Telegram Web Link
የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ካልቀየረ መንግሥት ተመጣጣኝ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ካልቀየረ መንግሥት ተመጣጣኝ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

የአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት ከሳምንት በፊት ለኢትዮጵያውያን የሚደረገውን የቪዛ አሰጣጥ ሒደት ለማጥበቅ ያሳለፈውን ውሳኔ ካልቀየረ፣ መንግሥት ተመጣጣኝ ውሳኔ እንደሚያስተላልፍ አስታወቀ፡፡

የአውሮፓ ኅብረት በቪዛ ጉዳይ በቅርቡ ያሳለፈውን ውሳኔ እንዲሽር ኢትዮጵያ እንደምትፈልግ ጠቅሰው፣ ይህ ካልሆነ ግን ከውሳኔው ጋር የሚጣጣም የራሷን ተመጣጣኝ ዕርምጃ ትወስዳለች ያሉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነብዩ ተድላ ናቸው፡፡

ቃል አቀባዩ በሳምንታዊ መግለጫቸው የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፈው የቪዛ ውሳኔ ትክክል እንዳልሆነ በመግለጽ፣ ኢትዮጵያ ለኅብረቱ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱን በጠበቀ መንገድ ማሳወቋን አስረድተዋል፡፡

ኅብረቱ ወደ አውሮፓ የገቡ ኢትዮጵያውያን ስደተኞችን ወደ አገራቸው በመመለሱ ረገድ ለኢትዮጵያ መንግሥት ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ቢያቀርብም፣ ባለሥልጣናት ተገቢውን ምላሽ ባለመስጠታቸው በኢትዮጵያውያን ላይ የቪዛ አሰጣጥ አሠራሩን ማጥበቁን በማስታወቅ ነበር ውሳኔውን ያስተላለፈው፡፡

በአውሮፓ ኅብረት በተለይም ‹‹ሸንገን ቪዛ›› ውስጥ በሚገኙ አገሮች ጥገኝነት የጠየቁ ኢትዮጵያውያን ጉዳያቸው የመኖሪያ ፈቃድ የማያሰጥ ሆኖ ሲገኝ፣ ጉዳዩ በፍርድ ቤት ታይቶ ወደ አገራቸው መመለስ አለባቸው የሚባሉትን ኢትዮጵያ እንድትወስድ በመጠየቁ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ የኢትዮጵያ መንግሥት ከኅብረቱ ጋር እየሠራ የቆየ መሆኑን የገለጹት ቃል አቀባዩ፣ ውሳኔው በበርካታ ሚዲያዎች እንደተዘገበው የቪዛ ክልከላ አይደለም ብለዋል፡፡

በመሆኑም ማንኛውንም መሥፈርት የሚያሟላ ግለሰብ ቪዛ ማመልከትና ማግኘት እንደሚችል፣ ነገር ግን ከዚህ ቀደም ለቪዛ ማመልከቻ ይሰጥ የነበረው 15 ቀናት ወደ 45 ቀናት፣ እንዲሁም ወደ ኅብረቱ አባል አገሮች በተደጋጋሚ እንዲገቡ ይፈቅድ የነበረውን የቪዛ አሰጣጥ ለአንድ ጊዜ ብቻ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ በኅብረቱ በኩል ከቪዛ ጋር በተገናኘ የተወሰዱ ዕርምጃዎች ተገቢ እንዳልሆኑ ቃል አቀባዩ ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ ወደ ኅብረቱ አባል አገሮች የገቡ ዜጎቿን በተለይ በገቡበት አገር መኖር እንደማይችሉ በፍርድ ቤት ተወስኖ ሒደቱ ካለቀ በኋላ፣ መመለስ ያለባቸው ዜጎች ክብራቸውንና ደኅንነታቸውን በጠበቀ መንገድና ዓለም አቀፍ ተሞክሮን ብቻ ተመርኩዞ መከናወን አለበት የሚል አቋም እንዳላትም አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያውያንን ከአውሮፓ አገሮች የማስመለስ ሥራ እንዲያከናውን የተቋቋመ ብሔራዊ ኮሚቴ መሥራት ስለሚቻልበት ከኅብረቱ ጋር ሲመክር መቆየቱን፣ ዜጎችን በማስመለሱ ሒደት በሁለት ዙር ከአውሮፓ ኅብረት አመራሮችና አባላት ጋር ውይይት አድርጎ መመለሱን ተናግረዋል፡፡

 ከውይይቱ በኋላ የግለሰቦችን ዜግነት በተመለከተ አስፈላጊው ማጣራት የሚያደርገው ብሔራዊ ኮሚቴ በኖርዌይ፣ በስዊድን፣ በፊላንድ፣ በስዊዘርላንድና በኔዘርላንድስ የማጣራት ተግባራት አከናውኖ መመለሱም ተገልጿል፡፡

ኮሚቴው ከጥገኝነት ጠያቂዎች ውስጥ ኢትዮጵያዊ ናቸው ተብለው በኅብረቱ ከተለዩ ተመላሽ ግለሰቦች መካከል ማጣራት ሲያደርግ የቆየ ቢሆንም፣ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ በሕገወጥ መንገድ ወደ አውሮፓ የሚገቡ ሰዎች ተመሳሳይ የሆነ ባህል፣ ቋንቋና ሃይማኖት ጭምር የሚጋሩ በመሆናቸው፣ ዜግነታቸውን ለማጣራት ጊዜ የሚወስድና ጥንቃቄ የሚጠይቅ መሆኑን አቶ ነብዩ ተናግረዋል፡፡

በአውሮፓ ኅብረት በኩል ኢትዮጵያውያን ናቸው ተብለው የተለዩና ወደ አገራቸው ይመለሱ ተብለው የቀረቡ 89 ሰዎች ቢኖሩም፣ ከእነሱ ውስጥ ኢትዮጵያውያኑ 26 ብቻ  መሆናቸው ተረጋግጧል ብለዋል፡፡ እነዚህም መካካል አምስት ከስዊድን፣ አምስት ከኖርዌይ፣ ስምንት ከስዊዘርላንድ፣ ስድስት ከኔዘርላንድስና ሁለት ከፊላንድ ይገኙበታል ሲሉም አክለዋል፡፡

ኢትዮጵያውያን የመሆናቸውን ጉዳይ የማጣራት ሥራ አዳጋች በመሆኑ፣ ማጣራት ከተደረገ ወዲህ እስካሁን ከአውሮፓ 15 ዜጎች ወደ አገር ቤት እንዲመለሱ መደረጉም ተነግሯል፡፡

ሥራው በዚህ መልኩ እየተከናወነ ባለበት ወቅት ኅብረቱ የወሰደው ዕርምጃ፣ በተለይም የኢትዮጵያ መንግሥት ፈጣን ትብብር አላሳየም በሚል ምክንያት የተደረሰበት ውሳኔ ግን ተገቢ አይደለም ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ኅብረቱ እንደሚለው በኢትዮጵያ በኩል መታየት ያለባቸው ክፍተቶችና ጉዳዮች ካሉ በትክክለኛው የመግባቢያ መንገድ እንደሚታይ ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያና የአውሮፓ ኅብረት ካላቸው ጠንካራ አጋርነት አኳያ ይህ ዓይነት አካሄድ ጊዜውን ይመጥናል ተብሎ አይታሰብም ብለዋል፡፡

በሕገወጥ መንገድ ወደ አውሮፓ የተሻገሩና በአገሪቱ መኖር ያልቻሉ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ለመመለስ፣ ኢትዮጵያ ኃላፊነት በተሞላበትና ዓለም አቀፍ አሠራሩን ተከትላ እንደምትሠራ አስረድተዋል፡፡  

The post የአውሮፓ ኅብረት በኢትዮጵያ ላይ ያሳለፈውን ውሳኔ ካልቀየረ መንግሥት ተመጣጣኝ ዕርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ሲሳይ ሳህሉ
ለዴሞክራሲና ለነፃነት መነጋገርን ማወቅ
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

ለዴሞክራሲና ለነፃነት መነጋገርን ማወቅ

በገነት ዓለሙ

ዓውደ ዓመት ወይም በዓል እንደየአገሩና በየአገሩ ይለያያል፡፡ በየዓመቱ ያምጣሽ/ያምጣህ ወይም ‹‹Many Happy Returns›› እየተባለ የሚከበረውና የሚነግሠው የበዓል ዓይነት በየአገሩ፣ በአገር ውስጥም የተለያየ ነው፡፡ ከዚህ ለየት ብሎ ግን መላው ዓለም፣ ዓለም በመላው በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) አማካይነት የሚጋራቸው የጋራ የወል ያደረጋቸው በዓላት አሉ፡፡ የተመድ ዓለም አቀፋዊ ቀናት ይባላሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪና በተጓዳኝም አኅጉራዊ ድርጅቶች (ለምሳሌ አፍሪካ ኅብረት) የሚያከብራቸው፣ የሚያነግሣቸው በዓላት አሉ፡፡ በዓለም ያለው ችግር ሁሉ ከሞላ ጎደል ለክብሩ፣ ለመፍትሔው ሲባል የተሰዋለት የተመደበለት ዓለም አቀፋዊ ቀን አለ፡፡ የሴቶች ቀን፣ የሠራተኞች ቀን፣  የፕሬስ ነፃነት ቀን የመሳሰሉት ለምሳሌ በብዛት የሚታወቁት ናቸው፡፡

አንዳንዶቹ ደግሞ ምናልባትም ጨርሰው የማይታወቁ፣ ‹‹ይህ ደግሞ ምናባቱ ያደርጋል?›› የሚባሉ ዓይነት አሉ፡፡ ለምሳሌ ከሜይ ወር ሳንወጣ ሜይ ሁለት (በዓለም የሠራተኞች ቀንና በዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን መካከል የሚገኘው ሁለት) የዓለም የቱና ቀን ነው፡፡ ተመድን በመሰለ የዓለም ማኅበር ደረጃ የዓሳ ኢንዱስትሪው ቱና የሚባለውን (የዓሳ ዓይነት) ቀን የሚያከብረው ከኢንቫይሮመንት (አካባቢ) ጥበቃ አኳያ ነው፡፡ ኢትዮጵያ አገራችን በአቅሟ በሚደንቅ አቅሟና ሠልፍ ለዕልቂት የተቃረቡ፣ ለዕልቂት አደጋ የተጋለጡ እንደ ዋልያ አይቤክስና እንደ ቆርቄ የመሳሰሉ እንስሳት/አራዊት የሚያስብ፣ የሚጠብቅ አገልግሎት ያለው የፖስታ ቴምብር አሳትማለች፡፡ በተመሳሳይ በማዕከላዊ ባንኳ (በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ደንብ አውጭነት ለምሳሌ በመጥፋት ላይ ያሉት የዱር አራዊት ጥበቃ መታሰቢያ ቅንስናሽ ገንዘቦች ደንብ ቁጥር 61/1970 አማካይነት) ተመሳሳይ አንድን ጉዳይ ‹‹ጉዳዬ›› ነው ያገባኛል ባይ ሆና አራምዳለች፣ የሴቶች ቀን የታወቀ ቀን ነው፡፡ የቱና ቀን ብዙም አይገባም፣ አይታወቅም ይሆናል፡፡ ኢትዮጵያ ለዱር አራዊት ጥበቃ እንዳደረጋቸው በደንብ ቁጥር 86/1976 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሴቶች አሥር ዓመት መታሰቢያ ቀን ቅንስናሽ ገንዘቦች አውጥታ ነገሩን ጉዳዬ ብላለች፡፡

ተመድ ከተመሠረተ ከ1945 (እ.ኤ.አ.) ጀምሮ 200 ያህል ቀናት በየዕለታቸው የሚታሰቡ፣ የሚሰለሰሉ፣ የሚንገበገቡባቸው ሆነው እንዲከበሩ ወስኗል፡፡ ለምሳሌ የኢትዮጵያ የሕዝብ በዓላት ሕግ ማሻሻያ ረቂቅ እየታየ ባለበት ጊዜና ከወራት መካከል በአንፃራዊነት ብዙ የሕዝብ በዓላት በሚገኙበት በዚህ በሚያዝያ ወር ውስጥ ሜይ ደይንና የፕሬስ ነፃነት ቀንን አክብረናል፣ ጉዳያችን አድርገን አስበናል፡፡ አሳሳቢነቱንም ለማሳሰብ ሞካክረናል፡፡ በዚህም መካከል የሚያሳስቡ ጉዳዮችን ዓይተናል፡፡

የምንለውን ነገር ይበልጥ ለማፍታታት ይረዳን ዘንድ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በዚህ አጋጣሚ፣ በዚህ አጋጣሚ ከማለት ይልቅ መደበኛ የዕለት ተዕለት፣ የዘወትር ሥራውን ሲያከናውን ካወጣቸው መግለጫዎች፣ ከሰጣቸው አስተያየቶች፣ ወዘተ መካከል አንዳንዶቹን ዋቢ እያደረግሁ ጉዳዩን አስረዳለሁ፡፡ መነሻ/መንደርደሪያ የማደርጋቸው አስተያየቶች ግን የኢሰመኮን ብቻ አይደለም፡፡ የመላው ዓለም ጉዳይ ነውና ዓለም በሙሉ፣ በተለይም እኛን አስመልክቶ በተለይም እዚሁ ከቅርብ የሚሰጣቸውን መግለጫዎች፣ አስተያየቶችንም መነሻችን ይልቁንም ቆስቋሾቻችን ናቸው፡፡ ከእነዚህ መካከል አንዱ ‹‹አስተያየት›› አዲስ አበባ/ኢትዮጵያ የሚገኙ የውጭ አገር፣ በተለይም የምዕራብ አገሮች መንግሥታት (ከኢዩ ጋር አሥራ ሰባት አገሮች) የሰጡት የዓለም የፕሬስ ነፃነት ቀን የጋራ መግለጫ ነው፡፡ መነጋገርን፣ ስለመናገር እየተነጋገርንና እያከበርን ሐሳብን የመግለጽ ነፃነትን እያከበርንና እያነገሥን ለምን ተናገሩ አንልም፡፡ የሰብዓዊ የመብቶች ጥበቃ በነዚህ አገሮች የሚገኝበትን የጥበቃ ደረጃ እያየንም፣ የሰብዓዊ መብቶች ጥበቃ የእነዚህን አገሮች ደንታ ከጥቅሞቻቸው ጋር እንደሚገነዘቡ አሳምረን እያወቅንም ለምን ይናገራሉ? ለምን ይናገሩናል? ብለን የምናከብረውን ጉዳይ አናናንቅም፡፡ ዋናውን ጭብጥ አንሸሽም፡፡ መጀመሪያ መናገር መብታቸው ጭምር ነው፡፡ ሳይጠየቁ መቅረት መኖር የለበትም ብለን ስለምናምን፣ ማመን ስላለብን እምነት ብቻ ሳይሆን ይህንኑ መተግበር መግለጽና መኗኗሪያችን ማድረግ ስለሚገባን አጉል ተናገሩ፣ ለምን ተናሩን ብለን ተሸፋፍኖ መተኛት›› አንሻም፡፡ ‹‹ገልጦ የሚያይ ጌታ አለ ብለንም እናምናለን››፡፡ እንጂማ አዲስ አበባ ላይ በተለይ በዚህ የፕሬስ ነፃነት ቀን ‹‹ባልተለመደ›› ሁኔታ ‹‹በማኅበር ተደራጅተው ‹‹በሠልፍ ወጥተው›› የፕሬስ ነፃነት የታሰሩ ጋዜጠኞች ጉዳይ ያሳስበናል ያሉ መንግሥታት ኤምባሲዎች ይህን ቢያደርጉ የሚያምርባቸው፣ ቤታቸው ውስጥ ተግባራቸው ከቃላቸው ቢጣጣም ይልቁንም ባይፈነካከር ነበር፡፡

አሜሪካና ታላቋ ብሪታንያ ጁልየን አሳንጅ የሚባል አሳታሚ/ጋዜጠኛ ጉዳዩን የመስለ መደበኛ የማይችሉት ቁስል፣ ቡግንጅና ነቀርሳ ውስጣቸው ይዘውና የዩኒቨርሲቲዎች ግቢ ውስጥ ተቆስቁሶ መላው አሜሪካን ያጥለቀለቀውና የለውጥም ግፊት የሆነው የቬትናም ጦርነት፣ የዘር መድልኦና ተቃውሞ ታሪክ አለኝ ብሎ የሚደነፋው የአገርና የዩኒቨርሲቲዎች አመራር እዚያው ዩኒቨርሲቲ  ውስጥ መመርመርን፣ መጠየቅን፣ መቃወምን በፀረ አይሁድነት (አንቲ ሴመቲዝም) መከላከል ስም ሲደፍቅ እያየን፣ እነ ሲኤንኤን የዚህን ዜና ጉዳይ እንዴት አድርገው እንደሚሠሩት፣ እንዴት አድርጎ እንደሚሠራራቸው እየመሰከርን የእነዚህን አገሮች የመብትና የነፃነት ተቆርቋሪ ነን ባይነት ውሸትነትና አስመሳይነት ከዋናው ጉዳያችን ከዋናው መንገዳችን ውጭ ቢያደርጉን አይደንቅም፡፡ ዋናው ጉዳያችን ግን እነሱም ጋ ጥፋት/ጥሰት አለ ብለን የእኛን ስህተት፣ ጥፋትና ጥሰት ማደባበስና መመረቅ አይደለም፡፡ ዕድሜ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን እንጂ የእነሱ ነገር ከመንገድ አያወጣንም፡፡

አነሰም በዛም ከፋም ለማም የኢትዮጵያ የራሷ የለውጥ ሒደት ያፈራውና የጎለበተው (ገና ብዙ የሚቀረውም) ኮሚሽኑ የፕሬስ ነፃነትን ቀንም ከፍርድ/ክስ በፊት የእስራትንም ጉዳይ በተለያዩ አጋጣሚዎችና አቅጣጫዎች እያየ አሳይቶናል፡፡ ዝም ብሎ ድፍን መግለጫ ሳይሆን የዘንድሮውን (2024) የፕሬስ ነፃነት ቀን አከባበር/ክብር፣ በተለይም ከሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 29(5) አንፃር እንዲታይ ከዚህ አኳያ የሚታይ፣ የሚያቃጥልና የሚያንገበግብ ችግር እንዳለብን አሳስቦናል፡፡ ይህ ምን ማለት ነው? የተጠቀሰውን የሕገ መንግሥት ድንጋጌ ማየት ነው፡፡ ‹‹በመንግሥት ገንዘብ የሚካሄድ ወይም በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለ መገናኛ ብዙኃን የተለያዩ አስተያቶችን ለማስተናገድ በሚያስችለው ሁኔታ እንዲመራ ይደረጋል፤›› ይላል፡፡ በዚህ ሕገ መንግሥታዊ
የሃይማኖት ጉዳዮችን በሚመለከት እየተረቀቀ ባለው አዋጅ ላይ ቅሬታ ቀረበ
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

የሃይማኖት ጉዳዮችን በሚመለከት እየተረቀቀ ባለው አዋጅ ላይ ቅሬታ ቀረበ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የወንጌል አማኞች ካውንስል በተናጠል ለሰላም ሚኒስቴር በላኩት ደብዳቤ፣ አዲስ በመረቀቅ ላይ ያለው የሃይማኖት ጉዳዮች አዋጅ ላይ ያላቸውን ቅሬታ አሰሙ፡፡

የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትና የወንጌል አማኞች ካውንስል ረቂቅ አዋጁ ባይደርሳቸውም፣ ከዚህ ቀደም የአዋጁን መንፈስ በቃል በተረዱት መሠረት ሊካተቱ ይገባቸዋል ያሏቸውን ምክረ ሐሳቦች፣ አስተያየቶችና ቅሬታዎች ለሰላም ሚኒስቴር መላካቸውን ሪፖርተር የደረሰው መረጃ ያመለክታል፡፡   

የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ሚያዝያ 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሰላም ሚኒስቴር በላከውና ሪፖርተር የተመለከተው ምክረ ሐሳብ፣ ረቂቅ አዋጁ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን በዘመናት ትግል ለማረጋገጥ እየሞከሩ ያሉትንና በሕገ መንግሥቱ የተደነገገውን የዜጎች እኩልነትና የሃይማኖት ነፃነት መብቶችን የሚጥስ፣ ሙስሊሞች በዓለም አቀፍ ሕግ የተቀመጠላቸውን የሃይማኖት ነፃነትና ሰብዓዊ መብቶች የሚገረስስ ሆኖ አግኝቼዋለሁ ብሏል፡፡ 

‹‹መንግሥት፣ የመንግሥትን ከሃይማኖት የመለያየትና የዜጎችን ሃይማኖታዊ ነፃነትና እኩልነት መብት መርሆዎች ዝርዝር ለመደንገግ የጀመረውን እንቅስቃሴ እናደንቃለን፡፡ ሆኖም ለረቂቁ ግብዓት የሚሆኑ ውይይቶች እንደሚኖሩ በመጠበቅ ላይ ባለንበት ወቅት መጀመሩን ባላወቅነው ረቂቅ ላይ ለመወያየት ሚያዝያ 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በሰላም ሚኒስቴር መጋበዛችን ቅሬታ ፈጥሮብናል፤›› ብሏል፡፡ 

ምክር ቤቱ የረቂቁን ቅጂ አለማግኘቱን አስታውቆ፣ ይህ ባልሆነበት አስተያየቱን መጠየቁ ለሚያቀርበው ግብዓት ተገቢውን ትኩረት እንዳልተሰጠና ለይስሙላ መሆኑን የሚያሳይ ሆኖ አግኝቼዋለሁ በማለት ገልጿል፡፡ ምክር ቤቱ አስተያየቱን በጽሑፍ እስኪሰጥ ሳይጠበቅ የፍትሕ ሚኒስቴር ባልደረቦች ከቀናት በኋላ ወደ ክልል ከተሞች ለውይይት ማቅረብ እንደሚጀምሩ መግለጻቸውንም ጠቁሟል፡፡ በተያዘው የግንቦት ወር አጋማሽ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ፍትሕ ሚኒስቴር ረቂቁን ለማቅረብ ማቀዱን ገልጿል፡፡

ረቂቁ የሃይማኖቶችንና የሃይማኖት ተከታዮችን እኩልነት እንዳይረጋገጥ የሚያደርግ፣ የእስልምና መሠረታዊ አስተምህሮዎችን ከግምት ያላስገባ፣ ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ከሃይማኖቱና ከዜግነት ተሳትፎው እንዲመርጥ የሚያስገድድ፣ ለመንግሥት በሃይማኖት ውስጥ ያልተገባ ተቆጣጣሪነት የሚሰጥ መሆኑን በመግለጽ ምክር ቤቱ ቅሬታውን አቅርቧል፡፡

ረቂቁ የያዛቸውን ዝርዝር ጉዳዮች በሚመለከትም ሃይማኖታዊ ምልክቶችን እንደ የቤተ እምነቱ አስገዳጅ ሕግጋቶች ልዩ ሁኔታዎችን መደንገግ ሲገባው ሃይማኖታዊ መገለጫዎችን ሙሉ በሙሉ ከትምህርት ቤትና ከሥራ ገበታ የሚያስወግዱ ድንጋጌዎችን መያዙ፣ እንዲሁም የሙስሊም ሴቶችን ሰብዓዊ መብት በግልጽና በጥቅሉ የሚጥስ መሆኑን እንደተመለከተ ምክር ቤቱ አስታውቋል፡፡

በተጨማሪም በትምህርት፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ የጋራ አምልኮ ተግባራትን መከልከል፣ ሙስሊሙን ማኅበረሰብ ከእምነቱና ከሥራው ወይም ከእምነቱና ከትምህርቱ እንዲመርጥ የሚያስገድድ መሆኑ፣ እንዲሁም አምልኮን ከተፈቀደለት ቦታ ውጪ ማከናወን መከልከሉ፣ የእምነት ነፃነት መብቶች አተገባበር ላይ ጫና የሚያሳድር መሆኑን ገልጿል፡፡ 

የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን ሐሳብ የሚጋራ ደብዳቤ ዓርብ ግንቦት 2 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሰላም ሚኒስቴር የላከው ደግሞ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ነው፡፡ ካውንስሉ ረቂቅ አዋጁ አባላቱን በተመለከተ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1208/2012 የሚቃረን መሆኑን ገልጾ፣ ሕገ መንግሥታዊ የሆኑ የእምነትና የሃይማኖት ነፃነት መብትና ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብትን የሚመለከት በመሆኑ፣ ረቂቁን ለማየት እንዲሰጠው ቢጠይቅም እንዳልተሰጠው አስረድቷል፡፡

ረቂቁ በቤት ውስጥ የሚደረግን አምልኮና የአደባባይ ስብከትን የሚከለክል መሆኑን ካውንስሉ ከሰላም ሚኒስቴርና ከፍትሕ ሚኒስቴር ጋር በነበረው ውይይት ወቅት በተደረገለት ገለጻ መረዳቱን በመግለጽ፣ ይህም በቀጥታ የወንጌል አማኞችን የሚነካና ሕገ መንግሥታዊ መሠረት የሌለው መሆኑን አስታውቋል፡፡

በሕገ መንግሥቱ መሠረት ዜጎች የአምልኮ ሥርዓት ለመፈጸም በመንግሥት አካል የግድ መመዝገብ የማያስፈልጋቸው ቢሆንም፣ በረቂቁ ውስጥ ግን የነፃነቱ ሰጪና ነሺ የምዝገባው መኖር አድርጎ ማስቀመጡ ትክልል አለመሆኑን፣ እንዲሁም ከመፅደቁ በፊትም ካውንስሉ እንዲስተካከሉ በደብዳቤ የጠየቃቸው ጉዳዮች እንዲስተካከሉ አሳስቧል፡፡

የሁለቱን የእምነት ተቋማት ምክረ ሐሳብ፣ አስተያየትና ቅሬታ አስመልክቶ የሰላም ሚኒስቴር ምላሽና አስተያየት ለማካተት የተደረገው ተደጋጋሚ ጥረት አልተሳካም፡፡

The post የሃይማኖት ጉዳዮችን በሚመለከት እየተረቀቀ ባለው አዋጅ ላይ ቅሬታ ቀረበ first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by Faris Mushaga
አገርን ከቀውስ ውስጥ ማውጣት ብሔራዊ አጀንዳ ይሁን!
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

አገርን ከቀውስ ውስጥ ማውጣት ብሔራዊ አጀንዳ ይሁን!

የአገራቸው መፃኢ ዕድል የሚያሳስባቸው በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ የሚኖሩ ወገኖች፣ በየቀኑ የሚሰሟቸው ማቆሚያ ያጡ ልብ ሰባሪ የግጭትና የጦርነት ዜናዎች እንቅልፍ ይነሷቸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት ማንኛውም ዓይነት ጥረት ተደርጎ አገራቸው ከገባችበት ቀውስ ውስጥ ትወጣ ዘንድ፣ በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችና መድረኮች ግጭት ወይም ጦርነት ይብቃ እያሉ ነው፡፡ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚኖረው ሕዝብም በአገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሰላም እንዲሰፍን እየተማፀነ ነው፡፡ ባለፈው ሰሞን ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ተገናኝተው የመወያየት ዕድል የገጠማቸው የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎችን የወከሉ ወገኖችም፣ አገራቸው ከግጭት ማዕበል ውስጥ ወጥታ ዘለቄታዊ ሰላም እንዲሰፍን ሲያሳስቡ ተደምጠዋል፡፡ በኢትዮጵያ ምድር ከነገሠው ፅኑ ድህነት በተጨማሪ የሰላም ዕጦት ሕዝባችንን ከማሰቃየት አልፎ፣ ነገን በተስፋ ለመቀበል ከመዘጋጀት ይልቅ ምን ይመጣ ይሆን የሚል ሥጋት ፈጥሮበታል፡፡

አሁን ዋነኛ ጥያቄ መሆን ያለበት ኢትዮጵያ ከገባችበት አደገኛ አረንቋ ውስጥ ወጥታ ሕዝቧ ዕፎይ እንዲል ምን መደረግ አለበት የሚለው ነው፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ አትፈርስም›› እየተባለ መፈክር ማሰማትም ሆነ ቀና ቀናውን ብቻ በማሰብ ባለህበት እርገጥ የትም አያደርስም፡፡ በየቀኑ በተለያዩ አካባቢዎች በሚካሄዱ ግጭቶች፣ ጦርነቶችና ጭካኔ የተሞላባቸው ጥቃቶች የንፁኃን ደም እንደ ጎርፍ እየፈሰሰ ነው፡፡ ይህንን ዓይነቱን አደገኛ ሒደት ማስቆም ካልተቻለ የኢትዮጵያ ትንሳዔ ሳይሆን መፍረስ ነው የሚታወጀው፡፡ ይህንን ዘግናኝና ሲሰሙት የሚያስደነግጥ እውነታ ከልብ ተቀብሎ ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ብሔራዊ አጀንዳ ያስፈልጋል፡፡ ኢትዮጵያ በአገር በቀል የግጭት አፈታትና የሽምግልና ባህሎች የታደለች ስለሆነች፣ ለአገር እናስባለን የምትሉ በሙሉ ግጭት ከማጋጋልና የዳር ተመልካች ከመሆን ተላቃችሁ የሚፈለግባችሁን ኃላፊነት ተወጡ፡፡ አገር አንዴ ካመለጠች እንደማትገኝ ተገንዘቡ፡፡

የጥንቶቹ ኢትዮጵያውያን በጨቋኝ ገዥዎች መዳፍ ውስጥ ሆነው ሳይቀር አገራቸውን ከውጭ ወራሪዎችና ተስፋፊዎች መከላከል የቻሉት፣ ለአገራቸው በነበራቸው ጥልቅ ፍቅርና የአርበኝነት ስሜት እንደነበረ ብዙ የተባለበት ነው፡፡ ታላቁን ፀረ ኮሎኒያሊስት የዓድዋ ድል የተጎናፀፉት ከምንም ነገር በላይ አገራቸውን በማስቀደማቸው ነበር፡፡ ለዓለም ጥቁር ሕዝቦችና ለተገፉ ጭምር ተምሳሌት የሆኑት ከአገራቸው በፊት ራሳቸውን መስዋዕት ለማድረግ የቆረጡ ስለነበሩ ነው፡፡ ከገዥዎች ጭቆና ይልቅ የእርስ በርስ ፍቅር፣ መከባበር፣ መተሳሰብና አርቆ አሳቢነት ነው ታላቁን የዓድዋ ድል ያስገኘው፡፡ በዚህ ዘመን ግን ከአገር በፊት ሥልጣን፣ ጥቅም፣ ብሔር፣ እምነትና የመሳሰሉት ተቀጥላዎች በመብዛታቸው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን የመከራ አዝመራ እያጨዱ ነው፡፡ ገለልተኛ የሃይማኖት መሪዎች፣ የአገር ሽማግሌዎችና የሰከኑ ዜጎች የሚያቀርቧቸው ሰላማዊ ጥሪዎች እየተናቁ ጦርነት ይቀነቀናል፡፡ በዚህ ሁኔታ ግን የትም መድረስ አይቻልም፡፡

በተለያዩ መስኮች የተሰማሩ ኢትዮጵያውያን በብሔር፣ በእምነት፣ በፖለቲካ አቋምና በመሳሰሉት ቢለያዩም በአገር ጉዳይ ግን አንድ መሆን ነው ያለባቸው፡፡ አገርን ከሥልጣንና ከተለያዩ ፍላጎቶች በታች ማድረግ የሚያስከትለው መዘዝ ከባድ ነው፡፡ ለዚህም ነው በሥልጣን ላይ ያለው ብልፅግና ፓርቲ፣ ተፎካካሪ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የዴሞክራሲ ተቋማት፣ ቤተ እምነቶችና የአገር ጉዳይ የሚመለከታቸው በሙሉ ግጭቶችን የሚያስቆሙ አማራጮች ላይ ማተኮር ያለባቸው፡፡ አገርን በመምራት ላይ ያለው መንግሥት ከፍተኛ አደራ ስላለበት በተቻለ መጠን ለዘለቄታዊ ሰላም መስፈን በግንባር ቀደምነት መሠለፍ ይጠበቅበታል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች አኩርፈው ትጥቅ ያነገቡ ወገኖችም ለሰላም መስፈን የድርሻቸውን ሊወጡ ይገባል፡፡ ከአንድ ጦርነት ወደ ሌላው ጦርነት እንደ ዘበት የሚገባበት ደም ፍላት፣ ከዕልቂትና ከውድመት የዘለለ ምንም ፋይዳ እንዳልነበረው የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ህያው ምስክር ነው፡፡

የኢትዮጵያ ልማትና ዕድገት የሚገኘው ከሰላም እንጂ ከጦርነት እንዳልሆነ ማንም በቀላሉ የሚገነዘበው ጉዳይ ነው፡፡ ጦርነት ንፁኃንን ሲፈጅ፣ ንብረታቸውን ሲያወድም፣ አካላዊና ሥነ ልቦናዊ ጉዳት ሲያስከትልባቸው፣ የአገርን ኢኮኖሚ ሲያደቅና መቅኖ ቢስ ሲያደርግ ነው የሚታወቀው፡፡ በትግራይ፣ በአማራ፣ በአፋር፣ በኦሮሚያ፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላና በተለያዩ ሥፍራዎች በርካቶች አልቀዋል፣ ከፍተኛ የአገር ሀብት ወድሟል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተለይ በአማራና በኦሮሚያ ክልል በሚካሄዱ ውጊያዎች አገር ሰላም አጥታለች፡፡ ዜጎች ከቦታ ወደ ቦታ ተንቀሳቅሰው መሥራት ካለመቻላቸውም በላይ፣ ምርቶችን ወደ ገበያ ማውጣት በማቃቱ ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ተከስቷል፡፡ ሰላም ጠፍቶና ድህነት ተንሰራፍቶ መኖር አልበቃ ብሎ የአገር ህልውና ዋናው ሥጋት ሲሆን፣ ሰከን ብሎ ተነጋግሮ የጋራ አገራዊ መድረክ ለመፍጠር ዳተኛ መሆን መዘዙ ከሚታበው በላይ ነው የሚሆነው፡፡

ማንም ሆኑ ማን የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ በሙሉ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ደኅንነትና ጥቅም፣ ሰላም፣ ልማት፣ ዕድገትና የወደፊት ብሩህ ተስፋ የሚጠቅም ሐሳብ ካላቸው ይደመጡ፡፡ በኢትዮጵያ ምድር በእኩልነት ለመነጋገር የሚያስችል የጋራ መድረክ ተፈጥሮ፣ ሁሉም ብሔራዊ ጉዳዮች ላይ በነፃነት እንዲመከርባቸው ዕድሉ ይመቻች፡፡ ለኩርፊያ የማያበቁ የሐሳብ ልዩነቶች እየተለጠጡ እርስ በርስ መጋደልና አገር ማውደም ይቁም፡፡ ከማንኛውም ሥልጣን፣ ጥቅምና ፍላጎት በላይ ለአገር ህልውና ቅድሚያ ተሰጥቶ ለንግግርና ለድርድር በሩ ወለል ብሎ ይከፈት፡፡ ልዩነትን በሕጋዊና በሰላማዊ መንገድ አለማስተናገድ ያተረፈው ነገር ቢኖር ዕልቂትና ውድመት ብቻ ነው፡፡ የሐሳብ ልዩነት ለንግግርና ለድርድር መተው ሲገባው፣ እንደ ዘመነ መሣፍንት እርስ በርስ መፋጀት ለዚህ ዘመን የሚመጥን ተግባር አይደለም፡፡ ይልቁንም የተለያዩ ሐሳቦች ተፋጭተው ለአገር የሚጠቅሙ ተግባራት ይከናወኑ፡፡ ለዚህ ደግሞ አገርን ከቀውስ ውስጥ የሚያወጣ ብሔራዊ አጀንዳ ላይ ይተኮር!

The post አገርን ከቀውስ ውስጥ ማውጣት ብሔራዊ አጀንዳ ይሁን! first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by በጋዜጣዉ ሪፓርተር
ድንጋጌ አማካይነት አገር የተሰጠውን የቤት ሥራ አደራና ግዳጅ ምን ያህል ተወጥቶታል? ወይስ አድበስብሶታል? ወይስ ሸውዶታል? ወይስ የሚያበረታታ ሥራ አለ? የፕሬስ ነፃነትን ቀን ከሌሎች መካከል እነዚህን ጥያቄዎች እያነሳን የምንነጋርበት፣ የምንመራመርበት፣ የምንፈታተሽበት ቀን ነው፡፡ አገራችን ቢያንስ ቢያንስ በቲዮሪ ደረጃ ፐብሊክ ብሮድካስቲንግ የሚባል ተቋም ታውቃለች፡፡

የሕገ መንግሥቱ የአንቀጽ 29/5 ቃልና ድንጋጌ በመንግሥት ቁጥጥር ሥር የሚካሄድ፣ ወይም በመንግሥት ቁጥጥር ሥር ያለ›› የሚለው/ያለው የመገናኛ ብዙኃን ዓይነት ‹‹ፐብሊክ ብሮድካስተር›› ሆኗል ወይ? ንግግር የማይረግበት ራሱ ንግግርን የሚፈራ ጥያቄ ነው፡፡ ሌላው ቀርቶና የሚገርመውም፣ ከሕግ በላይ ሆነውና ሕግ ጥሰው ገዥ ፓርቲዎች በባለቤትነት ያቋቋሟቸው የመገናኛ ብዙኃን እንደነበሩ እያወቅን፣ የግል ሚዲያ ብቻ ሳይሆን የመጀመሪያው የግል ሚዲያ እስከመባል ደረሰ መረን የለቀቀ ማናለብኝነት ውስጥ ከነበሩት ከእነዚህ ሚዲያዎች መካከል ውስጥ ብዙዎቹን ሌሎቹም ዛሬ የመንግሥት/የሕዝብ ሚዲያ መባል የበቁበትን ታሪክ/ሒደት ማንም አይናገርም፣ አልነገረውም፡፡ የነፃነት የመብት በዓል ስናከብር ከምንጠያየቃቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ ይህንን ጉዳይ ነው፡፡

ጥያቄው ደግሞ እነዚህ የፓርቲ ሚዲያዎች እንዴት አድርገው ሕጋዊ ሆኑ? (የሚዲያ ሕጉ ያኔም ሲቋቋሙም ሆነ ዛሬም የፓርቲ የሚዲያ ባለቤትነት አይፈቀድም) የሚለው ብቻ ሳይሆን፣ ከመንግሥት ሚዲያነት ወደ ፐብሊክ ሚዲያነት ሽግግር ተደረገ ወይ? ማለትም ስለሆነ ጭምር ነው፡፡ በዚህም ጉዳይ ሆነ በሌሎችም ይህን ጉዳይ የሚገዛ ሕግ አለ ወይ?  የዚህ ጉዳይ/ዘርፍ የዓይን ብርሃንና የእግር  መንገድ ሆኖ የሚያገለግል ሕግና ተቋም አለ ወይ? በቂ ነወ ወይ? መሻሻል የሚገባው አለው?  አዲስ ሕግ ሊወጣለት መሻር ያለበት ሕግ አለን? እነዚህን ሁሉ በዓል ስናከብር ይቆረቁረናል ያንገበግበናል የምንለውን ጉዳይ ስናነግሥ መጠየቅ ያለባቸው ጥያቄዎች ናቸው፡፡ እንዲህ ያለ የተሟላ ሕግ መኖር አንዱ ጉዳይ ነው፡፡ ይህን የመሰለ ከበላዩ ሌላ ጌታ የሌለው ሕግ አለሁላችሁ ይለናል ወይ? የመጀመሪያው ጥያቄና ከዋስትናዎቹ መካከል አንዱ ነው፡፡ ይህ ብቻ ግን አይደለም፡፡ ሁልጊዜም፣ በዓል ስናከብርም ሆነ በ‹‹አዘቦት›› ቀን ‹‹ሥራ›› ስንሠራም ሌላ መጠየቅ ያለበት ምትክ የሌለው ጉዳይ አለ፡፡ እንደተባለው የሕጉ አለሁላችሁ ባይነት በአፈጻጸምም ሆነ በሌላ ምክንያት ቢፈዝና ቢጓደል ለሕጉ ጥበቃ የሚያደርግለት ዕውናዊ መተማመኛ የሚሰጠውን ዴሞክራሲ አደላድለናል ወይ? ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን በተለይ በአሁኑ ጊዜ መጠየቅና ቅድሚያ መስጠት ያለብን ነገር ይህንን ነው፡፡ የምንነጋገረው ከሌሎች መካከል ስለፕሬስ ነፃነት ቀን ነውና የዚህ ባለጉዳይ ሁሉ በተለይም የሚዲያዎች ተቀዳሚ ተግባር የፕሬስ ነፃነትን፣ ሐሳብን የመግለጽና የሚዲያ ነፃነታቸውን የሚያጎናፅፋቸው ሰላምና ዴሞክራሲ እንዲደላደል፣ ሥር እንዲይዝና እንዲፀና መታገላቸውን የመጀመሪያው አጀንዳቸውና ጭንቅ ጥባቸው ማድረግ አለባቸው፡፡

ስለነፃነት ስለመብት፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ አሁን (አፕሪል 25 ስለተከበረው ከክስ በፊት ያለመታሰር ቀን) በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 17 ስለተደነገገው የነፃነት መብት ስናወራ ዋናው ጥያቄ እንዲህ ያለ ሕግ አለ ወይ ብቻ አይደለም፡፡ ሕጉ ለዚያውም በሕገ መንግሥት ደረጃ በሕግ ከተደነገገው ሥርዓት ውጪ ማንኛውም ሰው ወንድም ሆነ ሴት ነፃነቱን/ነፃነቷን አያጣም/አታጣም፣ ማንኛውም ሰው በሕግ ከተደነገገው ሥርዓት ውጪ ሊያዝ፣ ክስ ሳይቀርብበት ወይም ሳይፈረድበት ሊታሰር አይችልም ይላል፡፡ ይህ በ1987 ነሐሴ የወጣ ሕግ ነው፡፡ ከዚያ በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ ከ1945 ዓ.ም. ጀምሮ ከ1923ቱ ሕገ መንግሥት ጋር የአገር የበላይ ሕግ አካል በሆነው የፌዴራል አክት በሚባል ሕግ መሠረት፣ ‹‹የቆመውን ሕግ በመጣስ ወንጀል በመሥራት ላይ ካልተገኘ በቀር ደንበኛ ባለሥልጣን ካላዘዘ ማንኛውም ሰው መያዝ ወይም መታሰር የለበትም…›› የሚል የሕግ መተማመኛ ነበረን፡፡ እንዲህ ያለ ሕግ አለን ወይ ተገቢ ጥያቄ ነው፡፡ መብታችንና ነፃነታችን የሕግ መተማመኛ ይሻሉ፡፡ ይህ ሕግ ሺሕ ጊዜ የተሟላ ቢሆንም፣ መጀመሪያ ግን ከበላዩ ሌላ ጌታ የሌለው ሁሉም የሚያከብረው መንግሥት ብቻ ሳይሆን ጉልበተኛም የሚገዙለት/ሕግ ነው ወይ? መመለስ ያለበት የማይናቅ ጥያቄ ነው፡፡

ይህን ጥያቄና መተማመኛ በአዎንታዊ መመለስም ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ ድንገት ወይም ከተቋም ግንባታችን ፍጥርጥር የተነሳ የሕጉ አለሁላችሁ ባይነት ቢፈዝና ቢጓደል ወይም ድንገት ውሸት ቢሆን ለሕጉ ጥበቃ የሚያደርግለት እውነተኛ መተማመኛ የሚሰጥ ዴሞክራሲ አደልድለናል ወይ? ጋዜጠኞች፣ ሚዲያዎች በግንባር ቀደምትነትና መጀመሪያ ገለልተኛ ተቋማት የየትኛውም ቡድን ተቀጽላ ወይም ንብረት ያልሆኑ ተቋማት እንዲገነቡ፣ በሕግ፣ በበላይ ሕግ የተደነገጉ መብቶች ከእርጥባን በዘለለና ከጉልበተኛ ጥቃት ነፃ በሆነ ደረጃ መኖር ደረጃ ላይ መድረሳቸውን የሚያረጋግጥ ሥራ አለን? ወይም ሠርተናል ወይ? ብለው ለዚህ መትጋትና መታገል አለባቸው፡፡ የመናገርና ሐሳብን የመግለጽ ነፃነታችንን የሚያጎናፅፈንን ሰላምና ዴሞክራሲ ሥር እንዲያዝና እንዲፀና የመታገል ሥራ፣ በተለይም ገና ለዚህ ዓይነት ጉዞ አዲስ ለሆነ አገር ከባድ የመሰናዶ ሥራ ይጠይቃል፡፡ የቀደመው አፈናና ጥርነፋ በመቅረቱ ጭንቅ ጥብ ውስጥ የገባው፣ በተለይም በተጠቁ ኃይሎች ከሰላማዊና ከሕጋዊ መንገድ ውጪ የሆነ ትግል የሚገዳደረው የሕግ ማስከበር ተግባር ተቋማትን ከማሻሻል፣ የሰው ኃይሉን ንቃትና ግንዛቤ ከመለወጥ ጋር የሚሠራ በመሆኑ ጭምር የሚታየው የመንግሥት ልዩነት ጭምር ያስከተለው ዴሞክራሲ ገና ሥርዓታዊ አልሆነም፡፡

ዋናው ተግባራችን የሆነውን ይህን ግዳጅና አደራችንን የተገኘውን ዴሞክራሲ የግርግር መደገሻ አድርገን እንማግጥበት ብንል፣ በተለይም በሚኝበት ደረጃ በቀላሉ ይሰበርና መራራ ፅዋ ያስጠጣል፡፡ መብትና ነንነት ኃላፊነት አለበት፣ ኃላፊነቱም የሚጠይቀውን ጨዋነትና ሥነ ምግባር ይፈልጋል የሚባለው ሁልጊዜም እውነት ነው፡፡ በተለይ ወደ ዴሞክራሲ በሚደረግ ጉዞ ወቅት ይህ እጅግ በጣም እውነት ነው፡፡ የአገራችን የዴሞክራሲ ትግል በተለይም ጋዜጠኞችን፣ በተለይም ታጋዮችን ‹‹እታለም (ወይም ወንድም ዓለም) ሥሪው ቤትሽን›› የሚሉት በዚህ ምክያት ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ሰላምና ዴሞክራሲ ሥር እንዲይዝና እንዲፀና መታገል በሰላማዊና በሕግ ባልተከለከሉ መንገዶች ሐሳብን ማፋጨትና ሕዝብን መሳብ እንጂ፣ ዴሞክራሲን ‹የኖህ መርከብ› የሚያሰኘው የተለያዩ ፍላጎት ያለበት መሆኑን መነሻ አድርጎ መርከቡን በጥይትም፣ በመጥረቢያም፣ በቆንጨራም፣ በገጀራም መፍለጥና መሸንቆር የማይፈቀድበት፣ የተከለከለበት ሥርዓት የመሆኑ ቋንቋና ወግ አገራችን ገና አዲስ ነው፡፡ ሁልጊዜም አዲስ  ሆኖ መኖር የለበትም፡፡  

‹‹አዲስ››ነታችን ደግሞ በጣም የሚገርም ነው፡፡ ዴሞክራሲ ይቋቋም ማለት መሰናዶ ይጠይቃል፡፡ ዝም ብሎ ይሁን ቢሉት አይሆንም፡፡ በአዋጅ፣ በምርቃት፣ በፀሎት፣ በስለት አይመጣም፡፡ ዴሞክራሲ ማለት ከሌሎች መካከል የቡድኖች መንግሥታዊ ገዥነት ከነፃና ከትክክለኛ ምርጫ የሚመነጭበት፣ አዲስ፣ ከዚህ በፊት ያልነበረ አዲስ ምዕራፍ ይከፈት ማለት ነው፡፡ ይህን ለማድረግ ገና ሲጀመር የምናማርጣቸውን ቡድኖች (ፓርቲዎች) መኖር ይፈልጋል፡፡ ይህ ራሱ ገና ‹‹ዘንቦ ተባርቆ›› የሚያሰኝ ሥራ አለበት፡፡
የምናማርጣቸው ፓርቲዎች ሁሉ የተወሰነ የዴሞክራሲያዊ አመለካከትና የድርጅት አኗኗር መለኪያን ያለፉ እንዲሆኑ ይፈለጋል፣ ግዴታም ነው፡፡ ፓርቲዎች፣ የፖለቲካ ታጋዮች ከጫካ/ከበረሃ ንቃትና ግንዛቤ ሳይወጡ፣ ወደ ሕጋዊ ሰላማዊ ተፎካካሪዎች ሳይለወጡ፣ እንንዲህ ያለ የሠለጠነና የሰከነ ትግል የሚጠይቀውን ምግባርና ባህሪይ ሳይዙ፣ ጥይት እየተኮሱ፣ ቦምብ እየጣሉ፣ ሰው እያገቱ፣ ከሌሎች መካከል ስለነፃነት መብት ያለ ሕግ፣ ያለ መያዝና ያለ መታሰር መብት መታገል ምን ትርጉም አለው?

ይህ ማለት ይህ ሁሉ እስኪሟላ ድረስ የኢትዮጵያ መንግሥት ያለ ሕግ መያዝ፣ ማሰር በጊዜ ቀጠሮ ‹‹አመሉ መቀጠል›› የፖሊስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝን ጥሶ የያዘውን ሰው ላለመሳቀቅ እንቢ ማለት ይፈቀዳል ማለት አይደለም፡፡ የተረጋጋ የኑሮ ጊዜን ከቀውጢ ወይም የርብርብ ጊዜ ለይተው ሳያዩ ዝም ብለው ‹‹ስለመብትና ነፃነት›› እኝኝ ከሚሉት ጋር ባልስማማም፣ የመንግሥት ሕግ አክባሪነት ግዴታው ግዳጁና ተግባሩ መሆኑን አውቃለሁ፣ የምንታገለውም ለዚሁ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ለሕግ መከበር እንቅፋት እየሆኑ ይልቁንም ሕገወጥነትን፣ አመፅን፣ ወንጀልን፣ መብት መጣስን፣ አገር ማውደምን የትግል መሣሪያ እያደረጉ፣ የትጥቅ ትግልንና ጉልበትን/ኃይልን ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ የትግል መሣሪያ አድርጎ ይዞ ስለሰላምና ዴሞክራሲ ግንባታ ማውራት ውሸት ነው፡፡

መልካም ዓላማ፣ ሰናይ ዓላማ፣ የተቀደሰ ግብ ወይም ‹‹ጉድ ኮዝ›› የሚባል ነገር፣ ‹‹የሚሞትለትም›› ነገር አለ፡፡ ሰናይ ጦርነት፣ መልካም ጦርነት፣ የተቀደሰ ጦርነት ብሎ ነገር ግን ዛሬ እየቀረ ብቻ ሳይሆን፣ የድሮዎችም ይህ ስም የተሰጣቸው ትግሎች ለምን? ለምን? ለምን? ለምን? እየተባሉ ናቸው፡፡

በአዘቦት ቀንም ሆነ የትኛውን የተመድ ወይም የአፍሪካ ኅብረት የመብትና የነፃነት ቀን በምናከብርበትና በምናነግስበት፣ ስለእነዚህም ትርጉም ያለው ንግግርና ጭውውት በምናደርግበት ወቅት ሁሉጊዜም መጠያየቅ መነጋገር ያለብን ለመሆኑ ሰላማችንን አደጋ ላይ የጣለው፣ የዴሞክራሲያችንን ጉዞ አበሳ ያበዛበት ምንድነው ብለን ነው፡፡ ዋነኛው ምናልባትም ብቸኛው ምክንያት የተለያዩ ኃይሎች ፓርቲዎች ቡድኖች ግብግብ መሆኑ አይደለም፡፡ ወይም ራሱ ልዩነታችን አይደለም፡፡ ልዩነት ባላቸው፣ እኔ ልክ፣ እኔ እበልጥ በሚባባሉ ቡድኖች መካከል ያለው ግብግብ/ትግል ከሕግና ከሰላማዊ መንገድ ውጪ መውጣቱ ነው፡፡ ዴሞክራሲን የምንናፍቀው መነጋገርን ሳናውቅ ነው፡፡ ይህንን ችግር  ዳንኤል በቀለ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ዋና ኮሚሽነር ራሳቸው ባለፈው ሳምንት ከሪፖርተር ጋዜጣ ጋር ባደጉት ቆይታ ገልጸውታል፡፡ ‹‹ኢትዮጵያውያ ውስጥ የገባንበት ውጥንቅጥ ስተመለከተው ቢያንስ የተወሰኑ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ወንድሞች የሐሳብና የአስተሳሰብ ልዩነት የሰዎች መብት መሆኑን መቀበል ያቅታቸዋል…›› ብለዋል፡፡ ለዚህም ነው የማያባራ ግጭት፣ የማያባራ የሚመስል ግጭት ውስጥ የገባነው ብለዋል፡፡ ‹‹መንግሥት ኃይሉን ተጠቅሞ የሐሳብ ልዩነት ያላቸውን ሰዎች አለማጥቃት፣ ተቃዋሚ ቡድኖችም ቢሆኑ ከእነሱ የተለየ ቡድን ብለው የሚያስቡትን መንግሥትንም ሆነ ሌሎች አካላትን በሐሳብ ልዩነት የተነሳ ማጥቃታቸው መቆም አለበት፡፡ እነዚህን ነገሮች አክብሮ መኖር የሰብዓዊ መብቶች ባህል ጉዳይ ነው…›› ነው ያሉት እውነት ነው፡፡

በግልም ሆነ በይፋና በፖለቲካ መድረካችን ላይ የተለያዩና ዝርዝር ሐሳቦችን በጤናማነት የማቃረብ፣ የማፍራትና ፈልፍሎ የመረዳት ልምድ ገና አጠገባችን አልደረሰም፡፡ በየትኛውም መስክ በፖለቲካም፣ ከፖለቲካ መለስ ባሉ ጉዳዮችም ከራሳችን የተለየ ሐሳብን ለመስማት ቻይ አይደለንም፡፡ ሐሳባችን ሲተች ኩርፍያን፣ ሐሜትን መሣሪያ አድራጊዎች ነን፡፡ የተለያዩና የማይጥሙንን ሐሳቦች እንኳንስ ጥቅሜ ብሎ ማድመጥና ማቅረብ፣ የሰው መብት ነው ብሎ መስማት አንችልም፡፡ ሳይቀየሙ፣ ቂም ሳይቋጥሩ መለያየት የሚባል ነገር ገና አልገባንም፡፡ የደፈረሱና የተበላሹ ስሜቶቻችን አቃልሎና አረጋግቶ መፈራራትና ኩርፊያን ተሻግሮ፣ በጥያቄዎችና በቅሬታዎች ላይ ለመነጋገር ሳይጻፍና ተቃራኒ ሐሳቦችን ከራስ ሐሳብ እኩል እያከበሩ የሚያቀራረቡ ነገሮችን መፈለጊያ መንገድ፣ አንድም ሳይያዝ በአጠቃላይ መነጋገርን ሳያውቁ ‹‹ድንገት›› የዴሞክራሲ ታጋይ፣ የዴሞክራሲ ቀን፣ የንግግር ነፃነት ቀን፣ ወዘተ አክባሪ/አስከባሪ መሆን ከንቱ ምኞትና የማይጨበጥ ሕልም ነው፡፡ 

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊዋን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

The post ለዴሞክራሲና ለነፃነት መነጋገርን ማወቅ first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ
የኢትዮጵያ ትንሳዔ ትክክለኛ ቀኑ መቼ  ነው?
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

የኢትዮጵያ ትንሳዔ ትክክለኛ ቀኑ መቼ  ነው?

በጌታነህ አማረ

ትንሳዔ ማለት ከሞት፣ ከመከራ፣ ከችግር፣ ከሥቃይ፣ ከረሃብ፣ ከድርቅ፣ ከበሽታ፣ ከመፈናቀል፣ ከግጭትና ከጦርነት ወጥቶ ዩቶፒያ  መሆን  ማለት ነው። ‹‹ዩቶፒያ›› ማለት ደግሞ መረዳዳት፣  መፈቃቀር፣ መዋደድ፣ መከባበር፣ መተሳሰብ፣ ሰላም፣ ዕድገትና ብልፅግና ያለበት ሕይወት መኖር  እንደሆነ  ይነገራል።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ትንሳዔ አንድ ቀን እንደሚፈጸም በብዙዎች ዘንድ እምነት እንዳለ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሠረት አንዳንድ ሰዎች የኢትዮጵያ ትንሳዔ እንደተፈጸመ ነገር ግን ትንሳዔው መከወን ብቻ እንደቀረው ሲናገሩ፣  ሌሎች  ደግሞ መፈጸሚያ ቀኑ እየደረሰ እንደሆነ ይናገራሉ፡፡  ይህንንም ትንሳዔ ከሚጠባበቁት ውስጥ ትንቢተኞች፣ መንግሥትና ሐሳብ አመንጪዎች ይገኙበታል፡፡

ትንቢተኞች ኢትዮጵያ በእግዚአብሔር የተባረከችና የተቀደሰች አገር በመሆኗ ከብዙ የሰው ልጅ ፈተናና ሥቃይ  በኋላ ትንሳዔዋ እንደሚፈጸም ትንቢት እንዳለ፣ ይህም ትንቢት በቅርብ እንደሚፈጸም ይናገራሉ፡፡ መንግሥት  የእግዚአብሔር ዕርዳታ ተጨምሮበት ባጠረ ጊዜ ውስጥ በሰው ልጅ ቀን ከሌት ጠንክሮ በመሥራትና ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ትንሳዔውን ማምጣት እንደሚቻል ይገልጻል፡፡  

በሌላ በኩል ደግሞ ምሁራን ወይም ሐሳብ አቅራቢዎች  የኢትዮጵያን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብና ያለውን ምቹ ዕድል በመጠቀም ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ በኢኮኖሚው፣ በፖለቲካውና በማኅበራዊው ዘርፎች ያሉ ዕሳቤዎችን ወደ ዘመናዊ ዕሳቤዎች በመቀየር ቀላልና  ምቹ ሥርዓት ወይም ሲስተም በመፍጠር   ትንሳዔውን መፈጸም እንደሚቻል ይናገራሉ፡፡

በመሆኑም ይህንን ሁሉ ሐሳብ ወደ አንድ ስንጠቀልለው ትንቢተኞች  ትንሳዔው እንደሚፈጸም የተነገረ ትንቢት መኖሩንና በዚያ መሠረት እንደሚፈጸም፣ መንግሥት ደግሞ   ሌት ተቀን ጠንክሮ  በመሥራትና ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ትንሳዔውን ባጠረ ጊዜ ማምጣት እንደሚቻል፣ ምሁራንን ወይም ሐሳብ አመንጪዎች በሳይንሳዊ መንገድ ብዙ መልፋት ሳይጠበቅብን በቀላሉ እንደሚፈጸም፣ ከሦስት በአንዱ አካል ትንሳዔው እንደሚመጣና እንደሚከናወን የሚጠባበቀው ደግሞ ማኅበረሰቡ ነው፡፡

ከዚህም በመነሳት ስለትንሳዔው የሚያስቡ አካላት በአጠቃላይ አራት ሆኑ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህ አካላት አራት ከሆኑ ዘንዳ በመካከላቸው ያለው ግንኙነት፣ ትስስርና ልዩነት ምንድነው የሚለውን ለይተን ለማየት እንሞክር፡፡ 

 ትንቢተኞችን እያሉ ያሉት በተጻፈው ወይም በተነገረው ትንቢት መሠረት በአንድ ሰው ምክንያት ትንሳዔው ይፈጸማል የሚል ነው፡፡ ይህም ሰው  ጎዳና ተዳዳሪ፣ እረኛ፣ ገበሬ፣  ተማሪ፣ አስተማሪ፣ ምሁር፣ ተመራማሪ፣ ሠራተኛ  ወይም ደግሞ የመንግሥት ባለሥልጣን ሊሆን ይችላል የሚል ነው፡፡ በመሆኑም የእነዚህ አካላት ትንሳዔውን መጠባበቅ በሌሎች ማለትም በመንግሥት፣ በምሁራን  ወይም በሐሳብ አቅራቢዎችና በማኅበረሰቡ ውስጥ ያለውን ሐሳብ ይደግፋሉ እምነትም አላቸው ማለት ነው፡፡

የመንግሥት ሐሳብ  ከሌሎች ጋር ያለው ልዩነት ደግሞ ኑ ተደምረን አብረን ሌት ተቀን ጠንክረን በአንድነት ሠርተን የኢትዮጵያን ትንሳዔ አብረን እናብስር፣ በዚህ ሒደት የማትሳተፉ ግን አትረብሹን አርፋችሁ ተቀመጡ፣ ብትችሉ ከእኛ ጋር ተደምራችሁ አብረን እንሥራ ካልሆነ ግን እኛ የምንሠራው እናንተንም የሚጠቅም በመሆኑ በምትችሉት መንገድ  ሁሉ አግዙን የሚል ነው፡፡ ጥሪ የሚደረግላቸው ሰዎች ደግሞ ሒደቱ ረጅም፣ አድካሚና ከፍተኛ ፅናት የሚጠይቅ በመሆኑ ብዙም ተነሳሽነት ሲኖራቸው አይታይም፡፡

ምሁራንን ወይም ሐሳብ አመንጪዎችን በተመለከተ የመንግሥት ሐሳብ በውስጣቸው ጥሩና ለአገር የሚጠቅም ዕው ቀት እንዳለ ያምናል።  በዚህም መሠረት ከመንግሥት ውጪ ያሉ ምሁራንና ሐሳብ አመንጪዎችን በልዩ ሁኔታ መርጦ በማስቀመጥ እንዲያግዙት ሲያደርግ ይታያል።  ለዚህ ደግሞ እንደ ምሳሌ ሊጠቀስ የሚችለው  ገለልተኛ የኢኮኖሚ አማካሪዎች ቦርድ ነው፡፡

ነገር ግን ይህ በመሆኑ ምክንያት ከእነዚህ ከተመረጡ ኣካላት ውጪ ያሉ ምሁራንና ሐሳብ አመንጪዎች እንዳይሳተፉ  የሚያደርግ ሕግ እንዳለና ይህም ሕግ ትክክል እንዳልሆነ መንግሥት ውስጥም ከመንግሥት ውጭ የሆነ ሰው ለአገር ጠቃሚ የሆነ ፖሊሲ ወይም የፖሊሲ ሐሳብ   እስካለው ድረስ ለአገር አበርክትዎ እንዲያደርግ ዕድል እንዲሰጠውና እንዲሳተፍ መደረግ እንዳለበት ቢነገርም አሁንም ግን ሐሳብ አመንጪ ሰዎችን ለመጠቀም ያለው ሥርዓት በጣም ደካማ ይመስላል፡፡

መንግሥት ሁለጊዜ ሐሳብ አመንጭዎችንና ምሁራንን ሐሳባችሁንና ዕውቀታችሁን ደብቀችሁ የጋን ውስጥ መብራት አትሁኑ በጋዜጣ፣ በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥንም ሆነ በሌላ መንገድ ብትገልጹት እኛ እንሰማችኋለን አውጡትና አገር ትጠቀምበት ዕውቅናና ሽልማቱ ቆይቶ ይደርሳል የሚል ሐሳብ ቢኖረውም ለአገር የሚበጀው ሐሳብ ግን ከምሁራንም ሆነ ከሐሳብ አመንጪዎች አገርን ከድህነት የሚታደግ ሐሰብ በሚባለው መንገድ  እየወጣ አይደለም፡፡

ይህን ጉዳይ ስንመለከተው ሐሳብ ሲባል ለአገር ባለው አበርክቶ ልክ ይመዘናል፡፡ ትናንሽና በማይክሮ ደረጃ ያሉ ሐሳቦችን ልክ መንግሥት ባለው መንገድ ማስተናገድ ይቻል ይሆናል፡፡ ነገር ግን ትልልቅና  በማክሮ ደረጃ ያሉ ሆነው አገርን ከሥር መሠረቱ ሊቀይሩ የሚችሉ  ሐሳቦችን ግን በሚባለው መንገድ  ማውጣት አይቻልም፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሐሳቦች አገርን የመለወጥ  ኃይል እንዳላቸው ሁሉ፣ በሒደታቸው የመጣልም ኃይል ስለሚኖራቸው ከፍተኛ ጥንቃቄን የሚሹ ናቸው፡፡

ስለዚህ መንግሥት እነዚህን ሐሰቦች የሚያስተናግድበት መንገድ የተለየና ሐሳብ አቅራቢውም ሆነ ምሁሩ በሚፈልገው  መንገድና በምክክር  መሆን እንዳለበት ሊታመንበት ይገባል፡፡    የአገር ባለቤት የሆነው ማኅበረሰብ ትንሳዔው ይፈጸማል ብለው በሚያስቡትና በሚነግሩት አካላት ላይ እምነት በመጣል፣ ትንሳዔው የሚመጣበትን ቀን በከፍተኛ ጉጉትና ፀሎት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል፡፡

አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ኢትዮጵያ ድህነትና አሰቃቂ ግጭት  ያለባት አገር ስትሆን ይህንን ደግሞ ያባባሱት ከፍተኛ የዋጋ ንረት፣ ሥራ አጥነት፣ የውጭ የዕዳ ጫናና ሌሎችም ናቸው፡፡ እነዚህንም ችግሮች ለመቅረፍ መንግሥት የተለያዩ ዕርምጃዎችን እየወሰደ ይገኛል፡፡ ከእነዚህም ዕርምጃዎች ውሰጥ በዋናነት የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ፕሮግራም ይገኝበታል፡፡

ይህንንም ለማድረግ በዋናነት የተጠቀመበት ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ መከተል (Monetary Policy Tightening)፣ የመንግሥት በጀትን መቆጣጠር (Budget Control)፣  የመንግሥት ወጪዎችን መቀነስ  (Cut Spending) የግብር መሠረትን ማስፋት (Expansion of Tax Base) እና መዋቅራዊ ሪፎረም (Structural Reform) አገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሚባለው ፕሮግራም ማካሄድ ነው (በዚህ ጽሑፍ አዘጋጅ ዕይታ  አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ባለው ነባራዊ ሁኔታ  ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ
ከስቀለው ከይሰቀል ፖለቲካ ባህል መላቀቅ ስለምን ተሳነን?
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

ከስቀለው ከይሰቀል ፖለቲካ ባህል መላቀቅ ስለምን ተሳነን?

በተረፈ ወርቁ (ዲ/ን)

የዛሬ ጽሑፌን ፈር ማስያዣ ይሆነኝ ዘንድ በአንድ ገጠመኜ ለመንደርደር ወደድሁ። ከዓመታት በፊት ተማሪ በነበርንበት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ዋናው ግቢ በተለያዩ ፖለቲካዊ ጥያቄዎች የሚናጥበት ቀውጢ ወቅት ነበር።

ታዲያ የዛን ቀውጢ ሰሞን የሥነ ተግባቦት /Communication Skill/ መምህራችን የነበሩት ስምዖን ገብረመድኅን (ዶ/ር) በአንድ የትምህርት ክፍለ ጊዜያችን፣ ‹‹ያለ ምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም!›› ተብሎ የተጀመረና እርሳቸውም በተማሪነት ዘመናቸው አባል የነበሩበት የዛን ጊዜው የለውጥ ጥያቄ የነጎደበትን የእርስ በርስ መጠፋፋትና የስቀለው ፖለቲካችን ባህልን ከወቅቱ የግቢያችን ነውጥ ጋር እያነጻጸሩ አስገራሚም፣ አሳዛኝም የሆነ አንድ ገጠመኛቸውን እንዲህ አወጉን።

‹‹መሬት ላራሹ፣ ዲሞክራሲያዊ መብት ያለ ገደብ፣ የሃይማኖት እኩልነት… ወዘተ.›› የሚሉ ጥያቄዎችን በማቀንቀን የሚታወቁት የዛን ጊዜው የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ የአሁኑ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በልደት አዳራሽ ተስብስበው መፈክር በሚያሰሙበትና በማርኪሲስት ርዕዮተ ዓለም ዙሪያ በሚሟገቱበት አንድ ወቅት ላይ እንዲህ ሆነ።

በ6 ኪሎው የልደት አዳራሽ እጅግ በተሟሟቀ አብዮታዊ ስሜት፤ በአገራዊ ወኔ በሚካሄድ ስብሰባ ወቅት የዚህ ስብሰባ ተሳታፊ የሆነ አንድ ተማሪ አስተያየት ለመስጠት ፈልጎ እጁን ያወጣል፤ ተማሪው ይፈቀድለትና ወደ መድረክ ይወጣና አስተያየቱንም እንዲህ ሲል ይጀምራል፡-

‹‹… ወገኖቼ እያነሳናቸው ያሉት የለውጥ፣ የፍትሕ ያለ እና የዲሞክራሲ መብት ይከበር ጥያቄዎቻችን ተገቢ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ ነገሥታት/መንግሥታት የሚሾሙትም ሆነ የሚወርዱት በአምላክ ፈቃድ ነውና ምናልባት ሳናውቀው ከፈጣሪ ስንጣላ እንዳንገኝ…›› የስብሰባው ተሳታፊ ተማሪዎች ንግግሩን አላስጨረሱትም በአንድ ድምፅ ሆነው፣ ‹‹ይሰቀል! ስቀለው! ስቀለው!›› በሚል መብረቃዊ ጩኸትና መፈክር አዳራሹ ተናወጠ፡፡ ያ ምስኪን ተማሪም በጓደኞቹ እየተገፈታተረ ከመድረኩ እንዲወርድ ሆነ በማለት መምህራችን ስምዖን (ዶ/ር) የዛን ጊዜ የአብዮት ዘመን ትዝታቸውን በቁጭትና በኀዘን ስሜት ውስጥ ሆነው አውግተውናል።

በዛን ዘመን የሶሻሊስት አራማጆች ዘንድ፤ ‹‹ሃይማኖት ሕዝብን የማደንዘዣ ዕፅ ነው›› (Religion is an Opium) የሚለውን ፀረ ሃይማኖት የሆነ አስተምህሮአቸውን ያስታውሷል።

ይህን የመምህራችን ስምዖንን ትዝታን እንደያዝን ዛሬም ድረስ ‘ከስቀለው፤ ከመጠፋፋት ፖለቲካ’ ባህል መላቀቅ ስለምን ተሳነን በሚለው ሐሳብ ላይ አብረን ጥቂት እንቆዝም እስቲ።

ለሺሕ ዘመናት የዘለቀ የሃይማኖት አስተምህሮ ውስጥ ያለፍን፣ ገናና ሥልጣኔ የገዘፈ ታሪክና የዳበረ ባህል አለን የምንል ማኅበረሰቦች ምን ብንሆን ነው – የሃይማኖት አባትን ያህል ሰው በገመድ አንቀን ለመገደል የደፈርነው? የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አባትና መንፈሳዊ መሪ የነበሩትን የሰማዕቱን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን የጭካኔ አገዳደልን ያስታውሷል።

በተመሳሳይም የመካነ ኢየሱስ ቤተክርስቲያን ፕሬዚዳንት የነበሩት ቄስ ጉዲና ቱምሳም የኦነግ አባልና ደጋፊ ነዎት በሚል ነበር በጭካኔ በጥይት ተደብደበው የተገደሉት። የአሁኑ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስም በለውጥ/በአብዮት ስም ነበር ለሰባት ዓመታት በወኅኒ በግፍ ተግዘው እንዲማቅቁ የተደረጉት። እንዲሁም የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳሳት የሆኑት ካርዲናል ብፁዕ ብርሃነ ኢየሱስም ታስረው ነበር፡፡ 

‹‹የአፍሪካ አባት›› በሚል ጥቁሩ ዓለም የሚያደንቃቸው የአዛውንቱ የግርማዊ ቀዳማዊ  ኃይለ ሥላሴና የ60ዎቹ ኢትዮጵያውያን ሚኒስትሮች፣ ሹማምንትና አርበኞች የጅምላ ጭፍጨፋንም ልብ ይሏል። ይህን ከኢትዮጵያ አልፎ መላውን ዓለም በድንጋጤ ጭው ያደረገውን በለውጥ ስም የተወሰደ አብዮታዊ ርምጃን/የጅምላ ጭፍጨፋን አስመልክቶ በወቅቱም፤ እንደ ቢቢሲ ያሉ ዓለም አቀፍ የመገናኛ ብዙኃን፤ “What Happened to the Bloodless Ethiopian Revolution?!” ሲሉ ድንጋጤ የታከለበትን ዜናን አከታትለው ነበር።

ፖለቲካችንን ክፉኛ የተጣባው ይሄ የይሰቀልና የመጠፋፋት ባህል ዛሬም አብሮን ዘልቋል። ታቦት በቆመበት፣ ምሕረትና ይቅርታ በሚታወጅበት ዓውደ ምሕረት ላይ ቆመው፤ “…እንዴት አንድ ወንድ ይጠፋል እንደ ዳዊት ግንባሩን ብሎ የሚገድለው?!” ብለው ጦርነትን/ሞትን የሚያውጁ፣ ጥላቻን የሚሰብኩ የሃይማኖት አባቶችን ለመታዘብ የበቃንበት አስጨናቂ ዘመን ላይ መድረሳችንን ልብ ይሏል። 

እነርሱ ላም ሲያርዱ፣

እኛም ጥጃ እንረድ፣

ቢሆንም ባይሆንም፣

እጃችን ደም ይልመድ።

     ደመናው ሲደምን ይወረዛል ገደል፣

     ይዘገያል እንጂ መች ይረሳል በደል።

ላዩ ጨረቃ፤ ታቹ ጨረቃ፣

‹ደምላሽ› አለችው እናቱም አውቃ።

የሚሉ ቂምን ያረገዙ፣ የጦር አውርድ ዓይነት ስያሜዎችና ሥነ ቃሎች ያሉን ኩሩ ሕዝብ ነን። በገደምዳሜውም ቢሆን ከዕርቀ ሰላም ይልቅ ለበቀልና ለእርስ በርስ እልቂት/መጠፋፋት የቀረብን/የመረጥን ማኅበረሰብ ነን የሚለውን የመከራከሪያ ሐሳብ ሊክድ የሚደፍር ካለ… እንደው ሌላው ሁሉ ቢቀር ባሳለፍናቸው ሁለት ዓመት አንድ ሚሊዮን ወገኖቻችንን ሕይወት በከንቱ የቀጠፈውን የእርስ በርስ ጦርነት/እልቂት ማስታወስ ብቻ በቂ ይሆናል።

ያለፈውን የቅርብ ታሪካችንን ዘመን ስንፈትሽም፣ ‹‹ያለ ምንም ደም ኢትዮጵያ ትቅደም›› በሚል መፈክር የተጀመረው የ1966ቱ ለውጥ/አብዮት አፍታም ሳይቆይ፤ ‹‹አብዮት የገዛ ልጆቿን እንኳን ሳይቀር ትበላለች!›› ወደሚል አስፈሪ ፅልመት ተቀይሮ- ያለ ምንም ደም በሚል የሰላምና የዕርቅን መንገድ የመረጠ የመሰለው አብዮት፤ ‹‹የማይታረቅ የመደብ ቅራኔ ውስጥ ነን፤ እናም ወይ እኛ ወይ እነርሱ ካልጠፉ በስተቀር…›› ወደሚል ጠላትነት/ባላንጣነት ነበር የተቀየረው።

በአብዮቱ ግራና ቀኝ የተሰለፉት ኃይላት ተቀራርቦ ለመነጋገርና ለዕርቀ ሰላም አማራጭ በሩን ጥርቅም አድርገው ሲዘጉ- በኢትዮጵያ ምድር የሞት መላእክት የጥፋት ሰይፋቸውን መዘው በአራቱ ማእዘን ቆሙ። ከዚህ በኋላ በምድራችን ላይ የሆነውን ዘግናኝ እልቂት ለማወቅ የሚፈልግ እንደምንም ጨክኖና ስሜቱን ተቆጣጥሮም ቢሆን በደም የጨቀየ፤ ዘግናኝ የታሪካችንን ምዕራፍ ማንበብ ነው የሚጠበቅበት።

አሊያም በመስቀል አደባባይ ያለውን የቀይ የሽብር እልቂት/የሰማዕታት ቤተ መዘክርን ቢጎበኝ የሄድንበት የጥፋት መንገድ ምን ያህል ከባድ እንደነበርና የዛን ዘመን አስፈሪ ፅልመት በጥቂቱም ቢሆን ይከስትለታል።

ኢትዮጵያ ሀገሬ ታጠቂ በገመድ፣

የወንድ ልጅ እናት ታጠቂ በገመድ፣

ልጅሽን አሞራ እንጂ አይቀብረውም ዘመድ።

የሚለው የኢትዮጵያውያን ምስኪን እናቶችን እንጉርጉሮ መነሻውም ይኸው ዕርቅንና ሰላምን የገፋው የይሰቀል የፖለቲካ
የትግራይ ክልልን በዘጠኝ ወራት ሪፖርቱ ማካተት ባለመቻሉ ጫና እንደፈጠረበት ጤና ሚኒስቴር ገለጸ
ሪፖርተር – Ethiopian Reporter – #1 Best and reliable news source in Ethiopia (RSS)

ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia

የትግራይ ክልልን በዘጠኝ ወራት ሪፖርቱ ማካተት ባለመቻሉ ጫና እንደፈጠረበት ጤና ሚኒስቴር ገለጸ

በትግራይ ክልል በነበረው ግጭት ኮምፒዩተሮችና የኢንተርኔት ዝርጋታዎች በመበላሸታቸው የትግራይ ክልል ሪፖርት አለመላኩን፣ በዚህም ምክንያት የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ውስጥ ባለመካተቱ ጫና እንደተፈጠረበት የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የክልሉ ሪፖርት ባለመላኩ ምክንያት በሥራዎቹ ላይ ጫና ማሳደሩን፣ ወደፊት ለሚከናወኑ ተግባራት እንቅፋት እንደሚሆን የጤና ሚኒስትር ዴኤታው ደረጀ ዱጉማ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ገልጸዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የጤና፣ ማኅበራዊ ልማት፣ ባህልና ስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሐሙስ ግንቦት 1 ቀን 2016 ዓ.ም. የጤና ሚኒስቴር የዘጠኝ ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርትን ገምግሟል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ  ደረጀ ዱጉማ (ዶ/ር) በትግራይ ክልል በነበረው ግጭት ብዙ የጤና ጣቢያዎች፣ የጤና ኬላዎች፣ ኮምፒዩተሮችና የኢንተርኔት ዝርጋታዎች መበላሸታቸውን፣ እንዲሁም አብዛኞቹ የጤና ባለሙያዎች በሥራ ላይ ስላልነበሩ የሪፖርት ማቅረብ ሒደቱ ተቋርጦ መቆየቱን ገልጸዋል።

በ2016 ዓ.ም. መጀመሪያ አካባቢ ሪፖርቶችን ለመላክ የተወሰነ ሙክራ እንደነበር ለሪፖርተር የገለጹት ደረጀ (ዶ/ር)፣ ግጭቱ ከተከሰተ ጀምሮ በክልሉ ያለውን የጤና ዘርፍ የሚመለከት ሪፖርት ተልኮ እንደማያውቅ አስረድተዋል። ‹‹ይህ ማለት ግን በስልክና በተለያዩ መንገዶች ሪፖርቶችን አንወስድም ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን ትክክለኛውና በሚኒስቴሩ የዕቅድ አፈጻጸም መካተት የሚገባው ሪፖርት የሚላክበት የመረጃ ሥርዓት በኢንተርኔት ብቻ ስለሆነ ለማካተት አልተቻለም፤›› ብለዋል።

ከሁለት ወራት በኋላ ክልሉ ሪፖርቱን ለመላክ መዘጋጀቱን የገለጹት ሚኒስትር ዴኤታው፣ የሚላከው ሪፖርት ከ2016 ዓ.ም. በፊት የነበረውን አፈጻጸም ጭምር እንደሚካተትበት፣ በዋናነት እየተሠራበት ያለው ግን ከሐምሌ ጀምሮ የ2017 ዓ.ም. ሪፖርት በተሟላ መልኩ እንዲላክ ለማስቻል ነው በማለት አስረድተዋል።

በትግራይ ክልል የሚገኙ የጤና ተቋማትን ለመደገፍ ሚኒስቴሩ እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን አስመልክቶ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሻቸውን የሰጡት ደረጀ (ዶ/ር)፣ ከ400 በላይ የሚሆኑ ኮምፒዩተሮች መዘጋጀታቸውንና ሰሞኑን እንደሚሠራጩ ተናግረዋል፡፡ በወረቀት የተላኩ መረጃዎችን በማሳተም መቀሌ ከተማ መድረሳቸውንና፣ ወደ ወረዳዎቹ ለመላክ የፋይናንስ ድጋፍ መደረጉንም አስታውቀዋል።

ከትግራይ ክልል ውጪ አሁንም በግጭት ዓውድ ውስጥ በሚገኙ አካባቢዎች የኢንተርኔት አገልግሎት ባለመኖሩ ሪፖርቶች በወቅቱ እየተላኩ አለመሆናቸውን፣ ለዚህ ማሳያም በአማራ ክልል ባለው ግጭት ምክንያት 65 በመቶ የሚሆኑ የጤና ተቋማት ብቻ ሪፖርት እንደላኩ አስረድተዋል። ‹‹ሆኖም በአፈጻጸም ወደኋላ ከቀሩና ግጭት ካለባቸው አካባቢዎች ጋር በተለየ መንገድ በየሁለት ወራት እንገናኛለን፤›› ብለዋል።

ድጋፍ የሚደረገው ሪፖርቶቹን መሠረት አድርጎ በመሆኑ፣ ሚኒስቴሩም ሆነ አጋር ድርጅቶች የሚያስፈልገውን ዕገዛ እንዳያደርጉ እንቅፋት እንደሚሆንባቸው፣ ግብዓቶችን ለመላክና በአጋር ድርጅቶች የሚደገፉ ፕሮጀክቶችን ለማንቀሳቀስ፣ የሪፖርቶች በወቅቱ አለመቅረብ ችግር መሆኑን  ደረጀ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

The post የትግራይ ክልልን በዘጠኝ ወራት ሪፖርቱ ማካተት ባለመቻሉ ጫና እንደፈጠረበት ጤና ሚኒስቴር ገለጸ first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by ፅዮን ታደሰ
መከተል  (Monetary Policy Tightening) የሚደረግበት መንገድና የመንግሥት ወጪዎችን መቀነስ  (Cut Spending) የሚመከሩ አይደሉም)፡፡  

ነገር ግን ይህን  ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ ፕሮግራም   ለማከናወን አንድ ቁልፍ ነገር እንደቀረ  ይነገራል፡፡ ይህም የገንዘብ ምንጭ መጥፋት ነው፡፡ ይህንን የገንዘብ ምንጭ ለማገኘት ደግሞ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት በተለያየ መንገድ  ለማግኘት ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡ ገንዘብ ለማግኘት ደግሞ ብዙ ቅድመ ሁኔታዎች ይቀርባሉ፡፡ ከእነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች  ውስጥ ደግሞ አንዱ የብርን ከውጭ ገንዘቦች ጋር ያለውን ዋጋ ማዳከም የሚል እንደሆነ ይነገራል፡፡

ይህ ጉዳይ በነፃ የኢኮኖሚ ሥርዓት ዕሳቤ ትክክል ነው፡፡ ነገር ግን እስካሁን ድረስ በትመና (Official Exchange Rate) የቆየን የውጭ ገንዘብ ትመና ሥርዓትን ለመቀየር አሁናዊ የአገሪቷን ነባራዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ማገናዘብ ያስፈልጋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የብርን የመግዛት አቅም ማዳከም ማለት አሁን ያለውን ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ከመጠን በላይ ማጥበቅና እንዲበጠስ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ይህ ሆነ ማለት ደግሞ ይህን በጣም የጠበቀ የገንዘብ ፖሊሲ  የአገሪቷ ኢኮኖሚ መሸከም ስለማይችል ተንኮታኩቶ እንዲወድቅ ያደርገዋል፡፡

በዚህም መሠረት የውጭ ምንዛሪው ሥርዓት ለገበያው ቢተው ከመጠን በላይ በመውረድ የብር የመግዛት አቅም በመጠንከርና አሁን ካለበት ይፋዊ የምንዛሪ ተመን 57 ብር አካባቢ ምናልባትም በጣም ዝቅ በማለት ብዙ ድርጅቶችን ለኪሳራ፣ እንዲሁም አገርን ለኢኮኖሚ ውድቀት ሊዳርግ  ስለሚችል ጥንቃቄ ሊደረግበት ይገባል እላለሁ፡፡  በዚህም  የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያውን ለመፈጸም እንደ መተግበሪያ  (Application) ይጠቅማል ተብሎ ከሚታሰበውና ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት  ይገኛል ተብሎ ከሚጠበቀው ገንዘብ በላይ፣ የምሁራንና የሐሳብ አመንጪዎች ሐሳባብ የኢኮኖሚውን ማሻሻያ ለማስፈንጠርና የሚፈለገውን ግብ ለመምታት እንደ ዋና መተግበሪያ (Application) ማገልገላቸው ምንም ጥርጥር የለውም፡፡

ይህን ተግባር ላይ ለማዋል ደግሞ ፍፁም ጨዋና ሥርዓት ያለው መሆን፣  ኋላቀርና የማይጠቅሙ ሐሳቦችን መሻር  ብሎም ለተፈጻሚነቱ ቃል ኪዳን  (Hippocratic Oath) መፈጸምና በአንድነት ትንሳዔውን ነገ ሳይሆን፣ ዛሬ በመፈጸምና በመከወን የምትፈለገውን ዪቶፒያ ማምጣት ያስፈልጋል። ዛሬ ማለት ዛሬ የቆምንበት ቀን፣ ነገ ላይ ሆነን የምንጠራው ቀን፣ ከነገ በስቲያ ላይ ሆነን የምንጠራው ቀን፣ ወይም ደግሞ ሌላ ቀን ላይ ሆነን የምንጠራው ቀን ሁሉ ዛሬ ነው።  ስለዚህ የኢትዮጵያ ትንሳዔ ትክክለኛ ቀኑ ዛሬ ነው፡፡

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው የኢኮኖሚና የባንክ ባለሙያ ሲሆኑ ከ16 ዓመታት በላይ የባንክ ሙያ ልምድ ሲኖራቸው፣ ጽሑፉ የእሳቸውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡ 

The post የኢትዮጵያ ትንሳዔ ትክክለኛ ቀኑ መቼ  ነው? first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ
ታሪካችን መራር ሐቅ አካል ነው…።

ግን… ግን… ደግሞ፤

በአንፃሩ በዚህ ሁሉ ውስጥ እንደ ማኅበረሰብ እንዴት አብረን ቆየን ብለን ብንጠይቅ፤ ‹‹ይቅር ለእግዚአብሔርና ዕርቅ ደም ያደርቅ!›› የሚል በተግባር የሚገለጽ ሥነ ቃል ያለን ሕዝብ መሆናችንንም መዘንጋት ያለብን አይመስለኝም። ለአብነትም፣ ከጥቂት ዓመታት በፊት የጋሞ አባቶች እንደ ባህላቸው ሣር በጥሰው ሄደው ጫፍ ላይ የደረሰን የእልቂት ድግስን በዕርቀ ሰላም እንዲፈታ ያደረጉበትን ክስተት ማስታወስ ይገባናል።

እንዲህ ዓይነቱ የዕርቀ ሰላም ባህል ከሰሜን ኢትዮጵያ ጫፍ እስከ ደቡብ፤ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ ኢትዮጵያ የተንሰራፋ ነው። አሁን ላለንበት የሰላም እጦትና የይሰቀል ፖለቲካዊ ባህላችን ለፈጠረው ቀውሶቻችን መፍትሔ ለመሻት እነዚህን አገራዊ እሴቶቻችንን በቅጡ መፈተሽ ያለብን ይመስለኛል። አበቃሁ!

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብና በምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት በዋና ጸሐፊነት ሆነው ያገለገሉ፣ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ በጥናትና ምርምር ዘርፍ ከፍተኛ ተመራማሪ፣ የታሪክና የቅርስ አስተዳደር ባለሙያ፣ እንዲሁም በዩኒቨርሳል ፒስ ፌዴሬሽን (Universal Peace Federation – UPF) የሰላም አምባሳደር ሆነው እያገለገሉ ሲሆን፣ ጽሑፉ የእሳቸውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

The post ከስቀለው ከይሰቀል ፖለቲካ ባህል መላቀቅ ስለምን ተሳነን? first appear on ሪፖርተር - Ethiopian Reporter - #1 Best and reliable news source in Ethiopia and is written by አንባቢ
የተመድ ጠቅላላ ጉባኤ የፍልስጤምን ሙሉ አባልነት ደገፈ
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

አሜሪካ እና እስራኤልን ጨምሮ ዘጠኝ ሀገራት የፍልስጤምን ሙሉ አባልነት ተቃውመዋል
አሜሪካ ለዩክሬን ተጨማሪ የ400 ሚሊዮን ዶላር ወታደራዊ እርዳታ ይፋ አደረገች
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

የአሜሪካ የተወካዮች ምክርቤት ለዩክሬን የ61 ቢሊዮን ዶላር ወታደራዊ ድጋፍ አጽድቋል
ደቡብ አፍሪካ የአለማቀፉ ፍርድቤት እስራኤል ከራፋህ እንድትወጣ እንዲያዝ ጠየቀች
جديد አል ዐይን ኒውስ (RSS)

አለማቀፍ ጫናው የበረታባቸው ኔታንያሁ ግን “በጥፍራችንም ቢሆን እንዋጋለን እንጂ ወደኋላ አንመለስም” እያሉ ነው
2024/06/09 07:29:27
Back to Top
HTML Embed Code: