Telegram Web Link
መጠነ ሰፊ የመብት ጥሰቶችን ይፋ ያደረገው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዓመታዊ ሪፖርት
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

መጠነ ሰፊ የመብት ጥሰቶችን ይፋ ያደረገው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዓመታዊ ሪፖርት

በየዓመቱ የአገሮችን የሰብዓዊ መብት አያያዝ ሪፖርት የሚያወጣው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ከቀናት በፊት ወደ 200 የሚጠጉ አገሮችንና ግዛቶችን በተመለከተ ያጠናቀረውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡

ኢትዮጵያን በተመለከተ ይፋ ባደረገው ባለ 68 ገጽ ሪፖርት በሰሜን ኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ ክልል የተካሄደው ጦርነት በፕሪቶሪያ ስምምነት ቢገታም፣ በኢትዮጵያና በኤርትራ ድንበር አካባቢዎች የኤርትራ ታጣቂዎች የሚያደርጉት ጥቃት መቀጠሉን በመጀመሪያው የሪፖርቱ ማብራሪያ ላይ ገልጿል፡፡

በ2015 ዓ.ም. ልዩ ኃይሎች ወደ መደበኛ ፖሊስ ወይም የመከላከያ ሠራዊት አባልነት ወይም ወደ ማኅበረሰቡ እንዲቀላቀሉ መደረጉን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ይህንንም ተከትሎ በአማራ ክልል ከፋኖ ታጣቂዎችና በኦሮሚያ ክልል ከኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት (ኦነግ ሸኔ) ጋር ግጭት መቀጠሉንም ያወሳል፡፡

ሪፖርቱ በነሐሴ 2016 ዓ.ም. በአማራ ክልልና እንደ አስፈላጊነቱ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ተፈጻሚ ይሆናል ተብሎ በታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣ በመንግሥት ኃይሎች አማካይነት ሰፋ ያሉ የመብት ጥሰቶች ተፈጽመዋል ይላል፡፡ ከሕግ ውጪ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ የተፈጸሙ ግድያዎች፣ አስገድዶ መሰወር፣ ማሰቃየትና ኢሰብዓዊ ቅጣቶች በመንግሥት አካላት መፈጸማቸውን በሰፊው አብራርቷል፡፡

ከባድና ሕይወትን አደጋ ውስጥ የሚጥሉ የእስር ቤት አያያዞች፣ በኃይል አስገድዶ ማሰርና ማቆየት፣ በጦርነት ወቅት ከሕግ አግባብ ውጪ የሚከናወኑ የንፁኃን ዜጎች ግድያና የአካል ጉዳት፣ በኃይል ማፈናቀልና ከአንዱ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ እንዲዘዋወሩ ማድረግ፣ አካላዊ ጥቃት ማድረስ፣ ፆታዊ ጥቃት፣ የሚዲያ ነፃነትን በከፍተኛ ሁኔታ መገደብ የሚሉት ተጠቅሰዋል፡፡

በጋዜጠኞች ላይ የሚደርስ ዛቻና ጥቃት፣ ያለ ምክንያት በቁጥጥር ሥር ማዋል፣ ሳንሱር፣ በሐሰተኛ ስም የማጥፋት ዘመቻና ውንጀላ፣ የኢንተርኔት ነፃነትን በከፍተኛ ሁኔታ መገደብ፣ ሐሳብን በሰላማዊ መንገድ ለመግለጽ የሚደረጉ የመብት ጥያቄዎችንና የመደራጀት መብት ላይ ጫናና ጣልቃ ገብነት በሰፊው መስተዋሉ በሪፖርቱ ተካቷል፡፡ በተጨማሪም በድርጅቶች ላይ ማውጣት ተጠቅሷል፡፡

በተመሳሳይ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትንና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን የፋይናንስ አጠቃቀማቸውንና እንቅስቃሴያቸውን የሚገድቡ ሕጎች፣ በመንግሥት ውስጥ የሚፈጸም ከፍተኛ ሙስና፣ በዓለም አቀፍና በአገር አቀፍ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ላይ የሚደረግ ዘለፋ፣ ጥቃትና ገደብ፣ አስገድዶ መድፈርና ትንኮሳዎች፣ ፆታዊ ጥቃቶች፣ በአናሳ ብሔረሰቦች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችና የወንጀል ድርጊቶች በሪፖርቱ ተዘርዝረዋል፡፡

ሰፋ ያሉ የንፁኃን ዜጎች ግድያ፣ በጅምላ ማፈናቀል፣ በታጣቂዎች የሚደረግ ዝርፊያና የንብረት ማውደም፣ እንዲሁም በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ከሕግ አግባብ ውጪ የተገደሉ የመንግሥት አመራሮች መኖራቸውን ጠቅሶ በአፋር፣ በኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች በአካባቢ የሚሊሻ አባላት መገደላቸውንና በርካቶች መፈናቀላቸው በሪፖርቱ ተተንትኗል፡፡

የአሜሪካ መንግሥት የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ዓመታዊ ሪፖርት በተጠናቀቀው እ.ኤ.አ. ከ2023 በመንግሥት አካላት ከፍተኛ የሆነ የመብት ጥሰት መከናወኑን አረጋግጫለሁ ብሏል፡፡ መረጃውን ከአምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ ከሂዩውማን ራይትስዎች፣ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ)፣ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ (ኢሰመጉ)፣ በተለይም በአማራ፣ በኦሮሚያና በትግራይ ክልሎች ተፈጸሙ የተባሉ የመብት ጥሰት ሪፖርቶችን በመመልከት መሆኑን አስታውቋል፡፡

የክልል የፖሊስ አካላት አደገኛና ከመጠን በላይ የሆነ ኃይል በንፁኃን ዜጎች ላይ እንደሚጠቀሙ፣ ለአብነትም እ.ኤ.አ. በየካቲት 2023 በወልቂጤ ከተማ የመጠጥ ውኃ ጥያቄ እንዲመለስላቸው በሰላማዊ ሠልፍ ለመጠየቅ የወጡ 30 ዜጎችን በጦር መሣሪያ መግደላቸውን፣ በአዲስ አበባ የመስጊድ መፍረስን የተቃወሙ ሦስት ንፁኃን ዜጎችን የመንግሥት ኃይሎች መግደላቸውን፣ በዚህም ረገድ የፌዴራል ፖሊስ የተፈጸሙ የወንጀል ድርጊቶችን ለመመርመር የሄደበት ርቀት ውስን መሆኑን አብራርቷል፡፡ የተወሰዱ ዕርምጃዎችም ሚስጥራዊ ተደርገው መቀመጣቸውን ጠቅሷል፡፡

በኃይል አስገድዶ መሰወር በተለይም በመንግሥት ላይ የተለየ ሐሳብ የሚሰነዝሩ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የፖለቲካ ተንታኞች፣ የቀድሞ የሠራዊት አባላት፣ የምርመራ ጋዜጠኞችና የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎች ላይ በብዛት ሥወራ እንደሚፈጸም አስታውቋል፡፡

ከአዲስ አበባ ወደ ጂቡቲ የሚጓዙ ሾፌሮች የሚያነሱት የፀጥታ ችግር መንግሥት ለመፍታት አለመቻሉን፣ ሾፌሮች ሲታገቱና ሲገደሉ የፀጥታ ሁኔታውን ለማስተካከል እንደተሳነው በሪፖርቱ ተመላክቷል፡፡

በሕገ መንግሥቱ የተከለከለ በቁጥጥር ሥር በዋሉ ግለሰቦች ላይ ማሰቃየትና አካላዊ ጥቃቶች መፈጸሙንና በተለይም በአማራ፣ በቤኒሻንጉል በጉሙዝ፣ በጋምቤላና ሶማሌ ክልሎች እስረኞችን በመደብደብ መረጃ እንዲያወጡ ይደረጉ እንደነበር ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ተረድቻለሁ ብሏል፡፡

የማይታወቁና ሚስጥራዊ የማቆያ ቦታዎች መኖራቸውን፣ መጥፎና አሳሳቢ የሆነ የእስረኞች አያያዝና የማሰቃየት ተግባር በተለይም በፖሊሶች፣ በማረሚያ ቤት ጠባቂዎች ወይም በሌሎች ወታደራዊና የፀጥታ ኃይሎች አማካይነት ይፈጸም እንደነበር ጠቅሷል፡፡ እነዚህ ድርጊቶች ይፈጸሙ የነበሩት በፖሊስ ጣቢያዎች፣ በማቆያ ቦታዎች፣ በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች፣ በወታደራዊ ማዕከላት፣ ሚስጥራዊ በሆኑና ባልታወቁ የማቆያ ቦታዎች እንደሆነ ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

የማረሚያ ቤቶች ሁኔታ ከባድና ሕይወትን አደጋ ውስጥ የሚጥል መሆኑን የሚያብራራው ሪፖርቱ፣ ይህም ሊሆን የቻለው ታራሚዎችና በቁጥጥር ሥር የዋሉ ግለሰቦች በተጨናነቀ ቦታ እንዲሆኑ በመደረጉ ሳቢያ በምግብ እጥረት፣ በሚደርሰባቸው አካላዊ ጥቃት፣ በቂ ባልሆነ የመፀዳጃ አገልግሎትና መሰል አሳሳቢ ምክንያቶች ነው ብሏል፡፡

በጅምላ አስሮ ማቆየት የተለመደ አሠራር ነው የሚለው የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤቱ ሪፖርት፣ ለታራሚዎች ጥራት ያለው ምግብና ውኃ፣ እንዲሁም የመፀዳጃ አገልግሎት፣ የሕክምና አለመኖር፣ በመኖሪያ ቤት ውስጥ የኤሌክትሪክ አቅርቦት አለመኖሩን ይጠቅሳል፡፡

ታራሚዎችን በተደበቀና ለብቻው በተሠራ ቤት ውስጥ እንደሚቆዩ፣ በዚህ ማቆያ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ማድረግ የማይችሉ መሆኑንና የምግብ፣ የውኃና የመፀዳጃ አገልግሎት እንደማያገኙም ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

የአገር መከላከያ ሠራዊት አባላት ጭምር እስረኞችን ከማቆያ ቤት እያወጡ ይረሽኑ እንደነበር የገለጸው ሪፖርቱ፣ መንግሥት ብዙ ያልታወቁ ሚስጥራዊ የማቆያ ቦታዎችን መጠቀሙ እየጨመረ ነው ይላል፡፡ 

በሕገ መንግሥቱና በሌሎች ሕጎች አማካይነት ያለ ፍርድ
ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማበረታቻ ጎን ለጎን ዋጋቸውና ጥራታቸውም ይታሰብበት!
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማበረታቻ ጎን ለጎን ዋጋቸውና ጥራታቸውም ይታሰብበት!

መንግሥት በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ በተለያዩ መንገዶች ክልከላ እያደረገ ነው፡፡ በአንጻሩ በነዳጅ ከሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ይልቅ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች እንዲገቡ ማበረታቻዎችን እየሰጠ ነው፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በተለይ ሙሉ በሙሉ ተበትነው የሚመጡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በአገር ውስጥ ሲገጣጠሙ የማኅበራዊ ዋስትና ከሚባለው የሦስት በመቶ ታክስ ውጪ ከታክስ ነፃ ናቸው፡፡

በቀጥታ የሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በነዳጅ ከሚሠሩ ተሽከርካሪዎቹ ያነሰ ታክስ እንዲከፈልባቸው ተደርጎ የሚገቡም ናቸው፡፡ በተወሰነ ደረጃ ዕቃዎቻቸው መጥተው እዚህ የሚገጣጠሙ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች የሚከፍሉት ደግሞ አምስት በመቶ የጉምሩክ ቀረጥ ብቻ ነው፡፡

በቀጥታ የሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ላይ የሚጣለው ታክስም በነዳጅ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ላይ ከሚጣለው ታክስ በእጅጉ እንዲቀንስ ተደርጓል፡፡ አሁን በተሰጠው ማበረታቻ በቀጥታ የሚገቡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ሌሎች ታክሶች ሳይታሰብባቸው የሚጠበቅባቸው 15 በመቶ ቀረጥ ብቻ ነው፡፡

ማበረታቻው ይህ ብቻ አይደለም፡፡ በኤሌክትሪክ ለሚሠሩ ተሽከርካሪዎች የውጭ ምንዛሪ ከባንኮች ማግኘት ይቻላል፡፡ ይህም ማበረታቻ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን ለማስመጣት ሌላ የተሻለ ዕድል መስጠቱን ያስገነዝበናል፡፡

እንዲህ ያለው ማበረታቻ በእርግጥም በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች በገፍ እንዲገቡ ያስችላል ተብሎ ይታመናል፡፡ ከቤት አውቶሞቢሎች ባሻገር የከተማ አውቶቡሶችን በኤሌክትሪክ በሚሠሩ አውቶቡሶች የመተካት ዕቅድ ያለ መሆኑም፣ መንግሥት የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን በማብዛት የነዳጅ ወጪውን ለመቀነስ ቁርጠኛ መሆኑን ያመለክታል፡፡

መንግሥት በዚህ ዘርፍ ያለውን ጠንከር ያለ አቋሙን የምናይበት ሌላው መገለጫ ደግሞ፣ በቅርቡ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ የታክሲ አገልግሎት የሚሰጡ ሚኒባሶችን ለሙከራ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሥራ እንዲጀምሩ ማድረጉ ነው፡፡

የመንግሥት ውሳኔ በዚህ ብቻ የሚያበቃ አልሆነም፡፡ በነዳጅ የሚሠሩ ሞተር ሳይክሎች የማይበረታቱ መሆኑንም አሳውቋል፡፡ እንዲህ ያሉ ዕርምጃዎች መንግሥት በነዳጅ ከሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ይልቅ በኤሌክትሪክ ለሚሠሩት ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ያሳያል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተጨባጭ እያየን ያለነውም በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች መንገዱን እየያዙ መሆኑን ነው፡፡ ጥቂት የማይባሉ የመኪና መሸጫዎች በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎችን አብዝተው መያዝ መጀመራቸው በራሱ መጪው ጊዜ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ብልጫ እንደሚይዙ ጠቋሚ ነው፡፡

ሆኖም የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች አስፈላጊነት ታምኖበትና ጠቀሜታውም ተሰልቶ ማበረታቻ እየተሰጠ እንዲገቡ መፈቀዱ ብቻ፣ የሚፈለገውን ውጤት ያስገኛል ማለት እንዳልሆነም ሊታወቅ ይገባል፡፡

ተሽከርካሪዎቹን እንዲገቡ ከመፍቀድ ጎን ለጎን ዘላቂ ጠቀሜታ እንዲሰጡ፣ አብረው ሊተገበሩ የሚገባቸው ወሳኝ ጉዳዮች የተዘነጉ ስለሚመስል እነዚህን ወሳኝ የሚባሉ ዕርምጃዎች በቶሎ መተግበር ይገባል፡፡

ከእነዚህ ተሽከርካሪዎች ጋር በተያያዘ በአፋጣኝ መተግበር አለባቸው ተብለው ከሚጠቀሱ ዕርምጃዎች መካከል፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች በትክክል የጥራት ደረጃቸውን ጠብቀው የተፈበረኩ ወይም የተገጣጠሙ መሆናቸውን በሚገባ ማረጋገጥ አንዱ ነው፡፡ እንደ ተገልጋይ ወይም እንደ ሸማች ይህ ቁልፍ ጉዳይ ነው፡፡

ሁለተኛው ጉዳይ በዚህን ያህል ደረጃ ማበረታቻ የተሰጣቸው የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ አስመጪዎችና መገጣጠሚያዎች፣ የመሸጫ ማበረታቻውን ባገናዘበ መልኩ ዋጋቸው የተመጣጠነ ሆኖ ለተጠቃሚው ማስተላለፍ አለባቸው፡፡

ማበረታቻ የሚሰጠው አስመጪውን ወይም መገጣጠሚያውን ለመጥቀም ብቻ እንዳልሆነም መታወቅ አለበት፡፡ መንግሥት ሊያገኝ የሚገባውን ግብር የሚተመነው ዜጎች ከተሰጠው ማረታቻ በዋጋ ደረጃ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማሰብ ጭምር መሆኑ ሊሳት አይገባም፡፡ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች እንዲገቡ የሚሰጠው ማበረታቻ ግቡን እንዲመታ እንዲሁም ዜጎች ፈልገው እንዲገለገሉበት ለማድረግ በተመጠነ የትርፍ ህዳግ ግብይቱ ሲፈጸምና ይህም ከወዲሁ ሊታሰብበት ይገባል፡፡

ሦስተኛውና ጊዜ ሊሰጠው የማይገባው ጉዳይ ደግሞ፣ የእነዚህ ተሽከርካሪዎች የጥገና አገልግሎትና አገልግሎቱ በሠለጠነ የሰው ኃይል እንዲካሄድ ማስቻል ነው፡፡ ሌላው ጥያቄ ደግሞ፣ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎቹ በቀላሉ ኤሌክትሪክ ሊሞሉበት የሚችሉበት የኤሌክትሪክ ማደያ ስቴሽኖች ግንባታ ነው፡፡

እነዚህ ወሳኝ የመሠረተ ልማት ግንባታና አገልግሎቶች መተግበር ያለባቸው ወይም ሊጀመሩ የሚገባቸው ተሽከርካሪዎቹ መንገድ ከሞሉ በኋላ ሳይሆን ከዲሁ ነው፡፡ በተለይ የባትሪ መሙያዎች ወደ ሥራ እንዲገቡ ማመቻቸት ግድ ይላል፡፡

የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን መጠቀም ሌላው እንደ ሥጋት እየታየ ያለው ባትሪያቸው ካለቀ ወይም ከተበላሸ መልሶ ለመተካት ከፍተኛ ወጪ ይጠይቃል መባሉ ነው፡፡

ይህ ሥጋት ትክክል ከሆነ እንዲህ ያሉ ዛሬ ሳይሆን ወደፊት የሚያጋጥሙ ችግሮትን ለማቃለል ከወዲሁ ሊታሰብበት ይገባል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያም ኅብረተሰቡ በቂ መረጃ እንዲኖረው ማድረግና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታውን በአግባቡ መተንተን ሁሉ ይጠይቃል፡፡

ሥጋቱን ለመቀነስም እንደ ኢንሹራንስ ያሉ ተቋማት የሚኖራቸው አስተዋጽኦ ከፍተኛ በመሆኑ፣ እነርሱም የበኩላቸውን በማድረግ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎችን ለሚጠቀሙ ተገልጋዮች የተለየ የኢንሹራንስ ሽፋን በማዘጋጀት ኃላፊነታቸውን እየተወጡ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ዕድል ሊያመቻቹ ይገባል፡፡

በአጠቃላይ የኤሌክትሪክ ተሽከርካዎች አገራችን ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ አንፃር ጠቀሜታ የሚኖራቸው ቢሆንም፣ በአግባቡ እንዲያገለግሉ ምቹ ሁኔታዎች ሊፈጠሩላቸው ይገባል፡፡

The post ከኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ማበረታቻ ጎን ለጎን ዋጋቸውና ጥራታቸውም ይታሰብበት! first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ናታን ዳዊት
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አድልኦ እየፈጸመ ነው የሚል ቅሬታ ቀረበበት
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አድልኦ እየፈጸመ ነው የሚል ቅሬታ ቀረበበት

አገልግሎቱ ቅሬታውን አስተባብሏል

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዜጎች ሊያሟሏቸው የሚገቡ መረጃዎችን ይዘው ቢቀርቡም፣ በቀለማቸው ተለይተው አገልግሎቱን ከማግኘት የሚከለከሉበት ተቋም መሆኑን በመግለጽ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ቅሬታቸውን አቀረቡ፡፡

ዓርብ ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸሙን ያቀረበው አገልግሎቱ፣ በተለይ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሚመጡ ዜጎች በቀለማቸው ምክንያት አገልግሎቱን ከማግኘት እየተከለከሉ መሆናቸውን፣ በምክር ቤቱ የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አባል አቶ ሙባረክ ኤሊያስ ቅሬታ አቅርበዋል፡፡

‹‹ሌሎች ዜጎች ብቻ ሳይሆኑ የክልሉ ካቢኔ አባላት ሳይቀሩ የአገሪቱ ዜጎች እንዳልሆኑ በሚገልጽ ስሜት፣ አገልግሎቱን ሳያገኙ እንዲመለሱ ተደርገዋል፤›› ያሉት አቶ ሙባረክ፣ ከፍተኛ እንግልት እየደረሰባቸውም ነው ብለዋል፡፡

አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ በአሥራ ሦስት ክልሎች ድጋፍና ክትትል እየተደረገ መሆኑን፣ ነገር ግን ውጤታማነቱ ጥያቄ የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ የአገልግሎቱ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤቶች ቢከፈቱም አገልግሎት እየሰጡ አለመሆናቸውን አቶ ሙባረክ አስረድተዋል፡፡ 

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት ባለፉት አምስት ዓመታት የየብስ ትራንስፖርት አለመኖሩን፣ በዚህም ምክንያት ዜጎች ፓስፖርት ፍለጋ ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

ከዚህ ቀደም በተቋሙ ከፍተኛ የሆነ የአሠራር ብልሹነት በመኖሩና ከአመራር ጀምሮ ያሉ ሠራተኞቹ በሙስና ተዘፍቀዋል ብለው ባለፈው ዓመት መገባደጃ በአዲስ አመራሮች እንዲተኩ መደረጉ ይታወሳል፡፡ በ2015 ዓ.ም. መጨረሻ የተሾሙት ዋና ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት፣ በቋሚ ኮሚቴው አባል የተነሳው ጥያቄ የተፈጠረው በምን አጋጣሚ እንደሆነ እንደማያውቁ ገልጸው፣ የተባለው ዓይነት አሠራር በተቋማቸው እንደሌለ በመግለጽ ቅሬታውን አስተባብለዋል፡፡

‹‹በድንበር አካባቢ ካሉ ቦታዎች የሚመጡ ዜጎች ይዘውት የሚመጡትን ማስረጃ ማረጋገጥ ስላለብን የልደት ካርድ፣ በተጨማሪም መታወቂያ እናያለን፡፡ ባለሙያው ማስረጃው ሕጋዊ መስሎ ካልታየው ተጨማሪ ማስረጃዎችን የሚጠይቀው ክፍል እንዲሄድ ይደረጋል፤›› ብለዋል፡፡

ሁሉም ሰው አገልግሎቱን ማግኘት ያለበት በሚያቀርበው መረጃ መሠረት ሊሆን እንደሚገባ ገልጸው፣ ‹‹በቀለም ተመርጦ አገልግሎት ይሰጣል›› የሚለው ግን ትክክል አይደለም በማለት ተከራክረዋል፡፡ የዳይሬክተሯ ምላሽ ያልተዋጣላቸው አቶ ሙባረክ በበኩላቸው ማስረጃ ማቅረብ ካስፈለገ ማቅረብ እንደሚችሉ በመግለጽ፣ የአሠራር ችግር ካለ እናስተካክላለን መባል ሲገባው፣ ‹‹በእኛ በኩል ዕውቅና የለም›› የሚለው ተቀባይነት የለውም ብለዋል፡፡

‹‹ማስረጃ ከቀበሌና ከክልል ተሰጥቷቸው ሱዳናዊ ናችሁ ተብለው አገልግሎቱን ተከልክለዋል፣ ይህም ዜጎቻችንን ያስከፋ ተግባር ነው፤›› ሲሉም አክለዋል፡፡   

‹‹የአባትና የእናት እንዲሁም የትምህርት ሰነድ ሲጠየቁ እንደሌላቸው የሚገልጹ ዜጎች በመኖራቸው ተጨማሪ ምርመራዎች ማድረግ ያስፈልጋል፤›› ሲሉ የአገልግሎቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ቢቂላ መዝገቡ ተናግረው፣ ይህ ሒደት ጊዜ እንደሚወስድና አንዳንዶችም የውጭ አገር ዜጎች ሆነው እንደሚገኙ አስረድተዋል፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ700 ሺሕ በላይ ፓስፖርቶችን ለተገልጋዮች ማድረስ መቻሉን የተቋሙ የሥራ ኃላፊዎች የገለጹ ሲሆን፣ ከአንድ ዓመት በላይ ሳይታተሙ የቀሩ ውዝፍ ኅትመቶችን በማሳተም 65 በመቶ ተገልጋዮች ፓስፖርታቸውን እንዲወስዱ መደረጉን አመላክታል፡፡

በተጨማሪም ለፓስፖርት ኅትመት የሚወጣውን የውጭ ምንዛሪ ለማስቀረት በሚቀጥለው ዓመት በአገር ውስጥ ማሳተም እንደሚጀመር አስታውቀዋል፡፡

The post የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት አድልኦ እየፈጸመ ነው የሚል ቅሬታ ቀረበበት first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ፅዮን ታደሰ
ቤት ማዘዣ ማንንም በቁጥጥር ሥር ማዋል እንደማይቻል ቢደነግግም፣ ባለሥልጣናት ተጠርጣሪን ያለ ምንም ማስረጃ በቁጥር ሥር እንደሚያውሉ፣ ክስ ሳይመሠረት ለ14 ቀናት እንደሚያቆዩ፣ ፍርድ ቤቶች በተጠረጠሩ ግለሰቦች ላይ ለሚቀርቡ ክሶች ማስረጃ እንዲቀርብ ግፊት ቢያደርጉም ፖሊስ ተጨማሪ መረጃ እየጠየቀ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን የእስር ጊዜ እንደሚያራዝም በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በዋስትና መፈታት መብት ቢሆንም ፖሊስ በዋስትና እንዲፈቱ በፍርድ ቤት ውሳኔ ያገኙ ዜጎችን እንደማይለቅ፣ ይባስ ብሎ ሌላ ተጨማሪ ክስ እንደሚመሠርት የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ በተደጋጋሚ የዋስትና መብቶች እንደሚጣሱ አንዳንዴም እስረኞችን ወደ ክልሎች በማዘዋወር በሌላ ተጨማሪ ወንጀል እንዲጠየቁ እንደሚያደርግ ተጠቅሷል፡፡

መንግሥት ከነሐሴ 2015 ዓ.ም. ወዲህ ተግባራዊ እያደረገ ባለው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት መጋዘኖችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ የወጣት ማዕከላትን፣ የግል መኖሪያዎችንና ሌሎች ቦዎታችን ወደ ማቆያነት በመቀየር በሺዎች የሚቆጠሩ የአማራና የኦሮሞ ብሔር ተወላጆች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡ በተወሰኑ አካባቢዎች ሕፃናትን በወንጀል ተጠርጥረዋል በሚል ጥርጣሬ ብቻ በማቆያ ቦታ እንደሚታገቱ አብራርቷል፡፡

ረዥም ጊዜ የሚወስድ የፍርድ ሒደት፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው እስረኛ፣ ቀልጣፋ ያልሆነ የፍርድ ቤት ውሳኔና ውስን የሰው ኃይል ያላቸው ፍርድ ቤቶች ለፍርድ ሒደት መዘግየት አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በሕጉ መሠረት ፍርድ ቤቶች ነፃና ገለልተኛ እንዲሆኑ ቢጠበቅም፣ የመንግሥት ጣልቃ ገብነት የፍርድ ቤቶችን ገለልተኛናትና ሚዛናዊነት የማያከብር መሆኑን የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ የፍትሐ ብሔር ችሎቶች በተሻለ በገለልተኝነት ቢሠሩም የወንጀል ጉዳይ ችሎቶች ደካማና በከፍተኛ ሁኔታ የታጨቁና የተጨናነቁ ናቸው ይላል፡፡

የመንግሥት አካላት ከድንበር ያለፈ የማስፈራራት ተግባር ይፈጽማሉ የሚለው ሪፖርቱ፣ ለአብነትም ከሳዑዲ ዓረቢያ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተላልፎ የተሰጠ ጋዜጠኛ ስለመኖሩ አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ በውጭ አገር የሚኖሩ ዳያስፖራ ጋዜጠኞች በኢትዮጵያ ያሉ ቤተሰቦቻቸው ማስፈራሪያና ዛቻ እየደረሰባቸው ነው ብሏል፡፡

ያለ ፍርድ ቤት ማዘዣ የግል ንብረትን መበርበር እንደማይቻል በሕግ የተቀመጠ ቢሆንም መንግሥት ይህንን ፈጽሞ እንደማያከብር ያብራራል፡፡

መንግሥት የፖለቲከኞችንና የግለሰቦችን ስልክ በአቅጣጫ ጠቋሚ የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችና በኢንተርኔት የታገዘ የኮሙዩኒኬሽን መሣሪያዎችን በመጠቀም፣ የመጥለፍ ሥራ ላይ መሰማራቱ በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

የመንግሥት አካላት እ.ኤ.አ. ከ2021 ጀምሮ በቁጥጥር ሥር የዋሉ ዜጎችን ስልክ ለመበርበር የሚረዳ ሰለብራይት ከተባለ የእስራኤል ኩባንያ የስለላ መሣሪያ ገዝቶ ሥራ ላይ ማዋሉን፣ የኦንላይን የመረጃ ምንጭ የሆኑ ድረ ገጾችንና ኢንተርኔት በተደጋጋሚ መዝጋቱንና ለዚህም ይግባኝና አቤቱታ የሚጠየቅበት መንገድና አሠራር አለመኖሩን አብራርቷል፡፡

የመንግሥትን አሠራር አጥብቀው የሚጠይቁ የሰብዓዊ መብቶችና የሚዲያ ተቋማት ቢሮዎች ተሰብሮ መገባቱን፣ የሚዲያና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ ተቋማት ላይ የሚፈጸምን ዝርፊያ በተመለከተ ምርመራ እንዲያካሂድ መንግሥት ቢጠይቅም እስከ ዓመቱ መጨረሻ ድረስ ምን ዓይነት ዕርምጃ እንደወሰደ ማወቅ አልተቻለም ብሏል፡፡

የሰሜኑን ጦርነት ተከትሎ የሚነሱ የሰብዓዊ ዕርዳታዎች አቀራረብና የፀጥታ ሁኔታውን በተመለከተ አስተያየት የሚሰጡ ጋዜጠኞች፣ የማኅበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና ሌሎችንም አስገድዶ እንደሚያስር በሪፖርቱ ተገልጿል፡፡

በርካታ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞችን በበቀል ዕርምጃ በወንጀል ክሶች በተለይም ከፅንፈኝነትና ከአሸባሪነት ጋር በተገናኘ በቁጥጥር ሥር ካዋላቸው በኋላ፣ በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ጉዳይ ሳይጠየቁ የጋዜጠኝነት ሥራቸውን ስላከናወኑ ብቻ ለተወሰነ ጊዜ ታስረው እንደሚለቀቁ፣ ይህም የመንግሥት ባለሥልጣናት ጋዜጠኞችን አፋቸውን ለማዘጋትና ፍራቻን ለመልቀቅ የሚጠቀሙበት ሥልት በመሆኑ ነው ሲል ሪፖርቱ ያስረዳል፡፡

በኢትዮጵያ በቴሌኮሙዩኒኬሽን ዘርፍ የመንግሥት ተፅዕኖ መስፋቱን የገለጸው ሪፖርቱ፣ በኢትዮ ቴሌኮም አማካይነት የኦንላይን ሚዲያ በአገር አቀፍ ደረጃ እየዘረጋ ነው ብሏል፡፡

ዕውቅና ያልተሰጣቸው ሰላማዊ ሠልፎች የወንጀል ዕርምጃ እንደሚያስከትሉ የጠቀሰው ሪፖርቱ፣ ሰላማዊ ሠልፎችን ማድረግ ያልተለመደ ተግባር መሆኑን፣ ሰላማዊ ሠልፎች ከተካሄዱ ግን የፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ ለውጥ መኖሩ ማሳያ ስለመሆኑ ሪፖርቱ ያመለክታል፡፡

ሕጉ በአገር ውስጥ መንቀሳቀስ፣ የውጭ አገሮች ጉዞ ማድረግ፣ መሰደድና መመለስን የሚያከብር ቢሆንም መንግሥት የዜጎችን እንቅስቃሴ በአገር ውስጥም ሆነ ከአገር ውጭ ጉዞዎች ላይ ክልከላና ገደብ ስለማስቀመጡ ያወሳል፡፡ በአገር ውስጥ ከአንድ ክልል ወደ ሌላ ክልል በሚደረጉ ጉዞዎች በተለይም ትግራይ፣ አማራ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝና ምዕራብ ወለጋ አካባቢዎች መንቀሳቀስ የማይቻል ነው ይላል፡፡ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት በርካታ የኬላ መቆጣሪያዎች በተለይ ክልሎችን በሚያገናኙ መንገዶች መኖራቸው፣ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ለማከናወን እንዳይቻል ስለማድረጉ አብራርቷል፡፡

ሪፖርቱ እ.ኤ.አ. በ2023 የኦሮሚያ ክልልና የፌዴራል ፖሊስ በሕዝብ በዓላትና መሰል ጉዳዮች ወደ አዲስ አበባ የሚደረጉ ጉዞዎችን የፀጥታ ሥጋት በሚል ሰበብ ከከተማ ውጭ የሚመጡ ዜጎች እንዳይገቡ ገደብ ስለመጣላቸው አውስቷል፡፡ በዚህ ገደብ የተነሳ በአመዛኙ ከጎጃምና ከጎንደር የአማራ ክልል ከተሞች የሚመጡ ወጣቶች ላይ ያተኮረ እንደነበር አስረድቷል፡፡ በተመሳሳይ ወደ ውጭ አገር የሚጓዙ ግለሰቦች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ያለ ምንም ትዕዛዝ ከአገር እንዳይወጡ እንደሚከልከሉ አመላክቷል፡፡ ለአብነትም የቀድሞ የአማራ ልዩ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞ ለሕክምና ወደ እስራኤል ሊያደርጉት የነበረው ጉዞ በፀጥታ ኃይሎች መሰረዙን አስታውሷል፡፡

መንግሥት እ.ኤ.አ. ከ2020 ጀምሮ ከኤርትራ ወደ ኢትዮጵያ ለጥገኝነት የሚመጡ ዜጎችን መመዝገብ ማቆሙን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የስደተኞች ድርጅት ማስታወቁን ጠቅሶ በዚህም የተነሳ ያልተመዘገቡ ኤርትራውያን ጥገኝነት ፈላጊዎች ቁጥር ማሻቀቡንና እንደ ስደተኛ ባለመመዝገባቸው ምንም ዓይነት አቅርቦት እንደማይደርሳቸው ጠቅሷል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ኤርትራውያንን መመዝገብ ቢያቆምም ለ40 ሺሕ ሱዳናውያንና ለ100 ሺሕ የሶማሌላንድ ዜጎች የጥገኝነት ምዝገባ ማድረጉን አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም የጥገኝነት ምዝገባ ተደርጎላቸው የሚኖሩ ሰዎች የመንቀሳቀስ መብታቸው የተገደበ ነው ይላል፡፡

በአገሪቱ ሕግ በሙስና ድርጊት የተሳተፉ አካላት በወንጀል እንደሚጠየቁ የተደነገገ ቢሆንም፣ መንግሥት ሕጉን በሚገባው መጠን እንደማይተገብረው ሪፖርቱ አስታውቋል፡፡

የተለያዩ የአገር ውስጥና የውጭ የሰብዓዊ መብቶች ድርጅቶች ሰብዓዊ መብቶችን በተመለከተ የሚያከናውናቸው ተግባራት፣ በማያቋርጥ የደኅንነት ሥጋትና ገደብ የተነሳ ምርመራ አካሂደው ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ እንደሚቸገሩ ጠቅሷል፡፡ የአገር ውስጥ ድርጅቶች በተደጋጋሚ፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ድገሞ አልፎ አልፎ ከፀጥታ አካላት ማስፈራሪያና ዛቻ እንደሚደርሰባቸውና  በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡

ሪፖርቱ ዓለም አቀፍና አገር አቀፍ የዕርዳታ ድርጀቶች፣ የሰብዓዊ መብት ተቋማትና ዲፕሎማቶችና በተለዩ ቦታዎች እንዳይንቀሳቀሱ ገደብ እንደሚጣልባቸው ሪፖርቱ ያብራራል፡፡

አስገድዶ መድፈር
አገር ባለውለታነቷን የምታረጋግጥበት ሥርዓታችንን እንፈትሽ!
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

አገር ባለውለታነቷን የምታረጋግጥበት ሥርዓታችንን እንፈትሽ!

በገነት ዓለሙ

በሕግ አምላክ እያለ የሚማጠነው ፖለቲካችን፣ ሰላማችን በአጠቃላይ አኗኗራችን ሁሉ ሕግ ማክበርን፣ ለሕግ መገዛትን የግድ እንደሚጠይቅ ሳይታለም የተፈታ በየትም አገር የታወቀ እውነት ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት ጽሑፌ እንደጠቆምኩት ሕጋዊና ቀጥተኛ መንገዶች እንዲታመኑና እንዲመረጡ፣ ዘወርዋራ፣ መሠሪና ሕገወጥ መንገዶች እርም እንዲባሉ፣ በየትኛውም ዘርፍ ያለው ሕይወት በተገኘው ማናቸውም አቋራጭና አጋጣሚ ሁሉ የመጠቀም ቁማር መሆኑ እንዲቀር የመንግሥት ድርሻም ከፍተኛና ወሳኝ ነው፡፡ ሕግ ገዥ ወደ ሆነበት ሥርዓት ለመሸጋገርና ያንንም ጉዞ ለመጀመር፣ እንዲሁም የዚህን መንገድ ለማንጠፍ የመንግሥት የራሱ ለሕግ ተገዥነት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ መንግሥት የገዛ ራሱን (አገር) ሕግ አክባሪና ባወጣው ሕግ ተዳዳሪ የመሆን ጉዳይ የሕግ አወጣጡን ሕግ፣ የሚወጣውን ሕግ ዓይነት፣ ይህንን ሕግ ለማስፈጸም በማደራጀት በሚዘረጉት ተቋማትና አሠራሮች ላይም የተመሠረተ ነው፡፡

ለምሳሌ ለመላው ዓለም እንግዳ ደራሽ ሆኖ ከሞላ ጎደል አዲስ ዓይነት የሕግ ዝግጁነት የጠየቀው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተራርቆ መኖርን ግድ የሚያደርግ፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ሕግ እንዲወጣ ያደረገ (መጨባበጥንና መሰባሰብን የከለከለ፣ ከውጭ አገር የሚመጣ እንግዳን ሆቴል እንዲያርፍ ያስገደደ) ጥንቃቄ ጠይቆናል፡፡ በአጠቃላይ አደጋውን እንደነገሩ የተወጣነው በሽታ የመከላከል የሕግ አሠራርና የተቋም ዝግጁነትን ነበር ብሎ አፍ ሞልቶ መናገር ያስቸግራል፡፡

ሌላ ምሳሌ እንመልክት፡፡ ሰው ሁሉ ዛሬ ስለቅርስና ስለታሪክ የሚነጋገርበት፣ አልፎ አልፎም ጠበኛ የሆነበት ነው፡፡ ግን የቅርስ ጥበቃ ሕግ አለ፡፡ የቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን የሚባል ተቋምም አለን፡፡ ክርክሩና ሙግቱ ግን እነዚህን ሲማጠን፣ ሲጠቅስ፣ ዋቢ ሲያደርግ አንሰማም፡፡ የመንግሥት የተለያዩ የሥልጣን አካላት የአገርን ‹‹የሕግ አምላክ›› የማልማት፣ የማጠናከር ድርሻ እነዚህን የስም ጌጥ ብቻ ሆነው የቀሩ ሕጎችንና ተቋማትን የመፈተሽ አደራና ግዳጅም ይጨምራል፡፡ ይህን የመሳሰሉ ሪሰሲቴሽን (Resucitation) ወይም ተንሰአት የሚጠይቁ አዲስ መወጣትና ያለውን ጎዶሎ ለመሙላት የሚያስፈልጉ የሕግ ዓይነቶች አሉ፡፡ ከነዚህ መካከል አንዱ የሜዳይ፣ የኒሻንና የሽልማት ረቂቅ ሕግ ነው፡፡

አሁን በምንገኝበት ተጨባጭ ሁኔታ ስለዚህ ጉዳይ፣ ስለሜዳይ፣ ኒሻንና ሽልማት ማውራት ቀልድ ተደርጎ ሊታይ ይችላል፡፡ በየአቅጣጫውና በየመስኩ ግን በተቋም ግንባታ ሥራችን እጅግ መበርታት አለብን፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ስም ያለው፣ በመላው ዓለማት የታወቀና የተከበረ፣ አሁንም በታሪክና በቅርስ ሰዎች ዘንድ ከፍ ያለ ቦታ ተሰጥቶ የሚጠናና የሚሰበሰብ የ‹‹አመሠግናለሁ›› ሥርዓት ነበራት፡፡ አገር ባለውለታነቷን የምትገልጽበት ይህ የክብርና የማዕረግና ሥርዓት ግን አንድም በየዘመኑ ሥልጣን ላይ በነበሩት ገዥዎች እምነት አምሳል የተሟሸ ዘመናዊውንም የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት የማያውቅ ወይም ያላከበረ በመሆኑ፣ ሌላም ደግሞ የአንዱ ገዥ የሥልጣን ዘመን በኃይልና በጉልበት ሲያከትም ተከታዩ ገዥ የቀድሞውን የክብርና የማዕረግ ሥርዓት እንዳለ አሽቀንጥሮ የሚጥለው በመሆኑ ይህ ሥርዓታችንና ሥርዓቱን የሚገዛው ሕግ ክፍት ሆኖ ኖሯል፡፡ ለዚህ ባዶነት ተወያይቶ ሕዝብና ያገባኛል ባዮችን ሁሉ አማክሮ፣ ባለሙያም አነጋግሮና መላ መፍጠር በቀጠሮ የሚያድር ሥራ አይደለም፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ማቋቋሚያ ሕግ የተቋሙን አስተዳደራዊና አስፈጻሚ አካል ሥልጣንና ተግባር በሚደነግግበት አንቀጹ (አንቀጽ 13) (1) (ኤል) ‹‹A System of Awards, Medals and Prizes›› እንዲቋቋም ያዛል፡፡ በቅርቡ መጋቢት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ትግራይ ክልል ውስጥ ለተሰማሩት በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት በተቋቋመው የስምምነቱ ‹‹ሞኒተሪንግ ቬሪፊኬሽንና ኮምፕላየንስ ሚሽን›› ሥራ ለሚያከናውኑ ሃያ አንድ ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከናይጄሪያና ከደቡብ አፍሪካ ለተወጣጡ ወታደራዊና ሲቪል ባለሙያዎች የተሰጠው የአገልግሎት ሜዳልያ መነሻና መሠረት አኅጉራዊው ድርጅት ባለውለታነቱን የሚገልጽበት ሥርዓት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለዚህ የፕሪቶሪያ ስምምነትና አመሠግናሁ ላላቸው ሰዎች ‹‹የምስክር ወረቀት›› (ሰርተፊኬት) ሲሰጥ ዓይነተናል፡፡ የዚህ የምስክር ወረቀትና ዋጋ የሕግ መሠረቱ ምንድነው ብሎ መጠየቅ ‹‹ጉድለታችንን›› ያጋልጣል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ ከዚህ ቀደም ጥር 2 ቀን 2011 ዓ.ም. በዚህ ጉዳይ ላይ ያቀረብኩትን በጋዜጣው ፈቃድ ጋብዣለሁ፡፡

ይህን በመሰለ አስቸጋሪ ጊዜ ውስጥ የብዙ ዘመን ታሪክ ያለውን፣ ዛሬ ግን ጎዶሏችን የሆነውን ያለ ብልኃትና ያለ ዕውቀት ደግሞ ዝም ብለን የቀጠልንበትን፣ የአገራችንን የ‹‹ክብር የማዕረግ›› ሥርዓት (Honour System) ጉዳይ እንመልከት፡፡ ስመ ጥሩው ባላምባራስ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል እስከ 1928 ዓ.ም. ድረስ ያሉትን የመንግሥት ሰነዶች አደራጅተውና አብራርተው ባቀረቡበት ‹‹ዝክረ ነገር›› መጽሐፋቸው እንደሚነግሩን ወግ ማዕረግ ያለው የክብር ምሥጋና መስጠት፣ ይህንንም በሽልማት፣ በማዕረግ፣ በኒሻንና በሜዳልያ መግለጽ ረዥም ታሪክ ያለው አሠራር ነው፡፡

በተለይም፣ ‹‹የኢትዮጵያ… መንግሥት በዓለም ላይ ያሉ የሠለጠኑ መንግሥታት እንደሚያደርጉት ሁሉ…›› በታማኝነትና በቅንነት ብዙ ዘመን ላገለገሉ፣ በጦር ሜዳ ላይ በሚያኮራ ሁኔታ ለተዋጉ፣ ጥበብ በማውጣት ድርሰት በመድረስ ለአገራቸው ዕድገትና ክብር ለደከሙ፣ ወዘተ የሚሰጡ ሜዳሊያዎችን ማዘጋጀት ከመንግሥት ሥራዎች ውስጥ አንዱ ሆኖ ኖራል፡፡ የእነዚህንም ኒሻኖችና ሜዳልያዎች ዝርዝር ‹‹ሙሉ ሀተታና የአሸላለሙን ዝርዝር ደንብ›› ይዘታቸውንና መልካቸውን ይነግሩናል፡፡

ከጣሊያን ወረራ በኋላም ይህ አሠራርና ሥርዓት ተጠናክሮ ቀጥሎ፣ በዘመናዊ የሕግ አወጣጥ ሥርዓት ታግዞ የኢትዮጵያ ሕግ አካል ሆኖ በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከአገር ውጭም ጭምር የሚታወቅ ‹‹Honour System›› ሆኖ ኖሯል፡፡ በዚህም መሠረት አገራችን የማይናቅ ረዥም ዝርዝር ያላቸው የማዕረግ ደረጃም የወጣላቸው ሜዳልያዎችና ኒሻኖች ነበራት፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ የጦር ሜዳይ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጦር ሜዳይ፣ የዳግማዊ ምኒልክ የውትደርና አገልግሎት ሜዳይ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የብሔራዊ አገልግሎት ሜዳይ፣ የውስጥ አርበኞችና የስደተኞች ሜዳይ፣ የድል ኮከብ ሜዳይ፣ የመምህራን ሜዳይና የኮሪያ ጦርነት ሜዳይ የሚባሉ ነበሩ፡፡ 

የኒሻኖች ደንብ ደግሞ በየጊዜውና በየዘመኑ የተቋቋሙትንና የተወሰነላቸውን ደንብ በማሻሻልና በማጠቃለል የማኅተመ ሰሎሞን ማዕረግ፣ የንግሥተ ሳባ ማዕረግ፣ የሥላሴ ኒሻን ማዕረግ፣ የዳግማዊ ምኒልክ ኒሻን ማዕረግ፣ የኢትዮጵያ የክብር ኮከብ ኒሻን ማዕረግ የሚባሉ እያንዳንዳቸው
አምስት፣ አምስት ደረጃ ያላቸው የኒሻን ዓይነቶችን አቋቁሟል፡፡

ዝርዝሩን በተለይም አሁን ላይ ሆኖ ለሚያየው በጣም ይደንቃል፣ ይገርማል፡፡ መንግሥትና ሕግ በእንዲህ ያለ ጉዳይ እንዲህ ‹‹ሥራ ይፈታሉ?›› ጉልበትና ገንዘብ ያባክናሉ? ያሰኛል፡፡ ለምሳሌ የማኅተመ ሰሎሞን ማዕረግ የሚባለው ኒሻን የመጀመርያው ዓይነት ባዝግና (ኮለር) በተለይ ለማን እንደተወሰነ (ለንጉሠ ነገሥቱና ለእቴጌዪቱ የተመደበ መሆኑን)፣ ንጉሠ ነገሥቱ በልዩ አስተያየታቸው ለንጉሣዊ ቤተ ዘመዳቸውና ለውጭ አገር ነገሥታት፣ እንዲሁም ደግሞ እጅግ ከፍ ያለ አገልግሎት ላላቸው ሰዎች የሚሰጥ እግጅ በጣም የከበረ ሽልማት መሆኑ ተደንግጓል፡፡ የእያንዳንዱ ምሥልና ቅርፅ ከተጓዳኝ ዝርዝሮች ጋር በሕግ ተወስኗል፡፡ የእያንዳንዱ የኒሻን ዓይነትና ማዕረግ በተለይም የማኅተመ ሰሎሞን፣ የንግሥተ ሳባ ማዕረግ ኒሻኖች ተሸላሚዎች ቁጥር ከተወሰነ ቁጥር እንዳይበልጥ በሕግ ተደንግጓል፡፡ ከሦስት፣ ከአሥር፣ ከ20 … ፣ ከ45፣ ከ55 አይበልጥም ተብሎ በሕግ ተከልክሏል (በነገራችን ላይ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታኅሳስ 2 ቀን 1940 ዓ.ም. ለፊልድ ማርሻል ሞንትጎመሪ የሸለሟቸው ታላቁን የሰሎሞን ኒሻንን ነው)፡፡

ይህ የክብርና የማዕረግ የሽልማት ሥርዓት በመላው የንጉሠ ነገሥቱ የሥልጣን ዘመን ዘለቀ፡፡ ከመስከረም 1967 ዓ.ም. ጀምሮ ሥልጣን የያዘው ወታደራዊ መንግሥት በ1971 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ (ስለቀድሞዎቹ ሜዳይዎችና ኒሻኖች በሕግ በግልጽ ሳይነገር) የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥትን የሜዳይና የኒሻን አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 169/71) አወጀ፡፡ በአዋጁም በሕጉ በዝርዝር በተወሰኑት ሜዳይዎችና ኒሻኖች መሠረት በጦር ሜዳ ሜዳልያዎቹ ዝርዝር ውስጥ፣ የጦር ሜዳ ሜዳልያዎችና ዓርማ የሚባሉት የኅብረተሰባዊ ኢትዮጵያ ወደር የሌለው ጀግና ሜዳይ፣ የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ፣ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሦስተኛ ደረጃና የጦር ሜዳ ቁስለኛ ሜዳይ፣ እንዲሁም የአብዮታዊ ዘማች ዓርማ የሚባሉ ተደንግገዋል፡፡ እነዚህ የሜዳይ ሽልማቶች ለማንና ምን ለፈጸመ እንደሚሰጡና ተሸላሚውም የሚያገኘው ልዩ መብት በዝርዝር ተወስኗል፡፡

በዚሁ ፈርጅ ውስጥ የተወሰኑ የሥራና የአገልግሎት ሜዳልያዎችም አሉ፡፡ የኅብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ የሥራ ጀግና ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የከፍተኛ ውትድርና አገልግሎት ሜዳይ፣ የብሔራዊ አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የውትድርና አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የፖሊስነት አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ እንዲሁም የአገልግሎት ዘመን ሪባን የሚባሉ አሉ፡፡ ሕጉ የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ታላቅ የክብር ኮከብ ኒሻን፣ የየካቲት 1966 አብዮት ኒሻን (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የቀይ ባህር ኒሻን (ባለሦስት ደረጃዎች)፣ የጥቁር ዓባይ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ)፣ የአፍሪካ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ) የሚባሉ የኒሻን ዓይነቶችንም መሥርቷል፡፡ እነዚህ ሁሉ ለማን እንደሚሰጡ፣ የሚያገኘው ሰው የሚኖረው ልዩ መብት፣ የሜዳሊያዎቹና የኒሻኖቹ ቅርፅ፣ መጠንና አካል ምንነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ኮሚሽንም ተቋቁሟል፡፡ ከርዕሰ ብሔሩ ፈቃድ ሳያገኝ ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ሜዳይ ወይም ኒሻን መቀበል የተከለከለ መሆኑም ተደንግጓል፡፡ ይህም የአገር ሕግ ሆኖ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ ዘለቀ፡፡ ደርግ ወደቀ፡፡ ኢሕአዴግ መጣ፡፡

በኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን በወታደራዊው ዘርፍ እንኳን የሜዳይ፣ የኒሻንና የሽልማት ጉዳይ የመከላከያ ሠራዊት የ1987 ዓ.ም. አዋጅ ውስጥ የተካተተው በ1990 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ በአዋጅ ቁጥር 123/1990 (የመከላከያ ሠራዊት ማሻሻያ አዋጅ) ነው፡፡ በዚህ ሕግ የዓድዋ ድል ሜዳይ የሚባል ወደር የሌለው ጀግንነት በዓውደ ውጊያ ለፈጸመ ኢትየጵያዊ ግለሰብ ወይም የሠራዊት አሃድ ወይም ቡድን የሚሰጥ የመጨረሻ ከፍተኛ የጀግና ሽልማት ሆኖ የተቋቋመውን ጨምሮ የተለያዩ የሜዳሊያዎች፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ሽልማቶች ተመሠረቱ፡፡

ፖሊስን የሚመለከት የሜዳይ፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ነገር በቀዳማዊ ሕግ ደረጃ (ፓርላማ በሚያወጣው ሕግ) የተነሳው ገና አሁን በቅርቡ በ2004 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 720 ነው፡፡ እሱም ለፖሊስ አባላት የሚሰጡ ሜዳዮች፣ ሪባኖችና የምስክር ወረቀቶች በፌዴራል ፖሊስ መተዳደሪያ ደንብ ይወሰናል ሲል ወሰነ፡፡ በዚህም መሠረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 268/2005 የጀግንነት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የላቀ ሥራ ውጤት ሜዳይ፣ የፖሊስ አገልግሎት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ) እና የፖሊስ አገልግሎት ሪባን የሚባሉ የሽልማት ዓይነቶችን አቋቋመ፡፡

አገር ባለውለታነቷን ከምታረጋግጥበት፣ ውለታዎችን ከምትስታውስበትና ለወደፊትም እንዲበረታቱ ከምታደርግበት መንገዶች አንዱ ይህ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ሥርዓት የአገሪቱን ያህል ረዥም ዘመን ያለው ቢሆንም፣ ተከታታይ መንግሥታት እየወረሱ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ባህልና የአገር ሀብት አልሆነም፡፡ ይህ ሳያንስ የተከታታይ መንግሥታት ይህንን የመንግሥት ታላቅ ሥራ የሚከናወንበትን የሕግና የተቋም ጎዶሎ፣ ቶሎና ወዲያውኑ መሙላት አለመቻላቸው፣ በተለይም በዚህ የኢሕአዴግ መንግሥት ዘመን እንደተመሰከረው አወቅነውም፣ አላወቅነውም ብሔራዊ/የአገር ማፈሪያ እየሆነ ነው፡፡ እስካሁን እንደተመለከትነው በኢሕአዴግ/በኢፌዴሪ መንግሥት የመከላከያው ጎን (የፖሊስን ጨምሮ) የሜዳይና የኒሻን ሽልማት እንኳን የተሟላው ከረዥም ጊዜ ግዴለሽነትና ቸልተኝነት በኋላ ነው፡፡ አገር ባለውለታዊነቷን የምትገልጽበትና የምታረጋገጥበት የሲቪል የመንግሥት ሽልማት ሥርዓት ግን ዛሬም ያልተሟላ ጎዶሏችን ነው፡፡

የሚሰማ ስለሌለ፣ ደንገጥ የሚልና የሚደንቀው ሰው ስለጠፋ እንጂ፣ ጉዳዩ በተለይም ጎልቶ የተነሳው የኢትዮጵያ ሚሊኒየም በተከበረበት ወቅት ‹‹ለማይመለስ ውለታህ …›› (የተሟላ ትክክለኛ መጠሪያው ምን እንደተባለ እርግጠኛ አይደለሁም) የሚል ዓይነት አስቀድሞ በሕግ ያልተቋቋመ ሜዳሊያ ስንሰጥ/ሰጠን ስንል ነው፡፡

ከዚያ በፊትና ከዚህ ወዲህም ባለሥልጣኑና ሥልጣን አለኝ የሚለው ሁሉ እየተነሳ ‹‹የከተማውን ቁልፍ››፣ ‹‹የክብር ዜግነት›› ሲሰጥ ዓይተናል፡፡ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥና አጠራርም ጭምር በጣም ግራ የተጋባና መሳቂያ ሆኖ አርፎታል፡፡ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸውን እነዚህን ቁምነገሮች የሚገዙ ሥርዓትና አሠራር መዘርጋት፣ ለመንግሥትና ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለምን የቸገረ ነገር ይሆናል፡፡

ያኔ ፕሬዚዳንት ኦባማ በአቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአስተዳደር ዘመን ኢትዮጵያን ሲጎበኙ በአጋጣሚው ‹‹ማሳሰቢያ›› ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ ኢትዮጵያ ለዜጋም ሆነ ለውጭ ሰው የምትሰጠው የሲቪል ሜዳሊያ ወይም ኒሻን ወይም ሌላ በሕግ የተቋቋመ ሽልማት የሌላት መሆኑን ነበር፡፡ ያ ከሆነ በኋላ ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ለአቶ ኃይለ ማርያምና ለባለቤታቸው ‹‹ሜዳሊያ›› እና ‹‹የአገሪቱ ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጡ ዓይተናል፡፡ ከዚያም በኋላ አሁን ለዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ለተሰናባቹ የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት (ለባለቤታቸውም) ‹‹ኒሻን›› እና ‹‹ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጣቸው መስክረናል፡፡

ሽልማቱ በተሰጠበት የሥር ምክንያት ላይ ተቃውሞም ሆነ
ወንጀል መሆኑ በሕግ ቢደነገግም በትዳር አጋሮች  የሚፈጸሙ መሰል የአስገድዶ መድፈር ወንጀሎችን ሕጉ የማይተገብር መሆኑን፣ ፆታ ተኮር ጥቃቶች የማይታዩ መሆናቸውን፣ የጠለፋ ትዳር ሕገወጥ ቢሆንም አሁን በበርካታ የአገሪቱ አካባቢዎች ችግሩ መቀጠሉ በሪፖርቱ የተዳሰሱ ጉዳዮች ናቸው፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ይኖራሉ የሚባሉ ከ10,000 በላይ አይሁዳውያን (ቤተ እስራኤላውያን) በመንግሥት ጥበቃ የሚደረግላቸው ቢሆንም፣ በማኅበረሰቡ መገለል እንደሚደርስባቸው ተገልጿል፡፡ በተመሳሳይ በገጠሩ የአገሪቱ አካባቢ ተመሳሳይ መገለልና እንደ ልዩ ፍጥረት አድርጎ የማየት፣ እንዲሁም በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ችግር እንደሚፈጠርባቸው በሪፖርቱ ተካቷል፡፡

The post መጠነ ሰፊ የመብት ጥሰቶችን ይፋ ያደረገው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዓመታዊ ሪፖርት first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ሲሳይ ሳህሉ
የሐሳብ ኮሪደር!
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

የሐሳብ ኮሪደር!

ሰላም! ሰላም! ውድ ወገኖቼ ሳምንት አልፎ ሳምንት እየተተካ ስንገናኝ ደስታዬ ወደር የለውም፡፡ እኔ ደላላው አንበርብር ምንተስኖት ለአገሬና ለወገኖቼ ብቻ ሳይሆን፣ በመላው ዓለም የሚኖሩ ሰብዓዊ ፍጡራን ጭምር ሰላም እንዲሆኑ እመኛለሁ፡፡ እናንተም እንደ እኔ ይህ ምኞት እንደሚኖራችሁ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ‹‹ሰላም… ሰላም… በዓለም ዙሪያ ሁሉ ለሰው ልጅ በሙሉ…›› እንዳለው የወርቃማው ዘመን ድምፃዊ መሐሙድ አህመድ፣ እኛም ለሰላም አበክረን ብንተባበር መልካም ነው እላለሁ፡፡ ምሁሩ የባሻዬ ልጅ፣ ‹‹እኛ የሰው ልጆች ከፈጣሪ በተሰጠን ፀጋ መጠቀም ብንችል እኮ እንኳንስ እርስ በርሳችን፣ በጣም አስፈሪ የሚባሉ የዱር አውሬዎችን አላምደን በሰላምና በፍቅር መኖር እንደሚቻል የናሽናል ጆግራፊን ዶክመንትሪ ማየት በቂ ነው…›› የሚለው ሲታሰበኝ አዛውንቱ አባቱ የነገሩኝ ታሪክ አይረሳኝም፡፡ አዛውንቱ ባሻዬ ከረጅሙ ዕድሜያቸውና ከሰፊው ልምዳቸው በመነሳት በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች የሚነግሩኝ ታሪኮች፣ ምሳሌዎች፣ አባባሎች፣ ተረቶችና ወጎች ለእኔ እንደ ዩኒቨርሲቲ ዕውቀት ጠቅመውኛል ብላችሁ ያጋነንኩ እንዳይመስላችሁ፡፡ በእሳቸውና በልጃቸው ድጋፍ ባይሆን ኖሮ እኔ አንድ ተራ ደላላ ከእናንተ ጋር በየሳምንቱ ሐሳብ ለመለዋወጥ አልገናኝም ነበር፡፡ በጭራሽ አይሞከርም!

አዛውንቱ ባሻዬ የሰው ልጅ እንኳንስ እርስ በርሱ ጥቅጥቅ ያለ ደን ውስጥ ከሚኖሩ አስፈሪ አውሬዎች ጋር መላመድ እንዴት እንደሚችል፣ በአንድ ወቅት የነገሩኝን ላካፍላችሁ እስቲ፡፡ ‹‹ልጅ አንበርብር አሁን የምነግርህ ነገር አዲስ አይደለም፣ ምናልባት በአለፍ ገደም ሰምተኸው ሊሆን ይችላል፡፡ በአንድ ወቅት አንዲት ሴት ከባሏ ጋር የነበራት የደራ ፍቅር ቀዝቅዞባት ትበሳጫለች፡፡ መፍትሔ ፍለጋ ዘመድ፣ ወዳጅና ጎረቤት ስታማክር ጠብ የሚል ነገር አጣች፡፡ አንድ ችግሯ ያሳሰባቸው እናት እስቲ እዚያ ማዶ ያሉ አዋቂ መፍትሔ አያጡምና አማክሪያቸው ብለው ይነግሯታል…›› ብለው ባሻዬ ንግግራቸውን ገታ አድርገው በሐሳብ ጭልጥ አሉ፡፡ እኔ ደግሞ ወጋቸው በመቌረጡ ደስተኛ ስላልነበርኩ፣ ‹‹ባሻዬ ይቀጥሉ እንጂ ምን ነካዎት…›› ስላቸው፣ ‹‹አይ ልጅ አንበርብር በዚህ ዘመን እኛም እኮ እስኪ መፍትሔ እንዲሆናችሁ እንዲህ አድርጉ የሚል መካሪ ብናገኝ ኖሮ፣ አገራችን እንዲህ መላ ቅጧ ይጠፋ ነበር ወይ…›› ብለው ሲመልሱልኝ እኔም ክፍት አለኝ፡፡ እውነት ነው ጎበዝ እንዲህ የመሰለ ሐሳብ የለም እኮ፡፡ ሕመሙ በዛብን!

ባሻዬ ከሰጠሙበት ትካዜ ውስጥ ወጥተው፣ ‹‹…ያቺ የከፋት ምስኪን ሴት ከመንደሯ ማዶ ያለው አካባቢ ያሉ አዋቂ ዘንድ ደርሳ የደረሰባትን ችግር ተናገረች፡፡ በጣም የሚወዳት ባሏ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አመሉ እየተለወጠ መሆኑን፣ በፍፁም የማታወቀው እስኪመስላት ድረስ መቸገሯን ነገረቻቸው፡፡ አዋቂው በይ እንግዲህ መፍትሔ የምትፈልጊ ከሆነ ዱር ሄደሽ ከአንበሳ ጋማ ላይ ሦስት የፀጉር ዘለላዎችን ይዘዥ ነይ ሲሏት፣ ሴትየዋ ደንግጣ እንዴት አድርጌ ስትላቸው፣ መፍትሔ ለመፈለግ ማድረግ የሚቻለው ይኸው ብቻ ነው ብለው አሰናበቷት…›› ብለው ሲስቁ እኔ ግን እንደ ሴትየዋ ደነገጥኩ፡፡ ከአንበሳ ጋማ ላይ ሦስት ዘለላ ፀጉሮች ምን ዓይነት ጀግና ነው በመቀስ መቁረጥ የሚችለው ብዬም ተጨነቅኩ፡፡ ‹‹አንበርብር የቸገረው መላ አያጣም እንደሚባለው፣ ሴትየዋ አውጥታና አውርዳ ካሰበችበት በኋላ ወስና ለወሳኙ ተግባር ራሷን አዘጋጀች…›› ሲሉ በፍርኃት ልቤ ፍስስ አለችብኝ፡፡ እንዴት ነው አንዲት ግራ የገባት ምስኪን ሴት የደኑ ንጉሥ ዘንድ ሄዳ ከጋማው ላይ የፀጉር ዘለላዎች የምትወስደው የሚለው ግራ አጋባኝ፡፡ ጎበዝ በተፈጥሮዬ ደፋርና ጀግና የምወድ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ብሆንም፣ አጉል ጀብደኝነት ለእኔ ሐሳብ አይመችም፡፡ ወድጄ አይደለም!

አዛውንቱ ባሻዬ ግን ወጋቸውን ቀጥለዋል፡፡ ‹‹ቆራጧ ሴት ያሰበችውን ዓላማ ለማሳካት አዋቂው በነገሯት መሠረት መሰናዶዋን ጀመረች፡፡ ይህች ብልህ ሴት ከአንበሳ ጋማ ላይ ዘለላ ፀጉር አምጪ ተባለች እንጂ፣ ዘዴው እንዴት እንደሆነ ስላልተነገራት በራሷ መንገድ ዝግጅት ማድረጓ አስደናቂ ነበር፡፡ በመጀመሪያ አያ አንበሳ የሚገኝበትን የደን ክፍል አውቃ ከዚያ ከእንቅልፉ የሚነቃበትን ጊዜ አረጋገጠች፡፡ ከእንቅልፉ ሲነሳ ለቁርሱ የሚሆነውን በቀጥታ ገበያ ሄዳ አንድ ሙክት በግ ገዛች፡፡ በጉን አሳርዳ በብልት በብልት ከመደበች በኋላ በመጀመሪያ ቀን አንድ የፊት እግር ይዛ ወደ ደኑ ንጉሥ ገሰገሰች፡፡ ከእንቅልፉ ሊነቃ ሲገላበጥ ራቅ ብላ የበጉን እግር ወርውራለት ሄደች፡፡ በነጋታው ስትመጣ አንበሳ እየተገላበጠ ሳለ ትንሽ ጠጋ ብላ ሁለተኛውን የፊት እግር አስቀመጠችለት፡፡ በሚቀጥለው ቀን እስኪነቃ ጠብቃ ሲነሳ አንዱን የኋላ እግር በጣም ጠጋ ብላ ልትሰጠው ስትቃረብ ጭራውን እየቆላ ጠበቃት፡፡ እሷም በጣም ተጠግታው የሚበላውን ስትሰጠው፣ እየተሻሻት መብላት ሲጀምር ደስታዋ ወደር አልነበረውም…›› ብለው ሲስቁ እኔም በሐሳቤ አጀብኳቸው፡፡ ውይ ደስ ሲል!

እሳቸው በተመስጦ ውስጥ ሆነው፣ ‹‹በአራተኛው ቀን የቀረውን እግር ይዛለት ስትሄድ፣ አንበሳው ቀድሞ ነቅቶ በደስታ መሬት ላይ እየተንከባለለ ሲጠብቃት ከትናንቱ የባሰ ቀረበችው፡፡ እሱም እናቱ ከገበያ የመጣችለት ሕፃን ልጅ ይመስል እየቦረቀ እግሯ ሥር ሲንከባለል ያስደንቅ ነበር፡፡ ከዚያም የመጨረሻውን የበግ እግር ሰጥታው በደስታ መመገብ ሲጀምር ከጋማው ላይ የተወሰኑ ዘለላዎችን ቆርጣ ተሰናብታው ሄደች፡፡ በመሃረቧ ጥቅልል አድርጋ የያዘቻቸውን የአንበሳ ጋማ የፀጉር ዘለላዎች ይዛ ወደ አዋቂው ቤት በደስታ እየከነፈች ደረሰች…›› ብለው አሁንም ወጋቸውን ቆም ሲያደርጉ እኔም አዋቂው ምን መፍትሔ ይሰጧት ይሆን ብዬ፣ ‹‹ከዚያስ ባሻዬ…›› ከማለቴ፣ ‹‹አዋቂው ለመሆኑ እንዴት ነው አንበሳው ዘንድ የደረሽውና ከጋማው ላይ የፀጉር ዘለላዎችን የቆረጥሽው ብለው ሲጠይቌት፣ አጠቃላይ ዝግጅቷንና ክንውኗን ዘርዝራ ስታስረዳቸው መፍትሔ ለማግኘት ያደረገችውን ደፋር ጥረት በእጅጉ አመሠገኑ፡፡ ከዚያም መፍትሔ ለማግኘት በዚህ ደረጃ ማንም ሊያስብ የማይችለውን አድርገሽ፣ ከአስፈሪው የደኑ ንጉሥ አንበሳ ጋማ ላይ በጥበብ ዘለላ ፀጉሮች ማምጣት ከቻልሽ፣ ለዓመታት አብረሽ የኖርሽውን ባልሽን በቀላሉ የአንቺ ማድረግ አያቅትሽምና መልሱ እጅሽ ላይ ነው ብለው አሰናበቷት…›› ሲሉኝ የአዋቂው ድንቅ ሐሳብ በእጅጉ አስገረመኝ፡፡ ግሩም ድንቅ ነው!

ወገኖቼ ያው እንደምታውቁት ይህንን ወግ አስታውሼ ያመጣሁት ወግ ለመጠረቅ አይደለም፡፡ በኩዳዴ ፆም ሱባዔ ላይ ያሉት አዛውንቱ ባሻዬ ያኔ ይህንን ከላይ የነገርኳችሁን ወግ ያኔ ሲነግሩኝ፣ ‹‹ልጅ አንበርብር እየለገምን እንጂ ሰላማችንም ሆነ ተስፋችን ያለው እጃችን ላይ ነው፡፡ ፈጣሪ በሚወደው መንገድ ተከባብረን፣ ተፈቃቅረንና ተረዳድተን ለአገራችን በአንድነት መቆም ብንችል እንኳንስ ደም ልንፋሰስ ለኩርፊያ የሚበቃ ቅራኔ የለንም…›› ብለውኝ ነበር፡፡ ምሁሩ ልጃቸው ደግሞ፣
‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት በሕገወጥ መንገድና በሐሰተኛ ሰነድ አገር ውስጥ የሚገኙ የውጭ አገር ዜጎችን በፍርድ ቤት በመክሰስ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ሲሞከር፣ በዋስ እየተለቀቁ መቸገሩን አስታወቀ፡፡

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ሚያዝያ 18 ቀን 2016 ዓ.ም. የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርቱን ባቀረበበት ወቅት የመኖሪያ ፈቃድ የጨረሱ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ሕጋዊ ዕርምጃ ከመውሰድ አንፃር ምን እየተሠራ እንደሆነ ከሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጥያቄ ቀርቦለታል፡፡ 

ቋሚ ኮሚቴው የውጭ አገር ዜጎች ፈቃድ በተፈቀደላቸው የመኖሪያ የጊዜ ገደብ ብቻ እንዲቆዩ ከማድረግ አንፃር አፈጻጸሙ 36 በመቶ ብቻ መሆኑን በሪፖርቱ እንደተመለከተ በመግለጽ፣ በተቀመጠላቸው ጊዜ ማከናውን ለምን እንዳልተቻለ ጠይቋል፡፡

ተቋሙን እየመሩ ያሉት አመራሮች ወደ ኃላፊነት ሲመጡ ባደረጉት የዳሰሳ ጥናት፣ ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎች ሐሰተኛ የመኖሪያ ፈቃድ እያዘጋጁ ሲጠቀሙና ሲሸጡ ቆይተዋል ሲሉ የተቋሙ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጎሳ ደምሴ ገልጸዋል፡፡

‹‹ይህ ሕገወጥ አሠራር ተለምዶ በመቆየቱ ዕርምጃ መወሰድ ሲጀመር በሁሉም አካላት እንደ አዲስና በመጥፎ ታይቷል፤›› ብለዋል፡፡ ተቋሙ ከ18 ሺሕ በላይ የሚሆኑ የውጭ አገር ዜጎችን በፍርድ ቤት ከሶ ዕርምጃ እንዲወሰድባቸው ለማድረግ ሲሞከርም፣ ‹‹አካልን ነፃ ማውጣት›› በሚል በዋስ እንዲለቀቁ እየተደረገ መቸገሩን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡ በዚህም በቀን የሚከፍሉትን ውዝፍ ገንዘብና ላጠፉት ጥፋት አስተዳደራዊ ቅጣት እየተቀጡ እንዲመለሱ ተደርጓል በማለት ገልጸዋል፡፡ 

በዚህ ወንጀል የተሳተፋ ዜጎችን የመለየት ሥራ የተከናወነውም ከደኅንነትና ከፀጥታ ተቋማት በተውጣጡ ጥምር የኮሚቴ አባላት መሆኑ ተመላክቷል፡፡ 

ተቋሙ ከዚህ በፊት ተጠሪነቱ ለሰላም ሚኒስቴር መሆኑ ቀርቶ ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የሆነ ራሱን የቻለ አደረጃት እንዲኖረው የሕግ ማሻሻያ ሥራዎች እየተሠሩ መሆናቸውንና ለሚኒስትሮች ምክር ቤት መቅረቡን፣ የሚሻሻለው ሕግ ሲፀድቅም አሁን ለሚነሱት ችግሮች መፍትሔ እንደሚያገኙ ጠቁመዋል፡፡  

ከዚህ ባለፈም ‹‹የአገሪቱ የቁጥጥር ሥርዓት ደካማ እንደሆነ ስለሚያውቁ›› በኢንቨስትመንት ስም ወደ አገር የገቡ በርካታ የውጭ አገር ዜጎች አምስት ዓመትና ከዛ በላይ በሕገወጥ ሥራዎች ላይ ተሰማርተው መገኘታቸውንም ገልጸዋል፡፡  

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግና ፍትሕ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በበኩሉ ባከናወነው የመስክ ምልከታ የአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ለእንግልት የሚዳርጉ አሠራሮችን መመልከቱን ገልጾ ማሻሻያ እንዲደረግበትና የሠራተኞች አያያዝ፣ ምቹ የሥራ ቦታን መፍጠር ላይ ትኩረት ተደርጎ እንዲሠራ አሳስቧል፡፡

The post ‹‹በሐሰተኛ ሰነድ በሚኖሩና በሚሸጡ የውጭ አገር ዜጎች ላይ ዕርምጃ መውሰድ አልቻልኩም›› የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ፅዮን ታደሰ
ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን

በአሮን ሰይፉ

የሰው ዘር መገኛ የሆነችውና የቀደምት ሥልጣኔዎች ባለቤት የሆነችው አፍሪካ በተለያዩ የታሪክ ዑደቶች ውስጥ ያለፈች አኅጉር ናት፡፡ በረዥሙ የአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ታላላቅ ሥልጣኔዎችን፣ የንግድ ልውውጦችን፣ የትምህርትና የባህል በረከቶቿ እንደሚነሳው ሁሉ በአሥር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ወጣት አፍሪካውያንን ለባርነት አትላንቲክ ውቅያኖስን አቋርጠው ወደ አውሮፓና አሜሪካ መጫናቸው፣ እንዲሁም በአውሮፓውያን ቅኝ ግዛት ሥር የመውደቅ ጨለማ ጊዜያትንም አሳልፋለች፡፡

እ.ኤ.አ. በ1884/85 በታሪክ የአፍሪካ ቅርምት ተብሎ በሚታወቀው የበርሊን ጉባዔ አውሮፓውያን አፍሪካን በቅኝ ለመያዝ ተከፋፈሉ፣ ኢትዮጵያ ዓድዋ ላይ ወራሪውን ጣልያንን ድል ነስታ፣ እንዲሁም ላይቤሪያ ከአሜሪካ ወደ አፍሪካ በተመለሱ ጥቁሮች የተመሠረተች አገር በመሆኗ ሁለቱ ብቻ ሲቀሩ መላ አፍሪካን አንድ በአንድ በቅኝ ግዛት መዳፋቸው ውስጥ አስገቡ፡፡ ይህ ወቅት አፍሪካ የራሷን ሥልጣኔና ነፃነት ያጣችበትና የአውሮፓውያን የጉልበትና የጥሬ ዕቃ ማግኛ ሥፍራ ብቻ እንድትሆን አድርጓል፡፡ የአፍሪካ ከራሷ ሐዲድ በመውጣት ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ጉዳዮቿ የአውሮፓውያኑን ጥቅም በማማከል ይወሰን ስለነበር አፍሪካ በችግር አዙሪት ውስጥ እንድትዳክር አድርጓል፡፡

አፍሪካን ከቅኝ አገዛዝ ነፃ ለማውጣት መላ አፍሪካውያን እልህ አስጨራሽ ትግል አድርገዋል፡፡ ሚሊዮኖችም ለዚህ ቅዱስ ዓላማ ሕይወታቸውን ሰውተዋል፡፡ ከጋና እስከ ሱዳን፣ ከአልጄሪያ እስከ ናሚቢያ፣ ከኮንጎ እስከ ሞዛምቢክ  በአራቱም የአፍሪካ ማዕዘናት የተስፋፋው የነፃነት ትግል በጊዜ ሒደት ፍሬ እያፈራ በተለይ በ1950ዎቹና 60ዎቹ በርካታ የአፍሪካ አገሮች ነፃነታቸውን መቀዳጀት ችለዋል፡፡

አፍሪካውያን ነፃነታቸውን ማግኘት ሲጀምሩ የተፈጠረው መላ አፍሪካን ነፃ የማውጣት ተስፋና ጉጉት፣ ነፃዎቹ የአፍሪካ አገሮች እየተሰባሰቡ እንዲመክሩ አስችሏል፡፡ ይሁን እንጂ የአፍሪካውያን መሰባሰብ አንድ ወጥ መሆን አልቻለም፡፡ የካዛብላንካ ቡድን በመባል የሚታወቀው አንደኛው ቡድን አፍሪካ አንድ አገር መሆን ይገባታል የሚል አቋም የነበረው ሲሆን፣ ሁለተኛውና የሞኖሮቪያ ቡድን የሚባለው የአፍሪካ አንድ አገርነት በሒደት የሚመጣ ሆኖ ነፃ አገሮቹ ለጋራ ዓላማ በጋራ መቆምን የሚጠይቅ ነበር፡፡ የሁለቱ ቡድኖች አለመግባባት በቅኝ ግዛት ሥር እየማቀቁ ላሉ አፍሪካውያን ጥሩ ዜና አልነበረም፡፡

እ.ኤ.አ. በሜይ 1963 ይህ የአፍሪካ በሁለት ጎራ መሠለፍን ሊያስቀርና አፍሪካን በአንድ ድምፅ እንድትናገርና በአንድነት ለመቆም ማስቻልን ዓላማ ያደረገ ጉባዔ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በአዲስ አበባ ተካሄደ፡፡ የአፍሪካ ብሥራትም ተበሰረ፡፡ በሁለት ቡድኖች የተከፋፈሉት ነፃዎቹ የአፍሪካ አገሮች በአንድነት በመቆም ከቅኝ አገዛዝ መውጣት ያልቻሉትን አፍሪካውያን ነፃ ለማውጣት እ.ኤ.አ. ሜይ 25 ቀን 1963 የአፍሪካ አንድነት ድርጅትን ይፋ አደረጉ፡፡ ይህች ታላቅ ቀን ‹‹የአፍሪካ ቀን›› በመባል በአፍሪካና በመላው ዓለም ለመታወቅ በቃች፡፡ ለዚህች ታሪካዊ ቀን ዕውን መሆን የኢትዮጵያ ሚና በእጅጉ የላቀ እንደነበር ዘለዓለም የሚዘከር ሆኖ፣ በወቅቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩትና ለአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምሥረታ ታላቅ አስተዋጽኦ ያበረከቱት አቶ ከተማ ይፍሩ እ.ኤ.አ. በ1991 ለአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ላይ በሰጡት ቃለ ምልልስ፣ ‹‹አንድ ነገር ኢትዮጵያ ለአፍሪካ አደረገች ብንል አንዱና ዋናው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት መቋቋም ነው፤›› በማለት ገልጸውታል፡፡  

የአፍሪካ ቀን በአፍሪካና በመላው ዓለም ያለው አከባበር

የአፍሪካ ቀን በአፍሪካ ታሪክ ውስጥ ታላቁ ቀን ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ ከቅኝ ግዛት ቀንበር መላቀቅ ያቃታቸው አፍሪካውያን ባሉበት የተስፋ ዜናን የሰሙበት፣ የነፃነትን አየር የሚተነፍሱ አፍሪካውያንም በአንድነት ለአንድ ዓላማ መሠለፍን ያስቻለ ታላቅ ቀን ነው፡፡ አንድነቱም ተስፋ ብቻ ሆኖ አልቀረም፡፡ የነፃነት ትግሉን በማፋፋም መላ አፍሪካ ነፃ እንዲወጣ የዲፕሎማሲና ወታደራዊ ትግሉን አስተባብሮ ለድል እንዲበቃ አድርጓል፡፡ ይህ የታሪክ እውነታ ነው የአፍሪካ ቀን በአፍሪካና ጥቁሮች በሚኖሩባቸው የዓለማችን ክፍሎች በደማቅ እንዲከበር ያደረገው፡፡

ደቡብ አፍሪካ የሜይ ወርን የአፍሪካ ወር የሚል ስያሜን የሰጠች ሲሆን፣ በወሩ ውስጥ የአፍሪካን ታሪክ፣ የነፃነት ትግልና ብሩህ ተስፋ፣ ወዘተ ይዳሰሳሉ፡፡ ይህም ሆኖ የአፍሪካ ቀን ብሔራዊ በዓል ሆኖ አልታወጀምና የአገሪቱ ዋና የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ የሆነው ጁሊየስ ማሌማ ፓርቲያቸው የአፍሪካ ቀንን ሲያከብር ለአባላቶቻቸው ባደረጉት ንግግር ይህን ብለዋል፡፡ ‹‹Africa Day is a celebration and recognition of Pan Africanism. We must not make a mistake comrades, and confuse this day to any other day. This day is a day when we celebrate our selves, this day is a day when we tell the whole world and those who care to listen that we are Africans and we are proud. …. But we must ask ourselves a question. Why is Africa Day not a public holiday in South Africa?››            

እንደ ዚምባቡዌ፣ ናሚቢያ፣ ማሊ፣ ዛምቢያ፣ ጋምቢያ፣ ሌሶቶ፣ ሞሪታኒያ ያሉ የአፍሪካ አገሮች የአፍሪካ ቀንን በብሔራዊ በዓልነት ያከብራሉ፡፡ ዋና መቀመጫውን በምሥረታ ቦታው ያደረገው የአፍሪካ ኅብረትም ሥራ ዝግ ሆኖ የሚከበር ቀን ነው፡፡ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት፣ በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች፣ እንዲሁም በተለያዩ የዓለማችን ክፍሎች በተለያዩ የፌስቲቫልና የፓናል ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

ከአፍሪካ ውጭ ያሉ አገሮች የአፍሪካ ቀንን ከአፍሪካ ጋር ያላቸውን ትስስር የሚያጠናክሩበት መድረክ አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡ በተለይ የሪፐብሊክ ኦፍ አየርላንድ የአፍሪካ ቀን አከባበር ከሌሎች አገሮችም በተሻለ የሚጠቀስ ነው፡፡ ለ2024 የአፍሪካ ቀን አከባበር በመንግሥት ድረ ገጽ ላይ ያለ ከወራት በፊት የተቀመጠው ማስታወቂያ እንዲህ ይላል፡፡

“Africa Day is returning this May – and set to be bigger and better than ever!

Events will be held in every county in Ireland to mark the day that celebrates Ireland’s growing links with the continent of Africa. Irish Aid is working with local authorities all over Ireland to plan a series of
‹‹አንበርብር መላ አገራችንን ዞረህ ብታካልል እኮ በሕዝባችን መካከል አንዳችም የሚያጣላ ነገር የለም፡፡ ይልቁንም ሕዝባችን ገበያ በለው ወይም ሌላ ሥፍራ ሲገናኝ እኮ ስለዝናብ መኖርና አለመኖር፣ ስለማኅበራዊ ክንውኖችና ሌሎች መልካም ነገሮች በፍቅር ከመጠያየቅ ውጪ አንዳችም ፀብ የለውም፡፡ ግና ምና ያደርጋል እኛ ተምረናል የምንባለው በማይረባ ከንቱ ፖለቲካችን ለአገር ልማት፣ ለሕዝብ ኑሮ ዕድገት ሳይሆን ለሥልጣንና ለጥቅም ስንል አገራችንን የደም ምድር አደረግናት፡፡ በሕዝብ ስም እየማልንና እየቆመርን አገሪቱን ሲኦል አድርገን ሕዝባችንን መከራ እናበላለን፡፡ መፍትሔ ከመፈለግ ይልቅ ግጭት መጠንሰስና መጥመቅ የዕለት ተዕለት ሥራችን ከሆነ ዓመታት እየነጎዱ ነው…›› ሲለኝ ሐሳቤ ዝብርቅርቅ እያለ እናደዳለሁ፡፡ ያበግናል!

ምንም እንኳ የድለላ ሥራ ተቀዛቅዞ ቢከርምም በአለፍ ገደም ስልኬ ስትጮህ በከፍተኛ ጉጉት ውስጥ ሆኜ ማንሳቴ አልቀረም፡፡ ብዙዎቹ ጥያቄዎች የባንክ ብድር መቼ ተለቆ የመሬትና የይዞታ ሽያጭ ቢዝነስ የሚጦፈው የሚል ነው፡፡ እንዴት ነው ነገሩ ጎበዝ፣ እኔ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሹም አይደለሁም፡፡ እንዲያውም እኮ ከባንኮች አጠቃላይ ብድር ከ23 በመቶ ወይም ከ440 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር የወሰዱ አሥር ግለሰቦች ብቻ ናቸው ከተባለ ወዲህ፣ ጭቁኑ ሕዝባችን ሀብታም የሚባል ስም አትጥሩብን ብሎ ሰላማዊ ሠልፍ እንዳይወጣ ሥጋት ይዞኛል፡፡ የባንኮቻችን ጉዳይ ተከድኖ ይብሰል ተብሎ ካልተተወ በስተቀር ብሔራዊ ባንክ በውስጥ ገመናቸው መደንገጡን እየነገረን፣ ለዘረፋ የመጋለጥ ደረጃቸው በጣም እያሳሰበው እንደሆነ በቀጥታ እያሳሰበን የብድር ጣሪያ መለቀቅና አለመለቀቅ ጉዳይ ሲነሳ ክፍት እያለኝ ነው፡፡ በቀደም አንድ የከተማው የዘመኑ ባለሀብት የሚባል ለአንድ ሥራ ፈልጎኝ ስንነጋገር፣ በንግግሩ መሀል ከአፉ አልጠፋ ያለው ይኸው የባንክ ብድር ጉዳይ ነው፡፡ እርግጥ ነው ለሚሠራ ሰው ገንዘብ ያስፈልገዋል፡፡ ገንዘቡ ግን ሥራ ላይ ሳይውል ቀርቶ ባንኮችንም ሆነ አገርን ዕዳ ውስጥ እንዳይከት ቁጥጥር የማስፈለጉ ሐሳብ ውልብ አለብኝ፡፡ የግድ ነው!

የኑሮአችን ጉዳይ ሲነሳ ደግሞ መንግሥት ሰሞኑን የደረሰበት ውሳኔ ግን አንጀቴን አርሶታል፡፡ የውጭ ባለሀብቶች በወጪና በገቢ ንግድ፣ እንዲሁም በጅምላና በችርቻሮ ሥራ እንዳይሳተፉ ተጥሎ የነበረው ገደብ መነሳቱ በበኩሌ ትልቅ ዕርምጃ ነው እላለሁ፡፡ የአገራችን አስመጪና ጅምላ ነጋዴም በሉት ቸርቻሪ በጣም ክፉ ከመሆኑ የተነሳ አዘኔታ እንደሌለው እኔ ዋናው ምስክር ነኝ፡፡ አንድ ጊዜ አንዱ ከውጭ በገፍ የምግብ ዘይት እያስገባ መክበሩን አውቃለሁ፡፡ ሰውዬው በጣም ጨካኝ ከመሆኑ የተነሳ በእኛ በምስኪኖች ላይ በአንድ ጊዜ ከውጭ ባስገባው ዘይት ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ ማትረፉን ሰምቻለሁ፡፡ እኛ ላይ ስንጥቅ ቢያተርፍ እንኳ መቶ ሚሊዮን ብር ማትረፍ ይችል ነበር፡፡ ነገር ግን የትርፍ ህዳግ ሕግ ስለሌለ ከአሥር እጥፍ በላይ እያተረፈ፣ ዛሬ አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ሰባት ያህል ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች አሉት፡፡ የአገራችን ባለሀብቶች በአግባቡ አትርፈው ቢበለፅጉ ደስ ይላል እንጂ አያስከፋም፡፡ ነገር ግን አልጠግብ ባይ ስለሆኑ አሁን ቢበቃቸው እኔ ደስተኛ ነኝ፡፡ እኛ በእነሱ መበልፀግ ሳይከፋን እነሱ ግን ሲጨክኑብን ደስ አይልም፡፡ የኑሮ ውድነቱ የሚባባሰው በእነሱ የማይጠረቃ ፍላጎት ስለሆነ የውጮቹ ገብተው ተንፈስ ሲያደርጉን ማየት ስለምፈልግ፣ መንግሥትን በዚህ ውሳኔው አመሠግነዋለሁ፡፡ መልካም ሐሳብ ይደገፋል!

ምሁሩ የባሻዬ ልጅ በተለያዩ አገሮች ሲዞር የገጠመውን ሲነግረኝ፣ ‹‹ሌላው ቀርቶ ከኬንያ ጀምሬ እስከ ደቡብ አፍሪካ በነበረኝ ጉዞ በርካታ የውጭ የጅምላና የችርቻሮ ገበያዎችን አይቻለሁ፡፡ እንደ ሾፕራይት፣ ፒክ ኤንድ ፔይ፣ ስፓር፣ ማስ ማርት፣ ውል ዎርዝስና የመሳሰሉት ትልልቅ ሱፐር ማርኬቶች በምርቶች አቅርቦትና ዋጋ ተመራጭ ናቸው፡፡ በተለይ እንደ ቅቤ፣ ወተት፣ ሥጋ፣ ዶሮ፣ እንቁላል፣ አትክልትና ፍራፍሬዎች ዋጋ ከአገራችን ጋር በአቅርቦት ብዛትና ጥራት፣ እንዲሁም በዋጋ ሲነፃፀሩ በጣም ያስገርማል፡፡ እኛ እኮ የኋላቀር ግብይት ሥርዓትና የስግብግብ ነጋዴዎች ሰለባና መጫወቻ ነን…›› የሚለኝ አይረሳኝም፡፡ ሰሞኑን ከመንግሥት ውሳኔ በኋላ ይህንን ጉዳይ ሳነሳለት፣ ‹‹አንበርብር የአገራችን ባለሀብቶች ባይንገበገቡ ኖሮ የውጮቹ ገብተው ሥራቸውን እንዲቀሟቸው አንፈልግም ነበር፡፡ እንግዲህ እነሱ በአድማ ገበያውን ተቆጣጥረውት ከብዝበዛ አንላቀቅም ካሉ፣ እኛም ነፃ አውጭ ብንፈልግ ሊፈረድብን አይገባም፡፡ ምነው ቢባል ገበያው በሥርዓት ተመርቶ እኛም እንደ ሰው መኖር ስላለብን ነው…›› ሲለኝ፣ እሱ ውስጥ ያለው እውነት ከእኔ ጋር እየተጣጠመ ነበር፡፡ የጋራ ጉዳዮቻችን እንዲህ ቢጣጣሙ እኮ የማይረቡ ሐሳቦች መጫወቻ አንሆንም ነበር፡፡ እውነቴን ነው!

በሉ እስኪ እንሰነባበት፡፡ ቀኑ አልቆ ምሽቱ ሲቃረብ ለሐሳቤም ሆነ ለውሎዬ ማሳረጊያ ወደ ሆነችው ግሮሰሪ ማምራት የግድ ነበር፡፡ ምሁሩ የባሻዬ ልጅ እዚያ እየጠበቀኝ ስለሆነ ግሮሰሪያችን ደረስኩ፡፡ የግሮሰሪያችን ነባር ደንበኞችን ሰላምታ እየሰጠሁ ምሁሩ ወዳጄ ወደ ተቀመጠበት አመራሁ፡፡ የቀረበልንን ያላበው ቢራ እየተጎነጨን የባጥ የቆጡን ስንቀበጣጥር ሳለ፣ ‹‹እኔ እኮ የማይገባኝ ዘንድሮ እዚህ አገር የሚታመን ሰው ጠፋ በቃ…›› የሚል ድምፅ ከወደ ባንኮኒ አካባቢ ተሰማን፡፡ ባንኮኒው ላይ ከቆሙ አራት ሰዎች ወግ የተረዳነው፣ በቅርቡ የአፍሪካ ኅብረት ግቢ ውስጥ ስድስት ሚሊዮን ዶላር ሊያዘዋውሩ ሲሉ ስለተያዙት ካህን ጉዳይ ነበር ወሬው፡፡ ከእነሱ ትይዩ ያለውን ጠረጴዛ ከበው ከተቀመጡ አንዱ፣ ‹‹ጣታችንን ሌሎች ላይ ስንቀስር የራሳችንንም እንከኖች ማስተዋልም ተገቢ ነው…›› እያለ ሲናገር ሰማነው፡፡ ምሁሩን የባሻዬ ልጅ በዓይኔ ጠቀስ ሳደርገው ጥያቄ መሆኑ ገብቶት፣ ‹‹ችግር እንደ ተራራ የተቆለለባት አገር ውስጥ በየቀኑ አዳዲስ አጀንዳ መፈልፈል አለመቆሙ ይደንቃል…›› እያለ ሲመልስልኝ እኔ በሐሳብ ጭልጥ እያልኩ ነበር፡፡ ቁሳዊው የልማት ኮሪደር ብቻ ሳይሆን ለችግሮቻችንም የሐሳብ ኮሪደር ሳያስፈልገን አይቀርም፡፡ መልካም ሰንበት!

The post የሐሳብ ኮሪደር! first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by በጋዜጣዉ ሪፓርተር
events.”

ኢትዮጵያና የአፍሪካ ቀን አከባበር

አገራችን ኢትዮጵያ የአፍሪካ ቀን ተብሎ ለተሰየመው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ምሥረታ ያበረከተችው አስተዋጽኦ ከየትኛውም አገር የላቀ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ለአፍሪካ ቀን ሌሎች አገሮች እንደሰጡት ክብር አልሰጠችም፡፡ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች የአፍሪካ ቀንን ብሔራዊ በዓል አድርገው ሲያከብሩ፣ የአፍሪካ ሳምንትና የአፍሪካ ወር በማለት ሰይመው አፍሪካዊ ሥራዎች ላይ የተለየ ትኩረት ሲያደርጉ በኢትዮጵያ ግን የአፍሪካ ቀን ይህ ነው የሚባል አከባበር አይደረግም፡፡ አፍሪካ ዴይ ኢኒሼቲቭ በሜይ 25 ቀን  2023 ዓ.ም. 60ኛው የአፍሪካ አንድነት ምሥረታ በዓል (የአፍሪካ ቀን) 60 ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች የተሳተፉበት የሥዕል ኤግዚቢሽን በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን በማዘጋጀት፣ እንዲሁም በፓናል ውይይት የአፍሪካ ቀንን ሲያከብር የአፍሪካ ቀን በአገራችን ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ የራሱ ሚና እንደሚኖረው ተስፋ በማድረግ ነበር፡፡ ወደ ታች ዝቅ ብዬ እንደማነሳው ከአንድ ወር በኋላ ለሚከበረው 61ኛው የአፍሪካ ቀን በዓል ዝግጅት እየያደረገ ይገኛል፡፡

የኢፌዴሪ አዋጅ ቁጥር 1209/2012

አተገባበሩን በምሉዕ አላየነውም እንጂ ሐምሌ 9 ቀን 2012 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 1209/2012 ‹‹የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማ፣ መዝሙርና የአፍሪካ ቀን አዋጅ›› የአፍሪካ ቀንን በክብር እንድናከብር ብቻ ሳይሆን እንደ አገር ሰፊ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎችን ሊያስገኝልን የሚችሉ ሥራዎችን እንድንሠራ የሚያግዘን ክፍሎች ያሉት አዋጅ ነው፡፡ የአዋጁን የተወሰነ ክፍል እንመልከት፡፡ የአዋጁ መግቢያ መርሆ እንዲህ ይላል፡፡ 

‹‹የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀጽ 86(5) ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች ጋር በየጊዜው እያደገ የሚሄድ ኢኮኖሚያዊ ኅብረትና የሕዝቦች ወንድማማችነትን ማጎልበት የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት መርሕ እንደሆነ በመደንገጉ፣ አገራችን ከአፍሪካ አገሮች ጋር ያላትን አጋርነት ለማሳደግ፣ ለፓን አፍሪካኒዝምና ለአፍሪካ የውህደት አጀንዳ ተግባራዊነት ያላትን ቁርጠኝነት ለማስቀጠል፣ እንዲሁም የኅብረቱ ኮሚሽን አስተናጋጅ አገርነት ሚናዋን ለመወጣት ከምታከናውናቸው ተግባራት በተጨማሪ የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማን ማውለብለብ፣ የአፍሪካ ኅብረት መዝሙርን ማዘመርና የአፍሪካ ቀን ታስቦ እንዲውል ማድረጉ አገራችን ለኅብረቱ ያላትን ቁርጠኝነት የሚያሳይ በመሆኑ፣ በአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ የኅብረቱ ሰንደቅ ዓላማና መዝሙር በአባል አገሮች እንዲውለበለብና እንዲዘመር፣ እንዲሁም የአፍሪካ ቀን እንዲከበር ያስተላለፈውን ውሳኔ በኢትዮጵያ ተግባራዊ ለማድረግ የሕግ ማዕቀፍ በማስፈለጉ፣ ይህን ስምምነት የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰኔ 18 ቀን 2012 ዓ.ም. ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ያፀደቀው በመሆኑ፣ በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 55(1) እና (12) መሠረት የሚከተለው ታውጇል፡፡››

የአዋጁን የኅብረቱን ሰንደቅ ዓላማ አሰቃቀልን በሚደነግገው የአዋጁ ክፍል ሁለት አንቀጽ 4/1 ላይ የትኞቹ ተቋማት የኅብረቱን ሰንደቅ ዓላማ እንደሚሰቅሉ እንዲህ ይደነግጋል፡፡

የኅብረቱን ሰንደቅ ዓላማ መውለብለብ የሚያግድ ከአቅም በላይ የሆነ ምክንያት ካላጋጠመ በስተቀር የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፣ የፌዴሬሽን ምክር ቤት፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት፣ የክልል ቢሮዎች፣ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች፣ የሌሎች አስፈጻሚ አካላት ጽሕፈት ቤቶች፣ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ በትምህርት ቤቶች፣ የአገር መከላከያ ተቋማት፣ አውሮፕላን ማረፊያዎች፣ የፖሊስና የጠረፍ ጥበቃ ተቋማት፣ የኢትዮጵያ ሚሲዮኖች፣ የአምባሳደሮች መኖሪያ ቤት ሕንፃዎች፣ እንዲሁም ከዓለም አቀፉ የባህር ላይ ሰንደቅ ዓላማ አጠቃቀም ደንቦች ጋር በተጣጣመ አኳኋን የኢትዮጵያ ንግድ መርከቦችና ጀልባዎች በየቀኑ የኅብረቱን ሰንደቅ ዓላማ ይሰቅላሉ፡፡

በአዋጁ ከተጠቀሱት ተቋማት ውስጥ የትኞቹ ተቋማት የኅብረቱን ሰንደቅ ዓላማ እየሰቀሉ እንደሆነ በእርግጠኛነት መናገር አልችልም፡፡ ይሁን እንጂ የዚህ ጽሑፍ የትኩረት አቅጣጫዬ በሆነው ትምህርት ቤቶች እየተሰቀለ እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡ ነገር ግን አዋጁ ትምህርት ቤቶችን በተለየ የአሰቃቀሉን ሥነ ሥርዓት ጭምር በግልጽ ያስቀምጣል፡፡ የኅብረቱን ሰንደቅ ዓላማ የሚሰቀልበትና የሚወርድበትን ጊዜ በሚደነግግበት አንቀጽ 5 ይህን ይላል፡፡ 5/1  በዚህ አዋጅ አንቀጽ 4/1 በተጠቀሱት መሥሪያ ቤቶች የኅብረቱ ሰንደቅ ዓላማ ከጠዋቱ በ12 ሰዓት ተሰቅሎ ከምሽቱ 12 ሰዓት ይወርዳል፡፡ 5/3 የዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀጽ 1 ቢኖርም በትምህርት ቤቶች የኅብረቱ ሰንደቅ ዓላማ የሚሰቀለው ጠዋት ተማሪዎች ተሠልፈው ትምህርት ከመጀመሩ በፊት ይሆናል፡፡ የሚወርደውም ከምሽቱ 12 ሰዓት ይሆናል፡፡

በአዋጁ በግልጽ እንደተቀመጠው የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማና መዝሙር ከኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማና መዝሙር ጋር በትምህርት ቤቶቻችን በየቀኑ እንዲዘመርና እንዲውለበለብ ተደንግጓል፡፡ ይሁን እንጂ አዋጁን የማስፈጸም ኃላፊነት ያለበት የትምህርት ሚኒስቴር  አዋጁን ሳያስፈጽም አራት የትምህርት ጅማሮ መስከረሞች አልፈዋል፡፡ ተማሪዎቻችን በየዕለቱ የአፍሪካን ሰንደቅ ዓላማን መዝሙሩን እየዘመሩ ቢሰቅሉ፣ በብሔረሰባዊ ማንነት ተቧድኖ ወደ መጨራረስ እየመራን ያለውን ፖለቲካ ሊያርቁ የሚችሉ ራሳቸውን በአፍሪካዊ ማንነት ያነፁ ወጣቶችን ለማፍራት ቀላል ያልሆነ ሚና እንደሚኖረው ዕሙን ነው፡፡

ፖለቲካችን በብሔረሰባዊ ማንነት ታጥሮ እርስ በርስ በመተጋተግ የተኮላሸ በመሆኑ፣ በአፍሪካ ውስጥ ለሚሆኑ ጉዳዮች የፖለቲካ ልሂቃኖቻችን ብዙም ጉዳይ ያላቸው አይመስሉም፡፡ አንድ ዓመት ያስቆጠረው በጎረቤታችን ሱዳን ያለው የእርስ በርስ ጦርነት፣ ኮንጎንና ሩዋንዳን ወደ ጦርነት ሊከት የሚችለው የምሥራቅ ኮንጎ ግጭት፣ ጊኒ፣ ኒጀርና ቡርኪናፋሶ ከምዕራብ አፍሪካ አገሮች ኅብረት (ኤኮዋስ) ራሳቸውን ማግለልና የጋራ ተቋም መመሥረት በአፍሪካ አንድነት ላይ ሊፈጥረው የሚችለው ጉዳት፣ የአፍሪካ ኅብረት የሪፎርም አጀንዳዎች፣ ወዘተ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ልሂቃን ዘንድ የረባ ትኩረት የላቸውም፡፡

የምሥራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ ውስጥ አገራችን ለምን አባል እንዳልሆነች፣ በፖለቲካችን ውስጥ አጀንዳ  እንዴት ሊሆን እንዳልቻለ የሚገርም ነው፡፡ የኢኮኖሚ ማኅበረሰቡ ኬንያ፣ ኡጋንዳ፣ ታንዛንያ፣ ሩዋንዳ፣ ቡሩንዲ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኮንጎና ሶማሊያን በአባልነት የያዘ ሲሆን፣ ወደ ኮንፌዴሬሽን ለማሳደግ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ፡፡ የአፍሪካ ነፃ የንግድ ቀጣናን በተሟላ ሁኔታ ለመተግበር እየተቃረብን ባለንበት በዚህ ወቅት፣ የኢትዮጵያ የንግዱ ማኅበረሰብ የጋራ የንግድ ቀጣናን በበቂ ከተለማመዱት እንደ ምሥራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ማኅበረሰብና የሌሎችም ቀጣናዊ የኢኮኖሚ ኅብረት አገሮች የንግድ ማኅበረሰብ ጋር እንዴት ሊወዳደሩ እንደሚችሉ አሳሳቢ ነው፡፡ 

በአጠቃላይ ፖለቲካችን ወደ ውስጥ ቁልቁል ያቀረቀረ በመሆኑ ከኢትዮጵያ ባሻገር ስላሉ ዕድሎችና ሥጋቶች የሚመለከት አልሆነም፡፡ የአፍሪካ ችግሮች ላይ እንደ ሌሎች አፍሪካውያን የድርሻችንን ኃላፊነት ለመወጣት የሚያስችል ቁመናና ሁኔታ ውስጥ ልንገኝ አልቻልንም፡፡ የፖለቲካችን አልፋና ኦሜጋ የኢትዮጵያን
የፖለቲካ ሥልጣን መያዝ ላይ ብቻ ያጠነጠነ ሆነና እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ በአፍሪካ ጉዳዮች ንቁ ተሳታፊ መሆን አልቻልንም፡፡ የአፍሪካን አሥር በመቶ የሕዝብ ቁጥር መያዝ ብቻ ሳይሆን፣ የአፍሪካ ኅብረት መቀመጫ የሆነ አገር ለአፍሪካዊ ጉዳዮች ባዳ ሆኖ የአፍሪካ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ነፃነት ትግል ስኬት ላይ የሚፈጥረው ውስንነት በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡

አፍሪካዊ ማንነትን የተላበሰና በአፍሪካ የፖለቲካ፣ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ ኃላፊነቱን የሚወጣ የፖለቲካ ባህል የገነቡ አገሮች ገዥው ፓርቲም ይሁን የተቃዋሚ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ይሁን ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በአፍሪካ ጉዳዮች ላይ ንቁ ተሳታፊዎች ናቸው፡፡ ደቡብ አፍሪካን ለአብነት እናንሳና ለአፍሪካ ቀን የሚሰጡትን ትኩረት በጨረፍታ እንመልከት፡፡

የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ገዥ ፓርቲ የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ (ANC) የአፍሪካ ቀንን በተለይዩ ፕሮግራሞች ያከብራል፡፡ ፕሬዚዳንቱን ጨምሮ የቀድሞ ፕሬዚዳንቶችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎችና ንግግር አቅራቢዎች ናቸው፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲ በኩልም ለምሳሌ የኢኮኖሚ ፍሪደም ፋይተርስ (EFF) የአፍሪካ ቀንን በየዓመቱ በደማቅ ሁኔታ ያከብራል፡፡ በተለይ እ.ኤ.አ. በ2022 የአፍሪካ ቀን ሲከበር የፓርቲው አባላት በመሪያቸው ጁሊየስ ማሌማ መሪነት በፈረንሣይ ኤምባሲ በመገኘት፣ ፈረንሣይ በቀድሞ የቅኝ ግዛቶቿ ላይ ያላትን ተፅዕኖ እንድታቆም የሚጠይቅና ጦሯን ከእነዚሁ የአፍሪካ አገሮች እንድታወጣ የሚጠይቅ ሰላማዊ ሠልፍ በማድረግ ነበር፡፡ መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማትም በኩል በተለይ የቀድሞው የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት ታቦ ምቤኪ ፋውንዴሽን የአፍሪካ ቀን ዓመታዊ ገለጻዎች (Annual Africa Day Lecture) ላለፉት 14 ዓመታት የተካሄደ ሲሆን፣ የቀድሞው የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ  እ.ኤ.አ. በ2019 በደቡብ አፍሪካ ዩኒቨርስቲ ውስጥ በተዘጋጀው የአፍሪካ ቀን ፕሮግራም ላይ ንግግር አቅራቢ እንደነበሩ እናስታውሳለን፡፡ የደቡብ አፍሪካን ልምድ ከአገራችን ጋር ማነፃፀሩን ብቻ ሳይሆን ምን እንማራለን የሚለው የሁላችንም ጥያቄ ይሁን፡፡

ፖለቲካችን ከኢትዮጵያ ተሻግሮ አፍሪካዊ ማንነትን ወደተላበሰ ፖለቲካ ቢሸጋገር እንደ አፍሪካዊ ማኅበረሰብ ለአፍሪካችን የምናበረክተው አበርክቶ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ ለአገራችን የሚኖረው በረከት ዘርፈ ብዙ ነው፡፡ በዚህ ዙሪያ ከሰሞኑ በሌላ ጽሑፍ እመለስበታለሁ፡፡

ወደ ነጥቤ ስመለስ የትምህርት ሚኒስቴር በተለይም የሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) ቁርጠኝነትና ተባባሪነትን በመመኘት ነው፡፡ የመጀመሪያው ከላይ በተጠቀሰው አዋጅ 1209/2012 መሠረት የአፍሪካ ኅብረት ሰንደቅ ዓላማ በትምህርት ቤቶች እንዲሰቀል፣ እንዲሁም መዝሙሩ እንዲዘመር የማድረግ ኃላፊነቱን ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ እንዲወጣ ነው፡፡ የአዋጁ መተግበር አፍሪካዊ ማንነቱን የሚያወድስ፣ በአፍሪካ ውስጥ ያሉትን ዕድሎች የሚያይና ተግዳሮቶቿን በአሸናፊነት እንድትወጣ የድርሻውን መወጣት የሚችል ዜጋ ለማፍራት ትልቅ ሚና ይኖረዋል፡፡  

ሁለተኛው የዘንድሮው የአፍሪካ ቀን አከባበር ነው፡፡ እንደሚታወቀው የአፍሪካ ኅብረት የ2024 መሪ ቃል ትምህርት ነው፡፡ ትምህርት የአኅጉራችን የትኩረት አቅጣጫ በሆነበት በዚህ ወቅት፣ የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች ከእስከ ዛሬው የተለየ ዝግጅቶች ሊኖር እንደሚችል ይጠበቃል፡፡ ወትሮውንም ትምህርት ቤቶች ዋና የአፍሪካ ቀን የድምቀት ቦታዎች ናቸው፡፡ ትምህርት ቤቶቻችን ከመዝናኛነት ባሻገር ምንም ዓይነት ታሪካዊም ሆነ ትምህርታዊ ፋይዳ የሌላቸው ‹‹ከለር ዴይ፣ ኦልዲስ ዴይ፣ ክሬዚ ዴይ…፣ ወዘተ›› እያከበሩ የአፍሪካ ቀን አለማክበራቸው አሳዛኝ ነው፡፡ ይህን ታሪክ ለመቀየር የዘንድሮ የአፍሪካ ኅብረት የትኩረት አቅጣጫው ትምህርት መሆኑ የኢትዮጵያ ትምህርት ቤቶች የአፍሪካ ቀንን ማክበር እንዲጀምሩ ለማስቻል፣ ከዚህ የተሻለ ወቅትና ዕድል ያለ አይመስለኝም፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር በሁሉም ክልሎችና የከተማ አስተዳደር የትምህርት ቢሮዎች በኩል የአፍሪካ ቀን በትምህርት ቤቶች እንዲከበር ጥሪ ቢያስተላልፍ ውጤቱ ለዘንድሮው የአፍሪካ ቀን በዓል ብቻ ሳይሆን፣ ለመጪዎቹም ዓመታት ተማሪዎቹ የአፍሪካ ቀን በየዓመቱ እንዲያከብሩና ስለአፍሪካ የተሻለ የማወቅ ዝንባሌ እንዲኖራቸው ያግዛል፡፡

አፍሪካ ዴይ ኢኒሼቲቭ የአፍሪካን ብዝኃነት፣ ባህል፣ ታሪክ፣ ሙዚቃና ዳንስ ከተማሪዎች ጋር ለማክበር ዝግጅት እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚያም ባሻገር ተማሪዎቹ ስለአፍሪካ ያላቸውን ዕውቀት የሚፈትሹበትና ለወደፊቱም ስለአፍሪካ የበለጠ ለማወቅ እንዲተጉ የሚያደርጉ የጥያቄና መልስ ውድድሮች ይኖራሉ፡፡ ትብብሩን ካገኘን የአፍሪካ ቀን የትውልድ ቦታውን የሚመጥን የአፍሪካ ቀን አከባበር ይኖረናል፡፡ አፍሪካዊ ማንነታችንን እያወደስን የአፍሪካ ቀንን በጋራ እናክብር!

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

The post ልንዘነጋው የማይገባንና የዘነጋነው የአፍሪካ ቀን first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ
አገር ባለውለታነቷን የምታረጋግጥበት ሥርዓታችንን እንፈትሽ!
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

አገር ባለውለታነቷን የምታረጋግጥበት ሥርዓታችንን እንፈትሽ!

በገነት ዓለሙ

በሕግ አምላክ እያለ የሚማጠነው ፖለቲካችን፣ ሰላማችን በአጠቃላይ አኗኗራችን ሁሉ ሕግ ማክበርን፣ ለሕግ መገዛትን የግድ እንደሚጠይቅ ሳይታለም የተፈታ በየትም አገር የታወቀ እውነት ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት ጽሑፌ እንደጠቆምኩት ሕጋዊና ቀጥተኛ መንገዶች እንዲታመኑና እንዲመረጡ፣ ዘወርዋራ፣ መሠሪና ሕገወጥ መንገዶች እርም እንዲባሉ፣ በየትኛውም ዘርፍ ያለው ሕይወት በተገኘው ማናቸውም አቋራጭና አጋጣሚ ሁሉ የመጠቀም ቁማር መሆኑ እንዲቀር የመንግሥት ድርሻም ከፍተኛና ወሳኝ ነው፡፡ ሕግ ገዥ ወደ ሆነበት ሥርዓት ለመሸጋገርና ያንንም ጉዞ ለመጀመር፣ እንዲሁም የዚህን መንገድ ለማንጠፍ የመንግሥት የራሱ ለሕግ ተገዥነት የግድ አስፈላጊ ነው፡፡ መንግሥት የገዛ ራሱን (አገር) ሕግ አክባሪና ባወጣው ሕግ ተዳዳሪ የመሆን ጉዳይ የሕግ አወጣጡን ሕግ፣ የሚወጣውን ሕግ ዓይነት፣ ይህንን ሕግ ለማስፈጸም በማደራጀት በሚዘረጉት ተቋማትና አሠራሮች ላይም የተመሠረተ ነው፡፡

ለምሳሌ ለመላው ዓለም እንግዳ ደራሽ ሆኖ ከሞላ ጎደል አዲስ ዓይነት የሕግ ዝግጁነት የጠየቀው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተራርቆ መኖርን ግድ የሚያደርግ፣ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ሕግ እንዲወጣ ያደረገ (መጨባበጥንና መሰባሰብን የከለከለ፣ ከውጭ አገር የሚመጣ እንግዳን ሆቴል እንዲያርፍ ያስገደደ) ጥንቃቄ ጠይቆናል፡፡ በአጠቃላይ አደጋውን እንደነገሩ የተወጣነው በሽታ የመከላከል የሕግ አሠራርና የተቋም ዝግጁነትን ነበር ብሎ አፍ ሞልቶ መናገር ያስቸግራል፡፡

ሌላ ምሳሌ እንመልክት፡፡ ሰው ሁሉ ዛሬ ስለቅርስና ስለታሪክ የሚነጋገርበት፣ አልፎ አልፎም ጠበኛ የሆነበት ነው፡፡ ግን የቅርስ ጥበቃ ሕግ አለ፡፡ የቅርስ ጥበቃ ባለሥልጣን የሚባል ተቋምም አለን፡፡ ክርክሩና ሙግቱ ግን እነዚህን ሲማጠን፣ ሲጠቅስ፣ ዋቢ ሲያደርግ አንሰማም፡፡ የመንግሥት የተለያዩ የሥልጣን አካላት የአገርን ‹‹የሕግ አምላክ›› የማልማት፣ የማጠናከር ድርሻ እነዚህን የስም ጌጥ ብቻ ሆነው የቀሩ ሕጎችንና ተቋማትን የመፈተሽ አደራና ግዳጅም ይጨምራል፡፡ ይህን የመሳሰሉ ሪሰሲቴሽን (Resucitation) ወይም ተንሰአት የሚጠይቁ አዲስ መወጣትና ያለውን ጎዶሎ ለመሙላት የሚያስፈልጉ የሕግ ዓይነቶች አሉ፡፡ ከነዚህ መካከል አንዱ የሜዳይ፣ የኒሻንና የሽልማት ረቂቅ ሕግ ነው፡፡

አሁን በምንገኝበት ተጨባጭ ሁኔታ ስለዚህ ጉዳይ፣ ስለሜዳይ፣ ኒሻንና ሽልማት ማውራት ቀልድ ተደርጎ ሊታይ ይችላል፡፡ በየአቅጣጫውና በየመስኩ ግን በተቋም ግንባታ ሥራችን እጅግ መበርታት አለብን፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ስም ያለው፣ በመላው ዓለማት የታወቀና የተከበረ፣ አሁንም በታሪክና በቅርስ ሰዎች ዘንድ ከፍ ያለ ቦታ ተሰጥቶ የሚጠናና የሚሰበሰብ የ‹‹አመሠግናለሁ›› ሥርዓት ነበራት፡፡ አገር ባለውለታነቷን የምትገልጽበት ይህ የክብርና የማዕረግና ሥርዓት ግን አንድም በየዘመኑ ሥልጣን ላይ በነበሩት ገዥዎች እምነት አምሳል የተሟሸ ዘመናዊውንም የመንግሥትና የሃይማኖት መለያየት የማያውቅ ወይም ያላከበረ በመሆኑ፣ ሌላም ደግሞ የአንዱ ገዥ የሥልጣን ዘመን በኃይልና በጉልበት ሲያከትም ተከታዩ ገዥ የቀድሞውን የክብርና የማዕረግ ሥርዓት እንዳለ አሽቀንጥሮ የሚጥለው በመሆኑ ይህ ሥርዓታችንና ሥርዓቱን የሚገዛው ሕግ ክፍት ሆኖ ኖሯል፡፡ ለዚህ ባዶነት ተወያይቶ ሕዝብና ያገባኛል ባዮችን ሁሉ አማክሮ፣ ባለሙያም አነጋግሮና መላ መፍጠር በቀጠሮ የሚያድር ሥራ አይደለም፡፡

የአፍሪካ ኅብረት ማቋቋሚያ ሕግ የተቋሙን አስተዳደራዊና አስፈጻሚ አካል ሥልጣንና ተግባር በሚደነግግበት አንቀጹ (አንቀጽ 13) (1) (ኤል) ‹‹A System of Awards, Medals and Prizes›› እንዲቋቋም ያዛል፡፡ በቅርቡ መጋቢት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ትግራይ ክልል ውስጥ ለተሰማሩት በፕሪቶሪያ ስምምነት መሠረት በተቋቋመው የስምምነቱ ‹‹ሞኒተሪንግ ቬሪፊኬሽንና ኮምፕላየንስ ሚሽን›› ሥራ ለሚያከናውኑ ሃያ አንድ ከኢትዮጵያ፣ ከኬንያ፣ ከናይጄሪያና ከደቡብ አፍሪካ ለተወጣጡ ወታደራዊና ሲቪል ባለሙያዎች የተሰጠው የአገልግሎት ሜዳልያ መነሻና መሠረት አኅጉራዊው ድርጅት ባለውለታነቱን የሚገልጽበት ሥርዓት ነው፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለዚህ የፕሪቶሪያ ስምምነትና አመሠግናሁ ላላቸው ሰዎች ‹‹የምስክር ወረቀት›› (ሰርተፊኬት) ሲሰጥ ዓይነተናል፡፡ የዚህ የምስክር ወረቀትና ዋጋ የሕግ መሠረቱ ምንድነው ብሎ መጠየቅ ‹‹ጉድለታችንን›› ያጋልጣል፡፡ ይህንን መነሻ በማድረግ ከዚህ ቀደም ጥር 2 ቀን 2011 ዓ.ም. በዚህ ጉዳይ ላይ ያቀረብኩትን በጋዜጣው ፈቃድ ጋብዣለሁ፡፡

ይህን በመሰለ አስቸጋሪ ጊዜ ውስጥ የብዙ ዘመን ታሪክ ያለውን፣ ዛሬ ግን ጎዶሏችን የሆነውን ያለ ብልኃትና ያለ ዕውቀት ደግሞ ዝም ብለን የቀጠልንበትን፣ የአገራችንን የ‹‹ክብር የማዕረግ›› ሥርዓት (Honour System) ጉዳይ እንመልከት፡፡ ስመ ጥሩው ባላምባራስ ማኅተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል እስከ 1928 ዓ.ም. ድረስ ያሉትን የመንግሥት ሰነዶች አደራጅተውና አብራርተው ባቀረቡበት ‹‹ዝክረ ነገር›› መጽሐፋቸው እንደሚነግሩን ወግ ማዕረግ ያለው የክብር ምሥጋና መስጠት፣ ይህንንም በሽልማት፣ በማዕረግ፣ በኒሻንና በሜዳልያ መግለጽ ረዥም ታሪክ ያለው አሠራር ነው፡፡

በተለይም፣ ‹‹የኢትዮጵያ… መንግሥት በዓለም ላይ ያሉ የሠለጠኑ መንግሥታት እንደሚያደርጉት ሁሉ…›› በታማኝነትና በቅንነት ብዙ ዘመን ላገለገሉ፣ በጦር ሜዳ ላይ በሚያኮራ ሁኔታ ለተዋጉ፣ ጥበብ በማውጣት ድርሰት በመድረስ ለአገራቸው ዕድገትና ክብር ለደከሙ፣ ወዘተ የሚሰጡ ሜዳሊያዎችን ማዘጋጀት ከመንግሥት ሥራዎች ውስጥ አንዱ ሆኖ ኖራል፡፡ የእነዚህንም ኒሻኖችና ሜዳልያዎች ዝርዝር ‹‹ሙሉ ሀተታና የአሸላለሙን ዝርዝር ደንብ›› ይዘታቸውንና መልካቸውን ይነግሩናል፡፡

ከጣሊያን ወረራ በኋላም ይህ አሠራርና ሥርዓት ተጠናክሮ ቀጥሎ፣ በዘመናዊ የሕግ አወጣጥ ሥርዓት ታግዞ የኢትዮጵያ ሕግ አካል ሆኖ በአገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከአገር ውጭም ጭምር የሚታወቅ ‹‹Honour System›› ሆኖ ኖሯል፡፡ በዚህም መሠረት አገራችን የማይናቅ ረዥም ዝርዝር ያላቸው የማዕረግ ደረጃም የወጣላቸው ሜዳልያዎችና ኒሻኖች ነበራት፡፡ የቅዱስ ጊዮርጊስ የጦር ሜዳይ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የጦር ሜዳይ፣ የዳግማዊ ምኒልክ የውትደርና አገልግሎት ሜዳይ፣ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የብሔራዊ አገልግሎት ሜዳይ፣ የውስጥ አርበኞችና የስደተኞች ሜዳይ፣ የድል ኮከብ ሜዳይ፣ የመምህራን ሜዳይና የኮሪያ ጦርነት ሜዳይ የሚባሉ ነበሩ፡፡ 

የኒሻኖች ደንብ ደግሞ በየጊዜውና በየዘመኑ የተቋቋሙትንና የተወሰነላቸውን ደንብ በማሻሻልና በማጠቃለል የማኅተመ ሰሎሞን ማዕረግ፣ የንግሥተ ሳባ ማዕረግ፣ የሥላሴ ኒሻን ማዕረግ፣ የዳግማዊ ምኒልክ ኒሻን ማዕረግ፣ የኢትዮጵያ የክብር ኮከብ ኒሻን ማዕረግ የሚባሉ እያንዳንዳቸው
አምስት፣ አምስት ደረጃ ያላቸው የኒሻን ዓይነቶችን አቋቁሟል፡፡

ዝርዝሩን በተለይም አሁን ላይ ሆኖ ለሚያየው በጣም ይደንቃል፣ ይገርማል፡፡ መንግሥትና ሕግ በእንዲህ ያለ ጉዳይ እንዲህ ‹‹ሥራ ይፈታሉ?›› ጉልበትና ገንዘብ ያባክናሉ? ያሰኛል፡፡ ለምሳሌ የማኅተመ ሰሎሞን ማዕረግ የሚባለው ኒሻን የመጀመርያው ዓይነት ባዝግና (ኮለር) በተለይ ለማን እንደተወሰነ (ለንጉሠ ነገሥቱና ለእቴጌዪቱ የተመደበ መሆኑን)፣ ንጉሠ ነገሥቱ በልዩ አስተያየታቸው ለንጉሣዊ ቤተ ዘመዳቸውና ለውጭ አገር ነገሥታት፣ እንዲሁም ደግሞ እጅግ ከፍ ያለ አገልግሎት ላላቸው ሰዎች የሚሰጥ እግጅ በጣም የከበረ ሽልማት መሆኑ ተደንግጓል፡፡ የእያንዳንዱ ምሥልና ቅርፅ ከተጓዳኝ ዝርዝሮች ጋር በሕግ ተወስኗል፡፡ የእያንዳንዱ የኒሻን ዓይነትና ማዕረግ በተለይም የማኅተመ ሰሎሞን፣ የንግሥተ ሳባ ማዕረግ ኒሻኖች ተሸላሚዎች ቁጥር ከተወሰነ ቁጥር እንዳይበልጥ በሕግ ተደንግጓል፡፡ ከሦስት፣ ከአሥር፣ ከ20 … ፣ ከ45፣ ከ55 አይበልጥም ተብሎ በሕግ ተከልክሏል (በነገራችን ላይ ንጉሠ ነገሥቱ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ታኅሳስ 2 ቀን 1940 ዓ.ም. ለፊልድ ማርሻል ሞንትጎመሪ የሸለሟቸው ታላቁን የሰሎሞን ኒሻንን ነው)፡፡

ይህ የክብርና የማዕረግ የሽልማት ሥርዓት በመላው የንጉሠ ነገሥቱ የሥልጣን ዘመን ዘለቀ፡፡ ከመስከረም 1967 ዓ.ም. ጀምሮ ሥልጣን የያዘው ወታደራዊ መንግሥት በ1971 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ (ስለቀድሞዎቹ ሜዳይዎችና ኒሻኖች በሕግ በግልጽ ሳይነገር) የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥትን የሜዳይና የኒሻን አዋጅ (አዋጅ ቁጥር 169/71) አወጀ፡፡ በአዋጁም በሕጉ በዝርዝር በተወሰኑት ሜዳይዎችና ኒሻኖች መሠረት በጦር ሜዳ ሜዳልያዎቹ ዝርዝር ውስጥ፣ የጦር ሜዳ ሜዳልያዎችና ዓርማ የሚባሉት የኅብረተሰባዊ ኢትዮጵያ ወደር የሌለው ጀግና ሜዳይ፣ የላቀ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ፣ የጦር ሜዳ ጀብዱ ሜዳይ ከአንደኛ ደረጃ እስከ ሦስተኛ ደረጃና የጦር ሜዳ ቁስለኛ ሜዳይ፣ እንዲሁም የአብዮታዊ ዘማች ዓርማ የሚባሉ ተደንግገዋል፡፡ እነዚህ የሜዳይ ሽልማቶች ለማንና ምን ለፈጸመ እንደሚሰጡና ተሸላሚውም የሚያገኘው ልዩ መብት በዝርዝር ተወስኗል፡፡

በዚሁ ፈርጅ ውስጥ የተወሰኑ የሥራና የአገልግሎት ሜዳልያዎችም አሉ፡፡ የኅብረተሰብአዊት ኢትዮጵያ የሥራ ጀግና ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የከፍተኛ ውትድርና አገልግሎት ሜዳይ፣ የብሔራዊ አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የውትድርና አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ የፖሊስነት አገልግሎት ሜዳይ (አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ)፣ እንዲሁም የአገልግሎት ዘመን ሪባን የሚባሉ አሉ፡፡ ሕጉ የኅብረተሰባዊት ኢትዮጵያ ታላቅ የክብር ኮከብ ኒሻን፣ የየካቲት 1966 አብዮት ኒሻን (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የቀይ ባህር ኒሻን (ባለሦስት ደረጃዎች)፣ የጥቁር ዓባይ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ)፣ የአፍሪካ ኒሻን (ባለሦስት ደረጃ) የሚባሉ የኒሻን ዓይነቶችንም መሥርቷል፡፡ እነዚህ ሁሉ ለማን እንደሚሰጡ፣ የሚያገኘው ሰው የሚኖረው ልዩ መብት፣ የሜዳሊያዎቹና የኒሻኖቹ ቅርፅ፣ መጠንና አካል ምንነት በዝርዝር ተደንግጓል፡፡ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ኮሚሽንም ተቋቁሟል፡፡ ከርዕሰ ብሔሩ ፈቃድ ሳያገኝ ኢትዮጵያዊ የውጭ አገር ሜዳይ ወይም ኒሻን መቀበል የተከለከለ መሆኑም ተደንግጓል፡፡ ይህም የአገር ሕግ ሆኖ እስከ 1983 ዓ.ም. ድረስ ዘለቀ፡፡ ደርግ ወደቀ፡፡ ኢሕአዴግ መጣ፡፡

በኢሕአዴግ የሥልጣን ዘመን በወታደራዊው ዘርፍ እንኳን የሜዳይ፣ የኒሻንና የሽልማት ጉዳይ የመከላከያ ሠራዊት የ1987 ዓ.ም. አዋጅ ውስጥ የተካተተው በ1990 ዓ.ም. መጨረሻ ላይ በአዋጅ ቁጥር 123/1990 (የመከላከያ ሠራዊት ማሻሻያ አዋጅ) ነው፡፡ በዚህ ሕግ የዓድዋ ድል ሜዳይ የሚባል ወደር የሌለው ጀግንነት በዓውደ ውጊያ ለፈጸመ ኢትየጵያዊ ግለሰብ ወይም የሠራዊት አሃድ ወይም ቡድን የሚሰጥ የመጨረሻ ከፍተኛ የጀግና ሽልማት ሆኖ የተቋቋመውን ጨምሮ የተለያዩ የሜዳሊያዎች፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ሽልማቶች ተመሠረቱ፡፡

ፖሊስን የሚመለከት የሜዳይ፣ የሪባንና የምስክር ወረቀት ነገር በቀዳማዊ ሕግ ደረጃ (ፓርላማ በሚያወጣው ሕግ) የተነሳው ገና አሁን በቅርቡ በ2004 ዓ.ም. በአዋጅ ቁጥር 720 ነው፡፡ እሱም ለፖሊስ አባላት የሚሰጡ ሜዳዮች፣ ሪባኖችና የምስክር ወረቀቶች በፌዴራል ፖሊስ መተዳደሪያ ደንብ ይወሰናል ሲል ወሰነ፡፡ በዚህም መሠረት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 268/2005 የጀግንነት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ)፣ የላቀ ሥራ ውጤት ሜዳይ፣ የፖሊስ አገልግሎት ሜዳይ (ከአንደኛ እስከ ሦስተኛ ደረጃ) እና የፖሊስ አገልግሎት ሪባን የሚባሉ የሽልማት ዓይነቶችን አቋቋመ፡፡

አገር ባለውለታነቷን ከምታረጋግጥበት፣ ውለታዎችን ከምትስታውስበትና ለወደፊትም እንዲበረታቱ ከምታደርግበት መንገዶች አንዱ ይህ የሜዳይና የኒሻን ሽልማት ሥርዓት የአገሪቱን ያህል ረዥም ዘመን ያለው ቢሆንም፣ ተከታታይ መንግሥታት እየወረሱ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ባህልና የአገር ሀብት አልሆነም፡፡ ይህ ሳያንስ የተከታታይ መንግሥታት ይህንን የመንግሥት ታላቅ ሥራ የሚከናወንበትን የሕግና የተቋም ጎዶሎ፣ ቶሎና ወዲያውኑ መሙላት አለመቻላቸው፣ በተለይም በዚህ የኢሕአዴግ መንግሥት ዘመን እንደተመሰከረው አወቅነውም፣ አላወቅነውም ብሔራዊ/የአገር ማፈሪያ እየሆነ ነው፡፡ እስካሁን እንደተመለከትነው በኢሕአዴግ/በኢፌዴሪ መንግሥት የመከላከያው ጎን (የፖሊስን ጨምሮ) የሜዳይና የኒሻን ሽልማት እንኳን የተሟላው ከረዥም ጊዜ ግዴለሽነትና ቸልተኝነት በኋላ ነው፡፡ አገር ባለውለታዊነቷን የምትገልጽበትና የምታረጋገጥበት የሲቪል የመንግሥት ሽልማት ሥርዓት ግን ዛሬም ያልተሟላ ጎዶሏችን ነው፡፡

የሚሰማ ስለሌለ፣ ደንገጥ የሚልና የሚደንቀው ሰው ስለጠፋ እንጂ፣ ጉዳዩ በተለይም ጎልቶ የተነሳው የኢትዮጵያ ሚሊኒየም በተከበረበት ወቅት ‹‹ለማይመለስ ውለታህ …›› (የተሟላ ትክክለኛ መጠሪያው ምን እንደተባለ እርግጠኛ አይደለሁም) የሚል ዓይነት አስቀድሞ በሕግ ያልተቋቋመ ሜዳሊያ ስንሰጥ/ሰጠን ስንል ነው፡፡

ከዚያ በፊትና ከዚህ ወዲህም ባለሥልጣኑና ሥልጣን አለኝ የሚለው ሁሉ እየተነሳ ‹‹የከተማውን ቁልፍ››፣ ‹‹የክብር ዜግነት›› ሲሰጥ ዓይተናል፡፡ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የክብር ዶክትሬት አሰጣጥና አጠራርም ጭምር በጣም ግራ የተጋባና መሳቂያ ሆኖ አርፎታል፡፡ ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸውን እነዚህን ቁምነገሮች የሚገዙ ሥርዓትና አሠራር መዘርጋት፣ ለመንግሥትና ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ለምን የቸገረ ነገር ይሆናል፡፡

ያኔ ፕሬዚዳንት ኦባማ በአቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአስተዳደር ዘመን ኢትዮጵያን ሲጎበኙ በአጋጣሚው ‹‹ማሳሰቢያ›› ከሰጡባቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ፣ ኢትዮጵያ ለዜጋም ሆነ ለውጭ ሰው የምትሰጠው የሲቪል ሜዳሊያ ወይም ኒሻን ወይም ሌላ በሕግ የተቋቋመ ሽልማት የሌላት መሆኑን ነበር፡፡ ያ ከሆነ በኋላ ሚያዝያ 16 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ለተሰናባቹ ጠቅላይ ሚኒስትር ለአቶ ኃይለ ማርያምና ለባለቤታቸው ‹‹ሜዳሊያ›› እና ‹‹የአገሪቱ ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጡ ዓይተናል፡፡ ከዚያም በኋላ አሁን ለዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ለተሰናባቹ የሪፐብሊኩ ፕሬዚዳንት (ለባለቤታቸውም) ‹‹ኒሻን›› እና ‹‹ከፍተኛ የክብር ዲፕሎማ›› ሲሰጣቸው መስክረናል፡፡

ሽልማቱ በተሰጠበት የሥር ምክንያት ላይ ተቃውሞም ሆነ
2024/05/14 16:08:35
Back to Top
HTML Embed Code: