ስለዚህ አንድ ነገር ከመከሰቱ በፊት ያለው ዕውቀት “ዒልሙል ገይብ” ሲባል ከተከሰተ በኃላ የሚገልጠው ዕውቀት “ዒልሙዝ ዛሂር” ይባላል።
ዒልሙዝ ዛሂር” عِلْمٌ الظَهِير ማለት “ግልፅ ወይም ቅርብ አሊያም ተጨባጭ ዕውቀት”objective knowledge” ማለት ነው፤ “ዛሂር” ظَهِير ማለት “ሸሀደት” شَهَٰدَة “ግልፅ” ወይም “ቅርብ” ማለት ሲሆን አንድ ነገር ሲከሰት ነው።
አምላካችን አላህ ሁሉንም ነገር ማለትም መልካሙ ይሁን መጥፎ ነገር ከመከሰቱ በፊት ያውቀዋል፦
59፥22 *እርሱ አላህ ነው፤ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ "ሩቁን እና ቅርቡን ዐዋቂ የኾነ ነው"፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ ነው*፡፡ هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ عَالِمُ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ ۖ هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ
ኢንሻላህ ስለ ቀደር ሁለተኛ ደረጃ ይቀጥላል.....
✍ ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
ዒልሙዝ ዛሂር” عِلْمٌ الظَهِير ማለት “ግልፅ ወይም ቅርብ አሊያም ተጨባጭ ዕውቀት”objective knowledge” ማለት ነው፤ “ዛሂር” ظَهِير ማለት “ሸሀደት” شَهَٰدَة “ግልፅ” ወይም “ቅርብ” ማለት ሲሆን አንድ ነገር ሲከሰት ነው።
አምላካችን አላህ ሁሉንም ነገር ማለትም መልካሙ ይሁን መጥፎ ነገር ከመከሰቱ በፊት ያውቀዋል፦
59፥22 *እርሱ አላህ ነው፤ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፣ "ሩቁን እና ቅርቡን ዐዋቂ የኾነ ነው"፡፡ እርሱ እጅግ በጣም ርኅሩህ በጣም አዛኝ ነው*፡፡ هُوَ اللَّهُ الَّذِي لَا إِلَـٰهَ إِلَّا هُوَ ۖ عَالِمُ الْغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ ۖ هُوَ الرَّحْمَـٰنُ الرَّحِيمُ
ኢንሻላህ ስለ ቀደር ሁለተኛ ደረጃ ይቀጥላል.....
✍ ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ቀደር
ከታች ያለውን ባለአራት ክፍል ደርስ ከኡስታዙና አቡሃይደር አላህ ይጠብቀው የተማርኩት ትምህርት ነው፤
✍ ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
------------------------------------------------
ክፍል አንድ
https://tiriyachen.org/ቀደር/
------------------------------------------------
ክፍል ሁለት
https://tiriyachen.org/ቀደር-2/
------------------------------------------------
ክፍል ሦስት
https://tiriyachen.org/ቀደር-3/
------------------------------------------------
ክፍል አራት
https://tiriyachen.org/ቀደር-4/
------------------------------------------------
ገብታችህ አንብቡት ብዙ ትማሩበታላችህ
ኢንሻላህ
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ከታች ያለውን ባለአራት ክፍል ደርስ ከኡስታዙና አቡሃይደር አላህ ይጠብቀው የተማርኩት ትምህርት ነው፤
✍ ኡሥታዝ ወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
------------------------------------------------
ክፍል አንድ
https://tiriyachen.org/ቀደር/
------------------------------------------------
ክፍል ሁለት
https://tiriyachen.org/ቀደር-2/
------------------------------------------------
ክፍል ሦስት
https://tiriyachen.org/ቀደር-3/
------------------------------------------------
ክፍል አራት
https://tiriyachen.org/ቀደር-4/
------------------------------------------------
ገብታችህ አንብቡት ብዙ ትማሩበታላችህ
ኢንሻላህ
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ነቢዩ ኢስማዒል
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
19፥54 በመጽሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ *መልክተኛ ነቢይም ነበር*፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
“ኢስማኢል” إِسْمَٰعِيْل የሚለው የዐረቢኛው ቃል የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ “ኢስማ” إِسْم ማለት “ሰማኝ” ማለት ሲሆን “ኢል” َٰعِيْل ማለት “አምላክ” ማለት ነው፤ “አምላክ ጸሎቴን ሰማኝ” ማለት ነው፤ ኢብራሂም ወደ አላህ ልመናው፦ “ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ” የሚል ነበር፤ አላህም ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰረው፤ በዚህ ምክንያት “ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና” አለ፦
37፥100 *ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ*፡፡ رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
14፥39 «ለእዚያ ከሽምግልና በኋላ *ኢስማዒልን ኢስሐቅንም ለእኔ ለሰጠኝ* አላህ ምሰጋና ይገባው፡፡ *ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና*፡፡ الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي وَهَبَ لِي عَلَى الْكِبَرِ إِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ ۚ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ
አላህ ወደ ኢስማዒል ወሕይ አውርዷል፤ አላህ ስለ ኢስማኢል ሲናገር “በኢስማዒልም ላይ በተወረደው አመንን በሉ” በማለት ግህደተ-መለኮት ወርዶለት እንደነበር ይናገራል፦
3፥84 «በአላህ አመንን፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም፣ በኢብራሂምና *በኢስማዒልም*፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም፣ በነገዶችም ላይ *በተወረደው*፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው *አመንን*፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» *በል*፡፡ قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ
2፥136 «በአላህ እና ወደኛ በተወረደው ወደ ኢብራሂምም *ወደ ኢስማዒል* እና ወደ ኢስሐቅም ወደ ያዕቁብና ወደ ነገዶቹም *በተወረደው* በዚያም ሙሳና ዒሳ በተሰጡት በዚያም ነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጡት ከእነርሱ በአንድም መካከል የማንለይ ስንኾን *አመንን*፤ እኛም ለእርሱ ለአላህ ታዛዦች ነን» *በሉ*፡፡ قُولُوا آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَا أُوتِيَ النَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ
4፥163 እኛ ወደ ኑሕ እና ከእርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት እንዳወረድን ወደ አንተም አወረድን፡፡ ወደ ኢብራሂምም፣ *ወደ ኢስማዒልም*፣ ወደ ኢስሓቅም፣ ወደ ያዕቆብም፣ ወደ ነገዶቹም፣ ወደ ዒሳም፣ ወደ አዩብም፣ ወደ ዩኑስም፣ ወደ ሃሩንና፣ ወደ ሱለይማንም *አወረድን*፡፡ ለዳውድም ዘቡርን ሰጠነው፡፡ إِنَّا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ كَمَا أَوْحَيْنَا إِلَىٰ نُوحٍ وَالنَّبِيِّينَ مِن بَعْدِهِ ۚ وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَعِيسَىٰ وَأَيُّوبَ وَيُونُسَ وَهَارُونَ وَسُلَيْمَانَ ۚ وَآتَيْنَا دَاوُودَ زَبُورًا
ኢስማዒልን መልክተኛ ነቢይም ነበር፦
19፥54 በመጽሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ *መልክተኛ ነቢይም ነበር*፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
19፥55 ቤተሰቦቹንም *በሶላትና በዘካ ያዝ ነበር*፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡ وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُ بِالصَّلَاةِ وَالزَّكَاةِ وَكَانَ عِندَ رَبِّهِ مَرْضِيًّا
“እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና” ይለናል፤ የትኛውን ቀጠሮ አክባሪ ነው? ይህም ቀጠሮ ኢብራሂም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የ#ማ#ር#ድ#ህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፤ እርሱም «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ *«ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የ#ማ#ር#ድ#ህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ»* አለ፡፡
እጌታውም ዘንድ ተወዳጅና ከመልካሞቹ የሆነ ይህ ልጅ አላህ ለኢብራሂም የሰጠው የበኩር ልጅ ነው፦
14፥39 «ለእዚያ ከሽምግልና በኋላ *ኢስማዒልን ኢስሐቅንም ለእኔ ለሰጠኝ* አላህ ምሰጋና ይገባው፡፡ ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና፡፡ الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي وَهَبَ لِي عَلَى الْكِبَرِ إِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ ۚ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ
እዚህ አንቀጽ ላይ ከኢስሐቅ በፊት ኢስማዒል መጠቀሱ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ አላህ በልጅ ጉዳይ ኢብራሂም ያበሰረው ሁለት ጊዜ ነው፤ የመጀመሪያው፦ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው” የሚል ነው፦
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
በመቀጠል ሁለተኛው፦ “በኢስሐቅም አበሰርነው” የሚል ነው፦
37፥103 *በኢስሐቅም አበሰርነው*፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَٰهُ بِإِسْحَٰقَ نَبِيًّۭا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
“አበሰርነው” የሚለው ቃል አንድ ዐውድ ላይ ሁለቴ መምጣቱ ኢስሐቅ እና ከላይ የተጠቀሰው በዱዓ የመጣው ልጅ ይለያያሉ፤ በተጨማሪም “ወ” و የሚለው አርፉል አጥፍ ብስራቱ ሁለት ጊዜ መሆኑን ያሳያል፤ አንደኛው ረድፍ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ” ሲሆን ሁለተኛው ረድፍ “በኢስሐቅም አበሰርነው” የሚለው ነው፤ ኢስሐቅ ደግሞ ኢብራሂም አላህን ለምኖ የተሰጠ ልጅ ሳይሆን አንወልድም ብለው ተስፋ በቆረጡበት የተበሰሩት ልጅ ነው፦
ክፍል አንድ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
19፥54 በመጽሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ *መልክተኛ ነቢይም ነበር*፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
“ኢስማኢል” إِسْمَٰعِيْل የሚለው የዐረቢኛው ቃል የሁለት ቃላት ውቅር ነው፤ “ኢስማ” إِسْم ማለት “ሰማኝ” ማለት ሲሆን “ኢል” َٰعِيْل ማለት “አምላክ” ማለት ነው፤ “አምላክ ጸሎቴን ሰማኝ” ማለት ነው፤ ኢብራሂም ወደ አላህ ልመናው፦ “ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ” የሚል ነበር፤ አላህም ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰረው፤ በዚህ ምክንያት “ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና” አለ፦
37፥100 *ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን ልጅ ስጠኝ*፡፡ رَبِّ هَبْ لِى مِنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
14፥39 «ለእዚያ ከሽምግልና በኋላ *ኢስማዒልን ኢስሐቅንም ለእኔ ለሰጠኝ* አላህ ምሰጋና ይገባው፡፡ *ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና*፡፡ الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي وَهَبَ لِي عَلَى الْكِبَرِ إِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ ۚ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ
አላህ ወደ ኢስማዒል ወሕይ አውርዷል፤ አላህ ስለ ኢስማኢል ሲናገር “በኢስማዒልም ላይ በተወረደው አመንን በሉ” በማለት ግህደተ-መለኮት ወርዶለት እንደነበር ይናገራል፦
3፥84 «በአላህ አመንን፡፡ በእኛ ላይ በተወረደውም፣ በኢብራሂምና *በኢስማዒልም*፣ በኢስሓቅም፣ በያዕቆብም፣ በነገዶችም ላይ *በተወረደው*፤ ለሙሳና ለዒሳም ለነቢያትም ሁሉ ከጌታቸው በተሰጠው *አመንን*፡፡ ከእነርሱ መካከል አንድንም አንለይም፡፡ እኛ ለእርሱ ታዛዦች ነን» *በል*፡፡ قُلْ آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ عَلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ عَلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَالنَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ
2፥136 «በአላህ እና ወደኛ በተወረደው ወደ ኢብራሂምም *ወደ ኢስማዒል* እና ወደ ኢስሐቅም ወደ ያዕቁብና ወደ ነገዶቹም *በተወረደው* በዚያም ሙሳና ዒሳ በተሰጡት በዚያም ነቢያት ሁሉ ከጌታቸው በተሰጡት ከእነርሱ በአንድም መካከል የማንለይ ስንኾን *አመንን*፤ እኛም ለእርሱ ለአላህ ታዛዦች ነን» *በሉ*፡፡ قُولُوا آمَنَّا بِاللَّهِ وَمَا أُنزِلَ إِلَيْنَا وَمَا أُنزِلَ إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَمَا أُوتِيَ مُوسَىٰ وَعِيسَىٰ وَمَا أُوتِيَ النَّبِيُّونَ مِن رَّبِّهِمْ لَا نُفَرِّقُ بَيْنَ أَحَدٍ مِّنْهُمْ وَنَحْنُ لَهُ مُسْلِمُونَ
4፥163 እኛ ወደ ኑሕ እና ከእርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት እንዳወረድን ወደ አንተም አወረድን፡፡ ወደ ኢብራሂምም፣ *ወደ ኢስማዒልም*፣ ወደ ኢስሓቅም፣ ወደ ያዕቆብም፣ ወደ ነገዶቹም፣ ወደ ዒሳም፣ ወደ አዩብም፣ ወደ ዩኑስም፣ ወደ ሃሩንና፣ ወደ ሱለይማንም *አወረድን*፡፡ ለዳውድም ዘቡርን ሰጠነው፡፡ إِنَّا أَوْحَيْنَا إِلَيْكَ كَمَا أَوْحَيْنَا إِلَىٰ نُوحٍ وَالنَّبِيِّينَ مِن بَعْدِهِ ۚ وَأَوْحَيْنَا إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ وَيَعْقُوبَ وَالْأَسْبَاطِ وَعِيسَىٰ وَأَيُّوبَ وَيُونُسَ وَهَارُونَ وَسُلَيْمَانَ ۚ وَآتَيْنَا دَاوُودَ زَبُورًا
ኢስማዒልን መልክተኛ ነቢይም ነበር፦
19፥54 በመጽሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ *መልክተኛ ነቢይም ነበር*፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا
19፥55 ቤተሰቦቹንም *በሶላትና በዘካ ያዝ ነበር*፡፡ እጌታውም ዘንድ ተወዳጅ ነበር፡፡ وَكَانَ يَأْمُرُ أَهْلَهُ بِالصَّلَاةِ وَالزَّكَاةِ وَكَانَ عِندَ رَبِّهِ مَرْضِيًّا
“እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና” ይለናል፤ የትኛውን ቀጠሮ አክባሪ ነው? ይህም ቀጠሮ ኢብራሂም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የ#ማ#ር#ድ#ህ ሆኜ አያለሁ፤ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፤ እርሱም «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፦
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ *«ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የ#ማ#ር#ድ#ህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ»* አለ፡፡
እጌታውም ዘንድ ተወዳጅና ከመልካሞቹ የሆነ ይህ ልጅ አላህ ለኢብራሂም የሰጠው የበኩር ልጅ ነው፦
14፥39 «ለእዚያ ከሽምግልና በኋላ *ኢስማዒልን ኢስሐቅንም ለእኔ ለሰጠኝ* አላህ ምሰጋና ይገባው፡፡ ጌታዬ ልመናን በእርግጥ ሰሚ ነውና፡፡ الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي وَهَبَ لِي عَلَى الْكِبَرِ إِسْمَاعِيلَ وَإِسْحَاقَ ۚ إِنَّ رَبِّي لَسَمِيعُ الدُّعَاءِ
እዚህ አንቀጽ ላይ ከኢስሐቅ በፊት ኢስማዒል መጠቀሱ አንባቢ ልብ ይለዋል፤ አላህ በልጅ ጉዳይ ኢብራሂም ያበሰረው ሁለት ጊዜ ነው፤ የመጀመሪያው፦ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው” የሚል ነው፦
37፥101 *ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው*፡፡ فَبَشَّرْنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٍۢ
በመቀጠል ሁለተኛው፦ “በኢስሐቅም አበሰርነው” የሚል ነው፦
37፥103 *በኢስሐቅም አበሰርነው*፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡ وَبَشَّرْنَٰهُ بِإِسْحَٰقَ نَبِيًّۭا مِّنَ ٱلصَّٰلِحِينَ
“አበሰርነው” የሚለው ቃል አንድ ዐውድ ላይ ሁለቴ መምጣቱ ኢስሐቅ እና ከላይ የተጠቀሰው በዱዓ የመጣው ልጅ ይለያያሉ፤ በተጨማሪም “ወ” و የሚለው አርፉል አጥፍ ብስራቱ ሁለት ጊዜ መሆኑን ያሳያል፤ አንደኛው ረድፍ “ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅ” ሲሆን ሁለተኛው ረድፍ “በኢስሐቅም አበሰርነው” የሚለው ነው፤ ኢስሐቅ ደግሞ ኢብራሂም አላህን ለምኖ የተሰጠ ልጅ ሳይሆን አንወልድም ብለው ተስፋ በቆረጡበት የተበሰሩት ልጅ ነው፦
15፥53 «አትፍራ፤ እኛ ዐዋቂ በኾነ ወንድ ልጅ *እናበስርሃለን*» አሉት፡፡ قَالُوا۟ لَا تَوْجَلْ إِنَّا نُبَشِّرُكَ بِغُلَٰمٍ عَلِيمٍۢ
15፥54 *«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ»* አለ፡፡ قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِى عَلَىٰٓ أَن مَّسَّنِىَ ٱلْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ
15፥55 «በእውነት *አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን*» አሉ፡፡ قَالُوا۟ بَشَّرْنَٰكَ بِٱلْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ ٱلْقَٰنِطِينَ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን አትፍራ አሉት፤ ሳቀችም፡፡ *በኢስሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በልጁ በያዕቁብ አበሰርናት*፡፡ وَٱمْرَأَتُهُۥ قَآئِمَةٌۭ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَٰهَا بِإِسْحَٰقَ وَمِن وَرَآءِ إِسْحَٰقَ يَعْقُوبَ
ኢብራሂም በኢስሀቅ ሲበሰር፦ “እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ?” ማለቱ ለምኖ ያገኘው ልጅ ሳይሆን ያላሰበው ልጅ መሆኑ ቁልጭና ፍንትው አድርጎ ያሳያል፤ ኢብራሂም የተበሰረው በኢስሀቅ ብቻ ሳይሆን በልጅ ልጁ በያዕቁብም ነው፤ ኢብራሂም ኢስሀቅ ሳይ#ታረ#ድ ተርፎ የልጅ ልጁ ያዕቆብ እንደሚወለድ ካወቀ፤ ኢስሀቅ ያዕቁብ የሚባል ልጅ እንደሚኖረዉ አስቀድሞ ከተበሰረ ልጅህን እ*ረ*ድ*ል*ኝ ብሎ ማዘዙ ፈተናው ትርጉም አልባ ይሆን ነበር፤ ምክንያቱም ልጅህን እ#ረ#ድ#ል#ኝ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፤ ፈተና ትርጉም የሚኖረው ተፈታኙ የሚፈተነውን የማያውቅ ሲሆን ብቻ ነው፦
37፥106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የ#ማ#ር#ድ#ህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
በተጨማሪም አላህ ኢብራሂምንም በቃላት በፈተነው ጊዜ ተያይዞ ኢብራሂምና ኢስማኢል የአላህን ቤት መሠረቶቹን ከፍ በማድረግ እና አላህም፦ “ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ” ብሎ ያዘዘው ኢብራሂምና ኢስማኢል ነው፦
2፥124 *ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው* እና በፈጸማቸው ጊዜ አስታውስ፤ «እኔ ለሰዎች መሪ አድራጊህ ነኝ» አለው፡፡ «ከዘሮቼም አድርግ» አለ፡፡ ቃል ኪዳኔ በዳዮቹን አያገኝም አለው፡፡ وَإِذِ ٱبْتَلَىٰٓ إِبْرَٰهِـۧمَ رَبُّهُۥ بِكَلِمَٰتٍۢ فَأَتَمَّهُنَّ ۖ قَالَ إِنِّى جَاعِلُكَ لِلنَّاسِ إِمَامًۭا ۖ قَالَ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۖ قَالَ لَا يَنَالُ عَهْدِى ٱلظَّٰلِمِينَ
2፥127 *ኢብራሂምና ኢስማኢልም «ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡ አንተ ሰሚውና ዐዋቂው አንተ ነህና» የሚሉ ሲኾኑ ከቤቱ መሠረቶቹን ከፍ ባደረጉ ጊዜ አስታውስ*፡፡ وَإِذْ يَرْفَعُ إِبْرَاهِيمُ الْقَوَاعِدَ مِنَ الْبَيْتِ وَإِسْمَاعِيلُ رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا ۖ إِنَّكَ أَنتَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
2፥125 ቤቱንም ለሰዎች መመለሻና ጸጥተኛ ባደረግን ጊዜ አስታውስ፡፡ ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ፡፡ *ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም* ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ *ስንል* ቃል ኪዳን ያዝን፡፡ وَإِذْ جَعَلْنَا الْبَيْتَ مَثَابَةً لِّلنَّاسِ وَأَمْنًا وَاتَّخِذُوا مِن مَّقَامِ إِبْرَاهِيمَ مُصَلًّى ۖ وَعَهِدْنَا إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ أَن طَهِّرَا بَيْتِيَ لِلطَّائِفِينَ وَالْعَاكِفِينَ وَالرُّكَّعِ السُّجُودِ
ይህ እ#ር#ድ የሚካሄድበት ቦታ በመካ እንጂ በሻም አለመሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። እንግዲህ ከእነርሱ የትውልድ መስመር በትንቢት ቃል ኪዳን የተገባላቸው የነብያት መደምደሚያ ነብያችን”ﷺ” መጥተዋል፦
2፥129 «ጌታችን ሆይ! *በውስጣቸውም ከእነርሱው የኾነን መልክተኛ በእነርሱ ላይ አንቀጾችህን የሚያነብላቸውን መጽሐፍንና ጥበብንም የሚያስተምራቸውን ከክህደት የሚያጠራቸውንም ላክ*፤ አንተ አሸናፊው ጥበበኛው አንተ ብቻ ነህና» የሚሉም ሲኾኑ፡፡ رَبَّنَا وَٱبْعَثْ فِيهِمْ رَسُولًۭا مِّنْهُمْ يَتْلُوا۟ عَلَيْهِمْ ءَايَٰتِكَ وَيُعَلِّمُهُمُ ٱلْكِتَٰبَ وَٱلْحِكْمَةَ وَيُزَكِّيهِمْ ۚ إِنَّكَ أَنتَ ٱلْعَزِيزُ ٱلْحَكِيمُ
2፥151 *በውስጣችሁ ከእናንተው የኾነን በእናንተ ላይ አንቀጾቻችንን የሚያነብላችሁና የሚያጠራችሁ፣ መጽሐፍንና ጥበብንም የሚያስተምራችሁ፣ ታውቁት ያልነበራችሁትንም ነገር የሚያሳውቃችሁ የኾነን መልክተኛ እንደላክን ጸጋን ሞላንላችሁ*፡፡ كَمَا أَرْسَلْنَا فِيكُمْ رَسُولًا مِّنكُمْ يَتْلُو عَلَيْكُمْ آيَاتِنَا وَيُزَكِّيكُمْ وَيُعَلِّمُكُمُ الْكِتَابَ وَالْحِكْمَةَ وَيُعَلِّمُكُم مَّا لَمْ تَكُونُوا تَعْلَمُونَ
በቁርአን ላይ ስለ ነቢዩ ኢስማዒል ያለውን ምልከታ ለእይታ ያክል ካየን ዘንዳ ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ስለ ነቢዩ ኢስማዒል በባይብል ላይ ያለውን ምልከታ ለእይታ ያክል እንመለከታለን።
✍ ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
የበለጠ ለማወቅ
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
15፥54 *«እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ»* አለ፡፡ قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِى عَلَىٰٓ أَن مَّسَّنِىَ ٱلْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ
15፥55 «በእውነት *አበሰርንህ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን*» አሉ፡፡ قَالُوا۟ بَشَّرْنَٰكَ بِٱلْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ ٱلْقَٰنِطِينَ
11፥71 ሚስቱም የቆመች ስትኾን አትፍራ አሉት፤ ሳቀችም፡፡ *በኢስሐቅም አበሰርናት፡፡ ከኢስሐቅም በኋላ በልጁ በያዕቁብ አበሰርናት*፡፡ وَٱمْرَأَتُهُۥ قَآئِمَةٌۭ فَضَحِكَتْ فَبَشَّرْنَٰهَا بِإِسْحَٰقَ وَمِن وَرَآءِ إِسْحَٰقَ يَعْقُوبَ
ኢብራሂም በኢስሀቅ ሲበሰር፦ “እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ?” ማለቱ ለምኖ ያገኘው ልጅ ሳይሆን ያላሰበው ልጅ መሆኑ ቁልጭና ፍንትው አድርጎ ያሳያል፤ ኢብራሂም የተበሰረው በኢስሀቅ ብቻ ሳይሆን በልጅ ልጁ በያዕቁብም ነው፤ ኢብራሂም ኢስሀቅ ሳይ#ታረ#ድ ተርፎ የልጅ ልጁ ያዕቆብ እንደሚወለድ ካወቀ፤ ኢስሀቅ ያዕቁብ የሚባል ልጅ እንደሚኖረዉ አስቀድሞ ከተበሰረ ልጅህን እ*ረ*ድ*ል*ኝ ብሎ ማዘዙ ፈተናው ትርጉም አልባ ይሆን ነበር፤ ምክንያቱም ልጅህን እ#ረ#ድ#ል#ኝ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፤ ፈተና ትርጉም የሚኖረው ተፈታኙ የሚፈተነውን የማያውቅ ሲሆን ብቻ ነው፦
37፥106 ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلْبَلَٰٓؤُا۟ ٱلْمُبِينُ
37፥102 ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የ#ማ#ር#ድ#ህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
በተጨማሪም አላህ ኢብራሂምንም በቃላት በፈተነው ጊዜ ተያይዞ ኢብራሂምና ኢስማኢል የአላህን ቤት መሠረቶቹን ከፍ በማድረግ እና አላህም፦ “ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ” ብሎ ያዘዘው ኢብራሂምና ኢስማኢል ነው፦
2፥124 *ኢብራሂምንም ጌታው በቃላት በፈተነው* እና በፈጸማቸው ጊዜ አስታውስ፤ «እኔ ለሰዎች መሪ አድራጊህ ነኝ» አለው፡፡ «ከዘሮቼም አድርግ» አለ፡፡ ቃል ኪዳኔ በዳዮቹን አያገኝም አለው፡፡ وَإِذِ ٱبْتَلَىٰٓ إِبْرَٰهِـۧمَ رَبُّهُۥ بِكَلِمَٰتٍۢ فَأَتَمَّهُنَّ ۖ قَالَ إِنِّى جَاعِلُكَ لِلنَّاسِ إِمَامًۭا ۖ قَالَ وَمِن ذُرِّيَّتِى ۖ قَالَ لَا يَنَالُ عَهْدِى ٱلظَّٰلِمِينَ
2፥127 *ኢብራሂምና ኢስማኢልም «ጌታችን ሆይ! ከእኛ ተቀበል፡፡ አንተ ሰሚውና ዐዋቂው አንተ ነህና» የሚሉ ሲኾኑ ከቤቱ መሠረቶቹን ከፍ ባደረጉ ጊዜ አስታውስ*፡፡ وَإِذْ يَرْفَعُ إِبْرَاهِيمُ الْقَوَاعِدَ مِنَ الْبَيْتِ وَإِسْمَاعِيلُ رَبَّنَا تَقَبَّلْ مِنَّا ۖ إِنَّكَ أَنتَ السَّمِيعُ الْعَلِيمُ
2፥125 ቤቱንም ለሰዎች መመለሻና ጸጥተኛ ባደረግን ጊዜ አስታውስ፡፡ ከኢብራሂምም መቆሚያ መስገጃን አድርጉ፡፡ *ወደ ኢብራሂምና ወደ ኢስማዒልም* ቤቴን ለዘዋሪዎቹና ለተቀማጮቹም ለአጎንባሾች ሰጋጆቹም አጥሩ *ስንል* ቃል ኪዳን ያዝን፡፡ وَإِذْ جَعَلْنَا الْبَيْتَ مَثَابَةً لِّلنَّاسِ وَأَمْنًا وَاتَّخِذُوا مِن مَّقَامِ إِبْرَاهِيمَ مُصَلًّى ۖ وَعَهِدْنَا إِلَىٰ إِبْرَاهِيمَ وَإِسْمَاعِيلَ أَن طَهِّرَا بَيْتِيَ لِلطَّائِفِينَ وَالْعَاكِفِينَ وَالرُّكَّعِ السُّجُودِ
ይህ እ#ር#ድ የሚካሄድበት ቦታ በመካ እንጂ በሻም አለመሆኑ አንባቢ ልብ ይለዋል። እንግዲህ ከእነርሱ የትውልድ መስመር በትንቢት ቃል ኪዳን የተገባላቸው የነብያት መደምደሚያ ነብያችን”ﷺ” መጥተዋል፦
2፥129 «ጌታችን ሆይ! *በውስጣቸውም ከእነርሱው የኾነን መልክተኛ በእነርሱ ላይ አንቀጾችህን የሚያነብላቸውን መጽሐፍንና ጥበብንም የሚያስተምራቸውን ከክህደት የሚያጠራቸውንም ላክ*፤ አንተ አሸናፊው ጥበበኛው አንተ ብቻ ነህና» የሚሉም ሲኾኑ፡፡ رَبَّنَا وَٱبْعَثْ فِيهِمْ رَسُولًۭا مِّنْهُمْ يَتْلُوا۟ عَلَيْهِمْ ءَايَٰتِكَ وَيُعَلِّمُهُمُ ٱلْكِتَٰبَ وَٱلْحِكْمَةَ وَيُزَكِّيهِمْ ۚ إِنَّكَ أَنتَ ٱلْعَزِيزُ ٱلْحَكِيمُ
2፥151 *በውስጣችሁ ከእናንተው የኾነን በእናንተ ላይ አንቀጾቻችንን የሚያነብላችሁና የሚያጠራችሁ፣ መጽሐፍንና ጥበብንም የሚያስተምራችሁ፣ ታውቁት ያልነበራችሁትንም ነገር የሚያሳውቃችሁ የኾነን መልክተኛ እንደላክን ጸጋን ሞላንላችሁ*፡፡ كَمَا أَرْسَلْنَا فِيكُمْ رَسُولًا مِّنكُمْ يَتْلُو عَلَيْكُمْ آيَاتِنَا وَيُزَكِّيكُمْ وَيُعَلِّمُكُمُ الْكِتَابَ وَالْحِكْمَةَ وَيُعَلِّمُكُم مَّا لَمْ تَكُونُوا تَعْلَمُونَ
በቁርአን ላይ ስለ ነቢዩ ኢስማዒል ያለውን ምልከታ ለእይታ ያክል ካየን ዘንዳ ኢንሻላህ በክፍል ሁለት ስለ ነቢዩ ኢስማዒል በባይብል ላይ ያለውን ምልከታ ለእይታ ያክል እንመለከታለን።
✍ ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
የበለጠ ለማወቅ
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ነቢዩ ኢስማዒል
ክፍል አንድ
https://tiriyachen.org/ነቢዩ-ኢስማዒል/
_______
ክፍል ሁለት
https://tiriyachen.org/ነብዩ-ኢስማዒል/
________
ክፍል አንድ
https://tiriyachen.org/ነቢዩ-ኢስማዒል/
_______
ክፍል ሁለት
https://tiriyachen.org/ነብዩ-ኢስማዒል/
________
Tiriyachen
ነቢዩ ኢስማዒል - Tiriyachen
ክፍል አንድ በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡ በመጽሐፉ ኢስማዒልንም አውሳ፡፡ እርሱ ቀጠሮን አክባሪ ነበረና፡፡ መልክተኛ ነቢይም ነበር፡፡ وَاذْكُرْ فِي الْكِتَابِ إِسْمَاعِيلَ ۚ إِنَّهُ كَانَ صَادِقَ الْوَعْدِ وَكَانَ رَسُولًا نَّبِيًّا ቁርኣን 19፥54 “ኢስማኢል” إِسْمَٰعِيْل የሚለው የዐረቢኛው ቃል የሁለት…
የተፈጠርንበት ዓላማ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
51፥56 *ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም*፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
አምላካችን አላህ ብዙ አንቀጾች ላይ “አምልኩኝ” እያለ በመጀመሪያ መደብ ይናገራል፦
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ *”እኔንም ብቻ አምልኩኝ”*፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّىَ فَٱعْبُدُونِ
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ *”እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ”*፡፡ إِنَّ هَٰذِهِۦٓ أُمَّتُكُمْ أُمَّةًۭ وَٰحِدَةًۭ وَأَنَا۠ رَبُّكُمْ فَٱعْبُدُونِ
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ *”የምናወርድለት”* ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
ጂን እና ሰው የተፈጠረበት ዓላማ ሁሉንም የፈጠረውን አንዱን አምላክ አላህ በብቸኝነት እንዲያመልኩት ነው፦ .......
ሙሉውን ያንብቡ 👇🏻👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/የተፈጠርንበት-ዓላማ/
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
51፥56 *ጂኒን እና ሰውንም ሊያመልኩኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም*፡፡ وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
አምላካችን አላህ ብዙ አንቀጾች ላይ “አምልኩኝ” እያለ በመጀመሪያ መደብ ይናገራል፦
29፥56 እናንተ ያመናችሁ ባሮቼ ሆይ! ምድሬ በእርግጥ ሰፊ ናት፤ ብትቸገሩ ተሰደዱ፡፡ *”እኔንም ብቻ አምልኩኝ”*፡፡ يَٰعِبَادِىَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُوٓا۟ إِنَّ أَرْضِى وَٰسِعَةٌۭ فَإِيَّىَ فَٱعْبُدُونِ
21፥92 ይህች አንዲት መንገድ ስትሆን በእርግጥ ሃይማኖታችሁ ናት፤ *”እኔም ጌታችሁ ነኝና አምልኩኝ”*፡፡ إِنَّ هَٰذِهِۦٓ أُمَّتُكُمْ أُمَّةًۭ وَٰحِدَةًۭ وَأَنَا۠ رَبُّكُمْ فَٱعْبُدُونِ
21፥25 ከአንተ በፊትም እነሆ *”ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና አምልኩኝ”* በማለት ወደ እርሱ *”የምናወርድለት”* ቢኾን እንጅ ከመልክተኛ አንድንም አልላክንም፡፡ وَمَآ أَرْسَلْنَا مِن قَبْلِكَ مِن رَّسُولٍ إِلَّا نُوحِىٓ إِلَيْهِ أَنَّهُۥ لَآ إِلَٰهَ إِلَّآ أَنَا۠ فَٱعْبُدُونِ
ጂን እና ሰው የተፈጠረበት ዓላማ ሁሉንም የፈጠረውን አንዱን አምላክ አላህ በብቸኝነት እንዲያመልኩት ነው፦ .......
ሙሉውን ያንብቡ 👇🏻👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/የተፈጠርንበት-ዓላማ/
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
ከአህለል ኪታብ ሴት ጋር መጋባት ይቻላልን? ያረዱትንስ መብላት ይቻላልን?
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
5፥5 ዛሬ መልካሞች ሁሉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ *የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው፡፡ ምግባችሁም ለእነሱ የተፈቀደ ነው*፡፡ ከምእመናት ጥብቆቹም *ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው*፡፡ ከእምነትም የሚመለስ ሰው በእርግጥ ሥራው ተበላሸ፡፡ በመጨረሻም ቀን እርሱ ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ ٱلْيَوْمَ أُحِلَّ لَكُمُ ٱلطَّيِّبَٰتُ ۖ وَطَعَامُ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ حِلٌّۭ لَّكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّۭ لَّهُمْ ۖ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلِكُمْ إِذَآ ءَاتَيْتُمُوهُنَّ أُجُورَهُنَّ مُحْصِنِينَ غَيْرَ مُسَٰفِحِينَ وَلَا مُتَّخِذِىٓ أَخْدَانٍۢ ۗ وَمَن يَكْفُرْ بِٱلْإِيمَٰنِ فَقَدْ حَبِطَ عَمَلُهُۥ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
አምላካችን አላህ በእርሱ ላይ ሌሎች ማንነትንና ምንነትን የሚያጋሩ ሙሽሪኮችን እንዳናገባ እና ከእርሱ ስም ውጪ በሌላ ፍጡር ስም ተባርኮ የታረደን እርድ እንዳንበላ ከልክሏል፦
2፥221 *አጋሪ የሆኑ ሴቶች እስከሚያምኑ ድረስ አታግቡዋቸው*፡፡ ከአጋሪይቱ ምንም ብትደንቃችሁም እንኳ ያመነችው ባሪያ በእርግጥ በላጭ ናት፡፡ *ለአጋሪዎቹም እስከሚያምኑ ድረስ አትዳሩላቸው*፡፡ ከአጋሪው ጌታ ምንም ቢደንቃችሁ ምእምኑ ባሪያ በላጭ ነው፡፡ *እነዚያ አጋሪዎች ወደ እሳት ይጣራሉ፡፡ አላህም በፈቃዱ ወደ ገነትና ወደ ምሕረት ይጠራል*፡፡ ሕግጋቱንም ለሰዎች ይገልጻል እነርሱ ሊገሰጹ ይከጀላልና፡፡ وَلَا تَنكِحُوا الْمُشْرِكَاتِ حَتَّىٰ يُؤْمِنَّ ۚ وَلَأَمَةٌ مُّؤْمِنَةٌ خَيْرٌ مِّن مُّشْرِكَةٍ وَلَوْ أَعْجَبَتْكُمْ ۗ وَلَا تُنكِحُوا الْمُشْرِكِينَ حَتَّىٰ يُؤْمِنُوا ۚ وَلَعَبْدٌ مُّؤْمِنٌ خَيْرٌ مِّن مُّشْرِكٍ وَلَوْ أَعْجَبَكُمْ ۗ أُولَـٰئِكَ يَدْعُونَ إِلَى النَّارِ ۖ وَاللَّهُ يَدْعُو إِلَى الْجَنَّةِ وَالْمَغْفِرَةِ بِإِذْنِهِ ۖ وَيُبَيِّنُ آيَاتِهِ لِلنَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَتَذَكَّرُونَ
6፥121 *በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ*፡፡ እርሱም በእርግጥ አመጽ ነው፡፡ ሰይጣናትም ወደ ወዳጆቻቸው በክትን በመብላት ይከራከሯችሁ ዘንድ ያሾከሹካሉ፡፡ *ብትታዘዙዋቸውም እናንተ በእርግጥ አጋሪዎች ናችሁ*፡፡ وَلَا تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ وَإِنَّهُ لَفِسْقٌ ۗ وَإِنَّ الشَّيَاطِينَ لَيُوحُونَ إِلَىٰ أَوْلِيَائِهِمْ لِيُجَادِلُوكُمْ ۖ وَإِنْ أَطَعْتُمُوهُمْ إِنَّكُمْ لَمُشْرِكُونَ
"ለናሙና ያክል" “ሺርክ” شِرْك የሚለው ቃል “አሽረከ” أَشْرَكَ ማለትም “አጋራ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ማጋራት” ማለት ነው፤ የሚያጋራው ሰው ደግሞ “ሙሽሪክ” مُشْرِك ማለትም “አጋሪ” ይባላል፤ እንዲሁ በአላህ ላይ የሚያጋሩት ማንነትና ምንነት “ሸሪክ” شَرِيك ማለትም “ተጋሪ” ይባላሉ፤ ከአህለል ኪታብ ሙሉ ለሙሉ ባይሆንም ከነሳራዎች አበይት የሚባሉት ሙሽሪኪን ናቸው፦
5፤72 *እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን ተገዙ፡፡» *እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ*፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ لَقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ ۖ وَقَالَ الْمَسِيحُ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ ۖ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ
እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፤ እነሆ ይህ ንግግራቸው ማጋራት ነውና አላህ በእርሱ ላይ የሚያጋራ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፤ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ይህ ጥቅላዊ መልእክት “ሙጅመል” مجمل ወይም “ዓም” عام ይባላል፤ ነገር ግን አላህ ከሙሽሪኪን አህለል ኪታቦችን በተናጥል “ሙፈሰል” مُفَصَّل ወይም “ኻስ” خاص በማድረግ ለያቸው፤ ይህም ሙሽሪኪን እና አህለል ኪታብ በሚሉ ቃላት መካከል “ወ” وَ ማለትም “እና” የሚል መስተጻምር አስቀምጧል፦
98፥1 *እነዚያ ከመጽሐፉ ባለቤቶች እና ከአጋሪዎቹም የካዱት ግልጹ አስረጅ እስከ መጣላቸው ድረስ ተወጋጆች አልነበሩም፡፡ لَمْ يَكُنِ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ وَالْمُشْرِكِينَ مُنفَكِّينَ حَتَّىٰ تَأْتِيَهُمُ الْبَيِّنَةُ
“በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ” የሚለው “ዓም” عام ሆኖ ከመጣ በኃላ “የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው” “ኻስ” خاص ሆኖ እንደመጣ ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ” ተናግሯል፦
ሱነን አቢ ዳውድ :መጽሐፍ 16, ሐዲስ 30
ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ” እንደተናገረው፦ 6፥118 “የአላህ ስም በእርሱ ላይ ከተወሳበት እንስሳ ብሉ” የሚለው አንቀጽ እና 6፥116 “በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ” የሚለው አንቀጽ ኢስቲስናዕ በመሆን “የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው” በሚለው ተነሥኻል” عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ { فَكُلُوا مِمَّا ذُكِرَ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ } { وَلاَ تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ } فَنُسِخَ وَاسْتَثْنَى مِنْ ذَلِكَ فَقَالَ { وَطَعَامُ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ حِلٌّ لَكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّ لَهُمْ } .
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
5፥5 ዛሬ መልካሞች ሁሉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ *የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው፡፡ ምግባችሁም ለእነሱ የተፈቀደ ነው*፡፡ ከምእመናት ጥብቆቹም *ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው*፡፡ ከእምነትም የሚመለስ ሰው በእርግጥ ሥራው ተበላሸ፡፡ በመጨረሻም ቀን እርሱ ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ ٱلْيَوْمَ أُحِلَّ لَكُمُ ٱلطَّيِّبَٰتُ ۖ وَطَعَامُ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ حِلٌّۭ لَّكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّۭ لَّهُمْ ۖ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلِكُمْ إِذَآ ءَاتَيْتُمُوهُنَّ أُجُورَهُنَّ مُحْصِنِينَ غَيْرَ مُسَٰفِحِينَ وَلَا مُتَّخِذِىٓ أَخْدَانٍۢ ۗ وَمَن يَكْفُرْ بِٱلْإِيمَٰنِ فَقَدْ حَبِطَ عَمَلُهُۥ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
አምላካችን አላህ በእርሱ ላይ ሌሎች ማንነትንና ምንነትን የሚያጋሩ ሙሽሪኮችን እንዳናገባ እና ከእርሱ ስም ውጪ በሌላ ፍጡር ስም ተባርኮ የታረደን እርድ እንዳንበላ ከልክሏል፦
2፥221 *አጋሪ የሆኑ ሴቶች እስከሚያምኑ ድረስ አታግቡዋቸው*፡፡ ከአጋሪይቱ ምንም ብትደንቃችሁም እንኳ ያመነችው ባሪያ በእርግጥ በላጭ ናት፡፡ *ለአጋሪዎቹም እስከሚያምኑ ድረስ አትዳሩላቸው*፡፡ ከአጋሪው ጌታ ምንም ቢደንቃችሁ ምእምኑ ባሪያ በላጭ ነው፡፡ *እነዚያ አጋሪዎች ወደ እሳት ይጣራሉ፡፡ አላህም በፈቃዱ ወደ ገነትና ወደ ምሕረት ይጠራል*፡፡ ሕግጋቱንም ለሰዎች ይገልጻል እነርሱ ሊገሰጹ ይከጀላልና፡፡ وَلَا تَنكِحُوا الْمُشْرِكَاتِ حَتَّىٰ يُؤْمِنَّ ۚ وَلَأَمَةٌ مُّؤْمِنَةٌ خَيْرٌ مِّن مُّشْرِكَةٍ وَلَوْ أَعْجَبَتْكُمْ ۗ وَلَا تُنكِحُوا الْمُشْرِكِينَ حَتَّىٰ يُؤْمِنُوا ۚ وَلَعَبْدٌ مُّؤْمِنٌ خَيْرٌ مِّن مُّشْرِكٍ وَلَوْ أَعْجَبَكُمْ ۗ أُولَـٰئِكَ يَدْعُونَ إِلَى النَّارِ ۖ وَاللَّهُ يَدْعُو إِلَى الْجَنَّةِ وَالْمَغْفِرَةِ بِإِذْنِهِ ۖ وَيُبَيِّنُ آيَاتِهِ لِلنَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَتَذَكَّرُونَ
6፥121 *በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ*፡፡ እርሱም በእርግጥ አመጽ ነው፡፡ ሰይጣናትም ወደ ወዳጆቻቸው በክትን በመብላት ይከራከሯችሁ ዘንድ ያሾከሹካሉ፡፡ *ብትታዘዙዋቸውም እናንተ በእርግጥ አጋሪዎች ናችሁ*፡፡ وَلَا تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ وَإِنَّهُ لَفِسْقٌ ۗ وَإِنَّ الشَّيَاطِينَ لَيُوحُونَ إِلَىٰ أَوْلِيَائِهِمْ لِيُجَادِلُوكُمْ ۖ وَإِنْ أَطَعْتُمُوهُمْ إِنَّكُمْ لَمُشْرِكُونَ
"ለናሙና ያክል" “ሺርክ” شِرْك የሚለው ቃል “አሽረከ” أَشْرَكَ ማለትም “አጋራ” ከሚል ግስ የመጣ ሲሆን “ማጋራት” ማለት ነው፤ የሚያጋራው ሰው ደግሞ “ሙሽሪክ” مُشْرِك ማለትም “አጋሪ” ይባላል፤ እንዲሁ በአላህ ላይ የሚያጋሩት ማንነትና ምንነት “ሸሪክ” شَرِيك ማለትም “ተጋሪ” ይባላሉ፤ ከአህለል ኪታብ ሙሉ ለሙሉ ባይሆንም ከነሳራዎች አበይት የሚባሉት ሙሽሪኪን ናቸው፦
5፤72 *እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ*፡፡ አልመሲህም አለ፡- «የእስራኤል ልጆች ሆይ! ጌታዬንና ጌታችሁን አላህን ተገዙ፡፡» *እነሆ! በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ*፡፡ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ለበዳዮችም ምንም ረዳቶች የሏቸውም፡፡ لَقَدْ كَفَرَ الَّذِينَ قَالُوا إِنَّ اللَّهَ هُوَ الْمَسِيحُ ابْنُ مَرْيَمَ ۖ وَقَالَ الْمَسِيحُ يَا بَنِي إِسْرَائِيلَ اعْبُدُوا اللَّهَ رَبِّي وَرَبَّكُمْ ۖ إِنَّهُ مَن يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ ۖ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنصَارٍ
እነዚያ «አላህ እርሱ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ነው» ያሉ በእርግጥ ካዱ፤ እነሆ ይህ ንግግራቸው ማጋራት ነውና አላህ በእርሱ ላይ የሚያጋራ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ፤ መኖሪያውም እሳት ናት፡፡ ይህ ጥቅላዊ መልእክት “ሙጅመል” مجمل ወይም “ዓም” عام ይባላል፤ ነገር ግን አላህ ከሙሽሪኪን አህለል ኪታቦችን በተናጥል “ሙፈሰል” مُفَصَّل ወይም “ኻስ” خاص በማድረግ ለያቸው፤ ይህም ሙሽሪኪን እና አህለል ኪታብ በሚሉ ቃላት መካከል “ወ” وَ ማለትም “እና” የሚል መስተጻምር አስቀምጧል፦
98፥1 *እነዚያ ከመጽሐፉ ባለቤቶች እና ከአጋሪዎቹም የካዱት ግልጹ አስረጅ እስከ መጣላቸው ድረስ ተወጋጆች አልነበሩም፡፡ لَمْ يَكُنِ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ وَالْمُشْرِكِينَ مُنفَكِّينَ حَتَّىٰ تَأْتِيَهُمُ الْبَيِّنَةُ
“በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ” የሚለው “ዓም” عام ሆኖ ከመጣ በኃላ “የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው” “ኻስ” خاص ሆኖ እንደመጣ ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ” ተናግሯል፦
ሱነን አቢ ዳውድ :መጽሐፍ 16, ሐዲስ 30
ኢብኑ ዐባሥ”ረ.ዐ” እንደተናገረው፦ 6፥118 “የአላህ ስም በእርሱ ላይ ከተወሳበት እንስሳ ብሉ” የሚለው አንቀጽ እና 6፥116 “በእርሱም ላይ የአላህ ስም ካልተጠራበት ነገር አትብሉ” የሚለው አንቀጽ ኢስቲስናዕ በመሆን “የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው” በሚለው ተነሥኻል” عَنِ ابْنِ عَبَّاسٍ، قَالَ { فَكُلُوا مِمَّا ذُكِرَ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ } { وَلاَ تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ } فَنُسِخَ وَاسْتَثْنَى مِنْ ذَلِكَ فَقَالَ { وَطَعَامُ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ حِلٌّ لَكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّ لَهُمْ } .
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ይህንን ሪዋያህ ሼኹል አልባኒ ሐሠን ነው ብለውቷል፤ “ወኢሥተስና” وَاسْتَثْنَى የሚለው ይሰመርበት፤ “ኢሥቲስናዕ” اِسْتِثْنَاء ማለት “ግድባዊ ቃል”Exceptional word” ነው፤ ከዚህ ሐዲስ የምረዳው አምላካችን አላህ ከጥቅላዊ መልእክት ተናጥሏዊ መልእክት ይህንን አንቀጽ ማውረዱ ነው፦
5፥5 ዛሬ መልካሞች ሁሉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ *የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው፡፡ ምግባችሁም ለእነሱ የተፈቀደ ነው*፡፡ ከምእመናት ጥብቆቹም *ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው*፡፡ ከእምነትም የሚመለስ ሰው በእርግጥ ሥራው ተበላሸ፡፡ በመጨረሻም ቀን እርሱ ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ ٱلْيَوْمَ أُحِلَّ لَكُمُ ٱلطَّيِّبَٰتُ ۖ وَطَعَامُ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ حِلٌّۭ لَّكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّۭ لَّهُمْ ۖ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلِكُمْ إِذَآ ءَاتَيْتُمُوهُنَّ أُجُورَهُنَّ مُحْصِنِينَ غَيْرَ مُسَٰفِحِينَ وَلَا مُتَّخِذِىٓ أَخْدَانٍۢ ۗ وَمَن يَكْفُرْ بِٱلْإِيمَٰنِ فَقَدْ حَبِطَ عَمَلُهُۥ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
አላህ ለሙስሊም ወንድ ከአህለል ኪታብ ሴትን የፈቀደበት ሂክማ ሴት በቀጥታ ሙስሊም ቤት ስለምትገባ ነው፤ በተቃራኒው ሴት ሙስሊም ወንድ ካፊርን ማግባት ያልፈቀደበት ሴቷ ሙስሊም ሙሽሪክ ቤት ስለምትገባ ነው።
ከላይ የተዘረዘረው ግንዛቤ የዐሊሞቻችን አንዱ እይታ”dimension” ነው፤
ስለ አህለል ኪታብ ሁለተኛው የዐሊሞቻችን እይታ” ደግሞ “ሢያቅ” سیاق ማለትም “አውዳዊ መልእክት”context” ነው። ይህንን እስቲ ነጥብ በነጥብ እንመልከት። ከሙሳ እና ዒሳ ተከታዮች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ ነገር ግን አላህ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጣቸው፤ በእነርሱ ላይ ቁርአን በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፤ እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን» ይላሉ፦
28፥52 እነዚያ ከእርሱ በፊት መጽሐፍን የሰጠናቸው እነርሱ *በእርሱ ያምናሉ*፡፡ الَّذِينَ آتَيْنَاهُمُ الْكِتَابَ مِن قَبْلِهِ هُم بِهِ يُؤْمِنُونَ
28፥53 በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፡፡ *እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን*» ይላሉ፡፡ وَإِذَا يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ قَالُوا آمَنَّا بِهِ إِنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّنَا إِنَّا كُنَّا مِن قَبْلِهِ مُسْلِمِينَ
ልብ አድርግ “እኛ ከእርሱ ማለትም ከቁርአን መውረድ በፊት ሙስሊም ነበርን” ማለታቸው ምክንያታዊ ነው፤ ሙስሊም” مُسْلِم ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው። እንደሚታወቀው ከመጽሐፉ ሰዎች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ አይሁዳውያን አላህ የተቆጣባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳቱተት ናቸው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3212
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ አይሁዳውያን የተቆጣባቸው ናቸው፤ ክርስቲያኖች የተሳቱተት ናቸው። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ الْيَهُودُ مَغْضُوبٌ عَلَيْهِمْ وَالنَّصَارَى ضُلاَّلٌ ” .
ነገር ግን ከአይሁዳውያን ጥቂት ያልተቆጣቸው፤ እንዲሁ ከክርስቲያኖች ጥቂት ያልተሳሳቱ ነበሩ፤ እኛም ከመንገዱ እንዳንስት የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋለላቸውን መንገድ ምራን ብለን እንቀራለን፦
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፣ በእነርሱ ላይ *”ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን”*፤ በሉ። صِرَٰطَ ٱلَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ ٱلْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا ٱلضَّآلِّينَ
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4475
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ “ኢማሙ፦ “ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን” ባለ ጊዜ አሚን በሉ፤ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” إِذَا قَالَ الإِمَامُ {غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلاَ الضَّالِّينَ} فَقُولُوا آمِينَ.
ስለዚህ ከመጽሐፉ ሰዎች በተውሒድ ያሉትን የኢስራኢል ልጆች እና ነሳራዎች ያረዱትን መብላትን እና በሃላል ሴቶቻቸውን ማግባት ተፈቅዷል፦
5፥5 ዛሬ መልካሞች ሁሉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ *የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው፡፡ ምግባችሁም ለእነሱ የተፈቀደ ነው*፡፡ ከምእመናት ጥብቆቹም *ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው*፡፡ ٱلْيَوْمَ أُحِلَّ لَكُمُ ٱلطَّيِّبَٰتُ ۖ وَطَعَامُ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ حِلٌّۭ لَّكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّۭ لَّهُمْ ۖ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلِكُمْ إِذَآ ءَاتَيْتُمُوهُنَّ أُجُورَهُنَّ مُحْصِنِينَ غَيْرَ مُسَٰفِحِينَ وَلَا مُتَّخِذِىٓ أَخْدَانٍۢ ۗ وَمَن يَكْفُرْ بِٱلْإِيمَٰنِ فَقَدْ حَبِطَ عَمَلُهُۥ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
“መጽሐፍን የተሰጡት” በሚለው ቃል መነሻ ቅጥያ ላይ “ሚን” مِنَ ማለትም “ከ” የሚል መስተዋድድ አለ፤ ያ የሚያሳየው ከአህለል ኪታብ መካከል ያሉትን ያላሻረኩ፣ የፍጡር ስም ሳይሆን የአላህን ስም ብቻ የሚጠሩ እና ከዝሙት ብልቶቻቸውን ጥብቆች የሆኑ ሴቶች ማግባት ሙባህ ነው። ይህ ሁለተኛው እይታ ነው። ሁለቱም እይታዎች ቁርኣናዊ ናቸው፤ መርጦ መቀበል የግል ምርጫ ነው።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
5፥5 ዛሬ መልካሞች ሁሉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ *የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው፡፡ ምግባችሁም ለእነሱ የተፈቀደ ነው*፡፡ ከምእመናት ጥብቆቹም *ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው*፡፡ ከእምነትም የሚመለስ ሰው በእርግጥ ሥራው ተበላሸ፡፡ በመጨረሻም ቀን እርሱ ከከሳሪዎቹ ነው፡፡ ٱلْيَوْمَ أُحِلَّ لَكُمُ ٱلطَّيِّبَٰتُ ۖ وَطَعَامُ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ حِلٌّۭ لَّكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّۭ لَّهُمْ ۖ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلِكُمْ إِذَآ ءَاتَيْتُمُوهُنَّ أُجُورَهُنَّ مُحْصِنِينَ غَيْرَ مُسَٰفِحِينَ وَلَا مُتَّخِذِىٓ أَخْدَانٍۢ ۗ وَمَن يَكْفُرْ بِٱلْإِيمَٰنِ فَقَدْ حَبِطَ عَمَلُهُۥ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
አላህ ለሙስሊም ወንድ ከአህለል ኪታብ ሴትን የፈቀደበት ሂክማ ሴት በቀጥታ ሙስሊም ቤት ስለምትገባ ነው፤ በተቃራኒው ሴት ሙስሊም ወንድ ካፊርን ማግባት ያልፈቀደበት ሴቷ ሙስሊም ሙሽሪክ ቤት ስለምትገባ ነው።
ከላይ የተዘረዘረው ግንዛቤ የዐሊሞቻችን አንዱ እይታ”dimension” ነው፤
ስለ አህለል ኪታብ ሁለተኛው የዐሊሞቻችን እይታ” ደግሞ “ሢያቅ” سیاق ማለትም “አውዳዊ መልእክት”context” ነው። ይህንን እስቲ ነጥብ በነጥብ እንመልከት። ከሙሳ እና ዒሳ ተከታዮች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ ነገር ግን አላህ ከእነርሱም ለእነዚያ ላመኑት ምንዳቸውን ሰጣቸው፤ በእነርሱ ላይ ቁርአን በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፤ እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን» ይላሉ፦
28፥52 እነዚያ ከእርሱ በፊት መጽሐፍን የሰጠናቸው እነርሱ *በእርሱ ያምናሉ*፡፡ الَّذِينَ آتَيْنَاهُمُ الْكِتَابَ مِن قَبْلِهِ هُم بِهِ يُؤْمِنُونَ
28፥53 በእነርሱ ላይ በሚነበብላቸውም ጊዜ «በእርሱ አምነናል፡፡ እርሱ ከጌታችን የኾነ እውነት ነው፡፡ *እኛ ከእርሱ በፊት ሙስሊሞች ነበርን*» ይላሉ፡፡ وَإِذَا يُتْلَىٰ عَلَيْهِمْ قَالُوا آمَنَّا بِهِ إِنَّهُ الْحَقُّ مِن رَّبِّنَا إِنَّا كُنَّا مِن قَبْلِهِ مُسْلِمِينَ
ልብ አድርግ “እኛ ከእርሱ ማለትም ከቁርአን መውረድ በፊት ሙስሊም ነበርን” ማለታቸው ምክንያታዊ ነው፤ ሙስሊም” مُسْلِم ትርጉሙ “አቢድ” عَابِدُ ማለትም “አምላኪ” አሊያም “ቃኒት” قَانِتِ ማለትም “ታዛዥ” ማለት ነው። እንደሚታወቀው ከመጽሐፉ ሰዎች ብዙዎቹ አመጸኞች ናቸው፤ አይሁዳውያን አላህ የተቆጣባቸው ሲሆኑ ክርስቲያኖች ደግሞ የተሳቱተት ናቸው፦
ጃምዒ አት-ተርሚዚ መጽሐፍ 47, ሐዲስ 3212
ዐዲይ ኢብኑ ሓቲም እንደተረከው ነብዩም”ﷺ” አሉ፦ አይሁዳውያን የተቆጣባቸው ናቸው፤ ክርስቲያኖች የተሳቱተት ናቸው። عَنْ عَدِيِّ بْنِ حَاتِمٍ، عَنِ النَّبِيِّ صلى الله عليه وسلم قَالَ “ الْيَهُودُ مَغْضُوبٌ عَلَيْهِمْ وَالنَّصَارَى ضُلاَّلٌ ” .
ነገር ግን ከአይሁዳውያን ጥቂት ያልተቆጣቸው፤ እንዲሁ ከክርስቲያኖች ጥቂት ያልተሳሳቱ ነበሩ፤ እኛም ከመንገዱ እንዳንስት የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋለላቸውን መንገድ ምራን ብለን እንቀራለን፦
1፥7 የእነዚያን በእነርሱ ላይ በጎ የዋልክላቸውን፣ በእነርሱ ላይ *”ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን”*፤ በሉ። صِرَٰطَ ٱلَّذِينَ أَنْعَمْتَ عَلَيْهِمْ غَيْرِ ٱلْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلَا ٱلضَّآلِّينَ
ኢማም ቡኻርይ : መጽሐፍ 65, ሐዲስ 4475
አቢ ሁረይራህ”ረ.ዐ.” እንደተረከው የአላህ መልእክተኛ”ﷺ” አሉ፦ “ኢማሙ፦ “ያልተቆጣህባቸውን እና ያልተሳሳቱትንም ሰዎች መንገድ ምራን” ባለ ጊዜ አሚን በሉ፤ عَنْ أَبِي هُرَيْرَةَ ـ رضى الله عنه ـ أَنَّ رَسُولَ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم قَالَ ” إِذَا قَالَ الإِمَامُ {غَيْرِ الْمَغْضُوبِ عَلَيْهِمْ وَلاَ الضَّالِّينَ} فَقُولُوا آمِينَ.
ስለዚህ ከመጽሐፉ ሰዎች በተውሒድ ያሉትን የኢስራኢል ልጆች እና ነሳራዎች ያረዱትን መብላትን እና በሃላል ሴቶቻቸውን ማግባት ተፈቅዷል፦
5፥5 ዛሬ መልካሞች ሁሉ ለእናንተ ተፈቀዱ፡፡ *የእነዚያም መጽሐፍን የተሰጡት ሰዎች ምግብ ያረዱት ለእናንተ የተፈቀደ ነው፡፡ ምግባችሁም ለእነሱ የተፈቀደ ነው*፡፡ ከምእመናት ጥብቆቹም *ከእነዚያ ከእናንተ በፊት መጽሐፍን ከተሰጡት ሴቶች ጥብቆቹም፤ ዘማዊዎችና የምስጢር ወዳጅ ያዢዎች ሳትኾኑ ጥብቆች ኾናችሁ መህሮቻቸውን በሰጣችኋቸው ጊዜ ልታገቡዋቸው የተፈቀዱ ናቸው*፡፡ ٱلْيَوْمَ أُحِلَّ لَكُمُ ٱلطَّيِّبَٰتُ ۖ وَطَعَامُ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ حِلٌّۭ لَّكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّۭ لَّهُمْ ۖ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلْمُؤْمِنَٰتِ وَٱلْمُحْصَنَٰتُ مِنَ ٱلَّذِينَ أُوتُوا۟ ٱلْكِتَٰبَ مِن قَبْلِكُمْ إِذَآ ءَاتَيْتُمُوهُنَّ أُجُورَهُنَّ مُحْصِنِينَ غَيْرَ مُسَٰفِحِينَ وَلَا مُتَّخِذِىٓ أَخْدَانٍۢ ۗ وَمَن يَكْفُرْ بِٱلْإِيمَٰنِ فَقَدْ حَبِطَ عَمَلُهُۥ وَهُوَ فِى ٱلْـَٔاخِرَةِ مِنَ ٱلْخَٰسِرِينَ
“መጽሐፍን የተሰጡት” በሚለው ቃል መነሻ ቅጥያ ላይ “ሚን” مِنَ ማለትም “ከ” የሚል መስተዋድድ አለ፤ ያ የሚያሳየው ከአህለል ኪታብ መካከል ያሉትን ያላሻረኩ፣ የፍጡር ስም ሳይሆን የአላህን ስም ብቻ የሚጠሩ እና ከዝሙት ብልቶቻቸውን ጥብቆች የሆኑ ሴቶች ማግባት ሙባህ ነው። ይህ ሁለተኛው እይታ ነው። ሁለቱም እይታዎች ቁርኣናዊ ናቸው፤ መርጦ መቀበል የግል ምርጫ ነው።
✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
ንግሥተ ሳባእ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
27፥22 ወፉ ዕሩቅ ያልኾነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ *ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ*፡፡ فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍۢ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِۦ وَجِئْتُكَ مِن سَبَإٍۭ بِنَبَإٍۢ يَقِينٍ
“ንግሥተ ሳባእ” ማለት በዕብራይስጥ “መለከት ሰባእ” מַלְכַּת־שְׁבָא ትባላለች፤ ትርጉሙም “የሳባ ንግሥት” ማለት ነው፤ ስለ ሳባ ንግሥት ከማየታችን በፊት ስለ ሳባ አገር እንመልከት፤ ሳባ የአብርሃም የልጅ ልጅ ነው፤ አብርሃም ኬጡራ የተባለች ሚስት አገባ፤ ከእርሷም ዮቅሳንን ወለደ፤ ዮቅሳን ሳባን ወለደ፦
ዘፍጥረት 25፥1-3 አብርሃምም ደግሞ ስምዋ ኬጡራ የተባለች ሚስት አገባ። እርስዋም ዘምራንን፥ ዮቅሳንን፥ ሜዳንን፥ ምድያምን፥ የስቦቅን፥ ስዌሕን ወለደችለት። ዮቅሳንም *ሳባን* እና ድዳንን ወለደ። የድዳንም ልጆች አሦርያውያን፥ ለጡሳውያን፥ ለኡማውያን ናቸው።
1ኛ ዜና መዋዕል 1፥32 የአብርሃምም ገረድ የኬጡራ ልጆች ዘምራን፥ ዮቅሳን፥ ሜዳን፥ ምድያም፥ የስቦቅ፥ ስዌሕ። *የዮቅሳንም ልጆች ሳባ፥ ድዳን*።
ከዛ በኃላ ከሳባ የተወለዱ ዝርያዎች ሳባውያን ይባላሉ፤ አገራቸውም ሳባ ትባላለች፤ የዚህች አገር ንግሥት የሰሎሞንን ዝና በሰማች ጊዜ በግመሎች ላይ ሽቱና ብዙ ወርቅ የከበረም ዕንቍ አስጭና ከታላቅ ጓዝ ጋር ሰሎሞንን በኢየሩሳሌም በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ መጣች፤ ንጉሡም ሰሎሞን፥ በገዛ እጁ ከሰጣት ሌላ፥ የወደደችውን ሁሉ ከእርሱም የለመነችውን ሁሉ ለሳባ ንግሥት ሰጣት እርስዋም ተመልሳ ከባሪያዎችዋ ጋር ወደ ምድርዋ ሄደች፦
1ኛ ነገሥት 10፥1 *የሳባም ንግሥት* በእግዚአብሔር ስም የወጣለትን የሰሎሞንን ዝና በሰማች ጊዜ በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ መጣች።
2ኛ ዜና መዋዕል 9፥1 *የሳባም ንግሥት የሰሎሞንን ዝና በሰማች ጊዜ በግመሎች ላይ ሽቱና ብዙ ወርቅ የከበረም ዕንቍ አስጭና ከታላቅ ጓዝ ጋር ሰሎሞንን በኢየሩሳሌም በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ መጣች*፤ ወደ ሰሎሞንም በገባች ጊዜ በልብዋ ያለውን ሁሉ አጫወተችው።
1ኛ ነገሥት 10፥13 ንጉሡም ሰሎሞን፥ በገዛ እጁ ከሰጣት ሌላ፥ የወደደችውን ሁሉ ከእርሱም *የለመነችውን ሁሉ ለሳባ ንግሥት ሰጣት እርስዋም ተመልሳ ከባሪያዎችዋ ጋር ወደ ምድርዋ ሄደች*።
ዳዊትም ስለ ልጁ ስለ ሰለሞን በሚናገርበት አንቀጽ ላይ የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ ብሏል፦
መዝሙር 72፥10 የተርሴስ እና የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ፤ የዓረብ እና *የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ*።
“ሳባ” ስለምትባለው አገር ለማወቅ ቀላል ነው፤ ኢሳይያስ ስለ እስራኤል በተናገረበት የዐውድ ፍሰት ላይ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ እና ሳባን የተለያዩ አገር ናቸው፦
ኢሳይያስ 43፥3 እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር መድኃኒትህ ነኝ፤ *ግብጽን ለአንተ ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያን እና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ*።
ኢሳይያስ 45፥14 እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ *የግብጽ ድካምና የኢትዮጵያ ንግድ ቁመተ ረጅሞችም የሳባ ሰዎች ወደ አንተ ያልፋሉ*፤
ሳባውያን በነጋዴነታቸው ይታወቃሉ፤ ሽቶ፣ የከበረ ድንጋይ፣ ወርቅ፣ እጣን ወዘተ ይነግዱ ነበር፦
ኢሳይያስ 60፥6 የግመሎች ብዛት፥ የምድያምና የጌፌር ግመሎች፥ ይሸፍኑሻል፤ *ሁሉ ከሳባ ይመጣሉ፥ ወርቅንና ዕጣንን ያመጣሉ* የእግዚአብሔርንም ምስጋና ያወራሉ።
ኢዮኤል 3፥8 እግዚአብሔር ተናግሮአልና ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁን በይሁዳ ልጆች እጅ እሸጣለሁ፥ እነርሱም ለሩቆቹ ሕዝብ *ለሳባ ሰዎች* ይሸጡአችኋል።
ሕዝቅኤል 27፥22 *የሳባ እና የራዕማ ነጋዴዎች እነዚህ ነጋዴዎችሽ ነበሩ*፤ በጥሩ ሽቶና በከበረ ድንጋይ ሁሉ በወርቅም ስለ አንቺ ሸቀጥ ይነግዱ ነበር።
ይህቺ ሳባ የምትባለው አገር የት ናት የሚለውን ለማወቅ አሁንም ጥናታችንን እንቀጥል፤ ቅድሚያ “አዜብ” ተብሎ የተቀመጠው በዕብራይስጥ “ኔጌብ” נֶ֫גֶב ሲሆን “ደቡብ” ማለት ነው፦
ሉቃስ 12፥55 *በአዜብም* ነፋስ ሲነፍስ፦ ትኩሳት ይሆናል ትላላችሁ፥ ይሆንማል።
1ኛ ነገሥት 7፥39 ኵሬውንም በቤቱ ቀኝ *በአዜብ* በኩል አኖረው።
ሳባ በእስራኤል በስተ ደቡብ የምትገኝ አገር ናት፤ አብርሃም የተጓዘበትና በእንግድነት የሄደበት ቦታ ነው፦
ዘፍጥረት 12፥9 አብራምም ከዚያ ተነሣ፥ እየተጓዘም ወደ *አዜብ* ሄደ።
ዘፍጥረት 13፥1 አብራምም ከግብፅ ወጣ፤ እርሱና ሚስቱ ለእርሱ የነበረውም ሁሉ ሎጥም ከእርሱ ጋር ወደ *አዜብ* ወጡ።
ይህ አዜብ የተባለው ቦታ በቃዴስና በሱር መካከል ያለ ቦታ ነው፦
ዘፍጥረት 20፥1 አብርሃምም ከዚያ ተነሥቶ *ወደ አዜብ ምድር ሄደ*፥ *በቃዴስ እና በሱር መካከልም ተቀመጠ* በጌራራም በእንግድነት ተቀመጠ።
ዘምዘም ማለትም መካ የሚገኘው ምንጭ በቃዴስ እና በባሬድ መካከል ሲሆን እዚህ ቦታ አብርሃም ምን እንዳደረገ ባይብል አይናገርም፦
ዘፍጥረት 16፥7 የእግዚአብሔር መልአክም በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት፤ *ምንጩም ወደ ሱር በምትወስደው መንገድ አጠገብ ነው*።
ዘፍጥረት 16፥14 ስለዚህም *የዚያ ጕድጓድ ስም ብኤርለሃይሮኢ* ተብሎ ተጠራ፤ እርሱም *በቃዴስ እና በባሬድ* መካከል ነው።
በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ሲና፣ ሴይር፣ ፋራን፣ ሳባ ወዘተ ናቸው፤ የሳባ ንግሥት የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከደቡብ መጥታለች፤ “ንግሥተ ዓዜብ” ማለት “የአዜብ ንግሥት” ወይም “የደቡብ ንግሥት” ማለት ነው፦
ማቴዎስ 12፥42 *ንግሥተ ዓዜብ* በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ *የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና*፥
ታዲያ ከእስራኤል በስተ ደቡብ ያለችዋ ሳባ የምትባለው አገር ማን ናት? ባይብል በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ካለን የታሪክ ምሁራን ደግሞ ሳባ ደቡባዊ የዐረብ ክፍል የሆነችው የመን ስለመሆኗ ቁልጭ አርገው በወርቃማ ብዕራቸው አስፍረዋል፤ ይህቺን የሳባ ንግሥት የመኖች “ቢልቂሥ” بلقيس ይሏታል፤ የእኛ አገር ሰዎች “ማክዳ” ይሏታል፤ ግራም ነፈሰ ቀኝ የባይብል፣ የግብጽ፣ የየመን፣ የአይሁድ ሆነ የዓለም ታሪክ ላይ ይህቺ ንግሥት የየመን ንግሥት እንደነበረች ያትታል፤ የኢትዮጵያ ንግሥት ነበረች የሚለው ዲቃላ ትረካ ሁሌም ሁሉ የእኔ በምትለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በተቀነባበረው በክብረ ነገሥት ላይ የተቀመጠ ትረካ ነው፤ ክብረ ነገሥት እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1225 AD ላይ በንቡረ እድ ይስሐቅ የተቀነባበረ ታሪክ ነው።
እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1270 AD ላይ የሰለሞን ስርወ-መንግሥት ተብሎ የሚጠራውን የመሰረተው ይኩኖ አምላክ ከ 900-1270 AD ላሊበላ ላይ ማእከል ያደረገውን የዛጉዌ ስርወ-መንግሥት ከገረሰሰ በኃላ ነው፤ ይኩኖ አምላክ በተክለ ሃይማኖት ትምህርት በማደጉ በዚህ ጊዜ ነው ንግሥት ሳባ የኢትዮጵያ ንግሥት ሆና ከንጉሥ ሰለሞን ጋር ተራክቦ አርጋ ቀዳማይ ሚኒሊክ የሚባል ልጅ ወልዳ እስከ 1974 AD ሀይለ ሥላሴ ድረስ ያሉት ነገሥታት “ንጉሠ ነገሥት” ማለትም “የነገሥታት ንጉሥ” እየተባሉ ከእነዚህ የነገሥታት ንጉሥ “ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ- ይሁዳ” ማለትም “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ይመጣል ተብሎ ይጠበቅ ነበር፦
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
27፥22 ወፉ ዕሩቅ ያልኾነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ *ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ*፡፡ فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍۢ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِۦ وَجِئْتُكَ مِن سَبَإٍۭ بِنَبَإٍۢ يَقِينٍ
“ንግሥተ ሳባእ” ማለት በዕብራይስጥ “መለከት ሰባእ” מַלְכַּת־שְׁבָא ትባላለች፤ ትርጉሙም “የሳባ ንግሥት” ማለት ነው፤ ስለ ሳባ ንግሥት ከማየታችን በፊት ስለ ሳባ አገር እንመልከት፤ ሳባ የአብርሃም የልጅ ልጅ ነው፤ አብርሃም ኬጡራ የተባለች ሚስት አገባ፤ ከእርሷም ዮቅሳንን ወለደ፤ ዮቅሳን ሳባን ወለደ፦
ዘፍጥረት 25፥1-3 አብርሃምም ደግሞ ስምዋ ኬጡራ የተባለች ሚስት አገባ። እርስዋም ዘምራንን፥ ዮቅሳንን፥ ሜዳንን፥ ምድያምን፥ የስቦቅን፥ ስዌሕን ወለደችለት። ዮቅሳንም *ሳባን* እና ድዳንን ወለደ። የድዳንም ልጆች አሦርያውያን፥ ለጡሳውያን፥ ለኡማውያን ናቸው።
1ኛ ዜና መዋዕል 1፥32 የአብርሃምም ገረድ የኬጡራ ልጆች ዘምራን፥ ዮቅሳን፥ ሜዳን፥ ምድያም፥ የስቦቅ፥ ስዌሕ። *የዮቅሳንም ልጆች ሳባ፥ ድዳን*።
ከዛ በኃላ ከሳባ የተወለዱ ዝርያዎች ሳባውያን ይባላሉ፤ አገራቸውም ሳባ ትባላለች፤ የዚህች አገር ንግሥት የሰሎሞንን ዝና በሰማች ጊዜ በግመሎች ላይ ሽቱና ብዙ ወርቅ የከበረም ዕንቍ አስጭና ከታላቅ ጓዝ ጋር ሰሎሞንን በኢየሩሳሌም በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ መጣች፤ ንጉሡም ሰሎሞን፥ በገዛ እጁ ከሰጣት ሌላ፥ የወደደችውን ሁሉ ከእርሱም የለመነችውን ሁሉ ለሳባ ንግሥት ሰጣት እርስዋም ተመልሳ ከባሪያዎችዋ ጋር ወደ ምድርዋ ሄደች፦
1ኛ ነገሥት 10፥1 *የሳባም ንግሥት* በእግዚአብሔር ስም የወጣለትን የሰሎሞንን ዝና በሰማች ጊዜ በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ መጣች።
2ኛ ዜና መዋዕል 9፥1 *የሳባም ንግሥት የሰሎሞንን ዝና በሰማች ጊዜ በግመሎች ላይ ሽቱና ብዙ ወርቅ የከበረም ዕንቍ አስጭና ከታላቅ ጓዝ ጋር ሰሎሞንን በኢየሩሳሌም በእንቆቅልሽ ትፈትነው ዘንድ መጣች*፤ ወደ ሰሎሞንም በገባች ጊዜ በልብዋ ያለውን ሁሉ አጫወተችው።
1ኛ ነገሥት 10፥13 ንጉሡም ሰሎሞን፥ በገዛ እጁ ከሰጣት ሌላ፥ የወደደችውን ሁሉ ከእርሱም *የለመነችውን ሁሉ ለሳባ ንግሥት ሰጣት እርስዋም ተመልሳ ከባሪያዎችዋ ጋር ወደ ምድርዋ ሄደች*።
ዳዊትም ስለ ልጁ ስለ ሰለሞን በሚናገርበት አንቀጽ ላይ የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ ብሏል፦
መዝሙር 72፥10 የተርሴስ እና የደሴቶች ነገሥታት ስጦታን ያመጣሉ፤ የዓረብ እና *የሳባ ነገሥታት እጅ መንሻን ያቀርባሉ*።
“ሳባ” ስለምትባለው አገር ለማወቅ ቀላል ነው፤ ኢሳይያስ ስለ እስራኤል በተናገረበት የዐውድ ፍሰት ላይ ግብጽ፣ ኢትዮጵያ፣ እና ሳባን የተለያዩ አገር ናቸው፦
ኢሳይያስ 43፥3 እኔ የእስራኤል ቅዱስ አምላክህ እግዚአብሔር መድኃኒትህ ነኝ፤ *ግብጽን ለአንተ ቤዛ አድርጌ፥ ኢትዮጵያን እና ሳባንም ለአንተ ፋንታ ሰጥቻለሁ*።
ኢሳይያስ 45፥14 እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ *የግብጽ ድካምና የኢትዮጵያ ንግድ ቁመተ ረጅሞችም የሳባ ሰዎች ወደ አንተ ያልፋሉ*፤
ሳባውያን በነጋዴነታቸው ይታወቃሉ፤ ሽቶ፣ የከበረ ድንጋይ፣ ወርቅ፣ እጣን ወዘተ ይነግዱ ነበር፦
ኢሳይያስ 60፥6 የግመሎች ብዛት፥ የምድያምና የጌፌር ግመሎች፥ ይሸፍኑሻል፤ *ሁሉ ከሳባ ይመጣሉ፥ ወርቅንና ዕጣንን ያመጣሉ* የእግዚአብሔርንም ምስጋና ያወራሉ።
ኢዮኤል 3፥8 እግዚአብሔር ተናግሮአልና ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁን በይሁዳ ልጆች እጅ እሸጣለሁ፥ እነርሱም ለሩቆቹ ሕዝብ *ለሳባ ሰዎች* ይሸጡአችኋል።
ሕዝቅኤል 27፥22 *የሳባ እና የራዕማ ነጋዴዎች እነዚህ ነጋዴዎችሽ ነበሩ*፤ በጥሩ ሽቶና በከበረ ድንጋይ ሁሉ በወርቅም ስለ አንቺ ሸቀጥ ይነግዱ ነበር።
ይህቺ ሳባ የምትባለው አገር የት ናት የሚለውን ለማወቅ አሁንም ጥናታችንን እንቀጥል፤ ቅድሚያ “አዜብ” ተብሎ የተቀመጠው በዕብራይስጥ “ኔጌብ” נֶ֫גֶב ሲሆን “ደቡብ” ማለት ነው፦
ሉቃስ 12፥55 *በአዜብም* ነፋስ ሲነፍስ፦ ትኩሳት ይሆናል ትላላችሁ፥ ይሆንማል።
1ኛ ነገሥት 7፥39 ኵሬውንም በቤቱ ቀኝ *በአዜብ* በኩል አኖረው።
ሳባ በእስራኤል በስተ ደቡብ የምትገኝ አገር ናት፤ አብርሃም የተጓዘበትና በእንግድነት የሄደበት ቦታ ነው፦
ዘፍጥረት 12፥9 አብራምም ከዚያ ተነሣ፥ እየተጓዘም ወደ *አዜብ* ሄደ።
ዘፍጥረት 13፥1 አብራምም ከግብፅ ወጣ፤ እርሱና ሚስቱ ለእርሱ የነበረውም ሁሉ ሎጥም ከእርሱ ጋር ወደ *አዜብ* ወጡ።
ይህ አዜብ የተባለው ቦታ በቃዴስና በሱር መካከል ያለ ቦታ ነው፦
ዘፍጥረት 20፥1 አብርሃምም ከዚያ ተነሥቶ *ወደ አዜብ ምድር ሄደ*፥ *በቃዴስ እና በሱር መካከልም ተቀመጠ* በጌራራም በእንግድነት ተቀመጠ።
ዘምዘም ማለትም መካ የሚገኘው ምንጭ በቃዴስ እና በባሬድ መካከል ሲሆን እዚህ ቦታ አብርሃም ምን እንዳደረገ ባይብል አይናገርም፦
ዘፍጥረት 16፥7 የእግዚአብሔር መልአክም በውኃ ምንጭ አጠገብ በበረሀ አገኛት፤ *ምንጩም ወደ ሱር በምትወስደው መንገድ አጠገብ ነው*።
ዘፍጥረት 16፥14 ስለዚህም *የዚያ ጕድጓድ ስም ብኤርለሃይሮኢ* ተብሎ ተጠራ፤ እርሱም *በቃዴስ እና በባሬድ* መካከል ነው።
በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ሲና፣ ሴይር፣ ፋራን፣ ሳባ ወዘተ ናቸው፤ የሳባ ንግሥት የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከደቡብ መጥታለች፤ “ንግሥተ ዓዜብ” ማለት “የአዜብ ንግሥት” ወይም “የደቡብ ንግሥት” ማለት ነው፦
ማቴዎስ 12፥42 *ንግሥተ ዓዜብ* በፍርድ ቀን ከዚህ ትውልድ ጋር ተነሥታ ትፈርድበታለች፤ *የሰሎሞንን ጥበብ ለመስማት ከምድር ዳር መጥታለችና*፥
ታዲያ ከእስራኤል በስተ ደቡብ ያለችዋ ሳባ የምትባለው አገር ማን ናት? ባይብል በቃዴስ እና በሱር መካከል ያለው ቦታ ካለን የታሪክ ምሁራን ደግሞ ሳባ ደቡባዊ የዐረብ ክፍል የሆነችው የመን ስለመሆኗ ቁልጭ አርገው በወርቃማ ብዕራቸው አስፍረዋል፤ ይህቺን የሳባ ንግሥት የመኖች “ቢልቂሥ” بلقيس ይሏታል፤ የእኛ አገር ሰዎች “ማክዳ” ይሏታል፤ ግራም ነፈሰ ቀኝ የባይብል፣ የግብጽ፣ የየመን፣ የአይሁድ ሆነ የዓለም ታሪክ ላይ ይህቺ ንግሥት የየመን ንግሥት እንደነበረች ያትታል፤ የኢትዮጵያ ንግሥት ነበረች የሚለው ዲቃላ ትረካ ሁሌም ሁሉ የእኔ በምትለው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በተቀነባበረው በክብረ ነገሥት ላይ የተቀመጠ ትረካ ነው፤ ክብረ ነገሥት እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1225 AD ላይ በንቡረ እድ ይስሐቅ የተቀነባበረ ታሪክ ነው።
እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር 1270 AD ላይ የሰለሞን ስርወ-መንግሥት ተብሎ የሚጠራውን የመሰረተው ይኩኖ አምላክ ከ 900-1270 AD ላሊበላ ላይ ማእከል ያደረገውን የዛጉዌ ስርወ-መንግሥት ከገረሰሰ በኃላ ነው፤ ይኩኖ አምላክ በተክለ ሃይማኖት ትምህርት በማደጉ በዚህ ጊዜ ነው ንግሥት ሳባ የኢትዮጵያ ንግሥት ሆና ከንጉሥ ሰለሞን ጋር ተራክቦ አርጋ ቀዳማይ ሚኒሊክ የሚባል ልጅ ወልዳ እስከ 1974 AD ሀይለ ሥላሴ ድረስ ያሉት ነገሥታት “ንጉሠ ነገሥት” ማለትም “የነገሥታት ንጉሥ” እየተባሉ ከእነዚህ የነገሥታት ንጉሥ “ሞዓ አንበሳ ዘእምነገደ- ይሁዳ” ማለትም “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ይመጣል ተብሎ ይጠበቅ ነበር፦
ዘፍጥረት 49፥9-10 ይሁዳ የአንበሳ ደቦል ነው፤ ልጄ ሆይ፥ ከአደንህ ወጣህ፤ እንደ አንበሳ አሸመቀ፥ እንደ ሴት አንበሳም አደባ፤ ያስነሣውስ ዘንድ ማን ይችላል? በትረ መንግሥት ከይሁዳ አይጠፋም፥ የገዥም ዘንግ ከእግሮቹ መካከል፥ ገዥ የሆነው እስኪመጣ ድረስ፤ የአሕዛብ መታዘዝም ለእርሱ ይሆናል።
“ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ግን መሲሑ እንደሆነ ቅቡል ቢሆንም ቅሉ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር እና ንጉሠ ነገሥት” ሆነው ተሹመዋል፦
ራእይ 5፥5 ከሽማግሌዎቹም አንዱ፦ አታልቅስ፤ እነሆ፥ *ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ* እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል፡ አለኝ።
ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ መሲሑ ኢየሱስ ሆኖ ሳለ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር”፣ “ንጉሠ ነገሥት” እና “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ለምን ማለትስ አስፈለገ? ዛሬ ለራስተፈሪያን እምነት መመስረት ተጠያቂዎቹ የክብረ ነገስት ጸሐፊ፣ ይኩኖ አምላክ እና ተክለ ሃይማኖት ናቸው።
ቁርአን የአምላካችን የአላህ ንግግር ነው፤ ከነብያችን”ﷺ” በፊት ያለው ድርጊት “አል-ገይቡል ማዲ” الغيبه المادي ሲሆን ያለፈ ክስተት ነው፤ ይህም ድርጊቱ ከዚህ በፊት አላፊ የሆነ ነገር ነው፤ ከፍጡራን በፊት ያሉትን የሩቅ ወሬዎች አላህ ብቻ ነው በትክክል የሚያውቃቸው፤ አላህ ይህንን የሩቅ ወሬ “ነቁስሱ አለይከ” نَقُصُّ عَلَيْكَ “እንተርክልሃለን” በማለት ለነብያችን”ﷺ” ይናገራል፦
11:120 ከመልክተኞቹም “ወሬዎች” ተፈላጊውን ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን “*እንተርክልሃለን*፤ በዚህችም እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّۭا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ ٱلرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِۦ فُؤَادَكَ ۚ وَجَآءَكَ فِى هَٰذِهِ ٱلْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌۭ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ
አላህ ለነብያችን”ﷺ” የሚተርክበት ምክንያት ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ ነው እንጂ እከሌ እከሌን ወለደ ብሎ የሚናገር የቀበሌ አሊያም የእድር መዝገብ አይደለም፤ እኛ እንድንማርበት ከተረከን አንዱ የሰበእ ማለትም የሳባ ንግሥት ታሪክ ነው፤ ይህም በሱረቱል ነምል 27፥22-44 ላይ አለ፦
27፥22 ወፉ ዕሩቅ ያልኾነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ *ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ*፡፡ فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍۢ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِۦ وَجِئْتُكَ مِن سَبَإٍۭ بِنَبَإٍۢ يَقِينٍ
27፥23 «እኔ የምትገዛቸው የኾኑችን ሴት ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችኝ አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡ إِنِّى وَجَدتُّ ٱمْرَأَةًۭ تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِن كُلِّ شَىْءٍۢ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌۭ
አላህ ስለ ሳቢያን ህዝቦች በረከትና ቅጣት በሱረቱል ሰበእ 34፥15-20 ነግሮናል፤ በተጨማሪም ሳቢያን በአላህ እና በመጨረሻው ቀን አምነው መልካም ከሰሩ መልካም ምንዳ እንዳላቸው እና በመጨረሻው ቀን በእነርሱ መካከል እንደሚፈርድ ተናግሯል፦
34፥15 *ለሰበእ በመኖሪያቸው በእውነት አስደናቂ ምልክት ነበራቸው*፡፡ ከግራና ከቀኝ ሁለት አትክልቶች ነበሯቸው፡፡ «ከጌታችሁ ሲሳይ ብሉ፡፡ ለእርሱም አመስግኑ፡፡ አገራችሁ ውብ አገር ናት፡፡ ጌታችሁ መሓሪ ጌታም ነው» ተባሉ፡፡ لَقَدْ كَانَ لِسَبَإٍۢ فِى مَسْكَنِهِمْ ءَايَةٌۭ ۖ جَنَّتَانِ عَن يَمِينٍۢ وَشِمَالٍۢ ۖ كُلُوا۟ مِن رِّزْقِ رَبِّكُمْ وَٱشْكُرُوا۟ لَهُۥ ۚ بَلْدَةٌۭ طَيِّبَةٌۭ وَرَبٌّ غَفُورٌۭ
2፥62 እነዚያ ያመኑ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ፣ ክርስቲያኖችም፣ *ሳቢያኖችም ከእነርሱ በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው*፡፡ በነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالنَّصَارَىٰ وَالصَّابِئِينَ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَعَمِلَ صَالِحًا فَلَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
22፥17 እነዚያ ያመኑት፣ እነዚያም ይሁዳውያን *ሳቢያኖችም*፣ ክርስቲያኖችም፣ መጁሶችም እነዚያም ያጋሩ *አላህ በትንሣኤ ቀን በመካከላቸው በፍርድ ይለያል*፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ በእርግጥ ዐዋቂ ነውና፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالصَّابِئِينَ وَالنَّصَارَىٰ وَالْمَجُوسَ وَالَّذِينَ أَشْرَكُوا إِنَّ اللَّهَ يَفْصِلُ بَيْنَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ
✍️ በኡሥታዝወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen
ቴሌግራም ፦ https://www.tg-me.com/tiriyachen
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/tiriyachen?mibextid=ZbWKwL
ወሰላሙ አለይኩም
“ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ግን መሲሑ እንደሆነ ቅቡል ቢሆንም ቅሉ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር እና ንጉሠ ነገሥት” ሆነው ተሹመዋል፦
ራእይ 5፥5 ከሽማግሌዎቹም አንዱ፦ አታልቅስ፤ እነሆ፥ *ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ* እርሱም የዳዊት ሥር መጽሐፉን ይዘረጋ ዘንድ ሰባቱንም ማኅተም ይፈታ ዘንድ ድል ነሥቶአል፡ አለኝ።
ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ መሲሑ ኢየሱስ ሆኖ ሳለ ግን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሥዩመ እግዚአብሔር”፣ “ንጉሠ ነገሥት” እና “ከይሁዳ ነገድ የሚሆነው አንበሳ” ለምን ማለትስ አስፈለገ? ዛሬ ለራስተፈሪያን እምነት መመስረት ተጠያቂዎቹ የክብረ ነገስት ጸሐፊ፣ ይኩኖ አምላክ እና ተክለ ሃይማኖት ናቸው።
ቁርአን የአምላካችን የአላህ ንግግር ነው፤ ከነብያችን”ﷺ” በፊት ያለው ድርጊት “አል-ገይቡል ማዲ” الغيبه المادي ሲሆን ያለፈ ክስተት ነው፤ ይህም ድርጊቱ ከዚህ በፊት አላፊ የሆነ ነገር ነው፤ ከፍጡራን በፊት ያሉትን የሩቅ ወሬዎች አላህ ብቻ ነው በትክክል የሚያውቃቸው፤ አላህ ይህንን የሩቅ ወሬ “ነቁስሱ አለይከ” نَقُصُّ عَلَيْكَ “እንተርክልሃለን” በማለት ለነብያችን”ﷺ” ይናገራል፦
11:120 ከመልክተኞቹም “ወሬዎች” ተፈላጊውን ሁሉንም ልብህን በእርሱ የምናረካበትን “*እንተርክልሃለን*፤ በዚህችም እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡ وَكُلًّۭا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ ٱلرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِۦ فُؤَادَكَ ۚ وَجَآءَكَ فِى هَٰذِهِ ٱلْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌۭ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ
አላህ ለነብያችን”ﷺ” የሚተርክበት ምክንያት ለምእምናን ግሳጼ እና ማስታወሻ ነው እንጂ እከሌ እከሌን ወለደ ብሎ የሚናገር የቀበሌ አሊያም የእድር መዝገብ አይደለም፤ እኛ እንድንማርበት ከተረከን አንዱ የሰበእ ማለትም የሳባ ንግሥት ታሪክ ነው፤ ይህም በሱረቱል ነምል 27፥22-44 ላይ አለ፦
27፥22 ወፉ ዕሩቅ ያልኾነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም «ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ *ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ*፡፡ فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍۢ فَقَالَ أَحَطتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِۦ وَجِئْتُكَ مِن سَبَإٍۭ بِنَبَإٍۢ يَقِينٍ
27፥23 «እኔ የምትገዛቸው የኾኑችን ሴት ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችኝ አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡ إِنِّى وَجَدتُّ ٱمْرَأَةًۭ تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِن كُلِّ شَىْءٍۢ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌۭ
አላህ ስለ ሳቢያን ህዝቦች በረከትና ቅጣት በሱረቱል ሰበእ 34፥15-20 ነግሮናል፤ በተጨማሪም ሳቢያን በአላህ እና በመጨረሻው ቀን አምነው መልካም ከሰሩ መልካም ምንዳ እንዳላቸው እና በመጨረሻው ቀን በእነርሱ መካከል እንደሚፈርድ ተናግሯል፦
34፥15 *ለሰበእ በመኖሪያቸው በእውነት አስደናቂ ምልክት ነበራቸው*፡፡ ከግራና ከቀኝ ሁለት አትክልቶች ነበሯቸው፡፡ «ከጌታችሁ ሲሳይ ብሉ፡፡ ለእርሱም አመስግኑ፡፡ አገራችሁ ውብ አገር ናት፡፡ ጌታችሁ መሓሪ ጌታም ነው» ተባሉ፡፡ لَقَدْ كَانَ لِسَبَإٍۢ فِى مَسْكَنِهِمْ ءَايَةٌۭ ۖ جَنَّتَانِ عَن يَمِينٍۢ وَشِمَالٍۢ ۖ كُلُوا۟ مِن رِّزْقِ رَبِّكُمْ وَٱشْكُرُوا۟ لَهُۥ ۚ بَلْدَةٌۭ طَيِّبَةٌۭ وَرَبٌّ غَفُورٌۭ
2፥62 እነዚያ ያመኑ እነዚያም ይሁዳውያን የኾኑ፣ ክርስቲያኖችም፣ *ሳቢያኖችም ከእነርሱ በአላህና በመጨረሻው ቀን ያመነ መልካምንም ሥራ የሠራ ለነርሱ በጌታቸው ዘንድ ምንዳቸው አላቸው*፡፡ በነርሱም ላይ ፍርሃት የለባቸውም፤ እነሱም አያዝኑም፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالنَّصَارَىٰ وَالصَّابِئِينَ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَعَمِلَ صَالِحًا فَلَهُمْ أَجْرُهُمْ عِندَ رَبِّهِمْ وَلَا خَوْفٌ عَلَيْهِمْ وَلَا هُمْ يَحْزَنُونَ
22፥17 እነዚያ ያመኑት፣ እነዚያም ይሁዳውያን *ሳቢያኖችም*፣ ክርስቲያኖችም፣ መጁሶችም እነዚያም ያጋሩ *አላህ በትንሣኤ ቀን በመካከላቸው በፍርድ ይለያል*፡፡ አላህ በነገሩ ሁሉ ላይ በእርግጥ ዐዋቂ ነውና፡፡ إِنَّ الَّذِينَ آمَنُوا وَالَّذِينَ هَادُوا وَالصَّابِئِينَ وَالنَّصَارَىٰ وَالْمَجُوسَ وَالَّذِينَ أَشْرَكُوا إِنَّ اللَّهَ يَفْصِلُ بَيْنَهُمْ يَوْمَ الْقِيَامَةِ ۚ إِنَّ اللَّهَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ شَهِيدٌ
✍️ በኡሥታዝወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
የበለጠ ለማወቅ
ጥሪያችን Tiriyachen
ቴሌግራም ፦ https://www.tg-me.com/tiriyachen
ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/tiriyachen?mibextid=ZbWKwL
ወሰላሙ አለይኩም
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
መስቀል
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
“ሡጁድ” سُّجُود የሚለው ቃል የዐረቢኛው ቃል“ሠጀደ” سَجَدَ ማለት “ሰገደ” ወይም “ታዘዘ” ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን “ስግደት” ወይም “መታዘዝ” ማለት ነው፤ ሡጁድ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፦ አንዱ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ሲሆን ሌላው “ሡጁዱ አተሒያ” سُّجُود التحيه ማለትም “የአክብሮት ስግደት” ነው፤ ነገር ግን ይህ አክብሮት አቅጣጫውን ቀይሮ አምልኮ እየሆነ ስላለ ከሰላምታ ውጪ በሱጁድ ለፍጡራን ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ ቁርአን ሲወርድ ቆሟል፤ የአክብሮት ስግደት ከአምልኮ ስግደት ጋር እንዳይደባለቅ የተከለከለው በነብያችን”ﷺ” ጊዜ ነው፤ አላህም ሁሉን ለፈጠረው ለእርሱ እንጂ ለሌላ አትስገዱ ብሎናል፤ ከአላህ ሌላ የሚገዙት ግኡዛን ነገር የገሀነም ማገዶዎች ናቸው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
21፥8 እናንተ ከአላህ ሌላ የምትገዟቸውም የገሀነም ማገዶዎች ናችሁ፡፡ እናንተ ለእርሷ ወራጆች ናችሁ إِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ حَصَبُ جَهَنَّمَ أَنتُمْ لَهَا وَٰرِدُونَ ፡፡
ማገዶዎች በሚለው ቃላት “ማ” َمَا የሚለው አንፃራዊ ተውላጠ-ስም አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ አቅል ያላቸውን ማንነቶች “መን” مَّن የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም የሚጠቀመው፤ ግን እዚህ አንቀፅ ላይ “ማ” የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም መጠቀሙ አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ይባላል፤ ይህም ጣዖት በሁለት ይከፈላል፤ አንዱ “አውሳን” أَوْثَٰن ሲሆን ሁለተኛው “አስናም” أَصْنَام ነው፤ “አውሳን” ማለት ከድንጋይ ተቀርፀው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ሲሆን፤ “አስናም” ደግሞ ከእንጨት፣ ብር፣ ነሐስ ተሰርተው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ነው፤ እነዚህ ሁለቱም በቁርአን ተጠቅሰዋል፦
1.”አውሳን”
29:17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት “ጣዖታትን” أَوْثَانًا ብቻ ነው፤ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፤ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኩአቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፤
2. “አስናም”
6:74 ኢብራሒምም ለአባቱ ለአዘር “ጣዖታትን” أَصْنَامًا አማልክት አድርገህ ትይዛለህን እኔ አንተንም ሕዝቦችህንም በግልጽ መሳሳት ውስጥ ኾናችሁ አያችኋለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ።
ወደ ባይብል ስንመጣ “ስግደት” የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሻቻህ” שָׁחָה ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ፕሮስካኒኦ” προσκυνέω ይባላል፤ ይህም ለተለያየ ምንነት ሆነ ማንነት በኒያ”intention” የሚቀርብ አምልኮን”Adoration” ወይም አክብሮትን”prostration” ነው ለማመልከት በባይብል ተጠቅሞበታል፤ የአምልኮት ስግደት በባህርይ የአንድ አምላክ ሃቅና ገንዘብ ሲሆን የአክብሮት ስግደት ደግሞ በፀጋ ለህያዋን ማንነት ማክበርን ያመለክታል፤ ግን ለግኡዛን ነገሮች አምልኮም ይሁን ስግደት ተከልክሏል፤ በዕብራይስጥ “ኤሊል” אֱלִיל ማለት “ምስል”፣ “ቅርፅ”፣ “ጣዖት” ማለት ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ኤዶሎን” εἴδωλον ነው፤ ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው። የሙሴ አምላክ ለሙሴ “”ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፣ የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”” ብሎ ተናግሯል፤ እንደውም ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ ይላል፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ *”ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ”*፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር *”የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”*፤
መዝሙር 97፥7 *”ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ*”፤ መላእክቱ ሁሉ ስገዱለት።
ታዲያ ነጥብህ ምንድን ነው? ከመስቀል ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለ? ትሉ ይሆናል፤ መስቀል እኮ በሃውልት ድንጋይ፣ እንጨት፣ ወርቅ፣ ብር፣ ብረት፣ ነሐስ ወዘተ ነው፤ ይህ ግኡዝ ነገር በአበይት ክርስቲያኖች ይሰገድለታል ምስጋና ይቀርበለታል፤ ይህ በተግባር ሲሆን በጽሑፍ የዘወትር ፀሎት ላይ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፦
ግዕዙ፦
“እሰግድ “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር”
ትርጉም፦
“ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”ተሰቀለበት መስቀል እሰግዳለው”
ግዕዙ፦
“ስብሐት “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በምህረቱ ይዘከረነ”
ትርጉም፦
” “ለ”ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምስጋና ይገባዋል”
ምን ትፈልጋለህ? “ለ”ተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ እየተባለ ለምንድን ነው ለግኡዝ ነገር የፀጋ ስግደት የሚሰገድለት? ምስጋናስ የሚቅብለት የሚሰማበት ዐቅል የት አለውና ነው? መስቀል መሳለም ሆነ በመስቀል ማሳለም የትኛው ነብይና ሃዋርያ አደረገስ አድርጉስ አለ? እኔስ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ትዝ አለኝ፦
ኢሳይያስ 44፥15-19 ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። ግማሹን በእሳት ያቃጥላል፥ በዚያ በግማሹ ሥጋ ይበላል፥ ሥጋም ይጠብስበትና ይጠግባል፤ ይሞቃልና፦ እሰይ ሞቅሁ፥ እሳቱን አይቻለሁ ይላል። የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። በልቡም ማንም አያስብም፦ ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም።
ከአላህ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱምና ወደ አላህ በንስሃ ተመለሱ፦
7፥197 እነዚያም ከእርሱ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱም وَٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِهِۦ لَا يَسْتَطِيعُونَ نَصْرَكُمْ وَلَآ أَنفُسَهُمْ يَنصُرُونَ ፡፡
✍ ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው፡፡
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
“ሡጁድ” سُّجُود የሚለው ቃል የዐረቢኛው ቃል“ሠጀደ” سَجَدَ ማለት “ሰገደ” ወይም “ታዘዘ” ከሚል ግስ የተገኘ ሲሆን “ስግደት” ወይም “መታዘዝ” ማለት ነው፤ ሡጁድ ደግሞ በሁለት ይከፈላል፦ አንዱ “ሡጁዱል ዒባዳ” سُّجُود العبادة ማለትም “የአምልኮ ስግደት” ሲሆን ሌላው “ሡጁዱ አተሒያ” سُّجُود التحيه ማለትም “የአክብሮት ስግደት” ነው፤ ነገር ግን ይህ አክብሮት አቅጣጫውን ቀይሮ አምልኮ እየሆነ ስላለ ከሰላምታ ውጪ በሱጁድ ለፍጡራን ማጎብደድ፣ መተናነስ፣ ማሸርገድ ቁርአን ሲወርድ ቆሟል፤ የአክብሮት ስግደት ከአምልኮ ስግደት ጋር እንዳይደባለቅ የተከለከለው በነብያችን”ﷺ” ጊዜ ነው፤ አላህም ሁሉን ለፈጠረው ለእርሱ እንጂ ለሌላ አትስገዱ ብሎናል፤ ከአላህ ሌላ የሚገዙት ግኡዛን ነገር የገሀነም ማገዶዎች ናቸው፦
41፥37 ሌሊትና ቀንም ፀሐይና ጨረቃም ከምልክቶቹ ናቸው፡፡ ለፀሐይና ለጨረቃ “አትስገዱ”፡፡ ለእዚያም ለፈጠራቸው አላህ “ስገዱ” ፡፡ እርሱን ብቻ “የምታመልኩ” እንደ ኾናችሁ *”ለሌላ አትስገዱ”*፡፡
21፥8 እናንተ ከአላህ ሌላ የምትገዟቸውም የገሀነም ማገዶዎች ናችሁ፡፡ እናንተ ለእርሷ ወራጆች ናችሁ إِنَّكُمْ وَمَا تَعْبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ حَصَبُ جَهَنَّمَ أَنتُمْ لَهَا وَٰرِدُونَ ፡፡
ማገዶዎች በሚለው ቃላት “ማ” َمَا የሚለው አንፃራዊ ተውላጠ-ስም አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ አቅል ያላቸውን ማንነቶች “መን” مَّن የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም የሚጠቀመው፤ ግን እዚህ አንቀፅ ላይ “ማ” የሚል አንፃራዊ ተውላጠ-ስም መጠቀሙ አቅል የሌላቸውን ጣኦታት ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ነው፤ ከአላህ ውጪ የሚደረግ ባዕድ አምልኮ “ጣጉት” لطَّاغُوتِ ይባላል፤ ይህም ጣዖት በሁለት ይከፈላል፤ አንዱ “አውሳን” أَوْثَٰن ሲሆን ሁለተኛው “አስናም” أَصْنَام ነው፤ “አውሳን” ማለት ከድንጋይ ተቀርፀው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ሲሆን፤ “አስናም” ደግሞ ከእንጨት፣ ብር፣ ነሐስ ተሰርተው አምልኮ ለሚቀርብላቸው ነው፤ እነዚህ ሁለቱም በቁርአን ተጠቅሰዋል፦
1.”አውሳን”
29:17 ከአላህ ሌላ የምታመልኩት “ጣዖታትን” أَوْثَانًا ብቻ ነው፤ ውሸትንም ትቀጣጥፋላችሁ፤ እነዚያ ከአላህ ሌላ የምታመልኩአቸው ለእናንተ ሲሳይን ሊሰጧችሁ አይችሉም፤
2. “አስናም”
6:74 ኢብራሒምም ለአባቱ ለአዘር “ጣዖታትን” أَصْنَامًا አማልክት አድርገህ ትይዛለህን እኔ አንተንም ሕዝቦችህንም በግልጽ መሳሳት ውስጥ ኾናችሁ አያችኋለሁ» ባለ ጊዜ አስታውስ።
ወደ ባይብል ስንመጣ “ስግደት” የሚለው ቃል በዕብራይስጥ “ሻቻህ” שָׁחָה ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ፕሮስካኒኦ” προσκυνέω ይባላል፤ ይህም ለተለያየ ምንነት ሆነ ማንነት በኒያ”intention” የሚቀርብ አምልኮን”Adoration” ወይም አክብሮትን”prostration” ነው ለማመልከት በባይብል ተጠቅሞበታል፤ የአምልኮት ስግደት በባህርይ የአንድ አምላክ ሃቅና ገንዘብ ሲሆን የአክብሮት ስግደት ደግሞ በፀጋ ለህያዋን ማንነት ማክበርን ያመለክታል፤ ግን ለግኡዛን ነገሮች አምልኮም ይሁን ስግደት ተከልክሏል፤ በዕብራይስጥ “ኤሊል” אֱלִיל ማለት “ምስል”፣ “ቅርፅ”፣ “ጣዖት” ማለት ሲሆን በግሪክ ደግሞ “ኤዶሎን” εἴδωλον ነው፤ ትርጉሙ ተመሳሳይ ነው። የሙሴ አምላክ ለሙሴ “”ለእናንተ ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ፣ የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፣ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”” ብሎ ተናግሯል፤ እንደውም ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ ይላል፦
ዘሌዋውያን 26፥1 እኔ ያህዌህ አምላካችሁ ነኝና ለእናንተ *”ጣዖት አታድርጉ፥ የተቀረጸም ምስል ወይም ሐውልት አታቁሙ”*፤ ትሰግዱለትም ዘንድ በምድራችሁ ላይ የተቀረጸ ድንጋይ አታኑሩ።
ዘጸአት 20፥4 በላይ በሰማይ ካለው፥ በታችም በምድር ካለው፥ ከምድርም በታች በውኃ ካለው ነገር *”የማናቸውንም ምሳሌ፥ የተቀረጸውንም ምስል ለአንተ አታድርግ፤ አትስገድላቸው፥ አታምልካቸውምም”*፤
መዝሙር 97፥7 *”ለተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ፥ በጣዖቶቻቸውም የሚመኩ ይፈሩ*”፤ መላእክቱ ሁሉ ስገዱለት።
ታዲያ ነጥብህ ምንድን ነው? ከመስቀል ጋር ምን የሚያገናኘው ነገር አለ? ትሉ ይሆናል፤ መስቀል እኮ በሃውልት ድንጋይ፣ እንጨት፣ ወርቅ፣ ብር፣ ብረት፣ ነሐስ ወዘተ ነው፤ ይህ ግኡዝ ነገር በአበይት ክርስቲያኖች ይሰገድለታል ምስጋና ይቀርበለታል፤ ይህ በተግባር ሲሆን በጽሑፍ የዘወትር ፀሎት ላይ ደግሞ እንዲህ ይነበባል፦
ግዕዙ፦
“እሰግድ “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘተቀደሰ በደሙ ክቡር”
ትርጉም፦
“ዓለምን ለማዳን ሲል ኢየሱስ ክርስቶስ “ለ”ተሰቀለበት መስቀል እሰግዳለው”
ግዕዙ፦
“ስብሐት “ለ”መስቀለ እግዚእነ ኢየሱስ ክርስቶስ በምህረቱ ይዘከረነ”
ትርጉም፦
” “ለ”ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ምስጋና ይገባዋል”
ምን ትፈልጋለህ? “ለ”ተቀረጸ ምስል የሚሰግዱ ሁሉ ይፈሩ እየተባለ ለምንድን ነው ለግኡዝ ነገር የፀጋ ስግደት የሚሰገድለት? ምስጋናስ የሚቅብለት የሚሰማበት ዐቅል የት አለውና ነው? መስቀል መሳለም ሆነ በመስቀል ማሳለም የትኛው ነብይና ሃዋርያ አደረገስ አድርጉስ አለ? እኔስ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ትዝ አለኝ፦
ኢሳይያስ 44፥15-19 ለሰውም ማገዶ ይሆናል፤ ከእርሱም ወስዶ ይሞቃል፥ አንድዶም እንጀራ ይጋግርበታል፤ ከእርሱም አምላክ አበጅቶ ይሰግድለታል፥ የተቀረጸውንም ምስል ሠርቶ በእርሱ ፊት ይንበረከካል። ግማሹን በእሳት ያቃጥላል፥ በዚያ በግማሹ ሥጋ ይበላል፥ ሥጋም ይጠብስበትና ይጠግባል፤ ይሞቃልና፦ እሰይ ሞቅሁ፥ እሳቱን አይቻለሁ ይላል። የቀረውንም እንጨት አምላክ አድርጎ ምስል ይቀርጽበታል፤ በፊቱም ተጐንብሶ ይሰግዳል ወደ እርሱም እየጸለየ፦ አምላኬ ነህና አድነኝ ይላል። አያውቁም፥ አያስቡም፤ እንዳያዩ ዓይኖቻቸውን፥ እንዳያስተውሉ ልቦቻቸውን ጨፍነዋል። በልቡም ማንም አያስብም፦ ግማሽዋን በእሳት አቃጥያለሁ፥ በፍምዋም ላይ እንጀራን ጋግሬአለሁ፥ ሥጋም ጠብሼ በልቻለሁ፤ የቀረውንም አስጸያፊ ነገር አደርጋለሁን? ለዛፍስ ግንድ እሰግዳለሁን? እንዲልም እውቀትና ማስተዋል የለውም።
ከአላህ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱምና ወደ አላህ በንስሃ ተመለሱ፦
7፥197 እነዚያም ከእርሱ በቀር የምትጠሯቸው ሊረዷችሁ አይችሉም፤ እራሳቸውንም አይረዱም وَٱلَّذِينَ تَدْعُونَ مِن دُونِهِۦ لَا يَسْتَطِيعُونَ نَصْرَكُمْ وَلَآ أَنفُسَهُمْ يَنصُرُونَ ፡፡
✍ ከወሒድ ዐቃቢ ኢሥላም
Follow us on:
https://fb.me/tiriyachen
https://www.tg-me.com/tiriyachen
https://tiriyachen.org
https://bit.ly/3eVixKv
https://www.tiktok.com/@tiriyachen
ወሰላሙ አለይኩም
ድብርትና መድኃኒቱ
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
ቁርኣን 16፥97 ከወንድ ወይም ከሴት እርሱ አማኝ ኾኖ በጎን የሰራ “”መልካም ኑሮን በእርግጥ እናኖረዋለን””፡፡ ይሠሩትም ከነበሩት ነገር በመልካሙ ምንዳቸውን እንመነዳቸዋለን፡፡
“ስሜት”emotion” ማለት ፍቅር እና ጥላቻ ወይም ደስታ እና ሃዘን ናቸው፤ “ውሳኔ” ደግሞ በስሜት ውስጥ ከተወሰነ ትርፉ ፀፀት ነው፤ ብዙ ጊዜ ሰዎች ወደ ጥፋት የምንገባው በስሜት
ነው፤ ነገር ግን ከስሜት ወጥተን በምክንያታዊ እውቀት ስንወስን ፅናት ይኖረናል፤ “ምክንያታዊነት”Rationality” መሰረቱ እውቀት ነው፤ እውቀት ሳይኖር መከተል እንደማይቻል አምላካችን አላህ በተከበረ ቃሉ ይነግረናል፦
ቁርኣን 17፥36 ለአንተም በእርሱ “”ዕውቀት”” የሌለህን ነገር “”አትከተል””፤ መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ ተጠያቂ ነውና፡፡ ......
▫️ገብተው ሙሉን ያንብቡ👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/ድብርትና-መድኃኒቱ/
በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኛ በሆነው፡፡
ቁርኣን 16፥97 ከወንድ ወይም ከሴት እርሱ አማኝ ኾኖ በጎን የሰራ “”መልካም ኑሮን በእርግጥ እናኖረዋለን””፡፡ ይሠሩትም ከነበሩት ነገር በመልካሙ ምንዳቸውን እንመነዳቸዋለን፡፡
“ስሜት”emotion” ማለት ፍቅር እና ጥላቻ ወይም ደስታ እና ሃዘን ናቸው፤ “ውሳኔ” ደግሞ በስሜት ውስጥ ከተወሰነ ትርፉ ፀፀት ነው፤ ብዙ ጊዜ ሰዎች ወደ ጥፋት የምንገባው በስሜት
ነው፤ ነገር ግን ከስሜት ወጥተን በምክንያታዊ እውቀት ስንወስን ፅናት ይኖረናል፤ “ምክንያታዊነት”Rationality” መሰረቱ እውቀት ነው፤ እውቀት ሳይኖር መከተል እንደማይቻል አምላካችን አላህ በተከበረ ቃሉ ይነግረናል፦
ቁርኣን 17፥36 ለአንተም በእርሱ “”ዕውቀት”” የሌለህን ነገር “”አትከተል””፤ መስሚያ፣ ማያም፣ ልብም እነዚህ ሁሉ ባለቤታቸው ከእነርሱ ተጠያቂ ነውና፡፡ ......
▫️ገብተው ሙሉን ያንብቡ👇🏻👇🏻
https://tiriyachen.org/ድብርትና-መድኃኒቱ/