Telegram Web Link
የኢድ ሶላት ኃይማኖታዊ ስርዓቱን በጠበቀና በድምቀት ተከብሮ መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓልን አስመልክቶ በአዲስ አበባ ስታዲየም በአቃቂ ቃሊቲና በሌሎችም ክ/ከተማ በሚገኙ መስጂዶች የተደረገው የኢድ ሶላት ኃይማኖታዊ ስርዓቱን በጠበቀና በድምቀት ተከብሮ መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ፡፡

1446ኛው የኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በድምቀት እየተከበረ የሚገኝ ሲሆን በዓሉን አስመልክቶ በርካታ የእምነቱ ተከታዮች በአዲስ አበባ ስታዲዮም፣ በአቃቂ ቃሊቲና በሌሎችም ክ/ከተማ በሚገኙ መስጂዶች ያደረጉት የኢድ ሶላት ኃይማኖታዊ ስርዓቱን ጠብቆ በድምቀትና በሠላም ተከብሮ መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፡፡ከኢድ ሶላቱ ጋር ተያይዞ ለተሽከርካሪ ዝግ የነበሩ መንገዶች ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንም ፖሊስ ጨምሮ ገልጿል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
ከአዲስ አበባ የተሰረቀውን የሞባይል ስልክ ሀዋሳ ከተማ  ላይ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ ሁለት ልዩ ስሙ መካነ ኢየሱስ አካባቢ፣ ግሩም ግዛው የተባለ ግለሰብ 150 ሺ ብር ግምት ባለው አይፎን ፕሮማክስ 15 ስልክ እያወራ እያለ  ኮድ-2-1226 A/A  በሆነ ሞተር ላይ የነበረ ግለሰብ ከጆሮው መንትፎ  እንደወሰደበት የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

የግል ተበዳይ ስልኩ እንደተወሰደበት ወዲያው  ለፖሊስ ማመልከቱን ተከትሎ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ባደረገው ክትትል፣ በሀዋሳ ከተማ ስልኩን ገዝታ እየተጠቀመችበት ከምትገኝ ጸጋ ጴጥሮስ ከተባለች ግለሰብ እጅ ስልኩ ሊያዝ መቻሉን ፖሊስ ገልጿል፡፡

ከተሰረቀው ስልክ ጋር በቁጥጥር ስር የዋለችው ጸጋ ጴጥሮስ በበኩሏ፣ ምንተስኖት መቻል ከሚባል ግለሰብ እንደገዛች ለፖሊሰ ተናግራለች፡፡

የመንታፊዎችን ሰንሰለት አድኖ በቁጥጥር ስር ለማዋል የአዲስ አበባ ፖሊስ በሰራው ስራ፣ ምንተስኖት የተባለውን ግሰለብ ከያዘው በኋላ ሌላ ተጨማሪ አማኑኤል ሻንቆ የተባለ ሰው አብሮት እንደነበር  ባገኘው መረጃ መሰረት በቁጥጥር ስር ማዋሉን ጠቁሟል፡፡

ይህን ተከትሎም ገዢዋን ጸጋ ጴጥሮስን ጨምሮ የተሰረቀውን የሞባይል ስልክ ሸጠዋል በሚል ወንጀል የተጠረጠሩ ሁለቱን ግለሰቦች ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ አምጥቶ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ ፖሊስ አስታውቋል፡፡

በሞተር የሞባይል ስልክ ቀምቶ መሰወር ለጊዜው የማይደረስበት ቢመስልም ፖሊስ ቴክኖሎጂ በመጠቀም በእንዲህ መልኩ ወንጀለኞችን አድኖ እንደሚይዝና የግል ተበዳዮችም የትኛውም ዓይነት ወንጀል ሲፈጸምባቸው በአቅራቢያቸው በሚገኝ ፖሊስ ጣቢያ ሊያመለክቱ እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል።
በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቡለን ከተማ በተፈጸመ ጥቃት ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናገሩ 

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በመተከል ዞን፣ በቡለን ከተማ ዛሬ ንጋት ላይ ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ቢያንስ 10 ሰላማዊ ሰዎች እና የጸጥታ ኃይሎች መገደላቸውን የከተማይቱ ነዋሪዎች ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” ተናገሩ። የመተከል ዞን እና የቡለን ወረዳ አስተዳደር በከተማይቱ ላይ በተፈጸመ ጥቃት የሰዎች ህይወት መጥፋቱን፣ ባንክ ቤትን ጨምሮ በተቋማት ላይ ዝርፊያ እና ጉዳት መድረሱን አረጋግጠዋል።

ጥቃቱ በቡለን ከተማ ላይ የተሰነዘረው፤ ዛሬ አርብ ግንቦት 29፤ 2017 ከንጋቱ 12 ሰዓት ገደማ ጀምሮ እንደነበር ነዋሪዎቹ እና የቡለን ወረዳ አስተዳደር ገልጸዋል። ለደህንነታቸው በመስጋት ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሶስት የቡለን ከተማ ነዋሪዎች ጥቃቱ እስከ ረፋዱ አራት ሰዓት ገደማ ድረስ የቆየ እንደነበር አመልክተዋል።

ታጣቂዎቹ ዛሬ ንጋት ላይ ወደ ከተማ ሲገቡ መመልከታቸውን ለ“ኢትዮጵያ ኢንሳይደር” የዓይን እማኝነታቸውን የሰጡ አንድ ነዋሪ፤ መቶ ገደማ የሚሆኑ ታጣቂዎች በአንድ መስመር ሲጓዙ ማየታቸውን ተናግረዋል። ከታጣቂዎቹ ውስጥ ገሚሶቹ ቡላ ቀለም ያለው የደንብ ልብስ እንደለበሱ እና የተቀሩት ግን የሲቪል ልብስ መልበሳቸውን መመልከታቸውን አክለዋል።

ነዋሪው “ክላሽ እና ብሬል የያዙ ነበሩ” ያሏቸው ታጣቂዎች ጥቃት መሰንዘር ሲጀምሩ በቤታቸው እንደነበሩ ገልጸዋል። በጥቃቱ አስር ሰዎች መገደላቸውን፣ የባንክ እና ፖሊስ ጣቢያ መዘረፉን መስማታቸውንም አስረድተዋል።

🔴 ለዝርዘሩ ➡️ https://ethiopiainsider.com/2025/16129/
የ27 ጊዜ የአለም ክብረ ወሰን ባለቤት የሆነው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ መፅሀፍ ተፃፈለት።

የአትሌት ኃይሌን የህይወትና የስራ ፍልስፍና የሚያስረዳውን መፅሀፍ የፃፈችሁ ልጁ ሜላት ኃይሌ ገብረስላሴ ናት።ረዳት ፀሀፊው ደግሞ አባዮሚ ሮቲሚ  የተባለ ፀሀፊ መሆኑን ሰምተናል። በ12 ምዕራፍ ተከፋፍሎ የተዘጋጀውን መፃፍ ለማሳናዳት ሁለት ዓመት እንደፈጀ ፀሀፊዋ አስረድታለች።

አትሌት ኃይሌ ብዙውን የህይወት ታሪኩን ህዝብ የሚያውቀው ቢሆንም መፃህፉ የሚያተኩረው የህይወትና የስራ ፍልስፍናው ላይ እንደሆነ ተነግሯል።ለዚህም ልጁ እንደመሆኗ ከሌሎች ሰዎች በተለየ የአትሌት ሀይሌ ህይወት ለማወቅና ለመፃፍ እንዳስቻላት ሜላት ኃይሌ ጠቅሳለች።

መፅሀፉ አትሌት ከእድገቱ እስከ አሁን ባለው የሯጭነትና የቢዝነስ ምዕራፍ የተከተላቸውን አመለካከቶቹን፣ ፍልስፍናውን፣ የህይወት ልምዱ የተካተተበት መሆኑን ልጁ ሜላት ስትናገር ሰምተናታል።

ለጊዜው ''Dissecting Haile'በሚል ርዕስ ለህትመት የሚበቃው መፅሀፋ ወደፊት ወደ አማርኛ እና ሌሎች ቋንቋዎች እንደሚተረጎም ተነግሯል።መፅሀፉ ለገበያ የሚቀርበው በመጪው ነሀሴ ወር መሆኑንም ሰምተናል።የአትሌት ኃይሌን የህይወት ታሪክ የሚመለከት ሌላ መፃህፍ በማዘጋጀት ላይ መሆኗንም ልጁ ተናግራለች።

Via Sheger
@YeneTube @FikerAssefa
Ethiopian Building Code Standards
Private Sector Engagement in Code Revision: Week 2 Sessions


We’re back with five expert-led sessions in Week 2 of our 14-part workshop series, continuing the dialogue between private sector professionals and code developers:

🏢 Building Facility Management
🧯 Fire Safety & OHS
🏗 Structural Design Fundamentals
🚿 Building Plumbing Systems
📐 Spatial Design in Buildings


📅 June 10, 12 & 14, 2025
📍 The Urban Center
🖥 Also, live on TUC Facebook page & Google Meet
☕️ Free sessions with refreshments

Participants are encouraged to register only for the sessions most relevant to them.

📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7
🔗 Google Meet links will be shared 30 minutes before each session.

Many thanks to our partners for making this possible!

#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #FireSafety #StructuralDesign #Plumbing #FacilityManagement #SpatialDesign
Forwarded from YeneTube
#ከቴምር ሪልስቴት
7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ መሀል ሣር ቤት አፓርትመንት እና ሱቅ ፒያሳ ለሽያጭ ያወጣነው 

🎯የክፍያ አማራጮች 40/60 ለሚከፍል

👉1መኝታ 75ካሬ 4,815,000ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 94ካሬ 6,034,800ብር ሙሉ ክፍያ
👉2መኝታ 103ካሬ 6,612,600ብርሙሉክፍያ
👉3መኝታ 132ካሬ 8,474,400ብር ሙሉ ክፍያ
👉3መኝታ 146ካሬ 9,373,200ብር ሙሉ ክፍያ 9,373,000ብር 

‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273
https://www.tg-me.com/TemerRealEstateSalesConsultant
WhatsApp. https://wa.me/251939770177
Forwarded from YeneTube
🌺🌸  #ግእዝን_በርቀት 🌺🌸


የግእዝን ቋንቋ በ፲፬ ዙሮች እስካኹን ለብዙ ሺሕ ተማሪዎች በቀላል መንገድ ማስተማር ተችሏል። አኹን ደግሞ በ፲፭ኛ ዙር በቴሌግራም ለኹለት ወራት ( ከሐምሌ ፩ እስከ ነሐሴ ፴፥ ፳፻፲፯ ዓ.ም. በተመጣጣኝ ክፍያ ለጀማሪ ተማሪዎች የሚኾን ትምህርት ለመስጠት ስለታሰበ ባሉበት ኾነው በቀላሉ መማር ከፈለጉ አኹኑኑ
                  
@geezdistance15


የሚለውን የቴሌግራም የመጠቀሚያ ስም በመጫን ወደ ትምህርት መስጫ ቻናሉ መግባት ይችላሉ።



🌺🌸  #ግእዝን_በርቀት 🌺🌸
አሳዛኝ መረጃ

ወጣቱ ምንተስኖት ሰንበቱ ይባላል።

የወልቂጤ ዩኒቨርስቲ የ2ኛ አመት ተማሪ ሲሆን በዛሬው እለት  በከምባታ ዞን አዲሎ ዙሪያ ወረዳ በገመድ ተሰቅሎ ሕይወቱ ጠፍቶ ተገኝቷል።

ፖሊስ አስክሬኑ ለምርመራ ወደ ወራቤ ሆስፒታል መላኩ ታውቋል ።


@Yenetube @Fikerassefa
የሩሲያ ሠራዊት የዩክሬን የጦር ኢንዱስትሪ ኮምፕሌክስ ድርጅቶችና የጦር ሰው አልባ አውሮፕላን መገጣጠሚያዎች ላይ የቡድን ጥቃት መፈፀሙን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ።

@Yenetube @Fikerassefa
ሕንድ የዓለም ረጅሙን የባቡር ድልድይ አስመረቀች

የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ የዓለማችንን ረጅሙን የባቡር ድልድይ መርቀው ከፍተዋል።

359 ሜትር የሚረዝመው እና በችናብ ወንዝ ላይ የተገነባው ይሕ ግዙፍ ድልድይ የካሽሚር ግዛትን ከተቀረው የሕንድ ክፍል በባቡር የሚያገናኝ ነው ተብሎለታል። የድልድዩ ርዝመት ከፈረንሳዩ ኤፍል ታዎር በ35 ሜትር የሚበልጥ እንደሆንም ተገልጿል።

ለግንባታው 5.1 ቢሊየን ዶላር የወጣበት ይሕ ፕሮጀክት አጠቃላይ የባቡር መስመሩ 272 ኪ.ሜ የሚረዝም ነው።

በተራራማው የካሽሚር ግዛቶች ውስጥ ያለው አስቸጋሪ የመሬት አቀማመጥ ለትራንስፖርት አገልግሎት የማይመች እና አስቸጋሪ ቢሆንም ሕንድ የሰራችው ይሕ በዓይነቱ ልዩ የሆነ ድልድይ እና የባቡር መስመር በአካባቢው ያለውን የትራንስፖርት ችግር የሚፈታ ነው ሲል የዘገበው ኢንዲፔንዳንት ነው።

@Yenetube @Fikerassefa
ፍተሻ በአዲስ አበባ

የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕግ አግባብን የተከተለ ፍተሻና ብርበራ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ከሶስት ቀን በፊ ባወጣው መግለጫ፣ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች ላይ የሕግ አግባብን የተከተለ ፍተሻና ብርበራ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታወቀ።

ኅብረተሰቡ ለፀጥታው ሥራ ስኬታማነት እያደረገ ያለውን ትብብር አጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ፣ የከተማውን ሰላምና ፀጥታ ሥጋት ላይ የሚጥሉ ወንጀለኞችን አስመልክቶ ለጠቅላይ መምሪያው በደረሱ ጥቆማዎችና በጥናት በለያቸው የሰላምና ፀጥታ ሥጋቶች ላይ ዕርምጃ ለመውሰድና ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የሚያስችል የተጠናከረ ቁጥጥርና ፍተሻ ለማድረግ መዘጋጀቱን አስታውቋል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ደረሱኝ ካላቸው ጥቆማዎችና በጥናት እንደለያቸው ከገለጻቸው ከባድ ወንጀሎች መካከል "የጦር መሣሪያ ዝውውር፣ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውርና ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ይገኙበታል"ብሏል።

@Yenetube @Fikerassefa
በዳነሰነች ወረዳ የኦሞ ወንዝ ሞልቶ ባስከተለው ጎርፍ 8,445 ሰዎች “ዳግም” ተፈናቀሉ

በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በተከሰተ ጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የአካባቢው መንግሥት አስታወቀ።

ጎርፍ የተከሰተው የኦሞ ወንዝ በመሙላቱ እና የቱርካና ሀይቅ መደበኛ የውኃ ይዞታውን በከፍተኛ ፍጥነት በመልቀቁ ነው። የወረዳው ባለሥልጣናት በአጠቃላይ 8,445 ሰዎች “ዳግም” መፈናቀላቸውን ገልጸዋል።

በደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ በተከሰተ ጎርፍ 1,753 አባወራዎች ከቀያቸው መፈናቀላቸውን የአካባቢው መንግሥት አስታወቀ። በወረዳው ጎርፍ የተከሰተው “የኦሞ ወንዝ ሞልቶ መደበኛ የመፍሰሻ አቅጣጫውን ለቆ በመውጣቱ እና የቱርካና ሀይቅ መደበኛ የውኃ ይዞታውን በከፍተኛ ፍጥነት በመልቀቁ” እንደሆነ የዳሰነች ወረዳ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ጽህፈት ቤት ትላንት አርብ አስታውቋል።

በወረዳው በተከሰተው ጎርፍ ምክንያት በአጠቃላይ 8,445 ሰዎች “ዳግም”

መፈናቀላቸውን የዳሰነች ወረዳ አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ኡስማን ሰይድ መናገራቸውን መግለጫው ይጠቁማል።
ከኢትዮጵያ በኬንያ ወደሚገኘው ቱርካና ሐይቅ የሚፈሰው የኦሞ ወንዝ እየሞላ የአካባቢውን ነዋሪዎች ሲያፈናቅል የአሁኑ የመጀመሪያ አይደለም።

ከዚህ ቀደም በተከሰተ ተመሣሣይ የጎርፍ አደጋ ከቀያቸው የተፈናቀሉ ሰዎች አሁንም በሦስት ቦታዎች በጊዜያዊነት ተጠልለው እንደሚገኙ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ መናገራቸውን የክልሉ የመንግሥት ኮምዩንኬሽን ቢሮ ከትላንት በስቲያ ሐሙስ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጹ ያሰራጨው ጽሁፍ ይጠቁማል። ኃላፊው እንዳሉት በ2016 ክረምት የተከሰተ ተመሳሳይ የውኃ ሙሌት “የ28 የሚሆኑ ቀበሌያትን” አፈናቅሎ ነበር።

የኦሞ ወንዝ ሲሞላ የአካባቢውን ነዋሪዎች ከቀያቸው ከማፈናቀል ባሻገር የዳሰነች እና የኦሞራቴ ከተሞችን አደጋ ውስጥ ሲጥል ቆይቷል።

@Yenetube @Fikerassefa
በወላይታ ሶዳ ከተማ በግድያ ወንጀል ተፈርዶበት በምህረት የተለቀቀው ተከሳሽ የ8 ዓመቷ ታዳጊ ላይ በፈፀመው የአስገድዶ መድፈር ወንጀል በእስራት ተቀጣ

በወላይታ ሶዶ ከተማ አራዳ ቀበሌ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል የፈፀመው ግለሰብ በእስራት እንዲቀጣ መወሰኑን የሶዶ ከተማ ፖሊስ አስታውቋል።

በወላይታ ሶዶ ከተማ የጉሩሞ ላዲሳ ቀበሌ ነዋሪ የሆነው ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማ የተባለ ግለሰብ የካቲት 15 ቀን 2017 ዓ.ም አመሻሽ 12፡30 አካባቢ የግል ተበዳይ የሆነችውን የ8 ዓመት ታዳጊ ጁስ እና ኮሾሮ ገዝቶ በማታለል የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ ተገልፆል፡፡

ግለሰቡ ከዚህ በፊት በነፍስ ግድያ ወንጀል ተባባሪ ሆኖ 14 ዓመት ፅኑ እስራት የተፈረደበትና የእስር ጊዜውን ሳይጨርስ በምህረት የወጣ መሆኑን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

የወላይታ ሶዶ ከተማ መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ግንቦት 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ኤፍሬም ጪማን በ20 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አስተላልፎበታል።

ዳጉ ጆርናል
@Yenetube @Fikerasssefa
‹‹ሠራተኞች ለመኖር የሚያስችላቸው ደመወዝ ተከፍሏቸው እየኖሩ ነው ማለት አይቻልም››  የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ)

በኢትዮጵያ ሠራተኞች ለመኖር የሚያስችላቸው ደመወዝ እየተከፈላቸው ነው ለማለት እንደማይቻል፣ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ድሪብሳ ለገሠ፣ አሁን ባለው ሁኔታ በኢትዮጵያ ሠራተኞች ደመወዝ ተከፍሏቸው በመኖር ላይ ናቸው ብሎ አፍን ሞልቶ ለመናገር የሚከብድ መሆኑን ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
በአገራዊ የምክክር ኮሚሽን በተዘጋጀ የአጀንዳ መድረክ ላይ የተገኙት አቶ ድሪብሳ ከሪፖርተር ጋር በነበራቸው ቆይታ፣ ‹‹የሠራተኞች የደመወዝና ሌሎች ዋና ዋና ጥያቄዎቻቸውን እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድረስ ስናቀርብ ቆይተናል፤›› ብለው፣ እየታዩ ያሉ ተጨባጭ እውነታዎችን ተቀብሎ በማስተካከል በኩል መዘግየቶች በመኖራቸውና በፍጥነት ካልተፈቱ ወዳልተፈለገ ግጭት ሊያመሩ ይችላሉ የሚል ሥጋት እንዳለ ገልጸዋል፡፡

Via:- Reporter

@Yenetube @Fikerassefa
መንግሥት፣ በሕገ-መንግሥቱ ውስጥ መሻሻል ያለባቸው በርካታ አንቀጾች አሉ ብሎ እንደሚያምን ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽን ባስገባው ባለ 30 ገጽ መነሻ ሃሳብ ላይ መጠቆሙን ሪፖርተር አስነብቧል።

መንግሥት፣ አንቀጾቹ "በሰፊ ውይይት"፣ "በክርክር" እና "በሙሉ መግባባት" መሻሻል እንዳለባቸው በሰነዱ ላይ መጠቆሙንም ዘገባው ጠቅሷል። ኾኖም ሕገመንግሥቱ "ሕገመንግሥታዊነት" እምብዛም ያልታየበትና እስካኹንም "በተግባር ያልተፈተነ" መኾኑን የጠቀሰው የመንግሥት ሰነድ፣ ሕገመንግሥቱን ማሻሻል አንዳንድ ችግሮች ሊያስከትል እንደሚችልም ገልጧል ተብሏል።

ከዚህ አንጻር የሕገመንግሥት ማሻሻያ ማድረግ፣ "አዲስ ሕገመንግሥት ማስተዋወቅ ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል" በማለት መንግሥት በሰነዱ ላይ ስጋቱን እንዳሠፈረም ዘገባው አመልክቷል።

@Yenetube @Fikerassefa
2025/07/05 14:25:14
Back to Top
HTML Embed Code: