Telegram Web Link
ሉካ ሞድሪች ሪያል ማድሪድን ተሰናበተ !

ክሮሽያዊው አማካይ ሉካ ሞድሪች ዛሬ ምሽት የሪያል ማድሪድ የመጨረሻ ጨዋታውን አድርጓል።

ከሪያል ማድሪድ ጋር ያለው ውል በዚህ ክረምት ያበቃው ሉካ ሞድሪች ክለቡን እንደሚለቅ መገለፁ አይዘነጋም።

ሉካ ሞድሪች በሪያል ማድሪድ ቤት 28 ዋንጫዎችን ሲያሳካ 600 የሚጠጉ ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ ተጫውቷል።

የ አንድ ጊዜ ባሎን ዶር አሸናፊው ሉካ ሞድሪች በቀጣይ የጣሊያን ሴርያውን ክለብ ኤሲ ሚላን የሚቀላቀል ይሆናል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
226👏48😢29🙏8
“ ማሸነፍ ይገባናል “ ሀኪሚ

የፒኤስጂው የመስመር ተጨዋች አሽራፍ ሀኪሚ ቡድናቸው ሪያል ማድሪድ ላይ የተቀዳጀው ድል እንደሚገባው ገልጿል።

“ ጨዋታውን ስላሸነፍን ጥሩ ስሜት ላይ ነን ፤ ጨዋታው በሙቀቱ ምክንያት አስቸጋሪ ነበር ፣ የገጠምነውም ጠንካራ ቡድን ነው " ሲል ሀኪሚ ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

" በየትኛውም ቦታ እንድጫወት ነፃነት ስለተሰጠኝ ደስተኛ ነኝ እኔ ወደፊት በምወጣ ሰዓት ቦታውን የሚሸፍኑ የቡድን አጋሮቼን አመሰግናለሁ " ሀኪሚ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
313👍48👏16🤔6🤬2🔥1
“ ደጋፊውን ይቅርታ እንጠይቃለን “ ኩርቱዋ

የሎስ ብላንኮዎቹ ግብ ጠባቂ ቲቧ ኩርቱዋ ቡድኑ የክለቡን ደጋፊዎች ይቅርታ እንደሚጠይቅ ከጨዋታው በኋላ ተናግሯል።

“ ደጋፊዎችን ይቅርታ መጠየቅ እንፈልጋለን “ ሲል የተደመጠው ቲቧ ኩርቱዋ ለሽንፈቱ መሰረታዊ ችግር እንደ ቡድን አለማጥቃታችን ነው ብሏል።

“ በጨዋታው መጀመሪያ የሰራናቸው ሁለት ትልልቅ ስህተቶች ተፅዕኖ በማሳደር ዋጋ አስከፍለውናል “ ሲል ኩርቱዋ ተናግሯል።

“ የዣቢ አሎንሶን ሀሳብ መቀበል አልቻልንም በድጋሜ ማየት አለብን ከባድ ሽንፈት ነው ነገርግን እንማርበታለን “ ኩርቱዋ

" አቋማችን ለፒኤስጂ ደረጃ የቀረበ እንኳን አልነበረም " ኩርቱዋ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
136😁77👍35👎9😢7
“ አዲስ ታሪክ መፃፍ እንፈልጋለን “ ኤንሪኬ

የፒኤስጂው ዋና አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ በክለቡ አዲስ ታሪክ መፃፍ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።

“ ለዚህ ክለብ አዲስ ታሪክ መፃፍ እንፈልጋለን “ ሲሉ አሰልጣኙ ካስመዘገቡት ድል በኋላ ተናግረዋል።

እክለውም “ እኛ ኳስ መቆጣጠር የምንወድ ቡድን ነን ለተጋጣሚያችን ያንን ለማድረግ አስቸጋሪ ነው ፤ በትክክለኛው ሰዓት ግብ አስቆጥረናል ድሉ ይገባናል " ብለዋል።

“ የአሰልጣኝ አላማው ለተጨዋቾቹ እና ደጋፊው ደስታ መስጠት ነው ጥሩ የውድድር አመት እያሳለፍን ነው “ ኤንሪኬ

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🔥25193👍28
“ ፒኤስጂ ጊዜ ነበረው እኛ ገና እየጀመርን ነው “ ዣቢ አሎንሶ

የሪያል ማድሪዱ ዋና አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ፒኤስጂ ቡድናቸው ላይ ያደረገው በውድድር አመቱ ሌሎች ክለቦች ላይ ያደረገውን መሆኑን ተናግረዋል።

“ ፒኤስጂ ቡድኑን ለመገንባት ጊዜ ነበረው “ ያሉት ዣቢ አሎንሶ “ እኛን በተመለከተ ገና እየጀመርን ነው “ ሲሉ ተደምጠዋል።

“ ይሄ የመጀመሪያ የውድድር አመቴ መጀመሪያ አይደለም ያለፈው የውድድር አመት መጨረሻ ነው “ ሲሉ ዣቢ አሎንሶ ገልጸዋል።

አክለውም “ ሌሎች ክለቦች በዚህ አመት በፒኤስጂ ጉዳት እንደደረሰባቸው ሁሉ እኛም ዛሬ ደርሶብናል እነሱ አስደናቂ ቡድን ናቸው “ብለዋል።

“ መሻሻል እንችላለን የሚሻሻሉ ብዙ ክፍተቶች አሉ ፤ አሁን አንዳንድ ነገሮች ላይ ግልጽ እውነታ አግኝቻለሁ ያለ ጥርጥር አዲስ ለውጦች ይኖራሉ “ ሲሉ አሎንሶ ተናግረዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
😁301👍170148👎8😢6👏1🤔1🤬1
ኦዶች ዛሬም ከፍ ብለዋል!
ታዲያ ምን ይጠብቃሉ? ለማሸነፍ በተመቻቹ ኦዶች ይወራረዱ!
አሁኑኑ Betika.et ላይ ብቻ!
ቤቲካ የአሸናፊዎች ቤት!
10
ክረምትን በምን ሊያሳልፋ አስበዋል?

Can PlayStation 🎮  መፍትሄ ይዞ ብቅ ብሎሎታል🫴

-Sony
  PlayStation 2
  PlayStation 3
  PlayStation 4
  PlayStation 5

-Microsoft
   Xbox 360
   Xbox one
   Xbox one s
   Xbox Series

ምርቶችን አዘጋጅቶ እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን
እንግዲያውስ እርሶ በተመቻቹ ሰአት ብቅ በማለት ሱቃችን መጎብኘት ይችላሉ

እቃዎቻችን 6 ወር ዋስትና ስላለው የለ ሀሳብ ይዝናኑ

ለልጅም  ለአዋቂ የሚሆኑ PlayStation Cidi Game ስላሉን ይደውሉልን

Tv በተለያየ Brand እና Size እኛ ዘንድ ያገኛሉ

ባሎት ማንኛውም እቃ መቀያየር ይቻላል

ለክፍለ ሀገር እናቀርባለን ይደውሉ

🤝Tanks for choice

ስልክ፦ 0904658609 ወይም     
0977349492  ይደውሉ

ለአዳዲስ መረጃ Telegram channel join ይበሉ ፦
https://www.tg-me.com/CanPlaystation

                       👍Update Your Life

    Can PlayStation እና Tv Market
18
ስልኬ በባርሴሎና ደጋፊዎች ተጨናንቋል “

ስኬታማ አመትን ከፔኤስጂ ጋር እያሳለፉ የሚገኙት አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ ከባርሴሎና ደጋፊዎች የ እንኳን ደስ አለህ መልዕክት እየተላከላቸው መሆኑን ገልፀዋል።

“ ስልኬ በአጭር መልዕክት ተጨናንቋል “ ያሉት ሉዊስ ኤንሪኬ “ ብዙ የባርሴሎና ደጋፊዎች መልዕክት እየላኩልኝ ነው “ ብለዋል።

አሰልጣኝ ሉዊስ ኤንሪኬ የካታላኑን ክለብ ባርሴሎና ለሶስት የውድድር ዓመታት በሀላፊነት መምራታቸው የሚታወስ ነው።

ሉዊስ ኤንሪኬ ፒኤስጂን እየመሩ ሁሉንም ዋንጫዎች ማሸነፉ የቻሉ ብቸኛው ታሪካዊ አሰልጣኝ ለመሆን የፍፃሜውን ጨዋታ ይጠባበቃሉ።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
😁341260👍55👏13🥰7🤔7🔥1
ጆርዳን ሄንደርሰን ከአያክስ ጋር ተለያየ !

እንግሊዛዊው የመሐል ሜዳ ተጨዋች ጆርዳን ሄንደርሰን ከኔዘርላንዱ ክለብ አያክስ ጋር መለያየቱ ይፋ ተደርጓል።

በአያክስ ለተጨማሪ አንድ አመት የመቆየት አማራጭ የነበረው ጆርዳን ሄንደርሰን ከክለቡ ጋር የተለያየ ሲሆን በቀጣይ በነፃ አዲስ ክለብ መቀላቀል ይችላል

ጆርዳን ሄንደርሰን ኮንትራቱን ለማቋረጥ ክለቡን መጠየቁ ተነግሯል።

የ 35ዓመቱ የቀድሞ የሊቨርፑል ተጨዋች ጆርዳን ሄንደርሰን በቀጣይ ሰንደርላንድን ሊቀላቀል እንደሚችል ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
99👍13😁1
ሉዊስ ዲያዝ ወደ ፖርቹጋል አቅንቷል !

የሊቨርፑሉ የፊት መስመር ተጨዋች ሉዊስ ዲያዝ የዲያጎ ጆታን ለቅሶ ለመድረስ ወደ ፖርቹጋል ማቅናቱ ተገልጿል።

የዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ የአንድ ሳምንት መታሰቢያ ሲካሄድ በመታሰቢያ ስነስርዓቱ ሉዊስ ዲያዝ መገኘቱ ተነግሯል።

ሉዋስ ዲያዝ በዲያጎ ጆታ ስርዓተ ቀብር ላይ ሳይገኝ በመቅረቱ ምክንያት ከፍተኛ ትችት ሲቀርብበት ነበር።

በተጨማሪም በመታሰቢያው ላይ ብራዚላዊው ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር በመገኘት ሀዘኑን መግለፁ ተነግሯል።

አሊሰን ቤከር በጉዞ አለመመቻቸት ምክንያት በቀብር ስነስርዓቱ ላይ ሳይገኝ ቀርቶ ነበር።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
🤬187117😢40😁6🥰5👏2🔥1🤩1
“ ጎሉን ለጓደኛዬ ማበርከት እፈልግ ነበር “ ጎንካሎ ራሞስ

የፒኤስጂን አራተኛ ጎል ትላንት ምሽት ያስቆጠረው ጎንካሎ ራሞስ ጎሉን ለብሔራዊ ቡድን አጋሩ ዲያጎ ጆታ መታሰቢያ ማድረጉ ይታወቃል።

ከጨዋታው በኃላ በሰጠው አስተያየት “ለጓደኛዬ ጆታ መታሰቢያ ለማድረግ ጎል ማስቆጠር ፈልጌ ነበር “ ብሏል።

ጎንካሎ ራሞስ ስለ ሁነቱ “ ብዙ መናገር አልፈልግም “ ሲል “ ለዲያጎ ጆታ ክብር ስል ጎል ማስቆጠር እፈልግ ነበር “ በማለት ተናገሯል።

@tikvahethsport @kidusyoftahe
296😢32🙏2
TIKVAH-SPORT
Photo
“ ጆታ በፍጥነት እያሽከረከረ አልነበረም “

የዲያጎ ጆታ እና ወንድሙ መኪና በተቃጠለበት ወቅት የነበረ የከባድ መኪና አሽከርካሪ የአደጋው መንስኤ በፍጥነት ማሽከርከር አለመሆኑን ተናግሯል።

የስፔን ባለስልጣናት የተጨዋቾቹን ህይወት የቀጠፈው የመኪና አደጋ ምክንያት ከተፈቀደ ፍጥነት በላይ ማሽከርከር መሆኑን ተናግረው ነበር።

መኪናው ሲቃጠል የተመለከተው አሽከርካሪ በበኩሉ የባለስልጣናቱን መግለጫ ውድቅ በማድረግ “ ተረጋግተው እየተጓዙ ነበር “ ብሏል።

“ እኔን በርጋታ እያሽከረከሩ ነበር ያለፉኝ “ ያለው አሽከርካሪው በፍጹም በፍጥነት እየተጓዙ አልነበረም በማለት ተናግሯል።

አክሎም " መንገዱን ከሰኞ እስከ አርብ እጓዝበታለሁ በደንብ ነው የማውቀው ፤ መንገዱ ጥሩ ያልሆነ እና ጨለማ ነው “ ሲል ገልጿል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
🔥267132😢82🤬13😁4🤔4👎3🙏1
“ ጋርናቾ ዩናይትድን ከለቀቀ ብቃቱ ይጨምራል “

የናፖሊው ፕሬዝዳንት ዲ ላውረንቲስ አሌሀንድሮ ጋርናቾ ማንችስተር ዩናይትድን ከለቀቀ አቅሙ በእጥፍ ይጨምራል የሚል እምነታቸውን ገልጸዋል።

ቡድናቸው ጋርናቾን ማስፈረም እንደሚፈልግ የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ “ ጋርናቾ ጥሩ ብቃት እና ፍጥነት አለው “ ብለዋል።

አክለውም “ እኛ ልናስፈርመው የፈለግነው አቅሙን ብቻ አይተን ሳይሆን የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋች ስለሆነ ነው “ ብለዋል።

“ ጋርናቾ ዩናይትድን ከለቀቀ አቅሙ በእጥፍ ይጨምራል “ የሚሉት ፕሬዚዳንቱ ማንችስተር ዩናይትድ ውስጥ እኔ መግለጽ የማልችለው ችግር አለ ብለዋል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
😁238👍7341👎5🔥4🥰3🤔2👏1
TIKVAH-SPORT
አርሰናል የኖርጋርድን ዝውውር አጠናቀቀ ! የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የብሬንትፎርዱን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር ማጠናቀቃቸው ተገልጿል። መድፈኞቹ ለ 31ዓመቱ አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር 10 ሚልዮን ፓውንድ እና ተጨማሪ ሁለት ሚልዮን ማውጣታቸው ተነግሯል። ተጨዋቹ የህክምና ምርመራውን በማጠናቀቅ የአርሰናል ተጨዋች መሆኑ መረጋገጡን ለክለቡ ቅርብ የሆኑ ምንጮች…
አርሰናል በይፋ ተጨዋች አስፈረመ !

የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል የብሬንትፎርዱን የመሐል ሜዳ ተጨዋች ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር ማጠናቀቃቸውን ይፋ አድርገዋል።

መድፈኞቹ ለ 31ዓመቱ አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ዝውውር 10 ሚልዮን ፓውንድ እና ተጨማሪ ሁለት ሚልዮን ፓውንድ አውጥተዋል።

ለአርሰናል የሁለት አመት ኮንትራት የፈረመው ኖርጋርድ በቀጣይ በክለቡ የ 16 ቁጥር ማልያ የሚለብስ ይሆናል።

ኖርጋርድ ከማርቲን ዙቢሜንዲ እና ኬፓ አሪዛባላጋ በመቀጠል የአርሰናል የክረምቱ ሶስተኛ ፈራሚ በመሆን ኤምሬትስ ደርሷል።

ዴንማርካዊው አማካይ ክርስቲያን ኖርጋርድ ለብሬንትፎርድ በሁሉም ውድድሮች 192 ጨዋታዎች ሲያደርግ 13 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
199😁53🙏6👎4👍3🔥3
“ በሻምፒየንስ ሊግ እሳተፋለሁ ብዬ አልጠበቅኩም “ ኖርጋርድ

አርሰናልን የተቀላቀለው ክርስቲያን ኖርጋርድ ከአርሰናል ጋር በአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ሊጫወት በመሆኑ መደሰቱን ገልጿል።

" ሻምፒየንስ ሊግ የልጅነት ህልሜ ነበር " ያለው ኖርጋርድ እወን ይሆናል ብዬ ግን ጠብቄ አላውቅም ነበር በጣም ደስተኛ ነኝ ብሏል።

“  በሻምፒየንስ ሊግ ልጫወት መሆኑ ስሜታዊ አርጎኛል በሻምፒየንስ ሊግ መጫወት ወደ እግርኳስ ማብቂያ ጊዜዬ ስቃረብ ለመተው ያሰብኩት ህልም ነበር።" ኖርጋርድ

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
🔥184😁8659👍6
“ ታክቲካል ግንዛቤው ልዩ ነው " አርቴታ

አሰልጣኝ ሚኬል አርቴታ አዲሱ ፈራሚያቸው ክርስቲያን ኖርጋርድ “ ጠንካራ አማካይ ነው “ ሲሉ ከፊርማው በኋላ ተናግረዋል።

ኖርጋርድ በፕርሚየር ሊግ ጥሩ ልምድ እንዳለው ያስረዱት አርቴታ “ እሱ ታክቲካል ግንዛቤው ልዩ ነው " ሲሉ ገልፀውታል።

አክለውም “ ሁለገብ እና ጠንካራ አማካይ በመሆኑ አስፈርመነዋል “ ብለዋል።

" ጠንካራ የአካል ብቃት እና ጨዋታ የመረዳት አቅም አለው ቡድኑ ሚዛኑን እንዲጠብቅ እና አማራጩን እንዲያሳድግ ይረዳል “ አርቴታ

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
👍14756😁52
ኢንተር ሚያሚ ሮድሪጎ ዲ ፓውልን ሊያስፈርሙ ነው !

የአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከሩ ክለብ ኢንተር ሚያሚ ሮድሪጎ ዲ ፓውልን ከአትሌቲኮ ማድሪድ ለማስፈረም በንግግር ላይ መሆናቸው ተገልጿል።

አርጀንቲናዊው አማካይ ሮድሪጎ ዲ ፓውል በአትሌቲኮ ማድሪድ ቤት እስከ ሚቀጥለው ክረምት የሚያቆይ ኮንትራት አለው።

ኢንተር ሚያሚ ተጫዋቹን ለረጅም ጊዜ ሲፈልግ የቆየ ሲሆን አሁን ላይ ከክለቦች አለም ዋንጫ መሰናበቱን ተከትሎ ተጫዋቹን ለማስፈረም መቁረጡ ተነግሯል።

የ 31ዓመቱ ሮድሪጎ ዲ ፓውል በአትሌቲኮ ማድሪድ 187 ጨዋታዎች ሲያደርግ 14 ጎሎችን አስቆጥሮ 26 አመቻችቶ አቀብሏል።

@Tikvahethsport     @kidusyoftahe
47😁15👍7🔥4😱3
ኤዲን ዤኮ ወደ ፊዮሬንቲና አምርቷል !

ቦሲኒያዊው የፊት መስመር ተጨዋች ኤዲን ዤኮ የቱርኩን ክለብ ፊነርባቼ በመልቀቅ ፊዮሬንቲናን ተቀላቅሏል።

በበርካታ ክለቦች መጫወት የቻለው ቦሲኒያዊ የፊት መስመር ተጨዋች ኤዲን ዤኮ አሁን ላይ በነፃ ዝውውር ፊዮሬንቲናን መቀላቀል ችሏል።

የ 39ዓመቱ የፊት መስመር ተጨዋች ኤዲን ዤኮ በዋነኝነት በዎልፍስበርግ ፣ ማንችስተር ሲቲ ፣ ሮማ እና ኢንተር ሚላን በርካታ አመታትን አሳልፏል።

ኤዲን ዤኮ ለክለብ እና ሀገሩ አጠቃላይ 437 ግቦችን ማስቆጠር ችሏል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
39👍11
#Wanawsportswear✔️

Nathan Douala joins Canon Yaoundé
The new face of Cameroon’s football future. From the golden days of African football to the bold vision of tomorrow, Canon’s story is being rewritten and WANAW is proud to stitch every chapter.

🔗Follow us🔗
Instagram|Facebook |TikTok |X|Youtube
⭐️ |Built To Deliver | Moving Forward»»»
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
4
TIKVAH-SPORT
ማድሪድ ሮድሪጎን ለመሸጥ ዝግጁ መሆኑ ተገለጸ ! ሪያል ማድሪድ እና አሰልጣኝ ዣቢ አሎንሶ ብራዚላዊውን ተጨዋች ሮድሪጎን በዚህ ክረምት ለመሸጥ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል። ትክክለኛው የዝውውር ሒሳብ የሚቀርብ ከሆነ ክለቡ በተጨዋቹ መንገድ ላይ ላለመቆም ከስምምነት መደረሱ ተዘግቧል። የ 24ዓመቱ ሮድሪጎ ሪያል ማድሪድ በክለቦች አለም ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ ሲያደርግ ከ 53 ቀናት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ…
የሮድሪጎ የሪያል ማድሪድ ቆይታ ?

ሪያል ማድሪድ ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጨዋች ሮድሪጎ በዚህ ክረምት ለመሸጥ ዝግጁ መሆኑ መገለፁ አይዘነጋም።

ሎስ ብላንኮዎቹ አሁን ላይ የሮድሪጎን የወደፊት ቆይታ ለመወሰን በሚቀጥለው ሳምንት ከተጨዋቹ ጋር ለንግግር እንደሚቀመጡ ተገልጿል።

ሪያል ማድሪድ ሮድሪጎንን ለመልቀቅ ዝግጁ መሆኑ ሲገለፅ ውሳኔው ለተጨዋቹ እንደሚሰጥ ተነግሯል።

ሮድሪጎ በቀጣይ ወደ ሳውዲ አረቢያ ማምራት እንደማይፈልግ እና በአውሮፓ መቆየት እንደሚፈልግ ተዘግቧል።

@tikvahethsport     @kidusyoftahe
49😁3🤬1😢1
2025/07/10 13:49:06
Back to Top
HTML Embed Code: