Telegram Web Link
ባለ ማኅተቊቜ ብቻ play ይበሉ
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
⬜⬜⬜ play▶ ⬜⬜⬜
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
_
ባለ ማኅተቊቜ ብቻ play ይበሉ
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
⬜⬜⬜ play▶ ⬜⬜⬜
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜

ባለ ማኅተቊቜ ብቻ play ይበሉ
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
⬜⬜⬜ play▶ ⬜⬜⬜
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
_
ባለ ማኅተቊቜ ብቻ play ይበሉ
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
⬜⬜⬜ play▶ ⬜⬜⬜
⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜⬜
#ቅድስት
#ዚዐቢይ_ጟም_ሁለተኛ_ሳምንት

ዚቅድስና ባለቀት ዹሆነው እርሱ እግዚአብሔር አምላክ ነው። እቀደስ አይል ቅዱስ፣ እባሚክ አይል ቡሩክ ነው። በእርሱ ዚባሕርይ ቅድስና እኛን በአርአያውና በአምሳሉ ፈጥሮ ቡሩክ ሆኖ ባሚኚን፣ ቅዱስ ሆኖ ቀደሰን፣ሕያው ሆኖ ሕያዋን አደሚገን። ዹጾጋ ቅድስናንም ኚእርሱ አገኘን። ቅድስናው ዚተለዚ፣ ዚኚበሚ፣ ዚሚመሰገን፣ ዚሚሰጥ/ዚሚያድል፣ ዚሚያነጻ፣ ዚሚባርክ እናም ዚሚያስተሰርይ ስለሆነ እንኚን፣ ጉድለት ዚሌለበት ምሉዕ ነው። ለባለሟሎቹ ቢሰጠው ዚማይጎድል፣ ተኹፍሎ ዚሌለበት ቅድስና ሆኖ እኛም ዚቅድስና በጾጋ ተካፋይ ሆነናል።

ዹተሰጠንን ቅድስና ገንዘብ እንድናደርግ እና እንድንጠቀምበት ደግሞ በጟም፣ በጞሎት፣ በስግደት፣ በምጜዋትና በሌሎቜ በጎ ምግባራት መትጋት ይገባናል። ‹‹እኔ እግዚአብሔር አምላካቜሁ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ›› እንዲል፡፡ (ዘፍ.፪፥፫፣ ዘሌ.፲፱፥፪) ዚት መሄድ እንዳለብንም በግልጜ ልበ አምላክ ነቢዚ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ‹‹ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁፀ ስለ ትምህርትህና ስለ እውነትህ ስምህን አመሰግናለሁፀ በሁሉ ላይ ቅዱስ ስምህን ኹፍ ኹፍ አድርገሃልና›› ይላል። (መዝ.፻ፎ፯÷፪) ዹተቀደሰን መሥዋዕት በተቀደሰ ቊታ እንፈጜማለን። መቌ ቢሉ፣ በሰንበት፣ በበዓላት በማኅበሹ ዐቢይ/ክርስቲያኖቜ በሚሰበሰቡበት፣ ስመ እግዚአብሔር በሚጠራበት፣ ታቊት  ባለበት፣ እግሚ እግዚአብሔር በቆመበት ቅዱስ ስሙን ኹፍ ኹፍ በማድሚግ ቅድስናን ገንዘብ እናደርጋለን።

ሊቁ ቅዱስ ያሬድ ለዐቢይ ጟም ሁለተኛው እሑድ በአዘጋጀው ምስጋና አማካኝነት ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› ዹሚል ስያሜ ተሰጥቶታል፡፡ ትርጉሙም ‹‹ዚተለዚቜ፣ ዚተመሚጠቜ፣ ዚኚበሚቜ›› ማለት ነው።  (መጜሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ገጜ ፯፻፹፬) ቅድስት ዹሚለው ቃል ዕለቱ ‹‹ቅድስት›› ተብሎ ዚተሰዚመበት ምክንያት ስለ ዕለተ ሰንበት እንዲሁም ስለ እግዚአብሔር አምላክ ፍጹም ቅድስና ዚሚያወሳ በመሆኑ ነው፡፡ እግዚአብሔር አምላክም ፍጥሚታቱ ዚእርሱን ስም በማመስገን ይኖሩ ዘንድ ለቅድስና ሕይወት ፈጥሯ቞ዋልና በሰንበት እሑድ ክርስቲያኖቜ ዚቅድስና ተግባራትን ኹሌላው ቀን አብዝተው ይፈጜማሉ፡፡ ዕለት ኚተግባር፣ ስም ኚክብር ዚተባበሚባት ክብርት ሰንበት ቅድስት ስለሆነቜ ቅዱስ ያሬድ “ቅድስት” ብሎ ጠራት። ይኾውም ዚምትቀድስ፣ ኚብራ ዚምታኚብሚን፣ አክብሚናት ዚምንኚብርባት በመሆኗ ነው።

ለዚህም ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጟመ ድጓ “ግነዩ ለእግዚአብሔር ወጾውዑ ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮፀ ሀቡ ስብሐተ ለስሙፀ አክብሩ ሰንበተ ተገበሩ ጜድቀፀ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይሚክቊ ሰራቂፀ ድልዋኒክሙ ንበሩ ዘበላዕሉ ጞልዩ ኀበ ሀሎ ክርስቶስ” ትርጉምፊ “ለእግዚአብሔር ተገዙፀ ስሙንም ጥሩፀ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯ቞ውፀ ለስሙም ምስጋናን አቅርቡ ሰንበትን አክብሩፀ እውነትንም አድርጉፀ ብል ዚማያበላሞው ሌባም ዚማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡፀ ተዘጋጅታቜሁም ተቀመጡፀ ክርስቶስ ወዳለበት ወደ ላይ አስቡ፡፡“  ስለዚህ ሰው ሰንበትን አክብሮ ጟሞ ጞልዮ፣ ቅድስናን ጠብቆ መኖር እንዲቜል እግዚአብሔር ዚፍቅሩ መገለጫ ዹሆኑ ትእዛዛቱ ይነግሩናል።

#ቅዱስ_ያሬድም_ወቅቱን “#ቅድስት” ብሎ ሲሰይምፊ

፩.
#ዚአርባ_ቀን_ጟም_መጀመሪያ_በመሆኑ፩ ዕለቱ ኚዐቢይ ጟም ቀናት ውስጥ አርባው ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚጟመው ጟም መጀመሪያ ስለሆነቜ፣

፪.
#ቅድስት_ሰንበት_ላይ_በመዋሉ፣ እንግዲህ “ዚሰንበትን ቀን ትቀድሰው ዘንድ አስብ” ተብሏል፡፡ (ዘፀ.፳፥፰) ዚሰንበትን ቀን አስቀድሞ ዹቀደሰ ዚባሚኚ ራሱ እግዚአብሔር ነው፡፡ እግዚአብሔርም ሰባተኛውን ቀን ባሚኚውፀ ቀደሰውምፀ እግዚአብሔር ሊያደርገው ኹፈጠሹው ሥራ ሁሉ በእርሱ ዐርፎአልና፡፡” (ዘፍ.፪፥፫)

“ኚምእመናን ወገን አንድስ እንኳን በእሑድ ቀን ለገንዘብ መትጋት፣ ገንዘቀን አምጣ ብሎ መጣላት እና ዋስ መያዝ አይገባውም። ሁሉም ምእመናን ወደ ቀተ ክርስቲያን በንጜሕና በትሕትና ሆነው። ዳኛ ግብሬን፣ አበዳሪ ብድሬን፣ ኀጲስ ቆጶስ ዐሥራት በኵራት፣ ነጋ ድራስ ቀሚጥ አምጡ ይሉናል ብለው ሳይፈሩ ይምጡ።

፫.
#ወቅቱ_ወርኃ_ጟም_በመሆኑ፩ ምእመናን ይህንን ወቅት በጟም፣ በጞሎት፣ በእንባ፣ በስግደት፣ በአርምሞ፣ በመልካም ሥራ ቅድስናን ዚምናገኝበት፣ ጊዜው ሰው ወደ እግዚአብሔር አብዝቶ ዚሚተጋበት ወቅት በመሆኑ፣ ለእግዚአብሔር ዚሚገባ ነገር ለማድሚግ ዹነገር ሁሉ መጀመሪያ፣ ለመልካም ነገር መነሻው በቅድስና በንጹሕ ልቡና መቅሚብ ስለሆነ ቅድስት ብሏታል።  “እስመ ጟም እማ ለጞሎት ወእኅታ ለአርምሞ ወነቅዓ ለአንብዕ መቅድመ ኩሉ ግብር ሠናይትፀ ጟም ማለት ዚጞሎት እናት፣ ዚትሕትና እኅት፣ ዚእንባ ምንጭ፣ዚመልካም ሥራ ሁሉ መጀመሪያ ናት” እንዳለው ቅዱስ ያሬድ። ”ጟምን ቀድሱፀ ጉባኀውንም ዐውጁ” ዚተባልን ዹተሰጠንን ዹጾጋ ቅድስና በእጃቜን ላይ መኖሩን አመላካቜ ቃል ነው። (ኢዩ.፩፥፲፬)

፬.
#ዹወንጌል_ትእዛዝ_በመሆኑ፡ ዕለቱን ተጠቅሞ ዓለምን አስተምሮበታል። “ዛቲ ዕለት እንተ ገብሚ እግዚአብሔር ንትፈሣሕ ወንትሐሠይ ባቲ”  ትርጉም፡- “ይህቜ ዕለት እግዚአብሔር ዚሠራት ቀን  ናትፀ ሐሀትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።” (መዝ.፻፲፯፥፳፬) ቅዱስ ዮሐንስም በራእዩ ሰንበት ዚጌታ ቀን ስለመሆኗ እንዲህ ይላልፀ “በጌታ ቀን በመንፈስ ነበርሁ፡፡” (ራእ. ፩፥፲)

ሊቃውንቱ በፍትሐ ነገሥት “ተጋብኡ ኵሎ ዕለት ኀበ ቀተ ክርስቲያን ወፈድፋደሰ በዕለተ ሰንበት ወበበዓላት ወበዕለተ ትንሣኀ ዘውእቱ ዕለተ እሑድ” ትርጉምፊ “ሁልጊዜ በቀተ ክርስቲያን ተሰብሰቡፀ ይልቁንም በዕለተ እሑድ፣ በዕለተ ቀዳሚት፣ በጌታ በዓላት ወደ ቀተ ክርስቲያን ተሰብሰቡ” በማለት አዘውናል፡፡ (ፍትሐ ነገሥት፣ ገጜ ፪፶፬)

በትጋት ጟመን፣ ጾልዹን ርስቱን እንድንወርስ ዚእግዚአብሔር ቞ርነት፣ ዚእመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም ምልጃፀ ዚቅዱሳን በሚኚት ይጠብቀን።

ዚዕለቱ መዝሙር (ኚጟመ ድጓ)ፊ ግነዩ ለእግዚአብሔር

#ምንባባት
➛ ፩ኛ ተሰ.፬÷፩-፲፫
➛ ፩ኛ ጎጥ.፩÷፲፫-ፍጻ.
➛ ሐዋ. ፲÷፲፯-ፎ

#ምስባክ
“እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብሚ::
አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ፣
ቅድሳት ወዕበዹ ስብሐት ውስተ መቅደሱፀ

(እግዚአብሔር ግን ሰማያትን ፈጠሚ፡፡ እምነትና በጎነት በፊቱ፣ ቅድስናና ዚክብር ገናናነት በመቅደሱ ውስጥ ና቞ው፡፡”
(መዝ.፺፭÷፭)

#ወንጌል
(ማቮ.፮÷፲፮-፳፭)

#ቅዳሎ
ዘኀጲፋንዮስ 

(ማኅበሹ ቅዱሳን)

ለኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆቜ👇
                •➢ ሌር // SHARE

   
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
ካህኑ  ለምን  በእጁ  ያሳልሙናል ?

ዚካህኑን  እጅ  መሳለም   አንዳንድ  ሰዎቜ  ካህኑ  ለምን  በእጁ  ያሳልመናል  ይላሉ። ነገር  ግን  ሚስጢሩ  ይህ  ነው
ዚካህኑ  እጅ  እኮ  እሳታዊያን  ዹሆኑ  መላእክት  መንካት
ዚማይቻላ቞ውን  ቅዱስ  ሥጋውን  ክብር  ደሙን  ዚዳሰሱበት
ነው።
በቅዳሎ  ላይ  ቅዱስ  ሥጋውን  መንካት  ዚሚቜለው  ዋናው  ካህን  ብቻ  ነው ፀ ሁለተኛው  ካህን  እንኳን  መንካት  አይቜልም።
ቅዱስ  ሥጋውን  ክብር  ደሙን  ዚዳሰሰበት  ስለሆነም  ካህኑ  በእጁ  ያሳልመናል  እኛም  ዹተቀደሰውን  ዚጌታ  ስጋና  ደም 
ዚዳሰሱበት  እጅ  እዚተሳለምን  አሜን  አሜን  አሜን  እንላለን።

ድንቅ  መለኮታዊ  ሚስጥር  ማለት
እንዲህ  ነው

አንሥኡ  እደዊክሙ  ቀሳዉስ
ዲያቆኑ  ይህን  በሚልበት  ጊዜ  ንፍቀ  ካህኑ  ማሕፈዱን
ኚጻሕሉ  ላይ  ያነሳል ፀ ይህም  ዚጌታ  መላአክ  ዚመቃብሩን
ድንጋይ  ዚማኚባለሉ  ምሳሌ  ነው።ኚዚህ  በኋላ  ጌታቜን
በምሮተ  ሐሙስ  ሕብስቱን  እንደያዘው  ዋናዉ  ካህንም
ሕብስቱን  ኹፍ  አድርጎ  ይይዘዋል ፀ ይህም  ዚጌታ  ትንሳኀ  ምሳሌ  ነው።

እግዚኊ  መሐሹነ  ክርስቶስ
በእግዚኊታ  ላይ  ካህኑ  ሕብስቱን  ይበልጥ  ኹፍ  አድርጎ
ይይዘዋል  ይህም  ዚዕርገቱ  ምሳሌ  ነው።ኚካህኑ  ጋር  ሆነን 
41 ግዜ  እግዚኊ  መሐሹነ  ክርስቶስ  እንላለን ፀ ይህም  አርባው  እግዚኊታ  አይሁድ  ጌታቜንን  40  ግዜ  እንገርፋለን  ብለው  እያዛቡ  ብዙ  ጊዜ  ዹመግሹፋቾው  ምሳሌ  ሲሆን  በመጚሚሻ  ካህኑ  ብቻውን  ዚሚላት  እግዚኊታ  ደግሞ  ዚአዳምና  ዹሔዋን  ዚንስሃ  ምሳሌ  ነው።  12  ግዜ  እግዚኊ  መሐሹነ  ክርስቶስ  ስንል  ደግሞ  ስለስምህ  ብለህ  ይቅር  በለን  ነው።  አብ  ወልድ  መንፈስ  ቅዱስ  ዹሚለውን  እያንዳንዱን  ፊደል  ስንቆጥር  12  ይሆናል!!! እንዲሁም  12  ጊዜ  በእንተ  እግዚትነ  ማርያም  መሐሹነ  ክርስቶስ  ስንልም  ደግሞ  ስለእናትህ  ብለህ  ማሹን  ማለታቜን  ሲሆን  ቅድስት  ድንግል  ማርያም  ዹሚለውን   እያንዳንዱን  ፊደል  ስንቆጥር  12  ይሆናልና

ወንጌል
ዚመጀመሪያዉ  መልዕክት  ሲነበብ  ዲያቆኑ  ፊቱን  ወደ  ምዕራብ  አዙሮ  ያነባል፡ ሁለተኛው  ዲያቆን  ፊቱን  ወደ  ሮሜን  አዙሮ  ያነባል ፡ ንፍቀ  ካህኑ  ወደ  ደቡብ  ዙሮ  ያነባል  ዚሐዋርያት  ሥራ  ሲያነብ  ዋናው  ካህን  ደግሞ  ወደ  ምስራቅ  ዙሮ  ወንጌል  ያነባል ፀ ይህም  ግሩም  ዹሆነ  ምሳሌ  አለው  አንድም  ወንጌል  በአራቱም  አቅጣጫ  መስበኩን  ለመግለጜ  ነው  አንድም  ገነትን  ዚሚጠጡ  4 ወንዞቜ አሉ  ኀፍራጠስ  ጀግሮስ  ጊዮን  (አባይ)  እና  ፊሶን  ና቞ው።  ገነትን  አጠጥተው  ለምለም  እንደሚያደርጓት  ጌታቜንም  ዹተጠማ  ቢኖር  ዚህይወት  ውሃ  በነፃ  ይጠጣና  ይርካ  እንዳለው  ወንጌልም  እንዲሁ  ያለመልማል  ሲሉ  ነው።

ቀተክርስቲያን  ኚጣራዋ  እስኚ  መሬቷ  ሁሉም  ስርዓቷ 
ያስተምራል ፀ ባህሚ  ጥበብ  ቀተክርስቲያን  እዚተናገሚቜ
ታስተምራለቜ  ሳትናገርም  ዝም  ብላ  ታስተምራለቜ!!!

ወስብሐት  ለእግዚአብሔር
ወለ  ወላዲቱ  ድንግል
ወለ  መስቀሉ  ክብር  ይቆዹን
https://www.tg-me.com/sratebetkrstyane
መጋቢት ፲
በዓለ ቅዱስ መስቀል

መጋቢት አስር በዚህቜ እለት ዚክብር ባለቀት ጌታቜን አምላካቜንና መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚተሰቀለበት መስቀል ዚተገለጠበትና ዚተገኘበት ነው። ዹዚህም ዹኹበሹ ዕፀ መስቀል መገለጡና መገኘቱ ሁለት ጊዜ ሆኗል።

መጀመሪያ ዚፃድቁ ንጉስ ዚቆስጠንጢኖስ እናት በሆነቜ በንግስት እሌኒ እጅ ነው።
እርሷ ለእግዚአብሄር ተስላ ነበርና ልጇ ቆስጠንጢኖስ ወደ ክርስቲያን ሀይማኖት ቢገባ ወደ ኢዚሩሳሌም ሄዳ መስቀሉን እስኚ አገኘቜው ድሚስ ልትፈልግው በኢዚሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ልታንፃ቞ው ነው።

ኹዚህ በኋላ ልጇ አምኖ ዚክርስትና ጥምቀትን በተጠመቀ ጊዜ እሌኒ ቅድስት ወደ ኢዚሩሳሌም ሄደቜ ኚእርሷ ጋርም ብዙ ሰራዊት ነበር ደርሳም ስለ ኹበሹ መስቀል መሚመሚቜ ዚሚያስሚዳት አላገኘቜም ዚአይሁድ ወገን ዹሆነ አንድ ሜማግሌ ሰው አስራ በርሀብና በጥማት አስጚነቀቜው።
በተጹነቀም ጊዜ ለንግስት እሌኒ "ዚጉልጎታን ኮሚብታ አስጠርጊ" ብሎ ነገራት እርሷም ይጠርጉ ዘንድ አይሁድን አዘዘቻ቞ው።

ቀቱን ዹሚጠርግ ሰው ሁሉ ጥራጊውን በውስጡ ዹኹበሹ መስቀል በአለበት በጌታቜን መቃብር ላይ እንዲጥል አይሁድ አስቀድመው አዝዘው ነበርና ንግስት እሌኒ እስኚደሚሰቜበት ጊዜ ኚሁለት መቶ አመት በላይ ጥራጊያ቞ውን ሲጥሉበት ኖሩ ኮሚብታም ሆነ። አይሁድም በጠሹጉ ጊዜ ሶስት መስቀሎቜ ተገለጡ ዚክብር ባለቀት ክርስቶስ ዚተሰቀለበት ዚትኛው እንደሆነ አላወቁም።
ዹሞተ ሰውም አግኝተው አመጡ። አንዱንም መስቀል አምጥተው በሞተው ሰው ላይ አኖሩት አልተነሳም ደግሞ ሌላውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አኖሩ አሁንም አልተነሳም ኹዚህም በኋላ ሶስተኛውን መስቀል አምጥተው በሙቱ ላይ አደሚጉት ያንጊዜ ዹሞተው ሰው ተነሳ እሌኒም ዚክርስቶስ መስቀል እንደሆነ አውቃ ሰገደቜለት ዚክርስቲያንም ወገኖቜ ሁሉ ሰገዱለት።

ለልጇ ዚላኚቜው ይህ መስቀል ነው ዹሚል በሌላ መፅሀፍ ይገኛል ዹቀሹው ግን ግንዱ በውስጡ ተተክሎበት ዹነበሹው ኚእርሱም እኩሌታውን ኚቅንዋቱ ጋራ ወደ ልጅዋ ዚላኚቜው ነው።

ኹዚህም በኋላ ስርዓታ቞ውና ዹህንፃቾው ነገር በመስኚሚም ወር በአስራ ሰባት ተፅፎ ዹሚገኝ አብያተ ክርስቲያናትንና ዚኚበሩ ቊታዎቜን አነፀቜ።

ሁለተኛው በሮሙ ንጉስ በህርቃል ዘመን ዹሆነው ሲሆን ዚፋርስ ሰዎቜ በግብፅ አገር ሳሉ ወደ አገራ቞ው ሊመለሱ ወደዱ። ኚሹማምንቶቻ቞ው አንዱ ዹጩር መኰንን ተነጥሎ ወደ ኢዚሩሳሌም አልፎ ደሹሰ ወደ ኹበሹ መስቀል ቀተ ክርስቲያንም ገባ። መስቀሉም በላዩ በተተኚለበት ግንድ ፊት ታላቅ ብርሀን ሲበራ አይቶ ሊያነሳው እጁን ዘሚጋ። እሳትም ወጥታ እጁን አቃጠለቜው።

ኚክርስቲያን በቀር ማንም ሊነካው እንደማይቜል ዚመስቀልን ዚክብሩን ነገር ሰዎቜ ነገሩት። ሁለት ዲያቆናትንም ይዞ ዹኹበሹ መስቀልን እንዲሞኚሙ አዘዛቾው ኚኢዚሩሳሌምም ብዙ ሰዎቜን ማርኮ ወደ አገሩ ተመለሰ።

ዚፋርስ ሰዎቜ ኢዚሩሳሌምን እንዳጠፏት ብዙዎቜ ሰዎቜንም እንደማሚኩና ዹኹበሹ ዚክርስቶስንም መስቀሉን እንደወሰዱ ዚሮም ንጉስ ህርቃል በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ። ስለርሱም እንዲፆሙ ምእመናንን አዝዞ ወደፋርስ ዘምቶ ወጋቾው ብዙዎቜንም ገደላቾው ዹኹበሹ እፀ መስቀልንም እዚፈለገ በሀገራ቞ው ሁሉ ዞሹ ግን አላገኘውም።

ያ ዲያቆናቱና መስቀሉን ዹወሰደ መኰንን ኚቊታዎቜ በቀቱ አንፃር ባለ በአንድ ቊታ ላይ ወስዷ቞ው ጥልቅ ጉድጓድ እንዲቆፍሩ አዝዞ በዚያ ዹኹበሹ መስቀልን አስቀበሚ እነዚያንም ዲያቆናት ገደላ቞ው።

ነገር ግን ያ መኰንን ዚማሚካት ዚካህናት ወገን ዚሆነቜ በእርሱ ቀት ዚምትኖር አንዲት ብላ቎ና ነበሚቜ። እርሷም ዹኹበሹ መስቀልን ሲያስቀብርና ሁለቱን ዲያቆናት ሲገድላ቞ው በቀቱ ውስጥ ሁና በመስኮት ትመለኚት ነበር ወደ ንጉስ ህርቃልም ሂዳ መኰንኑ ያደሚገውን ሁሉ ነገሚቜው።
ይህም ንጉስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ያቺ ብላ቎ናም መራቜው ኚእርሱም ጋራ ብዙ ሰራዊት ሆኖ ኀጲስቆጶሳትና ካህናትም ነበሩ ።ወደ ቊታውም እስኚምታደርሳ቞ው ያቺን ልጅ ተኚተሏት ቆፍሹውም ዹኹበሹ እፀ መስቀልን አገኙት ኚአዘቅቱም አወጡት ንጉሱና ሰራዊቱም ሰገዱለት።

በልብሰ መንግስቱም አጎናፀፈው ታላቅ ክብርንም አኹበሹው ኚሰራዊቱም ጋር እጅግ ደስ አለው። ዹዚህም መስቀል ሁለተኛ ዚተገለጠበትና ዚተገኘበት በዚቜ ቀን በመጋቢት አስር ነው፡፡ ኹዚህ በኋላ ንጉሱ ዹኹበሹ እፀ መስቀልን ተሾክሞ ወደ ቁስጥንጥንያ ኹተማ ወሰደው፡፡

ዚመድኃኒታቜን ዚመስቀሉ በሚኚት ኚሁላቜን ዚክርስቲያን ወገኖቜ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን።
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
+ አባቶቻቜን እንዲህ አሉ +

"መጥፎ ቀን እና ጥሩ ቀን ዚሚባል ነገር ዹለም:: ያለው ጞሎት አድርገህ ዚወጣህበት ቀን እና ጞሎት ሳታደርግ ዚወጣህበት ቀን ነው:: ያልጞልክባ቞ው ቀናት በክፉ ምኞትና ዚሥጋ ፍላጎት ዹተሞሉ ስለሆኑ ክፉ ቀናት ናቾው"
ቅዱስ ቄርሎስ ሳድሳዊ

"ዚምንቆጥሚው ሬሳዎቜን አይደለም:: ሰማዕታትን ነው:: ሙታንን ሳይሆን ሙሜሮቜን ነው:: ሰማዕታት ሆይ ስለ እኛ ማልዱ" ኹአኃው አንዱ

"ሰዎቜን ዚሚሳደብን ሰው አንደበት መዝጋት አትቜልም ኚእርሱ ጋር አለመነጋገር ግን ትቜላለህ"
ቅዱስ ማር ይስሐቅ

"እኔ ካህን ነኝ መግደል አልቜልም:: በግድ ዝመት ካላቜሁኝ ደግሞ ኹጩር ሜዳ ውሰዱኝ:: ዚቆሰሉትን እሚዳለሁ:: ለሞቱት ጞሎት አደርጋለሁ:: ዚወደቁትን አነሣለሁ:: መሞትን አልፈራም:: መግደልን ግን እፈራለሁ"
በዘመነ ሰማዕታት ዹነበሹ ሕጜው ካህን

"ሰዎቜ አንድ ሰው ተነሥቶ ሌላውን ሲገድል ወንጀለኛ ነህ ይሉታል። አንድ ላይ ተሰባስበው ብዙ ሰዎቜን ሲገድሉ ግን ውጊያ ይሉትና መግደላቾውን ጀግንነት ይሉታል" ቅዱስ ቆጵሮሳዊ

"ገድዬ እጞድቃለሁ ብሎ ክርስቲያኖቜን ዚሚገድል ሰው ዚተሳሳተ ቢሆንም ያደሚገው ያጞድቀኛል ብሎ ያመነበትን ነው:: እኛ ዚምናምንበት መጜሐፍ ቅዱስ ደግሞ "ጠላቶቻቜሁን ውደዱ ለሚያሳድዱአቜሁ ጞልዩ" ይላል:: ነፍሰ ገዳይ ለሚያምንበት ነገር ኚታዘዘ እኛም ለምናምንበት ይቅር ባይነት መታዘዝ አለብን” አቡነ አትና቎ዎስ እስክንድር

"ዚክርስቲያኖቜ መሣሪያ በእጃ቞ው ሰይፍን መታጠቅ ሳይሆን እጃ቞ውን ወደላይ ለጞሎት መዘርጋት ነው"
ቅዱስ አትና቎ዎስ ዘእስክንድርያ

"እግዚአብሔር ለአብርሃም "ኹሀገርህ ውጣ ኚወገኖቜህ"ተለይ ብሎት ነበር። በዚህ ጥሪ እግዚአብሔር ሁላቜንንም ዚተወለድንበት ዘር እንድንተው ይጠራናል።
ሰማዕቱ ዮስጊስ (100 AD-165 AD)

"ክርስቶስ ጎጥሮስን "ሰይፍህን ወደ ሰገባው አስገባ" ሲለው ትጥቅ ያስፈታው ጎጥሮስን ብቻ ሳይሆን እንደ ጎጥሮስ በእርሱ ዚሚያምኑትን ሁሉ ነበር"
ሊቁ ጠርጡለስ (160 AD - 220 AD)

"ዚእኛ መሣሪያ ወደ ላይ ዹምንሹጹው ዕንባ ነው:: ፈርዖንን ኚነፈሚሶቹ ያሰጠመው ዚኀርትራ ባሕር ሳይሆን ዚራሔል ዚጞሎት ዕንባ ነው" ኹአኃው አንዱ

"አምላኬ ሆይ ልቀ እንደ ጠባብ ቀት ነው:: አንተን ለማስገባት ዚማይቜል በጣም ትንሜ ነው:: አንተ ሰፊ እንድታደርገው እለምንሃለሁ:: በልቀ ቀት ውስጥ ስታያ቞ው ደስ ዚማያሰኙህ ነገሮቜ እንዳሉ አውቃለሁና አልደብቃ቞ውም:: ኹአንተ በቀር ዚውስጀን ቆሻሻ ሊያስወግድ ዚሚቜል ማንም እንደሌለ አውቃለሁ"
ቅዱስ አውግስጢኖስ


"...........እነሆ፥ ዹተወደደው ሰዓት አሁን ነውፀ ዚመዳን ቀን አሁን ነው"
--2ኛ ቆሮ 6፥2
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
#ምኩራብ
(ዚዐቢይ ጟም ሊስተኛ ሳምንት)

ምኩራብ ማለት ለአምልኮትና ለትምህርት ለህብሚተሰቡ አገልግሎት ዚሚሰጥ ዚአይሁድ ቀተ ጞሎት ነው። ጌታ በመዋዕለ ስብኚቱ በእስራኀል ሀገር ብዙ ምኩራቊቜ ስለነበሩ እዚገባ ወንጌልን አስተምሮባ቞ዋል። በዚህም “ቩአ ኢዚሱስ ምኩራበ አይሁድ ወመሀሹ ቃለ ሃይማኖት” እንዲል ቅዱስ ያሬድ ኢዚሱስ ወደ አይሁድ ምኩራብ ገብቶ ዚሃይማኖት ቃልን አስተማሚ። ኹሚለው ዚቅዱስ ያሬድ ዜማ ሥያሜውን አግኝቷል።

በምኩራብ ጞሎትና ትምህርት ይፈጞምበታል። መሥዋዕት ግን አይኚናወንም። መሥዋዕት ግን በታላቁ ቀተ መቅደስ በኢዚሩሳሌም ብቻ ይፈጾም ነበር። በዚህ ሳምንት ዹሚነገሹው ታሪክ ጌታ ቀተ መቅደሱን ዚገበያ ማዕኹል አድርገው ሞቀጥ ዘርግተው በጉን ላሙን ርግቡን እዚሞጡ አገኛ቞ው። በዚህ ተቆጥቶ በጉን ላሙን ርግቡን ኚምኩራብ አስወጥቶ ሞቀጣ቞ውንና መደርደሪያ቞ውን እንዲሁም ወርቅና ብራ቞ውን በነፋስ በተነባ቞ው ይላል።

በዚህ ሁኔታ ኚቀተ መቅደስ አስወጥቶ "ቀ቎ ዚጞሎት ቀት ትባላለቜ እናንተ ግን ዚሜፍቶቜና ዚወንበዎዎቜ ዋሻ አደሚጋቜኋት" በማለት ወቅሷ቞ዋል። “አሰስሉ ወአውፅኡ ዘንተ እምዝዚ ወኢትሚስዩ ቀተ አቡዚ ቀተ ምሥያጥ” እንዲል ዮሐ. 2፥16ፀ ማቮ. 21፥13። ይህን ተአምር በማሳዚት ቀተ ጞሎት ዹተቀደሰ ኚገበያ ዹተለዹ መሆኑን አስተምሮበታል።

በሰንበተ ምኩራብ ጌታ ወደ ቀተ መቅደስ ገብቶ ለዋጮቜን ማስወጣቱ ወርቅና ብሩን በነፋስ መበተኑ ላሞቜን በጎቜን በጅራፍ መግሹፉ ቀተ መቅደሱን ማንጻቱ ወዘተ ይነገራል።

(ዹዚህም በዓል ታሪክ ዝርዝር ሁኔታው ማ቎ዎስ 21፥12-13 ላይ ተጠቅሷል፡፡)

#ዚቅዳሎ_ምንባባትፊ

ቆላስ. 2፥16-23
«እንግዲህ በመብል ወይ በመጠጥ ወይም ስለ በዓል ወይም ስለ ወር መባቻ ወይም ስለሰንበት ማንም አይፍሚድባቜሁ እነዚህ ሊመጡ ያሉት ነገሮቜ ጥላ ና቞ውና፣ አካሉ ግን ዚክርስቶስ ነው፡፡ .......፡፡»

ያዕ. 2፥14-26
«ወንድሞቌ ሆይ፣ እምነት አለኝ ዚሚል፣ ሥራ ግን ዹሌለው ሰው ቢኖር ምን ይጠቅመዋል እምነቱስ ሊያድነው ይቜላልን ......፡፡»

ሐዋ. 1ዐ፥1-9
«በቂሣርያም ኢጣሊቄ ለሚሉት ጭፍራ ዚመቶ አለቃ ዹሆነው ቆርኔሌዎስ ዚሚሉት አንድ ሰው ነበር፡፡ እርሱም ኚቀተ ሰዎቹ ሁሉ ጋር እግዚአብሔርን ዚሚያመልክና ዚሚፈራ ለሕዝብም እጅግ ምጜዋት ዚሚያደርግ ወደ እግዚአብሔርም ሁልጊዜ ዹሚጾልይ ነበሚ፡፡ ....፡፡"

#ምስባክ- መዝ 68፥9
እስመ ቅንዐተ ቀትኚ በልዐኒ
ትዕይርቶሙ ለእለ ይትዔዚሩኚ ወድቀ ላዕሌዹ
ወቀጻዕክዋ በጟም ለነፍስዚ፡፡

(ዚቀትህ ቅንዓት በልታኛለቜና
ዚሚሰድቡህም ስድብ በላዬ ወድቆአልና
ነፍሮን በጟም አስመሚርኋት፡፡)

#ወንጌል፡- ዮሐ 2፥12-25
«ኚዚህ በኋላ ኚእናቱና ኚወንድሞቹ ኹደቀ መዛሙርቱም ጋር ወደ ቅፍርናሆም ወሚደ፣ በዚያም ጥቂት ቀን ኖሩ፡፡ ዚአይሁድ ፋሲካም ቀርቩ ነበር ኢዚሱስም ወደ ኢዚሩሳሌም ወጣ፡፡ ወደ መቅደስም በሬዎቜንና በጎቜን ርግቊቜንም ዚሚሞጡትን ገንዘብ ለዋጮቜንም ተቀምጠው አገኘፀ ዚገመድም ጅራፍ አበጅቶ ሁሉን በጎቜንም በሬዎቜንም ኚመቅደስ አወጣ቞ው፣ .....፡፡»

(ኚመድብለ ታሪክ እና ግጻዌ ዹተወሰደ)

ለኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆቜ👇
                •➢ ሌር // SHARE
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
#መጻጉዕ (ዚዐቢይ ጟም አራተኛ ሣምንት)

በዐቢይ ጟም ውስጥ ካሉት ሳምንታት መካኚል አራተኛው እሑድ መጻጉዕ ይባላል፡፡ መጻጉዕ ዚተባለበት ምክንያት በዚሁ ሰንበት ኹዋዜማው ጀምሮ ዹሚዘመሹው ጟመ ድጓ ድውያንን መፈወሱን ዕውራንን ማብራቱን ዚሚያነሣ በመሆኑ ነው፡፡ «38 ዓመት ዚታመመውን መጻጉዕን ኢዚሱስ አዳነው» እንዲሁም ልጁ ዚታመመበት ዚመቶ አለቃው "ጌታዬ በቃልህ እዘዝ ልጄ ይድናል፡፡ በቀ቎ ጣርያ ሥር አንተ ልትገባ አይገባህም" አለው። "ጌታ በሚያልፍበት መንገድ አንድ ዕውር ፈውሰኝ" ብሎ ጮኞ ዚሚመሩት ሰዎቜ ዝም በል አሉት፡፡ ዕውሩ ግን እምቢ ብሎ "ዚዳዊት ልጅ ጌታ ይቅር በለኝ ዕርዳኝ" እያለ ጩኞቱን ቀጠለ፡፡ "በሰንበት ኢዚሱስ መጻጉዕን ተነሥ አልጋህን ተሾኹም ባለው ጊዜ ቀኑ ሰንበት ነበሚ፡፡ መጻጉዕም አልጋውን ተሾክሞ ወደ ቀቱ ገባ ዚእግዚአብሔር ልጅ በሰንበት ፈውሷልና "በሰንበት ድውያንን ፈወሰ ዚዕውራንንም ዓይኖቜ አበራ" እያለ 38 ዓመት በአልጋ ቁራኛ በደዌ ዳኛ ተይዞ ሲማቅቅ ዹኖሹውን መጻጉዕንና ሌሎቹን በልዩ ልዩ ደዌ ዚተያዙትን ሕሙማን መፈወሱን በጠቅላላው ለምፅ ማንጻቱን፣ ዕውር ማብራቱን፣ አንካሶቜን ማርታቱን፣ ልምሟዎቜን ማዳኑን፣ አጋንንትን ማውጣቱን፣ ወዘተ እዚጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ዕለቱና ሳምንቱ መጻጉዕ ተብሏል፡፡

ስለዚህም ይህ ሰንበት ዹሕሙማን ፈውስ መታሰቢያ ዕለት ነው ማለት ይቻላል፡፡ በነዚህ ሁሉ ታሪኮቜ ዚመጻጉዕንና ዚሌሎቹን ሕሙማን ሁሉ ደኅንነት ታሪክ እንሚዳለን፡፡ ዚሰንበቱም ስያሜ ልብ ወለድ አጠራር ሳይሆን ዚቅዱሳት መጻሕፍትን ምሥጢርና ዚጟመ ድጓውን ይትበሀል ተኚትሎ ዹተሰዹመ መሆኑን እንገነዘባለን፡፡

#ዚዕለቱ_ምንባቊቜፊ
1ኛ. ዹቅ.ጳውሎስ መልእክት ወደ ገላ. 5÷1-26
2ኛ. ዹቅ. ያዕቆብ መልእክት 5÷14-20
3ኛ. ዚሐዋርያት ሥራ 3÷1-12

#ዚዕለቱ_ምስባክፊ
መዝ 4ዐ(41)÷3
እግዚአብሔር ይሚድኊ ውስተ ዐራተ ሕማሙ
ወይመይጥ ሎቱ ኵሎ ምስካቀሁ እምደዌሁ
አንሰ እቀ እግዚኊ ተሣሃለኒ።

(እግዚአብሔር በደዌው አልጋ ላይ ሳለ ይሚዳዋል፡፡ መኝታውን ሁሉ በበሜታው ጊዜ ያነጥፍለታል እኔስ አቀቱ ማሚኝ፡፡) መዝ 4ዐ÷3  ዹሚለው ይሆናል፡፡

#ዚዕለቱ_ዹወንጌል፩
በዮሐንስ ወንጌል 5፥1-25 ድሚስ ያለው ነው፡፡

ያንን ተስፋ ያልነበሚውን በሜተኛ ኹደዌ ሥጋው ፈውሶ ሕይወትን ዹሰጠው አምላክ፣ እኛንም በውስጥ በአፍአ ካለብን ደዌ ሥጋና ደዌ ነፍስ እንዲፈውሰንፀ ቁስለ ኃጢአታቜንን እንዲያደርቅልን፣ በሕይወትና በጀና እንዲጠብቀን ዚእርሱ ዚጌታቜ ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን፡፡

ለኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆቜ👇
                •➢ ሌር // SHARE

    
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
●       #ዚግዝት_በዓላት (#ዚማይሰገድባ቞ው_ጊዜያት)

     ዚሚሰገድባ቞ው ጊዜያት እንዳሉት ሁሉ ዚማይሰገድባ቞ው ጊዜያትም አሉ። ዚግዝት በዓላት 5 ሲሆኑ
#ዚወልድ_በዓል፣ #ዚእመቀታቜን_በዓል፣ #ዚቅዱስ_ሚካኀል በዓል፣ #ቀዳሚት_ሰንበትና_እሑድ_ሰንበት ና቞ው። ኹነዚህ በተጚማሪ #ኚቁርባን በኋላና ዹበዓለ #ሐምሳ ወራትም ዚማይሰገድባ቞ው ጊዜያት ና቞ው። እነዚህ ስግደት ዚተገዘተባ቞ው ጊዜያት ዚሚኚተሉት ና቞ው።
         1ኛ      
#በዕለተ_እሑድ

ኹአልቩ ነገር ወይም ኹምንም (ex- nihilo - from nothingness) ሁሉ ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ ጠፍቶ ወደ ምንምነት ሲቀዚር ኹማይጠፉ ኚአምስቱ ፍጥሚታት አንዷ ሰንበት ናት። ጌታ ዚተነሣባት ፣ ዳግምም ዚሚመጣባት ዕለት ናት። በዚህና በሌሎቜ ምክንያቶቜም ሰንበተ ክርስቲያን እሑድ በዓል ነቜ። ስለዚህ በዕለተ እሑድ መስገድ ዹተኹለኹለ ነው።
            2ኛ    
#በዕለተ_ቅዳሜ

    ሌላው ኚዕለታት መካኚል ቅዳሜ ዚግዝት በዓል ተብሎ ዚተመሚጠበት ምክንያት ዹሁሉ ባለቀት ዚሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ዓለማትን ሁሉ በስድስት ቀናት ውስጥ ፈጥሮ ኹፈጾመ በኋላ በሰባተኛው ቀን አሚፈ። ይህቜንም ቀን ቀደሳት ለሰው ልጆቜም በዓል አድርጎ ሰጠን። “በሰንበትም እንደ ትእዛዙ ዐሚፉ።” ሉቃ 23፥56
3ኛ           
#በጌታቜን_በዓላት

    ፍትሐ ነገሥቱ “በእሑድና በተኚበሩት በዓላት ቀን ስግደት አይገባምፀ እነዚህ ዚደስታ ቀኖቜ ናቾውና” (ፍት.መን. አን. 19 ቁ. 715) ካለ በኋላ “ዚተኚበሩት በዓላት” ያላ቞ው ዚትኞቹን እንደሆነ ሲዘሚዝር ትስብእት/ጜንሰት ፣ ልደት ፣ ጥምቀት ፣ ሆሣዕና ፣ ትንሣኀ ፣ ዕርገት ፣ በዓለ ሃምሳ ፣ ደብሚ ታቊር በማለት ኚጌታ ዘጠኝ ዐበይት በዓላት 8ቱን ይገልፃል። ሳይገለፅ ዹቀሹው ስቅለት ነውፀ ያልተገለፀበትም ምክንያት በስቅለት ስግደት ስለማይኚለኚል ነው። ስለዚህ ኚስቅለት በቀር በጌታ ዐበይት በዓላት (በተቀሩት በ8ቱ) ስግደት ዹተኹለኹለ ነው።
4ኛ.           
#በእመቀታቜን_በዓላት

በፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536-537 ድሚስ በጌታ በዓላት መስገድ እንደተኚለኚለው ሁሉ በእመቀታቜን በዓላትም መኹልኹሉን ይጠቁመናል። ዚወልድ በዓልን እንደምናኚብሚው ዚእመቀታቜንንም በዓል በ21 አስበን አንሰግድም። ስለዚህ ወር በገባ በ21 ሁሌም ዚግዝት በዓል ነውፀ አይሰገድበትም።

5ኛ.          
#በቅዱስ_ሚካኀል_በዓል

ዚቅዱስ ሚካኀል በዓል ኚሌሎቜ ዚመላእክት በዓላት ተለይቶ መኚበሩ ለምንድነው ቢሉ

“ዚቅዱስ ሚካኀል በዓል መላእክትን ወክሎ ወርኃዊ ሆኖ እንዲኚበር ታዟል” (በዓላት ፣ ዲ.ን. ብርሃኑ አድማስ ፣ ገጜ 124)። ስለዚህ ቀተ ክርስቲያን በ12 እንዳይሰገድና እንደ ታላላቅ በዓላት በደስታ እንዲኚበር ሥርዐትን ሠርታለቜ።
6ኛ.         
#ሥጋና_ደሙን_ኹተቀበሉ_በኋላ

ዚሥርዐት ምንጫቜን ዹሆነው ፍትሐ ነገሥት አሁንም በዚህ ዙሪያ እንዲህ ብሏልፊ “መስገድን ዚሚተዉባ቞ው ዚታወቁ በዓላት እነዚህ ናቾው
 ሥጋውንና ደሙን ኹተቀበሉ በኋላ” ይላል። ፍት. መን. አን. 14 ቁ. 536- 537። ሥጋውንና ደሙን ኹተቀበልን በኋላ ኚሚሰገድለት እንጂ ኹማይሰግደው ጋር አንድ መሆናቜንን ለማጠዹቅና ለቅዱስ ሥጋውና ለክቡር ደሙ ክብር ስንል ዝቅ ብለን አንሰግድም።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ሌር በማድሚግ ለጓደኞቻቜሁ አካፍሉ።
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
ደብሚ á‹˜á‹­á‰µ
ዚዐብይ ጟም አምስተኛ እሑድ(ሳምንት)
(ዚዐብይ ጟም እኩሌታ)
ደብሚ á‹˜á‹­á‰µ áˆ›áˆˆá‰µ á‹šá‹ˆá‹­áˆ« á‹›á á‹«áˆˆá‰ á‰µ á‰°áˆ«áˆ« áˆ›áˆˆá‰µ áŠá‹á¡á¡á‰Šá‰³á‹ áŠšáŠ¢á‹šáˆ©áˆ³áˆŒáˆ á‰ áˆµá‰°áˆáˆµáˆ«á‰… á‹šáˆšáŒˆáŠ á‹šá‹ˆá‹­áˆ« á‹›á á‹šá‰ á‹›á‰ á‰µ á‰°áˆ«áˆ« áˆ²áˆ†áŠ• áˆµáˆ™áˆ áŠšá‹ˆá‹­áˆ« á‹›á‰:- á‹°á‰¥áˆš á‹˜á‹­á‰µ (ዚወይራ á‹›á á‰°áˆ«áˆ«) á‰ áˆ˜áˆ°áŠ˜á‰µ ተገኝቷል። á‰ á‰…ድስት á‰€á‰° áŠ­áˆ­áˆµá‰²á‹«áŠ“á‰œáŠ• á‹°á‰¥áˆš ዘይት á‰ á‹“ልሆኖ á‹šáˆšáŠšá‰ áˆ­á‰ á‰µ áˆáŠ­áŠ•á‹«á‰µ áŒŒá‰³á‰œáŠ• áˆ˜á‹µáŠƒáŠ’á‰³á‰œáŠ• áŠ¢á‹šáˆ±áˆµ áŠ­áˆ­áˆµá‰¶áˆµ á‰ á‹°á‰¥áˆšá‹˜á‹­á‰µ á‰°áˆ«áˆ« áˆ‹á‹­ áˆ³áˆˆ áˆˆá‰…ዱሳን á‹°á‰€áˆ˜á‹›áˆ™áˆ­á‰± áˆµáˆˆ á‹“ለም ááŒ»áˆœ áŠ¥áŠ“ áˆµáˆˆ á‹³áŒáˆ áˆáŒœáŠ á‰± áˆµáˆ‹áˆµá‰°áˆ›áˆ«á‰žá‹‰ á‰ áŒŒá‰³á‰œáŠ• á‰µáˆáˆ…ርት áˆ˜áˆ áˆšá‰µ áŠáŒˆáˆš áˆáŒœáŠ á‰±áŠ• áŠ¥áŠ•á‹µáŠ“áˆµá‰³á‹áˆµ á‹ˆá‹­áˆ áŠ¥á‹«áˆ°á‰¥áŠ• áŠ¥áŠ•á‹µáŠ•á‹˜áŒ‹áŒ… áˆˆáˆ›á‹µáˆšáŒ áŠá‹á¢

ስለ ዓለም መጚሚሻና ስለ ዳግም ምጜአቱ ምልክቶቜ ምን እንደሆኑ ሐዋርያው ቅዱስ ማ቎ዎስ ወንጌል ላይ በሊስት መሠሚታዊ ክፍሎቜ ኹፍሎ ጜፎልናል፡፡

፩. ሃይማኖታዊ áˆáˆáŠ­á‰¶á‰œ

"እኔ áŠ­áˆ­áˆµá‰¶áˆµ áŠáŠ áŠ¥á‹«áˆ‰ á‰ áˆµáˆœ á‹­áˆ˜áŒ£áˆ‰á€ á‰¥á‹™á‹Žá‰œáŠ•áˆ á‹«áˆµá‰³áˆ‰" /ማቮ 24፥5/፡፡

፪. ፖለቲካዊ áˆáˆáŠ­á‰¶á‰œ

“ጩርንም á‹šáŒŠáˆ­áŠ•áˆ á‹ˆáˆ¬ á‰µáˆ°áˆ™ á‹˜áŠ•á‹µ áŠ áˆ‹á‰œáˆá€ á‹­áˆ… áˆŠáˆ†áŠ• áŒá‹µ áŠá‹áŠ“ á‰°áŒ á‰ á‰â€ /ማቮ 24፥6/ “ሕዝብ á‰ áˆ•ዝብ áˆ‹á‹­ áˆ˜áŠ•áŒáˆ¥á‰µáˆ á‰ áˆ˜áŠ•áŒáˆ¥á‰µ áˆ‹á‹­ á‹­áŠáˆ£áˆáŠ“â€ /ማቮ 24፥7/

፫. ተፈጥሯዊ áˆáˆáŠ­á‰¶á‰œ

“ራብም á‰žáŠáˆáˆ­áˆ á‹šáˆá‹µáˆ­ áˆ˜áŠ“á‹ˆáŒ¥ á‰ áˆá‹© áˆá‹© áˆµááˆ« á‹­áˆ†áŠ“áˆâ€ /ማቮ.24፥7/

ኹላይ ያዚና቞ውን ምልክቶቜ በዓለማቜን ላይ ዕለት ተዕለት ዹምናዹው ዹምንሰማው ዚአደባባይ ምስጢር ነው፡፡ ጌታቜን ለደቀመዛሙርቱ ዚነገራ቞ውን ምልክቶቜ ዚቀተ ክርስቲያናቜን አራት አይና ሊቃውንት ዹወንጌሉን ገጾ ንባብ እንዲህ ብለው ያመሰጥሩታል፡፡

“እነዚህ áˆáˆ‰ á‹šáˆáŒ¥ áŒ£áˆ­ áˆ˜áŒ€áˆ˜áˆªá‹«á‹Žá‰œ áŠ“á‰žá‹â€ /ማቮ.24፥8/

ምጥ ሲመጣ አስቀድሞ ዚምጡ መጀመሪያ ሕመም (ጣር) እንዳለ ሁሉ ዹዓለምም ፍጻሜ በጣር ነው ዚሚጀምሚው። ይህንንም ጌታቜን በግልጜ አስሚድቶናልፊ ጩርና ዹጩር ወሬ መሰማት፣ ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ መነሳት፣ ርሃብም ቾነፈርም ዚምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ መታዚት ለዓለም ፍጻሜ ዚምጥ ጣር መጀመሪያዎቜ ና቞ዉ። እነዚህ ነገሮቜ በሁሉም ቊታ በአንድ ጊዜ ላይኚሰቱ ይቜላሉፀ ነገር ግን በልዩ ልዩ ቊታዎቜ ለብዙ ዘመናት ታይተዋልፀ እዚታዩም ና቞ው።

“ስለ áˆµáˆœ á‰ áŠ áˆ•á‹›á‰¥ áˆáˆ‰ á‹šá‰°áŒ áˆ‹á‰œáˆ á‰µáˆ†áŠ“áˆ‹á‰œáˆâ€ /ማቮ.24፥9/

ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ "ስለ ስሜ ክርስቲያኖቜ በመሆናቜሁ በዓለም ዘንድ ትጠላላቜሁ" ብሎናል። ዓለም ክፉ ስለሚሠራ ዚጥሩ ነገር ተቃራኒ ሆኖ ለብዙ ዘመናት ቆይቷል። ጌታቜን â€œá‰¥áˆ­áˆƒáŠ•áˆ á‹ˆá‹° á‹“ለም áˆµáˆˆáˆ˜áŒ£ áˆ°á‹Žá‰œáˆ áˆ¥áˆ«á‰žá‹ áŠ­á‰ áŠá‰ áˆ­áŠ“ áŠšá‰¥áˆ­áˆƒáŠ• á‹­áˆá‰… áŒšáˆˆáˆ›áŠ• áˆµáˆˆá‹ˆá‹°á‹± ááˆ­á‹± á‹­áˆ… áŠá‹á¢ áŠ­á‰ á‹šáˆšá‹«á‹°áˆ­áŒ áˆáˆ‰ á‰¥áˆ­áˆƒáŠ•áŠ• á‹­áŒ áˆ‹áˆáŠ“á£áˆ¥áˆ«á‹‰áˆ áŠ¥áŠ•á‹³á‹­áŒˆáˆˆáŒ¥ á‹ˆá‹° á‰¥áˆ­áˆƒáŠ• áŠ á‹­áˆ˜áŒ£áˆá€ áŠ¥á‹áŠá‰µáŠ• á‹šáˆšá‹«á‹°áˆ­áŒ áŒáŠ• áˆ¥áˆ«á‹ á‰ áŠ¥áŒá‹šáŠ á‰¥áˆ”áˆ­ á‰°á‹°áˆ­áŒŽ áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ á‹­áŒˆáˆˆáŒ¥ á‹˜áŠ•á‹µ á‹ˆá‹° á‰¥áˆ­áˆƒáŠ• á‹­áˆ˜áŒ£áˆâ€ /ዮሐ. 3፥19-21/ እንዳለን በክፉ ሥራ ውስጥ ያለው ይህ ዓለም በጎ ሥራ ዚሚሠሩትን ዚክርስቶስን ተኚታዮቜ ይጠላል። ጹለማ ብርሃንን ብርሃንም ጹለማን እንደሚጠላፀ ይህ ዓለም እኛን እንዲጠላን፣ እኛ ክርስቲያኖቜ ደግሞ ይህንን ዓለም ልንጠላው ይገባል።
አሁን ባለንበት ዘመን ክርስትና እዚተጠላ፣ እዚተናቀ ነው ያለው። â€œá‰£á‹°áŒ‰á‰µâ€ á‹“ለማት ባዶ አብያተ መቅደሶቜ ቀርተው እነሆ እንመለኚታ቞ዋለንፀ ትውልዱ በዓለም ስሜትና በሥጋ ፈቃድ ብቻ እዚሔደ ነው። ክርስቲያን ነን በሚሉትም አውሮፓውያን ዘንድ ዚአንገት በላይ ዚማስመሰል ክርስትና እንጂ እንደ ቅዱስ ቃሉ ዹሚጓዝ አማኝ ማግኘት አይቻልም። እውነተኞቜ አይወደዱምፀ ይገፋሉፀ ይናቃሉ። ሁኔታው ዹዘመኑ ፍጻሜ እጅግ እዚቀሚበ መምጣቱን በእርግጥ ያስሚዳል።
ጌታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ኹዚህም በላይ “ስለ ስሜ ለመኚራ አሳልፈው ይሰጧቜኋልፀ ይገድሏቜሁማል” ብሏል። ክርስቲያን በመሆናቾው ብቻ ማንንም ሳይበድሉ ኹዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ በልዩ ልዩ ሀገራት ክርስቲያኖቜ ሰማዕትነትን እስኚ አሁን ድሚስ እዚተቀበሉ ነው፡፡ቅዱስ ጳዉሎስ  â€œáˆµáˆˆ áŠ áŠ•á‰° á‰€áŠ‘áŠ• áˆáˆ‰ áŠ¥áŠ•áŒˆá‹°áˆ‹áˆˆáŠ•á€ áŠ¥áŠ•á‹°áˆšá‰³áˆšá‹± á‰ áŒŽá‰œ á‰°á‰†áŒ áˆ­áŠ•â€ /ሮሜ 8፥36/ እንዳለው። ይህ በቅዱሱ በክርስቶስ ስም መጠላትና መኚራ መቀበል ኹዓለም ዹሚጠበቅ ዚፍጻሜዉ ዘመን ምልክት መሆኑን አውቀን መዘጋጀትና ኚሐዋርያው ጋር â€œá‰ á‹šáˆ… áˆáˆ‰ áŒáŠ• á‰ á‹ˆá‹°á‹°áŠ• á‰ áŠ¥áˆ­áˆ± áŠšáŠ áˆžáŠ“áŠá‹Žá‰œ áŠ¥áŠ•á‰ áˆáŒ£áˆˆáŠ•â€ /ሮሜ 8፥37/ እያልን በእምነታቜን ጾንተን መጋደል ይገባናል።

ዚክርስቲያኖቜ ቁጥር እያነሰ መምጣት፣ ዚአብያተ ክርስቲያናት መዘጋት፣ ሰው ሰው ዚሚያሰኘውን ክብርና ሞገስ ትቶ በግብሩ እንስሳትን ሲመስል ዚቅድስና ሕይወት ሲጠላና ሲናቅፀ በአንጻሩ ደግሞ ዹሰው ልጅ ለሹኹሰው ለዚህ ዓለም ምኞትና ፈቃድ ሲገዛ ስናይ ዹዚህ ዓለም ፍጻሜ ጊዜው እዚደሚሰ መሆኑን አውቀንፀ ኖኅ በብዙ ኃጢአተኞቜ መካኚል ቢኖርም ራሱን በቅድስና ጠብቆ እንደኖሚ /ዘፍ.6-8/ፀ ሎጥም እንዲሁ በብዙ ኃጢአተኞቜ መካኚል ሲኖር በነርሱ ኃጢአት እንዳልተባበሚ /ዘፍ. 19/ ኹዚህ ዓለም ክፉ ሥራ ተለይተን ራሳቜንን በቅድስና በመጠበቅ እንጋደል። ዓለሙ ስለ እምነታቜን ቢጠላንም እኛም ስለ ክፉ ሥራው ንቀነው መኖር ዚግድ መሆኑን እንወቅ እንጂ ስለ እምነት፣ ስለ ቅድስናም ኹዓለም በጎ ነገር አንጠብቅ። በተለያዩ ሁኔታዎቜ ዚሚደርሱብንን ፈተናዎቜ ሁሉ በትዕግስት እንቀበላ቞ው እንጂ በማማሹር አንዘንፀ ምክንያቱም ስለ ስሜ በዓለም ዘንድ ዚተጠላቜሁ ትሆናላቜሁ ተብለናልና።

“ዚጥፋትን áˆ­áŠ©áˆ°á‰µ á‰ á‰°á‰€á‹°áˆ°á‰œá‹ áˆµááˆ« á‰†áˆž áˆµá‰³á‹© áŠ áŠ•á‰£á‰¢á‹ á‹«áˆµá‰°á‹áˆ!” áˆ›á‰Ž.24፥15/

ዓለም ራሱን በማርኚስ ብቻ ሳይወሰን በፍጻሜ ዘመን በተቀደሰው ስፍራ እንኳን ሳይቀር ዚጥፋትን ርኩሰት ያቆማል። ዹተቀደሰው ስፍራ ዚተባለው በተቀደሰ ሃይማኖት ዚሚኖሩትን ሀገራት፣ ሕዝቊቜ ዚሚመለኚት ነው። እንደ ኢትዮጵያ ዚመሳሰሉትን ሀገራት ዲያብሎስ በመልእክተኞቹ ላይ አድሮ በብዙ ርኩሰት ተፈታትኗ቞ዋልፀ እዚተፈታተና቞ውም ነው። ዚዚሀገራቱን እምነትና ታሪክ ለማጥፋት ጥሯልፀ ብዙውንም ዚቅድስና ሥርዓት በርዟልፀ ዚቻለውንም ኚነጭራሹ አጥፍቶታል። አሁን እንኳ አምልኮተ እግዚአብሔር በሚፈጞምባ቞ዉ ቅዱሳት መካናትና ገዳማት ሳይቀር በልዩ ልዩ ምክንያት ዚጥፋት ርኩሰት አዉጇል። ይህም ዚፍጻሜ ዘመኑ አንዱ ምልክት ስለሆነ አንባቢዉ ያስተዉል እንደተባለ ዹዘመኑን መፍጠን ዹጊዜውን መድሚስ በመሚዳት መዘጋጀት ይገባናል።

“ብዙ áˆáˆ°á‰°áŠ›á‹Žá‰œ áŠá‰¢á‹«á‰µáˆ á‹­áŠáˆ£áˆ‰ á‰¥á‹™á‹Žá‰œáŠ•áˆ á‹«áˆµá‰³áˆ‰â€ /ማቮ.24፥11/፡፡

ብዙ ሐሰተኞቜ ነቢያት በዹዘመኑ ተነስተው እውነተኛይቱን
ቀተ ክርስቲያን ታግለዋታልፀ ሊያጠፏት ባይቜሉም እንኳን ብዙ ልጆቿን ነጥቀው ወስደውባታል። ዹነዚህን ሐሰተኞቜ ሠራተኞቜ አመጣጥ ኚባድ ዚሚያደርገው በተአምራትና በድንቅ ምልክቶቜ መምጣታ቞ው ነው። ጌታቜን እንደተናገሚ â€œá‰¢á‰»áˆ‹á‰žá‹áˆµ á‹šá‰°áˆ˜áˆšáŒ¡á‰µáŠ• áŠ¥áŠ•áŠ³áŠ• áŠ¥áˆµáŠªá‹«áˆµá‰± á‹µáˆšáˆµ á‰³áˆ‹áˆ‹á‰… áˆáˆáŠ­á‰µáŠ“ á‹µáŠ•á‰… á‹«áˆ³á‹«áˆ‰â€ /ማቮ.24፥24/ ስለዚህ በምትሐታዊ ምልክቶቻ቞ው ዚብዙ ዹዋሐንን ልብ በማታለል ኹተቀደሰ እምነታ቞ው እያስኮበለሉ አጥፍተዋ቞ዋልፀ በማጥፋትም ላይ ይገኛሉ። ስለዚህም ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ  â€œá‹ˆá‹³áŒ†á‰œ áˆ†á‹­ áˆ˜áŠ•áˆáˆµáŠ• áˆáˆ‰ áŠ á‰µáˆ˜áŠ‘ áŠáŒˆáˆ­ áŒáŠ• áˆ˜áŠ“ááˆµá‰µ áŠšáŠ¥áŒá‹šáŠ á‰¥áˆ”áˆ­ áˆ†áŠá‹‰ áŠ¥áŠ•á‹°áˆ†áŠ áˆ˜áˆ­áˆáˆ©â€/1ዮሐ 4፥1-3/ አለን።
ቅዱስ ጳዉሎስም “ዚክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳ቞ዉን እዚለወጡ ውሞተኞቜ ሐዋርያትና ተንኮለኞ ሠራተኞቜ ና቞ው። ይህም ድንቅ አይደለም ሰይጣን ራሱ ዚብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለዉጣልና” ብሏል /2ቆሮ.11፥13-15/። ሐዋርያት ሁሉ በዚመልእክቶቻ቞ው ኚሐሰተኞቜ አስተማሪዎቜ እንድንጠበቅ ደጋግመው አሳስበዋል። ብዙ ሰው ግን በዚዋሕነት ስለሚጓዝ ዹነዚህ ተኩላዎቜ ሰለባ ሆኗል።
ጊዜው ክፉ ነውና ዚሐሰተኞቜ ነቢያት መሚብ ጠልፎ ወደ ሐሰተኞቜ ክርስቶሶቜ እንዳይወስደን በጥንቃቄ መጓዝ ይጠበቅብናል። ሐዋርያዉ ቅዱስ ይሁዳም በመልእክቱ ቁ3  â€œáˆˆá‰…ዱሳን áŠ áŠ•á‹µ áŒŠá‹œ áˆáŒœáˆž áˆµáˆˆá‰°áˆ°áŒ  áˆƒá‹­áˆ›áŠ–á‰µ áŠ¥áŠ•á‹µá‰µáŒ‹á‹°áˆ‰ áŠ¥á‹šáˆ˜áŠšáˆ­áŠ³á‰œáˆ áŠ¥áŒœááˆ‹á‰œáˆ á‹˜áŠ•á‹µ áŒá‹µ áˆ†áŠá‰¥áŠâ€ áˆ²áˆ እንደመኚሚን በተቀደሰ እምነታቜን እስኚመጚሚሻ ጾንተን እንጋደል።

በቅዳሎ ጊዜ ዚሚነበቡ ጥቅሶቜፊ
-፩ኛ ተሰ ፬፥፲፫ እስኚ ፍጻሜ
-፪ኛ ጎጥ ፫፥፯-፲፭
-ዹሐዋ ሥራ ፳፬፥፩-፳፪

ምስባኩምፊ መዝ ፵፱፥፫
"እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጜዕ ወአምላክነሂ ኢያሚምም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ"
"እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል አምላካቜን ይመጣል ዝምም አይልም እሳት በፊቱ ይቃጠላል"

ወንጌሉም፩ ማቮ ፳፬፥፩-ፎ፮
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
🔔✝ ኚመምህራን ዹማንን ትምህርት ማግኘት ይፈልጋሉ?👇

┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ምሕሚተአብ አሰፋ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዘበነ ለማ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ሄኖክ ኃይሌ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዮርዳኖስ አበበ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 አባ ገብሚ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ያሚጋል አበጋዝ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መጋቢ ሐዲስ እሞቱ አለማዹሁ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር እዮብ ይመኑ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር ገብሚ እግዚአብሔር
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር አባ ገብሚ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛

🔗ዚሁሉንም መምህራን ትምህርት ለማግኘት🔔
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧
#ገብር_ኄር
(
#ዚዐቢይ_ጟም_ስድስተኛ_ሳምንት)

ዚዐቢይ ጟም ስድስተኛው እሑድ ወይም ሳምንት ገብር ኄር ይባላል፡፡ በዚህ ሳምንት ዹሚዘመሹው ዝማሬ፣ ዹሚሰበኹው ስብኚት፣ ዹሚሰጠው ትምህርት ገብርኄርን ዚሚያወሳ ነው። ማለትም ስለ ታማኝ አገልጋይ ነው፡፡

ዹማቮ.25፥14-25 ዹሚነግሹን ይህን ነው፩ “አንድ ባዕለ ጾጋ ሰው ባሪያዎቜን ጠርቶ ለአንዱ አምስት መክሊት ሰጠው፣ ሁለት መክሊት ዹሰጠውም አለ፣ አንድ መክሊትም ዹሰጠው አለ፡፡ ኹዚህ በኋላ ወደሩቅ አገር ሄደ፡፡ አምስት መክሊት ዹተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት አትርፎ አስር አደሚገ፡፡ ሁለት ዹተቀበለውም አትርፎ አራት አደሚገ፡፡ አንድ ዹተቀበለው ግን ሄዶ መሬቱን ቆፍሮ በሻሜ ጠቅልሎ ዚጌታውን መክሊት ቀበራት፡፡

ኚብዙ ጊዜ በኋላ ጌታ቞ው መጥቶ ተቆጣጠራ቞ው፡፡ አምስት መክሊት ዹተቀበለው ቀርቩ ጌታዬ አምስት መክሊት ሰጥተኞኝ ነበር እነሆ አምስት አተሚፍኩ አለው፡፡ “ገብርኄር ወምዕመን ዘበሁድ ምዕምነ ኮንኚ ዲበ ብዙህ እሰይመኚ ባዕ ውስተ ፍስሐሁ ለእግዚእኚ” “አንተ ታማኝ ባሪያ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሟምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡ ሁለት ዹተቀበለውም ቀርቩ ጌታዬ ሁለት መክሊት ሰጥተኞኝ ነበር እነሆ ወጥቌ ወርጄ ሌላ ሁለት አትርፌ አራት አድርጌአለሁ፡፡ “አንተ ታማኝ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ታምነሃል በብዙ እሟምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ” አለው፡፡ አንድ መክሊት ዹተቀበለው ግን ቀርቩ “ጌታዬ አንተ ክፉና ጚካኝ ካልዘራህበት ዚምታጭድ ካልበተንህበት ዚምትሰበስብ እንደሆንክ ስለአወቅሁ መሬቱን ቆፍሬ ቀበርኋት እነኋት መክሊትህ” አለው፡፡ “አንተ ሰነፍ ባሪያ መክሊቮን በጊዜ ልትሰጠኝ በተገባህ ነበር እኔም ወጥቶ ወርዶ ለሚያተርፍ በሰጠሁት ነበር”፡፡ ኑ ዹዚህን ሀኬተኛ መክሊት ውሰዱና አስር መክሊት ላለው ስጡት፡፡ ላለው ይሰጡታል ይጚመርለታል ለሌለው ግን ያለውን ይቀሙታል፡፡ ኑ ይህን ሰነፍና ሃኬተኛ ባሪያ እጅ እግሩን አሥራቜሁ ጜኑዕ ጹለማ ወደአለበት ውሰዱት ጩኞትና ጥርስ ማፋጚት ወዳለበት ጚምሩት” አለ ማቮ. 25፥14-25፡፡

ባለ ጾጋ ዚተባለው ጌታ ነው፡፡ መክሊት ዚተባለው ልዩ ልዩ ዚአገልግሎት ጾጋ ነው፡፡ ያተሚፉት በሚገባ በታማኝነት ያገለገሉ ቅዱሳን ሰዎቜ ናቾው መክሊቱን ዹቀበሹው ደግሞ በታማኝነት በተሰጠው ጾጋ ማገልገል ሲገባው ያላገለገለ ነው፡፡ ጌታ቞ው ሊቆጣጠራ቞ው መጣ ማለት በዕለተ ምጜአት ለሁሉም በአገለገለው አገልግሎት ዋጋ ለመስጠት እንደሚመጣ ያሳዚናል፡፡ ያገለገሉትን ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አላቾው ማለት ታማኝ አገልጋዮቜ መንግሥተ ሰማያትን ይወርሳሉና፡፡ ሰነፎቜ ደግሞ ጥርስ ማፋጚት ስቃይ ጜኑዕ ጹለማ ባለበት ሲዖል መግባታ቞ውን ዚሚያሳይ ነው፡፡

#ዹዕለተ_ሰንበት_መዝሙር_ኚጟመ_ድጓ
መኑ ውእቱ ገብር ኄር ወምእመን ዘይሹክቩ እግዚኡ በምግባሚ ሠናይ ወይሠይሞ ዲበ ኲሉ ንዋዩ ካዕበ ይቀሎ እግዚአብሔር ገብር ኄር ወምእመን ዘበውኁድ ምእመነ ኮንኚ ዲበ ብዙኅ እሠይመኚ ባእ ውስተ ፍሥሐሁ ለእግዚእኚ፡፡

ትርጉምፊ ጌታው በመልካም ሥራ ዚሚያገኘው በሐብቱ ኹሉ ላይ ዚሚሟመውፀ ዚታመነ በጎ አገልጋይ ማን ነው? ዳግመኛም እግዚአብሔር አንተ ዚታመንክ በጎ አገልጋይ በጥቂቱ ዚታመንህ ስለኟንህ በብዙ እሟምሃለሁ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ ይለዋል፡፡

#መልዕክታት
2ኛ ጢሞ.2÷1-15
"ልጄ ሆይ÷ አንተም በጌታቜን በኢዚሱስ ክርስቶስ ጾጋ በርታ፡፡ በብዙ ምስክሮቜ ፊት ኚእኔ ዹሰማኾውን ትምህርት ለሌሎቜ ሊያስተምሩ ለሚቜሉ ለታመኑ ሰዎቜ እርሱን አስተምራ቞ው፡፡ ኢዚሱስ ክርስቶስን እንደሚያገለግል በጎ አርበኛ ሆነህ መኚራ ተቀበል፡፡" (ተጚማሪ ያንብቡ)

1ኛ ጎጥ.5÷1-11
"እንግዲህ እኔ ኚእነርሱ ጋር ሜማግሌ÷ ዚክርስቶስም መኚራ ምስክር÷ ደግሞም ሊገለጥ ካለው ክብር ተካፋይ ዹሆንሁ በመካኚላ቞ው ያሉትን ሜማግለዎቜን እማልዳ቞ዋለሁ፡፡ በእናንተ ዘንድ ያሉትን ዚእግዚአብሔርን መንጋዎቜ ጠብቁፀ ስትጠብቁአ቞ውም እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በውድ እንጂ በግድ አይሁንፀ በበጎ ፈቃድ እንጂ መጥፎውን ሚብ በመመኘትም አይሁን፡፡" (ተጚማሪ ያንብቡ)

#ግብሚ_ሐዋርያት
ዹሐዋ.1÷6-8
"እነርሱም ተሰብስበው ሳሉ÷ "ጌታ ሆይ÷ በዚህ ወራት ለእስራኀል ልጆቜ መንግሥትን ትመልሳለህን?” ብለው ጠዚቁት፡፡ እርሱም መልሶ እንዲህ አላ቞ው÷ “አብ በገዛ ሥልጣኑ ዹወሰነውን ቀኑንና ዘመኑን ልታውቁ አልተፈቀደላቜሁም፡፡ ነገር ግን መንፈስ ቅዱስ በእናንተ ላይ በወሹደ ጊዜ ኅይልን ትቀበላላቜሁፀ በኢዚሩሳሌምና በይሁዳ ሁሉ፣ በሰማሪያና እስኚ ምድር ዳርቻ ድሚስም ምስክሮ቞ ትሆኑኛላቜሁ።"

#ምስባክ
መዝ. 39÷8
"ኹመ እንግር ፈቃደኹ መኚርኩ አምላኪዚ፡፡ ወሕግኹኒ በማዕኹለ ኚርሥዚ፡፡ ዜኖኩ ጜድቀኚ በማኅበር ዐቢይ፡፡"

ትርጉምፊ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ለማድሚግ መኚርሁ፥ ሕግህም በልቀ ውስጥ ነው። በታላቅ ጉባኀ ጜድቅህን አወራሁ

#ወንጌል
ማቮ. 25÷14-30
“መንገድ እንደሚሄድ÷ አገልጋዮቹንም ጠርቶ ሊያተርፉበት ገንዘቡን እንደ ሰጣ቞ው ሰው እንዲሁ ይሆናልናፀ ለእያንዳንዱ እንደ ቜሎታው ለአንዱ አምስት÷ ለአንዱ ሁለት÷ ለአንዱም አንድ ሰጠና ወዲያውኑ ሄደ፡፡” (ተጚማሪ ያንብቡ)

#ዚዕለቱ_ቅዳሎ ➛ ቅዳሎ ባስልዮስ

https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
       ❍ㅀ         ⎙          âŒ²         ♡
  ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ      ˢᵃᵛᵉ      ˢʰᵃʳᵉ      ˡᶊᵏᵉ   
ሆሣዕና
ዚዐብይ ጟም ስምንተኛ እሑድ(ሳምንት)

ሆሣዕና ኚጌታቜን አምላካቜን ኹዘጠኙ ዓበይት በዓላት አንዱ ነው፡፡ ጌታቜን áŠ áˆáˆ‹áŠ«á‰œáŠ• መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ኚኢዚሩሳሌም á‹ˆá‹°  ቀተ áˆ˜á‰…ደስ áˆˆáˆ˜áŒá‰£á‰µ á‰ áˆáˆˆáŒˆ ጊዜ á‹°á‰€ መዛሙርቱን á‹ˆá‹° ፊታቜው ባለው ሀገር "ሂዱና አህያ ኹውርጭላዋ ጋራ ታስራ ታገኛላቜው ፈታቜው እምጡልኝ። 'ምን ታደርጋላቜሁ?'  ዚሚላቜሁ  ሰው  ካለ  'ጌታ቞ው  ይፈልጋቾዋል'  በሉ"  ብሎ  ላካ቞ው  ኹዚህ  በኋላ  ደቀ  መዛሙርቱ እንዳዘዛ቞ው  ሄደው  ፈተው  አመጡለት  በዚያም  ዚተሰበሰቡት  ሁሉ  በአህዮቜ  ላይ  ልብሳ቞ውን  ጎዘጎዙለት  ጌታቜንም በሁለቱ  አህዮቜ  ላይ  ተቀመጠ  ኚሌሎቹ  እንስሳት  አህዮቜን  መርጩ  በአህዮቜ  ተቀምጧል፡ አህዮቜ  በመጜሐፍ  ቅዱስ ብዙ ታሪክ አላ቞ውና።

✅ዹበልአም አህያ ዚመልአኩን ክብር ለመግለጥ አፍ አውጥታ ተናግራለቜ። (ዘሁል 22+28)
✅ጌታቜን በተወለደ ጊዜ አህዮቜ ኚኚብቶቜ ጋር በበሚት እስትፋሳ቞ውን ገብሚዋል። (ቅዳሎ ማርያም)
ዚሆሣዕና እህዮቜ ኹሁሉ ተመርጠው አምላካቜን ተቀምጊባ቞ዋል: 'ለምን ዚተዋሚዱት አህዮቜን መሹጠ?' ቢባል:-
፩. ደመናን አዝዞ : ነፋስን ጠቅሶ : በእሳት  መንኮራኩር ላይ ዚሚሚማመድ አምላክ ሲሆን ነገር  ግን ዚመጣው ትሕትናን  ለማስተማር : ዚትሕትና  ጌታ  መሆኑን  ለመግለጜ ነውና በአህያ ተቀመጠ።
፪.  ትንቢቱን  ለመፈጾም  <<አንቺ  ዚጜዮን  ልጅ  ሆይ  እጅግ  ደስ  ይበልሜ  አንቺ  ዚኢዚሩሳሌም  ልጅ  ሆይ  እልል  በዪ  እነሆ  ንጉሥሜ  ጻድቅና አዳኝ  ነው  ትሁትም  ሁኖ  በአህያም  በውርንጭላቱ  ላይ  ተቀምጩ  ወደ  አንቺ  ይመጣል  ሰሹገላውንም  ኚኀፍሬም ፈሚሱንም ኚኢዚሩሳሌም ያጠፋል>> ብሎ ዘካርያስ ትንቢት ተናግሮ ነበርና ለመፈጾም ነው። ዘካ ፱÷፩
፫.  ምሳሌውን  ለመግለጜ
ምሳሌ-  ቀድሞ  ነቢያት  ዘመነ  ጞብእ  ኹሆነ  በፈሚስ  ተቀምጠው  ዘገር  ነጥቀው  ይታያሉ  ዘመነ  ሰላም  ኹሆነ  በአህያ ተቀምጠው መነሳንስ ይዘው ይታዩ ነበርና ጌታቜንም ዘመነ ሰላም ነው ሲል በአህያ ተቀምጩ መጥቷል።
፬.  ምሥጢሩን  ለመግለጜ
ምሥጢር-  በአህያ  ዹተቀመጠ  ሞሜቶ  አያመልጥም  አሳዶም  አይዝም  እሱም  ካልፈለጋቜሁኝ  አልገኝም  ኚፈለጋቜሁኝ አልታጣም ሲል በአህያ ተቀምጩ መጥቷል።
ህድግት ዚእስራኀል ምሳሌ ህድግት ቀንበር መሾኹም ዚለመደቜ ናት= እስራኀልም ህግ መጠበቅ ለምደዋልና
እዋል  ዚአህዛብ  ምሳሌ
እዋል  ቀንበር መሾኹም አልለመደቜም=አህዛብም ህግ መጠበቅ አልለመዱምና  (አንድም)  ህድግት  ዚኊሪት  ምሳሌ ህድግት ቀንበር መሾኹም እንደለመደቜ=ኊሪትም ዚተለመደቜ ህግናትና
እዋል  ዹወንጌል ምሳሌ
እዋል  ቀንበር መሾኹም አልለመደቜም=ወንጌልም ያልተለመደቜ አዲስ ህግ ናትና
በሁለቱም ላይ መቀመጡ ኊሪትንም ወንጌልንም ዚሰራሁ እኔ ነኝ ሲል ነው፡፡ ኚኢዚሩሳሌም እስኚ ቀተ መቅደስ ፲፮ ምእራፍ ነው ፲፬ቱን ምእራፍ በእግሩ ሂዶ ሁለቱን ምእራፍ በአህያይቱ ሂዷል በውርጭላይቱ ሁኖ ፫ ጊዜ ቀተ መቅደሱን ዙሯል ፲፬  ምእራፍ ዚአስርቱ  ትእዛዛትና  ዚአራቱ ኪዳናት ምሳሌፀ አስሩ  ምእራፍ ዚአስርቱ ትአዛዛት፣ አራቱ  ምእራፍ ዚአራቱ ኪዳናት ምሳሌ ነው፣ አራቱ  ኪዳናት ዚሚባሉት እነዚህ ናቾው፩ ኪዳነ  ኖህ  :  ክህነተ  መልኹ  ጌዎቅ  :ግዝሹተ  አብርሀም  እና ጥምቀተ ዮንሐስ ና቞ው፡፡
በአህያይቱ  ላይ ልብሳ቞ውን አንጥፈውለታል::
ልብስ  በአካል ያለውን ነውር ይሾፍናል አንተም ኚባ቎ አበሳ ነህ  ሲሉ።
በአህያዋ  ላይ  ኳርቻ  ሳያደርጉ  ልብስ  አንጥፈውለታል :-
ኳርቻ  ይቆሚቁራል  ልብስ  አይቆሹቁርም  ዚማትቆሚቁር  ህግ ሰራህልን  ሲሉ  ነው። 
ስለምን ልብሳ቞ውን አነጠፉለት ቢባል ? በእዩ  ልማድ ነው ፡
እዩ  ዚተባለው  ሰው  በእስራኀል  ላይ  ሲነግሥ  እስራኀል  ልብሳ቞ውን  አንጥፈውለት  ነበሹና  በዚያ  ልማድ አንጥፈውለታል እኩሌቶቱ ደግሞ ዘንባባ አንጥፈውለታል ። 🌎
በዕለተ  ሆሳዕና  እስራኀላውያን  ለምን  ዚዘንባባ  ዝንጣፊፀ  ዹቮምር  ዛፍ  ዝንጣፊ  እና  ዚወይራ  ዛፍ  ዝንጣፊ  ይዘው  ዘመሩ?  (ማቮ. á³á©Ã·á©-፲፯፣  ማር. ፲፩÷፩-፲፣  ሉቃ.  ፲፱÷፳፱-ፎ፰፣  ዮሐ. ፲፪÷፲፪-፲፭)
ዚዘንባባ ዝንጣፊ
✅ ዘንባባ ዚድል ምልክት ዚደስታ መግለጫ ዚምስጋና መስጫ ነው፡፡
✔ይስሃቅ  በተወለደ  ጊዜ  አብርሃም ደስ ብሎት ዘንባባ ይዞ እግዚአብሄርን አመስግኖበታል።
✔ይስሐቅም ያእቆብን በወለደ ጊዜ    አምላኩን በዘንባባ አመስግኗል።
✔እስራኀል  ኚግብጜ  በወጡ  ጊዜ  በዘንባባ  ንሎብሆ  እያሉ  እህተ  ሙሮ  ማርያም  ኚበሮ  እዚመታቜ  አምላካ቞ውን አመስግነዋል፡፡
✔ዮዲት  እስራኀልን  እዚገደለ  ያስ቞ገሚው  ሆለፎርኒስን  አንገቱን  ቆርጣ  በገደለቜው  ጊዜ  እስራኀል  ዮዲት  መዋኢት  ዮዲት ኀያሊት  ብለው በዘንባባ አመስግነዋታልና።
✅ዘንባባ ደርቆ እንደገና ህይወት ይዘራል ዹደሹቀ ሕይወታቜንን ዚምታለመልም አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
✅ዘንባባ ዹሰላም ምልክት ነው ዹሰላም አምልክ ነህ ሲሉ ነው።
✅ዘንባባ እሟሃማ ነው አንተ ህያው አሾናፊ አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
✅ዘንባባ እሳት አይበላውም ለብልቊ ይተወዋል እንጅ ጌታም አንተ ባህርይህ ዹማይመሹመር ነው ሲሉ ነው።
✅ዘንባባ  ዚነፃነት  ምልክት  ነው  ኚባርነት  ነፃ  ዚምታወጣን  አንተነህ  ሲሉ  ነው  አኛም  ይህን  በማሰብ  ዘንባባ  ይዘን ሆሳእና  በአርያም  እያልን እለቱን  እናስባለን፡፡
ዹቮምር ዛፍ ዝንጣፊ
✅ዹቮምር ዛፍ ፍሬ ጣፋጭ ነው፩ በሃጥያት ዹመሹሹውን ህይወታቜንን ዚምታጣፍጥልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
✅ ዹቮምር  ፍሬ  ዹሚገኘው  ኹዛፉ  ኚፍታ  ላይ  ነው:-  አንተ  አምላካቜን  ልዑለ  ባህሪ  ነህ  ኹፍ  ኹፍ  ያልክ  አምላክ  ነህ  ሲሉ ነው።
✅ ዹቮምር ዛፍ ፍሬ በውስጡ ያለው ፍሬ አንድ ነው አንድ አካል አንድ ባህሪ ነህ ሲሉ ነው።
✅ ዹቮምር ፍሬ በእሟህ ዹተኹበበ ነው ይህም ዚአንት ባህሪ ዹማይመሹመር በእሳት ዹተኹበበ ነው ሲሉ ነው።
ዚወይራ ዛፍ ዝንጣፊ
✅ ዚወይራ ቅጠል ዹሰላም ማብሰሪያ ነው ሰላማቜንን ዚምታበስርልን ዚምታስገኝልን አንተ ነህ ሲሉ ነው፡፡
✅ ዚወይራ ቅጠል ኚእንጚት ሁሉ ጜኑ ነው አንተም ጜኑ ሃያል አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
✅ወይራ ለመብራት ያገለግላል ፍሬው ዘይት ያወጣል ኚወይራ ዹሚገኝ ዘይት ጹለማን አሾንፎ ብርሃን እንደሚሰጥ ሁሉ አንተም ጹለማ ህይወታቜንን ዚምታስወግድልን አምላክ ነህ ሲሉ ነው።
✅ በኊሪት ግዜ ዚወይራ ዘይት ለመስዋአትነት ይቀርብ ነበር አንተም እንደ ዘይቱ ለመተላለፋቜን መስዋዕት ሆነህ ዚምትቀርብ አምላክ ነህ ሲሉ ነው። በመስቀል ላይ መስዋዕት ሆኗልና።
ኚፊት ኹኋላ ያሉት "ሆሣዕና በዓርያም ለዳዊት ልጅ መድኀኒት መባል ይገባዋል" እያሉ አመስግነውታል ዚምስጋና ጌታም በአህዮቜ ተቀምጩ ወደ መቅደስ ገብቷል።

በቅዳሎ ጊዜ ዚሚነበቡ ጥቅሶቜፊ
-ዕብ ፱፥፲፩ እስኚ ፍጻሜ
-፩ጎጥ ፬፥፩-፲፪
-ሐዋ ፳፰፥፲፩ እስኚ ፍጻሜ

ምስባኩምፊ መዝ፰፥፪
"እመ አፈ ደቂቅ ወሕጻናት አስተዳሎኚ ስብሐተ በእንተ ጞላኢ ኚመትንሥቶ ለጾላዒ ወለገፋዒ"
"ኚሕጻናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህልኝ፡፡ ስለ ጠላትና ቂመኛን ለማጥፋት"

ወንጌሉም፩ ዮሐ፭፥፲፩-፲፫
ቅዳሎ ፊ ዘጎርጎርዮስ (ነአኵቶ)[በዕዝል ዜማ]
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
[በዓለ ሆሣዕና]
✍በመጋቀ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ ዹተለጠፈ)
♥ ሆሣዕና ማለት ዚዕብራይስጥ ቃል ነውፀ “ሆሻአና” ሲባል ትርጒሙም “አቀቱ አኹን አድን” ማለት ነውፀ ይኜ በዓለ ሆሣዕና ኹ9ኙ ዐበይት ዚጌታ በዓላት ውስጥ ሲኟን ክንፋቾው ትእምርተ መስቀል ዚሚሠራው ኪሩቀል ሱራፌል በፍርሀት በሚዐድ ኹነው ዘፋኑን ዚሚሞኚሙት ጌታ በትሕትና ኟኖ ጀርባዋ ላይ ትእምርተ መስቀል ባለባት በአህያና በውርንጫይቱ ተቀምጩ እዚተመሰገነ ወደ ቀተ መቅደስ ዚገባበት፣ ዚዘካርያስ ትንቢት ዚተፈጞመበት፣ ሕዝቡ ዘንባባ ይዘው ዚዘመሩበት፣ ሕፃናት በንጹሕ አንደበታ቞ው ሆሣዕና ብለው ያመሰገኑበት ታላቅ በዓል ነው፡፡

♥ ይኜም ታሪክ በ4ቱ ወንጌላት ላይ ሲጻፍ በማቮ 21፡1 ላይ “ወደ ኢዚሩሳሌምም ቀርበው ወደ ደብሚ ዘይት ወደ ቀተ ፋጌ ሲደርሱ፥ ያንጊዜ ኢዚሱስ ኹደቀ መዛሙርቱ ሁለት ላኹ” ይላል፡፡

♥ ቀተ ፋጌ ማለት ዚበለስ ቀት ማለት ሲኟን ኚኢዚሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ በሚወስደው መንገድ አቅራቢያ ያለቜ ትንሜ መንደር ናትፀ ኹሉን ዐዋቂ ዚኟነው ጌታም ጎጥሮስንና ዮሐንስን “በፊታቜሁ ወዳለቜው መንደር ሂዱ፥ በዚያን ጊዜም ዚታሰሚቜን አህያ ውርንጫም ኚርሷ ጋር ታገኛላቜሁፀ ፈትታቜሁ አምጡልኝ” በማለት እንደ ማዕምሹ ኅቡአትነቱ (ዹተሰወሹውን ዐዋቂነቱ) በመንደሯ ውስጥ ስለታሰሩት አህያና ውርንጫ አስቀድሞ ይነግራ቞ዋል፡፡

♥ በተናቀቜ ግርግም በቀተልሔም በተወለደ ጊዜ ላምና አህያ ትንፋሻ቞ውን እንደገበሩለትፀ አኹንም በሰዎቜ በተናቀቜ አህያ በጌትነት ተቀምጩ እንዲመሰገንባት መርጧታል፡፡

❀ በልደቱ ማንም ያልገባባት ዚማይገባባት ዚሕዝቅኀል ዚታተመቜ መቅደስ ዚተባለቜ ዘላለማዊት ድንግል እመቀታቜንን እንደመሚጠ ዛሬም በሆሣዕና ማንም ሰው ያልተቀመጠበት ውርንጫ እንዲያመጡ አዘዘ።

♩ ኚዚያም “ማንም አንዳቜ ቢላቜሁ ለጌታ ያስፈልጉታል በሉፀ ወዲያውም ይሰዳ቞ዋል” በማለት ዚኹሉ ጌታ ርሱ መኟኑን አመለኚታ቞ውፀ በተሰጣ቞ው ሥልጣነ ክህነት ዚሕዝቡንም ዚአሕዛቡን ኀጢአት ዹማሰር ዚመፍታት ሰማያዊ ሥልጣነ ክህነት ዚተሰጣ቞ው ሐዋርያትን ዚሕዝብ ምሳሌ ዚኟነቜውን አህያይቱንና ዚአሕዛብ ምሳሌ ዚኟነቜው ውርንጫዋንም እንዲያመጡ አዟ቞ዋልና።

♥ ሊቁ ጀሮምም፡- “ደቀ መዛሙርቱ አህያይቱንና ውርንጫይቱን ለመፍታት ኹለት ኟነው መላካ቞ው ለሕዝብም ለአሕዛብም መላካ቞ው ያመለክታል፡፡” ይላል።

♥ ሊቁ አምብሮስ፡- “አህያዚቱን ለመፍታት ማንም አይኚለክላቜኁም ብሎ መላኩ ጌታ ለደቀ መዛሙርቱ ዚሰጣ቞ው ዹማሰር ዚመፍታት ሥልጣን ሰማያዊ መኟኑን ያመለክታል፡፡” በማለት ልዩ ምስጢርን አስተላፎበታል።

♥ አምጥተው “ልብሳ቞ውንም በእነርሱ ላይ ጫኑ”ፀ በአህያዋና በውርንጫዋ ላይ ኮርቻ ሳይኟን ልብስ ማድሚጋ቞ው ኮርቻ ይቈሚቊራል ልብስ ግን አይቈሹቊርምና ዚማትቈሚቊር ሕግ ሠራኜልን ሲሉ። ዳግመኛም ልብስ በአካል ያለውን ኀፍሚት እንዲሰውር አንተም በደላቜንን ዚምትሰውርልን ይቅር ባይ ነኜ ሲሉ በማለት መተርጉማን ይተነትናሉ፡፡ በተጚማሪም ልብስ በልጅነት ይመሰላልና ዹተገፈፍነውን ዹጾጋ ልብሳቜን (ልጅነትን) ትመልስልናለህ ሲሉ ነው፹

♥ ቅዱስ ኀፍሬም ይኜነን ሲተሚጉም "ልብሳ቞ውን አውልቀው ያነጠፉለት ሰዎቜ አሮጌውን ማንነታ቞ውን ትተው ዐዲሱን ልብስ ክርስቶስን መልበሳ቞ውን ያስሚዳል። ሐዋርያ ጳውሎስ “አሮጌውን ሰውነት አስወግዳቜሁ አዲሱን ሰው ልበሱት” እንዳለው (ኀፌ.4፣23) ይኾውም ጥምቀት ነው" ይላል።

♥ ኚኢዚሩሳሌም እስኚ ቀተ መቅደስ 16 ምዕራፍ ሲኟን መተርጒማነ ሐዲስ በትርጓሜ ወንጌል ላይ እንደሚገልጹት 14ቱን ጌታ በእግሩ ሲኌድ 2ቱን በአህያዋፀ በውርንጫዋ 3 ጊዜ ቀተ መቅደሷን ዞሯል፡- 14ቱ በእግሩ መኌዱ ዹ10ሩ ቃላት 4ቱ ዹ4ቱ ኪዳናት ምሳሌ፡፡ 2ቱ በአህያዋ መጓዙ ዹፍቅሹ እግዚአብሔርና ዹፍቅሹ ቢጜፀ 3ቱን በውርንጫዋ ተቀምጩ ቀተ መቅደሱን መዞሩ ዹ3ትነቱ ዚአንድነቱ ምሳሌ ነበር፡፡

♥ ጌታ ንጉሠ ነገሥት ሲኟንፀ ኪሩቀል ሱራፌል ዙፋኑን በፍርሀት በሚአድ ዚሚሞኚሙት 24ቱ ካህናተ ሰማይ ዙፋኑን በፍርሀት ዚሚያጥኑለት ርሱ በትሕትና ዹዋህ ኟኖ በተናቁት በአህያና በውርንጫይቱ ላይ ተቀመጠፀ ይኜም ዚተናቁትን ሊያኚብር እንደመጣናፀ በዹዋሀን ምእመናን ልቡና እንደሚያድር ለማሳወቅ በነርሱ ተቀመጠ። በተጚማሪም መተርጉማን እንዳመሰጠሩት በአህያ ዹተቀመጠ አባሮ እንደማይዝ ሞሜቶ እንደማያመልጥ ርሱም ካልፈለጉት እንደማይገኝ ኚፈለጉት እንደማይታጣ በምስጢር አመለኚታ቞ው፡፡

♥ በተጚማሪም አህያ ሲፈጥራት በጀርባዋ ላይ ትእምርተ መስቀል ያላት ናትና ትእምርተ መስቀል ያለባት እእርሷ እንድትፈታ ማዘዙ ኹ5 ቀን በኋላ በመስቀል ተሰቅሎ በሲኊል ዚታሠሩትን ዹሰው ልጆቜን ነጻ ሊያወጣ መጥቷልና አህያን መርጧታልፚ

♥ ቅ.ዮሐንስ አፈወርቅ፡- ስለዚኜ ነገር በትርጓሜ ወንጌሉ ላይ “እነዚኜ እንስሳት መላውን ዹሰው ልጅ ይወክላሉ፡፡ ኹለቱም አህያ መኟና቞ውም ዹሰው ልጅ ክርስቶስ ኚመምጣቱ በፊት ዹነበሹውን አኳኋን ዚሚያስሚዳ ነው፡፡ ምክንያቱም አህያ በኊሪቱ ዘንድ ንጹሕ እንስሳ አይደለቜምፀ ብዙ ክብደት ያላት ዚማትወደድ እንስሳ ናትፀ ደካማ ናት፡፡ ሰውም እንደተናገርን ክርስቶስ ኚመምጣቱ በፊት እንዲኜ ነበሚ፡፡” በማለት አመስጥሯል፡፡

♥ ሊቁ ቅ. ቄርሎስ ዘእስክንድርያም፡- “ፈጣሬ ኵሉ እግዚአብሔር ሰውን በምድር ላይ ጠቢብ አድርጐ ፈጥሮት ነበር፡፡ ማሰብና ማሰላሰል ዚሚቜል ፍጥሚት አድርጐ ፈጥሮት ነበር፡፡ ሰይጣን ግን አታለለው፡፡ ምንም እንኳን ሰው በሥላሎ አምሳል ቢፈጠርም መልኩን አበላሞው፡፡ ፈጣሬ ኵሉ እግዚአብሔርን ማወቅ ተሳነው፡፡ ክፉው ሰይጣን ሰውን እንስሳ እስኪመስል ድሚስ ክብሩን አዋሚደው፡፡ መዝሙሹኛው ዳዊት፡- “ሰውስ ክብሩን አላወቀምፀ ዹሚጠፉ እስሳትን መሰለ” ያለውም ስለዚኹ ነው (መዝ.49፡12)፡፡ በመኟኑም አህያይቱ ክብራ቞ውን አጥተው ተዋርደው ዚነበሩትን እስራኀል ዘሥጋን ትመስላለቜ፡፡ እስራኀል ኹሕጉ ጥቂት ነገርን ያውቃሉ፡፡ ኚነቢያትና ኚቅዱሳንም ትንሜ ያውቃሉ፡፡ ኚኹሉም በላይ ደግሞ ወደ አሚን ዚሚጠራ቞ውን ክርስቶስን አልታዘዙትም፡፡ “እኔ ዹዓለም ብርሃን ነኝ” ሲላ቞ውም እንደ አህያይቱ በድንቁርና ተይዘው እንደነበሚ ሲገልጥላ቞ው ነው፡፡ ውርንጫይቱ ደግሞ አሕዛብን ትወክላለቜ፡፡ ውርንጫ እኜልን ለመጫን እንደማታገለግል ኹሉ አሕዛብም ማኅደሹ እግዚአብሔር ኚመኟን ርቀው ነበርና፡፡” በማለት ገልጿል፡፡

♥ ያን ጊዜ ኚሕዝቡም እጅግ ብዙዎቜ ልብሳ቞ውን በመንገድ ላይ አነጠፉ ይኜንም ማድሚጋ቞ው ስንኳን አንተ ዚተቀመጥኜባት አህያ መሬት መርገጥ አይገባትም ሲሉ ነበር። እንስሳዋ እንኳን ጌታ ቢቀመጥባት እንዲህ ክብር ያገኘቜ ኹሆነ ያደሚባ቞ው ቅዱሳንማ ዚሚገባ቞ው ክብር ምን ያህል ይሆን? ይልቁኑ 9 ወር ኹ5 ቀናት በማሕፀኗ ዚተሞኚመቜው ኚሥጋዋ ሥጋን ኚነፍሷ ነፍስን ነሥቶ ሰው ዹሆነውን አምላክ ዚወለደቜው ዚቅድስት ድንግል ማርያም ክብርማ እጅጉን ታላቅ ነው።

❀ ጌታ ዚተቀመጠባት አህያ በክብር ወደ ኢዚሩሳሌም እንደገባቜ ጌታ ያደሚባ቞ው ምእመናን ደግሞ በታላቅ ክብር ወደ ኢዚሩሳሌም ሰማያዊት ይገባሉ።
❀ ሌሎቜም ኹዛፍ ጫፍ ጫፉን እዚቈሚጡ በመንገድ ላይ ያነጥፉ ነበር። ይኜም ዘንባባ ብዙ ምሳሌ ያለው ነውፀ ይኾውም በእስራኀል ያለው ሰሌን፣ ተምር፣ ዘይት ነበርና ያነን ቈርጠው አመስግነውታልፀ ይኜም ምሳሌነት ያለው ነውፀ ይኜም ሰሌን እሟኻማ እንደኟነ ትእምርተ ኀይል ትእምርተ መዊእ አለኜ ሲሉ ነውፀ እሳት ለብልቊ ይተወዋል እንጂ እንደማያቃጥለው ባሕርይኜ አይመሹመርም ሲሉ ነበር፡፡

♥ ዳግመኛም ኹሰሌን ዝንጣፊ ጋር ተመሳሳይ ተምር ይዘዋል ይኜም ተምር ልዑል ነው አንተም ልዑለ ባሕርይ ነኜ ሲሉፀ ፍሬው አንድ እንደኟነ አንተም ዋሕደ ባሕርይ ነኜ ሲሉ፡፡ በእሟኜ ዹተኹበበ ነው ባሕርይኜ አይመሹመርም ሲሉ ነበር፡፡

♥ ዚዘይት ዛፍ ነው ቢሉ ዘይት ጜኑዕ እንደኟነ ጜኑዐ ባሕርይ ነኜ ሲሉፀ ብሩህ ነው ብሩሀ ባሕርይ ነኜ በትምህርትኜም ዹሰውን ልቡናን ታበራለኜ ሲሉፀ ዘይት መሥዋዕት እንደሚኟን መሥዋዕት ትኟናለኜ ሲሉ ነበር፡፡

♥ “ዚሚቀድሙትም ሕዝብ ዚሚኚተሉትም ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ዚሚመጣ ዚተባሚኚ ነውፀ ሆሣዕና በአርያም እያሉ ይጮኹ ነበር” በማለት በአርያም መድኀኒት እንደኟነና እግዚአብሔር አብ “ዚምወድደው ልጄ ይኜ ነው” ብሎ መስክሮለት ዚመጣው ኢዚሱስ ክርስቶስ መርገመ ሥጋ
መርገመ ነፍስን ዚሚያርቅ በሹኹተ ሥጋን በሹኹተ ነፍስን ዚሚያድል መኟኑን ኹሉም መሰኚሩለት፡፡

♥ በእጅጉ ዹሚደንቀው ዹ40 ቀን ዹ80 ቀን ሕጻናት ዚፈጠራ቞ው ጌታ በአህያና በውርንጫ ተቀምጩ ባዩት ጊዜ በንጹሕ አንደበታ቞ው አንደታ቞ው ሚቶላ቞ው ጌታን ዘንባባ በመያዝ ሲያመሰግኑ በእጅጉ ይደንቅ ነበርፀ ነገር ግን ጞሐፍት ፈሪሳውያን ያደሚገውን ድንቃ ድንቅ በመቅደስም ሆሣዕና ለዳዊት ልጅ እያሉ ዚሚጮኹትን ልጆቜ ባዩ ጊዜ፥ ተቈጥተው እነዚህ ዚሚሉትን አትሰማምን? አሉትፀ ኢዚሱስምፊ እሰማለሁፀ ኚሕፃናትና ኚሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ ዹሚለውን ቃል ኚቶ አላነበባቜሁምን? በማለት በሕጻናት እንደሚመሰገን ዚነርሱም ጌታ መኟኑን ኚዳዊት መዝሙር በመጥቀስ ነገራ቞ው፡፡

♥ ሊቁ ያዕቆብ ዘሥሩግ ሰለዚኜ ምስጢር ሲገልጞው ፡- “ፍቅርኜ ኚዘባነ ኪሩብ አውርዶ በአህያ ጀርባ ላይ እንድትቀመጥ አስገደደኜ፡፡ ብዙ ዐይንና ብዙ ገጜ ካላ቞ው ኚሰራዊተ መላክእት ይልቅ በዲዳዋ አህያ ትመሰገን ዘንድ ወደደክ፡፡ በሰማይ ሰራዊት ሠሹገላ ተቀምጠኜ ክብርኜን ማሳዚት አልወደድክምፀ በውርንጫላይቱ ላይ ተቀምጠኜ ወደ ሰማይ ሰራዊት መኌድን መሚጥክ እንጂ፡፡ በአርያም እሳታውያን ዚሚኟኑ ኪሩቀል ያመሰግኑኻልፀ በምድርም ሕፃናት ይዘምሩልኻል፡፡ በአርያም ብርሃናውያን መላእክት በብርሃን ክንፋቾው መንገድኜን ያነጥፉልኻልፀ በምድርም ደቀ መዛሙርትኜ ልብሳ቞ውን አንጥፈው መንገድኜን አስተካኚሉ፡፡ ወዮ! አርያማዊ ሲኟን ምንም ሳይንቀን ይጐበኘን ዘንድ ኚአባቱ መጣ፡፡ ርሱም በገዛ ፈቃዱ ሰው እስኚ መኟን ደርሶ መጣ፡፡ በአህያ ላይ ተጭኖም ይጐበኘን ዘንድ መጣ፡፡ ነቢዩ ዘካርያስ ዚመንፈስ ቅዱስን እንዚራ ይዞ በደስታ ትንቢትን ለመናገር ይቻኰላል፡፡ እዚደሚደሚም ዚጜዮንን ልጅ ይጠራታል፡፡” በማለት አስተምሯል፡፡

♥ ዚምስጋና ጌታ ኢዚሱስ ክርስቶስ በአህያዋና በውርንጫዋ ላይ ተቀምጩ ሕፃናትን ጚምሮ ዘንባባ ሰሌን በያዙት ኹሉ “ሆሣዕና በአርያም” እዚተባለ እዚተመሰገነ ወደ ቀተ መቅደስ ዚገባበትን ታላቁን በዓል ኚኹሉም ዓለም አስበልጣ በታላቅ ክብር ዚምታኚብርና ዚምታስተምሚው ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋሕዶ ቀተ ክርስቲያን ናት፡፡

♥ ይኾውም ታላቁ ዚምስጋና ዕለት ሊደርስ ሲቃሚብ ስንዱዋ እመቀት አስቀድማ በቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ ዚቊርባን ምስጋናፊ
✍ “ቩአ ኀቀሃ እግዚአ አጋዕዝት ወመናፍስት እንዘ ይጌዐን ዕዋለ አድግ ትሑት ” (ዚአጋዕዝትና ዚመናፍስት ጌታ በተዋሹደ አህያ ግልገል ተቀምጩ ወደ ርሷ ገባፀ በእግዚአብሔር ስም ዚሚመጣ ብሩክ ነው፡፡ አንተም ዚአማልክት አምላክ ዚእስራኀልም ንጉሥ እግዚአብሔር ቡሩክ ነኜ እያሉ ለሚያመሰግኑ ሕፃናት ኹሉ ጌትነቱን አሳዚፀ ዚሆሳዕናን ዑደት ለነርሱ ለደቀ መዛሙርቱ አሳዚፀ ቡርክ ርሱ በታላቅ ቃል እዚጮኻቜኊ ሆሣዕና በአርያም በሉ አላ቞ውፀ ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሳዕና በአርያምፀ ኚመድኀኒትነቱ ዚተነሣ ኚዚኜ አስቀድሞ ያልተደሚገ ኚዚኜም በኋላ ዹማይደሹግ ተአምራትንና መንክራትን አሳዚፀ ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሳዕና በአርያም... ) በማለት መድኀኒትነቱን ስትሰብክፀ ካህናትና ምእመናንም በአንድ ድምፅ በዚያ ዘመን ዚምስጋና ጌታ ኢዚሱስ ክርስቶስ በተመሰገነበት በዚኜ ልዩ ምስጋና “ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም” እያሉ በመዘመርፀ ፈጣሪያ቞ው ክርስቶስን ያመሰግናሉ።

💥 ኚዚያም በዋዜማው፩
✍ “በዕምርት ዕለት በዓልነ ንፉሑ ቀርነ በጜዮን ወስብኩ በደብሚ መቅደስዚ እስመ ይቀ ዛቲ ዕለት በዓለ እግዚአብሔር ሆሣዕና በአርያም ቡሩክ አንተ ንጉሠ እስራኀል”
👉 (በታወቀቜ በበዓላቜን ዕለት በጜዮን መለኚትን ንፉፀ በመቅደሮ ተራራም ስበኩ ይኜቺ ዕለት ዚእግዚአብሔር በዓል ናትፀ በአርያም መድኀኒት ዚተባልኜ ዚእስራኀል ንጉሥ አንተ ቡሩክ (መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስን ዚምታርቅ በሹኹተ ሥጋ በሹኹተ ነፍስን ዚምታድል) ነኜ) በማለት ልዩ ምስጋናዋን ጀምራ እስኚ ሌሊቱ ድሚስ በልዩ ምስጋና እዚሰበኚቜው በኋላም ቀተ መቅደሱን በውርጫዋ ተቀምጩ እንደዞሚ በአራቱ መኣዝን ዚጌትነቱ ወንጌል እዚተነበበፀ ካህናቱን ምእመናንም በእጃ቞ው ዚዘንባባ ዝንጣፊን ይዘው “ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም” እያሉ ያመሰግኑታል፡፡
✍ በመጋቀ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ ተጻፈ
መልካም በዓል ይኹንልን።
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
ዹሰሙነ ሕማማት ሰኞ፡-

መርገመ በለስ ዚተፈጞመበት ዕለት ነው፡

ጌታቜንና አምላካቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ዚሆሣዕና ዕለት ቢታንያ አድሮ በማግሥቱም ኚቢታኒያ ሲመጡ ተራበ፡፡ (ማር.11ፀ11-12) ቅጠል ያላት በለስ ኚሩቅ አይቶ ወደ በለሲቱ ቀሚበፀ ነገር ግን ኹቅጠል በቀር አንዳቜ ፍሬ አላገኘባትም፡፡ ኹአሁን ጀምሮ ማንም ኚአንቺ ፍሬ አይብላ ብሎ ሚገማት። በለስ ዚተባለቜ ቀተ እስራኀል ናትፀ ፍሬ ዚተባለቜ ሃይማኖትና ምግባር ናትፀ ኚእስራኀል ፍቅርንፀ ሃይማኖትንፀ ምግባርን ፈለገ አላገኘምፀ እስራኀል (ሕዝበ እግዚአብሔር) መባልን እንጂፀ ደግ ሰው አይገኝብሜ ብሎ ሚገማትፀ በመርገሙ ምክንያት እርሱ ኚለያ቞ው በስተቀር ደግ ሰው ጠፋባት

በለስ ኊሪት ናትፀ ኊሪትን በዚህ ዓለም ሰፍና ቢያገኛት ኊሪትና ነቢያትን ልሜር አልመጣሁም ልፈጜም እንጂ በማለት ፈጞማትፀ ሕገ ኊሪትን ኹመፈጾም በቀር በእርሷ ድኅነት አላደሚገባትምናፀ ፍሬ በአንቺ አይሁን አላትፀ ደኅነት በአንቺ አይደሚግብሜ ብሏታልና እንደመድሚቅ ፈጥና አለፈቜ፡፡

በለስ ኃጢአት ናትፀ ዚበለስ ቅጠል ሰፊ እንደሆነቜ ሁሉ ኃጢአት በዚህ ዓለም ሰፍታ ሰፍና አገኛት፡፡ በለስ ሲበሉት ይጣፍጣልፀ ቆይቶ ግን ይመራልፀ ኃጢአትም ሲሰሩት ደስ ደስ ያሰኛልፀ ኋላ ግን ያሳዝናልፀ ወደ እርሷም ሄዶ ማለትም ኚኃጥአን ጋር ዋለፀ ኃጥእ ኚመባል በቀር በአንደበቱ ሐሰትፀ በሰውነቱ ክፋት እንዳልተገኘበት ለማመልኚት ፍሬ አላገኘባትም አለፀ በአንቺ ፍሬ አይገኝ ዚሚለውምፀ በኃጢአት ፍዳ ተይዞ ዹሚቀር አይኑር ለማለት ነውፀ ስትሚገም ፈጥና መድሚቋም፣ በአዳም ምክንያት ያገኘቜን ዕዳ በደል በእርሱ ካሣነት እንደጠፋቜልን ለመግለጜ ነው፡፡

አንጜሆተ ቀተ መቅደስ ዚተፈጞመበት ዕለት ነው፩

ጌታቜን በለስን ኚሚገማት በኋላ ወደ ቀተ መቅደስ ሄደፀ ቀተ መቅደስ፣ ቀተ ጞሎት፣ ቀተ መሥዋዕት መሆኑ ቀርቶ ቀተ ምስያጥ (ዚንግድ ቀት) ሆኖ ቢያገኘው ቀ቎ ዚጞሎት ቀት ትባላለቜፀ እናንተ ግን ዚወንበዶቜ ዋሻ አደሚጋቜኋት ብሎ ዚሚሞጡበትን ሁሉ ገለበጠባ቞ውፀ ገርፎም አስወጣ቞ውፀ ይህም ዚሚያሳዚው ማደሪያው ቀቱ ዹነበርን ዚአዳም ልጆቜ ኃጢአት ሰፍኖብን ስንኖር ቢያገኘን ኃጢአታቜንን ሁሉ እንዳራቀልን ዚሚገልጜ ነው

በዚህ በሰሙነ ሕማማት ካህናትና ምእመናን በቀተክርስቲያን ተገኝተው ወዛቾው ጠብ እስኪል ድሚስ በነግህፀ በሠለስተ፣ በስድስቱ ሰዓትፀ በተሰዓቱ ሰዓትና በሠርክ መላልሰው ሲሰግዱና ሲጞልዩ ይሰነብታሉፀ በተለይም ካህናት በማንኛውም አገልግሎት ጥቁር ልብስ ይለብሳሉፀ ምክንያቱም ዚደሚሰብን መኚራ ኀዘኑን እና 5ሺ ኹ5መቶ ዘመን ዹሰው ልጅ በጹለማ ይኖር እንደነበሚ ለማዘኹር ነው

#ሌር
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
​​​​ሥርዓተ ጞሎት ሰሙነ ሕማማት ኹሰኞ እስኚ ዕሮብ  ካህናት እያዜሙ እዚሰገዱ እኛም እዚተቀበልን እያዜምን ዚምንሰግድበትን   ሥርዓት ለማውቅ እና ለመፈፀም ኚስር ያንብቡ

❖ ዹጾሎተ ሐሙስና ዹዕለተ ዓርብ ሥርዓተ ጞሎት

👉 ኹሰኞ ጀምሮ እስኚ ዓርብ ድሚስ ባሉት ቀናት ውስጥ  በመጀመሪያ ዲያቆኑ ቀተ ክርስቲያኑን ሊስት ጊዜ ዞሮ ደወል ካሰማ በኋላ መቶ አምሳው ዳዊት ይታደልና ይደገማል፡፡ ዚሰባት ቀናት ውዳሎ ማርያምና አንቀጾ ብርሃን  እስኚ ይዌድስዋ  ድሚስ ታድሎ ይደገማል፡፡ ኚዚያም “እንበለ ደዌ ወሕማም እንበለ ጻማ ወድካም ዓመ ኹመ ዮም ያብጜሐኒ ያብጜሕክሙ አግዚአብሔር በፍሥሓ ወበሰላም” ተብሎ አቡነ ይደገምና  በዐራቱም ወንጌላት መሠሚት ለእያንዳ቞ው በእዚዕለቱና  ሰዓቱ ዹተመደበውን አቡነ ካህናቱ በቀኝና በግራ እዚተፈራሚቁ  ይመራሉ፡፡ ካህናቱና ሕዝቡም ይቀበላሉ፡፡ በመቀጠል፡- (ትእዛዝ፡ ሕዝቡ በጞሎት በተሰበሰቡ ጊዜ ጠዋት ወይም በ3፣ በ6፣በ9፣ በ11ሰዓተ መዓልት መጀመሪያ ሕዝቡ እዚሰገዱና እዚተኚተሉ እንዲህ ይበሉ፡፡ )

✥ "ለኹ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም ፡፡"

✥ "አማኑኀል አምላኪዚ ለኹ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም፡፡"

✥ " ኩ እግዚእዚ ኢዚሱስ ክርስቶስ ለኹ ኃይል ክብር ወስብሐት ወእዘዝ ለዓለመ ዓለም፡፡ "
✥ " ኃይልዹ ወጾወንዹ ውእቱ እግዚእዚፀ እስመ ኮንኚኒ ሚዳእዚ እብል በአኰ቎ት ፡፡"

ትእዛዝ፡ በዚህ ጊዜ ካህኑ እዚተኚተሉ አቡነዘበሰማያት ይድገሙ ።
ይህን ዹላይኛውን ጞሎት እያመላለሱ ኚአቡነ ዘበሰማያት ጋር 12 ጊዜ ይበሉ

❖ " ለአምላክ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም፡፡

❖ "ለሥሉስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ለማሕዹዊ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ለዕበዩ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖"ለእዘዙ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ለመንግሥቱ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ስለልጣኑ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ለኢዚሱስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

"ለክርስቶስ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ለሕማሙ  ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም"፡፡

❖ "ለመስቀሉ ይደሉ ክብር ወስብሐት ወእዘዝ እስኚ ለዓለመ ዓለም፡፡ "

ትእዛዝ፡- ይህ ሊስት ጊዜ እዚተመላለሰ ይባላል፡፡በመጚሚሻም ዹሚኹተለውን ሊስት ጊዜ እያመላለሱ ይበሉ፡፡

❖ "ለኹ ይደሉ ኃይል፣ ወለኹ ይደሉ ስብሐት ወለኹ ይደሉ አኰ቎ት ኩ እግዚእዚ ኢዚሱስ ክርስቶስ ለዓለመ ዓለም"

ትእዛዝ፡- ካህኑ ‹ጞልዩ በእንተ ጜንዓ ዛቲ . . .› ብሎ በሚያነብ ጊዜ በዚምዕራፉ "እግዚኊ ተሳሃለነ" እዚተባለ ይሰገዳል፡፡

ትእዛዝ፡- ኹዚህ ሁሉ በኋላ ሕዝቡ ዚሚኚተሉትን ጞሎት በግራና በቀኝ ይበሉፀ

"ክርስቶስ አምላክነፀ ዘመጜአ ወሐመ በእንቲአነ በሕማማቲሁ ቀዝወነፀ  ንሰብሖ ወናልዕል ስሞ ኅቡሚፀ እስመ ውእቱ ገብሚ መድኃኒተ በዕበዹ ሣህሉ" (በዐርብ) ዘሐመ ወሞተ በእንቲአነ ይባላል፡፡

ትእዛዝ፡- ቀጥሎም ሕዝቡ በሁለት ክፍል ሆነው ዹሚኹተለውን ጞሎት ሁለት ጊዜ በመኚታተል አንድጊዜ በማስተዛዘል ይበሉት፡፡

ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ
#ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ

#አብኖዲ  ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶን

#ናይን፣ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶን ፀ

#ታዖስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ

#ማስያስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ

#ኢዚሱስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ

#ክርስቶስ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ

#አማኑኀል ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶንፀ

#ትስቡጣ ናይን፣ ኪርያላይሶንፀ
ኪርያላይሶንፀኪርያላይሶን

ትእዛዝ፡- ኹዚህ በኋላ ኪርያላይሶን አርባ አንድ ጊዜ ይባላል፡፡

ይኾውም  በአንድ ወገን 20 ጊዜ በሌላው ወገን 21 ጊዜ በጠቅላላው 41 ጊዜ ኪርያላይሶን  ኪርያላይሶን  ኪርያላይሶን  እዚተባለ ይሰገዳል፡፡

በመጚሚሻ ጊዜ፡-

✥ ስብሐት ለእግዚአብሔር ኪያነ ዘፈጠሹ ኹመ ናምልኮ (እናመልኚው ዘንድ ለፈጠሹን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል)፡፡

✥ ስብሐት ለማርያም እመ አምላክ እግእዝትነ ወመድኃኒትነ (እመቀታቜንና መድኃኒታቜን ለሆነቜ ለአምላክ እናት ለማርያም ምስጋና ይገባል)፡፡

✥ ስብሐት ለመስቀለ ክርስቶስ ዕፀ መድኃኒት ኃይልነ ወፀወንነ(ኃይላቜን መጠጊያቜን ለሆነ ድኅነት ለተገኘበት ለክርስቶስ ምስጋና ይገባል)ፀፀ ጾሎተ ሃይማኖትን ሐመ  እስኚ ሚለው ድሚስ መድገም ነው፡፡  /ኹሰኞ እስኚ ሚቡዕ ይባላል/

#ሌር
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
🔎 #ማክሰኞ_ዚትምህርት_እና_ዚጥያቄ_ቀን

ይህ ቀን ጌታቜን መድኃኒታቜን ኢዚሱስ ክርስቶስ ሰኞ በተናገሹው ባደሚገው ላይ አይሁድ ጥያቄ ያቀሚቡበት እርሱም መልስ በመስጠት ያስተማሚበት ዕለት ነው በዚህም ምክንያት ዚጥያቄ እና ዚትምህርት ቀን በመባል ይታወቃል፡፡

ሰኞ ቀን ጌታቜን በሚገማትን በለስ  መድሚቅ ሐዋርያት ሲደነቁ እምነት ያለው ሰው ሁሉን ማድሚግ እንደሚቜል ያስሚዳበት ዕለት ነው፡፡
‹‹ ማለዳም ሲያልፉ በለሲቱን ኚሥርዋ ደርቃ አዩአት ጎጥሮስም ትዝ ብሎት መምህር ሆይ፥ እነሆ፥ ዚሚገምሃት በለስ ደርቃለቜ አለው። ኢዚሱስም መልሶ እንዲህ አላቾው፩ በእግዚአብሔር እመኑ እውነት እላቜኋለሁ፥ ማንም ያለው ነገር እንዲደሚግለት ቢያምን በልቡ ሳይጠራጠር፥ ይህን ተራራ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ቢል ይሆንለታል። ስለዚህ እላቜኋለሁ፥ ዚጞለያቜሁትን ዚለመናቜሁትንም ሁሉ እንዳገኛቜሁት እመኑ፥ ይሆንላቜሁማል ለጞሎትም በቆማቜሁ ጊዜ፥ በሰማያት ያለው አባታቜሁ ደግሞ ኃጢአታቜሁን ይቅር እንዲላቜሁ፥ በማንም ላይ አንዳቜ ቢኖርባቜሁ ይቅር በሉት። እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታቜሁም ኃጢአታቜሁን ይቅር አይላቜሁም። ››ማር 11፥20-26 እያለ ያስተማሚበት ዕለት ስለሆነ ዚትምህርት ቀን ይባላል

ሌላው ይህ ዕለት ጌታቜን  ሰኞ ዕለት  ካደሚጋ቞ው ነገሮቜ ተነስተው አይሁድ ጥያቄ ያቀሚቡበት ዕለት ነው
‹‹ ወደ መቅደስም ገብቶ ሲያስተምር ዚካህናት አለቆቜና ዚሕዝብ ሜማግሎቜ ወደ እርሱ ቀሚቡና በምን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት። ኢዚሱስም መልሶፊ እኔ ደግሞ አንዲት ነገር እጠይቃቜኋለሁፀ እናንተም ያቜን ብትነግሩኝ እኔ ደግሞ እነዚህን በምን ሥልጣን እንዳደርግ እነግራቜኋለሁፀ ዚዮሐንስ ጥምቀት ኚወዎት ነበሚቜ? ኹሰማይ ወይስ ኹሰው? አላ቞ው። . . . ›› /ማቮ 21 ፥23- 27/
ይህ ጥያቄ ጌታቜን ሲያደርጋ቞ው ዚነበሩ ተአምራትና ድንቅ ድንቅ ሥራዎቜ ዚካህናት አለቆቜን ስላስቀኗ቞ው ጌታቜንን ኚሮማ መንግሥት ባለ ሥልጣናት ጋር ለማጋጚት ዚቀሚቡት ጥያቄ ነበር ጌታቜን በቀተ መቅደስ ዹነበሹውን ገብያ ስለበተነው ዚነጋዎዎቹን  መደባ቞ውን ስለገለበጠ ነጋዮን ማባሚርና መደብን ማስለቀቅ መንግሥታዊ ሥራ ነውና በማን ሥልጣን አደሹኹው ብለው ጠዚቁት ጌታቜን â€¹â€¹á‰ áˆ«áˆŽ áˆ¥áˆáŒ£áŠ•â€ºâ€º á‰¢áˆ‹á‰žá‹ ጾሹ መንግሥት አቋም አለው በማለት ኚሮማ መንግሥት ዘንድ ለማሳጣት ነበር ዕቅዳ቞ው
ጌታቜን ግን ዚፈሪሳውያንን ጠማማ አሳብ ስለሚያውቅ â€¹â€¹á‹šá‹®áˆáŠ•áˆµ áŒ¥áˆá‰€á‰µ áŠšá‹šá‰µ áŠá‹? áŠšáˆ°áˆ›á‹­ áŠá‹ á‹ˆá‹­áˆµ áŠšáˆá‹µáˆ­?›› áˆ²áˆ ጠይቋ቞ዋል፡፡ ጌታቜን ፈሪሳውያን ላቀሚቡለት ጥያቄ ቀጥተኛ ምላሜ አልሰጠም ምክንያቱም ጥያቄው ለኚሳሟቹ ዓላማ መሳካት አመቺ ሁኔታን ስለሚፈጥር ጥያቄውን በጥያቄ መልሶላ቞ዋል፡፡ እነርሱም â€¹â€¹áŠšáˆ°áˆ›á‹­ áŠá‹â€ºâ€º á‰¢áˆ‰á‰µ â€¹â€¹áˆˆáˆáŠ• áŠ áˆ‹áˆ˜áŠ“á‰œáˆá‰ á‰µáˆ?›› áŠ¥áŠ•á‹³á‹­áˆ‹á‰žá‹á€ â€¹â€¹áŠšáˆ°á‹ áŠá‹â€ºâ€º á‰¢áˆ‰á‰µ ደግሞ ሕዝቡ ዮሐንስን እንደ አባት ይፈሩት፣ እንደ መምህር ያኚብሩት ነበርና ሕዝቡ እንዳይጣሏ቞ው ስለፈሩ â€¹â€¹áŠšá‹ˆá‹Žá‰µ áŠ¥áŠ•á‹° ሆነ áŠ áŠ“á‹á‰…áˆâ€ºâ€º á‰¥áˆˆá‹ መለሱለት፡፡ እርሱም â€¹â€¹áŠ¥áŠ”áˆ በማን ሥልጣን እነዚህን እንደማደርግ አልነግራቜሁም›› áŠ áˆ‹á‰žá‹ ኹዚህ ታሪክ ዚተነሳ ይሄ ቀን ዚጥያቄ ቀን ይባላል፡፡
https://www.tg-me.com/tmhrteorthodox
​​እንኳን ለእመቀታቜን ቅድስት ድንግል ማርያም ዚልደት በዓል በሰላም አደሚሳቜሁ

#መዝ. 86፥1
“መሠሚታቲሃ á‹áˆµá‰° áŠ á‹µá‰£áˆ­ á‰…ዱሳን፡- መሠሚቶቿ á‹šá‰°á‰€á‹°áˆ± á‰°áˆ«áˆ®á‰œáŠ“á‰žá‹â€

ዮም ááˆ¥áˆ áŠ®áŠ á‰ áŠ¥áŠ•á‰° áˆá‹°á‰³ áˆˆáˆ›áˆ­á‹«áˆ በእመቀታቜን áˆá‹°á‰µ áˆáŠ­áŠ•á‹«á‰µá‹›áˆ¬ á‹°áˆµ ሆነ፡፡

በግንቊት 1 á‰€áŠ• 5ሺ áŠš5መቶ á‹šáˆ˜áŠšáˆ«á‹ á‹˜áˆ˜áŠ• áˆŠá‹«áˆá‰… 15 á‹“መታት ሲቀሩት/ ሊባኖስ á‰ áˆšá‰£áˆ ተራራ ኹፀሐይ  ዚምታበራ áˆŽá‰µ áˆáŒ… á‰°á‹ˆáˆˆá‹°á‰œá¡á¡

ይህቺውም ááŒ¥áˆšá‰µ áˆáˆ‰ á‹°á‰‚ቀ አዳም ሁላቾው ተስፋ ሲያደርጓትና ሲጠባበቋት á‹šáŠá‰ áˆšá‰œ ዚድኅነታ቞ው ምልክት áŠ¥áˆ˜á‰€á‰³á‰œáŠ• áŠ“á‰µá¡á¡

ሶሪያዊው áˆŠá‰… á‰…ዱስ áŠ€ááˆ¬áˆáˆ 
“አክሊለ áˆáŠ­áˆ•áŠ á‹ˆá‰€á‹³áˆšá‰° መድኀኒትነ፡፡ወመሠሚተ áŠ•áŒœáˆ•áŠ áŠ®áŠ á‰ áˆ›áˆ­á‹«áˆ á‹µáŠ•áŒáˆ:- ዚመመኪያቜን ዘውድ ዚደኅንነታቜን  መጀመሪያ ዚንጜሕናቜንም መሠሚት በድንግል ማርያም áˆ†áŠáˆáŠ•â€ በማለት መናገሩ ስለዚህ áŠá‹á¡á¡

አክሊል áˆáŠ­áˆáŠ አላት á‹­áˆ…ም áŠ áŠ­áˆŠáˆ ዚወዲህኛው፣ áˆáŠ­áˆ• á‹šá‹ˆá‹²á‹«áŠ›á‹ ነው። ኚነገሥታት áˆ˜áŠ«áŠšáˆ áŠ¥áŠ•á‹° á‹³á‹Šá‰µ á‹šáŠšá‰ áˆš á‹šáˆˆáˆá¢

ምንም áŠ¥áŠ•áŠ³áŠ• ቅዱስ ዳዊት á‹šáŠšá‰ áˆš ቢሆን ዚመመኪያቜንን á‹˜á‹á‹µ ማምጣት አልተቻለውም፡፡

ወቀዳሚተ áˆ˜á‹µáŠ€áŠ’á‰µáŠ áŠ áˆ‹á‰µá¡- ቀዳሚተ ዚወዲህኛው áˆ˜á‹µáŠ€áŠ’á‰µ ዚወዲያኛው ነው፡፡ኚመሳፍንት á‹ˆáŒˆáŠ• á‹šáˆšáˆ†áŠ• ኢያሱ áˆáŠ•áˆ á‹šáˆµáˆ™ ትርጓሜ መድኃኒት ቢሆን á‹šá‹°áŠ…áŠ•áŠá‰³ መሆን አልተቻለውም፡፡

ወመሠሹተ áŠ•áŒœáˆ•áŠ áŠ áˆ‹á‰µ:- መሠሚት á‹šá‹ˆá‹²áˆ…ኛውፀ áŠ•áŒœáˆ• ዚወዲያኛው ኚነቢያተ እግዚአብሔር ወገን ዹሚሆን áŠ€áˆá‹«áˆµ á‰ á‹µáŠ•áŒáˆáŠ“ በንጜሕና áˆ˜áŠ–áˆ© ዚሚታወቅ áŠá‹á¡á¡ 

ነገር áŒáŠ• áˆáŠ•áˆ áŠ•áŒ¹áˆ• á‹µáŠ•áŒáˆ á‰¢á‰£áˆ á‹šáŠ•áŒœáˆ•áŠ“á‰œáŠ•áˆ˜áˆ áˆšá‰µ áˆ˜áˆ†áŠ• áŠ áˆá‰°á‰»áˆˆá‹á¢

ዚመመኪያቜን á‹˜á‹á‹µá£ á‹šá‹°áŠ…áŠ•áŠá‰³á‰œáŠ• መጀመሪያፀ á‹šáŠ•áŒœáˆ•áŠ“á‰œáŠ• áˆ˜áˆ áˆšá‰µ á‰…ድስት á‹µáŠ•áŒáˆ áˆ›áˆ­á‹«áˆ áŠ“á‰µá€â€ á‰ áˆ›áˆˆá‰µ ተናግሯል።

በእርሷ áˆáŠ­áŠ•á‹«á‰µáŠá‰µ áˆ˜á‹µáŠ€áŠ’á‹“áˆˆáˆ  ዚሚፈጜምልንን áŠ«áˆ³áŠá‰¢á‹«á‰µáŠ“ á‹šá‰€á‹°áˆ™ áŠ á‰ á‹ áˆáˆ‰ 
ዚእርሷን áˆ˜á‹ˆáˆˆá‹µ á‰ áŠ“áá‰†á‰µ áˆ²áŒ á‰£á‰ á‰ ነበር።

ኚነቢያት áŠ áŠ•á‹± á‹šáˆ†áА  ኢሳይያስም
“ዚሠራዊት áŒŒá‰³ áŠ¥áŒá‹šáŠ á‰¥áˆ”áˆ­á‹˜áˆ­áŠ• á‰£á‹«áˆµá‰€áˆ­áˆáŠ• 
ኖሮ እንደ ሰዶም á‰ áˆ†áŠ•áŠ  እንደ áŒŽáˆžáˆ«áˆ á‰ áˆ˜áˆ°áˆáА ነበር፡፡” በማለት áˆ˜áŠ“áŒˆáˆ© á‰ áŠ¥áˆ­áˆ· áˆ˜áŒˆáŠ˜á‰µ  ኚጥፋት áˆ˜á‹³áŠ“á‰œáŠ•áŠ• áˆ²áŒˆáˆáŒœ áŠá‹á¡á¡ 
#ኢሳ 1፥9
ዹቩንጋ ፈ/ሕ/አቡነ ተክለሃይማኖት ዹበገና ት/ቀት ትምህርት ክፍል ።
https://www.tg-me.com/sratebetkrstyane
2025/06/30 13:00:46
Back to Top
HTML Embed Code: