጎሉን ለኒው ሮዝ ስፖርት ክለብ አስቆጥሯል። ጋቶች ፓኖም ትላንት ምሽት ቡድኑን መሪ ያደረገች ግብ ሲያስቆጥር የጨዋታው ኮከብ በመባልም ተመርጧል። ኒውሮዝ ክለብ ትላንት ምሽት ተጋጣሚውን…
“ ተከታታይ ጎል በማስቆጠሬ ደስ ብሎኛል “ ጋቶች ፓኖም
በኢራቅ ሊግ ለክለቡ ኒው ሮዝ ስፖርት ክለብ በተከታታይ ጨዋታዎች ጎሎችን ያስቆጠረው ጋቶች ፓኖም በቆይታው ደስተኛ መሆኑን ተናግሯል።
ጋቶች ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ለቡድኑ ብቸኛ የማሸነፊያ ግብን ጨምሮ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል።
“ ተከታታይ ጎል በማስቆጠሬ በግሌ ደስ ብሎኛል ፈጣሪንም አመሰግናለሁ “ ሲል ጋቶች ለዝግጅት ክፍላችን ሀሳቡን ሰጥቷል።
በተከታታይ ጎል ማግባት “ የሚጨምረው በራስ መተማመን አለ " የሚለው ጋቶች " እንደ ተጨዋች ጎል ባስቆጠርክ ቁጥር በራስ መተማመንህም ይጨምራል " ብሏል።
ከኢትዮጵያ ወደ ኢራቅ ካመራ ጀምሮ አሰልጣኙ እና የቡድኑ አባላት በእሱ ላይ ትልቅ እምነት እንዳጣሉ እና ቀጥታ በቋሚነት እንዳሰለፉት ጋቶች ተናግሯል።
“ አሰልጣኙ እኔ ላይ እምነት በመጣሉ ደስ ብሎኛል ማሳመን ደግሞ የእኔ ስራ ነበር እድሉን በአግባቡ ተጠቅሜ ከመጣሁ ጀምሮ እስካሁን በቋሚነት እየተጫወትኩ ነው።" ጋቶች ፓኖም
ስለ ቀጣይ ቆይታው ያነሳው ተጨዋቹ “ በቀጣይ እግዜር ነው የሚያውቀው የተሻለ ነገር ለማግኘት ፈጣሪ እንዲያሳካልኝ እመኛለሁ “ ብሏል።
ጋቶች ፓኖም በጥር ወር የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ነበር ኢትዮጵያ መድንን በመልቀቅ ወደ ኢራቅ ሊግ ያቀናው።
“ ኢትዮጵያ መድን ሻምፒዮን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ “ ያለው ጋቶች በትንሹ ለቡድኑ የአቅሜን ሰጥቻለሁ ለክለቡ አዲስ ታሪክ በመፃፋቸው ደስ ብሎኛል ብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
በኢራቅ ሊግ ለክለቡ ኒው ሮዝ ስፖርት ክለብ በተከታታይ ጨዋታዎች ጎሎችን ያስቆጠረው ጋቶች ፓኖም በቆይታው ደስተኛ መሆኑን ተናግሯል።
ጋቶች ባለፉት ሁለት የሊግ ጨዋታዎች ለቡድኑ ብቸኛ የማሸነፊያ ግብን ጨምሮ ሁለት ግቦችን አስቆጥሯል።
“ ተከታታይ ጎል በማስቆጠሬ በግሌ ደስ ብሎኛል ፈጣሪንም አመሰግናለሁ “ ሲል ጋቶች ለዝግጅት ክፍላችን ሀሳቡን ሰጥቷል።
በተከታታይ ጎል ማግባት “ የሚጨምረው በራስ መተማመን አለ " የሚለው ጋቶች " እንደ ተጨዋች ጎል ባስቆጠርክ ቁጥር በራስ መተማመንህም ይጨምራል " ብሏል።
ከኢትዮጵያ ወደ ኢራቅ ካመራ ጀምሮ አሰልጣኙ እና የቡድኑ አባላት በእሱ ላይ ትልቅ እምነት እንዳጣሉ እና ቀጥታ በቋሚነት እንዳሰለፉት ጋቶች ተናግሯል።
“ አሰልጣኙ እኔ ላይ እምነት በመጣሉ ደስ ብሎኛል ማሳመን ደግሞ የእኔ ስራ ነበር እድሉን በአግባቡ ተጠቅሜ ከመጣሁ ጀምሮ እስካሁን በቋሚነት እየተጫወትኩ ነው።" ጋቶች ፓኖም
ስለ ቀጣይ ቆይታው ያነሳው ተጨዋቹ “ በቀጣይ እግዜር ነው የሚያውቀው የተሻለ ነገር ለማግኘት ፈጣሪ እንዲያሳካልኝ እመኛለሁ “ ብሏል።
ጋቶች ፓኖም በጥር ወር የተጨዋቾች ዝውውር መስኮት ነበር ኢትዮጵያ መድንን በመልቀቅ ወደ ኢራቅ ሊግ ያቀናው።
“ ኢትዮጵያ መድን ሻምፒዮን በመሆናችሁ እንኳን ደስ አላችሁ “ ያለው ጋቶች በትንሹ ለቡድኑ የአቅሜን ሰጥቻለሁ ለክለቡ አዲስ ታሪክ በመፃፋቸው ደስ ብሎኛል ብሏል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
ጆን ኢቫንስ በዩናይትድ ሊቀጥል ነው ! ሰሜን አየርላንዳዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጆን ኢቫንስ በማንችስተር ዩናይትድ በአዲስ ሚና እንደሚቀጥል ተገልጿል። የ 37ዓመቱ ጆን ኢቫንስ ውሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር መለያየቱ ተገልጾ ነበር። ተጫዋቹ አሁን ላይ በክለቡ አካዳሚ በሌላ ሚና ታዳጊ ተጨዋቾች ላይ እንዲሰራ ሀላፊነት እንደተሰጠው ተገልጿል። ጆን ኢቫንስ በቀጣይ የታዳጊ…
ጆን ኢቫንስ በሀላፊነት ተሾመ !
ሰሜን አየርላንዳዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጆን ኢቫንስ በማንችስተር ዩናይትድ በሀላፊነት ተሾሟል።
የ 37ዓመቱ ጆን ኢቫንስ በማንችስተር ዩናይትድ ያለው ውል መጠናቀቁን ተከትሎ ጫማውን መስቀሉን በይፋ አስታውቋል።
ተጫዋቹ አሁን ላይ በማንችስተር ዩናይትድ የተጨዋቾችን ውሰት ውል እንዲከታተል በሀላፊነት መሾሙ ይፋ ተደርጓል።
ጆን ኢቫንስ በቀጣይ የውሰት ውሎችን እንደሚቆጣጠር የታዳጊ ተጨዋቾችን እድገት እንዲቆጣጠር እና ድጋፍ እንዲያደርግ ሀላፊነት እንደተሰጠው ተገልጿል።
ከክለቡ ጋር ሶስት የፕርሚየር ሊግ እና አንድ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ያሳካው ጆን ኢቫንስ ያለው የእግርኳስ ልምድ በክለቡ እንዲቀጥል እንዳስቻለው ተነግሯል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
ሰሜን አየርላንዳዊው የተከላካይ ስፍራ ተጨዋች ጆን ኢቫንስ በማንችስተር ዩናይትድ በሀላፊነት ተሾሟል።
የ 37ዓመቱ ጆን ኢቫንስ በማንችስተር ዩናይትድ ያለው ውል መጠናቀቁን ተከትሎ ጫማውን መስቀሉን በይፋ አስታውቋል።
ተጫዋቹ አሁን ላይ በማንችስተር ዩናይትድ የተጨዋቾችን ውሰት ውል እንዲከታተል በሀላፊነት መሾሙ ይፋ ተደርጓል።
ጆን ኢቫንስ በቀጣይ የውሰት ውሎችን እንደሚቆጣጠር የታዳጊ ተጨዋቾችን እድገት እንዲቆጣጠር እና ድጋፍ እንዲያደርግ ሀላፊነት እንደተሰጠው ተገልጿል።
ከክለቡ ጋር ሶስት የፕርሚየር ሊግ እና አንድ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ ያሳካው ጆን ኢቫንስ ያለው የእግርኳስ ልምድ በክለቡ እንዲቀጥል እንዳስቻለው ተነግሯል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
አርሰናል ተጨዋች ለማስፈረም ንግግር ጀመረ !
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የክሪስታል ፓላሱን የፊት መስመር ተጨዋች ኢዜ ለማስፈረም ንግግር መጀመሩ ተገልጿል።
መድፈኞቹ የተጫዋቹን ወኪሎች ማነጋገራቸው ሲገለፅ ተጫዋቹን ለማስፈረም ምን እንደሚያስፈልግ ማወቃቸው ተገልጿል።
ቶተንሀም በበኩሉ የተጨዋቹ ፈላጊ ክለብ መሆኑን የዝውውር ጉዳዮችን የሚከታተለው ጋዜጠኛ ፋብሪዝዮ ሮማኖ ተናግሯል።
ኢዜ ከዚህ በፊት " ህልሜ ለአርሰናል መጫወት ነው “ በሚለው ንግግሩ ይታወቃል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የክሪስታል ፓላሱን የፊት መስመር ተጨዋች ኢዜ ለማስፈረም ንግግር መጀመሩ ተገልጿል።
መድፈኞቹ የተጫዋቹን ወኪሎች ማነጋገራቸው ሲገለፅ ተጫዋቹን ለማስፈረም ምን እንደሚያስፈልግ ማወቃቸው ተገልጿል።
ቶተንሀም በበኩሉ የተጨዋቹ ፈላጊ ክለብ መሆኑን የዝውውር ጉዳዮችን የሚከታተለው ጋዜጠኛ ፋብሪዝዮ ሮማኖ ተናግሯል።
ኢዜ ከዚህ በፊት " ህልሜ ለአርሰናል መጫወት ነው “ በሚለው ንግግሩ ይታወቃል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
TIKVAH-SPORT
አስቶን ቪላ የሴት ቡድኑን ለመሸጥ አስቧል ! የፕርሚየር ሊጉ ክለብ አስቶን ቪላ የገጠመውን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ችግር ለማስተካከል እንዲረዳው የሴት ቡድኑን ለመሸጥ ማሰቡ ተገልጿል። አስቶን ቪላ ባለፉት ሁለት አመታት የገጠማቸው የ 195 ሚልዮን ፓውንድ ኪሳራ ክለቡን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ችግር ውስጥ ከቶታል። ይህንንም ተከትሎ ክለቡ የሴቶች ቡድኑን በመሸጥ ችግሩን ለማስተካከል ገዢ እያፈላለገ…
አስቶን ቪላ የሴት ቡድኑን ለመሸጥ ተስማማ !
የአስቶን ቪላ የገጠመውን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ችግር ለማስተካከል እንዲረዳው የሴት ቡድኑን ለመሸጥ ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል።
አስቶን ቪላ ባለፉት ሁለት አመታት የገጠማቸው የ 195 ሚልዮን ፓውንድ ኪሳራ ክለቡን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ችግር ውስጥ ከቶታል።
ይህንንም ተከትሎ አስቶን ቪላ የሴቶች ቡድኑን መቀመጫውን አሜሪካ ላደረገ ለእህት ተቋም ለመሸጥ መስማማቱ ተነግሯል።
ቼልሲ ከዚህ በፊት የሴት ቡድኑን ለክለቡ እህት ተቋም በ 200 ሚልዮን ፓውንድ ሸጦ ያገኘው ገቢ የፋይናንስ ችግሩን ለመቅረፍ እንደረዳው ይታወሳል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
የአስቶን ቪላ የገጠመውን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ችግር ለማስተካከል እንዲረዳው የሴት ቡድኑን ለመሸጥ ከስምምነት መድረሱ ተገልጿል።
አስቶን ቪላ ባለፉት ሁለት አመታት የገጠማቸው የ 195 ሚልዮን ፓውንድ ኪሳራ ክለቡን የፋይናንሻል ፌር ፕሌይ ችግር ውስጥ ከቶታል።
ይህንንም ተከትሎ አስቶን ቪላ የሴቶች ቡድኑን መቀመጫውን አሜሪካ ላደረገ ለእህት ተቋም ለመሸጥ መስማማቱ ተነግሯል።
ቼልሲ ከዚህ በፊት የሴት ቡድኑን ለክለቡ እህት ተቋም በ 200 ሚልዮን ፓውንድ ሸጦ ያገኘው ገቢ የፋይናንስ ችግሩን ለመቅረፍ እንደረዳው ይታወሳል።
@Tikvahethsport @kidusyoftahe