Telegram Web Link
#SankofaReads

ማንበብ ለምትወዱ ሁሉ

ሳንኮፋችን በስነ ጽሑፍ ዘርፍ የኖቤል ሽልማት አሸናፊ ጸሐፊያን መጽሐፍት ላይ ዳሰሳ መስራት አስባለችና ከዚህ ቀደም ከጸሐፊያኑ ያነበባችሁ ካላችሁ፣ለማንበብ ያሰባችሁና እንዲሁ ደግሞ ማንበብ ለምትወዱ ሁሉ አንድ አንድ መጽሐፍ  በማንበብ ያነበባችሁትን መጽሐፍ ላይ ደግሞ አጭር ዳሰሳና ገለጻ በመስራት እንድትሳተፉ ሳንኮፋችን ትጋብዛለች።

በቅድሚያ ከታች የተዘረዘሩት ጸሐፊያንና የተመረጡ ጽሁፎቻቸው ላይ ቢሆን ይመረጣል። ካልሆነም እናንተው አንብባችሁ የወደዳችኋቸው(የኖቤል አሸናፊ ጸሐፊያን) መጽሐፍትም መሆን ይችላሉ።

1. Kristin lavransdatter : Sigrid undset
2. The last gift: Abdulrazak Gurnah
3. A farewell to Arms: Ernest Hemingway
4. The bridal canopy: Shumuel Yosef Agnon
5. One hundred years of solitude: Gabriel García Márquez
6. The stranger: Albert Camus
7. Beloved: Toni Morrison
8. The remains of the day: Kazuo Ishiguro
9. The books of Jacob: Olga Tokarczuk
10. As I lay dying: William Faulkner
11. The Immoralist: Andre Gide
12. Ake: Wole Soyinka

(ግጥም ለምትወዱ የ Rabindranath Tagore( Gitanjali),  Pablo Neruda,Gabriela Mistral, Thomas Eliot, Wislawa Szymborska, louise glück, Octavio Paz  ግጥሞች ላይ ዳሰሳ መስራት ትችላላችሁ)


የዳሰሳ ጽሁፉ በእናንተ አጻጻፍና ፍላጎት ስለሚሆን የመጻፍ ችሎታ የለኝም ብላችሁ እንዳትጨነቁ፣ለጓደኛችሁ ያነበባችሁትን እንደመንገር ዓይነት እንደሆነ አስባችሁ ተሳተፉ።


የሚሳተፉት የሁሉም አንባብያን ዳሰሳ  ጭረት በተሰኘው የአንባብያን ማኅበሩ ዲጂታል መጽሔት  ላይ የሚወጣ ይሆናል።

👉 Telegram: @sankofabooks Email: [email protected]

#እናንብብ፣ እንለወጥ፣እናካፍል
     ሳንኮፋ የአንባብያን ማኅበር
Forwarded from ግጥም ብቻ 📘 (Leul Mekonnen)
ሥዕል ማሳል ለምትፈልጉ በሙሉ
በ +251984740577
ወይም @gebriel_19 ላይ  ፎቶ  በመላክ በ ተመጣጣኝ ዋጋ  ማዘዝ ይችላሉ!
#ሥዕል_ብቻ


@seiloch
@seiloch
'የማያረጅ ውበት የማያልቅ ቁንጅና'

ከ10 አመታት በፊት (እንደኛው አቆጣጠር በ2007 ዓ.ም.መሆኑ ነው) እሁድ እሁድ በኢ.ቲ.ቪ የሚተላለፍ "መለከት" የተሰኘ ተከታታይ ድራማ ነበረ።ያንኑ ድራማ ከሰሞኑ መገረብ ጀመርኩና አንድ ነገር ታዘብኩ...እንደ ሀገር ሊያሳስበን የሚገባ ትልቅ ጥያቄም ተፈጠረብኝ።"አለማየሁ ታደሰ መቼ ነው የሚያረጀው?"
ሴት አያቶቻችን 80 አልፏቸውም እንጀራ ጋግረው ይበላሉ።ወንዶቹ እርሻቸውን ለልጆቻቸው 'እንደፍቃዳችሁ አድርጉት' ብለው አይተውትም።እኛ በ20 አመታችን የሚያቅተንን እነሱ በ80 አመታቸው ሲያቀላጥፉት አይተን ''እንዴት?" ስንል "እነሱ እንደናንተ ምናምንቴ አይበሉም...በማርና በቅቤ ነው ያደጉት" ይሉናል።እና አለማየሁ ታደሰ የጢንዚዛ ማር ነው የበላው?አባቴ እንደነገረኝ አለማየሁ የገነት ንጋቱ የቴአትር መምህር ነበር።ጥንት "ዴዝዴሞና" የሚል ፊልም ላይ ሳየው ጀምሮ አሁን በስንቱና አጋፋሪ ላይ ሳይቀር መልኩ አንድ ነው።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኢትዮጵያን አዳርሶ ኤርትራና ሶማልያ ቅርንጫፍ ለመክፈት ዝግጅቱን ጨርሶም አለማየሁ አንዲት ነጭ ፀጉር አላወጣም።ካስቀመጥኳቸው መላምቶች አንዱ 'vampire ሊሆን ይችላል' የሚል ቢሆንም የጥርሶቹን አደራደር ሳይ ሀሳቤን ተውኩት።የሆነው ሆኖ አለማየሁ ስስታም ነው።እኒያ ወጣቶቹ የጥበብ ሰዎች በየቃለ መጠይቁ እድሜአቸውን ሲጠየቁ ከሚተናነቃቸው ምናል ምስጢሩን ሹክ ቢላቸው?ለኔስ ቢተርፍ ምናለበት?የአለማየሁ ሰውነት የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል እንኳን የእድሜ ነፋስ ሽው ሳይልበት እኔ "ሚጡ" ከመባል አልፌ የነሚጡ እናት የመሆኛ ዘመኔ ጥሎኝ ኮበለለ...የእናቴ የጠጉር ሽበት አንድ አንድ እያለ መላውን ጭንቅላቷን አዳረሰው...አባቴ ደርግ በሸለመው ከዘራ ይሰራ የነበረውን ሮንድነት ትቶ ጡረታ ከወጣ ዘመን የለውም...አለማየሁን ስናውቀው ያልተወለደው ታናሽ ወንድሜ ቁመት በልጦኝ በመሀላችን ያለውን የ10 አመት የእድሜ ኬላ ጥሶ "ከጎረምሳ ጋር አየሁሽ"በሚል ተልካሻ ምክንያት በኩርኩም እየነረተኝ ነው።እና...አለማየሁ መቼ ነው የሚያረጀው?

By ዘማርቆስ (@wogegnit)

@wegoch
@wegoch
@paappii
እህቴ ነበር ያሳደገችኝ:-

አራት ወይ አምስት አመት እያለሁ ነበር ወላጆቻችን ወደ ሞት የሄዱብን ። ሁለት ብቻ ነበር የወለዱት : እኔን እና እህቴን ። ስምንት አመት ትበልጠኝ ነበር ። መቼ ወደ አባትነት ፣ መቼ ወደ እናትነት እንደተቀየረች አላውቅም ።

ቤታችን ውስጥ አባትና እናት የሚወጣውን ሃላፊነት ተሸከመች ። ሸክሙ አላስጠናትም መሰለኝ ትምህርት አልገፋችም። አስረኛ ላይ የሙያ ውጤት መቶላት ነበር፤ እሱንም ተወችው ።

አልምልም : ከማልኩ ኤልዱ ትሙት እላለሁ በቃ ። ምድር ላይ ሞት መጥቶ ቻው ማለት የምትፈልገው ሰው ብባል፣ ዘመድ ጥራ ብባል ፣ አንደኛ ማን ያስብልሃል ብባል ፣ የማን ወዝ እና ህልም አልፎብሃል ብባል መልሴ ኤልዳና የሚል ብቻ ነው ።

ተሰብስበን ህልም ስንናገር ኤልዳና ህልሟ እኔ ነበርኩ ። እንደዚህ ሰው ይወደዳል እንዴ? እንደዚህ በፍቃድ ህልም ይሰዋል ? የሆነ ቀን ከስራ ስመጣ ኤልዳ ታማ ጠበቀችኝ ። ክሊኒክ ወሰድኳት ቀላል አይደለም ብለው ሪፈር ላኩን ።

ፊቷ ችፍፍፍ ፣ ቁስልስል አለ ። ቀኝ እግሯ እምቢ አላራምድ አለ ፣ ምግብ አልበላ አላት ። ብዙ ቦታ ሄድን መፍትሄ አጣን ።

ኢ- አማኝ ነበርኩ ፤ እንዲ አደረክብኝ ብዬ የምጠይቀው አካል፣ እንዲ አድርግልኝ ብዬ የምለምነው አካል የለም ። ነፍስ ካወኩ እንዲ ሀዘን ተጣብቶኝ አያውቅም ። የመኖር ፍላጎት እና ህልሜ ከሰመ። ህመሟን አለምደው አልኩ ። ሃኪሞች ተስፋ የላችሁም አሉን ።

የሆነ ቀን አስራ አንድ ሰዓት ለሊት ቀስቅሳኝ
"በዓታ ማርያም ሶስት ቀን ፀበል ተጠመቂ ትድኛለሽ ተባልኩ" አለችኝ ። ማመን የማይደክማት ልጅ ፤ መሞኘት የማይሰለቻት ልጅ ።
"እሺ እንሂድ" አልኳት ።

አማራጭ የሌለው ሰው ምንም አይፈላሰፍም። እንኳን ቤተክርስቲያን ስምጥ ሸለቆ እሄዳለሁ ። በርግጥ እኔ ከ 'Bible' የ Sigmund Freud - 'The Future of an Illusion' የተሻለ ያሳምነኛል።

ግን፤ ኤልዱ እድናለሁ ካለች የት አልሄድም ??

ሄድኩ : ተጠበለች ወደቤት መጣን ። እሷ በህልሟ፣ እሷ በበኣታ ፣እሷ በፀበል ያላት እምነት ትልቅ ነበር እና ውጤት ጠበቀች በርግጥ እኔ የምጠብቀው ነገር የለም ።

በነጋታው ጠዋት ፊቷ ለውጥ ያለው መስሎኝ ነበር እሷ አረጋገጠችልኝ ። በሁለተኛው ቀን ሄድን "እግሬ ቀለለኝ" እያለች ነበር ። የዛ ቀን በነጋታው "እግሬ ሰራ " አለች ።

የሆነ ነገር ማለት ፈልጌ ነበር ደስታ፣ እምባ አላናግር አለኝ እና ዝም አልኩ። ሶስተኛ ቀን ተጠመቀች ፊቷ፣ እግሯ ፣የምግብ ፍላጎቷ እንደነበረ ሆነ ።

ሶስተኛ ቀን እሷ ተጠምቃ ስትጨርስ "ወደቤት እንሂድ ወይ?" አለችኝ።

"እኔ ልጠመቅ እና እንሄዳለን" አልኳት። ስትድን ደስ ያላትን ያህል ደስ አላት። ሆድ ብሶኝ ነበር ፣ደስ ብሎኝ ነበር ፣ ማመን አቅቶኝ ነበር። እያለቀስኩ እያመሰገንኩ እየተደሰትኩ ተጠመኩ አመንኩ ።

ሃሌ ሉያ

By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
ስማቸውን ጥለው የሚሄዱ ኤክሶች!
(አሌክስ አብርሃም)

ኪያ ደወለችና " ገሲ አይንሽን አላይም ከዚህ በኋላ ብሎኝ ሄደ" ብላ አለቀሰች። ገሲ ገጣሚ ወዳጀ ገሰሰ ነው። በፍቅር አንድ አመት ቆይተው ነበር።
"እንዴ ለምን ?"
"እኔጃ በቃ አያምነኝም ፣ የሰው ወሬ እየሰማ ይበሳጫል!" ማልቀሷን ቀጠለች።

"ለዛ ነው ሰሞኑን የተለየሁሽ ለት ...ሴት ሞልቷል ባገሩ ፣ ቃልሽን የበላሽ... የጉም ጅብ ፣ የፀሐይ ቀበሮ የሚል ግጥም አከታትሎ ሲለጥፍ የነበረው? አልኩና ሁለቱንም ለማስታረቅ ቀጠርኳቸው። ልክ እንደገብረመድህን ፍልጥ ይዤ መሄድ ነበር የቀረኝ። ትዝ ይለኛል ቦታው ሁሉ ብሔራዊ የነበረች ኮፊ ሾፕ ፎቅ ላይ።

"ምን አጣላችሁ ደግሞ ?" አልኩ

ገጣሚ ወዳጀ ስካርቩን አስተካከለና "ተወኝማ አብርሽ! ሁልጊዜ የምትጠራኝ በሌላ ወንድ ስም ነው...ዳኒ ትለኛለች፣ ሳሚ ትለኛለች፣ ኬ ትለኛለች ኤም ትለኛለች አሹ ትለኛለች መረረኝ አልበዛም? ምንድነው ይሄ ሁሉ ወንድ ? ምንድነው? አፏ ላይ እኔ የለሁም።" አለ በብስጭት።

"አፍ ላይ ምን ታደርጋለህ? አንተኮ ልቧ ውስጥ ነህ ገሴ!" ብየ ወደደረቷ ስጠቁም ትልልቅ ጡቶቿን አይቶ ትንሽ ተረጋጋ። ወዲያው ጣልቃ ገባችና በችኮላ እጇን እጁ ላይ ጣል አድርጋ እንባ የሞሉ አይኖቿን አይኖቹ ላይ እያንከባለለች በሚያሳዝን ድምፅ ....

"አልተረዳኸኝምኮ ግርምሽ... " ከማለቷ አበደ፣ ስካርቩን ጣለ!
"ግርምሽ ደግሞ ማነው? ያለዛሬም አልሰማሁት። ማነው....?"

@getem
@getem
@paappii
ምን ማለት እንዳለበት ግራ ገብቶቷል። በሆነልኝ ያለው ነገር እጁ ስር መውደቁ ጨንቆቷል።ምንም ያህል ቢፈልገው፣ ምንም ያህል የእርሱ ይሆን ዘንድ ቢታትርም፤ የድካሙ ውጤት አሁን መከሰቱ ከደስታው በላይ ፀፀትን፣ ከፌሽታ በላይ ሀሳብን ወልዶለታል። አይ ጊዜ፣  ወይ ስሜት ።


   ቀኗ ለሷ ልዩ ነው። ጎህ ሲቀድ የውበቷን ልክ ለአፍቃሪዎቿ ልታስኮመኩም የቆመችው  ውብ ፀሐይ ለቀኗ ማማር አንዳችስ እንኳን አስተዋጽኦ የላትም፤ እንደው የምሽቱ ውበት፡ ጨረቃና ኮከቦች ለሳቋ ምንጭ ሆኑ እንጂ።  የሸበበው ልቧ የአንዲት አፍላ ኮረዳ መልክ የተቀዳጀላት ቀኑን በቀኝ እውለኝ በሚል ተስፋ አልያም ያስዋቧት ጌጣጌጦች አይደሉም። የቀኗ ማማር ዋናው ምክንያት፡ ስሜቷ፤ ያ ያሻችው ልቧን ያድነው ዘንድ የተማፀነችው  እውን መሆኑ እንጂ።የቀኗ ማማር ሚስጥር የፈለገችው፡ እንዲሆንላት አብልጣ የወደደችው በመሳካቱ ነው ። ወይ ስሜ....ት!።


  አንድ ቀን! ሁለት አይነት ስሜት፤ ለአንዱ ፌሽታ ለአንዱ ደግሞ ዱብዳ።  ከፈካው ቀኗ በፊት ባለው ምሽት ያልወጣላትን ፍቅሯን አግኝቷው ነበር። ህይወት  አንድ ዩኒቨርስቲ ነው ያገናኘቻቸው። እጅግ ሲበዛ ጨዋታ አዋቂ ነው። እሱ ካለ ዝምታ አይታሰብም። እርሱን ያገኘች ነፍስ ሳትፈልግ ከንፈሯን ትገልጥለታለች፤ በቀልዶቹ ድዶች ሁላ ይስቁለታል። ከሱ ጋር መዋል ለጤና ጥቅም አለው ሳይባል ሚቀርስ አይመስልም። ማንም ሴት ቀርቧው ዳግመኛ ባላየሁት ምትል አይነት ወንድ አይደለም። ቁመኗው ከፀጉሩ መሸሽ ጋር ተደምሮ ከጨዋታው ይበልጡኑ አስውበውታል። የአንዲት ምሽት አጋጣሚ ቢያገናኛትም በቀልዶቹ፣ በማያባራ ወሬው ጎርፍ መወሰዷን የአይኖቿ መመሰጥ ያሳብቁባታል። የጠይም ቆንጆ ናት። ስለ ጠይም ቁንጅና መዝገበ ቃሉ ፍቺውን እሷን እዩልኝ ብሏል። ከሰው ጋር ቶሎ የመግባባትን ተስጥዖ ፈጣሪ አዳልቶ ለሷ የሰጣት ነው ምትመስለው። ጨዋታ ይገባታል፤ የቀልዶች ቅመም እሷ ናት። ጥርሷ ሁሌ ስራ እንደበዛበት ነው። ከሷ አጠገብ ዲዳ ሁላ ያወራል። መተከዝህን መከፋትህን ታስረሳኻለች። 

 

   ለወደፊት ህይወታቸው መሸጋገሪያ ትሆን ዘንድ በሚኳትኑባት ዩኒቨርስቲ ባልታሰበች አጋጣሚ ነው በጓደኞቻቸው አማካኝነት የተዋወቁት።  እሷም  እሱም ለመግባባት የማቱሳላ ያህል እድሜ  አላስፈለጋቸውም። ምሽቱን ጨዋታና ፌሽታ ከበበው። ከዛ በኋላ ነው የነሱ ፍቅር ጉዞ ዕለት ተ ዕለት እያደገ የመጣው። መገናኘት፡ ማምሸት፡ ማውራት፡ መጫወት፤ ደግሞ መገናኘት፡ መሯሯጥ፡ መዝፈን፡ መዝለል፤ ድጋሚ መገናኘት፡ ማውራት፡  ማውራት፡ ድጋሚም ማውራት፡ በጣም ማውራት: ይበልጡኑ ማውራት  ስራቸው አረጉት። ዕለት ተ ዕለት ኮከብ ከመቆጠራቸው  የተነሳ ኮከቦች ከነሱ መሸሹን ከጀመሩ ሰነባብተዋል። ቀናት በነጎዱ  ቁጥር ፍቅራቸው ይጨምር ጀመር። ጊዜም ከነሱ ጋር አብሮ መጓዙን ተያይዞታል።


    ያቺ ምሽት ፍቅሯን መልሳ ያገኘችበት ቀን። በፍቅር መሀል በተፈጠረ ግጭት ከተጣሉ ሰነባብተዋል። እሱም ከትምህርት በተጨማሪ ለነገው ህይወት ዛሬ ላይ መሰነቁን አልዘነጋውም። በጓደኞቻቸው  መሰባሰብ የተራራቁ ልብን  ስጋ ያገናኛቸው ጀምሯል። እንደመጀመሪያው የግጭት ሰሞናት መዘጋጋትን ትተዋል። ፍቅረኛ የሚትባል ቃል በሁለቱ መሀል ባትኖርም የጎሪጥ መተያየቱን ትተው  ማውራት ከጀምሩ ሰነበቱ። በዛ አጋጣሚ ውስጥ ነው የሷን ፈገግታ፡ እየወደደችው የራቀችውን፤ ባለመግባባት  ያጣችውን ፍቅሯን መልሳ ያገኘችው። በዛ አጋጣሚ ነበር ቃላቷ ፍቅርን ዘርተው ያናግሩት የጀመሩት። ያቺ ቀን ናት ፍቅሯ እንደ ገደል-ማሚቱ ለልቡ ያስተጋቡለት። መራራቅ፡ መጣላት፡ መኮራረፍ፡ ፍቅሯን እንዳላሳጣው ያቺ ቀን ገልጣለታለች። የትላንቱ እሱነት ዛሬ ላይ አይታይበትም። ያቺ ምሽት ፍቅርን መለሰች። ፍቅረኛ በሚባል አጥር ድጋሚ አጠረቻቸው።


  ምን ማለት እንዳለበት ግራ ገብቶቷል። በሆነልኝ ያለው ነገር እጁ ስር መውደቁ ጨንቆቷል። ምድር ብትውጠው ደስ ይለዋል። በተጣሉበት ጊዜ የጀመረው የውጭ ትምህርት  እድል ተሳክቶለታል። ምንም ያህል ቢፈልገው፣ ምንም ያህል የእርሱ ይሆን ዘንድ ቢታትርም፤ የድካሙ ውጤት አሁን መከሰቱ ከደስታው በላይ ፀፀትን፣ ከፌሽታ በላይ ሀሳብን ወልዶለታል። እንደትላንት አብሯት ሊቀጥል፤ በፍቅር አብሯት ሊዘልቅ የወሰነ ሰው ዛሬ ላይ አብሯት የማይቀጥልበት ሁኔታ ሲፈጠር መግቢያ መውጫው ጠፍቶቷል። ስሜቷ፡ ፍቅሯ ላይ ድጋሚ ሊጫወትባት መሆኑ ተሰማው። አሳዘነችው። ትላንት አብረን እንቀጥል ሲላት የተሰማትን ደስታ ሊነጥቃት መሆኑን ሲያስብ ዘገነነው። ወይ ጊዜ እድልን አትሰጥ ነገር፤ ህይወት ትላንቱን እንዲያርም አንድ እድል ብትሰጠው ምንኛ ደስ ባለው ነበር። "አብረን እንቀጥላለን" ብሎ የሰጣት ተስፋ ፊቷን እንዳበራላት ያውቀዋል። መሄዱ የማይቀር ነገር ነው። ነገር ግን እሷን ምን ያርግ? ምን ይበላት?። ትላንትናውን ጠላው። ይንገራት ወይስ ለመሄድ የቀሩትን ጥቂት ቀናት ፍቅረኛዋ ሆኖ እንደሚቀጥል ያስመስል? ጨነቀው! አዘነላት፤ አሁኑኑ ቢነግራት ደስታዋን ሚነጥቃት መሰለው። በየቀናቶቹ ለመንገር ይወስንና ባገኛት፡ ባወጋት ቁጥር አብረው በሚያሳልፉት ጊዜ ምኖራትን ደስታና ፈገግታዋን  ባየ ቁጥር ፤ አስችሎት ቢነግራት ያ...ን ደማቅ ፊቷን ሚነፍጋት መስሎ ታየው። "ምነግርሽ ነገር አለ" የሁል ቀኑ ተግባር፡ "ሌላ ቀን" የሀሳቡ መቋጫ ሆኑት። ነግሯት ደስታዋን፡ ያከመውን ልቧን ድጋሚ ሲጎዳው ምን ይሰማት ይሆን? ህይወት በራሷ መንገድ አገናኝታ በራሷ መንገድ ስታራርቃቸው ምን ትል ይሆን?  ብዙ ቢጨነቅላትም እንዳትጎዳ ቢሸሽጋትም የመሄጃው ጊዜ እሱ እስኪወስን እየጠበቀው አልነበረው። ጊዜና ስሜት! መራቅና ፍቅር! አቤት ህይወት... እንደፈለገች ምታሾልበት!


   ሰማዩ  ከሱ ጋር ያዘነ ይመስል ማልቀሱን ተያይዟል። ሊነግራት ወስኗል። ሊያሳውቃት፡ እንደሚያማት፡ ለመቀበል እንደሚከብዳት እያወቀ ሊነግራት ወሰኗል። ምንም አማራጭ የለውም። በዝምታ መቆየቱ ይበልጡኑ ኋላ እንደሚጎዳት ተሰማው። በአካል አግኝቶ ሊነግራት ወሰነ። ሊያገኛት ደወለላት "Hello...."።

By 乃丨丂尺卂ㄒ

@wegoch
@wegoch
@paappii
ኔግሮ የሚባል ፍሬንድ ነበረኝ ፀባይኛ ነው፣ ሌባ ነው፥ እናቱን ይወዳታል፥ ትምህርት አይገባውም፤ ተንኮል፣ ኳስ ፣ጆተኒ ፣ ትረባ ጎበዝ ነበር።

በአንድ ሴሚስተር መቶ እና ሁለት መቶ መፅሃፍ ይሰርቃል መቼ? ...እንዴት?...ከማን?... አላውቅም!

መጨረሻ ላይ ውጤቱን እየሳቀ ይነግረኛል።
አንድ ቀን እንኳን ሲሰርቅ ተይዞ አያውቅም !

የሰረቀውን መፅሐፍ ሲሸጥ አብሬው ሄጄ አውቃለሁ። ከሚገዙት ጋር ደምበኛ እንደሆነ ሰላምታ አለዋወጣቸው ያስታውቃል። አሻሻጡ የሰረቀ ፣ ሳይለፋበት ያመጣ አይመስልም፤ በቸልታ አይደለም። በርጋታ እንደትልቅ ሰው... "አይሆንም...፣ ይቅር...፣በቃ፣ ጨምር " እያለ ነው ።

እናቱን "ሸቅዬ... እዛ ማዶ ያሉት ሃብታም ሰዎች፤ ለእናትህ ስጣት ብለው ብር ሰጡኝ" እያለ እንደሚሰጣት ነገሮኝ ያውቃል ።

ሰባተኛ ክፍል ፣ ስምንተኛ ክፍል እያለን እናቱን ያግዛት ነበር ። ይወዳታል፤ አወዳደዱ እንደትልቅ ሰው ነው። "ማሚዋ ደብሯታል ...አሟታል. . . ገበያ ቀዝቅዞባታል" እያለ ያስብላታል።

ከጓደኛው አይሰርቅም። ለጓደኛው ለኔ ለሚለው ሰው ይሳሳል።

አይኖቹ ትናንሽ ናቸው፣ አካባቢውን በትኩረት ያያል፣ ከወሬ ሁኔታን ያያል። ሌባ መሆኑን ብዙ የሩቅ ሰዎች አያውቁም።

ኔግሮ ቁርንጫጭ ፀጉር ያለው፣ ድቅቅ ያለ ገላ ያለው፣ ሲስቅ ቀጭን ድምፅ የሚያወጣ ልጅ ነበር ።

አንዳንድ ቀን ይፎርፍና ሜዳ ጥግ ውኃ ልኩ ጋር ብቻውን ይሆናል ። ዝም ይላል ኳስ አይጫወትም። ቀጭን ድምፅ እያወጣ የሚስቃት ሳቅ አትኖርም። ለመኮረጅ ብዙ አይሰቃይም።

...ጨዋታ ያበዛል...።

ስለ አባቱ አላውቅም፤ እናቱ ግን ትምህርት ቤታችን በር ጎን ላይ ቃርያ ፣ ቲማቲም፣ ነጭ ሽንኩርት፣ ድምብላል፣ ኮሰረት፣ ስኳር ድንች ...ምናምን ይሸጣሉ። ብዙ ደንበኛ ያላቸው አይመስለኝም። ስንወጣ ስንገባ የደራ ገበያ አንድም ቀን አይቼ አላውቅም ።

ኔግሮ የትምርት ቤት ስሙ መቆያ ነው። እኛ ነን ኔግሮ የምንለው።

እኛ ትምህርት ቤት የሚማሩ የሰፈሩ ልጆች ሲጠሩት ሰምተን መሰለኝ መቆያን ትተን ኔግሮ የምንለው።

መቆያ የሚባለው ክላስ ስም ሲጠራ ብቻ ነው። ኔግሮ ሲባል ነው እሱም ደስ የሚለው።

የሆነ ቀን ሃይሚ ግርማ መፅሃፍ ጠፍቶብኝ ኔግሮ ሰጠኝ አለችኝ። ጠየኩት "ከራሷ ቦክመህ ለራሷ ገጫሃት ኣ?" ስለው ፤ ሲስቅ የሚያወጣትን ቀጭን ድምፅ አውጥቶ ሳቀ "ባክህ እኔ እንደኔ ችስታ እናት ካለው ቤተሰብ አልሰርቅም "አለ ።

ከስምንት ወደ ዘጠኝ ስንዘዋወር ኔግሮ ታስሯል አሉን። ስሰማ "ዕድሜው ለእስር ደርሷል ወይ?" ብዬ ያኔ አልጠየኩም።

የመንግስት ትምህርት ቤት ስለተማርን ለብዙ ነገር ከዕድሜያችን በላይ ነበርን። የሚታሰሩት በግሩፕ የሚጣሉ ልጆች ስለነበሩ ብዙ አልገረመኝም።

መስከረም አስራ ሰባት ቀን ኔግሮ ሞተ አሉን። እናቱን ስናያቸው ጥቁር ለብሰዋል፥ ጉስቁልናው ብሶባቸዋል። ጉሊት የደረደሩት ከዚህ ቀደም ለመሸጥ ከሚደረድሩት በዐይነትም በመጠንም ቀንሶ አየሁ ።

ሞትን ያኔ ነበር በቅርብ ያወኩት ....በቅርብ የማውቀው፣ ሲያወራ የሰማሁት፣ አብሬው የተጫወትኩት ጓደኛዬ ሞተ ሲባል። ያኔ ነው ለመጀመሪያ ግዜ ያመንኩት።

የታሰሩበት ክፍል የነበረው ካቦ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ፖሊስ መቶት ነው ይላሉ፤ አንዴ ታሞ ነው ይላሉ ....
ኔግሮ ሞተ። እውነት ነበር!

"ልጅ ይሞታል እንዴ?!" አልኩኝ
ለምን መቆያ አሉት ግን እናቱ??
በዛ ዕድሜው እንዴት በዛ ልክ አሰበላቸው??
በምን ይሆን የሚፅናኑት??
ለምን ሌባ ሆኖ ለጓደኞቹ ታመነ??

እንዴት የሰረቀውን እንደትልቅ ሰው አስቦ ተከራክሮ ሸጠ?? ላለፋበት ነገር እንዴት ዋጋ ሰጠ?? ለምን ምንም ከሌላቸው ሰዎች አልሰርቅም አለ??

በዛ ዕድሜው እንዴት አረጀ ?
እሺ ይሁን መርህ እና ሌብነት እንዴት አብሮ ሄደለት!!

እኔንጃ ኔግሮ ግን ሞተ አሉ !!!

By Adhanom Mitiku

@wegoch
@wegoch
@paappii
ዕድሜዋ ወደ አርባዎቹ እየገሰገሰ ነው....በህይወት ውጣውረድ የዛለ ፊቷ አሁንም ድረስ ድንቡሽቡሽነቱን አላጣም። ዘውትር ለብሳት በምትዞረው አንድ ሺቲ ሙሉ ከተማውን ከጫፍ እስከ ጫፍ ታካልለዋለች። ካልነኳት ማትነካ ብቸኝነትንና ባይተዋርነትን የመረጠች ብቸኛ ነፍስ ናት። ፀጉሯን ማንጨብረር ወይም እንደ 90ዎቹ አፍሮ አርጎ ማቆየት ያስደስታታል። በዛ ድንቡሽቡሽ ገጿ እና ሺ ሀሳብ ቢያጠቃውም ፍንክች ባላለ ሰውነቷ እዚህም እዛም ትባዝናለች።
.
" ሰሚራ " ማህበረሰቡ እብድ የሚል ቅፅላ ሰጥቶ ቢያገላትም ፤ ለኔ ግን የተነጠቀችው ወጣትነት ፤ የተነጠቀችው ህልሟ ጎልቶ ይታየኛል። እደርስበታለሁ ካለችበት ፤ እኖረዋለሁ ካለችው ህይወት ተብትቦ ያደናቀፋት ማህበረሰብ ቀፅላ ሰጥቶ ቁስሏ ላይ ሌላ ቁስል የጨመረላት ምስኪን ነፍስ። የዛሬን አያርገውና አይምሮዋ ከመታወኩ በፊት እንደማንም ጤነኛና ለፍቶ አዳሪ ነበረች። በአንድ ወቅት ለምርመራ በሄድችበት ጊዜ የአባላዘር በሽታ እንዳለባት በሀኪሞች ይነገራታል። ከህይወት ጋ ግብግብ በገጠመችበት ወቅት ፤ አጋዥ ደጋፊ በሌላት ወቅት ይሄን መስማቱ ለእሷ የሞት ታህል ነበር።
.
ዐቅመ ቢስነቷ የእጇ ማጠር ፈውስን ነፍጎ በሽታዋን አበረታባት። ዕለት ተዕለት እየፀናባት ማህበረሰቡ የሚያስተውለው ደረጃ ሲደርስ ሁሉም አገለላት። ተፀይፎ በቃሽኝ ከማለት አልፎ ቅስምን የሚሰብሩ ቃላት እያቀበለ ጨርቋን አስጣላት። ከምላሳቸው ያወጧት ስንዝር ቃል ህልምና ውስጥኗን የቀረቻትን ጥቂት ተስፋ ይዞት ገደል ገባ። ጣት ጠቆሙባት መታመሟ ሳያንስ እብድ ነሽ ብለው የእብደት አክሊል አላበሷት....አሜን ብላ መኖር ቀጠለች።
.
ሳያት ታሳዝነኛለች ፤ እንዲህ ካረጋት ማህበረሰብ ጋር አሁንም ድረስ ተቻችላ ትኖራለች። ከሁሉ ከሁሉ ስታረገው ሳይ የሚያስደስተኝ አንድ ነገር አለ ። ብር እጇ ላይ ከሌለ መሃል አስፓልት ላይ ወጥታ መንገድ ትዘጋለች። ሚያውቋት ሹፌሮችም ባህሪዋን ስለሚያውቁ ገንዘብ ይሰጧታል።
.
ይሄን ስታረግ ሳይ ውስጤ ይረካል። ከመንገዷ ያደናቀፏትን ለደቂቃዎችም ቢሆን መንገዳቸውን አደናቅፋለች። ምትቀበለው ገንዘብ ለሞራሏ ካሳ ባይሆናትም ከኑሮ ወጪ ግን ይታደጋታል። ፖሊስ ቢመጣ ሰማይ ቢገለበጥ ከተቀመጠችበት ፍንክች አትልም።  ታድያ በተቀበለችው ገንዘብ ቡና ልትጠጣ የጀበና ቡና ሻጮች ጋር ትሄዳለች። ማያውቋት ፈርተው የከለከሏት እንደው ትንሽ ግርግር መፍጠሯ አይቀርም። አምነው ለሰጧት ግን ሂሳበቸውን ሰጥታ ሲኒ በስርዓት መልሳ ካገኘች ጫት ካላገኘች ገረባ ሸክፋ ጥጓን ይዛ እየቃመች አልያም ተኝታ ቀኗን ታሳልፋለች።
.
ሚግባቧት ፍቅር ይሏታል ለሌቹ ደሞ በስሟ ይጠሯታል። ከወደደችህ በፍቅር ከጠላችህ ደሞ በስድብ አቀባበል ማድረጓ የተለመደ ነው። አንድ ጊዜ በመንገድ ሳልፍ ምን አበሳጭቷት እንደሆነ ባላውቅም ውሃ ደፍታ አጥምቃኛለች። ብቻ የአንደበታችን ኃይል እንደምናስበው ቀላል አይደለም። መጠገን ከሚችለው በላይ መስበር ይችልበታል። ይች ሴት ምን አልባትም አለውልሽ ሚላት ቢኖር መጨረሻዋ እንዲህ ባልሆነ ነበር። ለኛ ተራ እና ፌዝ መስለው ሚታዩን ቃላት በለሌላው ህይወት ላይ እንደ ደውል ቀን በቀን ያቃጭላሉ።

[ ጥሩቤል ]
@ebuhbhr

@wegoch
@wegoch
@paappii
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በሁሉም ቀናት ከሰዓት አንድ ጉዳይ አስባለሁ። መኖራችንን። ከመሰደድ፣ ከመጋደልና ከመቧደን የተረፈ ቀናችንን። ኖረናል?! እንጃ?! እንደ Virginia Woolf አባባል ቀን ተቀን ከማውቀው ህይወታችን ወዲያ የምመኘውና በስሜት የሚንጠኝ አለ።(I have a deeply hidden and inarticulate desire for something beyond the daily life)። ያልደረስኩበት ሰላም፣ ያላሸተትኩት መውደድ፣ ያልኖርኩበት አንድነት፣ እንዳሻኝ የምዞርባት ሀገር ትናፍቀኛለች። እንደ መንግስቱ ኃይለማርያም ሀገርየምታምስ "ሰብአዊነት ይፋፋም" የምትል ቃል ብዬ የምወረውረው ነጭ ርግብ የያዘች ጠርሙስ አሊያም እንደ ቀይ ሽብር ፍቅር፣ ሰላም፣አንድነትና ነጻነት ይፋፋምብኝ ብላ የሞቷ ምክንያት ከጀርባዋ የተለጠፈባት ወጣት ። እንደ ህዝብ በሀዘን አንጀቴን አስሬና ተለጉሜ ከኖርኩባቸው ቀናት ወዲያ የሰላምና የደስታ አብዮት በታሪኬ እንዲጻፍ አልማለሁ።
በሰላም መኖርን

@wegoch
@wegoch
@paappii
ታረቂኝ ። በቃ ታረቂኝ አልኩሽ ታረቂኝ ። ዝም ብሎ ሆድ እየባሰኝ ነው ታረቂኝ ። ያለ ምክንያት እየከፋኝ ፥ እንዲሁ እየደበረኝ ነው ታረቂኝ ። ጥላቢስ ከውካዋ ሆኛለሁ ታረቂኝ ። ከቦሌ መገናኛ እንዲህ ሩቅ ነው እንዴ ታረቂኝ ። መንገድ ስሻገር ሾፌር ጮኸብኝ እኮ ታረቂኝ ። የዛ ቤት አስተናጋጅ "ጓደኛህስ የት ሄደች" አለኝ ታረቂኝ ። የታጠቡ ልብሶቼን መች ልልበሳቸው ታረቂኝ ። ገማሁልሽ እኮ ታረቂኝ ። ከነጋ 15ኛ ሲጋራዬን እያጨስኩ ነው ታረቂኝ ። የዛሬው ፍርፍር ደሞ ሲያስጠላ ታረቂኝ ። ጫማዬን ካስጠረግኩ በጣም ቆየሁ ታረቂኝ ። የሆነ ልጅ ዝም ብሎ እየተራመደ ነው ፤ ሄጄ ላጋጨው እንዴ ታረቂኝ ። ና ማነህ የ11 ደብል ጂን ሒሳብ ውሰድ ታረቂኝ ። ፀሐይ ነው ብዬ በቲሸርት ወጥቼ ዝናብ ቀጠቀጠኝ ታረቂኝ ። በፍቅር ያዘነ በምን ይደሰታል ታረቂኝ ። ከዚህ አገር ብን ብዬ ልጥፋ ወይ ታረቂኝ ። ዘፈን የሚባል ነገር ነው ያስጠላኝ ታረቂኝ ። ቱ !...ትፍ ሚሪንዳና ነው ሬት ? ታረቂኝ ። የእናትምስ ነው አቢይ አህመድ ታረቂኝ ። ቅዳሜና እሁድ አስጠላኝ ታረቂኝ ። እግዚአብሔር መልካም ነው - ወለሂ ? በቃ ታረቂኝ ። ወደ ማን ልደውል ነበር ስልኬን ያወጣሁት ? ታረቂኝ ። ሶስት ሲደመር አራት ሰባት ነው ስምንት ? ታረቂኝ ። ኧረ በህግ አምላክ ታረቂኝ ። ያምሻል እንዴ ታረቂኝ ።

By Hab Hd

@wegoch
@wegoch
@paappii
ማሪታ ሎሬንዝ

ዘመድ አይጥፋ ባለፈው ዙምባቤ ሐረሬ ዞር ዞር ስል ትንሽ ሃገሬ ብትናፍቀኝም ጓድ መንግስቱም እንኳን ተወለዱ ለማለት  እቤታቸው ጎራ አልኩኝ ።

ፍልቅልቋ ባለቤታቸው ወ/ሮ ውብባንቺ ቡና  አፍልተው እያጫጫሱ ሳለ በአይኔ የፊደል ካስትሮን እና  የጓድ መንግስቱ  ፎቶ ስቀላውጥ አይተው "ጥቁር ነብር " ሚላቸው በአሉ ግርማ  ጓድ መንግስቱ ፊታቸውን ጠቆር አርገው የማየውን ካጤኑ በኃላ

ይገርምሃል  ያኔ ሁለታችንም የበዛ የሃገር ፍቅራችን እራሳችን ላይ ወቶ ካቲካላ እንደጠጣ ሰው በሰከርንበት ጊዜ ነበር ይሄን ፎቶ የተነሳነው ብለው ላፍታ ትክዝ አሉ።

እንግዲ ወዳጄም አይደል እቺ ሰዓት ምን እያወራን መሰለክ ብለው የትዝታ ፈገግታ ብልጭ አረጉና ጉሮሮዋቸውን ጠራርገው እንዲ ሲሉ ጀመሩ ....

ስለ ሴት እያወራን ነበር ለዛውም ስለ ጉደኛ ሴት ...

ካስትሮ ሞት በቃኝ ካንተ ጋር ትግል ደከመኝ ስለተባለለት ከ600 በላይ ጊዜ የግድያ ሙከራ ስለተደረገበት የኔ ወዳጅ ፣ የህፃናት አንባ ልጆች አጎት፣ የኤርኔስቱ ቼ ጉቬራ የትግል ጎደኛ  ፣  ፣የሶሻሊስት አጥማቂ፣ የአሜሪካ ራስ ምታት ፣ ከከበርቴ ቤተሰብ የተገኘው የበኩር ልጅ ፣ የውቧ ኩባ ባላባት፣የራሁል ወንድም ፣ ፊደል ካስትሮ እንዴት ከሞት አፋፍ ስንት ጊዜ እንዳመለጠ አጫውትሃለሁ አሉኝ በኩራት ።

  በተለይ ደሞ ከሴት ወጥመድ እንዴት እንዳመለጠ ብታይ ብለው ወደጣሪያው እያዩ ወገባቸውን ወደ መደገፊያው አሳረፋ።

ነገር ጎንጓኟ አሜሪካ ልታስገድለው ያልቆፈረችው ጉድጓድ አልነበርምና

በEisenhower 38 ጊዜ፣በKennedy 42 ጊዜ፣በJohnson ፣በNixon፣በReagan ፣እንዲሁም በBush እና በClinton ጊዜ ጨምሮ ከ635 ጊዜ ሚሆን የግድያ ሙከራ የተደረገበት ብርቱው ሶሻሊት ነበር ፊደል ካስትሮ የኃላ ኃላ አሜሪካ ሴት ላከችበት!

አሉና ወደባለቤታቸው ዞር ብለው የፍቅር አዪዋት

ወ/ሮ ውብባንቺ አሄሄሄሄ ስለዛች ጉደኛ ስለ"ማሪታ" ልታወጋው ነው አሉ ፊታቸው ሙሉ እየሳቀ ።

"marita lorenz" እቺ ሴት  የጀምስ ቦንድን ሴቶች ምታስንቅ ቆንጆና በ25 ዓመታት የስለላ ታሪኳ ገዳዬ ገዳዬ ተብሎ የተዘፈነላት ቀላች እንጂ የሙት መንፍስ ስጋ ለብሶ በላት ።

ከጀርመን አባቷና ከአሜሪክዊት እናት የተወለደች የCIA ግርፍ ነች ብለው አከሉበት ።

ማሪታ ሎሬንዝ ምንትስ በተባለ መርስ ልትገለው ባንድ ክፍል ውስጥ እራሷን ከቁመተ ለግላጋው ከፊደል ካስትሮ ጋር ተገናኘች ቀድሞውኑ ቀልቡ የነገረው ፊደል ካስትሮ ቁልቁል እያያት እንድትገይኝ  ነው አይደል የላኩሽ አላት ፀጉሩዋን እየደባበሰ ።

" ቼ" አለችው በስፖኒች ቋንቋ "የኔ" ማለት ነው አሉ ጓድ መንግስቱ በእንክሮት ቃሉን ረገጥ አርገው ።

ማሪታ ሎሬንዝ ተንሰፈሰፈች ልገልህ አልችል   አለችው
( Quiero esta noche contigo un gastado papi ) አለችው

ትንሽ ማስተካከያ ታክሎበት

"ካንተ ጋር አድሬ ሲነጋ ልሙት"

ማለቷ ነው ብላ ከደረቱ ተለጥፋ ትኩስ እንባ በጉንጮቿ አወረደች ።

ጓድ መንግስቱ ወደኔ እየተጠጉና ሚስታቸውን አፈር እያሉ  "የኩባ ሴቶች በደንብ ካረካቸው እና የልባቸውን ካደረሱ
የእርካተ ጣሪያ ላይ ሲወጡ በነሱ ቋንቋ  "Carico papi"  ይላሉ አሉኝ ይህም ነጮቹ Am coming ሚሉት ነው ብለው በሳቅ ፈነዱ ።

እትዬ ውብአንቺም አንቱ !

ዘንድሮም አላረጁ አሉ በባላቸው ቅብጥብጥነት አየሳቁ።

ከነዚህ ሁላ የግድያ ሙከራዎች መክሸፍ ምን እንዳዳነው ገምት እስኪ ጃል ? አሉኝ

አይናቸውን አጨንቁረው መልሴን በመጠባበቅ።

እኔም የግል ጠባቂዎቻቸው ብርቱና ንቁ ናቸው ብዬ አስባለሁ አልኩ ጥርጣሬ ባዘለ ድምፅ

ልክ ነክ አሉ ጓድ መንግስቱ ፈገግ እያሉ አንዱ እሱ ሲሆን ግን ዋነኛው የሱ ደመ ነፍስ ነበር ።

ደመ ነፍስ ? አልኩ ጥያቄ ባላው ድምፀት

ጓድ መግስቱም ቀጠል አረገው ፊደል ካስትሮ ቡና ይወዳል እሱን ካልጠጣ እና ያንን ግንድ ሚያክል ወይራ ወይራ ሚል ሲጋሩን(Cigar)አፋ ላይ ካላረገ ስራ አይሰራም ።

አይኑም አይገለጥለትም አሉ ጥቁሩ ነብር ።

የነሱ ቡና እ'ንደኛ እንዳይመስልህ ቦንብ ነው ፣ቦንብ ሚጠጣው እራሱ ባረቄ መለኪያ ነው ።

አንዴ እሷን ቋ  ካረገ ሁሉ ነገር ወገግ ብሎ ይታየኛል ይላል ፤ አሉ ጓድ መንግስቱ  አይናቸውን ወደ ፎቶው ቡዝዝ አርገው ።

እናሳ በምን ተቋጨ የሲቲቱ ጉዳይ አልኩ መጨረሻውን ለመስማት ጓጉቼ

በዚህ ሰዓት ሁሉ ነገሬ ጆሮ ሆኖ ነበር ።

ሳትገለው የፍቅሩን አዙሪት አልቻልኩም ብላ ወደ ሃገሯ አሜሪካ ሄደች ።

ማሪታ ሎፔዝ ልገለው አልቻልኩም ብላ CIA ን ግን ዋሸች ።

አንድ ልጅ ወልዳለታለች ይባላል አሉ እሱ ግን ውሸት ነው ይላል አሉ ጥቁሩ ነብር ።

የጊዜ ጀግና እንጂ የሰው የለው ብለው ሚስታቸው ውብባንቺ በነገር ጎሸም አርጓቸው ።

ጓድ መንግስቱም ዞር ብለው ሚስታቸውን እስቲ ተይ ...ተይው ዓለሜ አሏትና በረጅሙ ተነፈሱ ።

የራሳቸው ትዝ ሳይላቸው አልቀረም

ብቻ አሜሪካም ልትገለው እንደቋመጠች በ90 ዓመቱ ዓረፈ አሉኝ ጥቁሩ ነብር ደግመው ፎቶውን እያዩ።

እኔም ፎቶውን ደግሜ ሳየው ፊደል ካስትሮ

"ገደገድኩባት " ሚሉ ነው ሚመስሉት ።

By Ermias frew

@wegoch
@wegoch
@paappii
መፈቀር ደስ ይላል

ለስለስ አርጌ ነው ማልወደውን ተይ የምላት በትህትና እሺ ትለኛለች እሺታዋ ውስጥ መብትህ ነው ስልጣን አለህ ስትለኝ የሚሰማኝ ስሜት ጥልቀቱን እወድላታለሁ ::

አስሬ እየደወለች እንደልጅ እየተፍነከነከች  ሲያሻትም እያጉረመረምች እየተበሳጨች ያጋጠማትን ነገር ትኩስ ዜና ደውላ ስትነግረኝ ድምፆ ላይ ያለው ቃና እውነተኛ ስለሆነ በፍፁም ልቤ ነበር ምቀበላት ::

ማታ ማታ

ጀንበር ከመሰለው ከንፈሯ መንፈስን ቀላቅላ እፍፍፍ ትልብኛለች እንደ ቡችላላ ስፍስፍ ትላለች ከነብሴ ትጣበቃለች እኔ ደሞ እፉዬ ገላ እሆናለሁ ፍፍፍ ባለችኝ ቁጥር ወደሰማይ በነፍሴ እቃትታለሁ::


እንደምትወደኝ ስለምታሳየኝ የሚሰማኝ ሰላም ወደር አልነበረውም አንዳንድ ቀንማ ስትንከባከበኝ "ከክሽ ክሽ”በኃላ ቢሆንም ንጉስ ባልጋው ሳለ ሚጎማለለውን ምተውን ይመስለኛል ::

ስትጨነቅልኝ ደሞ ደበረኝ ካልኳት አመመህ እንዴ ብላ ፊቷ  ላይ ያለው መረበሽ አንጀቴን ይበላዋል እንደ ታናሽ ወንድሟ ስትሳሳልኛለች እንደ ቆሎ ጓደኛዋ ስታሾፍብኛለች እንደ እናቷ (አባቷ )  ስትሰማኝ አይይይይይ... እላለሁ እናቴ የመረቀችኝ ምርቃት ደርሶ እንጂ እንደኔ አመል እንደኔ መደመር መቀነስ ሚጢሚጣ በቃሪያ የሆነች ልጅ ነበር ሚገባኝ ።

የሆነው ሆኖ መፈቀር ደስ ይላል ::

By ኤርምያስ ፍሬው

@wegoch
@wegoch
@paappii
"እናቴ ሁልጊዜ 'ደህና ነህ? ደህና ነህ?' ማለት ታበዛለች" አለኝ። ገና ከመግባቱ ። ጓደኛየ ነው፣ አብረን እንሰራለን። እናቱ ጋር አውርቶ ገና ስልክ መዝጋቱ ነበር። ሁልጊዜ ጧት ጧት ያወራሉ።

"እናት አይደሉ" ከማለቴ ፈጠን ብሎ
"ኖ ኖ ከኖርማሉ በዛ ይላል የሷ! በኋላ ስትነግረኝ በተወለድኩ በሁለት ወሬ አንዲት ደንቃፋ ሰራተኛ ትልቁ ባለአበባው የቡና ስኒ ታውቀዋለህ? ያ ስኒ አምልጧት ጭንቅላቴን ነርቶኝ ነበር። እና እናቴ የሆነ የአዕምሮ ችግር ይፈጠርብኛል ብላ ስትጨነቅ ነው የኖረችው። እንደምታየኝ ተርፊያለሁ! እሷ ግን እስከአሁን አታምንም። አለና ተሳሳቅን።

ወደቡና ማሽኑ ሄዶ ሁለት ቡና ይዞ መጣ ...አንዱን ዘረጋልኝ። ቡና ማቆሜን ለሃያኛ ጊዜ ትላንት ነግሬው ነበር። እንደገና ሳስታውሰው ሳቀና "እናቴ እውነቷን ነው መሰል አንተ?" አለ።

"እንደገና ደውልላቸውና ሰራተኛዋ የቡና ስኒ ነው ወይስ ዘነዘና የጣለችብኝ ብለህ ጠይቅ" ዝም አለ። የመልስ ምት እያሰበ ነው። ሲያስብ ትንሽ ይዘገያል ስኒው መሰለኝ። ቆይቶ

"ሰራተኛ ነበራችሁ" አለኝ
የለንም
ስኒስ ?
የለንም
ዘነዘናስ?
የለንም
በቃ አንተ ራስህ ሲያቅፉህ አምልጠህ በጭንቅላትህ መሬት ላይ ወድቀህ ነበር። 😁

By alex abrham


@wegoch
@wegoch
@paappii
ገደልኩት

ወሎ መስታወትን "መታዘቢያ" ይለዋል።

ራስን መመልከቻ፣ እድፍን ጉድፍን ማያ፣ ከራስ ጋር ማውጊያ መሆኑን አይቶ።

እውነት ነው !

ወርሃ ግንቦት  ከረጅምና አሰልቺ ቀን በኃላ
እቤቴ ውስጥ ካለው ሙሉ ገፅታዬን ከሚያሳየው መስታወት ፊት እርቃኔን በትካዜ ቆምኩ ፍዝዝ ብዬ እራሴን በእዝነት ተመለከትኩት ።

እኔ ለእኔ አዘንኩ መስታወቱ ውስጥ ያለው የራሴው ምስል አይኑ እንባ አቅርሮ ታየኝ በአይኑ የሆነ ነገር ይለኛል መናገር ማይቻል ቡቡ ልጅ ፊት እያሳየ ሆዴን ያባባኛል::


መስታወቱ:- እባክህ ዛሬም በዛ ባማይረባ ፍቅር በሚሉት ዝባዝንኬ ወሬ እኔንም ልብህንም ማሰልቸት ተውና ስለ ካሳኖቫ እናውራ ስለቬነስ ፈገግ እያልክ አጫውተኝ አለኝ ? ..........
ደሞ መጪው ክረምት ነው ፊትህን አታዝንበው !

እኔ :-የኔና የሲፈን የፍቅር ህይወት እራሱ እኮ ሃምራዊ ቀለም ነው ስለሱ እናውራ አልኩት::

መስታወቱ :-እንዴት አንድ ሰው  ጥንካሬም ድክመትም ይሆናል ?
ሲልህ ትልፈሰፈሳለህ ሲልህ ዘራፍ አርበኛው አያቴ ተጉሉት ምናምን ትላለህ ምንድነው ችግርህ ?

እኔ:- እኔ አላውቅም ....ብቻ እኔ ማውቀው የማትደራደርባቸው ነገሮች ተብዬ ብጠየቅ ከመልሶቼ መሃል  አንዱ እሷ ነበረች።

ሲፈን  እንዴት እወዳት ነበር መተው በማልችልበት ልክ እወዳት እደ'ነበር አተም ታውቃለህ !

እራስ ወዳድ እንዳልባል እየፈራው እንጂ አሁንም ድረስ እኮ እወዳታለሁ የእኔ እንድትሆን እፈልጋለሁ !
ለዘግ ላለ አመታትም አብረን ብንቆይ ሳልጠግባት ነው የተለያየነው::

መስታወቱ:-ምን ለያችሁ ታዲያ ?

እኔ:- ሁኔታዎች ድንግት ኑሮ ሚሉት ደራሽ ወንዝ ወሰደብኝ አልኩ እያቀረቀርኩ::

ከውጪ ሚሰማው ዝናብ የኔን ሃዘን የሚስደርስ የቅርብ ወዳጄ ነው ሚመስለው ሰማዩ ያነባዋል  ያንዠቀዥቀዋል !


መስታወቱ :- አንዳንዴ መለያየት ሳይኖርብህ ሁኔታዎች ይለዩሃል" እጣ ፍንታ ነው ምርጫ"የሚያስብሉ የህይወት መንታ መንገድ ጋር ትቆማለህ !

እሱን መረዳት አለብህ !

ከልክ እና ከስህተት ባሻገር አንድ ሜዳ አለ - እዛ እንገናኝ ትልሃለች  ዓለም ዱላዋ ይሰብርሃል ::
 
ስለዚህ እውነታውን መቀበል ነው ያለብህ ብትሸሽም ሲከተልህ ይኖራል እንጂ አታመልጠውም አለኝ ጎርነን ባለ ድምፅ ::

መብረቁ ተስረቀረቀ  የራሴው የሳግ ድምፅ መሰለኝ ።

ሳለላስበው በጉንጮቼ እንባ እየወረደ ነበር የአለም ዱላ ልቤን ቀጠቀጠው ::

መስታወቱ:-በአሽሙር አፉን አጣሞ ፈገግ አለ ደስ አለው ይህን ቀን እንደሚመጣ ነግሬህ ነበር አልሰማኽኝም ነበር አለኝ ::

ይሁን አሁንም ዋናው ምክር መስማትህ ነው እ'ውስጥህ ያለውን አንተነትህን ግደለው መሞት ይፋልጋል ፣ሸኘው አለኝ ...

እኔ:- በመስኮት አሻግሬ ተመለከትኩ ያንን ብዙአየሁን ከውስጤ ልገለው ተመኘው !


ዛሬዬ የተሰራው በእሷ ትላንትናዬ ውስጥ በመኖር ነው :: 

እንዴት ላርግ ያኛው ቡዙአየሁ እኮ መልካም ሰው ነው ፈገግታ ከፊቱ ማይጠፋ እምነት ፣ተስፍ ፣ፍቅር አብረው ፀንተው ይኖራሉ የሚል ደግ ሰው ነው አልኩት ::

መስታወቱ:- አየኽው ያኛው ብዙአየሁ ምን እንደሰህ?

ለማንም አልሆነም ላንተም አልበጀህም  እሷንም ለሰቀቀን እና እራሷን እንድትጠላ ነው ያረካት  ::

መስታወቱ:-ተዋታ በቃ ትቅርብህ

እኔ:- እንዴት ልተዋት

መስታወቱ:- ወንድ ልጅ አይደለህ ?
ቁረጥ ምድነው ገብርዬን ያጣ ካሳ ምትሆነው ቆፍጠን በል !

የነገን ማን ያውቃል ምን ይዞልህ እንደሚመጣ ?

እኔ:- አቤት እ/ር ግን ማኖር ሲያውቅበት !

ተመስገን🤲 በረጅሙ ተነፈስኩ::

እኔ:-አብቅቷል ካልኩ በኃላ ወጣልኝ ባልኩ ማግስት የትዝታ ፈረስ የኃሊት እያስጋለበ ከተጓዝኩት መንገድ ዳዴ እያስባለ ይመልሰኛል

አብረን የሆነው ሁሉ ይናፍቀኛል

መስታወቱ:-ብትመጣስ  ?

እኔ:- አላውቅም ግራ ያጋባል ግን ሲመስለኝ እንደዛ የሚል ተስፋ አይደል የሚያኖረኝ አንዳንዴ ህይወት የምታምረው ፣እንደ ሲፈን ጡት ምታጓጓው ከፊት ተስፋ ከኃላ ትዝታ ሲኖራት ነው ::

መስታውቱ:- ተስፋ እና ህልም ብቻውን እኮ እንደቆመ ውሃ ነው ይሸታል!


በልብህ ያለው ፍቅር የማይሞት ህልም ቢመስልህ ፣ ብትውተረተርም፥ የሚጨበጥ ያለ መስሎህ ብትዋትትም ፥ ምናልባትም እሷ ቆይታ ይሆናል ከገደለችህ ፤

ውስጥህ ያለው ፍቅር እኮ እድትገለው እየቃተተ ነው  ! አለኝ ለመተንፈስ መቸገሬን አይቶ ...


እኔ :-

ተለያየለን ፣ገደልኩት ፤መስታወቱን ሰበርኩት።

ከዚህ ቀን በኃላ የዚህ የህይወቴ ገፅ እንደመስታወቱ ፊቴንም ቆንጥሬ እንደማይበት ሁሉ የሲፈንም ታሪክ ቁንፅል ነው ታሪኳ፣ሽርፍራፊ ነው ትዝታዋ፣የደበዘዘ ነው መልኳ።

ጊዜ የዳበሰው ትዝታ !

ከኤርምያስ ፍሬው

@wegoch
@wegoch
@paappii
ቦግ እልም!
(አሌክስ አብርሃም)

በደርጉ ዘመን «ዕድገት በህብረት » የሚባል ዘመቻ ታውጆ ነበር አሉ። በየዩኒቨርስቲው ያለው ተማሪ በየገጠሩ እየሄደ ህዝቡን እንዲያስተምር፣ እንዲያነቃ ነበር ዘመቻው! ከዘማቾቹ ፍልስፍና ቢጤ ያነበበ ተማሪ ይሄድና አንዱን በሰላም የሚኖር አርሶ አደር "ፈጣሪ የሚባል ነገር የለም አጉል እምነት ነው» ይለዋል! ማለት ብቻ አይደለም የተማረ የሚታመንበት ዘመን ነበርና በመረጃና በማስረጃ ያንን ሚስኪን ገበሬ ራሱን አዙሮ አሳመነው! ገበሬው «በቃ ፈጣሪ የሚባል ነገር የለም » አለና ከቤተክርስቲያን ጠፋ! ለሌለ ሲኦል በከንቱ ነው ስፈራና ስጋየን ስጨቁን የኖርኩት አለና ጠጁን እየጠጣ፣የስጋ ነገሩን እንዳማረው እየፈፀመና እርሻውን እያረሰ ሲኖር ሲኖር ሲኖር ዘመቻው አልቆ ልማት የሚያለሙ ሚሽነሪዎች እዛው ገጠር ሄደው ያንኑ ሰው አገኙት «ፈጣሪ አለ፣ እንደውም ለአንተ ብሎ ሙቶ ተሰቅሎ . . . » ብለው ክፉኛ ሰበኩት፣ አመነ! ቤተክርስቲያን በስንት ጊዜው ሲሄድ «ምነው ከግዚሃር ቤት ጠፋህ» ቢሉት
«እኔማ ምን መጥፊያ አለኝ፣ እግዜሩ ራሱ በየተራ ሰው እየላከ ቦግ እልም ያደርጉብኛ እንጅ» አለ አሉ!

By Alex abrham

@wegoch
@wegoch
@paappii
እንደቆመብኝ ዓለም አይቶኝ ቢሆንስ ?
(አሌክስ አብርሃም)

ይሄ የተረገመ ኮሮና ሳያጠፋፋን በፊት አንድ ሶሪያዊ ጓደኛ ነበረኝ …ከመሬት ተነስቶ ኢትዮጲያን ይወዳል …በተገናኘን ቁጥር ግብፅን ተባብረን እንረግማለን እናማለን ! አገሩ የዩኒቨርስቲ መምህር ነበር ፣ወሬን እሱ ያውራት! ስንትና ስንት መከራ አልፎ ነው አሜሪካ የገባው ግን ሁልጊዜ ሳቅ ከፊቱ ላይ አይጠፋም አወራሩ ራሱ የሆነ ድራማ ነው የሚመስለው ….

‹‹ሚስቴ ጋር የተለያየነው የጋብቻችን ቀን ማታ ነው ›› አለኝ

‹‹አግብተህ ነበር ?››

‹‹ታዲያ! ያውም አይኖቿ እንደዳይመንድ የሚያንፀባርቁ ….ሳቋ ልብህን እንደሳሙና አኩረፍርፎ የሚጨርስ …የእጆቿ ጣቶች እንደባህር እንጉዳይ የሚስልከለኩ ….ከንፈሯ …የሚሳም ሳይሆን እንደአቮካዶ ጁስ በወፍራሙ ፉት የሚባል ዓይነት ….››
አገላለፁ አማሎኝ ‹‹እህት አላት ?›› ልል አስቤ ከአፌ ላይ መለስኩትና

‹‹እድለኛ ነህ ›› አልኩት

‹‹አይደለሁም ባክህ !››

‹‹ምነው? ››

‹‹የጋብቻችን ቀን ማታ … ከተማችን ውስጥ አለ ወደሚባል ኢንተርናሽናል ሆቴል ነበር የሄድነው …እዛ ነው ክፍል የተያዘልን …ሰፊ ይሄን አዳራሽ የሚያክል ክፍል ! በአበባ በተሞላ ክፍላችን ውስጥ ገብተን …የጓጓሁለትን ሰውነቷን በምኞት እየተቃጠልኩ አያለሁ !ጫማወቿን ስታወልቅ በሂና የተዋቡ በወርቅ አልቦ ተተሸቆጠቆጡ ከአንተ የእጅ ጣት የረዛዘሙ ውብ የእግር ጣቶቿ ….ሽፍንፍኗን ከፀጉሯ ላይ ስታነሳው ወገቧ ላይ የሚገማሸር ከክረምት ጨለማ የጠቆረ ውብ ፀጉሯ ….የሙሽራ ቀሚሷን ስትከፍተው የወርቅ ሃብል የሚጫወትበት የብርሃን ሜዳ የመሰለ ሰፊ ደረቷ ….ግራና ቀኝ ሙሉ ጨረቃቃ የመሳሰሉ ክብ ጡቶቿ …ከተፈጠረች እህል ቀምሳ ታውቃለች ወይ የሚያስብል እንዲህ በአንድ አጅ መዳፍህ የምትከበው ውብ ሽንጥ ….ወረድ ስትል በእቅፍ የማትደርሰው ኩርት ያለ ዳሌ ….

ምራቄን ዋጥኩና ‹‹እና ምን ተፈጠረ ?›› አልኩት

‹‹በቃ ያደረገችውን የወርቅ ጌጣጌጥ ሁሉ አወላልቃ ራቁቷን ስትሆን …ወርቅኮ ውበት ይቀንሳል አልኩ …ወርቁን ስታወላልቅ ውበቷ ወጣ ….በቃ እሷን ፈዝዠ ስመለከት የራሴን ልብስ ማውለቅ ረስቸ ነበር ….ወላሂ ! ስልምልም እያለች ‹‹አውልቅ እንጅ ›› ስትለኝ የድምፅዋ ፍስስስ ማለትና መለስለስ እንኳን ልብስ ቆዳን ማውለቅ ያስመኛል .... የአልጋ ልብስና አንሶላውን ገለጥ ሳደርገው የገነት በር የተከፈተ ነበር የሚመስለው …ሽቶው …በቃ በሽቶ የታጠበ አንሶላ በለው ….በባህላችን እንደዛ ነው ….ቀስ ብላ በነዛ ረዣዥምና ውብ እግሮቿ ወደአልጋው ሳብ ሳብ ሳብ እያለች …ስትመጣ በቃ እንደዚህና እንደዛ ጠረጴዛ …ነበር ርቀታችን ….. ፈገግ ብየ ስመለከታት ጅስሜ ሁሉ እንደእሳት እየነደደ ወንድነቴ ሁሉ ከተፈጠረ እንደዛ ቁሞ አያውቅም …እንኳን ሌላ ጆሮየ ቁሞ ነበር …ፀጉሬ ቁሞ ነበር ….

ድንገት አልጋው ጋ ልትደርስ አንድ ሁለት እርምጃ ሲቀር ያለንበት ሆቴል ምድር በሚያናጋ ፍንዳታ ወደፍርስራሽነት ተቀየረ …. የማስታውሰው እነዛ ውብ አበቦች በአየር ላይ ሲንሳፈፉ ነው .... ክፍሉ በአቧራ ብናኝና በሚፈነጣጠር እቃ ሲሞላ ነው …በቃ !!›› ብሎ ትክዝ አለ

‹‹ምን ተፈጠረ ከዛ …ባለቤትህ ….?››

‹‹እኔጃ ! የነቃሁት ከምንኖርበት ከተማ ውጭ ቃሬዛ ላይ ተሸክመውኝ ሲሮጡ ነበር …ከተማችን በጦርነት እየተናጠች ነው …ከሳምንት በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ካምፕ ገባን …ሚስቴ ትኑርም ትሙትም አላወቁም አላገኟትም …ከሶስት ዓመት በኋላ እዚህ ያሉ ቤተሰቦቸ ጋር መጣሁ …ፈለኩ አስፈለኩ በቃ አልተገኘችም …. የአላህ ....ህልም ነበር የምትመስለው ! ከሁሉም ግን እስካሁን ሳስበው የሚያስቀኝ ....›› ወዲያው ከትካዜው ወጥቶ መሳቅ ጀመረ

‹‹የሚያስቀኝ ምን መሰለህ? …ከፍንዳታው በኋላ ሲያገኙኝ …እንደዛ እንደቆመብኝ ይሆን ?….እያልኩ እስቃለሁ …ሃሃሃሃሃሃሃሃ ›› ጎርናና ሳቁ አካባቢውን ሞላው ...የነበርንበት ኮፊሾፕ ውስጥ የነበሩት ሁሉ ዙረው አዩን ...ማን ያምናል ያሳቀውን ነገር ቢሰማ …

‹‹…አስበኸዋል ? አልጀዚራ ፍንዳታውን ሲዘግብ እኔ ራቁቴን ከፍርስራሽ ውስጥ እንትኔን ሚሳኤል አስመስየ ተጎትቸ ስወጣ ….የአላህ ! ጦርነት ክፉ ነው ...አገርህንም አንተንም ከነገመናህ ነው ለአለም የሚያሰጣህ ››

@wegoch
@wegoch
@paappii
ጫካ ውስጥ አንዱ ዝንጀሮ ዛፍ ላይ ሆኖ ቅንዝርርር ይልበታል; እናም ካቅሙ በላይ ሲሆንበት ታች ያለው አንበሳ ጀርባ ላይ ጉብ ብሎ ፀጉሩን እንቅ አርጎ ይሰርረዋል …

አንበሳው ከጀርባው ለማውረድ በዚህ በዛ ሲታገል ዝንጀሮ እንቅ እንዳረገ ይጨርስና ወርዶ ላጥ ይላል …
አንበሳውም ተደፈርኩ ብሎ ሲያባርረው ዝንጀሮ ሆዬ በሆነች ቅያስ እጥፍ ብሎ ሌላ ዝንጀሮ በመምሰል ዱቅ ብሎ ጋዜጣ ማንበብ ይጀምራል፦

አንበሳው ይደርስና "የሆነ ዝንጀሮ በዚህ ሮጦ ሲያልፍ አይተሃል" ሲለው

"አንበሳውን የነፋው?" ይለዋል …

ይሄኔ አንበሳው ድንግጥ ብሎ ፦

"ከመቼው ጋዜጣ ላይ አወጡት? 🤔"

By hasen enjamo

@wegoch
@wegoch
@paappii
ሰውዬው በድመቱ ይበሳጭና አውጥቶ ይጥላታል። ምሽት ላይ ድመቷ ወደ ቤት ትመለሳለች።በማግስቱ እንደገና ራቅ ወዳለ ስፍራ ወስዶ ይጥላታል። ይሁንና እሱ እቤቱ ሳይደርስ ድመቷ ቀድማው ደርሳ አገኛት። ንዴቱ የባሰ ጨመረ፣ ደሙ ፈላ። ከዚያ በጆኒያ አድርጎ እርሱ ራሱ ወደማያውቀው ሌላ ከተማ ወስዶ በጣም ውስብስብ ባለ ሰፈር ውስጥ አዙሮ፣ አሽከርክሮ ጣላት። ይሁንና  ይህን እርምጃ ከወሰደ በኋላ እሱ ራሱ እንዴት ወደ ቤቱ ይመለስ? ቢዞር፣ ቢሽከረከር መንገዱ ጠፍቶት ወደ ቤቱ መመለስ አቃተው። የመጨረሻ ሲጨንቀው ወደ ቤቱ ስልክ ደወለና ባለቤቱ ስልኩን አነሳች   ....
ባል: ሄሎ ሃኒ

ሚስት: ሄሎ የት ጠፋህ የኔ ማር?

ባል: ትንሽ ለጉዳይ ወጣ ብዬ ነው። ድመቷ አለች?

ሚስት: አዎ  ምነው?

ባል: አንዴ አቅርቢልኝ  😅

By hasan enjamo

@wegoch
@wegoch
@paappii
"አንድ ሽበት ታያለህ ፀጉሬ ላይ?" አለኝ አንገቱን ጎንበስ አድርጎ

"አይይይ..." አልኩ አንገቴን ከግራ ወደቀኝ እየነቀነኩ

"አየህ... የእኔ ሚስት እናት በላት። ያኖረችኝ እንደ እናት ነው። ተግሳፅዋም፣ ፍቅሯም፣ እንክብካቤዋም፣ አሳቢነቷም ልክ እንደ እናት...ይገርምሀል ሳገባት ለብዙ ሰው መሳለቂያ ሆኜ ነበር...የሆነ ማዕበል ነው የተነሳብኝ..."

ለምን?

"በእኔና በእሷ መካከል ያለው የዕድሜ ልዩነት የተለመደ አልነበረም። 13 ዓመት ትበልጠኝ ነበር። እኔ የ27 ዓመት እያለሁ እሷ 40 ዓመቷ ላይ ነበረች። ይህ ነገር ብዙ ሰውን አስገረመ፣ ቤተሰብ ተንጫጫ (እናቴን ጨምሮ)፣ ጓደኞቼ በሙሉ አሽሟጠጡ አሾፉ፤ በሄድኩበት ሁሉ "ምነው ምነው አንተ?፤ ምነው ብጤህን ብትፈልግ?" እያለ አሸማቃቂው በዛ፤ ደግነቱ እኔ ላመንኩበት ነገር ምድር ከፍ ሰማይ ዝቅ ቢል አንድም ለውጥ አላደርግም። እናም እሷ ትበልጥብኛለች ብዬ 'አዲዮስ' አልኳቸው። አኮረፉ... ፍጡር የተባለ ሁላ ነው ያኮረፈኝ ከሚስቴ ውጪ፤ ርቀን ብቻችንን መኖር ጀመርን። በሄድንበት ሁሉ ባለትዳር መሆናችንን አይቶ ተገራሚው ቢበዛም 'ወይ ፍንክች' አልን፤ ኃላ ኃላ ነገሩን ተላመድነው። በዓመቱ መንታ ልጆች ወለድን ሁለት ወንድ፤ እነሱ በተወለዱ በሁለተኛው አመት አንድ ሴት ልጅ ደሞ ደገምን።

በስመአብ እንዴት ደስ ይላል...አሁን ስንት ዓመትህ ነው?" አልኩት ነገሩ እያስገረመኝ።

"አሁን 50 አለፍኩ...ልጆቼም ጎርምሰዋል"

"ኦ አትመስልም ግን...ልጆችህ አብረውህ ነው የሚኖሩት"

"ሴቷ ከእኔው ጋ ነች ወንዶቹ ውጪ ሀገር ሄደዋል።...ባለቤቴ የተረጋጋ ህይወት ነበር ያኖረችኝ...በጣም ነው የምወዳት፤ እሷ ደሞ ስትወደኝ የእኔን ሺ እጥፍ አይበቃውም፤ ብዙ እንክብካቤ ነበረኝ። እኔም በሁሉም ነገር እጅግ እታመንላታለሁ (ታምነኛለች) ፣ ከሰው ሀሜታ ሁሉ በፍቅር እሸፍናታለሁ...ቅንጣት እንዲከፋት አልፈልግም። ለነገሩ ቀስ በቀስ ሰዉም ስለእኛ ማውራቱን እርግፍ አድርጎ ተወ...ያው ተረቱ "ጉድ አንድ ሰሞን ነው" ይባል የለ። የሚገርምህ ያኔ ሲስቁብኝ የነበሩ ጓደኞቼ ዛሬ ከፊሎቹ በህይወታቸው የተረጋጉ አይደሉም...አንዳንዱ ቤተሰቡን በትኖ ጤና የማይሰማው አለ...አንዳንዱ ኑሮ እና ሚስቱ አቃጥለው ጠብሰውት ዕድሜው ትንሽ ሆኖ ግርጅፍ ያለ አለ... አንዳንዱ ያለ ትዳርም የሚኖር አለ። ብቻ ምን ልበልህ..."

"ይገርማል ...ባለቤትህስ ታድያ?"
"አልፋለች። ሁለት ዓመት ሊሞላት ነው ካለፈች።"

ይቅርታ

"የጤና ረዳት ነበረች። ክፍለ ሀገር ለስራ እንደሄደች በወባ ምክንያት ታማ ነው የሞተችው።የሚገርምህ ስትሄድ ውስጤን ብዙም ደስ አላለውም ነበር።ያው የስራ ነገር ሆነና ሄደች በህይወት አልተመለሰችም።" ትክዝ አለ። ፊቱ ላይ ጥልቅ የሆነ ሀዘን አ ሳየኝ

"ይቅርታ...መጥፎ ትዝታ ጣልኩብህ " አልኩ

"አይ ምንም አይደል...ባይገርምህ አሁን ጎኔ እንዳለች ነው የሚሰማኝ...ከህልፈቷ በኃላ የመጀመሪያ ዓመት ላይ እጅግ ከብዶኝ ነበር። ኋላ በልጆቼ ተፅናናሁ በተለይ ሴቷ ልጄ የእናቷን መልክ ከነ ልቧ ነው የወረሰችው...ይመስገን በእነሱ ተፅናናሁ።...ትዳር ውስጥ ስትገባ አብዛኛው የሚስማማበትን ሳይሆን...ለአንተ የምትስማማህ ላይ ወስን...ያኔ ምንም መናወጥ የሌለበት ባህር ላይ ታንኳህን እንዳሳረፍክ ይገባሀል። ምክንያቱም ከታደልክ የዘላለም ህይወትህ ነው።" ቀና ብሎ አየኝ። ባለ ሙሉ ልብነቱ ከአወራሩ ያስታውቃል። ስልኩ ጠራ "ህምምም ...አየህ እቺ የእናቷ ቢጤ ደወለች..." ፈገግ እያለ ስልኩን አንስቶ ስፒከር ላይ አደረገና በዓይኑ ስማት ብሎ ምልክት አሳየኝ
"ሄሎ አባቢ...የት ነህ?"
"አለሁ...እዚሁ መናፈሻው አካባቢ ቁጭ ብዬ ነው..." ልክ በዓይኑ እንደሚመለከታት ነው ድምፅዋን በስስት ነው የሚሰማው

"አይ ይሁን ...አትገባም ወደ ቤት ንፋስ እንዳይመታህ... ምግብም አስቀምጬልሀለሁ ቡና ከፈለክ አለልህ ሞቅ አድርገህ መጠጣት ነው...ወይ በዛው ሳልፍ ላግኝህ እንዴ?"አለች። ስታወራ በፍጥነት ነው መልስ እስኪመልስላት አትጠብቅም
"ነይ እሺ...ትላንት የጠየቅሽኝንም ትወስጃለሽ በዛው"
"መጣሁ እሺ..."ብላ ስልኩ ተዘጋ።
"ተመለከትክልኝ በዚህ ሁሉ ፍቅር መሀል ሆኜ እርጅና ከየት ይመጣል ብለህ? ሀ ሀ ሀ ሀ😊... እስካሁን ግን እኮ አልተዋወቅንም...ስምህን ማን ልበል?" አለኝ። ለካ ድንገት እራሴን ላናፍስ ብዬ በገባሁበት መናፈሻ ቦታ ነው ድንገት ከዚህ ሰው ጋር አብረን ተቀምጠን ወግ የጀመርነው።

"አብርሃም እባላለሁ...እኔስ ማን ልበል?"

"እኔ አድማሱ እባላለው። እዚህ አካባቢ አይቼህ ግን አላውቅም... እዚህ ነዋሪ ነህ?" በደንብ ልብ ብሎ እያየኝ ጠየቀኝ...
"አይ እኔ እንኳን ለዘመድ ጥየቃ ከዝዋይ ነው የመጣሁት በዛውም አንድ ጉዳይ ነበረኝ...እዚህ ፀሀዩም ከረር ሲልና ቦታውን ሳልፍ ስለወደድኩት ገብቼ ቁጭ አልኩና ተገጣጠምን። "
"ግሩም ነው።እኔም ቦታውን እጅግ ነው የምወደው ለቤቴም ቅርብ ነው።ብዙ ጥሩ ጥሩ ተጨዋወትን!...ያቿትልህ አበባዬ መጣች..." ቀና አልኩኝ... እውነትም አበባ እየተራመደ መጣ። ከቁመቷ ዘልግ ማለት፣ከመልኳ ጥራት፣ከዓይኗ፣ከጥርሷ፣ከአፍንጫዋ ምኗንም ጥንቅቅ አድርጎ ነው የሰራት...ቅልጥፍናዋ ከአረማመዷ ያስታውቃል። ደነገጥኩ።
አባቷን አቅፋ ሳመች። ወደ እኔ እጇን ዘረጋች "አብርሃም ይባላል። የዝዋይ ልጅ ነው።" አላት አባቷ ትከሻዬን ነካ አድርጎ እያስተዋወቃት። እኔ ዝም ብዬ እጄን ዘረጋሁ። ከአባቷ ጋ የረጅም ግዜ ግንኙነት እንጂ፤ ፈፅሞ ዛሬ የተገናኘን አንመስልም።
"አበባ..." አለችኝ። ውበቷ በጣም ነው ያስደነገጠኝ። አባቷ ሳይታዘበኝ አይቀርም። በራሴ አፈርኩ።"ታድያ እቤት ይዘኸው አትመጣም ነበር? ከአንድ ሰዓት በፊት ብትመጡ እኮ ቡና አፈላላችሁ ነበር።ደሞ ምግብም አብ ስዬ ነበር። ቅድም በስልክ አልኩህ አ? አስቀምጬልሀለው። ቡናውንም እንዳልኩ" አለች ሁለታችንንም እያየች...ስታወራ ምንም መልስ እንደማትጠብቅ አሁን ይበልጥ ተረዳሁ።

"እሱም ተፈጥሮ ወዳጅ እኔም ተፈጥሮ ወዳጅ...ጨዋታ ይዘን ከዚህ ቦታ መነሳቱ እንዴት ይሁንልን ብለሽ ..." ብሎ በዓይኑ ተመለከተኝ። ጭንቅላቴን በአዎንታ ነቀነኩ...

"እሺ ይሁን በቃ ሌላ ቀን ...አሁን ስጠኝና ልሂዳ ረፈደ...ጓደኛዬም እየጠበቀችኝ ነው።"አለች። ብር አውጥቶ ሰጣት ወይ የትራንስፖርት ይሆናል፣ ወይ የትምህርት ቤት አልያም ለሌላ ይሆን ይሆናል።ከተቀበለችው በኃላ ተሰናብታን በፍጥነት ሄደች። ከዓይናችን እስክትሰወር በዓይኑ ተከተላት።ዓይኑ ላይ ጥልቅ ትዝታ አለ።
"...እና መች ነው ወደ ከተማህ የምትመለሰው?" አለኝ ከዓይናችን ከተሰወረች በኃላ ወደእኔ ተመልሶ

"አይ ትንሽ መቆየቴ እንኳን አይቀርም። የምጨርሳቸው ጉዳዮች አሉኝ።" አልኩ

"የምረዳህ ነገር ካለ አለሁ፤ ብዙ ግዜ ከዚህ ቦታ አልጠፋም። እሁድ እንደውም ቤት ብትመጣ ደስ ይለኛል።በዚህ አቅጣጫ 100 ሜትር ሄደህ በግራ ስትዞር አንድ ሱቅ አለ፤ ከእሱ ቀጥሎ ያለው ሰማያዊ በር የኔ ነው።እንዳትቀር አጠብቅሀለው።በል ሰላም ሁን ልሂድ" ብሎ ከመቀመጫው ተነሳ።
"እሺ...መልካም ቀን..." ብዬ ቆሜ ተሰናበትኩትና ቁጭ ብዬ ከዓይኔ እስኪሰወር ከጀርባው አስተዋልኩት። ተክለ ሰውነቱ በእርጅና አንድም ንክች አላለም። የሚመስለው ገና የ 40 ዓመት ወጣት ነው።ለካ ዙሪያችን አድርገን የምንሸከማቸው ሰዎች ናቸው የሚያጎብጡንም፤ የሚያቃኑንም።

by Abrham. F Yekedas

@wegoch
@paappii
2025/06/28 10:21:56
Back to Top
HTML Embed Code: