Telegram Web Link
መሐላ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

ከሚሠራው ሁሉ አይጠየቅም፡፡ እነርሱ ፍጥረቶቹ ግን ይጠየቃሉ፡፡
ቁርኣን (21፥23)

“ቀሠም” قَسَم የሚለው ቃል “ቃሠመ” قَاسَمَ ማለትም “ማለ” “አጸና” “አሳመነ” ከሚል ሥርወ-ቃል የመጣ ሲሆን “መሐላ” “አጽንዖት” “መተማመኛ” ማለት ነው። አማንያን አንድን ነገር አጽንዖትና አንክሮት ለመስጠት አስፈላጊ ከሆነ በአሏህ ስም “ወሏሂ” وَٱللّٰه “ቢሏሂ” بِاللَّهِ በማለት ይምላሉ። ከአላህ ውጪ በሌላ ማንነት ሆነ ምንነት መማል ግን አይቻልም፦

ሠዕድ ኢብኑ ዑበይዳህ እንደተረከው፦
“አንድ ሰው፦ “በከዕባህ እምላለው” ብሎ ሲናገር ኢብኑ ዑመር ሰምቶ እንዲህ አለ፦ “ከአላህ ውጪ በሌላ መማል ከንቱነት ነው፥ የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” እንዲህ ሲሉ ሰምቻለው፦ “ማንም ይሁን ከአላህ ውጪ በሌላ የማለ ከፍሯል ወይም አሻርኳል”።

📚ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 20, ሐዲስ 13

እዚህ ሐዲስ ላይ “መን” مَنْ የሚለው አመልካች ተውላጠ ስም የሚያመለክተው ከአላህ ውጪ የሆነን ምንነት ነው፥ ይህ ከአላህ ውጪ የሆነ ማንም ፍጡር በአላህ ስም ብቻ እንጂ በፍጡራን መማሉ ኩፍርና ሺርክ ነው። ነገር ግን ምን አይነት ኩፍርና ሺርክ? ይህንን ለመረዳት ስለ ኩፍርና ሺርክ በግርድፉና በሌጣው እንይ፦

... ይቀጥላል
====================
ሙሉ ጽሁፉን ጥሪያችን ድረገጽ ላይ ያገኙታል።

https://tiriyachen.org/መሐላ/
👍6
ድነሃልን ?

አላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

የአላህንም የማመን ገመድ ሁላችሁም ያዙ፡፡ አትለያዩም፡፡ ጠበኞችም በነበራችሁ ጊዜ በእናንተ ላይ የዋለውን የአላህን ጸጋ አስታውሱ፡፡ በልቦቻችሁም መካከል አስማማ፡፡ በጸጋውም ወንድማማቾች ኾናችሁ፡፡ በእሳት ጉድጓድ አፋፍም ላይ ነበራችሁ፡፡ ከእርስዋም አዳናችሁ፡፡ እንደዚሁ ትመሩ ዘንድ አላህ ለእናንተ አንቀጾቹን ያብራራል፡፡

وَاعْتَصِمُوا بِحَبْلِ اللَّهِ جَمِيعًا وَلَا تَفَرَّقُوا ۚ وَاذْكُرُوا نِعْمَتَ اللَّهِ عَلَيْكُمْ إِذْ كُنتُمْ أَعْدَاءً فَأَلَّفَ بَيْنَ قُلُوبِكُمْ فَأَصْبَحْتُم بِنِعْمَتِهِ إِخْوَانًا وَكُنتُمْ عَلَىٰ شَفَا حُفْرَةٍ مِّنَ النَّارِ فَأَنقَذَكُم مِّنْهَا ۗ كَذَٰلِكَ يُبَيِّنُ اللَّهُ لَكُمْ آيَاتِهِ لَعَلَّكُمْ تَهْتَدُونَ
📜ቁርኣን (3፥103)

በየመንገዱ፣ በየትምህርት ቤት፣ በሥራ ቦታ ከክርስቲያኖች ወገኖች በተለይ ከፕሮቴስታንት አንጃ፦ “ድነሃልን? የሚል ዋስትና የሌለው ጥያቄ ተደጋግሞ ሲመጣ ይጤናል። ነገር ግን ከምን እንደሚዳን ጠቅሰውና አጣቅሰው በማስረጃ አይሞግቱም፥ አይሟገቱም። ከዚያ ይልቅ ስሜታውያን በመሆን ስሜታዊ ቃላት ይጠቀማሉ። አንዱ አምላክ አመጸኞችን በገሃነም ያጠፋል፥ ከዚህ ጥፋት የሚያድነውም እርሱ ነው፦

... ይቀጥላል
====================
ሙሉ ጽሁፉን ጥሪያችን ድረገጽ ላይ ያገኙታል።


https://tiriyachen.org/ድነሃልን/
👍6
አላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

መልክተኛውም የሰጣችሁን ማንኛውንም ነገር ያዙት፡፡ ከእርሱም የከለከላችሁን ነገር ተከልከሉ፡፡ አላህንም ፍሩ፡፡ አላህ ቅጣተ ብርቱ ነውና፡፡

وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ فَانتَهُوا ۚ وَاتَّقُوا اللَّهَ ۖ إِنَّ اللَّهَ شَدِيدُ الْعِقَابِ
📜ቁርኣን 59፥7

"ዐቂቃህ" عَقِيقه ማለት አዲስ ለተወለደ ሕፃን ልጅ የሚታረድ መስዋዕት የሚደረግ እርድ ነው። የተወደደ እና የተፀና የተከበደ ነቢያዊ"ﷺ" ፈለግ የሆነ እርድ ነው። ዐቂቃህ ማረድ "ማሱና ሙአከዳ" ማለትም በጣም የጠበቀ እና የተወደደ ሱናህ ነው። የዐቂቃህ ዓላማው የተደነገገበት ምክንያት ለአላህ ምስጋና ለማድረስ ነው። ይህም አንድ ሰው ልጅ ስለተወለደለት በመደሰት በ 7ኛው ቀን ደስታውን ለመግለፅ፣ ይህንንም ደስታውን ሰዎች እንዲያውቁት ለማድረግ እና የተወለደውም ልጅ የማን እንደሆነ ለማሣወቅ ነውና። አላህ ደግሞ ልጁን እንደሚጠብቀው፥ እንዲሁ ሷሊህ ልጅ እንዲሆንለት ምክንያትም እንዲሆነው የሚደረግ አርዶ ሰውን የማብላት ሥርዓት ዐቂቃህ ይባላል፦

ሙሉ ጽሁፉን ጥሪያችን ድረገጽ ላይ ያገኙታል።
https://tiriyachen.org/ዐቂቃህ/
👏5
የአላህ ይቅርታ እና ምሕረት በአላህ ስም
እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

“ባሮቼን እኔ ይቅርባዩ መሓሪው እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው”፡፡

نَبِّئْ عِبَادِي أَنِّي أَنَا الْغَفُورُ الرَّحِيمُ
📜ቁርኣን 15፥49

በቁርኣን ከተጠቀሱ ዘጠና ዘጠኝ ከአላህ የተዋቡ ስሞች መካከል “አል-ገፋር” الغَفَّار ወይም “አል-ገፉር” الغَفُور ሲሆን “ይቅርባዩ” ማለት ነው። “መግፊራህ” مَّغْفِرَة ማለት “ይቅርታ” ማለት ሲሆን የእርሱ ባሕርይ ነው። እንዲሁ በቁርኣን ከተጠቀሱ ዘጠና ዘጠኝ ከአላህ የተዋቡ ስሞች መካከል “አር-ረሒም” ٱلرَّحِيمِ ማለት ደግሞ “እጅግ በጣም መሓሪ” ማለት ነው፥ የአር-ረሕማን ባሕርይ ደግሞ “ረሕማህ” رَّحْمَةً ማለትም “ምሕረት ነው። አምላካችን አላህ በመጀመሪያ መደብ እና በሦስተኛ መደብ፦ “እኔ ይቅርባዩ መሓሪው ነኝ” ይላል፦

“ባሮቼን እኔ ይቅርባዩ መሓሪው እኔው ብቻ መኾኔን ንገራቸው”፡፡

نَبِّئْ عِبَادِي أَنِّي أَنَا الْغَفُورُ الرَّحِيمُ
📜ቁርኣን 15፥49

ሙሉውን ለማንበብ ....
https://tiriyachen.org/የአላህ-ይቅርታ-እና-ምሕረት/
👍6
#ጥምቀት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

2፥138 *የአላህን የተፈጥሮ ጥምቀት ያዙ፡፡ በማጥመቅም ከአላህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፤ እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን በሉ*። صِبْغَةَ اللَّـهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّـهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُون

"ጥምቀት" የሚለው የግሪኩ ቃል "ፓፕቲዝማ" βαπτισμός ሲሆን "ፓፕቲዞ" βάπτω ማለትም "ጠለቀ" ወይም "ተነከረ" ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጉሙ "መነከር" ወይም "መጥለቅ" የሚል ፍቺ አለው። ጥምቀት በባይብል የተለያየ ጥምቀት አለ፦ የውኃ ጥምቀት፣ የንስሐን ጥምቀት፣ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፣ የእሳት ጥምቀት፣ የመከራ ጥምቀት ወዘተ.. እነዚህን ነጥብ በነጥብ እስቲ እንያቸው፦

ነጥብ አንድ
"የውኃ ጥምቀት"
የውኃ ጥምቀት ሙሉ ሰውነትን ወደ ውኃ ውስጥ ማስገባትን ወይም ወደ ውኃ ውስጥ መጥለቅን ወይም ውኃው በሰው ላይ መፍሰሱን አሊያም መረጨቱን የሚያሳይ ነው፤ ለምሳሌ እስራኤላውያን በኤርትራ ባህር ሲሻገሩ እና በደመናው ዓምድ ሲያልፉ ከደመናው እና ከባህር ተጠመቁ ተብሏል፦
1ኛ ቆሮንቶስ 10፥1-2 ወንድሞች ሆይ፥ ይህን ታውቁ ዘንድ እወዳለሁ። አባቶቻችን ሁሉ ከደመና በታች ነበሩ ሁሉም በባሕር መካከል ተሻገሩ፤ ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ ዘንድ "በደመናና በባሕር ተጠመቁ""፤

የክርስቶስን ጥላነት"typology" ያሳያል የሚባለው ትምህርት ላይ ልዩ ልዩ የመታጠብ ስርዓት በመሴ ህግ ሰፍሮ ይገኛል፤ ይህ መታጠብ ግሪኩ ጥምቀት ይለዋል፤ "መታጠብ" ተብሎ የተቀመጠው የግሪኩ ቃል "ፓፕቲዞሞስ" βαπτισμοῖς ሲሆን መጠመቅ ማለት ነው፤ ይህም ልዩ ልዩ መታጠብ "ጥምቀቶች" ተብሏል፦
ዕብራውያን 9:10 እነዚህም እስከ መታደስ ዘመን ድረስ የተደረጉ፥ ስለ ምግብና ስለ መጠጥም ""ስለ ልዩ ልዩ መታጠብም"" βαπτισμοῖς የሚሆኑ የሥጋ ሥርዓቶች ብቻ ናቸውና የሚያመልከውን በህሊና ፍጹም ሊያደርጉት አይችሉም።"
ዕብራውያን 6:1-2 ስለዚህ የክርስቶስን ነገር መጀመሪያ የሚናገረውን ቃል ትተን ወደ ፍጻሜ እንሂድ፤ መሠረትን ደግመን አንመሥርት፥ እርሱም ከሞተ ሥራ ንስሐና በእግዚአብሔር እምነት፥ ስለ ""ጥምቀቶች"" እና እጆችንም ስለ መጫን ስለ ሙታንም ትንሣኤ ስለ ዘላለም ፍርድም ትምህርት ነው።

ነጥብ ሁለት
"የንስሐን ጥምቀት"
በተመሳሳይ ይህ የውኃ ጥምቀት መጥምቁ ዮሐንስ ለንስሃ የኃጢአት ስርየት ያጠምቅ ነበር፤ ይህ ጥምቀት የንስሐን ጥምቀት ይባላል፦
ማርቆስ 1:4 ዮሐንስ በምድረ በዳ እያጠመቀ "የንስሐንም ጥምቀት" ለኃጢአት ስርየት እየሰበከ መጣ።

ይህ የንስሐን ጥምቀት በውኃ ሲሆን ለመሲሁ መምጣት መስተንግዶ ነበር፤ ከዚህ ውጪ ኢየሱስ የውኃ ጥምቀት ተጠመቁ ወይም አጥምቁ ብሎ አላስተማረም። ማርቆስ 16፥16 ላይ "ያመነ የተጠመቀም ይድናል" ተብሎ ኢየሱስ እንደተናገረ የሚነገርለት ይህ ጥቅስ ኢየሱስ በሕይወት ዘመኑ የተናገረው ንግግር አይደለም ብለው ምሁራን ያትታሉ፥ ማርቆስ 16.9-20 ያለው የማርቆስ ክፍል አይደለም። በጣም ስመጥርና ገናና የሚባሉ የግሪክ እደ-ክታባት"manuscripts" በሆኑት በሳይናቲከስ፣ በቫቲካነስ፣ በአሌክሳንዲረስ፣ በኤፍሬማይ ላይ የሉም። ይህን ጉዳይ የመጽሐፍ ቅዱስ ማህበር ኦርቶዶስ፣ ካቶሊክና ፕሮተስታንት 1980 ባሳተሙት የአዲስ ትርጉም የግርጌ ማስታወሻ ላይ አስፍረውታል፣ ከዚያም ባሻገር ይህ ቃል የኢየሱስ ንግግር እንዳልሆነ በውጪው ዓለም አገር ያወቀው ጸሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። በተጨማሪ ማቴዎስ 28፥19 ላይ "በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው" ተብሎ ኢየሱስ እንደተናገረ የሚነገርለት ይህ ጥቅስ ኢየሱስ በሕይወት ዘመኑ የተናገረው ንግግር አይደለም ብለው ምሁራን ያትታሉ፣ ማቴዎስ 28፥19 ያለው ክፍል "በስሜ ደቀመዛሙርት አድርጉ" በሚል የተለወጠ ነው ብለው የተለያዩ መድብለ-እውቀቶች"Encyclopedias" ሆነ የባይብል ማብራሪያዎች ያትታሉ። ዋቢ መጽሐፍት ይመልከቱ፦
1. The Interpreters Dictionary of the Bible, 1962, page 351
2. The Anchor Bible Dictionary, Vol. 1, 1992, page 585:
3. The International Standard Bible Encyclopedia, Vol. 4, page 2637,
4. Word Biblical Commentary, Vol 33B, 1975, page 887-888:

ነጥብ ሶስት
"የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት"
የብዙዎች ክርስቲያኖች ጥምቀት ሲባል ሁልጊዜ በውኃ መጠመቅ ብቻ አርገው ያስባሉ፤ ነገር ግን በአንድ ነገር ውስጥ መጥለቅ ወይም መነከር እራሱ ጥምቀት ነው፤ ይህንን በየመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት ማየት ይቻላል፦
ማርቆስ 1:8 እኔ በውኃ አጠመቅኋችሁ እርሱ ግን "በመንፈስ ቅዱስ ያጠምቃችኋል" እያለ ይሰብክ ነበር።"
የሐዋርያት ሥራ 1:5 ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና፥ እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኃላ ""በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ"" አለ።
1ኛ ቆሮንቶስ 12፥13 "በአንድ መንፈስ" አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና።

መቼም በመንፈስ ቅዱስ መጠመቅ ማለት በመንፈስ ቅዱስ ቁጥጥር ስር መሆን እንጂ ሌላ በውኃ እንደመጠመቅ አይደለም።
ነጥብ አራት
"የእሳት ጥምቀት"
የእሳት ጥምቀት የሚለውን ቀደምት አብራሪዎች ሮማውያን እስራኤላውያንን በእሳት ማጥፋታቸው ነው የሚል ፍቺ አላቸው፤ ስንዴውን በጎተራ ከቶ በመንፈስ ቅዱስ ካጠመቀ በኃላ ገለባውን በእሳት ያቃጥላል ስለሚል የእሳት ጥምቀት በዚህ ይተረጉሙታል፦
ሉቃስ 3፥16-17 ዮሐንስ መልሶ። እኔስ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ነገር ግን የጫማውን ጠፍር መፍታት ከማይገባኝ ከእኔ የሚበረታ ይመጣል፤ እርሱ በመንፈስ ቅዱስ እና "በእሳት ያጠምቃችኋል፤ መንሹም በእጁ ነው፥ አውድማውንም ፈጽሞ ያጠራል፥ ስንዴውንም በጎተራው ይከታል፥ ገለባውን ግን ""በማይጠፋ እሳት ያቃጥለዋል"" አላቸው።

ዘመነኞቹ የካሪዝማ ተንታኞቹ ደግሞ አይ የእሳት ጥምቀት በተደጋጋሚ ጊዜ የመንፈስ ቅዱስ ልምምድ ነው፤ ምክንያቱን መንፈስ ቅዱስ የሚቀጣጠል እሳት ተብሏል የሚል ሙግት አላቸው፦
ሐዋርያት ሥራ 18፥25 የዮሐንስንም ጥምቀት ብቻ አውቆ *በመንፈስ ሲቃጠል* ስለ ኢየሱስ ይናገርና በትክክል ያስተምር ነበር።
ሮሜ 12፥11 "በመንፈስ የምትቃጠሉ" ሁኑ፤

አሁንም ልብ አድርጉ በእሳት መጠመቅ ፍካሬአዊ እንደሆነ እንጂ እማሬአዊ እንዳሆነ ቅቡል ነው።

ነጥብ አምስት
"የመከራ ጥምቀት"
ኢየሱስ በውኃ በመጥምቁ ዮሐንስ ከተጠመቀ በኃላ ሌላ የሚጠመቀው ጥምቀት እንደቀረው ይናገራል፦
ሉቃስ 12፥50 ነገር ግን ""የምጠመቃት ጥምቀት"" አለችኝ፥ እስክትፈጸምም ድረስ እንዴት እጨነቃለሁ?

ይህ ጥምቀት በስደት ወይንም በእንግልት ውስጥ ማለፍን ያሳያል፤ ይህንን ጥምቀት ሃዋርያትም ከእርሱ ጋር እንደሚጠመቁ ተናግሯል፦
ማርቆስ 10፥38 ኢየሱስ ግን፦ የምትለምኑትን አታውቁም። እኔ የምጠጣውን ጽዋ ልትጠጡ፥ እኔ ""የምጠመቀውንስ ጥምቀት"" ልትጠመቁ ትችላላችሁን? አላቸው። እነርሱም፦ እንችላለን አሉት። ኢየሱስም፦ እኔ የምጠጣውን ጽዋ ትጠጣላችሁ፥ ""እኔ የምጠመቀውንም ጥምቀት ትጠመቃላችሁ""፤
👍21
አሁንም ልብ አድርጉ በመከራ መጠመቅ ፍካሬአዊ እንደሆነ እንጂ እማሬአዊ እንዳሆነ እሙን ነው።
ከላይ የደረደርኳቸው የሙግት ነጥቦችpremises" በኢስላም ጥምቀት እንዳለ ለማሳየት ነው፥ ሙሥሊም ሲፈጠር የሚጠመቅበት የሃይማኖት ጥምቀት ኢሥላም ነው። ይህ ጥምቀት በ 40 ቀን ወይም በ 80 ቀን አሊያም ለአቅመ ኣደምና ሐዋ ስንደርስ የምንጠመቀው ሳይሆን በተፈጥሮ የምንጠመቀው ጥምቀት ነው፥ አጥማቂውን ቄስ አሊያም ፓስተር ሳይሆን የዓለማቱ ጌታ አላህ ነው፦
2፥138َ Our religion is the Baptism of Allah: And who can baptize better than Allah? And it is He Whom we worship. Yusuf Ali
*የአላህን የተፈጥሮ ጥምቀት ያዙ፡፡ በማጥመቅም ከአላህ ይበልጥ ያማረ ማነው? ማንም የለም፤ እኛም ለእርሱ ብቻ ተገዢዎች ነን በሉ*። صِبْغَةَ اللَّـهِ ۖ وَمَنْ أَحْسَنُ مِنَ اللَّـهِ صِبْغَةً ۖ وَنَحْنُ لَهُ عَابِدُون

አምላካችን አላህ ሰዎችን የፈጠረው እርሱን እንዲያመልኩና እንዲታዘዙ ስለሆነ ኢሥላም አላህ ሰዎችን የፈጠረበት ሃይማኖት ነው፦
30፥30 ወደ እውነት ተዘንባይ ኾነህም ፊትህን ለሃይማኖት ቀጥ አድርግ፡፡ የአላህን ፍጥረት ያችን *”አላህ ሰዎችን በእርስዋ ላይ የፈጠረባትን ሃይማኖት ያዟት”*፡፡ فَأَقِمْ وَجْهَكَ لِلدِّينِ حَنِيفًۭا ۚ فِطْرَتَ ٱللَّهِ ٱلَّتِى فَطَرَ ٱلنَّاسَ عَلَيْهَا ۚ لَا تَبْدِيلَ لِخَلْقِ ٱللَّهِ ۚ ذَٰلِكَ ٱلدِّينُ ٱلْقَيِّمُ وَلَٰكِنَّ أَكْثَرَ ٱلنَّاسِ لَا يَعْلَمُونَ

“ሙስሊም” مُسْلِم የሚለው ቃል “አስለመ” أَسْلَمَ “ታዘዘ”፣ “ተገዛ”፣ ” አመለከ” “ሁሉ ነገሩን ሰጠ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው፥ “ኢስላም” إِسْلَٰم ደግሞ ሃይማኖቱ ነው። አላህ ሰውን ሲፈጥር በተፈጥሮ ጥምቀት ሲሆን የህፃኑ ወላጆቹ ግን አይሁዳዊ ወይም ክርስቲያን አሊያም ዞሮስተርያን ያደርጉታል፦
ኢማም ቡኻርይ መፅሐፍ 23, ሐዲስ 138
ከአቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ” እንደተላለፈው ነቢዩም”ﷺ” እንዲህ አሉ፡- *“ማንም የሚወለድ ሰው “በአል-ፊጥራ በኢሥላም ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም”። ወላጆቹ ግን አይሁዳዊ ያደርጉታል ወይም ክርስቲያን ያደርጉታል አሊያም ዞሮስተርያን ያደርጉታል እንጂ”*። عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ قَالَ قَالَ النَّبِيُّ صلى الله عليه وسلم ‏ “‏ كُلُّ مَوْلُودٍ يُولَدُ عَلَى الْفِطْرَةِ، فَأَبَوَاهُ يُهَوِّدَانِهِ أَوْ يُنَصِّرَانِهِ أَوْ يُمَجِّسَانِهِ

“አል-ፊጥራህ” الْفِطْرَةِ ማለት “ተፈጥሮ” ማለት ነው። አንድ ሰው ከከሐዲያን ቤተሰብ ተወልዶ ወላጆቹ እስከሚያከፍሩት ወይም በአንደበቱ እኔ የዚህ እምነት ተከታይ ነኝ እስከሚል ድረስ በኢሥላም ሥር ነው፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐፍ 46, ሐዲስ 38
አቢ ሙዓዊያህ እንደተረከው፦ ነቢዩም”ﷺ” አሉ፦ *”ማንም የሚወለድ ሰው በአል-ፊጥራ በኢሥላም ላይ ሆኖ እንጂ አይወለድም፥ በአንደበቱ እስከሚል ድረስ”*። لَيْسَ مِنْ مَوْلُودٍ يُولَدُ إِلاَّ عَلَى هَذِهِ الْفِطْرَةِ حَتَّى يُعَبِّرَ عَنْهُ لِسَانُهُ

አላህ ሰዎችን በቀጥተኛው መንገድ በኢሥላም ላይ ፈጥሮ ሳለ ሸያጢን ግን ከዚህ ዲን በሺርክ ምክንያት ሰዎችን ያርቃሉ፦
ኢማም ሙሥሊም መጽሐግ 53, ሐዲስ 76
ዒያድ ኢብኑ ሒማር እንደተረከው፦ የአላህ መልእክተኛም”ﷺ” ኹጥባህ በሚደረግበት ቀን እንዲህ አሉ፦ *”ለእናንተ ያስተማርኩት ጌታዬ ያዘዘኝ፥ እናንተ የማታውቁትን እርሱ ዛሬ ያሳወቀኝን። አላህም አለ፦ “እኔ የሰጠኃቸውንና ሕጋዊ የሆነላቸው ያ ሁሉ ንብረት ነው። እኔ ሁሉንም ባሮቼን በቀጥተኛው መንገድ ላይ ፈጠርኳቸው፥ ሸያጢን መጥተው ከዲናቸው አራቋቸው”*። عَنْ عِيَاضِ بْنِ حِمَارٍ الْمُجَاشِعِيِّ، أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ذَاتَ يَوْمٍ فِي خُطْبَتِهِ ‏”‏ أَلاَ إِنَّ رَبِّي أَمَرَنِي أَنْ أُعَلِّمَكُمْ مَا جَهِلْتُمْ مِمَّا عَلَّمَنِي يَوْمِي هَذَا كُلُّ مَالٍ نَحَلْتُهُ عَبْدًا حَلاَلٌ وَإِنِّي خَلَقْتُ عِبَادِي حُنَفَاءَ كُلَّهُمْ وَإِنَّهُمْ أَتَتْهُمُ الشَّيَاطِينُ فَاجْتَالَتْهُمْ عَنْ دِينِهِم

ስንቋጨው ይህንን የተፈጥሮ ጥምቀት ልክ እንደ የመንፈስ ቅዱስ ጥምቀት፣ የእሳት ጥምቀት፣ የመከራ ጥምቀት በፍካሬአዊ እንረዳዋለን እንጂ ልክ እንደ የውኃ ጥምቀት በእማሬአዊ አንረዳውም። አላህ በተፈጥሮ ጥምቀት ፀንተው ከሚሞቱ ሙሥሊም ባሮቹ ያድርገን! አሚን።

በኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen
https://www.facebook.com/tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
👍3👏1😢1
ውይይት

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

16:125 ወደ ጌታህ መንገድ *በብልሃትና በመልካም ግሣጼ በለዘብታ ቃል ጥራ”፤ በዚያችም እርሷ መልካም በሆነችው “ዘዴ ተከራከራቸው”*፤ ٱدْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِٱلْحِكْمَةِ وَٱلْمَوْعِظَةِ ٱلْحَسَنَةِ ۖ وَجَٰدِلْهُم بِٱلَّتِى هِىَ أَحْسَنُ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ ۖ وَهُوَ أَعْلَمُ بِٱلْمُهْتَدِينَ

"ውይይት" በተቃናቃኝ እና በአቀንቃኝ አሊያም በአውንታዊ እና በአሉታዊ አመለካከት ባላቸው ሰዎች መካከል የሚደረግ ሙግት ብቻ ሳይሆን ችግር ሲመጣ የመጣው ችግር ለማንበብ፣ ለመረዳት፣ ለመፍታት አይነተኛ ቁልፍ ነው፤ ማንኛውም ውይይት አላህ ይሰማዋል፣ ያውቀዋል፣ የቂያማ ቀን በቀኝና በግራ ያሉት መላእክትም ውይይታችንን ጽፈውት ያስጠይቀናል፦
9፥78 አላህ ምስጢራቸውን እና *ውይይታቸውን የሚያውቅ መኾኑን* አላህም ሩቆችን ሁሉ በጣም ዐዋቂ መኾኑን አያውቁምን? أَلَمْ يَعْلَمُوٓا۟ أَنَّ ٱللَّهَ يَعْلَمُ سِرَّهُمْ وَنَجْوَىٰهُمْ وَأَنَّ ٱللَّهَ عَلَّٰمُ ٱلْغُيُوبِ
43፥80 ወይም እኛ ምስጢራቸውን እና *ውይይታቸውን የማንሰማ መኾናችንን ያስባሉን? አይደለም፤ መልክተኞቻችንም እነርሱ ዘንድ ይጽፋሉ*፡፡ أَمْ يَحْسَبُونَ أَنَّا لَا نَسْمَعُ سِرَّهُمْ وَنَجْوَىٰهُم ۚ بَلَىٰ وَرُسُلُنَا لَدَيْهِمْ يَكْتُبُونَ

ስለዚህ ውይይት ለአላህ ውዴታ ተብሎ የሚቀርብ የማስተማሪያ ጥበብ እንጂ የሌላውን ሰው ሃሳብና ስሜት ለማብጠልጠል፣ ለማጠልሸት፣ ለማበሻቀጥ፣ ለማነወር፣ ተብሎ የሚደረግ ንትርክ ወይም እሰጣገባ አይደለም። ለውይይት ምህዳር የሚሆኑ ቅድመ-ሁኔታ እስቲ ነጥብ በነጥብ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"ሥነ-እውነት"
የሥነ-እውነት ጥናት"metaphysics" ምሁራን እንደሚያትቱት እውነት አንድ ሲሆን ሁለት ገፅታዎች አሉት፤ አንዱ "ውሳጣዊ እውነታ"subjective truth" ሲሆን ለምሳሌ እኔ አሳ መብላት እወዳለው ብል፤ ሌላ ሰው አልወድም ብንል ሁለታችንም ትክክል ነን፤ ይህ "ውሳጣዊ እውነታ" ይባላል፤ ሁለተኛው ደግሞ "ውጫዊ እውነታ"objective truth" ሲሆን ለምሳሌ ቢጫ ቀለም በየትኛውም ቋንቋ ስሙ ይቀያየር እንጂ ቢጫ ቀይ፣ አረንጓዴ፣ ነጭ አይደለም፤ ይህ "ውጫዊ እውነታ" ይባላል፤ አንድ ሰው ይህንን እውነታ ሲቃረን ዕውቀት ጎድሎት በመሃይምነት እንዳለ ያሳብቅበታል። አምላካችን አላህ ከሰዎች ጋር ባለን መስተጋብር፦ "ትክክለኛውንም ንግግር” ተናገሩ" "ሐሰትንም ቃል ራቁ" ይለናል፦
33:70 እላንተ ያመናችሁ ሆይ አላህን ፍሩ፤ *ትክክለኛውንም ንግግር” ተናገሩ*። يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَقُولُوا۟ قَوْلًۭا سَدِيدًۭا
22፥30 ከጣዖታትም ርክሰት ተጠንቀቁ፡፡ *ሐሰትንም ቃል ራቁ*፡፡ فَٱجْتَنِبُوا۟ ٱلرِّجْسَ مِنَ ٱلْأَوْثَٰنِ وَٱجْتَنِبُوا۟ قَوْلَ ٱلزُّورِ

እውነትን ለመግለጥ ሃሰትን ለማጋለጥ እውነቱ ምንድን ነው? ሃሰቱ ምንድን ነው? ብሎ መሞገት እንጂ እውነተኛው ማን ነው? ሃሰተኛው ማነው? ካልክ ሰውዬው ወደ ግትረኛነት ወይም ወደ መበሻሸቅ ይሄዳል፤ ስለዚህ ውይይት ለማድረግ ሃቅ መያዝ አይነተኛ ሚና ነው፤ አንድ ሰው እውነተኛ ለመሆን ማስረጃ ማቅረብ አለበት፤ ሁሌም ማስረጃ ከያዙ እውነተኞች ጋር መሆን አለብን፦
2፥111 *እውነተኞች እንደኾናችሁ ማስረጃችሁን አምጡ* በላቸው፡፡ قُلْ هَاتُوا۟ بُرْهَٰنَكُمْ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ
9፥119 እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ *ከእውነተኞቹም ጋር ኹኑ*፡፡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ ٱتَّقُوا۟ ٱللَّهَ وَكُونُوا۟ مَعَ ٱلصَّٰدِقِينَ

የተሟላ ማስረጃ ማለት ደግሞ ከአላህ የሚመጣው የአላህ ንግግር ነው፦
6፥149 *የተሟላው ማስረጃ የአላህ ነው*፡፡ በሻም ኖሮ ሁላችሁንም ባቀናችሁ ነበር» *በላቸው*፡፡ قُلْ فَلِلَّهِ ٱلْحُجَّةُ ٱلْبَٰلِغَةُ ۖ فَلَوْ شَآءَ لَهَدَىٰكُمْ أَجْمَعِينَ
45፥6 *እነዚህ በአንተ ላይ በእውነት የምናነባቸው ሲኾኑ የአላህ ማስረጃዎች ናቸው፡፡ ከአላህና ከማስረጃዎቹም ወዲያ በየትኛው ንግግር ያምናሉ*? تِلْكَ ءَايَٰتُ ٱللَّهِ نَتْلُوهَا عَلَيْكَ بِٱلْحَقِّ ۖ فَبِأَىِّ حَدِيثٍۭ بَعْدَ ٱللَّهِ وَءَايَٰتِهِۦ يُؤْمِنُونَ

ነጥብ ሁለት
"ሥነ-ዕውቀት"
"የሥነ-ዕውቀት ጥናት"epistemology" ምሁራን ዕውቀት በሁለት ይከፍሉታል፤ አንዱ "ውሳጣዊ ዕውቀት"Rational knowledge" ሲሆን ለምሳሌ ከውስጥ የሚመጣ እሳቤ፣ ፈጠራ፣ መፍትሔ ወዘተ "ውሳጣዊ እውነታ" ይባላል፤ ሁለተኛው ደግሞ "ውጫዊ ዕውቀት"Irational knowledge" ሲሆን ለምሳሌ ልምድ፣ ተሞርኮ፣ ሰርቶ ማሳያ ወዘተ "ውጫዊ ዕውቀት" ይባላል፤ ዕውቀት ለብዙ ነገር ማስረጃ ነው፤ እውነተኛ ሰው በዕውቀት ይናገራል፤ ያለ ዕውቀት አንድን እምነት መከተል ያስጠይቃል፦
6፥143 *እውነተኞች እንደሆናችሁ በዕውቀት ንገሩኝ* በላቸው፡፡ نَبِّـُٔونِى بِعِلْمٍ إِن كُنتُمْ صَٰدِقِينَ
17፥36 *ለአንተም በእርሱ ዕውቀት የሌለህን ነገር አትከተል*፡፡ መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ ተጠያቂ ነውና፡፡ وَلَا تَقْفُ مَا لَيْسَ لَكَ بِهِۦ عِلْمٌ ۚ إِنَّ ٱلسَّمْعَ وَٱلْبَصَرَ وَٱلْفُؤَادَ كُلُّ أُو۟لَٰٓئِكَ كَانَ عَنْهُ مَسْـُٔولًۭا

አንድ ነገረኛ ወሬን ቢያመጣልን በስሕተት ላይ ሆነን ሕዝቦችን እንዳንጎዳ እና በሠራነው ነገር ላይ ተጸጻቾች እንዳንሆን በዕውቀት በተደገፈ ማስረጃ ማረጋገጥ አለብን፦
49:6 እላንተ ያመናችሁ ሆይ ነገረኛ *ወሬን ቢያመጣላችሁ” በስሕተት ላይ ሆናችሁ “ሕዝቦችን እንዳትጎዱ” እና በሠራችሁት ነገር ላይ “ተጸጻቾች” እንዳትሆኑ ”አረጋግጡ”*። يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِن جَآءَكُمْ فَاسِقٌۢ بِنَبَإٍۢ فَتَبَيَّنُوٓا۟ أَن تُصِيبُوا۟ قَوْمًۢا بِجَهَٰلَةٍۢ فَتُصْبِحُوا۟ عَلَىٰ مَا فَعَلْتُمْ نَٰدِمِينَ

ዕውቀት ከሰው ልጅ አዕምሮ ሲመጣ "ዐቅል" عقل ሲባል ወሕይ ሆኖ ወደ ነብያት ሲመጣ ደግሞ "ነቅል" نفل ይባላል፤ ለምሳሌ ቁርአን ከዕውቀት ጋርም የተዘረዘረ መጽሐፍ ነው፤ ነብያችን"ﷺ" የማያውቁት እና ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቃቸው አላህ ነው፦
👍1👏1
7፥52 *ከዕውቀት ጋርም የዘረዘርነው የኾነን መጽሐፍ ለሚያምኑ ሕዝቦች መምሪያና እዝነት ሲኾን በእርግጥ አመጣንላቸው*፡፡ وَلَقَدْ جِئْنَٰهُم بِكِتَٰبٍۢ فَصَّلْنَٰهُ عَلَىٰ عِلْمٍ هُدًۭى وَرَحْمَةًۭ لِّقَوْمٍۢ يُؤْمِنُونَ
4፥114 *አላህም በአንተ ላይ መጽሐፍንና ጥበብን አወረደ፤ የማታውቀውንም ሁሉ ዐሳወቀህ*፡፡ የአላህም ችሮታ በአንተ ላይ ታላቅ ነው፡፡ وَأَنزَلَ ٱللَّهُ عَلَيْكَ ٱلْكِتَٰبَ وَٱلْحِكْمَةَ وَعَلَّمَكَ مَا لَمْ تَكُن تَعْلَمُ ۚ وَكَانَ فَضْلُ ٱللَّهِ عَلَيْكَ عَظِيمًۭا
55፥1-2 *አል-ረሕማን ቁርኣንን አሳወቀ*፡፡ ٱلرَّحْمَٰنُ عَلَّمَ ٱلْقُرْءَانَ
96፥5 *ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን*፡፡ عَلَّمَ ٱلْإِنسَٰنَ مَا لَمْ يَعْلَمْ

ነጥብ ሶስት
"ሥነ-አመክንዮ"
"የሥነ-አመክንዮ"Logic" ምሁራን "ሙግት"argument" በሁለት ይከፍሉታል፤ አንዱ "ስሙር ሙግት"valid argument" ሲሆን ይህ ሙግት በእማኝነትና በአስረጂነት ጠቅሶና አጣቅሶ መሟገት ነው፤ በትክክለኛው የአስተላለፍ ስልትና አወቃቀር ስለተዋቀረ የራሱ የሆነ መንደርደሪ፣ የሙግት ነጥብ"premise"፣ መደምደሚያ ያለው ነው፤ ዕውቀት ላይ የተመሰረተ ማስረጃ በአጽንኦትና በአንክሮት ለማዳመጥ ጥልና ጥንፍፍ ያለ መረዳት ነው፤ ይህን ሙግት አምላካችን አላህ መልካም ክርክር ይለዋል፤ ይህ ዘዴ ርቱዕ አካሄድ"optimistic approach" ነው፦
16:125 ወደ ጌታህ መንገድ *በብልሃትና በመልካም ግሣጼ በለዘብታ ቃል ጥራ”፤ በዚያችም እርሷ መልካም በሆነችው “ዘዴ ተከራከራቸው”*፤ ٱدْعُ إِلَىٰ سَبِيلِ رَبِّكَ بِٱلْحِكْمَةِ وَٱلْمَوْعِظَةِ ٱلْحَسَنَةِ ۖ وَجَٰدِلْهُم بِٱلَّتِى هِىَ أَحْسَنُ ۚ إِنَّ رَبَّكَ هُوَ أَعْلَمُ بِمَن ضَلَّ عَن سَبِيلِهِۦ ۖ وَهُوَ أَعْلَمُ بِٱلْمُهْتَدِينَ
29፥46 የመጽሐፉን ባለቤቶችም በዚያች እርሷ *መልካም በኾነችው ክርክር እንጂ አትከራከሩ*፡፡ ከእነርሱ እነዚያን የበደሉትን ሲቀር፡፡ በሉም «በዚያ ወደኛ በተወረደው ወደናንተም በተወረደው አመንን፡፡ አምላካችንም አምላካችሁም አንድ ነው፡፡ እኛም ለእርሱ ታዛዦች ነን፡፡» وَلَا تُجَٰدِلُوٓا۟ أَهْلَ ٱلْكِتَٰبِ إِلَّا بِٱلَّتِى هِىَ أَحْسَنُ إِلَّا ٱلَّذِينَ ظَلَمُوا۟ مِنْهُمْ ۖ وَقُولُوٓا۟ ءَامَنَّا بِٱلَّذِىٓ أُنزِلَ إِلَيْنَا وَأُنزِلَ إِلَيْكُمْ وَإِلَٰهُنَا وَإِلَٰهُكُمْ وَٰحِدٌۭ وَنَحْنُ لَهُۥ مُسْلِمُونَ

ሁለተኛው ሙግት ደግሞ "ስሁት ሙግት"Invalid argument" ሲሆን ይህ ሙግት ያለ ዕውቀትና ያለ መረጃ እውርር ድንብር የሆነ ፀለምተኛ ሙግት ነው፤ ሰው ሱሪ በአንገቴ ካለ ዓይን ያስፈጠጠ እውነት ዓይኔን ግንባር ያርገው ብሎ የጨባራ ለቅሶ ውስጥ እርርና ምርር ብሎ የሚንጨረጨረውና የሚንተከተከው በዚህ ሙግት ነው፤ ይህ አካሄድ ኢርቱዕ አካሄድ"pessimistic approach" ነው፦
22፥8 *ከሰዎችም ውስጥ ያለ ዕውቀት፣ ያለ ማስረጃም፣ ያለ አብራሪ መጽሐፍም በአላህ ጉዳይ የሚከራከር ሰው አለ*፡፡ وَمِنَ ٱلنَّاسِ مَن يُجَٰدِلُ فِى ٱللَّهِ بِغَيْرِ عِلْمٍۢ وَلَا هُدًۭى وَلَا كِتَٰبٍۢ مُّنِيرٍۢ

በድርቅና ያለ ዕውቀት፣ ያለ ማስረጃም፣ ያለ አብራሪ መጽሐፍም የሚከራከርን ሰው መሃይምነት ስላጠቃው መሃይማን በክፉ ሲያነጋግሩን በሰላም ውይይቱን መተው ነው፤ ምክንያቱም ወደ ብሽሽቅ ስለሚያስገባ ነው፤ ብሽሽቅ ውስጥ መልካም የሆነችውን ቃል ስለማንናገር ሰይጣን በመካከላቸው ያበላሻልና፦
7:199 “ገርን ጠባይ ያዝ”፤ በመልካምም እዘዝ “መሃይማንን” الْجَاهِلِينَ ተዋቸው። خُذِ ٱلْعَفْوَ وَأْمُرْ بِٱلْعُرْفِ وَأَعْرِضْ عَنِ ٱلْجَٰهِلِينَ
25:63 የአልረሕማንም ባሮች እነዚያ በምድር ላይ “በዝግታ የሚኼዱት”፣ “መሃይማን” الْجَاهِلُونَ በክፉ ባነጋገሩዋቸው ጊዜ፣ “ሰላም” የሚሉት ናቸው። وَعِبَادُ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلَّذِينَ يَمْشُونَ عَلَى ٱلْأَرْضِ هَوْنًۭا وَإِذَا خَاطَبَهُمُ ٱلْجَٰهِلُونَ قَالُوا۟ سَلَٰمًۭا
17:53 ለባሮቼም በላቸው፦ ያችን እርሷ “መልካም የሆነችውን ቃል ይናገሩ”፤ ሰይጣን በመካከላቸው ያበላሻልና፤ ሰይጣን ለሰው ግልጽ ጠላት ነውና። وَقُل لِّعِبَادِى يَقُولُوا۟ ٱلَّتِى هِىَ أَحْسَنُ ۚ إِنَّ ٱلشَّيْطَٰنَ يَنزَغُ بَيْنَهُمْ ۚ إِنَّ ٱلشَّيْطَٰنَ كَانَ لِلْإِنسَٰنِ عَدُوًّۭا مُّبِينًۭا

ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም

የበለጠ ለማወቅ
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen

ወሠላሙ ዐለይኩም
1
አሐዳዊያን

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፤

«ያ ወደ እኔ የሚወረደው፦ ”አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው” ማለት ነው፤ ታዲያ እናንተ ፍጹም “ታዛዦች” ናችሁን?» በላቸው፡፡

قُلْ إِنَّمَا يُوحَىٰٓ إِلَىَّ أَنَّمَآ إِلَٰهُكُمْ إِلَٰهٌۭ وَٰحِدٌۭ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّسْلِمُونَ
ቁርኣን 21፥108

በሥነ-መለኮት ጥናት ክርስትና፣ አይሁድ እና እስልምና አሐዳዊ ሃይማኖት"monotheistic Religion" ተብለው ይመደባሉ፤ ክርስቲያን፣ አይሁዳውያን እና ሙስሊም አሐዳውያን"Monotheism" ይባላሉ፤ ምክንያቱም ፈጣሪ በህላዌ ማለትም በምንነት አንድ ኑባሬ ነው ብለው ስለሚያምኑ ነው።

ነገር ግን የክርስትና አሐዳውያን በሥስት ዋና ዋና ክፍል ይከፈላሉ፤ እነርሱም፦
1ኛ አሓዳውያን“Unitarian” ሲሆኑ፤ “uni” ማለት "አንድ" ማለት ሲሆን ለእነርሱ አምላክ በምንነት እና በማንነት አንድ ስለሆነ አምላካቸውን “mono-une God” ይሉታል፤ እነዚህ የመጀመሪያ መቶ ክፍለ-ዘመን የኢየሱስ ቀዳማይ ተከታዮች ነበሩ።
2ኛ ደግሞ ክሌታውያ“Binitarian” ይባላል፤ “Bini” ማለት "ሁለት" ማለት ሲሆን ለእነርሱ አምላክ በምንነት አንድ ሲሆን በማንነት ደግሞ ሁለቱ አብና ወልድ ናቸው፤ አምላካቸውን “Bini-une God” ይሉት ነበር፤ ይህ ትምህርት ሁለተኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ላይ የዳበረ ትምህርት ነው።
3ኛ ሥላሴአዊያን“Trinitarian” ይባላሉ፤ “Tri” ማለት "ሶስት" ማለት ነው፤ ለእነርሱ አምላክ በምንነት አንድ ሲሆን በማንነት ሶስት ስለሆነ አምላካቸው “Tri-une God” ይባላል፤ ይህ በአራተኛው መቶ ክፍለ-ዘመን ላይ የዳበረ ትምህርት ነው።

ሙሉን ለማንበብ
https://tiriyachen.org/አሐዳዊያን/
1
በስጋ ተገለጠ | ዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ | ጥሪያችን

🔗 https://youtu.be/1dzFncAMy44

👆  አዲስ ቪድዮ በዩትዩብ ቻነላችን ላይ


መልካም ቆይታ ከጥሪያችን ጋር
‐‐‐
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
1
ኢየሱስ ይመለካልን ?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

«በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል፦ ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡

مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَآ أَمَرْتَنِى بِهِۦٓ أَنِ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبَّكُمْ
ቁርኣን 5፥117

“ዒባዳ” عبادة የሚለው ቃል “ዓበደ عَبَدَ “አመለከ” ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን “አምልኮ” ማለት ነው፤ አምልኮ የሚገባው አንዱ አምላክ አላህ ብቻ ነው፤ አላህ ዒሳን በል ብሎ ያዘዘው ቃል፦ “ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ” ማለትን ነው፦

«በእርሱ ያዘዝከኝን ቃል፦ ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን አምልኩ ማለትን እንጂ ለእነርሱ ሌላ አላልኩም፡፡

مَا قُلْتُ لَهُمْ إِلَّا مَآ أَمَرْتَنِى بِهِۦٓ أَنِ ٱعْبُدُوا۟ ٱللَّهَ رَبِّى وَرَبَّكُمْ
ቁርኣን 5፥117

ነገር ግን በተቃራኒው ክርስቲያኖች ኢየሱስን በቀጥታ ያመልካሉ፤ “አምልኮ” የሚለው ቃል በእብራይስጥ “አባድ” עָבַד ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ላትሬኦ” λατρεύω ነው፤ ይህም ለአንዱ አምላክ ብቻ በሙሉ ሁለንተና የሚቀርብ ልመና፣ ስእለት፣ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ስግደት፣ መገዛት ፣ አገልግሎት Adoration ነው። ኢየሱስ፦ አምልኩኝ ያለበት፣ ሀዋርያት እና ነብያት፦ ኢየሱስን አምልኩ ያለበት እና ሰዎች ኢየሱስን ያመለኩበት አንድ አንቀጽ የለም። ነገር ግን ኢየሱስ የሚመለክ መሆኑን የሚጠቁሙ ጥቅሶች አሉ ይላሉ፤ እውን ይህ ጥቅስ ኢየሱስ ይመለካል ይላልን? እስቲ ጥቅሱን እንየው፦

ሙሉን ለማንበብ
https://tiriyachen.org/ኢየሱስ-ይመለካልን/
👍81
ያህዌህ እና መሢሑ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

የመርየም ልጅ አልመሲሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

مَّا الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُل
ቁርኣን 5፥75

“አል-መሢሕ” الْمَسِيح የሚለው የዐረቢኛው ቃል “መሠሓ” مسح ማለትም “አበሰ” አሸ” “ቀባ” ከሚል ሥርወ-ግንድ የተገኘ ሲሆን “የቀባ” አሊያም “የተቀባ” ወይንም “የሚያብስ” አሊያም “የታበሰ” ወይንም “የሚያሽ” አሊያም “የሚታሽ” የሚል ፍቺ አለው፤ ዒሣ ኢብኑ መርየም በሽተኞችን፣ ህሙማንን እና ሙታንን በማበስ፣ በማሸት እና በመቀባት ከበሽታቸው በአላህ ፈቃድ ያሽራቸው ስለነበረ እና በአላህ የተሾመ(የተቀባ) ነቢይ ስለሆነ “አል-መሢሕ” ተብሏል። አምላካችን አላህ በተከበረው ቃሉ በዘጠኝ አንቀፆች 11 ጊዜ ኢየሱስ መሢሕ መሆኑን ነግሮናል። ይህ መሢሕ አስተምረው ካለፉት መልእክተኞች አንዱ የአላህ ባሪያ ነው፦


ሙሉውን ለማንበብ
https://tiriyachen.org/ያህዌህ-እና-መሢሑ/
👍2
ፈጣሪ ፍጡር አይደለም!

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡

አላህ ሁለመናውን ፈጣሪ ነው፤ እርሱም አንዱ አሸናፊው ነው፤ በል፡፡ قُلِ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ وَهُوَ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ
ቁርኣን 13፥16

አምላካችን አላህ የሁሉን ነገር ፈጣሪ ነው፥ አላህ በፈጣሪነቱ ላይ ፍጡርነት የሚባል የነውር እና የጎደሎ ባሕርይ የለውም። አላህ ሁለመናው ፈጣሪ ነው፥ ነገርንም ማስገኘት በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው፡- «ኹን ነው» ወዲያውም ይኾናል፦

አላህ ሁለመናውን ፈጣሪ ነው፥ እርሱም አንዱ አሸናፊው ነው" በል፡፡ قُلِ اللَّهُ خَالِقُ كُلِّ شَيْءٍ وَهُوَ الْوَاحِدُ الْقَهَّارُ
ቁርኣን 13፥16

ሰማያትንና ምድርን ያለብጤ ፈጣሪ ነው፤ ነገርንም ማስገኘት በሻ ጊዜ ለእርሱ የሚለው፡- «ኹን ነው» ወዲያውም ይኾናል፡፡ بَدِيعُ السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ ۖ وَإِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ
📜ቁርኣን 2፥117

ሙሉውን ለማንበብ
https://tiriyachen.org/ፈጣሪ-ፍጡር-አይደለም/
1
ሰባው ሱባዔ

ገቢር አንድ

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

3፥78 *ከእነሱም እርሱ ከመጽሐፉ ያይደለ ሲኾን ከመጽሐፉ መኾኑን እንድታስቡ በመጽሐፉ ምላሶቻቸውን የሚያጣምሙ ክፍሎች አሉ፡፡ እርሱ ከአላህ ዘንድ ያልኾነ ሲኾን «እርሱ ከአላህ ዘንድ ነውም» ይላሉ፡፡ እነርሱ የሚያውቁ ሲኾኑም በአላህ ላይ ውሸትን ይናገራሉ*፡፡ وَإِنَّ مِنْهُمْ لَفَرِيقًا يَلْوُونَ أَلْسِنَتَهُم بِالْكِتَابِ لِتَحْسَبُوهُ مِنَ الْكِتَابِ وَمَا هُوَ مِنَ الْكِتَابِ وَيَقُولُونَ هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَمَا هُوَ مِنْ عِندِ اللَّهِ وَيَقُولُونَ عَلَى اللَّهِ الْكَذِبَ وَهُمْ يَعْلَمُونَ

ነቢዩ ዳንኤል የኢየሩሳሌም መፍረስ የሚፈጸምበትን ሰባውን ዓመት፥ ያህዌህ በቃሉ ለነቢዩ ለኤርምያስ የተናገረውን የዓመቱን ቍጥር በመጽሐፍ አስተዋለ፦
ዳንኤል 9፥2 እኔ ዳንኤል *የኢየሩሳሌም መፍረስ የሚፈጸምበትን ሰባውን ዓመት፥ እግዚአብሔር በቃሉ ለነቢዩ ለኤርምያስ የተናገረውን የዓመቱን ቍጥር በመጽሐፍ አስተዋልሁ*።

የባቢሎን ምርኮ 70 ዓመት የሚጀምረው በ 605 ቅድመ-ልደት"BC" የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር ዮአኪንንን እና የከበረውንም የእግዚአብሔርን ቤት ዕቃ ከእርሱ ጋር ባስወሰደ ጊዜ ነው፦
2 ዜና 36፥9-10 *"ዮአኪንም መንገሥ በጀመረ ጊዜ የአሥራ ስምንት ዓመት ጕልማሳ ነበረ፥ በኢየሩሳሌምም ሦስት ወርና አሥር ቀን ነገሠ፤ በእግዚአብሔርም ፊት ክፉ አደረገ። ዓመቱ ባለፈ ጊዜ ንጉሡ ናቡከደነፆር ልኮ ወደ ባቢሎን ወሰደው፥ የከበረውንም የእግዚአብሔርን ቤት ዕቃ ከእርሱ ጋር አስወሰደ፤ ወንድሙንም ሴዴቅያስን በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ አነገሠ"*።

ከዚህ ከ 605 ጀምረን 70 ዓመት ስንቆጥር 535 ቅድመ-ልደት"BC" ይሆናል፥ ከዚያ በኃላ ነቢዩ ዳንኤል የዓመቱን ቍጥር በመጽሐፍ አስተዋለ። በዚህ ጊዜ ገብርኤል ለዳንኤል፦ "በሕዝብህና በቅድስት ከተማህ ላይ ሰባ ሱባዔ ተቀጥሮአል" አለው፦
ዳንኤል 9፥24 ዓመፃን ይጨርስ፥ ኃጢአትንም ይፈጽም፥ በደልንም ያስተሰርይ፥ የዘላለምን ጽድቅ ያገባ፥ ራእይንና ትንቢትን ያትም፥ ቅዱሰ ቅዱሳኑንም ይቀባ ዘንድ *"በሕዝብህና በቅድስት ከተማህ ላይ ሰባ ሱባዔ ተቀጥሮአል"*።

"ሱባዔ" የሚለው የዕብራይስጥ ቃል "ሻቡኢም" שָׁבֻעִ֨ים ሲሆን "ሳምንታት" ማለት ነው፥ "ሻቡአ" שְׁבוּעַ ማለት "ሳምንት" ወይም "ሰባት" ማለት ነው። "ሰባ ሱባዔ" ማለት "ሰባ ሳምንት" ማለት ነው፥ አንድ ሳምንት ሰባት ቀናት ናቸው። ስለዚህ 70×7= 490 ይሆናል። ይህ ሰባ ሱባዔ በዳንኤል ሕዝብ እና በቅድስት ከተማ ላይ የተቆጠረ ስሌት ነው። ይህ ሰባ ሱባዔ ለሦስት ይከፈላል፥ እነርሱም 7 ሱባዔ፣ 62 ሱባዔ እና 1 ሱባዔ ይሆናል። ይህ 7+62+1=70 ሱባዔ ይሆናል። እነዚህን ነጥብ በነጥብ እስቲ እንመልከት፦

ነጥብ አንድ
"ሰባት ሱባዔ"
ስለ ኢየሩሳሌምን መጠገን እና መሥራት ቃሉ ከሚወጣበት ጀምሮ እስከ አለቃው እስከ መሢሕ ድረስ ሰባት ሱባዔ ይሆናል፦
ዳንኤል 9፥25 ስለዚህ እወቅ አስተውልም፤ *"ኢየሩሳሌምን ስለ መጠገን እና ስለ መሥራት ቃሉ ከሚወጣበት ጀምሮ እስከ አለቃው እስከ መሢሕ ድረስ ሰባት ሱባዔ ይሆናል"*። ከዚያም በስድሳ ሁለት ሱባዔ እርስዋም በጭንቀት ዘመን ጎዳና እና ከቅጥር ጋር ትሠራለች።
וְתֵדַע וְתַשְׂכֵּל מִן-מֹצָא דָבָר, לְהָשִׁיב וְלִבְנוֹת יְרוּשָׁלִַם עַד-מָשִׁיחַ נָגִיד--שָׁבֻעִים, שִׁבְעָה; וְשָׁבֻעִים שִׁשִּׁים וּשְׁנַיִם, תָּשׁוּב וְנִבְנְתָה רְחוֹב וְחָרוּץ, וּבְצוֹק, הָעִתִּים.
English Standard Version
Know therefore and understand that from the going out of the word to restore and build Jerusalem to the coming of an anointed one, a prince, there shall be seven weeks. Then for sixty-two weeks it shall be built again with squares and moat, but in a troubled time.

የዕብራይስጡን ያመጣሁት ምክንያት 7 እና 62 ቁልጭ አርጎ ስለሚለይ ነው። "ሌ" לְ ማለት "ስለ" ማለት ነው፥ ስለ ኢየሩሳሌምን መጠገን እና መሥራት ቃሉ ወጥቷል። "ዳባር" דָבָ֗ר ማለት "ቃል" ማለት ነው። ይህ ቃል የወጣው ከፈጣሪ ሲሆን በነቢዩ ኤርሚያስ በኩል ነው፦
ኤርምያስ 29፥10 እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ *"ሰባው ዓመት በባቢሎን በተፈጸመ ጊዜ እጐበኛችኋለሁ፥ ወደዚህም ስፍራ *"እመልሳችሁ"* הָשִׁיב֙ ዘንድ መልካሚቱን "ቃሌን" דְּבָרִ֣י እፈጽምላችኋለሁ።

"ቃሌ" ለሚለው ቃል የገባው "ዳባሪ" דְּבָרִ֣י ሲሆን "የዳባር አገናዛቢ መደብ ነው። "ሀሺብ" הָשִׁיב֙ ማለት "እመልሳለው" ማለት ሲሆን ዳንኤል ላይ "መጠገን" ለሚለው የገባው ቃል "ሀሺብ" הָשִׁיב֙ ነው፥ "ሀሺብ" הָשִׁיב֙ ማለት "ሹብ" שׁוּב "መመለስ" ማለት ነው፦
ኤርሚያስ 29፥14 ከእናንተም ዘንድ እገኛለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፥ ምርኮአችሁንም *"እመልሳለሁ"* וְשַׁבְתִּ֣י ፥ ከአሕዛብም ሁሉ ዘንድ እናንተንም ካሳደድሁበት ስፍራ ሁሉ እሰበስባችኋለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር፤ እናንተንም ለምርኮ ወዳፈለስሁበት ስፍራ "እመልሳችኋለሁ" הֲשִׁבֹתִ֣י ።

"እመልሳለሁ" ለሚለው ቃል "ሸብቲ" שַׁבְתִּ֣י የሚለው ቃል መግባቱ አስተውል። "እናንተንም ለምርኮ ወዳፈለስሁበት ስፍራ "እመልሳችኋለሁ" የሚለው ይህንኑ ታሳቢ ያረገ ነው።
ኢየሩሳሌምን "መሥራት" ለሚለው ቃል የገባው "ሊብኖውት" לִבְנ֤וֹת ሲሆን ይህም ቃል በኤርሚያስ በኩል ወጥቷል፦
ኤርምያስ 30፥18 እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የያዕቆብን ድንኳን ምርኮ እመልሳለሁ፥ ለማደሪያውም እራራለሁ፤ ከተማይቱም በጉብታዋ ላይ *"ትሠራለች"* נִבְנְתָ֥ה ፥ አዳራሹም እንደ ዱሮው የሰው መኖሪያ ይሆናል።

"ኒብናታህ" נִבְנְתָ֥ה ማለት "ትሠራለች" ማለት ነው። እዚህ ጋር መያዝ ያለብን ነጥብ በነቢዩ ኤርሚያስ ስለ መመለስ እና ስለ መሥራት ቃል ከያህዌህ የመጣበት ጊዜ በ 586 ቅድመ-ልደት"BC" ነው። የባቢሎን ንጉሥ ናቡከደነፆር በ 605 ቅድመ-ልደት"BC" ዮአኪንን ማርኮ ከ 8 ዓመት በኃላ ሴዴቅያስን በይሁዳና በኢየሩሳሌም ላይ የአሻንጉሊት መንግሥት አነገሠ፥ ሴዴቅያስ በነገሠ በ 11 ዓመት ኢየሩሳሌም አፈረሱ፦
2 ነገሥት 25፥2 *ከተማይቱም እስከ ንጉሡ እስከ ሴዴቅያስ እስከ አሥራ አንደኛው ዓመት ድረስ ተከብባ ነበር*።
2 ነገሥት 25፥8 *በባቢሎንም ንጉሥ በናቡከደነፆር በአሥራ ዘጠነኛው ዓመት በአምስተኛው ወር ከወሩም በሰባተኛው ቀን የባቢሎን ንጉሥ ባሪያ የዘበኞቹ አለቃ ናቡዘረዳን ወደ ኢየሩሳሌም መጣ*።
2 ነገሥት 25፥10 *ከዘበኞቹም አለቃ ጋር የነበረው የከለዳውያን ሠራዊት ሁሉ የኢየሩሳሌምን ቅጥር ዙሪያዋን አፈረሱ*።
1
2025/07/09 16:44:27
Back to Top
HTML Embed Code: