Telegram Web Link
🥰 ልጩህበት!! 🥰


ክፍል~~~~ዘጠኝ(9)

.
.

ድያቀዘቀዝኩ በቀስታ ስጠጋ ከጭፈራ ቤቱ
እየተሯሯጡ መውጣት ጀመሩ ከነዛ መሀል በደም የተጨማለቀችው ቀይ ረጅም ሴት የኤደን ጓደኛ መሆኗን ያወኩት ኤዱ •••
"ወይይይይይኔ ጉዴ ያቺ እኮ ጋደኛዬ ነች ብላ ስትጮህ ነበር ልብሷም ፉቷም ደም ለብሷል እጇን እያወራጨችና ደሟን ከአይኗ ላይ ለመጥረግ እየሞከረች እየተደነቃቀፈች ወጣችና አቅም አንሷት ወደቀች
የቷ!? አልኳት ደንግጬ ;
ያቺ ያቺ የወደቀችው እኮ ጋደኛዬ ረዱ ነች እያለች ከባጃጄ ላይ ተፈናጥራ በመውረድ ወደ ልጅቷ እያለቀሰች ስትሮጥ
እኔም ተከተልኳት•••••
•••
ተከታትለን ደረስን። መሬት የተዘረረችውን ጓደኛዋን አነሳናትና ወደ ባጃጇ ወሰድናት ። ልጅቷ ኤደንን ስታያት ከዱላው በላይ ቢዥ አለባት ። ግራ ተጋባች።
ግንባሯ አከባቢ ተፈንክታለች ። በቅርብ ርቀት ያለው ሆስፒታል ድል ጮራ ነው ። ወደ ድል ጬራ ድንገተኛ ክፍል ይዣቸው በረርኩ ።
እንደገባን ወድያው እርዳታ ተደረገላት ምናልባት የፈሰሳት ደምና ድንጋጤዉ እንጂ ፍንክቱ ያን ያህል የከፋ አልነበረም።
ከለሊቱ ስምንት ሰአት ተኩል ሆኗል።
" በቃ ደና ነች አይዟችሁ የሰጠሁዋትን አንድ ግልኮስ እንደጨረሰች ትሄዳላችሁ እስከዛው ደጅ ሁኑ አለችን ሌላ የተጎዳ ሰው ወደ ድንገተኛ ክፍሉ ስለመጣ ክፍሉ እንዳይጣበብ።
እኔና ኤደን ወጣንና ግቢ ውስጥ ካለው ቴሌቭዥን ፊት ለፊት ተቀመጥን።
ኤዱ ! አልኳት በዝምታችን መሀል ከድንጋጤዋ እንደተረጋጋች በአተነፋፈሷ እንደተረዳሁ።
ወዬ ዳኒ ! አለችኝ ለኔ የሚጨነቅ የሚመስለውን ገፅታዋን ወደኔ ዞራ እያሳየችኝ።
በጣም ገርመችሽኛል ! በእውነት የዋህ ልጅ ነሽ እናትሽ•••
" ሰው ክፉ የሆበበትን ሰው በክፋት ሳይሆን በደግነት የሚረታበት አጋጣሚ ከተፈጠረለት እና ከተጠቀመበት ትክክለኛ አሸናፊው እሱ እንደሆነ እየነገሩም በተግባር እያሳዩም አሳደጉሽ እሄው ዛሬ ፍሬውን እኔ አየሁት!ስላት•••
"እህህህህ በርግጥ ልክ ነህ ክፋትን በክፋት ስንመልስ ያን ሰው ለሌላ ክፋት እናዘጋጀዋለን!
ክፋትን በጥሩ ነገር ስንመልስ እኛም እናሸንፋለን ያን ሰውም ዳግም ሌላው ላይ ክፉ እንዳይሆን አድርገነው ልናልፍ እንችላለን የሚማርና የሚፀፀት ሰው ከሆነ !
እውነቱን ለመናገር እኔ ግን ረዱ እንደዛ ሆና ሳያት እሄን ሁሉ የሀሳብ ስሌት የማሰላበት ግዜ አልነበረኝም በቃ ውስጤ ያዘዘኝን ነው ያደረኩት!"
ተናደድሽባቸው እንጂ አልጠላሻቸውም ማለት ነው?! ስላት
አይ ለዛች እንዲህ እሆናለሁ ብለህ ነው እኔ እንጃ
ምን መሰለህ ይቺ የቲጂ ተከታይ ነች በቃ ቲጂ ወደመራቻት የምትጓዝ ዝም ብላ ወደ ነዷት ሁሉ የምትነዳ የዋህ አይነት ነገር ።
እኔን ወደዚህ አይነት ነገር ውስጥ ለማስገባት ያለፍላጎቴ ሲጫኑኝ ፊቷ ላይ ጭንቀት አነብ ነበር እሷ ግን ነገሮችን የማየትና የመሞከር ጉጉቷ ሀይለኛ ነው ለምን እንደሆነ አላውቅም!
ቢሆንም ከዛች ጭራቅ ጋር ሆነው አንቺን •••
ስላት ሳታስጨርሰኝ •••
"አስበው እስቲ ዳኒዬ ለመሲ እኔም ብሆን እኮ ተታልየላት ነበር ልጁ በአጋጣሚ እዛ ባይኖርና መሲ ያሰበችው ሁሉ ተሳክቶላት ቢሆን
በንጋታው ፊቴ ተቀምጣ
ካሁን ቡሀላ ሁለት አማራጮች አሉሽ አንዱ እኔ ነይ ስልሽ መምጣትና አድርጊ ያልኩሽን ማድረግ ሌላው ከኔ ጋር መጣላትና ለሊቱን ምን ስታደርጊ እንዳደርሽ ሚስጥርሽን በፎቶ አስደግፌ እንድበትንልሽ መፍቀድ ብትለኝ ምን ይውጠኝ ነበር ምንስ አማራጭ አለኝ
ወይ የሷ ለማዳ ውሻ መሆን ያለበለዚያ እራሴን ማጥፋት!"
ስትለኝ ከግር እስከራሴ ውርርር ሲያደርገኝ ታወቀኝ
አቦ የዚች መሲ እምትሏትን ልጅ ፎቶ ስጪኝ በናትሽ ካሁን ቡሀላ ፀባ ከኔ ጋር ነው
"ኧረ ባባባ ሞት እዚህ ነገር ውስጥ አትግባ በቃ ሁሉም አለፈኮ ካሁን በኋላ የት ታገኘኛለች "
ስትለኝ ዝም ብለሽ ስጭኝ በናትሽ አልኳት
"እኔ ጋር የሷ ፎቶ ምን ያደርጋል ረዱ ሞባይል ግን አለ ግን ምንም አያደርግልህም።"
በዚህ መሀል የረድኤት ቤተሰቦች ብላ ተጣራች ነርሷ። ተነስተን ኤዱ ከፊት እኔ ከኌላ በመሆን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ጭንቅላቷ ዙርያውን በነጭ ፋሻ የታሰረው ረድኤት ተነስታ ቁጭ ብላለች ኤዱን ስታያት አለቀሰች ኤዱም ተንደርድራ አቀፈቻት።
"እሄውልህ እነዚህን መድሀኒቶች ግዙላት እሺ" አለችና የሀኪም ማዘዣ ወረቀቱን ሰጠችኝ ነርሷ።
ካራ ማራ አከባቢ ፔንስዮን (የምኝታ ብቻ) አገልግሎት የሚሰጥ ቤት መኖሩ ትዝ አለኝና ወደዛው ይዣቸው ልሄድ አሰብኩ ገና ከሆስፒታሉ ቅጥር ግቢ ወጣ እንዳልን ኤዱ ረድኤትን በጥያቄ ታጣድፋት ጀመር•••
ምንድን ነው የተፈጠረው?
ማን ነው የመታሽ ?
ቆይ ከማን ጋር ነበርሽ?
ማን እንደመታኝ አላውቅም ከኔ ጋር የነበረው ልጅ ፍቅረኛ ነበረው ለካ!
አብረን እየደነስን ድንገት መጥታ ስታንቀውና ሲወረውራት አብረዋት ይምጡ አይምጡ አላውቅም ወረሩት አብሮኝ ስለነበር ሲወሩት ጮህኩ ብቻ ምናባሽ ትጮሂያለሽ የሚል ወፍራም የሴት ድምፅ ተሰምቶኝ ዘወር ከማለቴ ግንባሬ ላይ የቢራ ጠርሙሱን ስታፈነዳው ትዝ ይለኛል ከዛ በኋላ እንዴት እንደወጣሁ እራሱ አላስታውስም
ማነች እሷ የመታችሽ ፍቅረኛው
ኧረ እሷ እኔን ዞራም አላየችኝ እዛው የምትሰራ ሴተኛ አዳሪ ሳትሆን አትቀርም የመታችኝ ከዚህ በፊት ሳይተዋወቁ አይቀሩም ከገባን ጀምሮ ስትመነቃቀርብኝ ነበር ሳስበው ለፍቅረኛው እሷ ሳትሆን አትቀርም የደወለችላት በመሀል ስልኩን ተውሳው ነበር
ቆይ አንቺ እሱን መች ነው የተዋወቅሽው
ረድኤት "በቀደም መሲ ናት ያስተዋወቀችኝ •• ብላ ገና ወሬዋን ሳትጨርስ•••
አስተዋወቀችኝ አትበይ ረዱ ሸጠችኝ በይ ልጅቷ እኮ ምንም የማያውቁ ፍሬሾችን ከወንዶች ጋር እያገናኘች ቢዝነስ የምትሰራ ጭራቅ ነች እሄን ታውቂያለሽ በናንተ እየተጠቀመች ነው "!
እኔ ነኝ ባለጌዋ ኤዱ እኔ የማረባ ሴት ነኝ ላንቺ ጓደኝነት እንኳን የማልመጥን ተራ ሴት ሆኜ አንቺ ግን ••••
በቃ እራስሽን አትውቀሺ ያቺ ቲጂ ነች አንቺን እዚህ ሁሉ ነገር ውስጥ የከተተችሽ
አይደለም ኤዱ ማንንም ጥፋተኝ ማረግ አልፈልግም ስለኔ የማታውቂው ነገር አለ!
አልጋ አግኝተን ይዣቸው እንደገባሁ
"ምንድን ነው እሱ ስላንቺ የማላውቀው ?" አለቻት ኤዱ ገብተን ቁጭ እንዳልን
••• "ታውቂያለሽ አባቴ በጣም ሀይለኛ ነበር ታላቅ ወንድሜ ደግሞ ቁጭ አባቴን በሱ ነው የወጣው እናቴ ደግሞ በተቃራኒው ልጅን ክፉና ደጉን በመንገር እና በመምከር እንጂ የትወጣሽ የት ገባሽ ከማን ጋር አወራሽ ከማን ጋር ታየሽ ማለታቸውን ሁሌ የምትቃወም እናት ነበረች ግን አይሰሟትም
ውንድም እና አባቴ በኔ ላይ አምባገነን የሚለው ቃል አይገልፃቸውም እንኳን የወንድ የሴት ጓደኛዬ እነሱ ቀልባቸው ካልወደዳት ከኔ ጋር አትቀጥልም ምን ልበላችሁ አባቴ በቤት ታላቅ ወንድሜ በሰፈር እና በትምህርት ቤት መፈናፈኛ አሳጥተው ነው ያሳደጉኝ።
ትምህርት ቤት በጋራ የሚሰሩ የቤት ስራዎች ከወንዶች ጋር ከተደለደልኩ አወቁ አላወቁ ነፍስ ውጪ ነፍስ ግቢ ነው የክፍል ልጆች ግን ስለሚረዱኝ ነይ እንስራ ብለው ብዙም አይጫኑኝም ነበር!
👍246
ግን አባቴና ወንድሜ እንዳሰቡት በቁጥጥር ብዛት ስነስርዓት ያላት ሴት ሳይሆን በቁጥጥራቸው ብዛት አጋጣሚውን ስታገኝ ለመፈንዳት ሳይሄን ለመፈነዳዳት የተጠመደች ቦንብ አድርገውኝ አረፉት።
ዩንቨርስቲ ለመመደብ የድልድል ፎርም ስሞላ እንኳን ሆን ብዬ እራቅ እራቅ ያሉ ዩንቨርስቲዎችን ነበር በምርጫዬ ውስጥ የሞላሁት ከነሱ ለመራቅ ስል።
ቁጥጥራቸው ከመብዛቱ የተነሳ ምርር ስላለኝ ለኔ ብለው ነው ብዬ ከማሰብ ፈንታ እነሱን የምጎዳ መስሎኝ እልህ ውስጥ ገባሁ ግን ወድጄ አልነበረም እሄ የኔ ስሜት የሚገባሽ ያላደረግሽውን አደረግሽ ያልሆንሽውን ሆንሽ እየተባልሽ ስትቀጠቀጪ ካደግሽ ብቻ ነው።
እንደተመኘሁት እዚህ ተመድቤ መጣሁ።
ታስራ የተፈታች ውሻ ታውቃላችሁ በቃ እንደዛ አደረገኝ ሁሉንም መጀመር ያንንም ያንንም መሞከር ፣ማበድ ፣መስከር ፣ከወንድ ጋር መንዘላዘል ፣በቃ ምን ልበልሽ እንድርግ ያሉኝን ማደርግን ሁኚ ያሉኝን ሁሉ መሆንን ፍላጎቴ ብቻ ሳይሆን እልህ መወጫዬም ጭምር ነበር
እሄን ፍላጎቴን በፍጥነት ያሳካችልኝ መሲ ነበረች በርግጥ መሲ እንዳልሽው አስፈሪ ሴት ነች!"
እንዴት አልኳት እኔ ከኤደን ቀድሜ ንግግሯን ስትጨርስ የመሲን ፎቶ እንደምቀበላት በውስጤ እያሰብኩ
"የሷ ሚስጥር አልገባኝም ነበርና እኔ ከምፈልገው ደስ ካለኝ ወንድ ጋር ለመሆን ስሞክር ታጣጥልብኝ ነበር አንድ ሁለቴ በሀሳቧ ተስማማሁና ተውኩላት በሶስተኛው አንድ ቀን ግቢ ከተወወኩት ልጅ ጋር ኦቨር ማለት አብረን ጭፈራ ወጣን በመሀል ስትደውል አላነሳሁላትም እንዴት እንዳወቀች እንጃ ብቻ ያለንበት ድረስ ቀጥ ብላ መጣችና •••••
•••••••••••••

ይቀጥላል....
@yefikrclikic
@yefikrclinic
👍4311🕊64👌3🎅2
🌹 ለፍቅረኛዎ💕 ምን ማለት ይፈልጋሉ

ፍቅርዎን በመግለፅ surprise 😵 ማድረግ፤

HBD ለማለት፤ 🎂

ናፍቆትዎን ለመግለፅ፤ 🚶‍♀

ይቅርታ ለመጠየቅ፤🤦‍♂

🤩 የፈለጉትን የፍቅር ቃል ለኛ ላይ ይላኩልን 📬 በፍጥነት እናደርሳለን። @yefikrclinic_bot


contact us 👉 @yefikrclinic
ላይ ይላኩሉን
11👍76
ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 10


.
.
.
የሷ ሚስጥር አልገባኝም ነበርና እኔ ከምፈልገው ደስ ካለኝ ወንድ ጋር ለመሆን ስሞክር ታጣጥልብኝ ነበር አንድ ሁለቴ በሀሳቧ ተስማማሁና ተውኩላት በሶስተኛው አንድ ቀን ግቢ ከተወወኩት ልጅ ጋር ኦቨር ማለት አብረን ጭፈራ ወጣን በመሀል ስትደውል አላነሳሁላትም እንዴት እንዳወቀች እንጃ ብቻ ያለንበት ድረስ ቀጥ ብላ መጣችና •••••
ስትጠራኝ ከጀርባዬ ስለነበረች አለየኋትምም አልሰማኋትምም ነበር አብሮኝ ያለው ልጅ •••
"እንዴ ከዚች የሴት ነጋዴ ጋር ደግሞ የት ነው የምትተዋወቁት በይ ሂጂ እየጠራችሽ ነው ! ልታጫርትብሽ ሳይሆን አይቀርም እኔማ በምን አቅሜ እጫረታለሁ"
ሲለኝ አባባሉ ግራ እየገባኝ ዘወር አልኩ ፊቷን ምን አስመስላው እንደቆመች አትጠይቂኝ ።
እንዴት እንደተናደድኩ ከናባዬ ተገላገልኩ ስል እቺን ደሞ ማነው የላከብኝ እልኩ በውስጤ !
አልመጣም ልላት ሁላ ፈልጌ ነበር ።
ልጁን አንዴ አናግሪያት ብመለስ ቅር አይልህም አደል? ስለው•••
"ኧረ በጭራሽ እንደውም ባታናግሪያት ነው እሚሸክከኝ ይልቅ አፍጥኚው ወደዚህ ሳትመጣ!" አለኝ።
ሄድኩ ። ገና አጠገቧ እንደደረስኩ•••
"ስሚ ከኔ እና እኔ እኔ ከማውቃቸው የተከበሩ ሰዎች ጋር አንዴ ከታየሽ ከእንደዚህ አይነቱ መናጢ ተማሪ ጋር መታየት እንዳልነበረብሽ ሳልነግርሽ ማወቅ ነበረብሽ እኮ?!" ስትለኝ የእውነት ደሜ ፈላ
በምናቸው ነው የተከበሩት እሱ ከነሱ በምን ያንሳል?!
"በብራቸው ነዋ በብራቸው ብርርርር ታውቂያለሽ አደል ስንቱን እንደሚያበር ስንቱን እንደሚያስከብር እሄውልሽ እሄ ልጅ ምናልባት መልኩና ወጣትነቱ ያምር ይሆናል ግን ባዶ ነው ባዶ ታውቂያለሽ ለኔ በብዙ ደሀዎች መካከል ያለ አንድ ባለ ብር ለምን ሰላሳ ሁለት ጥርሱ ረግፎ በድዱ አይስቅም ለኔ ቆንጆው እሱ ነው !"
ለኔ ግን አይደለም አንቺም ቆንጆሽ ጋር ሂጂ እኔንም ከቆንጆዬ ጋር ተይኝ ብያት ጥያት ወደ ተማሪው ስመለስ ቤት በኩል እንደወጣ ድራሹ የለም ! አመዴ ቡን አለ!።
ሹክክ ብዬ ስመለስ ሲወጣ ትየው ወይ እንደሚወጣ ቀድማ ትወቅ ብቻ ቀድማ ነበር እየሳቀች የጠበቀችኝ "
አለችና በረጅሙ ተንፍሳ ጭንቅላቷን እየነካካች
"የሷ ጉድ መች ያልቃል እራሴን ሲሻለኝ አወራሻለሁ ። ግን እሄ ልጅ ማነው ኤዱ ?" አለች በአገጯ ወደኔ እያመለከተች። ሁለቱ አልጋ ላይ እኔ ደግሞ ከፊት ለፊታቸው ክፍሉ ውስጥ መስኮት ስር ባለችው አንዲት ወንበር ላይ ተቀምጫለሁ።
"ወንድሜ ነው! ያንቺዋ መሲ ሳታስበው የሰጠችኝ ምርጥ ወንድሜ!"አለቻት ።
ኤደን ስትናገር በጥልቀት እያየችኝ ነበር ንግግሯም ከልቧ ስለመሆኑ ቃናው ያስታውቃል።
"!?" እንዴት አለች ረድኤት ግራ ተጋብታ ።
በዚህ መሀል ጣልቃ ገባሁና እሱን እንቅልፍ እስኪወስዳችሁ ድረስ ታወራላችሁ እኔ ልሂድ አልኳቸው እና የመሲን ፎቶ በግድ ድርቅ ብዬ ከረድኤት ሞባይል ላይ ወደኔ ከላኩ በኋላ ኤዱን ነይ አንዴ ብያት ከክፍሉ ወጣሁ ።
ተከትላኝ እንደወጣች እሄን ለግዜው ያዥው ብዬ የተወሰነ ሳንቲም ሰጥቻት ስልኳን ወስጄ ደና እደሩ ነገ እደውልልሻለሁ ብያት ልሄድ ስል •••
ከአንደበቷ ቃል እንዳይወጣ ሰንጎ ከያዛት ሲቃ ጋር እየታገለች •••
"አመሰግናለሁ እሺ" አለችኝ ።
እንደተለየኋት ሰአቴን ስመለከት ዘጠኝ ተኩል ሆኗል።
ሁልግዜም ቢሆን በማታ ስራ ከዚህ ሰአት በፊት ገብቼ አላውቅም አንዳንዴ እስከ አስር ተኩልም ሰራለሁ። ቀጥታ ወደቤቴ አመራሁ። በንጋታው ከእንቅልፌ ስነቃ ከቀኑ ሰባት ሰአት ተኩልን አለፍ ብሏል። እዛው መኝታዬ ላይ ሆኜ ስልኳ ላይ ደወልኩ። ስልኳ ጥሪ አይቀበልም ግቢ ሄደዉም ተኝተዋል ማለት ነው አልኩና ትንሽ ተገላብጬ ተነሳው ተጣጥቤ ቀማምሼ ወጣ እንዳልኩ ነበር ጆሲ ስልክ ላይ የደወልኩት ዮሴፍ ይባላል በጣም የምወደው ጓደኛዬ ነው ።
ከስራ ወጥቼ እየመጣሁ ነው ስደርስ እደውላለሁ አለኝና ከሰላሳ ደቂቃ በኋላ ደርሶ ደወለልኝ ። እንደተገናኘን ማታ ያጋጠመኝን ነገር ንግግራችንን ሳይቀር አንድ በአንድ ነገርኩት።
በመሲ በጣም ተናዶ ለነኤዱ በጣም አዘነ እና እኔን ግን ከባድ ጥያቄ ጠየቀኝ•••
"ዳኒዬ ለልጅቷ ማለት ለ ኤደን ያልካትና ውስጥህ ያለው ስሜት አይጋጭም አደለ!?" አለኝ።
ምን ለማለት ፈልገህ ነው!? አልኩት ቢገባኝም እንዳልገባኝ ሆኜ ለማሰቢያ የሚሆነኝ አየር ለመያዝ
"ማለት እኔ አሁን በነገርከኝ በነኤደን አጋጣሚ ውስጥ የነበረውን ዳንኤልን አላውቀውም"
የቱን ነበር የምታውቀው? አልኩት አሁንም ባስብም ለአጥጋቢ መልስ ጠብ የሚል ሀሳብ ሲደርቅብኝ ግራ ተጋብቼ!
"ሰዎች ውልታ ውለውልሽ ከመንገድሽ ውጪ እንድትሄጂ ከጠየቁሽ ጥያቸው ብሎ እየመከረ ውለታ ለመዋል ቃል የገባው ጋደኛዬ ዳኒ ኋላ የራሱ ቃል ጠልፎ እንዳይጥለው ፈራሁለት! "አለኝ
አልገባኝም ስለው
" ባክህ ገብቶሀል አታድርቀኝ !" አለኝ
አዎ ገብቶኛል ጆሲዬ ግንኮ አንዳንዴ በንፁህ እህትነት ብቻ የምንቀርባቸው ሴቶች ያስፈልጉናል ቢያንስ አንድ እሷም እንደወንድሟ አንተም እንደህትህ የምታያት ሴት እንድትኖርህ አስበህ አታውቅም ?!ስለው•••
"አላውቅም!" አለኝ ፈርጠም ብሎ
ለምን ?
"የለም ማለቴ አደለም ግን መጨረሻው አያምርም!" አለኝ አሁንም ቁምጭጭ ብሎ
ጆሲዬ መጨረሻውን እያሰብን ነገሮችን የምናጣጥም ከሆነማ መጨረሻችን ሞት መሆኑን እያስታወስን ምንም እንዳይጥመን፣ ምንም እንዳይደንቀን፣ ምንም እንዳይሞቀን ፣ሆነን መኖራችን ነውኮ ስለው
እሱማ መታደል ነዎ የሰው ልእልና ጫፍ ላይ መድረስ ነገ መሞታችንን ሁሌ ካስታወስን ክፋት ይሸሸን ነበርኮ ዳኒዬ
ክርክር ከጀመረ አያቋርጥም ።
አቦ ተወኝ እንግዲህ ይልቅ ባለፈው ያልከውን ሀሳብ ተውከው እንዴ? አልኩት
"የቱን?"
ስራ እንደጀመርኩ አከባቢ ለሁለት አንዲት ክፍል ተከራይተን ለምን ከቤተሰቦቻችን ቤት አንወጣም ያልከኝን ስለው ሳቁን ለቀቀው
ምን ያስቅሀል አልኩት ተናድጄ!
"መከራየቱን አልተስማማህም ነበር እኮ አሁን ምን አዲስ ነገር ተገኘ አየህ ውስጥህ እና ለሷ ያልካት ነገር እንዳይጋጭ ያልኩህ ለዚህ ነው!"ሲለኝ•••
ባክህ ለዛ አደለም ለሊት ለሊት ከስራ ስገባ እየረበሽኳቸው ስለሆነ ነው አልኩት።
"ይሁንልህ" አለኝ አሁንም እየሳቀ።
ማታም ስልኳ ላይ ስሞክር ጥሪ አይቀበልም ዝም ብዬ ወደ ምትማርበት ዩንቨርስቲ ሄድኩና ትናንት አብረን የነበርንበት አከባቢ ጭለማ ውስጥ የባጃጄን መብራት በማጥፋት ስላሳ ደቂቃ ያህል ግቢ ውስጥ ውር ውር ከሚሉት ተማሪዎች በተጨማሪ ከግቢ የሚወጡትን እና የሚገቡትን በአይኔ ስሸኝና ሳስገባ ቆየሁ።
ኤዱን ግን አላየኋትም ። መሄዴን ለጆሲም አልነገርኩትም።
በንጋታው በደላላ አፈላልጌ ከሰፈር ብዙም በማይርቅ በአንድ ትልቅ ግቢ ውስጥ ስፋቷ አራት ባአራት የሆነች ሰርቪስ ቤት አገኘሁ ለጆሲ ደውዬ ማግኘቴን ስነግረው እየሳቀ በል እሺ ኪራዩን ክፈል ከስራ ስወጣ ብር አወጣና ፍራሽ ምናምኑን እንገዛዛለን አለኝ።
ቤታችንን ማብሰያም መቀቀያም የለላት ምርጥ የወንደላጤዎች ቤት አደረግናት በየፍራሻችን ላይ ጋደም እንዳልን ስልኬን አውጥቼ የኤዱ ስልክ ላይ ስሞክር ጠራ ፍንጥር ብዬ ስነሳ •••
"ምን ሆንክ!? " አለኝ ደንግጦ ከፍራሹ ላይ ቀና እያለ!
እየጠራ ነው ስለው
"ማነው እሱ!? አለኝ
የኤዱ ስልክ ነዎ ስለው •••
"ካካካካካካ ••••!" የጆሲ ሳቅ ነበር•••
ይቀጥላል....

━━━━━━━━ ✦×✦ ━━━━━━━━
♥️ @yefikrclinic
15👍5🫡2🕊1
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 11

.
.
.

የኤዱ ስልክ ላይ ስሞክር ጠራ ፍንጥር ብዬ ስነሳ •••
"ምን ሆንክ!? " አለኝ ደንግጦ ከፍራሹ ላይ ቀና እያለ!
እየጠራ ነው ስለው
"ማነው እሱ!? አለኝ
የኤዱ ስልክ ነዎ ስለው •••
"ካካካካካካ ••••!" የጆሲ ሳቅ ነበር•••
እስቲ ላውራበት የሚል መልክት የያዘ ግልምጫ ገላመጥኩት ኤዱ ስልኩን ያነሳችው መስሎት ሳቁን ባጭሩ ቀጨው።
የኤዱ ስልክ ግን አልተነሳም አሁንም እየጠራ ነው •••" ጢርርርርር•••••ጢርርርርርር••••ጢርርርርርርር•••!"
ጥሪው አለቀና ሴትዮዋ "የደወሉላቸው ደንበኛ ስልክ አይመልስም"! ብላ የማውቀውን እውነት ለመድገም ከመድከሟ በፊት "የ!" እንዳለች አቋረጥኳትና በዝግታ ወደ ፍራሼ ተመለስኩ።
ሽቅብ እያየኝ የነበረው ጆሲ•••
"ምነው? አላነሳችልህም እንዴ?"ሲለኝ •••
አይ "ቤተ መፃህፍት ውስጥ ነኝ ስወጣ እደውልልሀለሁ!" አለችኝ አልኩት።
"ለዚሁ ነው ሳቄን ያቋረጥከኝ ምናለ እስቲ ብስቅበት!"
ካቆምክበት ቀጥላ ! አልኩት በሽቄ።
ዳንዬ የምስቀው አንተን ለማናደድ ቢሆን ኖሮ ካቆምኩበት እቀጥል ነበር እኔ የሳኩት ግን የእውነት ሁኔታህ አስቆኝ ስለሆነ ከቆምኩበት መቀጠል አልችልም"
ባንድ ጉዳይ ላይ ካንድ ግዜ በላይ መሳቅ አይቻልም እያልከኝ ነው?
"አላልኩም እሱ እንደሁኔታው ይወሰናል መቼም ግን ባንድ ጉዳይ የመጀመሪያውን ሳቅ ደግመህ መሳቅም ሆነ ከቆምክበት መቀጠል አትችልም!
ለምሳሌ•••!"
ብሎ ሊቀጥል ሲል
በቃ! በቃ ! ጆሲ በቃህ በናትህ ! ምንድን ነው ነገር እንደዚህ ማስፋት! ያ ፍቅሩ የተባለ ጋደኛህ ግን መጥፎ ልማድ እያለማመደህ ነው!
"ስትል ? እንዴት?" አለኝ ግንባሩን ቋጥሮ
ምን እንዴት አለው ከሱ ጋር ስትገናኙ በቃ የሆነች ርእስ ካገኛችሁ ቀኑን ሙሉ ስትከራከሩባት አደል እንዴ የምትውሉት የሱ ባህሪ ባይጋባብህ ኖሮ ድንገት ተነስተህ
ሳቅ ይደገማል ? አይደገምም ?
በሚል ርእስ ከኔ ጋር ልትከራከር ባልሞከርክ ነበራ?
ቆይ ያ ጓደኛህ ግን እሚያነበው ለመከራከር ነው? ወይስ ለማወቅ? አልኩት•••
"እምትከራከረው እኮ ስታውቅ ነው አለኝ ገልበጥ ብሎ በጀርባው እየተንጋለለ
እማትከራከረው ስለማታውቅ ነው እያልከኝ ነው ? ስለው
"ሰው ያውቃል እሚባለው ምን ያህል ሲያውቅ ነው ? ቆይ የማወቅ መለኪያው ምንድን ነው መቼስ ሰርተፍኬት ነው አትለኝም እንደዛ ቢሆን ሀገራችን ውስጥ •••"
ብሎ ሊቀጥል ሲል ለሁለተኛ ግዜ አቋረጥኩትና•••
ደሞ ጀመርክ እሄን ፖለቲካህን!
ስለፖለቲካ ማውራት አልፈልግም ይልቅ የጠየኩህን መልስልኝ አልኩት•••
"ዳንዬ የሚከራከር ሁሉ ያውቃል ማለት አይደለም እንደውም ሀገራችን ውስጥ የማያውቀው ነው ሁሉንም ነገር ተቆጣጥሮት እሚንጫጫው የሚያውቀው የተሻለው ዝምምምምምምምምምም ብሏል ለምን ይመስልሃል?"
በናትህ እሄን ርእስ ከዛ ከፍቅሩ ጋር ተዳረቅበት ከፈለክ ደውዬ ልጥራልህ እኔን ግን ተወኝ ! አልኩት ኮስተር ብዬ•••
" ወይ ፎንቃ••••• እና እሺ ስለምን እናውራ ቆይ አንተ እምትፈልገው ስለኤደን ብቻ እንድናወራ ነው?"
በናትህ ጆሲ እንዲህ አትበለኝ እኔ እማ ትሙት ኤዱን በጣም እምሳሳላት እህቴ እንደሆነች ነው የሚሰማኝ በሌላ በምንም ነገር አላሰብኳትም! ስለው ፍጥጥ ብሎ ለሰከንዶች አየኝና•••
"በእውነት! አመንኩህ በቃ ካሁን ቡሀላ እንደዚህ አልልህም!" አለኝ ከልቡ ነበር።
በማላውቀው ቁጥር ስልኬ ላይ ተደወለ እንደዋዛ አነሳሁትና •••
ሀሉ ስል•••
" ሄሎ ዳንዬ የኔ ውድ ወንድም እንዴት ነህልኝ ይቅርታ እሺ ረዱን ትንሽ አሟት ስለነበረ እሄን ሁለት ቀን ችግር ላይ ነበርን !"
የሚለውን የኤዱን ድምፅ ሰማሁ!•••
ለምን ደውለሽ አልነገርሽኝም ስላት እየተንተባተበች እኔን ከዛ በላይ ላለማስቸገር አስባ እንጂ ሳላስፈልጋት ቀርቼ እንዳልሆነ ልታስረዳኝ ሞከረች።
በቃ ከዛን ቀን ቡሀላ ቢያንስ በየሁለት ቀኑ በስልክ ቢያንስ በየሁለት ሳምንቱ ደግሞ በአካል እየተገናኘን እናወራለን ሻይ ቡና እንባባላለን ማታ ማታ ከነበረው ስራዬ ቀንም ማታም እስከተወሰነ ሰአት ወደ መስራት ከተሸጋገኩ ቡሀላ አንዳንዴ ቀን ወደነሱ ግቢ ሰው ይዤ ከሄድኩ ሳላገኛት አልመለስም ።
ብዙ ግዜ እኔ ጋር ስትመጣ ረዱን ይዛት ትመጣለች ትግስት ስለምትባለው ጓደኛቸው ስጠይቃቸው ሁለቱም እየተጋገዙ "እሷ ከመሲ ጋር ተጣብቃ ቀረችኮ!
ዶርምም ለቃለች !
ማንበቡንም ጭራሽ ትታዋለች !
ክላስ እራሱ ብዙ እምትገባ አይመስለኝም!" በማለት ነግረውኛል እነሱ ግን መሲ ባለፈችበት መንገድ እንኳን አንደማያልፉ አውቃለሁ።
በዚህ መልኩ ቅርርባችን ቀጠለ። ከተዋወቅን አራት ወር ከሁለት ሳምንት ሆነን።
ከዛሬ ሶስት ሳምንት በፊት አንድ ጥያቄ ጠይቂያት ነበር መቼ ነው የተከራየኋት ቤት ውስጥ አንቺና ጓደኛሽ ቡና እምታፈሉባት? ብዬ የሁለተኛው መንፈቅ ፈተና መድረሱን ነግራኝ ፈተናውን እንደጨረሱ እንደምትመጣ ቃል ገባችልኝ ። እኔም ፈተናዋን ተፈትና እስክትጨርስ እየደወልኩ እንደማረብሻት ቃል ገባሁላት ። ችግር የለውም ደውል ብትለኝም ደውዬ አላውቅም ዛሬ አርብ ነው በነገረችኝ መሰረት ከሆነ ዛሬ ፈተናው ያልቃል። ስልኳን ስጠባበቅ ነው የዋልኩት እስካሁን ግን አልደወለችም ።
አመሻሹ ላይ ስራ ላይ ሆኜ ስልኬ ጠራ እየነዳሁ ነበርና ባጃጄን ጥግ አስይዤ ስልኬን ከኪሴ አውጥቼ ስመለከተው ኤዱ ነች ሰላምታ ከተለዋወጥን
ቡሀላ የነበረችበት ቦታ የሙዚቃ እና የሰው ጫጫታ ስለነበር የት ነሽ? አልኳት ግቢ ካፌ ውስጥ እንደሆነች ከነገረችኝ
ቡሀላ ነገ ማለት ቅዳሜ ስምንት ሰአት ላይ እንደምትመጣ ነገረችኝ እኔ እራሴ ግቢ ሄጄ እንደምውስዳት ነግሪያት ስራዬን ቀጠልኩ ልክ ከምሽቱ አራት ተኩል ላይ በቃ አቦ ደክሞኛል ልግባ ብዬ እያሰብኩ ስልኬ ጠራ በቋሚነት ስልክ ተቀያይረን ሲፈልጉ እየደወሉ ኮንትራት ከሚይዙኝና ደና ብር ከሚከፍሉኝ ሰዎች መሀከል ቀዳሚው ነበር የደወለው የማይታለፍ ስልክ አልኩ ገና ስልኩን እንዳየሁት።
እሄን ሰውዬ ሳስበው ነገረ ስራው ሁሉ ይገርመኛል የሆነ ድብቅ ማንነት ያለው ሰው ነው ኑሮው ድሬ ዳዋ አይደለም አልፎ አልፎ ነው ከጅግጅጋ ወደ ድሬ የሚመጣው ሁሌም እንደነገ ሊመጣ እንደዛሬ ይደውልልኝና ነገ መጣለሁ የተለመደው ቦታ አልጋ ያዝልኝና ውሃ አስገባልኝ ይለኛል ። ትዛዜን ተቀብዬ ክፍል ይዝለትና እሽግ ውሃውን በብዛት አስገብቼ እጠብቀዋለሁ ። ድሬ ሲቃረብ ይደውላል መግቢያው ላይ ጠብቄ ወደያዝኩለት ክፍል እወስደዋለሁ ።
ጥዋት ቁርስ ምሳ ሰአት ላይ ምሳና ኪሎ ጫቱን እንዲሁም ሌሎች የሚያስፈልጉትን ሁሉ ሴተኛ አዳሪን ጨምሮ አስገባለታለሁ ለሁለት ወይም ለሶስት ሳምንት በዚህ መልኩ ከያዝኩለት ክፍል ሳይወጣ ይቆይና ይሄዳል።
አሁን ከመጣ ስምንት ቀን አልፎታል ።
አንዳንዴ በቆይታው መሀል ቢበዛ አንድ ወይም ሁለት ቀን ወጣ ማለት ካስፈልገው ብቻ በዚህ ሰአት ይደውላል ዛሬም መውጣት ፈልጎ ይሆን እንዴ? እያልኩ ስልኩን አንስቼ ሳናግረው እንደጠረጠርኩት •••
"አቢቲ ዛሬ ወጣ ማለት አስኝቶኛል ትመጣልኝ?" አለኝ ባጃጄን አዙሬ ወዳለበት ከነፍኩ።
7👍6
ሰው ወደማይበዛበት እና ሁሉም ነገር ወደድ ወዳለበት ጭፈራ ቤት አድርሼው ስመለስ ከኋላዬ የተሳፋሪ መቀመጫው ላይ ስልክ ሲጮህ ስልኩን ጥሎ መውረዱ ገባኝ አንስቼ ሄሎ ስል•••
" አቢቲ ስልኬን ባጃጅህ ውስጥ ጥያት ወረድኩ ታቀብለኝ?" አለኝ።
ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ የተቀመጡበት ሶፋ ላይ አይኔ ተተክሎ ቀረ።
ደነገጥኩ!
ሰውየው የኤች አይ ቪ ኤድስ ተሻካሚ የሆነና ሚስቱ በዚሁ በሽታ የሞተችበት ሰው ነው ።
ሁለቱ ሴቶች ደግሞ ••••
•••••

ይቀጥላል.....
@yefikrclinic
👍61
ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 12

.
.
.

ጭፈራ ቤቱ ውስጠኛው ክፍል ውስጥ ገብቼ ስልኩን ሰጥቼው ልወጣ ሁለት እርምጃ እንደተራመድኩ ድንገት ወደ ቀኝ ገልመጥ ሳደርግ
ሁለት ሴቶችና አንድ የሰፈራችን ሀብታም ነጋዴ የተቀመጡበት ሶፋ ላይ አይኔ ተተክሎ ቀረ።
ደነገጥኩ!
ሰውየው የኤች አይ ቪ ኤድስ ተሻካሚ የሆነና ሚስቱ በዚሁ በሽታ የሞተችበት ሰው ነው ።
ሁለቱ ሴቶች ደግሞ ••••
•••ሁለቱ ሴቶች ደግሞ አንዷ ጭራቋ ስትሆን አንዷ ደግሞ ምናልባት የናኤዱ ጋደኛ ሳትሆን አትቀርም ወይኔ ቲጂ እንዲህ አንድፍሬ ልጅ ነሽ ቆይ ኧረ •••
አልኩና እየተጣደፍኩ ከጭፈራ ቤቱ በመውጣት ሞባይሌን ከኪሴ አውጥቼ ፎቶ ማህደሩን ከፈትኩ አልተሳሳትኩም መሲ እራሷ ነች ከንፈሮቼን በሶስት ጣቶቼ ተጭኜ የመሲ ፎቶ ላይ እንዳፈጠጥኩ ወደ ባጃጄ ውስጥ ገብቼ ተቀመጥኩ ።
መደበኛ ስራዎ እሄ መሆኑን አውቃለሁ እኔን ያስደነገጠኝ አገር ምድሩ ሚስቱ በምን እንደሞተችና እሱም ምን እንዳለበት ከሚያውቀው ከዚህ ህሊና ቢስ ቀበጥ ጋር መተዋወቋ ነው።
ምንም የማያውቁ ከየቦታው የሚመጡ ፍሬሽ ተማሩዎችን እያቀረበችለት ሲጫወትባቸው ታየኝ እሷና እሱን ከዚህ ውጪ ምንም ሊያገናኛቸው እንደማይችል ግልፅ ነው ።
ሰውየው እንደሆነ ከመጨረሻዋ ልጅ እኩዮች ጋር ለመጋደም ፈሪሀ ህሊንም ሆነ ፈሪሀ ፈጣሪ ያልፈጠረበት አረመኔ መሆኑን እንኳን እኔ በታክሲ ስራ ምክንያት ከተማ ውስጥ ስቅበዘበዝ የምውል ከቤት የማይወጣ የሰፈራችን ሰው ቢኖር እንኳን ስለዚህ ሰውዬ ለመስማት መጠየቅ አይጠበቅበትም ስለሰፈራችን ሀብታሞች ከተወራ የሚወራ ብዙ ነገር ያለው እሱ ነው።
ባጠቃላይ ሰባት ልጆች አሉት። እናት አባቶቻችን ስለሱ ሲያወሩ•••
" ሀብታም የሆነው አንድ ልጁን ለሰይጣን ገብሮ ነውኮ ልጁ መፍዙዝ ሆኖ ግቢያቸው ውስጥ ካለች አንድ ክፍል ውስጥ ጫቱን ሲደፈልቅ ውሎ ነው እሚያድረው ወደውጪ ሳሰማይወጣ ሰው አያውቀውም!" ሲሉ ሰምቻለሁ
ለሀብት ሲል የገዛ ልጁን እንደዛ ያረገ ሰው ደግሞ ለምድር ቆይታው በቀሩት የተገባደዱ ቀሪ እንጥፍጣፊ አመታት የልጁ ታናሽ እና እኩያ የሚሆኑ ሴት እህቶቻችንን በገንዘብ ሀይል ጨርሶ ለማለቅ ባይሽቀዳደም ነበር እሚገርመኝ!።
ምን እንደማደርግ ግራ ገባኝ ስለዚህ ሰው ማንነት እያወኩ ቢሳካም ባይሳካም ልጅቷን ከሱ ለማስጣል ሳልሞክር ወደቤቴ ብሄድ የሰላም እንቅልፍ እንደማይወሰደኝ ምናልባትም እስክረሳው እና ባስታወስኩት ቁጥር የጥፋተኝነት ስሜት እንደሚለበልበኝ አውቀዋለሁ ። የሆነ ነገር መሞከር አለብኝ አልኩ ለራሴ ሞክሬ ካቅሜ በላይ ሆኖ ባይሳካ እንኳን ከህሊና ክስ እተርፋለሁ!
አካሄዴን ከማጣራት መጀመር እንዳለብኝ አስብኩ ምክንያቱም መሲ የዚህ አገር ልጅ ስለሆነች ዘመዱ ብትሆንስ አብራቸው ያለችው ልጅ ደግሞ የነ ኤዱ ጓደኛ ትግስት ባትሆንስ?
እዛው ባጃጄ ውስጥ እንዳለሁ ኤዱ ጋር ደወልኩ
አነሳችው። ግዜ ሳላጠፋ ቀጥታ ወደገደለው ገባሁ•••
ኤዱ የጓደኛሽን የትግስትን ፎቶ በቴሌግራም ላኪሊኝ
"ለምን ? ምነው? በሰላም ነው?"
አዎ በሰላም ነው አፍጥኚው!
ላከችልኝ። ትግስት ናት ብላ ኤዱ የላከችው ፎቶና አሁን በዚህ ሰአት ከነመሲ ጋር ያለችው ልጅ ጭራሽ አይገናኝም!
ሌላ ነች ማለት ነው? የግቢ ልጅ ትሆን ? በራሴ ጥያቄዎች ስወዛገብ ኤዱ ደወለች•••
ወዬ ኤዱ
"ምንድን ነው እሱ?" አለችኝ ያየሁትን ነገርኳት
"እስቲ የልጅቷን መልክ ንገረን "አለች።
ከረዱ ጋር አብረው እንደሆኑ ገባኝ ምናልባትም ስልኳን ድምፅ ማጉያ ላይ አድርጋው ለሁለት እየሰሙኝ ነው።
የልጅታን መልክ ማብራራቴን ጀመርኩ•••
ልጅቷማ ደስ የሚል ቅጥነት ያላት! ፀጉሯን ብራውን የተቀባች በጣም ቀይ ! አፍንጫዋ •••
እያልኩ ከአናቷ ጀምሬ ቁልቁል ልወርድላት ስል ካንገቷ ሳልሻገር ልጅቷን አወቋት መሰለኝ ቆይ ቆይ አንዴ ቴሌግራም ላይ ገባና ጠብቀኝ ብላ መልሴን ሳትሰማ ስልኩን ጠረቀመችው።
የላከችው ፎቶ ቴሌግራሜ ላይ እንደገባ በፍጥነት በረገድኩት እሚገርመው ልጅቷ እሄን ፎቶ ከለቀቀች ቡሀላ ፎቶው ላይ ያለውን ልብሷን ሳትቀይር ነው ወደጭፈራ ቤቱ የመጣችው ምናልባትም ወደዚህ አምሮባት ስትመጣ ተነስታ ቴሌግራሟ ላይ ለቃው ይሆናል።
ኤዱ እሄን ፎቶ ኬት ነው ያገኘሽው?
"ዛሬ ቀን ዘጠኝ ሰአት አከባቢ ነው የፌስ ቡክ ፕሮፋይል ፒክቸሯን የቀየረችው ከዛ ላይ እስክሪን ሹት አድርጌ ነው የላኩልህ ምነው ልጅቷ እራሷ ነች እንዴ ዳንዬ!?
አዎ እሷ ናት ስላቸው ሁለቱም ጮሁ!!
ምንድን ነው ምንሆናችሁ ኤዱ?
ቆይ እሷ ትንገርህ እንቺ ብላ ስልኩን ለረድኤት ሰጠቻት •••
" መሲ በመጨረሻም ተሳክቶላት እቺን ልጅ ወጥመዷ ውስጥ ጣለቻት እኔ አላምንም! "
ማለት? አልኳት።
ግራ ገብቶኝ አንቺ ኤዱ እና ትግስትስ በወጥመዷ ውስጥ ገብታችሁ የለ እንዴ
የሚለውን ሀሳብ ለራሴ እያወራሁት ቀጠለች•••
"አንድ ቀን ልጅቷ ባጠገባችን ስታልፍ መሲ ልጅቷን በክፉ አይን ስታያት አየሁና ምነው? ስላት•••
እቺ ልጅ ለጓደኛዋ ድንግል ነኝ የጀመርኩት ነገር የለም ማለቷን ሰምቼ ላጠምዳት ብሞክርም ገገማ አሳ ሆነችብኝ!።
ጋደኛዋ በኔ ቀመር እየተሽቀረቀረች ልታስቀናት ብትሞክርም ልጅቷ አልሞቅ አልደንቅ እንዳላት ነገረችኝ አሁን ሳያት ታስጠላኛለች !
" ብላ ስትነግረኝ •••
ምነው የኔ አይን አርፎባት! ለሆነ ቢዝነስ አቀባብያት ! ሳልተኩሳት የምትክሽፍብኝ ሴት የለችም ስትይ አልነበር እንዴ ታድያ እቺ እንዴት ከሸፈችብሽ ? ስላት
ኮሚሽን ሼር ሳላደርግ ለብቻዬ ማጣጣም ስለፈለኩ እንጂ እኔ መሲ እልህ ውስጥ ከገባሁ የትኛዎም የግቢ ሴት በዘረጋሁላት መረብ ላይ መወዘፏ የማይቀር ነው! "
ኮሚሽን ሼር ላለማረግ ስትል ምን ለማለት ፈልጋ እንደሆነ ጠየኳት እንዲህ አለች•••
እቺ ልጅ ጋደኛዋ ብትሽቀረቀር ብትብለጨለጭ ብልጭ አይልባትም አደል ስለዚህ እቺን በብልጭልጭ ነገር ማጥመድ አይቻልም ለእንደዚህ አይነት ሴቴች ደግሞ እቅድ ሁለት (ፕላን ቢን) እጠቀማለሁ የቱንም ፈተና ብትቋቋም ያንን መቋቋም ይከብዳታል።
እንደዚች አይነቷን በሴት ሳይሆን በወንድ ታጠምጃታለሽ እንኳን የሷን የድንጋይን ልብ የሚያቀልጥ ስንት የድሬ ልጅ ሞልቷል እሄን ያህል እከፍልሀለሁ በግር በጇ ብለህ አጥምዳት ብለው ሁለት ሳምንት ባልሞላ ግዜ ውስጥ አምጣት ያልኩት ቦታ እያክለፈለፈ ያመጣልኛል ግን ከልጅቷ ሽያጭ ግማሹ የሱ ነው ያንን ነው ኮሚሽን ያልኩሽ ብላኝ ነበር ይገርማል በዛ መንገድ ሸውዳ እጇ አስገባቻት ማለት ነው!?"
ስትለኝ እልህ አንቀጠቀጠኝ !
በፍፁም አታስገባትም! ኡልኩና ስልኩን ዘጋሁባት!
ምናልባት ሰውየው በአይን ሊያውቀኝ ስለሚችል ባጃጄ ውስጥ ያለውን ጥቁር ኮፍያ አደረኩና እስከ ግንባሬ ዝቅ አድርጌ አጎበጥኩት !
ሰተት ብዬ ወደ ጭፈራ ቤቱ ገባሁና ከነሱ ትይዩ ኮርነር ላይ ተቀምጬ መጠጥ አዘዝኩ።
መሀላቸው ጎልተው ግራ እንዳጋቧት የሚቅበዘበዘው ፊቷ ይመስክራል ። ምናልባቷ አጥምዶ ያስረከባት ልጅ መጣሁ ብሎ በመውጣት በዛው ቀርቶባት ይሆን አስሬ ዘወር ዘወር እያለች እምታየው? አንጀቴን በላችኝ !!
9👍5👏1
እየጠጣሁ ሁለቱን አውሬዎች ባየኋቸው ቁጥር ንዴቴ እየጨመረ መጣ!
ሰውየው ያንን በድሜ ብዛት ቶሎ ቶሎ ኩበት እየሆነ የሚያስቸግረውን ከንፈሩን በምራቁ ለማውዛት እየመጠጠ ያቺን አንድ ፍሬ ልጅ ለማሽኮርመም ሲታገል ስመለከተው አለም አስጠላችኝ !
ተነስተህ በባክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘካት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከውኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭና መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••


ይቀጥላል....
@yefikrclinic
👍31👏1
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 13


.
.
.

ተነስተህ በቦክስ ወደ ጀርባው ዘርረውና ልጅቷን ይዘኃት ውጣ ውጣ አለኝ።
መሲ ተነስታ ወደ ሽንት ቤት ስትሄድ ከጀርባ ተከተልኳት ! እሷ ከፊት እኔ ከውኋላ ወደ ሽንት ቤት እምትወስደው ቀጭና መንገድ መሀል ላይ እንደደረስን ከጀርብዬ ኮቴ ሳያሰማ ማጅራቴ አከባቢ •••
ኮሌታዬን ቀብ ሲያደርገኝ በድንጋጤ መንጭቄው በፍጥነት ዞርኩ!
"ክክክ አንተ ምነው ? ሊያጠቃኝ ይችላል ብለህ የምታስበው ጠላት አለህ እንዴ?
ተፈናጠርክ እኮ ካካካ•••!"
ኮንትራት የያዘኝ ሰውዬ ነበር። የሚገርመው እራሴ አምጥቼው ሳበቃ እዛ ጭፈራ ቤት የውስጠኛው ክፍል ውስጥ መኖሩን ጭራሽ ረስቼዋለሁ!
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት ጎን ለጎን እየሄድን •••
"ደሞ ደክሞኛል ገብቼ ተኛለሁ ባጃጅ ከፈለክ ብለህ ሌላ ስልክ ሰጥተከኝ አልነበር እንዴ የሄድከው ነው ወይስ ሞባይሉን ሰጠኸኝ ስትወጣ አንዷ ጠልፋህ ነው? መሆን አለበት ! እዚ ቤት ያሉ ሴቶች እኮ ልዩ ናቸው እንኳን
እዚህ ድረስ እራሱ የመጣውን ሰው በአየር ላይ ፖይለቱን አማሎ አውሮፕላን ለመጥለፍ ወደኋላ የማይል ውበት ነው ያላቸው ቆይ የጭፈራ ቤቱ ባለቤት የቁንጅና ውድድር አዘጋጅቶ ከአንድ እስከ አምስት የሚወጡትን ነው እንዴ የሚቀጥረው! ካካካ!"
ኧረ መቆለል አልኩና በሆዴ !
ኧረ አይደለም ባጋጣሚ ነው አልኩት ሸንተን ስንመለስ•••
"ምኑ ነው አጋጣሚ ቆንጆዎች መሆናቸው?"
አይ የኔ እዚህ መከሰት!
"እና ብቻህን ነህ ብቻህን ከሆንክ ለምን ውስጥ እኔጋ አለመጣህም " እያለ አቁሞ ሲነዘንዘኝ መሲ ከሽንት ቤት ወጥታ እየተውረገረገች ባጠገባችን አለፈች። አፈጠጥኩባት ።
እሱም በሚስቁት አይኖቹ እኔ ላይ አፈጠጠብኝ ።
"ተመለስክ?!"
ኬት ?
"ከልጅቷ ላይ ነዎ!"
አዎ አልኩት ፈገግ ብዬ !
በል ና እሄንን እማ እየጠጣን ነው መስማት የምፈልገው ናናናና !" እያለ እጄን እንደያዘ ወደ ውስጥ ገባን።
እዛ የተገኘሁበትን እውነት ልንገረው? አልንገው ? ብነግረውስ ምን ብዬ ልንገረው? ምናልባት ጥሬ እውነቱን እንደወረደ ስነግረው ምናልባት እኔን የተሰምልኝ ስሜት ካልተሰማው•••
"ቆይ ከልጅቷ ጋር ዘመድ ናችሁ?"
ኧረ አይደለንም ።
"ትውውቅ አላችሁ ማለት ታውቃታለህ ?"
አይ!
"እሺ ቆይ ልጅቷን ወደሀታል?'
ኧረ በጭራሽ!
"ታድያ ምን አግብቶህ ነው እዚህ ሁሉ ፈተና ውስጥ እራስህን የምትከተው?!" ቢለኝስ!
እኔ የሴቶች እህቶቼ ጉዳትና ጥቃት እንደሚያገባኝ አምናለሁ ይሄ የሚያገባቸው የማይመስላቸው እሄን ምን አገባኝ እያሉ ነገር ግን በማያገባቸው ብዙ ነገሮች ውስጥ እጃቸውን የሚያስገቡ ሰዎች በዙርያችን ብዙ ናቸው።
የሴት ጥቃት አይመለከተኝም እያሉ የአርሰናል መጠቃት የሚያደባድባቸው በሞሉባት ሀገራችን
አላውቃትም!
ዝምድናም የለንም!
አልወደድኳትም!
እያልክ ለሷ መቆም እንቆቅልሽ የሚሆንበትና ምን አገባህ የሚልህ ቢያጋጥምህ ምን ይገርማል?!
ምንም!።
ስለዚህ ምን ልበለው? በቀላሉ የሚፋታኝ አይመስለኝም ።
"ምናገባህ!" እንዳይለኝ ትንሽ ቀየር አድርጌ ልነግረው ወሰንኩና•••
ይሄውልህ ቅድም ሞባይሉን ሰጥቼህ ስወጣ የአንደኛ አመት የዩንቨርስቲ ተማሪ የሆነችውን የአክስቴን ልጅ ከማይሆን ሰው ጋር አየኋት!
ከኔ ጋር ከተጣላን አመት ሆኖናል። ተኮራርፈናል። አንነጋገርም ግን ብንጣላም ስለሰውየው በደንብ ስለማውቅ ጥያት በጭራሽ አልገባም ልጅቷ እንደዚህ አይነት አመል የላትም እርግጠኛ ነኝ ቅድም የገላመጥኳት ልጅ በሆነ መንገድ ሸውዳ አምጥታለት ነው •••
አልኩና ስለመሲና ስለሰውየው በዝርዝር ነገርኩት።
እሄን ግዜ ሰውየው ከኔ በላይ የተቆጣ ነብር ሆኖ ቁጭ አለ። ፊቱ ተለዋወጠ።
"በቃ ይሄን ጉዳይ ለኔ ተወው አንተ ዝምበልና ቁጭ ብለህ ጠጣ!"
ማለት ምን ልታደርግ ነው?!
"ዝም ብለህ ጠጣ! ብዬሀለሁ ዝም ብለህ ጠጣ!" አለኝ ክርድድ ባለ ድምፅ።
ድሮም ነገረ ስራው ግራ ነበር የሚገባኝ አሁን ደግሞ ባንዴ ሲለዋወጥብኝ እኔ እራሴ ፈራሁት ።
ካጠገቤ ሄዶ እነመሲን ከሩቁ አይቷቸው ተመለሰ።
ከደቂቃዎች በኋላ ከነመሲ ጋር ያለው ሰውዬ ቦርጩን እያሻሸ ወደ ሽንት ቤት ሲያልፍ እኩል እየነው! ተያየን••
"እሄ አሁን ያለፈው ነው አደለ?
"አዎ ግን ምን ልታደርግ ነው?
"አቢቲ አማርኛዬ አልገባ ካለህ የፈለከውን የሚገባህን ቋንቋ ንገረኝና በሱ ላስረዳህ ከዚህ በኋላ ለኔ ተወው የትም እንዳትንቀሳቀስ እዚሁ ቁጭ ብለህ እየጠጣህ ጠብቀኝ !"
ብሎኝ ሰውየውን ተከትሎ ወደ ሽንት ቤት ሄደ።
ብዙም ሳይቆይ ተመልሶ መጣና ምንም ሳይለኝ መጠጣት ጀመረ
ወደሽንት ቤት የሄደውን ሰውዬ ካሁን ካሁን ይመለሳል ብዬ ብጠብቅም አልተመለሰም ጨነቀኝ እንዴ ምን አርጎት መጣ? ግራ ገባኝ
ምን አልከው ሰውየው እኮ ብር ያጠገበው ባለጌ ነው ምን አለህ? ስለው•••
መልስ ሳይሰጠኝ እሄን ውስኪ እንደውሃ እየጠጣ •••
"ጠጣ ጠጣ ያቺን አየሀት ዝም ብላ እያየችህ ነው አብረካት መደነስ ትፈልጋለህ ልጥራት እንዴ?"
አለኝ ጥግ ኮርነር ላይ ካሉት ሴቶች መሀል ወደኛ እያየች ወደምትናጠው ሴት እያመለከተኝ
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••

ይቀጥላል.....

@yefikrclinic
@yefikrclinic
@yefikrclinic
82🥰1🫡1
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 14


.
.
.
ወይ መደነስ እኔ ሰውየው እምጥ ይግባ
ስምጥ ሄዶ ካናገረው በኋላ ከሽንት ቤት ባለመመለሱ ምን አርጎት ነው የመጣው እያልኩ ግራ ተጋብቻለሁ ጭራሽ ደንስ ይለኛል ምን አይነት ባህሪ ያለው ሰው ነው እሄ ደግሞ ቢያንስ እንኳን የኔ ጭንቀት ለምን አይገባውም እንዴ በራሴ ጉዳይ ዝም በል ጠጣ ደንስ ስላለኝ ዝም የምል ይመስለዋል?!
ወደ ሽንት ቤት ሌላ ሰው በሄደ እና በወጣ ቁጥር እያየሁ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት እራሴ ሄጄ ለማረጋገጥ ስለፈለኩ•••
••• እሺ መጣሁ አንዴ ስመለስ አብሪያት እደንሳለሁ አልኩትና ሄድኩ መጀመሪያ ወደነመሲ ገልመጥ ሳደርግ ሁለቱ ብቻ ናቸው እነሱም እንደኔ ሰውየው የት ሄደ ብለው ግራ ተጋብተዋል መሰለኝ ግራና ቀኝ ይገላመጣሉ ።
ወደ ወንዶች ሽንት ቤት በፍጥነት ሄድኩና ከአምስቱ ሽንት ቤቶች መሀከል ክፍት የሆኑትን ሁለቱን አየት አድርጌ በማለፍ ሶስተኛውን ስበረግደው•••
----------
"ምን አይነት ሰው ነህ በናትህ! ምሽግ ውስጥ ነው እንዴ ያደከው? አታንኳኳም!" አለኝ በብስጭት አንድ የማላውቀው ሰው።
ይቅርታ ይቅርታ አልኩት ቆሌዬ ተገፎ!።
"ባክህ የምናባህ ይቅርታ ነው ይቅርታ ይላል እንዴ ደሞ የልቡን አድርሶ!" አለኝ።
ንግግሩ ሳቅ ጫረብኝ ።
አይይ ስካር ደጉ ታየኝ እኮ እሱን ሽንት ቤት ተቀምጦ በማየቴ የልቤ ሲደርስ እያልኩ ቀሪ ሁለቱ ክፍሎች ውስጥ ሰውየውን መፈለጌን ቀጠልኩ•••
ሰውየው ድራሹ የለም ። ግራ ተጋብቼ በቆምኩበት ሽንትቤቱን ድንገት ከፍቼበት የተበሳጨው ሰውዬ ቆየት እያለ ሲሳደብ ሰማሁት•••
እንዴ! እሄ ደሞ እያረፈ ነው እንዴ እሚሳደበው!
አልኩና ከውስጥ ዘግተህ አትቀመጥም ነበር ሰካራም! ብየው ወደ ቦታዬ ስመለስ የኮንትራት ደንበኛዬ (ዝም ብለህ ጠጣ ሲለኝ የነበረውን ሰው ) ቦታው ላይ አጣሁት።
የክፍሉን ዙርያ ገባ ቃኘት አደረኩ ። እክፍሉ ውስጥም የለም።
እየተደነባበርኩ እነመሲ ወዳሉበት ክፍል በር ስጠጋ •••
አይኔን ተጠራጠርኩት ! ሽንት ቤት ሰውየውን ፍለጋ ደርሼ እስክመጣ ከምኔው ሄዶ ከምኔው ተዋውቋቸው እና ተግባብቷቸው መሳሳቅ እንደጀመሩ ለማመን በሚከብድ ሁኔታ•••
እሱ ያወራል እነመሲ ይስቃሉ አሁንም ያወራል እነሱ ተያይተው ያሽካካሉ አፌን ከፍቼ ስመለከታቸው ቆየሁና እየሆነ ያለው ነገር ከመጠጡ ጋር ተደምሮ ትርምስምስ እንዳለብኝ ወደ ቦታዬ ተመለስኩ።
ትንሽ ቆየሁና እሱ አልመጣ ሲለኝ መኖር አለመኖራቸውን ላረጋግጥ ድጋሚ ሄድኩ።
ጭራሽ እሱና መሲ ተጣብቀው እየደነሱ ነው። ጀርባዋን ሰጥታው እላዩ ላይ ተጣብቃለች ወገቧን አቅፎ ማጅራቷ አከባቢ እንደመሳም እየቃጣው ለስለስ ባለው ሙዚቃ ይወዛወዛሉ ።
ልጅቷ ቦታዎ ላይ ተቀምጣ ትቁለጨለጫለች ።
ምናልባት አስጠማጇን እራሷን መሲን አጥምዶ ልጅቷን ሊያፋታት አስቦ ይሆን እንዴ?
ብዬ አሰብኩና የሆነ የደስታ ስሜት ውስጤን ሲነዝረው ታውቀኝ።
ሰውየውን ምን አድርጎት ነው? የሚለው ጥያቄ ስላልተመለሰልኝና ዝም ብለህ ጠጣ ከማለት ውጪ ምን እንዳደረገ? እና ምን ሊያደርግ እንዳሰበ በግልፅ ሊነግረኝ ፍቃደኛ ባለመሆኑ ግን ደስታዬ ብርዝ ሆነብኝ!!
በዳንሳችው መሀል ድንገት ተያየን ጠቀሰኝ እኔ ግን ግራ ተጋብቶ ያፈጠጠ እንጂ የሚጨፈን አይን አልነበረኝም እና ምኑም ላልገባኝ ጥቅሻው መልስ ነፈኩት ዝም ብዬው ከራሴ ጋር እያልጎመጎምኩ•••
ግራ አጋባኝ እኮ እሚገርም ሰው ነው እሄ ሰውዬ እያልኩ ወደ ቦታዩ ተመለስኩ ።
በተመለስኩ በደቂቃዎች ውስጥ ወደኔ በመምጣ
"ፈታ በል አቢቲ ዝም ብለህ አትጨናነቅ እኔ አንድ ነገር ላደርግ ካሰብኩ ውጤቱን እንጂ ጅማሬው ማውራት አልወድም! ለምን መሰለህ?••• መጀመራችንን እንጂ መጨረሳችንን የሚያውቀው ፈጣሪ ብቻ ስለሆነ በርግጥ አሁን ያሰብኩትን ነገር ፈጣሪ ሳይሆን ሰይጣን ነው አጨራረሱን የሚያሳምረው አየህ አንዳንዴ ጥሩ ነገር ለመስራት መጥፎ ነገር ውስጥ መግባቱ ግድ ይልሀል የስራህ ውጤት ከፊሉ የፈጣሪ ከፊሉ የሰይጣን ይሆናል ድብልቅ!
ነገር ግን ፈጣሪ ልብን ሰይጣን ስራን ይመረምራል ብዬ ስለማምን እሱ አያሳስበኝም ! ለማንኛውም ስጨርስ ሁሉንም ነገር እነግርሀለሁ አሁን አንተ አታስፈልገኝም ከሀያ ደቂቃ ቡሀላ በር ላይ ሁለት ባጃጅ እፈልጋለሁ ካንተ ጋር ካሁን ቡሀላ ምናልባት ነገ ካልሄድኩ እንገናኝ ይሆናል ብሎኝ ከኔ መልስ ሳይጠብቅ ጥሎኝ ሄደ ።
እንኳን ምን ለማለት እንደፈለገ ሊገባኝ ያለውን መልሼ ማስታወስ አልቻልኩም።
አንዳንድ ሰዎችን ትንሽ ግዜ አብረሀቸው በቆየህ ቁጥር ወይ በደንብ ታውቃቸዋለህ ወይ ጭራሽ እንደማታውቃቸው ይገባሀል የሚለው የጆሲ ጋደኛ ትዝ አለኝ።
ያለኝ አማራጭ መወዛገቤን ትቼ እስከመጨረሻው የሚሆነውን ነገር መመልከት ብቻ ሆነ።
ካስር ደቂቃ ቡሀላ ኮፍያዬን አዘቅዝቄ አንገቴን አቀርቅሬ ከጭፈራ ቤቱ በፍጥነት ወጣሁ ።
ከማውቃቸው በዛ ሰአት ስራ ላይ ይሆናሉ ብዬ ወዳሰበኳቸው ሁለት የባጃጅ ሹፌሮች ደወልኩና በር ላይ እንዲጠብቁአቸው ነግሬ እኔ ራቅ ብዬ ባጃጄ ውስጥ እንዳደፈጥኩ ስጠባበቅ ልክ ባለው ሰአት መሲ እና እሱ ተቃቅፈው ግራና ቀኝ እየትወዛወዙ እና እየተሳሳቁ ልጅቷም በሁኔታቸው አብራ ፈገግ እያለች ወደ ጎን ተደርድረው ከጭፈራ ቤቱ ሲቅወጡ ተመለከትኩ።
ባጃጆቹ ጋር እንደደረሱ ሰውየው ያቀፋትን መሲን ለቅቅ አድርጎ ወደ ልጅታ ተጠጋና አናገራት። ጨብጣው ከፉት ያለው ባጃጅ ውስጥ ጥልቅ አለች እሱና መሲ ሌላኛው ባጃጅ ውስጥ ገቡና ፊትና ኋላ ሆነው ተፈተለኩ እኔም ተከትያቸው ተፈተለኩ ።
በቅርብ እየተከተልኳቸው ልጅቷን ወደ ያዘው የባጃጅ ሹፌር ደወልኩ ። አነሳው።
ምን አለህ? ስለው•••
"ግቢ አድርሳት አለኝ ወደ ግቢ እየወሰድኳት ነው " አለኝ ። በረጅሙ ተነፈስኩ እና ጀግና አቦ አልኩት ግራ ያጋባኝን ሰው።
ወደ ግቢ የሚሄደው ባጃጅና እነመሲን የያዘው ባጃጅ የሚለያዩበት ቦታ ላይ ደረሱ ልጅቷን የያዘው በዲፖ በኩል ሽቅብ ወደ ሰይዶ ሲሸመጥጠው እነመሲን የያዘው ባጃጅ በፀሀይ ሆቴል በኩል ቁልቁል ቆሰቆሰው•••
ወደያዘው ክፍል ይዟት እየሄደ መሆኑን ብረዳም ልጅቷን ትቼ የመሲን መጨረሻ ለማየት ተከተልኳቸው ።
ደረሱ ። ከባጇጃ ወርደው የሰከረችውን መሲን ከመሸከም በማይተናነስ ሀኔታ ደግፎ ወደያዘው ክፍል አስገባት ።
ለሰው ያጠመድሽው እራስሽ ላይ ባርቆ ሊዘርርሽ ነው አይ መሲ !
እያልኩ ወደ ቤቴ ገብቼ ተዘረርኩ ጥዋት ሶስት ሰአት ላይ የቀሰቀሰኝ የስልኬ ጥሪ ነበር ሰውየው ነው በፍጥነት አንስቼው ሀሎ ስል•••
" ደና አደርክ አቢቲ ተመልሼ ወደመጣሁበት እየሄድኩ ነው ምናልባት ከስድስት ወር ቡሀላ እመጣ ይሆናል የማታውን ሙሉ ትያትር ለማየት እና ለመስማት እንደምትፈልግ አውቃለሁ ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዬ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዬዋን ልከህ ካሁን ቡሀላ በሴት ተማሪዎች ሂወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው •••

ይቀጥላል...

@yefikrclinic

@yefikrclinic
10👍9
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 15

.
.
.

ቴሌግራምህን ክፈት ሶስት መልእክቶች አሉህ በድምፅ! በፅሁፍና; በምስል! ቻው !!"ብቻ ብሎኝ ስልኩን ዘጋው•••
በፍጥነት ቴሌግራም አካውንቴን ስበረግደው ቀድሞ የታየኝ የመሲ ልብስ አልባ ገላ የሚያሳየው ቪድዮ ነበር ከስር የመሲን ስልክ ቁጥር አስቀምጦ
"አቢቲ በዚህ ቁጥሯ የተከፈተ ቴሌግራም አካውንቷ ላይ ቪድዮዋን ልከህ ካሁን ቡኋላ በሴት ተማሪዎች ህይወት መነገዷን እንድታቆም ያለ በለዚያ ግን ቪድዮዋን እንደምትለቀው ነግረህ አስጠንቅቃት!" ይላል በርግጌ ከፍራሼ ላይ ተነሳሁ።
ቪድዮውን ስከፍተው •••
የሶስት ደቂቃ እድሜ ሲኖረው በዚች ሶስት ደቂቃ ውስጥ መሲ ያልተቀረፀ የሰውነት እካሏ አልነበረም ስካሯ ከመጠን ያለፈ ነበርና ያላትን በሙሉ እያደረገች ትስቃለች ። የሚገርመው የሰውየው አንዲት ጣት እንኳን በትይንቱ ውስጥ አለመኖሯ ነው።
ተጫወተባት እናቴ ትሙት በደንብ አርጎ ነው የተጫወተባት አልኩኝ ጮክ ብዬ መጮሄ ሳይታወቀኝ።
ለኔ በአለም ደስ የሚሉ ግን ያልተፃፉ ህግ አስከባሪም ፍርድቤትም ዳኛም ሳያስፈልጋቸው ከሚተገበሩ ተፈጥሮአዊ ህጎች አንዱ
"ሁሉም የእጁን ያገኛል "የሚለው የውስጤ እምነት ነው ማንም ቢሆን በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ የዘራውን ማጨዱ የማይቀር ነው
ይዘግይም ይፍጠን፡ ይነስም ይብዛ ቅጣቱን መቀበሉ የማይቀር ነው
ስንቶቹን በክፋቷ አሳልፋ እንዳልሰጠቻቸው እሷን ከክፉ የሚጠብቃት ከሷ በብዙ ክንድ ራቀና አጋለጣት በክፋታችን ያራቅነውን የላይኛውን ጠባቂ የትኛውም የምድር ሀይል ሊተካው አይችልምና አብሯት የነበረው የሰፈራችን ሰውዬም አስረክቧት ፈረጠጠ።
ቪድዮውን ዘጋሁትና የድምፅ ቅጂ መልእክትን ከፈትኩት።
የድምፅ ቅጂው በሁለት ሰዎች መካከል የተደረገን ምልልስ ይዟል ።
የት እንደገባ እስካሁን ያልተመለሰልኝን ያንን ሽንት ቤት ድረስ ሄጄ የፈለኩት ሰውዬ ተከትሎት ሄዶ ሲያናግረው ይጀምራል•••
በቅጂው የመጀመሪያ አስር ሰከንዶች የኮቴ እና በጭፈራ ቤቱ በዛች ቅፅበት ሲዘፍን የነበረው የ ቦብ ማርሊ ዘፈን በስሱ ይሰማል ።
ልክ አስራ አንደኛው ሰከንድ ላይ •••
"ጤና ይስጥልኝ ?
ጤና ይስጥልኝ ምን ነበር እንተዋወቃለን ወንድም?
እኔ እንጃ እንተዋወቃለን መሰለኝ እንካ እስቲ እሄን ተመልከት!
ምንድን ነው እሱ ?
አይታይህም እንዴ መታወቂያ ነዋ !
ያ የሰፈራችን ሰው መታወቂያውን ካየ በኋላ መሰለኝ ድምፅ ተቀየረ።
ታድያ ም-ም-ም-ም-ም-ምን ልታዘዝ ጌታዬ? በርግጥ አላወኮትም ወይ ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ?
ያጠፋሁት ነገር ይኖር ይሆን ትላለህ እንዴ ደሞ?
ለነገሩ ላንተም ለብዙዎቹም ለህግም ጥፋት መስሎ የማይታይ ጥፋት ስለሆነ አይታወቅህም
ማለት? እንዴት? መቼ? ምን አድርጌ ? የኔ ጌታ እስቲ ና አረፍ በልና ልጋብዝህ እየጠጣን እናውራ!
ህሊናቸውን በብራቸው ቁልል አፍነው የትውልድን አእምሮ የሚያቀንጭር ስራ ላይ ከተሰማሩ ከብቶች መሀል አንዱ ነህና ሰውን ሁሉ በብር በግብዣ ከመግዛት የሚሻገር አስተሳሰብ የለህም እንኳን እኔን ልትጋብዘኝ ከዚች ሰከንድ ጀምሮ አብረሀት ያለችውን አንድ ፍሬ ልጅ ደግመህ ሳታያት እዚሁ ቆሜ እያየሁህ በጓሮ በር ሹልክ ብለህ ጥፋ! ያለበለዚያ •••
ኧረ እሺ እሺ ጌታዬ እሄዳለሁ ግን የጓሮ በር ያለው አይመስለኝም ቤቱ!
በዛጋ ወደ ሽንት ቤቱ መጊቢያ በስተቀኝ በኩል ባለችው ቀጭን መንገድ ወደ ውስጥ ትንሽ ሄደህ ደረጃውን ቁልቁል ስትወርድ በር ታገኛለህ
እሺ ጌታዬ እሄው ያለብኝ ሂሳብ ነው!
ፍጠን!
እሺ እሄው ሄድኩኮ!"
ሰውየውን በዚህ መልኩ ቆሌውን ገፎ ማባረሩን ሳዳምጥ ከተሰማኝን ደስታ ጋር ግን እሄ ሰውዬ ማን ነው? ለምንድን ነው መታወቂያውን ሲያሳየው እንደዛ ምላሱን የዋጣት ይመስል ንግግሩ ሁሉ የተቆላለፈበት ?የሚለው ጥያቄ ገዝፎ አንቃጨለብኝ!።
ሰውየውን ለግዜው እንቆቅልሽ እንደሆነብኝ ተውኩትና ጆሲን ቀስቅሼ ከማታ ጀምሮ የተፈጠረውን ነገር ነገርኩት።
"ለማንኛውም ቪድዮውን ለመሲ ከመላክህ በፊት አስብበት ማለቴ አረጋጋው !" አለኝ።
ቅዳሜን በጣም እወዳታለሁ በዛ ላይ ዛሬ ከኤዱ ጋር ቀጠሮ አለን።
ከቀኑ ልክ 7:30 ላይ ኤዱ ደወለችና ሰፈር መድረሷንና ያለችበትን ቦታ ነገረችኝ ።
ስትነሺ ደውይልኝ መጥቼ እወስድሻለሁ ብያት ስለነበር ለምን ቀድማ እንዳልደወለችልኝ እየጠየኳት ከቤት ወጣሁና ብር ላይ, ያቆምኳትን ባጃጄን! አስነስቼ ከነፍኩ ።
እነሱ ሳያዩኝ ገና ከሩቁ እንዳየሁዋቸው ደነገጥኩ ግን ምን አስደነገጠኝ ? እኔ እንጃ!
ኤዱ ብቻዋን አልነበረም የመጣችው ሶስት ናቸው ከረድኤት አንድ ባለባበሱ ፍንድትድት ያለ ወጣት ወንድ አብሮአቸው አለ።
ማንም አብሮአቸው ቢኖር ግን ምን አገባኝ ?
ግን ለምን ሶስት ሆነው እንደሚመጡ ቀድማ አልነገረችኝም ?
ግን ማን ነው? እያልኩ መልስ በለላቸው ጥያቄዎቼ እራሴንም ባጃጇንም እያጣደፍኩ አጠገባቸው ደረስኩ።
ከሷ እና ከረድኤት ጋር በመተቃቀፍ ሞቅ ያለ የቅርብ ሰው ሰላምታ ከተለዋወጥን ብሀላ ፈንጠር ብሎ ሞባይሉን የሚነካካውን ልጅ እያመለከተችኝ ዳንዬ ተዋወቀው ባለፈው ከመሲ አስመለጠኝ ያልኩህ የክፍሌ ልጅ ፣ ጓደኛዬ እሱ ነው አለችና ደሞ እሱን
ቴዲዬ ተዋወቁ ምርጥ ወንድሜን " አለችው
ልጥጥ እንዳለ እጁን ዘርፕጋልኝ ጨበጥኩትና ግቡ እንሂድ አልኳቸው።
ባጃጅ ውስጥ ገብተው ወደቤት እየሄድን በመካከላችን ወሬ ጠፋ!።
በኔ በኩል የልጁ ሁኔታ ይሁን ሌላ ባይገባኝም የሆነ ደስ የማይል አዲስ ስሜት ውስጤ ሲላወስ እያዳመጥኩት ነበርና ዝም ማለቴንም አላስተዋልኩትም ነበር ።
እቤት እንደደረስን የውስጤ ስሜት ፊቴ ላይ እንዳይታይ እየታገልኩ ላጫውታቸው ብሞክርም ልጁ እኔ ከረድኤትም ይሁን ከኤዱ አልያም ከሁለቱን ጋር ወሬ ስጀምር እየጠበቀ በማክሸፍ ነበርና የራሱን የሚተኩሰው ሊያስወራኝ አልቻለም።
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቡሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ ••••••••••••••••••••

ይቀጥላል....

@yefikrclinic

@yefikrclinic
9🕊1
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 16

.
.
.
ስላቆየንባቹ በጣም ይቅርታ እንጠይቃለን🙏
.
.
መናደድ ጀመርኩ። ልጁ እኔ ብቻ ላውራ
አድምጡኝ በማለት የሚከተለውን ሙድና የኔን ንዴት በመጠኑም ቡሆን የተረዳችው ኤዱ ጀርባዋን ለሱ ሰጥታ እኔን ለማዋራት ሞከረች።
ከቆይታ በኋላ ካርድ ልግዛ በሚል ሰበብ ወጣ ብሎ ሲመለስ በፊት የነበረበትን ቦታ ትቶ እኔና ኤዱ መሀል ገብቶ ሲቀመጥ ንዴቴን መመጠንም መቆጣጠርም አቅቶኝ ጠፍቶ ድንገት ሀይል ጨምሮ እንደመጣ መብራት ሁለመናዬ ቦግ
••••
ቦግ አለ። ነደድኩ!፤ ፊቴ ተቀያየረ!፤ ደምስሬ ተወጣጠረ!
ልጁ ግን አየት አደረገኝና ከቁብም ሳይቆጥረኝ •••
"ኤድሻ ፌስ ቡክ ላይ የሆነ ፈን ነገር አይቼ እኮ ነው ቆይ ላሳይሽ እይውሟ እሄንን፤ እሄን አየሽው"እያለ ከሞባይሉ ላይ አይኗ እንዳይነቀል ስላደረጋት እሷም ሳታየኝ ተንጨርጭሬ እንደቀዘቀዝኩ ሆን ብሎ እኔን ለማናደድ እንደዛ እንደሚያደርግ በደንብ ያስታውቃል ብድግ አልኩና•••
እቤቴ ባትመጣ በዚህ አመት ከተጣላኋቸው ሰዎች አንዱ ትሆን ነበር ግን ምን ያረጋል
እቤቱ የመጣን ሰው ካልነከስኩ የሚለው ውሻ ብቻ ነው ውሻ ነገር ነህ አቦ! ገገማ! እያልኩ በውስጤ እየተሳደብኩ ተነስቼ ወጣሁና ግቢ ውስጥ ፊቴን መታጠብ ጀመርኩ።
ተመልሼ ስገባ እራሱ እያወራ እነሱ ሳይስቁ እራሱ ይስቃል ። የነበረን ቆይታ በልጁ ምክንያት ምኑም ሳይጥመኝ በሱ ውትወታ " በቃ እንሂድ" ብለው ተነሱ አላግደረደርካቸውም።
ከቤት እንደወጣን ግቢ ላድርሰችሁ ? አልኳቸው።
ከልቤ ነበር ከኛ ሰፈር ግቢ ድረስ ኮንትራት ካልያዙ በስተቀር ቀጥታ የሚወስዳቸው ታክሲ የለምና እንዳይቸገሩ ብዬ በማሰብ
"ስራ ትወጣለህ እንዴ ከዚህ ቡሀላ? አለችኝ ኤዱ
ስራ እንደማልወጣና እነሱን ብቻ አድርሻቸው ወደ ቤት እንደምመለስ ስነግራት•••
" አይሆንም በቃ ለኛ ብለህማ እዛ ድረስ መድከም የለብህም በትራንስፖርት እንሄዳለን!" ብላ ድርቅ አለች!
ተሰነባብተን ወደ ቤት ተመለስኩ።
አመሻሹ ላይ ጆሲ ድንገት በሩን ብርግድ አድርጎ ሲገባ ደንብሬ ተነሳሁ•••
"በለው በለው በቅዳሜ ቀን መጋደም ! ምን ሆነሀል አንተ ? እኔኮ የዳኒ እንግዳ ሄደች እንዴ ብዬ ሚሚ ባለሱቋን ስጠይቃት " ቆዩኮ ከወጡ!" ስትለኝ ገርሞኛል ቆይ ቆይ•••
በማህበር ተደራጅተው ነው እንዴ የመጡት?
እኔ እሷን ብቻ የቀጠርካት መስሎኝ አደል እንዴ የተቀየስኩት እዚሁ ደቅ ብዬ የቅዳሜ በርጫየን እንዳላጣጥም መሄድ እማልፈልግበት ቦታ ሄጄ ተጦልቤ ነው የመጣሁት ሰራህልኝ አቦ ቀጥሪያታለሁ ትመጣለች ከምትለኝ ይመጣሉ አትለኝም ወይ ምናለ ከመጡ ቡሀላስ ብትደውል መጥቼ ጀማውን እቀላቀል አልነበር እንዴ ! ግን እንዴት ነበር ውሎ?"
ኧረ ብትኖርልኝ ይሻለኝ ነበር ጆስዬ እኔም የመጨረሻ ተደውኬ ነው የዋልኩት !።
"እንዴ ለምን?" አለኝ ከበር ላይ ወደ ውስጥ ገብቶ አጠገቤ እየተቀመጠ
አላ! አብሯት የመጣው ልጅ ደዋኪ ነገር ነው ባክህ
"ማነው ልጁ ዝም ብሎ ጀለሳቸው ነው ወይስ•••?
አቦ ! ያ ነዎ! ባለፈው መሲ ልታስበላት ስትል ከጀለሶቹ ጋር ቀመር ቀምረው አስመለጣት ብዬ የነገርኩሁ የክፍሏ ልጅ
የፈራሁት ደረሰ ወይኔ ወንድሜን አንተ በህትነት ምናምን ነው እምንከባከባት እያልክ እራስህንም እኔንም ስትሸውድ በፍቅር የሚንከባከባትን አምጥታ አስተዋወቀችህ? ፍቅረኛዬ ነው ተዋወቀው ብላህ እጅ አፈችው አደል ?"
ውይይይይ ጆሲ ደግሞ እስቲ አሁን ማን እንደዛ አለ ? እንደዛ አለችኝ አልኩህ? ወጣኝ!?
"ታድያ እንደዛ ካልሆነ ምን አናደደህ? ብዬ ነዋ!"
አሃ! እኔ እምናደደው እሱ ስለጠበሳት ብቻ ነው ማለት ነው?
"ታድያ ፍላጎቱ እንደዛ መሆኑን ወይ አብሯት መሆኑን ብታውቅ እንጂ በምን ትናደዳለህ በዚ የማትናደድ ከሆነማ በምንም ልትናደድ አትችልም!"
ማለት?
"በዚህ ካልተናደድክ ሌላው ምክንያት እንዳለ ከዚህ በታች ነው ብዬ ነዋ!"
ይሆናል ብሎ ከመደምደም በምን ተናደድክ ብሎ መጠየቅ አይሻልም?
"እሺ በምን ተናደድክ?"
በቃ ልጁ እኔን ብቻ አድምጡኝ ከኔጋ ብቻ አውሩ ሙድ የሚያራምድ ነገር ነው ማለት•••አልኩና ከመጡ ጀምሮ የነበረውን ሁኔታ ነግሬው ሳበቃ••••
"ካካካካካ•••!" ሳቁን ለቀቀው!።
ምን ያስቅሀል?! አልኩት ተናድጄ!
" አይ ዳንዬ በዚህ ያልተሳቀ በምን ይሳቃል የፍቅርን አመል ስለማውቀው ነው አንድ ፈላስፋ ምን እንደሚል ታውቃለህ••••"
አላውቅምም ደሞም እንዳታወራልኝ ! ኤጭ አሁንስ አንተና ያ ጓደኛህ ወሬያችሁ ጅማሮውን በሙሉ
" አንድ ፈላስፋ ምን እንዳለ ታውቃለህ?
"እገሌ የተባለው መፅሀፍ ላይ ምን እንደሚል ታውቃለህ?
አንድ ምሁር ሰው ምን እንዳለ ልንገርህ?
በሚል እያሟሻችሁ የራሳችሁን ሀሳብ በቀላሉ ሰው እንዲቀበለው ለማድረግ የምትሄዱበት መንገድና
አለም ላይ ምን ተፈጠረ ብዬ ዜና ለማዳመጥ በተቀመጥኩ ቁጥር የሀገራችን የቲቪና ራድዬ ሚድያዎች
"ምሁራን ተናገሩ!
የህግ ባለሞያዎች ገለፁ!።
ነዎሪዎች እንዲህ አሉ !/
እገሌ እንዲህ አለ
እገሊት እንዲህ አለች" እያሉ የግልን አስተያየት ምልከታ አንድ ሰአት በሙሉ ዜና ብለው የሚያደርቁን ነገር እንዴት እንደሰለቸኝ •••
"በናትህ ይጠቅምሀል እቺን ብቻ አድምጠኝ ፈላስፋው እውቅ የግሪክ ፈላስፋ ነው ምን አለ መሰለህ ••••" ብሎ ሊቀጥል ሲል•••
በናትህ ተወኝ አልኩትና በንዴት ተነስቼ ክፍሉን ለቅቄለት ወጣሁ ። ስራ አልወጣም ያልኩት ሰውዬ ባጃጄን አስነስቼ ወደ ከተማ ከነፍኩ።
ንዴቴን በስራ ለመርሳት ተፍ ተፍ ስል አምሽቼ ልክ ከምሽቱ አራት ሰአት አከባቢ ከገንደቆሬ ወደ ሼል እየመጣሁ ብሎሰም ሆቴል ክርባው ጋር እንደደረስኩ አንድ እድሜው በአርባዎቹ መጀመሪያ ላይ የሚሆነው ፈርጠም ያለ ጎልማሳ ሰው ሁለት እጁን በየተራ እያርገበገበ•••
"ባጃጅ ኮንትራት ኮንትራት " አለኝ ። አቆምኩና
የት? አልኩት ፉቱ ላይ እንደእሳት የሚንቀለቀለውን ንዴቱን እያስተዋልኩ
"የት እንደሆነች አላውቅም !
የገባችበት ጉድጓድ ውስጥ ገብቼ እስካገኛት ከኔ ጋር ነህ!
ያልከኝን እከፍላለሁ !"
አለኝና መጀመሪያ የምንሄድበትን ሆቴል ነገረኝ።
እየሄዱን በየመሀሉ •••
" እኔ ላይ! ለኔ እሄ ይገባኛል!" እያለ የአንዱ እጁን መዳፍ በሌላኛው እጁ ቡጢ ያጎነዋል።
ተናድጄ ብወጣ ከኔ የባሰ በንዴት የተከነ ሰው አጋጠመኝና የራሴን ንዴት ረሳሁት። ምን ሆኖ ይሆን እንዲህ ግብግብ ያለው? አልኩ ለራሴ።
ምን ሆነህ ነው ዘመዴ? አልኩት ፈራ ተባ እያልኩ•••
"ወይይይ ሴት ! አይይይ ሴት ገና ለገና ለሳምንት ያህል ለስልጠና ሀረር ሄጃለሁ ስላልኳት በከተማው የለም ብላ እግሬ ከመውጣቱ ቱ የማትረባ !
እሄማ መጀመሪያ የተቀባበለ እንጂ ሄጄ ገና ሶስት ቀን እንኳን ሳይሞላኝ ኬት ይመጣል እስካሁንም እየተጫወትሽብኝ ነበር ማለት ነው እኔ አንቺ ለማግባት ስሰናዳ በግዜ ጉድሽን ያሰማኝ!
ዛሬ ምን እንደሚውጥሽ አያለሁ "! አለ ።
ከንግግሩ ለኔ ጥያቄ መልስ እየሰጠኝ ይሁን ብሶቱን እየተነፈሰ መረዳት ተሳነኝና ግራ ተገብቼ ዝምታን መረጥኩ ።
16
ትንሽ ቆየና •••
"የገዛ ጓደኛዬ አይቷት አይቷት እኮ ነው የደወለልኝ በአይነ ብረቱ ነው ያያት ወይኔ ደጉ ደግነቴን የዋህነቴን አይታ ነው የተጫወተችብኝ እነሱ እኮ ደግ ወንድ አይወዱም ዛሬ እጅ ከፍንጅ ስይዛት ምን እንደሚውጣት አያለሁ አጠገባ ያለውን ሰውዬ ትውጠው እንደሆነ እንተያያለን !"አለ።
ሁሉም ነገር ገባኝ። ፍቅረኛውን ከሰው ጋር ያያት ጋደኛው ደውሎለት እንደመጣ ተረዳሁ። በዚህ ሁኔታው ቢያገኛት ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት በመውረድ እጁን እያወናጨፈ ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲግሰግስ ወርጄ ተከተልኩት
•••••••••••••••••

ይቀጥላል....

@yefikrclinic

@yefikrclinic
6
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 17

.
.
.

ምን ሊፈጠር እንደሚችል ሳስበው ጨነቀኝ ።
ከሰው ጋር ታየች የተባለበት ሆቴል በር ላይ እንደደረስን በፍጥነት በመውረድ እጁን እያወናጨፈ ወደ ሆቴሉ ቅጥር ግቢ ሲግሰግስ ወርጄ ተከተልኩት•••
ወደ ውስጥ ስንዘልቅ ያን ያህልም ሰው ስላልነበረ አየት አየት አድርጎ እየወጣን•••
"የለችም ባክህ••• እዚህ መጥታ ጭር ሲል ደብሯት ቦታ እንቀይር ብላው ይሆናል አውቃታለሁ እኮ ልትዝናና ስትወጣ ግርግር ትወዳለች ሰው ከማን ጋር እንደሆነች እንዳያስተውላት ነው መሰለኝ ከኔም ጋር ስትዝናና ቦታው በሰዎች ጢም ካላለ አይመቻትም!
ወይኔ ደጉ ያኔ መች ገባኝ !
አሁን አሁን እኮ ነው ቀስ እያለ ነገረ ስራዋ በሙሉ የሚገለጥልኝ •••
የባጥ የቋጡን እየለፈለፈ ተመልሰን ባጃጇ ውስጥ እንደገባን •••
"ንዳው! ንዳው! አለኝ።
ወዴት ልንዳው? ስለው•••
"ከሶስቱ ውጪ አትሆንም!" አለና •••
ትኖራለች ብሎ የሚጠረጥርባቸውን ሶስት ጭፈራ እና ሆቴል ቤቶች ነግሮኝ•••
"ከሚቀርብህ ጀምር" አለኝ።
በቅርብ ወዳለው አዙሬ መንዳት እንደጀመርኩ ፍቅረኛውን ከሌላ ሰው ጋር ስትቀብጥ ያያት ጓደኛው ሲደውልለት ከምሽቱ ሁለት ሰአት ተኩል አልፎ እንደነበርና በብስጭት ከሀረር ብቻውን አንድ ሚኒባስ በመያዝ የሙሉ ሰው ከፍሎ እንደመጣ ነገረኝ።
አሳዘነኝ።
ምናልባት የእውነት ሆኖ ከሆነ የሆነው ሆነ የኔ ስጋት ግን በሷ መከዳቱ ሳያንስ በብስጭት ያልሆነ ፀብ ውስጥ ገብቶ መታሰር የሚሉት ሌላ ጣጣ ውስጥ እንዳይገባ ነው።
ቢረጋጋ ጥሩ ነበር ምን ብዬ ላረጋጋው ? ትንሽ አሰብ አደረኩና•••
ቆይ ብታገኛት••• ማለቴ እንደተባለው ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት ምን ልታደርግ ነው?
"እኔ እንጃ ብቻ ላግኛት ያኔ የሚሆነው ይሆናል በናትህ ራቅ ስለሚል ፍጠን!
በበኩሌ ከወንድ ልጅ ጋር ተዝናናች ማለት ወሰለተች ማለት ነው ብዬ አላምንም!
ተዝናንታ ክብሯን ጠብቃ ወደ ቤቷ ልትመለስ አስባ ሊሆን እንደሚችልም ማሰቡ ጥሩ ነው ያንን ካሰብክ ቡሀላ የሚፀፅትህን ነገር ከማድረግ ትቆጠብና ቅድሚያ ቢያንስ እርግጠኛ ለመሆን ትሞክራለህ አይመስልህም ስለው•••
አይመስለኝም በጭራሽ አይመስለኝም እኔ የፍቅር ሂወቴን በመሰለኝ ሳይሆን ልቤ በሚለኝ በራሴ እምነት ነው የምመራው
በኔ እምነት ሴት ልጅ አንሶላ የተጋፈፈች ቀን ሳይሆን ወንዶችን ቀለል ብላ የመቅረብ ባህሪ ያላት መሆኑን ያወኩ ቀን ነው እምነቷንና እምነቴን የምታጎድለው!"
ማለት?•••
ቀለል ብላ የመቅረብ ስትል ጭራሽ የወንድ ዘር መቅረብ የለባትም እያልከኝ እንዳይሆን?! ስለው•••
"አንድ ነገር ልጠይቅህ ?" አለ ።
ጠይቀኝ•••
"ለግዜው የማይፈልገው ገንዘብ እንዳለው ማበደር እንደሚችል እያወክ 300 ብር አበድረኝ ስትለው የለኝም ብሎ የከለከለህን ሰው በሌላ ግዜ አንድ ሺ ብር አበድረኝ ብለህ ትጠይቀዋለህ?
ካላበድኩ በስተቀር እንኳን ሺ አንድ ብርም አልጠይቀውም ግን እሄ ከፍቅር ወይም ካነሳነው ጉዳይ ጋር ምን አገናኘው?
"ሌላ ጥያቄ ልድገምህ ያኔ በምን መልኩ እንደሚገናኝ ሳልነግርህ እራስህ ትረዳዋለህ"
እሺ ቀጥል•••
"ታክሲ ውስጥ ባጋጣሚ አጠገብህ የተቀመጠችውን ሴት ልታዋራት ልታጫውታት ስትሞክር ፊቷን እንዳኮማተረች ወደ አንተ አንድም ግዜ እንኳን ዞራ ሳታይ ልክ እንደሹፌሩ ፊት ለፊቷን ብቻ እየተመለከተች ጫወታህን ባጭር ባጭሩ ዝግት የሚያደርግ መልስ እየመለሰች ብታከሽፍብህ ከመለያየታችሁ በፊት ስልክ ቁጥሯን ለመጠየቅ ትደፍራለህ?"
ሰውየው ነገሮችን ቤት በኩል እያገናኛቸው እንደሆነ እያሰላሰልኩ መልስ ሳልሰጠው ስለ ዘገየሁ•••
"መልስልኛ! ትጠይቃታለህ?!
እንዴ ፊቷን አጨማዳው እንዴት ልጠይቃት እችላለሁ አልጠይቃትም መጀመሪያ ልግባባት ስሞክር ፊት ከነሳችኝ ከታክሲው እስክወርድ ዞሬም ሳላያት እንደምሄድ እርግጠኛ ነኝ።
" አየህ መጀመሪያ ቀለል ብላ አንተ የባጥ የቆጡን ስትቀባጥር ከገለፈጠችልህ ግን ስልክ ለመጠየቅ ቀለለህ ማለት ነው!
ስልክ ስጠይቅ በቀላሉ ከተሰጠህ ደግሞ ደውሎ እንገናኝ ልጋብዝሽ ለማለት ቀለለህ••
ግብዣህን በቀላሉ ከተቀበለች ወደ ቀጣዩ ጉዳይህ ለመግባት አልጋ ባልጋ ሆነልህ ማለት ነው ስለዚህ እቺ ሴት የኔዋ ብትሆን እምነቷን የሸረሸረችው መቼ ነው? ብዬ እራሴን ብጠይቅ
በኔ እምነት አልጋ ውስጥ ሳይሆን ታክሲ ውስጥ የተገናኛችሁ ቀን ነው ያን ቀን እኔ ባጋጣሚ እሷ ሳታየኝ ከጀርባችሁ ቁጭ ብዬ ቢሆን መጨረሻችሁን አልጠብቅም እንደከዳችኝ የምቆጥረው ያኔውኑ ነው!"
ሲለኝ የእውነት ነበርና አመለካከቱ ያስደነገጠኝ•••
በዚህ ሀሳብህ በፍፁም አልስማማም እስቲ አንተንም አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ አንዳንድ ሴቶች
ፍቅረኛም ባልም ሳይኖራቸው ፣ ያሉበት ሁኔታ ፍቅር ለመጀመር ፈቅዶላቸው፣ ውስጣቸውም ፍቅር ለመጀመር ፍላጎት እያለው
በዛ ላይ ሽቅርቅር ብለው እየወጡ በተለያየ አጋጣሚ ከወንዶች ጋር በተገናኙ ቁጥር ወንዶቹ ሊቀርቧቸው ሲሞክሩ ኮሶ የጋቷቸው ይመስል
ፊታቸውን ከስክሰው የወንዶችን ቆሌ የሚገፉት በምን ምክንያት ነው?ስለው•••
"አይነጥላ ነው አዎ አይነ ጥላ ያለባት ሴት ካልሆነች በስተቀር በዚህ ሁኔታ ላይ ሆና በጤናዋ እንደዚህ የምትሆን ሴት ብዙ የምትኖር አይመስለኝም! ብሎኝ አረፈው። ሳይታወቀኝ እየጮህኩ•••
አትሳሳት ይልቅ •••
የተግባባች ፣ የሳቀች፣ ወንዶችን በቀላሉ የቀረበች ሴት ሁሉ ሌላ ፍላጎት አላት የተኮሳተረች ሴት ሁሉ ደግሞ ፍላጎት ስለለላት ነው ብለህ መደምደም ትልቅ ስተት መሆኑንን ብታምን የተሻለ ይመስለኛል!
አንተ ምናልባት ከፍቅረኛህ ውጪ ልክ እንደወንዶች ጓደኛችህ በጓደኝነት የምትቀርባቸው ሴቶች ከለሉ አላቅም!
እኔም ወንድሜቼም ጋደኞቼም በዚህ መልኩ የምንቀርባቸው ሴቶች አሉ አንዳንድ ሴቶች እንደውም ሁሉም ወይም አብዛኛቹ የቅርብ ጋደኛቻቸው ወንዶች እንዲሆኑ እንደሚፈልጉና እንደሆኑም የሚናገሩ አሉ ።
በጋደኝነት ህይወታቸው ወጣ ብሎ ከመዝናናት አንስቶ ብዙ ነገሪችን በጋራ ያሳልፋሉ ያ ማለት በተገኘው አጋጣሚ በሙሉ ሌላ ጉዳይ ውስጥ ይገባሉ ማለት አይደለም!።
"እሱማ ፍቅረኛ ወይም ባል ሳይኖራቸው ሊሆን ይችላል"
ኧረ እያላችው ! እሄውልህ ማናችንም ብንሆን የምንፈልገውን ነገር ለማድረግ የሚከለክለን የፍቅር ጓደኛ መኖር ወይም አለመኖሩ ሳይሆን የውስጣችን ስብእናና የልባችን ትርታ ብቻ ነው
ምንም ነገር ለማድረግ መቀራረብ ሳይሆን መተዋወቅ በማያስፈልግበት በዚህ ዘመን ፍቅረኛህን ታሟኝ የምታደርገው ወንድ አትቅረቢ እያልክ በመጮህ ሳይሆን እራስህን ልቧ ውስጥ ማስቀመጥ ከቻልክ ብቻ ነው ያለበለዚያ ፍቅረኛ ሳይሆን እረኛ ሆነህ ትቀራለህ"! አንተን ለማለት ፈልጌ አይደለም ይቅርታ አመለካከቴን ነው ያወራሁት አልኩትና በዛው ቀጠል አድርጌ•••
ወደ ሆቴሉ እየደረስን ነው ይልቅ አሁን ወደ ጉዳያችን እንመለስና እንደታናሽ ወንድም እምመክርህ ምናልባት ከሰው ጋር ሆና ብታገኛት በኔ በኩል ኩሩና በሳል ወንድ ሆነህ ብታሳያት ደስ ይለኛል!
"ማለት?!"
የተባለው እውነት ሆኖ ከተገኘ በቃ አለ አይደል ምንም ሳትናደድ
17👏2
ለሁሉም ነገር አመሰግናለሁ እንኳንም በግዜ አወኩሽ መልካሙን ሁሉ እመኝልሻለህ!" ብለህ ብቻ ብትለያት
"ምንምንምምን !? "ያልተነካ ግልግል ያውቃል" አሉ ደሞ መች በግዜ አወኳት ከዛ በፊት ያንከራተተችኝን ተወው እሺ ብላኝ አብረን ከሆንን እንኳን አንድ አመት ከስድስ ወር ሆኖናል እኮ!"
ቢሆንም ገና አልተጋባችሁም ብዬ ነዋ!
"እና ባንጋባስ?!"
ማለቴ እንደምታገባት እርግጠኛ ካልሆነች•••
አልኩና መናደዱን ከድምፁ በመረዳቴ ያሰብኩትን ሳልጨርሰው ዝም አልኩ•••
"ካልሁነች ምን?! ጨርሰዋ !
ኧረ በናትህ ተወኝና ዝም ብለህ ንዳ አንተ ደሞ
ነው ወይስ አብሯት ያለው ሰውዬ አጎትህ ነው ብዙ ተከራከርክላት እኮ !"
ሲለኝ እውነትም ዝም ብዬ ብነዳስ አልኩና ዝም አልኩ ።
እንደደረስን ምንም ሳይለኝ ወርዶ ወደ ሆቴሉ ሲገባ ተከትየው ገባሁ።
በር ላይ ቆም ሲል ቆምኩ።
ወደውስጥ ገልመጥ ገልመጥ አደረገና ካጠገቤ ድንገት ተፈናጥሮ በመሄድ ቀዝቀዝ ባለው ዘፈን, ጥንድ ጥንድ ሆነው ተጣብቀው ከሚወዘወዙት መሀል•••
•••

ይቀጥላል....
@yefikrclinic
7🔥7👏2🕊2
🥰 ልጩህበት! 🥰

ክፍል- 18

.
.
.
ስላቆየንባቹ በጣም ይቅርታ እንጠይቃለን🙏
.
.

ኧረ በናትህ ተወኝና ዝም ብለህ ንዳ አንተ ደሞ
ነው ወይስ አብሯት ያለው ሰውዬ አጎትህ ነው ብዙ ተከራከርክላት እኮ !"
ሲለኝ እውነትም ዝም ብዬ ብነዳስ አልኩና ዝም አልኩ ።
እንደደረስን ምንም ሳይለኝ ወርዶ ወደ ሆቴሉ ሲገባ ተከትየው ገባሁ።
በር ላይ ቆም ሲል ቆምኩ።
ወደውስጥ ገልመጥ ገልመጥ አደረገና ካጠገቤ ድንገት ተፈናጥሮ በመሄድ ቀዝቀዝ ባለው ዘፈን ጥንድ ጥንድ ሆነው ተጣብቀው ከሚወዘወዙት መሀል•••
በስተግራዋ እስከ ባቷ መገባደጃ የተቀደደ ትከሻውን በዞሩ ሁለት ቀጫጭን ገመዶች ተንጠልጥሎ ከደረቷ ጀምሮ ቁልቁል ገላዋ ላይ ቀዳዋ እስኪመስል የተጣበቀ እሮዝ ቀለም ያለው የራት ልብስ ለብሷ አብሯት እሚደንሰው ሰው አንገት ውስጥ በፍቅር መርከብ እየተንሳፈፈች የምትደንሰውን ሴት ክንዷን ይዞ በመጎተት ከሰውየው እቅፍ ውስጥ መንጭቆ አወጣት!
እሷ ምን መጣ ብላ በድንጋጤ ስትዞር፤ እሱ ፊቷን አይቶ የሱ ፍቅር አለመሆኗን ሲረዳና አብሯት ያለው ሰው ይቅርታ የምትለውን ቃል ከፉ አውጥቶ እስኪጨርሳት እንኳን ግዜ ሳይሰጠው ተደፈርኩ በሚል ስሜት እንደነብር ተወርውሮ አንገቱን ሲያንቀው ዘልዬ መሀላቸው ገባሁ!
ይቅርታ አርግለት ባባ በስተት ነው በስተት ነው ስለው መጀመሪያውኑ ፊቷን እንዳየ ሲደነግጥ አስተውሎት ነበር መሰለኝ ከማነቅ ውጪ ቦክስ እንኳን ሳይሰነዝር•••
"እብድህን ወደዛ ይዘህልን ውጣ ባክህ ! ብሎ እሱን ገፈተረውና ሽምቅቅ ብላ ወደቆመችው ፍቅሩ ዞሮ •••
" አስደነገጠሽ አይደል የኔ ማር?!" አላት። እኛም በፍጥነት ተያይዘን ውልቅ አልን።
ባጃጅ ውስጥ ገብተን ወደሶስተኛው ቤት ጉዞ እንደጀመርን ድንጋጤው ለቀቀው መሰለኝ•••
"አይገርምም የሰይጣን ስራ ቁመቷ፣ ከለሯ፣ ፀጉራ ከነ አያያዟ እራሷን ቁጭ እኮ ነች በዛላይ የለበሰችው ልብስ ተውሳት ነው እንዴ እውነቴን ነው ሀሉንም ነገር ከፍቅረኛዬ የተዋሰችው እኮ ነው እምትመስለው ቢያንስ እንኳን በውፍረት መለያየት የለባቸውም ደባዋ እራሱ ቁጭ የኔዋን!" ሲል
ሳቄን በጭራሽ መቆጣጠር አልቻልኩም ኪኪኪኪኪ•••
"ሳቅ አንተ ምን አለብህ!"
እና በዛች ሰከንድ ውስጥ እሄን ሁሉ ደባዋን (ቂጧን ) ሳይቀር ማየትህ ቢያስቀኝ በኔ ይፈረዳል?
"ኧረ አይፈረድም"
እሄኔ ልጅቷ ከፍቅረኛህ ጋር በብዙ ነገሯ ትለያይ ይሆናል አንዳንዴ ውስጣችን የሚፈልገውን ነው አይናችን የሚያየው ለዛ ይሆናል።
አልኩትና በሆዴ ዛሬማ የከተሟዋ ሴቶች ሁሉ እሷን መስለው ነው እሚታዩህ ብዬ አከልኩበት።
ሶስተኛው ቤት ገባን እዛም አልነበረችም።
አሁን የቀረን አንድ ቦታ ብቻ ነው ወደዛው መብረር ጀመርን።
ልንደርስ ትንሽ ሲቀረን መንገድ ላይ ወዳለ ወደ አንድ ከፍንዳታዎችና ከዩንቨርስቲ ተማሪዎች ውጪ ሌላ ሰው ወደማይገባበት ቀውጢ ጭፈራ ቤት እየተገላመጥኩ መቸስ እዚህ አትኖርም አደል ስለው•••
ድንገት በሩ ላይ ኤዱን አየኋት ሊያውም ከዛ ልጅ ጋር!
በፍጥነት እየነዳ ድንገት ሰው እንደገባበት ሹፌር ልቤ ስንጥቅ ሲል ፍሬኑን ጭምቅ አደረኩት ባጃጇ ሲጢጢጢጢጢጢ ብላ ቀጥ ስትል ሰውየው ተፈናጥሮ ወደ ትከሻዬ መጣና ሳይመለስ •••
"ምነው! ሰው ገባብህ? ውሻ ገባብህ?" እያለ ወደ ፊት በማንጋጠጥ ምን እንደገባብኝ ለማየት ሲሞክር •••
ሰው አይቼ ነው።አልኩት።
"ማንን? አየሀት? እሷን ነው? የቱጋ? የታለች?" ሲል •••
ማነች እሷ አልኩት ግራ ተጋብቼ
" የኔዋ ነቻ! የኔዋ ጉድ ሌላ ማንን ታያለህ!"
ወይ ጉድ••••
"የጨነቀው እርጉዝ ያገባል ብለው ከሚተርቱ የጨነቀው የሚናገረውን አያውቀው ቢሉ ኖሮ ሳይሻል አይቀርም እስቲ አሁን የሱን ፍቅረኛ የት አውቂያት ነው የማያት ?
እንኳን ለኔ ለራሱም ሳትጠፋበት አትቀርም እያልኩ ውስጥ ጫጫታው ስላልተመቻቸው ሳይሆን አይቀርም ስልክ ለማናገር ወጥተው አንድ ስልክ እየተቀባበሉ በጋራ ከሚያውቁት ከሌላ ሰው ጋር እያወሩና እርስ በርስ እየተያዩ ወደ ሚሳሳቁት ወደ እነ ኤደን ከርቀት እንዳፈጠጥኩ •••
ወርደህ ቀጥ ብለህ ሂድላት ከዛ ኤዱ ቅድም ከቤት ስትወጡ ወደ ግቢ ነው እምንሄደው ብለሽ መዋሸቱ ለምን አስፈለገ እኔን ዋሽኝ ችግር የለውም ግን በዚህ ሰአት ሊያውም እዚህ በየቀኑ ፀብ በማያጣው ጭፈራ ቤት ውስጥ ምን ትሰሪያለሽ በላት በላት የሚል ስሜት ተሰማኝ።
ዘወር ብዬ ሰውየውን ሳየው እሱም ግራ ተጋብቶ እኔን ተከትሎ እነ ኤዱ ላይ አፍጥጧል።
መለስ አለና " ማነች? ታውቃታለህ? " አለኝ
ማነች ልበለው? አዎ ያክስቴ ልጅ ነች፤ የዩንቨርስቲ ተማሪ ነች በዚህ ሰአት ከወንድ ጋር ጭፈራ ቤት••••
አላስጨረሰኝም •••
"ታድያ ምን ችግር አለው አለው አብረው ተዝናንተው የሚለያዩ ንፁህ ጋደኛሞች ሊሆኑ ይችላሉ ። አለኝ በስላቅ ።
በንዴት •••
አዎ ችግር የለውም ይዝናኑ እኛም እንሂድ አልኩና ባጃጇን አስነስቼ ወደ መጨረሻው ቤት ጋለብኳት።
ደርሰን እሱ ከፊት እኔ ከጀርባው ተከታትለን እንደገባን
"ያቿትና"
አለኝ ፊት ለፊት ካንድ ሰው ጋር የተቀመጠች ቆንጂዬ ሴት ተመለከትኩ ።
ወደሱ ስዞር አራት ጣቶቹን ከንፈሩ ላይ ጭኖ እንዳፈጠጠባቸው ትንሽ ቆየና
"ውይ ውርዴት !
አቤት ቅሌት !
እሄ እኮ ውጪ ሀገር የነበረ ያክስቷ ልጅ ነው የሰርጋችሁን ግማሽ ወጪ እኔ እችላችሃምሀለሁ ብሎ ቃል ገብቴልናል! በቅርብ ነው የመጣው።
ጓደኛዬም ያላወቀው ለዛ ነው!
እነደመጣ አዲስ አበባ ነበር ያረፈው ሰሞኑን ወደ ድሬ ይመጣል ስትለኝ ነበር እንደዛ ሲፎክር የነበረው ሰው ጭራሽ "ደብቀኝ እንዳታየኝ ! "
እያለ እኔን ጎትቶ ከጀርባዬ ተደበቀና
"ዝም ብለህ ወደ ኋላ ና እንውጣ!" አለኝ።
•••

ይቀጥላል....
@yefikrclinic
@yefikrclinic
@yefikrclinic
64👍87
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
🫡2
እንደውም እግዜር ቢፈቅድ
በቸር በፀጋው ቢቀባኝ
በነጥብ ምልክት አርጎ
ከንፈርሽ ግርጌ ባስገባኝ!

አንቺም መስታወትሽ ፊት
ቀለም ልትቀቢ ከንፈርሽን
እሽኩርምም ፍንድቅ ስትይ
አያለሁና ማፈርሽን፤

ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ ማርያም በተኛሽበት
በድንገት እንደሳመችሽ
አወራሽ አይደል?
ይመችሽ!

ሳቂበት የታባቱና
ድመቂ ፍ-ክት ፍክትክት
በማርያም የተመሰልኩት
እኔ ነኝ ያንቺ ምልክት!

እንኳንስ ከንፈርሽ ግርጌ ቢያኖሩኝ ተረከዝሽ ስር
ለመኖር እንዴት ይመቻል
ሳይወደው ከኖረው ህይወት
በፈቃድ የተረገጠ አፍቃሪ መች ይሰለቻል!

ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ ማርያም በተኛሽበት
በድንገት እንደሳመችሽ
አወራሽ አይደል?

ይመችሽ!

(አስታወሰኝ ረጋሳ
)


━━━━━━━━✦🖤✦━━━━━━━━
ምርጫዎ ስለሆነ እናመሰግናለን  ❤️

       Join us 👇👇
@yefikrclinic
12
እንደውም እግዜር ቢፈቅድ
በቸር በፀጋው ቢቀባኝ
በነጥብ ምልክት አርጎ
ከንፈርሽ ግርጌ ባስገባኝ!

አንቺም መስታወትሽ ፊት
ቀለም ልትቀቢ ከንፈርሽን
እሽኩርምም ፍንድቅ ስትይ
አያለሁና ማፈርሽን፤

ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ ማርያም በተኛሽበት
በድንገት እንደሳመችሽ
አወራሽ አይደል?
ይመችሽ!

ሳቂበት የታባቱና
ድመቂ ፍ-ክት ፍክትክት
በማርያም የተመሰልኩት
እኔ ነኝ ያንቺ ምልክት!

እንኳንስ ከንፈርሽ ግርጌ ቢያኖሩኝ ተረከዝሽ ስር
ለመኖር እንዴት ይመቻል
ሳይወደው ከኖረው ህይወት
በፈቃድ የተረገጠ አፍቃሪ መች ይሰለቻል!

ለወዳጅ ዘመድ በሙሉ ማርያም በተኛሽበት
በድንገት እንደሳመችሽ
አወራሽ አይደል?

ይመችሽ!

(አስታወሰኝ ረጋሳ
)


━━━━━━━━✦🖤✦━━━━━━━━
ምርጫዎ ስለሆነ እናመሰግናለን  ❤️

       Join us 👇👇👇

@yefikrclinic

@yefikrclinic
17👍1
❤️💋በፍቅር ልሸኝህ🤦‍♀🤦‍♀


ጊዜ እንደማይቆመው ሰአትን ጠብቆ
ማለዳ ለቀትር ቦታውን አስታጥቆ
ደቂቃዎች ሰአት ቀናትና ወራት
ለአመት ሲያዘግሙ በራሪ ሰከንዶች
መርቄ ልሸኝህ ነበርን ተክቼ
ትላንቴን ዛሬዬን አሁኔን እረስቼ

ለካ ነበርን ማለት እንደዚ ይከብዳል
ያ ሁሉ ትዝታ እንዳልነበር ያልፋል
በሂወት መወሰን መደሰትም ያልቃል
ሳቅም ተቀይሮ እንባ እንኩዋን ይደርቃል
ለካ ነበርን ማለት እጅጉንም ያማል
ምክንያት አልባ ሲሆን ውስጥንም ያደማል

ቢለያይ ስሜቱ የሁለት አንዳችን
ህመሙ ቢያጋድል አንዱ ላይ ቢገንም
ሚዛኑ ቢዛነፍ ለብይን ባይሆንም
ከሳሽም ተከሳሽ ሆኜ ቀርቤአለሁ
ደስ ያለህን ፍረድ ደስ ያለህን በይን
ይግባኝ አልጠይቅም ያሻህንምተግብር

ባይሆን .......................

ፍቅርህን በቃላት በተግባር ስትገልፀው
መውደድንም ችለህ በእምነት ስትኖረው
ይህን ሁሉ አይቶ ለሽሽት መቅረቤ
ይቅርታ ለራሴ
መውደድን መቀበል ለተሳናት ልቤ
ላልታደለች ነብሴ

አሺ በቃ hubi መርቄ ልሸኝህ
ፍቅር እሚያፈቅረው ልዩ ማንነትህ
ከደስታ አጣምሮ ሳቅህን ያብዛልህ💔

━━━━━━━━✦🖤✦━━━━━━━━
ምርጫዎ ስለሆነ እናመሰግናለን  ❤️

       Join us
 👇👇👇

@yefikrclinic

@yefikrclinic
55👍9🕊1
2025/10/31 05:06:59
Back to Top
HTML Embed Code: