Telegram Web Link
#የረቢዕ _ናፋቂ_
በዒስነይን መደድ

ነቢ ያንቱ መዉሊድ ናፋቆት ሲበዛብን
አምና እንዳከበርን ቀን መቁጠር ጀመርን
አንድ, ሁለት ስንል ከወጣ ጀምሮ
ይሄው ደረሰልን ወራቶቹን ዞሮ
ይህ የደስታችን ቀን በጣም ርቆን ነበር
እጂግ ስለጓጓን ደርሶልን ለማክበር
ተርቦ ምግብን ጓጉቶ እንደ መጠበቅ
ደርሶ ሲቀርብልን ዘሎ እንደመፈንደቅ
ድግስ ተደግሶ ሰርግ እንደመጠበቅ
የጓጉለት ደርሶ ቀኑን እንደመቦረቅ
ዘጠኙን ወራቶች እንደምትቆጥረው
እናት ልጇን ጓጉታ እንደምትጠብቀው
ለአንድ ነገር ጓጉቶ ሆዱ እንደሚባባው
ውሀ ጥም አስክሮት ከመንገድ እንደገባው
የደረሰበት ነው ስሜቱን የሚያውቀው
ከዚህ በላይ ነበር ጓጉተን የጠበቅነው
ረቢዑ ደርሶ ቀናቶች ሲቀሩት
ያ የአንቱ አፋቃሪ ናፋቆቱ ጠናበት
ወሩ ላይ ለመድረስ ቀናት የቆጠረው
ማሰብ ይጀምራል የት እንደሚያከብረው
ማለት ይጀምራል ቀናቶች ሲቀሩት
እነዚያ ደጋግ ቦታወች እየታዮት
ነጃሽ እና ንጉስ መጂት እሄዳለሁ
አና #ዳናላይ ገታም አከብራለሁ
ደገር እጓዛለሁ ቃጥባሪም አልቀርም
መውሊድ ከደረሰ ዛሬ ነገ አልልም
ከጫሊ አልቀርም ዘንድሮ እሄዳለሁ
አብሬቶችም ሄጄ እዘክሮታለሁ
ማይባር አርባጫማ ደግሞ ቢለን
እኔስ እሄዳለሁ ልዘክር ነቢን
ባጃ ወረባቦ ደሴ ደረቅ ወይራ
ግራር አምባ ደገር ደግሞ መንደራ
ረቢዑ ይለፋ ስምሁን ስጠራ
ቦረና ገረዋ ደግሞ ጥሩሲና
ዘንድሮ አልቀርም ከደረስኩኝ ደህና
ምኞቴ ሰምሮልኝ ካሳካው ረቡና
መውሊድ አከብራለሁ ሀገርሁ መዲና
በሄደበት ሁሉ የሚዘክርሁ
ይሄው ነው ምኞቱ የእውነት አፋቃሪሁ
በአለም ላይ ያለው የሙስሊሙ ኡማ
መውሊድን አይጠላም ካልሆነ ጠማማ
አንድ ወር ቀርቶታል ሚን ሸህሪሂ ሶፈር
ከሁሉ ይደምቃል #ዳና_ልዩ_ሰፈር!!!!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
እዉነታን እንደ እዉነታዉ ማስቀመጥ እና መከፋፈል የተለያየ ነዉ

ከጅምሩ አትከፋፍሉን የሚለዉ ንግግር ልሂቃኖች "كلمة حق اريد به الباطل" እዉነተኛ ቃል ነገር ግን ስህተት የተፈለገበት እንደሚሉት ነዉ ። አንዳድ ነገሩን ከመሰረቱ ያልተረዱ እና እስልምና ትላንት እሱ ሲወለድ የመጣ የሚመስለዉ አትከፋፍሉን ይልሃል ወዳዉ እራሱ እከሌ እከሌ ብሎ ይከፋፍላል ። መጀመሪያ በልቡ ከፋፍሎ ከጨረሰ በኋላ አትከፋፍሉን ይላል ። ይህ ማህበረሰብን እያታለሉ የራስን አስተሳሰብ እና አስተምህሮ ለማስረጽ የማመቻቸት ስራ ነዉ።

ጉዳዩን ከመነሻዉ ስናየዉ

የአሏህ ነብይ ሰይዳችን በሂወት በነበሩበት ጊዜም ሆነ ከዛ ቀጥሎ በነበረዉ ትዉልድ
ሁሉም ከመሰረቱ የተቀዳ አስተምህሮት ስለሚደርስቸዉ ማንም በእስልምና መሰረታዊ አስተምህሮ ላይ የተንሸዋረረ አመለካከት አልነበረዉም ፣ቁርአንም የወረደዉ በቋንቋቸዉ ስለሆነ ለቋንቋቸዉ ከፍተኛ ቦታ ስለሚሰጡ ቁርአንና ሃዲስን ያለ አግባብ የሚረዳም አልነበረም ።

ከዛ ትዉልድ በኋላ እስልምና በከፍተኛ ሁኔታ በተስፋፋበት በሶስተኛዉ መቶ ክፍለ ዘመን የተለያዩ ፊርቃዎች መምጣት ጀመሩ ከነሱ መካከል ሺዓ፣ሙዕተዚላ እና ቀደርያ ፣ከራሚያ የሚባሉ (አሏህን አርሽ ላይ አለ የሚሉ) ሙሸቢሃዎች ፣ ሌሎችን የተለያየ ጽንፍ ይዘዉ ተከሰቱ።

በዚህ ሰአት ለትክክለኛዉ ከነብዩና ከሶሃቦች ለተቀዳዉ አስተምህሮት ሁለት ጉምቱ አሊሞች አቡልሃሰን አላሻሪይ እና አቡመንሱር አልማቱሪዲይ በአሏህ እገዛ የሙስሊሞችን እምነት እና አቂዳ አስጠበቀዉ ከዛ በኋላ የሚመጡ አሊሞች በሙሉ አሽዓርይ እና ማቱሪድይ ይባላሉ ።
ሙስሊሞች ናቸዉ እስልምናን አስቀጣይ ናቸዉ ነገር ግን በስልምና ስም የሚነግድ ስለበዛ ሙስሊሞች በነዚህ ሁለት አሊሞች እንቅስቃሴ አቂዳቸዉም ተጠበቀ። ለዚህም አሻአሪይ ማቱሪድይ ተባለ ልክ የፊቅህ ጉዳይ በአራቱ መዝሃብ እንደተደራጀዉ ሁሉ ማለት ነዉ። እኔ ሻፊዒይ ነኝ ሃነፍይ ነኝ እንደሚለዉ። (ያ ካልሆነ እኔ እኔ ናቹራልም ሶሻልም አደለሁም እንደሚል የዩኒቨርሲቲ ተማሪ ይሆናል)።
ሱፋያነትም በስልምና ዉስጥ እንደ ሱሉክ እንደሚታየዉ ሁሉ ማለት ነዉ።

ከዛ በአራቱም መዝሃብ አሊሞች የጋራ ስምምነት እስር ቤት ታስሮ የሞተዉ የሃሸዉያዎች መሪ ተከታዮቹ ሼኽ ኢብን ተይሚያ የሚሉት እና ከዛ በሂጅራ 12ኛዉ ክፍለ ዘመን ሳኡዲ አረቢያ ከመመስረቷ ከ150 አመት ቀደም ብሎ ሳኡድ የተባለዉ የአይሁድ ቤተሰብ ጋር ቃልኪዳን አስሮ ዲንን በመጀደድ ስም የተንቀሳቀሰዉ ተከታዮቹ ሼኽ ሙሃመድ ቢን አብዲል ወሃብ ይሉታል በርካታ ሙስሊሞችን በመግደል (ለሚያነብ ሰዉ በመቶዎች የሚቆጠር መጽሃፍ ማስረጃ አለ)
ይህንን የአሻዒራ እና ማቱሪድያን አቂዳ ልማጥፋት ተንቀሳቅሰዋል ብዙ ጥረቶችን አድርገዋል።

ምንም እንኳን አሁን ሳኡዲም ዉሃብያን ስናስፋፋ የነበረዉ የሶቬት ህብረትን በመካከለኛዉ ምስራቅ የሚያደርገዉን እንቅስቃሴ ለመከላከል ከአሜሪካና እንግሊዝ ጋር ተስማምተን ነዉ ብለዉ ቢቀበሉም ።
ይህንን አስተሳሰብ በመደገፍ ሙስሊሙን ዲንህ ተነካ ብሎ በሩሲያ ሲመራ የነበረኡ ሶቬት ህብረት ለማዳከም ነዉ ብለዉ በቅርብ በወጣ ዜና ይገልጻል በዚህ ማስፈንጠሪያ ያገኙታል ሌሎችም ይንን የሚገልጹ በርካታ ዘገባዎች እና ዶክመንተሪዎች አሉ ።
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
ኢኽዋን ማለት በግብጽ በ20ኛዉ ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ከ ኦቶማን ኢምፓየር መዉደቅ ጋር ተያይዞ የአሻሪይ እና ማቱሪድይ አቂዳ ተከታይ በነበረዉ እና ቤተሰቦቹም ይህንን መንገድ ሲከተሉ ከነበሩት ሃሰኑል በና የተወሰኑ ወጣቶችን ሰብስቦ የመሰረተዉ ጀመዓህ ነዉ ይህ ጀማዐህ ከምስረታዉ ከተወሰኑ አስርት አመታት በኋላ በስነጽሁፍ ችሎታዉ የሚታወቀዉ ሰይድ ቁጥብ ሙሉ በሙሉ ተዘወረ በሂደት ከላይ በጠቀስኩት የወሃቢዝም አስተሳሰብ ተቀላቀለ
በአሁን ሰአት ሙስሊም ብራዘር ሁድ የሆነ አከባቢ የአሻሪያ ወልማቱሪድያ አቂዳ ያላቸዉ ወደዚህ ጀማዐህ ይጠጋሉ ፣እንደ ሃገራችን እና በርካታ ሃገራት ግን ይህ ጀማዓህ ሙሉ በሙሉ በወሃብያ አስተሳሰብ ተከታዮች የሚያራምዱት እና የተመቻቸ ሁኔታን ካገኙም ይህንኑ አስተሳሰብ ለማንገስ እና የአሻሪያ ወልማቱሪዲያ አስተሳሰብ ያላቸዉ አሳደዉ ማጥፋት ይፈልጋሉ።

የወሃቢዝም አስተሳሰብ ከአስተምህሮቱ አስፈሪነት የተነሳ አንድም ሃገር ላይ ለማስረጽ አይቻልም ነበር ከኢኽዋን ጋር በጋራ ተናበዉ መስራት ከጀምሩ በኋል አንዱ ሙስሊሞችን አትከፋፍሉ ሙስሊም ነን ይላል በጎን የአስተሳሰብ አጋሩ ደግሚ የአሻሪና ማቱሪድይ አቂዳ እና እምነት ተከታዮችን አስደዉ ያጠፋሉ ። ኢትዮጲያም ላይ ያለዉ እዉነታ ይሄ ነዉ ምንም እንኳን የማይስማሙበት እና እስከ መገዳደል እና መጣፋፍት የኢደርሱበት አጋጣሚዎች ቢኖሩም።

የሱፍያን ጽንሰ ሃሳብ በሚመለከት ግን በነብዩ ዘመን እስልምናን ለማገልገል እና ለጂሃድ ብቻ የትቀመጡ ለዱንያ ምንም ግድ የሌላቸዉ አሏህ ያወደሳቸዉ አህሉ ሱፋዎች የአሏህ ምርጥ ባሮች የሱፍያነት እዉነተኛ ማንነትም የተቀዳዉ ከነዚህ ነዉ። እንዲሁም ኢህሳን ከሚለዉ ጽንሰ ሃሳብ ከያዘዉ ታዋቂ እና የእስልምናን ማእዘናት እና የኢማንን ማእዘናት ካካተተዉ ነብያዊ ሃዲስ የተቀዳ ነዉ።

ሱፍያነት አስተምህሮት አይደለም ሱፍያነት እስልምናን በትክክለኛዉ አመጣጡ ቀድቶ በእዉቀት በመጎልበት አካላዊም ሆነ ዉስጣዊ ክፍሉን ለኻሊቁ ማስገዛት ። ሱፍዮች ለንዋይ እና ለቅርቢቱ አለም ግድ ዬሌላቸው ናቸዉ።

አህባሽን በሚመለከት የአሽአሪያን እና ማቱሪድያን አስተምህሮ የሚያስቀጥል ጀማዐህ ነዉ ከጀመዓዉ መስራቾችም እንደምንረዳዉ አላማዉ ይህ ነዉ ታሪካቸዉም ይህ ነዉ ። አሁንም የሚንቀሳቀሱት ለዚሁ ነዉ ሱፍያነትንም በኩራት መንገዳችን ነዉ ብለዉ ይቀበላሉ ።

ከራሚያ፣ሃሸዉያ፣ወሃብያ (በየዘመኑ የተሰጠ ስም ነዉ) በአሁን ሰአት ከመስራቹ በኋላ በተከሰተ መከፋፈል
ሃዳድያ፣መድኸሊ፣ሰለፊ(ስያሜ) ሌሎችም ጀማዓዎች ወጥተዋል ።
ከዚህ አስተሳሰብም በርካታ አለም አቀፍ የሽብር ቡድኖች መነሻችን ይህ አስተምህሮት ነዉ ብለዉ በራስቸዉ አንደበት ተቀብለዋል።

ለማጠቃለል ያክል
አትከፋፍሉን እያሉ የራስን አተሳሰብ ማንገስ አሁን ላለዉ የኢትዮፒያ ሙስሊም አሽዓሪይ እና ማቱሪድይ አቂዳ ተከታይ በሱፍይነት መንገድን የሚኮራ ሙስሊም አያስኬድም።

ስለዚህ አስተምህሮ ደረጃ የምናወራ ከሆነ
አሽዓሪያ እና ከላይ በተለያየ ስም የጠቀስኩት ወሃብያ የምናስተያይ ሲሆን

ተሰዉፍ ግን አስተምህሮት አይደለም።
๑ኢብኑ ጀዉዝይ [ረዲየሏሁ ዓንሁ] እንድህ አሉ፦
“ኢብሊስ መጀመሪያ በሰዎች ላይ የሚሸፍንባቸው እውቀትን ነው፥ ምክንያቱም እውቀት ብርሃን ነው ብርሐናቸው ከጠፋ በጨለማ ውስጥ እንደፈለገ ያደርጋቸዋል። ”

" أول تلبيس إبليس على الناس صدُّهم عن العلم، لأنّ العلم نور، فإذا أطفأ مصابيحهم خبّطهم في الظلم كيف شاء ".

"تلبيس إبليس"
ኢብሊስን ማሸነፍ የምትችለው በእውቀት ብቻ ነው። ለእውቀት ቦታ ስጥ ....!
••••••••••••••••••••••••••
ሙሐረም -18|1444ሒ.
JOIN 🖇
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
《ኢነማ ዩዕረፉ አሪጃሉ ኢንደ አሸዳኢድ》
የጭንቅ ቀን ነው ወንዱ የሚለየው
ሸኸ ሰዒድ የኢትዮጲያ ብሩክ ማህፀን ከፈራቻቸው ጀግኖች መካከል ግንባር ቀደም የሚጠቀሱ የቁርጥ ቀን መሪያችን በወሬ ሳይሆን ሁሌም በተግባር ጠላቶቻቸውን 10 እርምጃ የቀደሙ የዘመናችን አርጦግሮል ናቸው።
ታዳ ከነዚህ አንጋፋ የዲን መሪ ጎን መቆም የሁሉም ሙስሊም የነፍስ ወከፍ ግዴታ ነው።
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
የጋዜጠኝነት ስነምግባርን በሚያንኳስስ መልኩ እየሠሩ የሚገኙ አንዳንድ የመንግሥት ሚዲያዎች ተ/ሙፍቲ ሀጅ ዑመር ኢድሪስን ኢንተርቪው ሊያደርጉ ሄዱ::

<<አክብራችሁ በመምጣታችሁ አላህ ያክብራችሁ:: እኔ የምችለውን ሁሉ ለሀገሬ አድርጌ ተከብሬ ተቀምጫለሁ:: እናንተም በክብር ወደመጣችሁበት ተመለሱና ሥራችሁን በሐቅ ሥሩ >> ብለው ያለኢንተርቪው ሸኟቸው::
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
በእነርሱ ቤት ኢንተርቪው አድርገው ቆራር^ጠውና ከታት^ፈው ሊያቀርቡ! ሙፍቲ ዑመር እንኳንስ የአሁኖቹ ይሄ ሰር^ቀው የበሉበትን ድስት ኮፊያቸውን ከድነው የሚሄዱትን ቀርቶ ሲ^ሰርቁ በተሰ^ራቂው እስኪሳበብ ድረስ ቀድመው ሰነድ የሚያዘጋጁት እነበረከት ስምዖንም ሙፍቲ ዑመርን ሊሸውዱ ብለው አልቻሏቸውም:: ያኔ ጎረምሶቹ የታሰሩ ሰሞን ለማስፈታት ሙፍቲ ሽምግልና ገብተው ነበርና መግለጫ ለመስጠት የኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ተቀጥረው ካሜራቸው እንደማይገባ ሲነግሯቸው ቀርተዋል:: እነበረከትና ጌታቸው ረዳ በሙፍቲ ዑመር ላይ ሊለጣጥፉ ሽተው ነበርና::
__
በግርጌ ማስታወሻ:-
በአሁኑ ሀጅ ዶላር በብላክ ገብቶ ሁሉም ሀጅ ተመዝጋቢ ይሂድ ሲሏቸው በባንክ በሕጋዊ ከተገኘ የቻልነውን ሁሉ እንሞክራለን:: ካልሆነ ግን አላደርገውም ብለው እምቢ አሉ:: የሸራተን የቤር^goው መጅሊሶች በ24 ሰዓት ያሉት በብላክ ሊመቱት አስልተው ነበር:: መያዛቸው አይቀርም ነበር:: በብላክ አጫውተውት ቢሆን ኖሮ እስር ቤት ነበሩ:: ግን ሸይኾቻችን ጫፉም አይደርሱ:: ባሕሪያቸው አይደለምና::
__
በነገራችን ራስጌ የሁጃጅ ብር ተመለሰ እንዴ? ወይስ <<እምጷ ጅረኒ>> ተብሏል?
አል-ቂያሙሁ ተዓላ ቢነፍስሂ፦ በራስ መብቃቃት!!

➣አሏሁ ተዓላ  ከ’ርሱ ውጭ ካለው ነገር ሁሉ የተብቃቃ ነው፥  ማለትም እሱ አሏህ ወደ ቦታ ፈላጊ አይደለም፥ ቦታ ፍጡር ነዉ አሏህ ነዉ የፈጠረዉ ቦታን ሲፈጥር ደግሞ ከቦታ ሀጃ/ጉዳይ ኑሮት አይደለም። 
እንደዚሁም ቦታን የፈጠረዉ ለ’ራሱ ሊጠቀምበት አይደለም በአሁኑ ሰአት ያሉ አንድ አንድ #ወፍ_ዘራሽ_ሀይማኖት ያላቸዉ ሰዎች ለሱ ለአሏህ ቦታ የሚባለዉን ነገር ለአሏህ ያረጋግጣሉ።

#ወልዒዙቢላሂ_ተዓላ በነሱ አባባል አሏህ አርሽ ላይ ነዉ ተቀመጠ ተደላደለ በማለት ፈጣሪን ይሳደባሉ፥ ከመሳደብም አልፈዉ አሏህን ከፈጠረዉ ፍጡር ፈላጊ ያደርጉታል።  እንደዚሁም እሱን #አሏህን በፍጡር ባህሪ ይገልፁታል መቀመጥ የሚባለዉ ነገር የአካል ባህሪ ነዉ።
አሏህ ደግሞ #የአካል ፈጣሪ እንጅ አካል አይደለም። አሏህን አካል ነዉ ያለ ከእስልምና እንደሚወጣ #ኢማሙ_ሻፊዕይ ረድየሏሁ ተአላ አንሁ ሲነግሩን

وقال الإِمام الشفعي رضي الله عنه "المجسم كافر"رواه السيوطي

(አሏህን አካል ነዉ ያለ ካፊር ነዉ።) ©ሱዩጢይ ዘግበዉታል

•እንደዚሁም #የሀገራችን_ታላቅ_አሊም የሆኑት #አሸይኽ_አንይ ረሂመሁሏህ፦

قال الشيخ ا َلأَني" أَن الله تقدس وتنزه عن التجسيم والتعطيل والحلول"
.كفاية الطالبين (ص/٢)

“አሏህ ከአካል፥ የሌለ ነገር ከመሆን ፥ አንድ ነገር ዉስጥ ከመሆን የተጥራራ ነዉ።”
በማለት ኪፋየቱ ጧሊቢን 📚በተባለዉ ኪታብ ገፅ 2 ላይ አስቀምጠዉታል።


•እንደዚሁም አሏህ ቦታ አለዉ ብለዉ የሚያረጋግጡ ሰዎች አሏህን መጠን ነዉ እያሉ ነዉ፥ ምክንያቱም የግዴታ ቦታን የሚይዝ ነገር መጠን መሆን አለበት። አሏህን መጠን ነዉ ካሉ ደግሞ ግዴታ ለሱ መጣኝ  ያስፈልገዋል መጣኝ አስፈለገዉ ከተባለ ደግሞ ደካማ ነዉ ደካማ ደግሞ ጌታ ሊሆን አይችልም።

የኛ ጌታ ከመጠንም ሆነ ከቦታ የተጥራራ ነዉ ልክ #ኢማሙ_አልይ_ረድየሏሁ አንሁ እንዳሉት፦

قال الإِمام علي رضي الله عنه "من زعم ان الهنا محدود فقد جهل الخالق المعبود"رواه ابو نعيم في حلية اَلأَولياء

“ጌታችን መጠን (ማለትም አካል) ነዉ ብሎ የሚያምን ሰዉ ካለ ይህ በርግጥ ጃሂል ነዉ የሚገዛዉን ጌታ አላወቀም።” አሉ
#አሏሁ_አክበር,
© አቡ ኑዓይም ሂልየቱል አዉሊያእ በተባለዉ 📚ኪታብ ላይ  አስቀምጠዉታል።

•እንደዚሁም #ኢማሙ_አቡ_ጃዕፈር አጡሀዊይ ታላቁ የሰለፍ ምሁር ረድየሏሁ አንሁ እንድህ ይሉናል፦

قال الإِمام أَبو جعفر الطحاوي رضي الله عنه "تعالى عن الحدود والغايات واَلأَركان وا َلأَعضاء وا َلأَدوات

“አሏሕ  ከወሰኖች፣ ከጎኖች፣ ከጫፎች፣ ከትላልቅ የሰዉነት ክፍሎችና ከትናንሽ የሰዉነት ክፍሎች የተጥራራ ነዉ።”

•ስለዚህ አሏሁ ሱብሐነሁ ወተዓላ ከሀዲዎች ከሚሉት ሁሉ የተጥራራ ነዉ ለመኖሩ ቦታ አያስፈልገዉም በራሱ የተብቃቃ ጌታ ነዉ። ቦታን (አርሽን) የፈጠረዉ ችሎታዉን ግልፅ ሊያደርግ ነዉ እንጅ ወደነሱ ፈላጊ ሁኖ አይደለም።

#ታላቁ_ሶሀባ_ኢማሙ_አልይ ረድየሏሁ አንሁ እንዳሉት፦

قال الإِمام علي رضي الله عنه  "إِن الله تعالى خلق العرش إِظهار لقدرته ولم يتخذه مكانا لذاته"رواه  الإِمام أَبو منصور البغدادي في الفرق بين الفرق(ص"٣٣٣)

“አሏህ አርሽን የፈጠረዉ ችሎታዉን ግልፅ ሊያደርግ ነዉ እንጅ ለሱ ለእዉኑ ቦታ አድርጎ ሊይዘዉ አይደለም”

©አቡ መንሱር አልበግዳድይ አልፈርቅ በይነል ፊረቅ በተሰኘዉ ኪታባቸዉ 📚ገፅ 333 ላይ አስቀምጠዉታል።

#የአቅል_ማስረጃ
➻❛አሏሁ ሱብሐነሁ ወተዓላ ወደ ፍጡር (ወደ ቦታ) የሚከጅል ቢሆን ኖር ይህ ከጃይነቱ ለሱ ባህሪ ሁኖ በተረጋገጠለት ነበር፥ ፈላጊነቱ ለሱ መገለጫ ይሆን ነበር። እሱ ፈላጊ ሆኖ ቢሆን ደግሞ #አለም መገኘቷ ዉሸት በሆነ ነበር አለም ዉስጥ ያሉ ነገሮች ባልተገኙ ነበር። 

•ለምን ካላችሁኝ?!......
እንዴ ከላይ ስንት ጊዜ ደጋገምነዉ!!!አሏህ ፈላጊ ከተባለ ደካማ ነዉ ደካማ ደግሞ ጌታ አይሆንም አለምን ማስገኘት አይችልም።

ስለዚህ አሏሁ ሱብሐነሁ ወተዓላ ከፈጠራቸዉ ፍጡራኖች ከማንም ከምንም በማንኛዉም አይነት መንገድ አይፈልግም፥ ከአርሽ ከኩርስይ ከሰማይ ከሙሉ ፍጥረቶቹ ፈላጊ አይደለም እሱ በራሱ የተብቃቃ ነዉ።❜

#የቁርአን ማስረጃ

በቁርአን ላይ እንደነገረን፦

قال الله تعالى"ألله لا إله إلا هو الحي القيوم)

“አሏህ ለጌትነቱ አጋር የለዉም አሱ ደግሞ ህያው ነዉ አይሞትም በራሱ የተብቃቃ ነዉ።”

እንደዚሁም በተጨማሪ

قال الله تعالى(ألله الصمد)
ትርጉም፦አሏህ የሁሉም መጠጊያ ነዉ

📚📚📚📚📚📚📚
ከአሏህ ባህሪያቶች ከዘረዘርነዉ፤
አል ቂያሙ ቢነፍሲ ነዉ አምስተኛዉ፤
ከሌላ አይከጅልም የተብቃቃ ነዉ፤
ፍጡርን ፈጣሪ ሁሉንም አስጠጊ፤
ከፈጠረዉ ፍጡር አይደለም ፈላጊ፤
የተብቃቃ ጌታ ጥቅምን አይፈልግም ከፍጡር በጭራሽ፤
ከትንሿም ዘራ ከትልቁም አርሽ፤

📚📚📚📚📚📚📚
JOIN 🖇
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
ሐድስ ❼

#የአሏሕ መልክተኛ ﷺ ቲርሚዝይ በዘገቡት ሀድስ እንደዚህ አሉ፦ [አሏሕ አንድንም ነብይ በመለክተኝነት አላከም መልኩና [ቁመናው] ድምፁ የሚያምር ቢሆን እንጂ ፥ የእናንተ ነብይ ደግሞ መልኩና ድምጽ ከሁሉም የበለጠ ያማረና የተዋበ ነው።]

ያ -ሰይዲ ያ -ረሱለሏሕ ﷺ

አሏሕ ሆይ ..! ሰይዳችንን ማየትን ወፍቀን..!

ሙሐረም -19|1444ሒ.
JOIN 🖇
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
------ *የመጅሊስ* *ቀማኛ* --------
🗡🔪🗡🔪

አሰላሙ አለይኩም እውነት ለምትወዱ
ሓቅን ምትፈልጉ ከሴትም ከወንዱ
እስኪ ለአላህ ብለን ስሜታችን ትተን
የመጅሊስ ቀሚ እንይ ተረጋግተን
ታድያ ማን ናቸው የመጅሊስ ዘራፊ
የልብ እምነት ሌባ ቀማኛ ቀፋፊ
በስም ሱና ነጋጅ በአቂዳ ገበያ
በፎርጅድ ቻፓ መች ሱናን መሸንገያ
የሱፍያን መንገድ አረዳድ ሰራቂ
የግርግር ሌባ መስሎ አስታራቂ
🙌🙌🙌🙌
ሓቅ ምትፈልጉ እስኪ ንገሩኛ
የእምነት ዘራፊ የአቂዳ ቀማኛ
🌿🌿🌿
ወተትና መርዙን በአንድ ያደባለቁ
ፍየል ከጎመን ጋር ሊኖር የለቀቁ
አህያና ጅብን ሹራ ያስቀመጡ
ስጋን ጅብ ሊጠብቅ አደራ የሰጡ
የሐቅ ፈላጊ እስኪ አስተውሉ
ጅብና አህያ እንዴት ይስማማሉ
ፍየልስ ከጎመን እንዴት ትተዋለች
አደለም ተለቃ ከአጥር ትዘላለች
😁😁😁😁😁
ሀቅን ምትፈልጉ እስኪ ተናገሩ
ከጥቅማቸው ይልቅ ኢማን ያከሰሩ
ቀለል ባለ መልኩ ልስጣቹ መለያ
ORGINAL ልትገዙ በዐቂዳ ገበያ
ቀማኞች ሚመስሉ ወደ ሐቅ ተጣሪ
ቢድአን አርግዘው ጽንሳቸው ቀባሪ
ዐሊም ካለያቸው በዒልም ላብራቶሪ
ሁሉም ሚቋቋሙ ቆዳቸው ቀያሪ
የሁሉም ነሽ ናቸው ዥዋዥዌ ሁሉ
በየደረሱበት ቦታውን ሚመስሉ
💐💐💐
አቶ አብረሃ ቱፍ ይተካል እያሉ
ንቀትና ማፌዜ በሰው ያቀለሉ
በተግራራ ፈትዋ ኡማ የፈተኑ
በሶሓቦች መንገድ መሄድ ያሳጠሩ
🎋🎋🎋
ሰለፍያ ሁሉ ይዘምን እያሉ
ኮከብ አሳቅፈው ወጣት ያማለሉ
የነቡዩ ክብር ምንም ማይመስላቸው
ሱሪያቸው አድርሰው ከመቀመጫቸው
ሴትእየጎተቱ ጺም እያበጠሩ
ሱኒዮች እኛ ነን ሲሉ እንኳ አያፍሩ
በሱፍዮች መንደር ሱፊይ የመሰሉ
ብዙም ሳያበዙት አብረው የጨፈሩ
በሱንዮች ሰፈር ቆዳ የቀየሩ
በተውሂድ ዙርያ ለይምሰል ያወሩ
በተብሊጎች መንደር ሪያድን ችከላ
በሰለፎች ቀያ ኡሱል ለሽንገላ
🌴🌴🌴
ወንድም እህቶቼ እስኪ ንገሩኛ
የልብ እምነት ሌባ ጠንሳሽ ሞገደኛ
🌱🌱🌱
በኡለሞቹ ላይ ድንበር ማለፋቸው
በጉቦ ውተፍ ሲነካ ክብራቸው
ሸይኽ ዑመር ኢማም ያልተነኩላቸው
ሸኽ ቃሲም ታጁድን የታሰሩላቸው
ለምን ይመስላሀል ሀቅ መጥላታቸው
🌷🌷🌷
በመረጃ አጥኑ ወደ አሊም ቀርባቹ
የ *ነቢዩን* *ሱና* አፍቃሪ የሆናቹ
🌹🌹🌹
በሱና ስም ነጋጅ የዓቂዳ ለፍላፊ
ኢኽዋን እኮ ናቸው *መጅሊሱን* *ዘራፊ*
ምን አስደነገጣቹ እስኪ ተረጋጉ
ሚስጥር ሳይገባቹ ለምትበረግጉ
ወንድም እህቶቼ ለነፍሳቹ እዘኑ
በጭፍን ተከታይ ከመሆን ዳኑ
እስኪ ለነፍሳችሁ ተረጋጋ በሉት
የነቢዩን ሱና በመረጃ አጥኑት
🍁🍁🍁
ለእገሌ ለፉላን ዘር መቆም ይቅርና
ስለ ዲን እንሰብ ሁሉን እንተውና
እገሌ ሲነካ ደማችን ይፈላል
ፉላን ከተባለ ስድባችን ይቀድማል
ለአላህ ዲን ሲነካ ለምን አያመንም?
ሱናን እንድንጠብቅ አደራ የለንም?
እስኪ ፍረዱ ለአላህ ብላቹ
እገሌ ተነካ ሲባል ሚያማቹ
*ኡስማንን* ሲሰድቡ *ሙሳንም* ሲተቹ
*ለአላህ* *ብላቹ* ለምን ዝም *ኣላቹ!!*
🌿🌿🌿
በሙስሊም ሀገር ላይ ፊትናን ያባባሱ
ቁንጽል ፈትዋ ሰጥተው ደም ያፋሰሱ
ሱፍይ እድጠፍ ሁሉ የፈቀዱ
ቅድሚያ ለስልጣን ብለው ያቀዱ
በሱፍያ ኡለሞች የተሳለቁ
በአፍ ቢሞግቱም በተግባር የራቁ
*መርሀቸው* ነውና ተደጋግፈህ ቀጥል
ሺዐው ሙጀሲሙ ሁሉንም አስቀጥል
ካይሁድ ከነሷራ ሁሉንም እንስማማ
ወንበሯን እስክኒዝ ስልጣን እስክንቀማ
🌿🙊🌿🙊🌿
ሐቅ ምትፈልጉ እስኪ ንገሩኛ
እነኚህ ዘራፊ የመጅሊስ ቀማኛ
🍃🍃🍃
ወንድም እህቶቼ እስኪ ተመለሱ
ወደ ሐቅ ጎዳና ፊታችሁ መልሱ
በቀደምቶች መንገድ ገድቡ ነፍሳቹ
ሙሉ እስልምናን ያዙ ከጥንቶቹ
🌻🌻🌻
100 አመት ያልሞላው ኢኽዋን ፍልስፍና
ጊዜያችን አንጨርስ አያዋጣምና
ይህ አጭር መልክቴ አያደናግራቹ
ዐቂዳችሁ አጽኑ *ከአሊም* ቀርባቹ
ይህ *አጭር ጽሁፌ *ወንድሜ* *ተረዳ*
*እህቴ* *ተረጂ፡*
*እውቀት* *አደለችም *ምልከታ* *ናት* *እንጂ፡፡*
🌾🌾🌾🌾🌾
*አላህ ሆይ!* ሐቅ እንደ ሐቅነቱ አሳየን
የምንከተለውም አድርገን
አላህ ሆይ! ውሸት እንደ ውሸትነቱ አሳየን
የምንጠነቀቀውም አድርገን፡

👇👇👇👇ሼር_ይደረግ ሼር ሼር
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
👍1
#ሰበር_ዜና

ነገ የብልፅግናው መጅሊስ ወደ አማራ ክልል በመምጣት ሊፈራገጥ እንደሆነ እየሰማን ነው።ስለዚህ የእውነት ሙስሊም ነኝ የምትል፣የአህሉሱና ወልጀመዓን መንገድ እከተላለሁ የምትል፣የሱፍያውች መንገድ እንዳይጠፋ የምትፈልግ ሁሉ ተዘጋጅ!!!የማንም ኦነግሸኔ ወለጋ አልበቃው ብሎ እዚህ መጥቶ አይጫወትብንም!!!ወጣት ጀመዓውም እውነታውን ተገንዝቦ ታሪካዊ ስህተት እንዳይሰራ ሙስሊም ወጣቶቻችንን በማደራጀትና በማናበብ መስጅዳችንንና መጅሊሳችንን እንዲስጠብቅ በአሏህ ስም እንጠይቃለን።
👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
ሰበር ዜና
ሰበር ዜና
ዘበር ዜና
አሏሁ አክበር አሏሁ አክበር
ይህ ከ ደመቀ መኮነን ጋር እና ከ ሙፈሪያት ካሚል ጋር የምታዩት ወንድማችን ኡስታዝ ፉአድ ሱሩር ነው የ ሸኾቹ የ ኮምቦልቻው ፈርጥ የሀጂ ሱሩር የሸኽ ሱሩር ልጅ ነው አሏህ ልጆቻቸውን ኸይር ያድርግልን እና በመጀመሪያ መናደዴን ልገልፅላችሁ ፈልጋለሁ ምክንያቱ ደሞ ወንድማችን መላው ኢትዮጲያ ስራ ፈጣሪወች ጋር ተወዳድሮ 3 ውስጥ ገብቶ የተሻለ ሁኖ በመገኘቱ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ደመቀ እና በ ሙፈሪሀት ካሚል ውዳሴና ክብር ሰተው አበረታተውልናል አልሀምዱ ሊላህ ይህ ሲሆን ግን አንድም የጀምአ ልጆች እንኳን ደስ አለን አላልንም ያ አናዶኛል ለ ዘፋኝ አበረታተናል እንኳን ለንደዚህ አይነቱ ድንቅ የማሽን ስራ ፈጠራ ጥበቡ ለማንኛውም ወንድማችን እንኳን ደስ ያለህ ብያለሁ ሽልማትህ ሲያንስብህ ነው አሏህ ይጠብቅህ
https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
👏1
#ውዴታ...!!
•••
ሰለፎች ማለትም
#የነብያችን ሙሐመድ ﷺ ባልደረቦችና በመልካም መንገድ የተከተሏቸው ለነቢያችን ሙስጠፋ አለይሂ ሶላት ወሰላም ያላቸውን ሙሀባ (ፍቅር) የሚያሳዩ ብዙ ምልክቶች ይታይባቸው ነበር፡፡
ከነዚያም መካከል፦

● ዓሊይ ኢብኒ አቢ-ጣሊብ ለነብያችን ﷺ ያላቸውን ሙሃባ (ፍቅር) ሲጠየቁ፦ “በአላህ ስም እምላለሁ! እርሱ ከንብረታችን፣ ከልጆቻችን ከአባቶቻችን ከእናቶቻችንና በጥም ጊዜ ከምናገኘው ቀዝቃዛ ውሃ ሁሉ የበለጠ እንወዳቸዋለን።”] በማለት መለሱ።

ሰለፎች የነቢያችን ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም ባልደረቦች (ሶሃባዎች) እርሳቸውን በመናፈቅ ቆዳቸው እስኪሳሳ ያለቅሱ ነበር። እንዴት አያለቅሱ?!!

•እኚህ ታላቅ ነብይ በአንድ መንገድ ሰብስበው የላይም የውስጥም ውበት የሰጧቸው ናቸው።

•እኚህ ታላቅ ነብይ ለነርሱ ካላቸው መልካም ምልከታ፣ ከነበራቸው እዝነት ርህራሄ አንፃር ውለታቸው የማይከፈል ነው።

•እኚህ ታላቅ ነብይ በማብሰርና በማስጠንቀቅ መካከል ሆነው ወደ አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ጥሪ ያደርግላቸው ነበር። በነበራቸው ጥበብም ትክክለኛውን መንገድ አስይዘዋቸዋል፣ ታዲያ እንዴት አያልቅሱ?!!
••••

JOIN
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
የመጀመሪያ ዙር የትዊተር ዘመቻ
••••••••••••••••••••
ውድና የተከበራችሁ የመሻይኽ ልጆች!
ዛሬ ምሽት 3 ሰአት ሲሆን የተቀናጀ የመጀመሪያ ዙር የትዊተር ዘመቻ እናካሂዳለን! ሁላችንም በጋራ አንድ ላይ በአንድ ጊዜ የምናስተላልፈው መልእክት መሸት ሲል በአዲስ አበባ ሙስሊም ወጣት ማሕበር ገፅ ይለቃቃል። ተፅእኖ ለመፍጠር ብዙ ሰው በተመሳሳይ ሰአት መሳተፍ ስላለበት ሁላችንም ለማታ 3 ሰአት እንዘጋጅ። ትዊተር ያልከፈታችሁ ክፈቱ ። ይህን መልእክት ሼር በማድረግ እናሰራጨው!
በዱኒያም ሆነ በአኺራ በላጩና ጥሩ ነገር አሏሕን መፍራትና መታዘዝ ነው፥ በዱኒያም ሆነ በአኺራ መጥፎው ነገር አሏህን መወንጀልና ትዕዛዙን መቃወም ነው።

ጁማዓ ሙባረክ...!
JOIN
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
#ተውበት...!
•••
“እንባህን ማነው የሚገዛህ?”

•ገበያ ቦታ ሒድህ እንባህን እንድገዙህ አቅርብላቸው፥ ገዥ ታገኛለህ በስንት ዋጋ? #ለእንባህ ምንም ዋጋ አታገኝም።

ነገር ገን የእንባህ ዋጋ ከጌታህ ዘንድ ምን ያክል እንደሆነ ታውቃለህ..?

قال رسول اللهﷺ  "عينان لا تمسهما النار عين بكت من خشية الله وعين باتت تحرس في سبيل الله"

«ሁለት አይኖች እሳት አይነካቸውም አሏሕን ፍርታ ያለቀሰች አይንና ሙጃሒዶችን ከጥላት ዘብ ቁማ ስትጠብቅ ያደረች አይን።»

● ቀደምት ሰለፎችን እንድህ ይላሉ፦
«ጥሩ ስራዎች ሚዛን ይገባሉ አሏህ ፈርታ ያለቀሰች አይን ሲቀር ለ'ሷ ግን ሚዛንም ሆነ ልኬታ የላትም፥ በአንድ ጠብታ እንባ ብቻ አሏሕ ከጀሃነም እሳት ይጠብቀዋል።»

አሏሕ ሆይ..!!! አንተን ከማይፈራ ልብ
በአንተ ፍራቻ ከማታለቅስ አይን በአንተ ዕጠበቃለሁ..!!!!!

•••
JOIN 📲
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
السَّلَام ورَاحْمَةُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُه

❤️❤️ ይከሰቱ!!!! ❤️❤️
#የዋህብያ_ቀንዶች
ሙሀመድ ሀሚድን እና ሰይድ አሀመድ ሙስጦፍ
ኮቻን መጥተው ለመነጀስ እንዳቀዱ እየተሰማ ነው
ይህን በማስመልከት የኮቻ ሱፍይ ንቅናቄ በማድረጋቸው፣ሊመጡ የነበሩት አንሷር መስጂድ
እለተ ቅዳሜ ነበር ነገር ግን ቅዳሜ አልፎ ዛሬ እሁድም አልመጡም በሚዲያ የኮቦልቻን ሱፍይ ንቅናቄ በማየታቸው ሬሳቸው እንደሚመለስ ስላወቁ የመምጣት እቅዳቸውን እንደቀየሩ ተሰማ

እናት የኮቦልቻን ሱፍይ በወለደች ያስብላል አይደል ይህን ወሬ በመስማታቸው

የኮ/ቻ መርከዝ High school እና ነባር የuniversity ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ
ፍልሚያውን እየተጠባበቁ እንደሆነ ተሰማ


Share share share

طريقنا علم وعمل منهجنا صدق واعتدال.

https://www.tg-me.com/yHbskwakebet
●አልሐፊዝ ኢብኑ ሐጀር አልዐስቀላንይ[ረዲየሏሁ ዓንሁ] እንድህ ይላሉ፦

قال بعض الأكابر

مَنْ شَغَلَهُ الْفَرْضُ عَنِ النَّفْلِ ؛ فَهُوَ مَعْذُورٌ
وَمَنْ شَغَلَهُ النَّفْلُ عَنِ الْفَرْضِ ؛ فَهُوَ مَغْرُورٌ .

«ታላላቅ ኦለሞች እንድህ አሉ፦ ከሱና ነገራቶች ግዴታን በመፈፀም ቢዚ {ባተሌ} ያደረገው ሰው ኡዝረኛ{ምክኒያታዊይ} ነው፥ ነገር ግን ሱና በመፈፀም ከግዴታ ቢዚ {ባተሌ}የሆነ ይህ ሰው የተታለለ {የተሸወደ} ነው።»
***
©ፈትሁ-ልባ
ሪ!!

ግዴታን መፈፀም እያለበት በሱና ነገር እራሱን ያጠመደ ይህ ሰው የተታለለ ነው። መጀመሪያ ማንኛውን መፈፀም እንዳለበት የማያቅ ጃሒል ነው። ግዴታ እያለ ሱናን የሚሰራ ምንም አይነት ምንዳ የለውም።
.
ሳናቅም ይሁን እያወቅን ያሳለፍናቸው ሶላቶች ወይም ፆምች ካሉ በሱና ነገራቶች ከምናሳልፍ ቀዷዎችን በማውጣት አሏሕ ግዴታ ያደረገብንን ነገር እንወጣ!


ከግዴታዎች ሁሉ በላጩ ደግሞ ኢልመ- ተውሒድ ነው። ተውሒድ ሳያቅ ሌሎች ነገራቶችን ቢፈፅም ስራው ተቀባይነት የለውም ምክንያቱም መሰረቱን አበላሽቷል።
||
[የተውሒድ እውቀት የሁሉ ነገር መሰረት ነው።]

العلم نعمة عظيمة جدا نسأل الله أن يكون حجة لنا
የዲን እውቀት ትልቅ የሆነ ጥቅም ነው፥ ለ’ኛ ምርኩዛችን እንድሆን #አሏሕን እንጠይቃለን!!
ومن يرد الله به خيرا ؛ يفقه في الدين .
#አሏሕ መልካም ነገር የፈለገለትን ባሪያ በዲኑ እውቀት እንድወስድ ያደርገዋል። ”
||
JOIN
https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
ሐድስ ⓫
እስልምና መልካም ስነምግባርን ልዩ ስፍራን ችሮታል፥ ተሰጥቶታል።

☞ አንድ ሠው መልካም ስነ ምግባርን የተላበሠ እና ’ራሡን ለአላሁ ተዓላ ብሎ  ዝቅ ያደረገ አሏሁ ተዓላ ዘንድም ሆነ ሠዎች ዘንድ የላቀ፥ የተከበረና የተወደደ ይሆናል።
.
የአሏሕ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ይላሉ፦ [የትም ብትሆን አላህን ፍራ፥ ወንጀል ከሰራህ መልካም ስራን አስከትል ታብሳታለችና፥ ከሰዎች ጋርም ትድድርህ በመልካም ስነምግባር ይሁን።]
© ቲርሚዝይ አውርተውታል...!

የአሏሕ መልክተኛ ﷺ በብዛት ጀነት የሚያስገባው ስራ ምንድነው? በማለት ተጠየቁ። እሳቸውም “አሏህን መፍራት እና መልካም ስነ ምግባር ነው” ብለው መልሠዋል...!
© ቡኻሪ

join...!

https://www.tg-me.com/+XBeaC-I2mctmNjE8
2025/07/13 22:37:25
Back to Top
HTML Embed Code: