Telegram Web Link
ኢባትሎ አዳዲስ መርከቦችን በሀገር ውስጥ ባንኮች ድጋፍ ሊገዛ ነው!

የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ (ኢባትሎ) የአስር መርከቦች ባለቤት የመሆን ግቡን ለማሳካት በሚደረገው ጥረት፣ አዳዲስ መርከቦችን ለመግዛት ማቀዱን እና ለዚህም ከሀገር ውስጥ ባንኮች የገንዘብ ድጋፍ ማግኘቱን አስታውቋል።የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ አዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ይህንን ግዙፍ ግዢ በጋራ ለመደጎም መስማማታቸው ተገልጿል።

ኢባትሎ አዲስ ሁለት የአልትራማክስ ሁለገብ የደረቅ ጭነት መርከቦችን ለመግዛት ጨረታ ያወጣ ሲሆን፣ በተጨማሪም አራት ያገለገሉ መካከለኛ መጠን ያላቸው መርከቦችን በመርከብ ደላሎች በኩል ለመግዛት ማቀዱን ካፒታል ሰምቷል።

የፋይናንስ ስምምነቱ ዝርዝር እንደሚያሳየው፣ አዋሽ ባንክ እና ዳሽን ባንክ ለአንድ ሁለገብ መርከብ እና ለአንድ የአልትራማክስ ደረቅ ጭነት መርከብ የገንዘብ ድጋፍ ያደርጋሉ።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሌላ በኩል አዲስ የአልትራማክስ ሁለገብ እና ሁለቱን ያገለገሉ ኮንቴይነር መርከቦችን ጨምሮ የሦስት ተጨማሪ መርከቦችን ግዥ ለመደገፍ ተስማምቷል።

በአጠቃላይ፣ ኢባትሎ ለአምስቱ መርከቦች ጠቅላላ ወጪ 30% የሚሆነውን በራሱ የሚሸፍን ሲሆን፣ ቀሪው 70% በባንኮቹ ይሸፈናል። ከዚህም ባሻገር፣ አንድ መርከብ በሙሉ በተቋሙ ፋይናንስ እንደሚደረግ ተገልጿል።

ኢባትሎ ያገለገሉትን አራት መርከቦችን በቅርብ ጊዜ ውስጥ ለመረከብ ሲጠብቅ፣ የአዲሶቹ ሁለት ሁለገብ መርከቦች ግንባታ ግን የጨረታ ሂደቱ ከተጠናቀቀ በኋላ ቢያንስ ሁለት ዓመታትን ይወስዳል ተብሎ ይገመታል።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
ጫጫታን የማያስተላልፉ(Noise Canceling የጆሮ ማዳመጫዎች አእምሯችንን ሚያታልሉት እንዴት ነው?

https://www.tiktok.com/@sociosaga/video/7522058529646202117
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ደንበኞች ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱ ተገለጸ!

ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ፍቃዱን ከተረከበ በአራት ዓመታት ውስጥ፤ በሀገሪቱ ዙሪያ ያሉ የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቹ ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዊም ቫንሄለፑት እንደተናገሩት፤ የቴሌኮም ኩባያው በኢትዮጵያ የቴሌኮም አገልግሎት መስጠት ከጀመረ አራት ዓመታትን ያስቆጠረ ሲሆን፤ በእነዚህ አራት ዓመታት ውስጥ 300 ቢሊየን ብር በላይ ሙዓለ ንዋይ ወጪ አድርጓል፡፡ 

የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቻችን ቁጥር 10 ሚሊዮን የደረሰ ሲሆን፤ 7 ነጥብ 1 ሚሊዮን የሞባይል ዳታ አገልግሎት ተጠቃሚዎች መኖራቸውን ተናግረዋል፡፡አክለውም አሁን ላይ ኩባንያው 900 ሠራተኞች ሲኖሩት ከእነዚህ ውስጥ 97 በመቶ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸውን በመግለጽ፤ በተጨማሪም ከ20 ሺሕ በላይ ለሚሆኑ ሰዎች ተዘዋዋሪ የሥራ ዕድል መፍጠሩ ገልጸዋል።

ሳፊሪኮም ኢትዮጵያ በየቀኑ 31 ሺሕ አዳዲስ የአገልግሎት ተጠቃሚዎች ደንበኞችን እየተቀላቀ  መሆኑን ተናግረዋል፡፡በአሁኑ ሰዓት ካሉት ደንበኞች 75 በመቶዎቹ በቋሚነት አገልግሎቱን እየተጠቀሙ መሆኑንም ዋና ሥራ አስፈጻሚው ጨምረው ተናግረዋል፡፡

አክለውም "በዚህ አራት ዓመት ውሰጥ ችግር ሆኖብን ነበረው፤ ተፎካካሪያችን በመንግሥት ባለቤትነት ያለ መሆኑ ነው" ብለዋል።ሳፊሪኮም ኢትዮጵያ 3 ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮ ቴሌኮም ለመሠረተ ልማት ኪራይ እንደሚከፈል የገለጹት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ኩባንያው የሚጠበቅነትን ግብር እስካሁኑ ሰዓት ድረስ በቴሌብር እንሚከፍል ተናግረዋል፡፡

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
የውጭ ሀገር ዜጎች በትንሹ 150 ሺህ ዶላር በመውጣት የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት እንዲሆኑ የሚፈቅደው አዋጅ ፀደቀ!

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ሀገር ዜጎች የማይንቀሳቀስ የመኖሪያ ቤት ባለቤት የመሆን መብት አዋጅን አጸደቀ። ከአዲስ አበባ ውጪ መስራት ቢፈልጉ በወጣው መመሪያ መሰረት ክልሎች ተፈፃሚ እንደሚያደርጉም ተገልጿል።የውጭ ሀገር ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን 150 ሺህ ዶላር ነው ተብሏል።

“አንድ የውጭ ሀገር ዜጋ የሊዝ ዋጋውን ጨምሮ ለአንድ መኖሪያ ቤት ግንባታ ሙሉ ዋጋ ወይንም ለመኖሪያ ቤት ግዢ የሚመድበው አነስተኛ የገንዘብ መጠን ከ150 ሺ ዶላር ያነሰ ሊሆን አይችልም” ተብሏል።150 ሺህ ዶላር ሁኖ የተቀመጠው አነስተኛ የገንዘብ መጠን በጊዜ ሂደት እየተሻሻለ እንደሚሄድም ተመላክቷል።

"ማንኛው የውጭ ዜጋ በማናቸውም ጊዜ፣ በአንድ ግዜ የሚኖረው የመኖሪያ ቤት ቁጥር አንድ ብቻ" መሆኑ የተቆመ ሲሆን ሚኒስቴሩ "ከአገር ጥቅም አንጻር አስፈላጊ ሁኖ ሲያገኘው ይህን ቁጥር በመመሪያ ማሻሻል ይችላል" ተብሏል።የመኖሪያ ቤት ባለቤት የሆነ የውጭ ሀገር ዜጋ “ለግለሰብ ወይም ለቤተሰብ የማከራየት መብቱ እንደተጠበቀ ሁኖ መኖሪያ ቤቱን ለንግድ አላማ ማዋል የተከለከለ መሆኑ” በአዋጁ ተቀምጧል።

ይህ የተገለጸው በምክር ቤቱ የከተማ፣ መሰረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በአዋጁ ዙሪያ ከምክር ቤቱ አባላት ለቀረቡለት ጥያቄ ምላሽ እና ማብራሪያ በሰጠበት ወቅት ነው።መሬት የመንግስት እና የህዝብ እንደመሆኑ ለኢንቨስትመንት የሚመጡ ዜጎች መሬቱን የመሸጥ እና የመለወጥ መብት የላቸውም ተብሏል።

የውጭ ሀገር ዜጎች በመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ላይ ኢንቨስት እንዲያደርጉ የቀረበው የገንዘብ መጠን ዝቅተኛ በመሆኑ ወደ ኢትዮጵያ በብዛት ሊገቡ ስለሚችሉ የሰው ቁጥሩ በሀገራችን እንዲጨምር ሊያደርግ ይችላል የሚል ጥያቄ ከአባላቱ ተነስቷል።

@YeneTube @FikerAssefa
የመንግስት ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” ማሳደግ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ ተናገሩ!

የፌደራል መንግስት የሚሰብሰበውን ገቢ በሚቀጥለው ዓመት “በከፍተኛ ደረጃ” ለማሳደግ ማቀዱ “የሞት የሽረት ጉዳይ ነው” ሲሉ የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሽዴ ተናገሩ። በኢትዮጵያ ያለውን የልማት ፍላጎት ከአሁን በኋላ ማሳካት የሚቻለው ገቢን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ፤ “አዲስ የልማት ጥያቄ ለመፍታት ብለን ከብሔራዊ ባንክ የምንበደርበት ሁኔታ አብቅቶለታል” ብለዋል። 

የገንዘብ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት ዛሬ ማክሰኞ ሰኔ 24፤ 2017 በተካሄደው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው። የዛሬው መደበኛ ስብሰባ ዋነኛ ትኩረቱን ያደረገው፤ የፌደራል መንግስት ለ2018 ባዘጋጀው በጀት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ነበር። 

የፌደራል መንግስት በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ለፓርላማ ያቀረበው የበጀት መጠን 1.93 ትሪሊዮን ብር ሲሆን ከሀገር ውስጥ ምንጮች ለመሰብሰብ ያቀደው የገንዘብ መጠን 1.23 ትሪሊዮን ብር ነው። በቀጣዩ በጀት ዓመት ከታክስ ይገኛል ተብሎ የሚጠበቀው 1.1 ትሪሊዮን ብር ገቢ፤ ለዘንድሮ በእቅድ ከተያዘው በ200 ቢሊዮን ብር ገደማ ጭማሪ አለው።

የ2018 በጀትን አስመልክቶ በዛሬው የፓርላማ ውይይት ላይ ማብራሪያ ያቀረቡት የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ፤ የፌደራል መንግስት የሀገር ውስጥ ገቢን “በከፍተኛ ደረጃ” የማሳደግ ዓላማ እንዳለው ገልጸዋል። መንግስት በአገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ የሚያገኘውን የገቢ መጠን በተመሳሳይ ሁኔታ ከፍ የማድረግ እቅድ እንዳለውም ጠቁመዋል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa
ክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በሚል፤ ህግ ወጥ ኬላዎችን እንደሚያቋቁሙ ሁለት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በጋራ ያስጠኑት ጥናት አመላከተ!

በኢትዮጵያ በክልል ፖሊሶች፣ የሚሊሻ መዋቅሮችና ለወጣቶች የስራ እድል በሚል 237 ህገወጥ ኬላዎች መቋቋማቸውን የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶቹ ጥናት አመላከተ።ንግድ እና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ከትራንስፖርት እና ሎጂስቲከስ ሚኒስቴር በጋራ በመሆን በሚያዚያ ወር 2017 ዓ.ም ባጠናቀቁት ጥናት መሰረት በሀገሪቱ 237 ህገ ወጥ ኬላዎች መኖራቸው መረጋገጡ ተገለጸ።

ክልሎች ለወጣቶች የስራ እድል ለመፍጠር በሚል፤ ህግ ወጥ ኬላዎችን እንደሚያቋቁሙ በጥናቱ መረጋገጡም የጉምሩክ ኮሚሽን ጠቁሟል።የጉምሩክ ኮሚሽን ይህን የተናገረው የ11 ወር የስራ ክንውን ሪፖርቱን ከገቢዎች ሚኒስቴር ጋር በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀት እና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት መሆኑ ተገልጿል።

ባለፉት 11 ወራት 19 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰቡን የተናገረው የጉምሩክ ኮሚሽን፤ በየክልሎች ገመድ እየተወጠረ ገቢ የሚሰበስብባቸው ህገ ወጥ ኬላዎች በሀገሪቱ ንግድ ሥርዓት ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደሩ እንደሆነ ተናግሯል፡፡ኬላዎችን ዘርግተው ግብር የሚሰበስቡት የክልለ ፖሊሶች፣ የሚሊሻ መዋቅሮች እንዳንድ ቦታ ደግሞ ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራ እና በወረዳ ግብረ ሃይል ተብሎም ጭምር የተቋቋሙ ኬላዎች እንዳሉ ምክትል ኮሚሽነሩ አቶ አዘዘው ጫኔ መናገራቸውን ከሸገር ሬድዮ ያገኘነው መረጃ ያሰያል።

@YeneTube @FikerAssefa
የህወሓት ክፍፍልን ተከትሎ ለሁለት የተከፈሉት የትግራይ ክልል ታጣቂዎች ወደ እርስ በርስ ግጭት ሊያመሩ ነዉ የሚል ከፍተኛ ስጋት መፈጠሩን በትግራይ በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሰው «ሳልሳይ ወያነ ትግራይ» አሳሰበ።

ሊፈጠር የሚችለዉን ቀውስ ለማስቀረትም በትግራይ ሁሉን አካታች ብሔራዊ ውይይት እንዲደረግ ፓርቲው ጥሪ አቅርቧል።የትግራይ ሐይሎች ወታደራዊ መኮንኖች ባለፈው ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም «ለአንዱ የህወሓት ክንፍ ያጋደለ» የተባለለትን የአቋም መግለጫ በማንፀባረቃቸው፣ በትግራይ ሐይሎች መካከል መከፋፈሎች መፈጠራቸው ይነሳል።

ይህ ደግሞ የትግራይ ሐይሎች ከፍተኛ አዛዦች ያሉበት ሌላ ታጣቂ ሐይል እንዲፈጠር ምክንያት መሆኑ ተነግሯል። በአፋር እና ትግራይ አዋሳኝ አካባቢዎች ለወራት የቆየው ይህ አዲስ ሐይል ወደ ትግራይ ክልል መንቀሳቀሱን መረጃዎች ያመለክታሉ።አዲሱ ታይል እዚያዉ ትግራይ ከሚገኘዉ ነባሩ ኃይል ጋር የእርስ በርስ ግጭት እንዳይገጥም የሚል ስጋት በበርካቶች ዘንድ ተፈጥሯል ሲል የዘገበው ዶይቼ ቬለ ነው፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ቴምርሪልስቴት
ከዚህ በፊት 7 ሳይቶችን ጥንቅቅ አርጎ ያስረከበዉ ቴምር ፕሮፐርቲስ አሁን
‼️ፒያሳ ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት ፊት ለፊት ያለውን ሳይት ለሽያጭ አውጥተናል

10% ቅድመ ክፍያ
ሰፊ የጋራ መገልገያ
ቢያከራዩት,ቢሸጡት ወይም ቢኖሩበት አዋጭ
ተመጣጣኝ ዋጋ

🏡  ሊሴ ገ/ማርያም አጠገብ
       👉1 መኝታ 63ካሬ=
     10% ቅድመ ክፍያ 693,000 ብር
        ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር

         👉2 መኝታ 86 ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 946,000 ብር
        ሙሉ ክፍያ 9,460,000 ብር

        👉3 መኝታ 114 ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,219,800 ብር
      ሙሉ ክፍያ 12,198,000 ብር
       
👉ቀሪውን 90% በ16ዙር ብር ያለምንም
ጭማሪ በብር ከፍለው የሚጨርሱት

👉Other locations include
📌 ሳር ቤት
📌  አያት
👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ

⚠️በተጨማሪም ሱቅ በ900ሺ ብር ቅድመ ክፍያ እዛው ፒያሳ ሚኒሊክ አደባባይእየሸጥን እንገኛለን::

ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251976195835

WhatsApp
Message Temer properties on WhatsApp. https://wa.me/251976195835

Telegram user
@Ruthtemersales

TEMER PROPERTIES
Create | Construct | Deliver
#TemerProperties #Temerrealestate
🎨 Graphic Design Course Registration Now Open!
Unlock your creativity and learn the skills to design stunning visuals for social media, branding, and more.
Beginner-friendly
Hands-on projects
Certificate included

📅 Limited seats – Register today!

Call us:
          ☎️
0989747878
0799331774

@merahyan
አቅመ ደካማወችን ሀረጋውያኖችን በነፃ

https://vm.tiktok.com/ZMSayMdXa
በተለያየ የጤና ችግር የሚሰቃዩትን እየ ፈወሰ
ደስታቸውን እየመለሰ የሚገኘውን የህክምና ተቋም https://vm.tiktok.com/ZMSay8eV2/
ሰወች እንዴት እንደተፈወሱ ሲመሰክሩ እንስማ እንይ ቻናሉን እንቀላቀል
https://vm.tiktok.com/ZMSaDEhoN

በስጋውይም ሆነ በመንፈስ ደውየ ከተቸገሩ መተው በመመርመር ይታከሙ ይፈወሱ
  44ት አይነት በሽታወችን እየፈወስን እንገኛለን
  አድራሻ አዲስ አበባ አየርጤና ወደካራ ናትራን ኩፓንያ ፊት ለፊት
ቁጥር ሁለት ባህርዳር ዲያስፖራ በአሮጌው አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት
☎️ 0917040506
☎️0912718883
ይደውሉ ይምጡ ይታከሙ ይፈወሱ ይመስክሩ
Ethiopian Building Code Standards
Private Sector Engagement in Code Revision: Final Week – Week 4 Sessions


We're closing out our 14-part expert-led workshop series with two crucial technical sessions in Week 4:

🧱 Concrete Design & Specifications
📏 Technical Specs & Measurement Methods


📅 Tuesday, June 24, 2025
📍 The Urban Center, Addis Ababa
🖥 Live on TUC Facebook page & Google Meet (link shared 30 min before each session)
☕️ Free sessions with refreshments

📲 Register now: https://forms.gle/NewtRdbnasiUFW6r7

🔗 Let’s finish strong, join the conversation, contribute your perspective, and help shape Ethiopia’s future building code.

Many thanks to all our incredible partners for making this journey possible!

#EBCS #CodeRevision #BuiltEnvironment #ECA #CoTBE #TUC #EngineeringEthiopia #ConstructionStandards #UrbanDevelopment #ProfessionalEngagement
እስራኤል ለ60 ቀናት በጋዛ የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማቷን ትራምፕ አስታወቁ!

የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ እስራኤል በጋዛ የ60 ቀናት የተኩስ አቁም ስምምነትን ለማድረግ "አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታዎችን" ለማሟላት ተስማምታለች ሲሉ ተናገሩ።

ፕሬዚደንቱ በትሩዝ የማኅበራዊ ሚዲያቸው ላይ እንደጻፉት ከሆነ በምክረ ሃሳቡ ስምምነት ወቅት "ጦርነቱን ለማቆም ከሁሉም አካላት ጋር እንሰራለን" ያሉ ሲሆን ቅድመ ሁኔታዎች ምን እንደሆኑ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

"ሰላም ለማምጣት በጣም ጠንክረው የሠሩት ኳታራውያን እና ግብፃውያን የመጨረሻውን ምክረ ሀሳብ ያቀርባሉ። . . . ሃማስ ይህንን ስምምነት ይቀበላል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። ምክንያቱም የተሻለ አይሆንም፤ እየባሰ ነው የሚሄደው" ሲሉ ትራምፕ ጽፈዋል።

መስከረም 26/2016 ዓ.ም. ሃማስ በእስራኤል ላይ ድንገተኛ ጥቀቃት ፈጽሞ 1,200 ሰዎችን ከገደለ በኋላ እስራኤል በጋዛ ወታደራዊ ዘመቻዋን ጀምራለች።

በግዛቱ በሐማስ የሚመራ የጤና ሚኒስቴር እንደገለጸው ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ቢያንስ 56,647 ፍልስጤማውያን ተገድለዋል።

@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮጵያ ወደ ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል መላክ ጀመረች!

ኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ወደ ታንዛኒያ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤሌክትሪክ ኃይል በሙከራ ደረጃ መላክ መጀመሯ ተገለጸ።የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለፁት፤ የሁለቱ ሀገራት የኤሌክትሪክ አቅርቦት ስምምነቱ ከተፈረመ የተወሰኑ ወራት ተቆጥረዋል።

በዚህም መሰረት አሁን ላይ በኢትዮጵያ በኩል 200 ሺህ ሜጋ ዋት ድረስ የመሸከም አቅም ያለው የማስተላለፊያ መስመር ተሰርቷል ብለዋል።አሁን በመስመሩ እየተላለፈ ያለው 200 ሜጋ ዋት መሆኑን በመጥቅስ፤ መስመሩ ተጨማሪ ግንባታ ሳይከናወን ተጨማሪ ኃይል ማስተላለፍ እንደሚችል ተናግረዋል።

ሙከራው በሂደት ላይ ያለ ነው ያሉት አቶ ሞገስ፤ በይፋ የኤሌክትሪክ ሽያጭ እንዳልተጀመረ ተናግረዋል።የኃይል ልማት ትስስሩ ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ልማት ለሌሎች ሀገራት ጭምር ሞዴል የሚሆን ሥራ እየሰራች መሆኑን የሚያመለክት መሆኑን አንስተዋል።

ሀገሪቱ ያላትን ሀብት ለራሷ ብቻ ሳይሆን በዙሪያው ከሚገኙ ጎረቤቶቿ ጋር የጋራ ተጠቃሚነትን አረጋግጣ በጋራ የማልማት ፍላጎት ያላት ሀገር መሆኗን የሚያሳይ ነውም ብለዋል።

የኬንያ ኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ ኩባንያ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ዶክተር ኢንጂነር ጆን ማቲቮ ኤምቢኤስ በማህበራዊ ሚዲያ ገፃቸው እንዳስታወቁት፤ በሙከራው የኤሌክትሪክ ኃይል ከኢትዮጵያ በኬንያ በኩል ኤሌክትሪክ የማስተላለፊያ መስመር በተሳካ ሁኔታ ኤሌክትሪክ ማስተላለፍ መቻሉን ተናግረዋል።

Via Gazeta+
@YeneTube @FikerAssefa
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ነገ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ!

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚያነሱላቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ የሚሰጡ ይሆናል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa
“ፌደሬሽኑ የፍትህ አካላት ዉሳኔን ሰጠ እንጂ የፍትህ ዉሳኔ አልተሰጠም" አቶ ኢሳያስ ጅራ

#Ethiopia | የኢትዮጲያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ትናንት ስራ አስፈፃሚዉ በወሰናቸዉ ዉሳኔዎች ዙሪያ ዛሬ በፌዴሬሽኑ ፕሬዝዳንት አቶ ኢሳያስ ጂራ እና በስራ አሰፈፃሚዉ ባህሩ በኩል መግለጫ ሰጥቷል።

ፌዴሬሽኑ የወሰነዉ ዉሳኔ የፍትህ አካላት ዉሳኔ እንጂ የፍትህ ዉሳኔ አላሰረፍም ሲሉ የፌዴሬሽኑ ፕሬዝደንት አቶ ኢሳያስ ጂራ ተናግረዋል።

የፋይናንስ ስርዓት ተቆጣጣሪ ኮሚቴዉ በአራት ክለቦች ላይ ዉሳኔ አሳረፈ እንጂ በ14 ክለቦች ላይ አጣርቶ ባልጨረሰበት ሁኔታ ይህን ክለቦቹ እንዲወርዱ ማድረግ እግርኳሱን ምስቅልቅሉን ያወጣዋል ሲሉ ገልፀዋል ፕሬዝዳንቱ።

Via:- Bisrat Fm
@Yenetube @Fikerassefa
አብዲራህማን መሃዲ የሚመራው ኦብነግ “በጅግጅጋ ተካሄደ የተባለውን የፓርቲውን ጉባኤ” በማውገዝ “ከጀርባ የፖለቲካ አጀንዳ ያለው ነው” ሲል ተቸ!

በአብዲራህማን መሃዲ የሚመራው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ባሳለፍነው ሳምንት ሌላኛው የፓርቲው አንጃ በጅግጅጋ ያካሄደውን ጉባኤ “ህገወጥ፣ በፖለቲካ የተቀነባበረ እና ሀሰተኛ ጉባኤ ነው” ሲል ተቃወመ።

በአብዲራህማን መሃዲ የሚመራው የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ይህን ያለው፤ ባሳለፍነው ሳምንት መገባደጃ ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የኦብነግ አንደኛው ቡድን የፓርቲውን 5ኛ መደበኛ ጉባኤ በማካሄድ አብዲራህማን ማህዲንን ከሊቀመንበርነት ማንሳቱን ማስታወቁን ተከትሎ ነው።

በጅግጅጋ የተካሄደው ጉባኤ “በብልጽግና ፓርቲ አስተባባሪነት፣ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና በሶማሌ ክልል አስተዳደር ድጋፍ የተደረገ ነው” ያለው አብዲራህማን መሃዲ የሚመራው ኦብነግ መግለጫው፤ “ፓርቲውን ለማፍረስ፣ የኦጋዴንን የተፈጥሮ ሀብት ለመበዝበዝ እና የሶማሌ ሕዝብ በህገመንግስቱ የተሰጠውን ራሱን የማስተዳደር መብት ለመሸርሸር” የሚደረገው ሰፊ ጥረት አካል ነው ሲል ከሷል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssef
የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ 400 ሺሕ ዶላር ድጋፍ አደረገ!

የአፍሪካ ልማት ባንክ የኢትዮጵያን የካፒታል ገበያ ለማጠናከር የ400 ሺሕ ዶላር ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል።ይህ ድጋፍ በኢትዮጵያ የካፒታል ገበያ ባለስልጣን የመሠረተ ልማት ግንባታዎችን ለማስፋፋት፣ የዋስትና ልውውጦችን እና የምርት አቅርቦቶችን ለማብዛት እንዲሁም አቅምን ለማጠናከር ይውላል።

ገንዘቡ የሚገኘው በአፍሪካ ልማት ባንክ ከሚተዳደረው የካፒታል ገበያ ልማት ትረስት ፈንድ ሲሆን፣ የተለያዩ ለጋሾች ድጋፍ ያደርጉለታል። የገንዘብ ድጋፉ ባለስልጣኑ ለባለሀብቶች፣ ለአክሲዮን ባለቤቶች እና ለሌሎች የገበያ ተዋናዮች ወቅታዊና ትክክለኛ መረጃ ለማሰራጨት የሚያስችል የሕዝብ ይፋዊ መድረክ እንዲቋቋም ይረዳል ተብሏል።

በተጨማሪም፣ የምንዛሪ ፈንዶችን፣ “ሱኩክ” የተሰኘውን ከወለድ ነጻ የቦንድ ሽያጭ አገልግሎት እና አረንጓዴ ቦንዶችን ጨምሮ አዳዲስ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ይጠቅማል።ይህ ፕሮጀክት የአፍሪካ ልማት ባንክ በኢትዮጵያ እያደረገው ያለው የመጀመሪያው የካፒታል ገበያ ልማት ድጋፍ ሲሆን፣ ኢትዮጵያም በዚህ የካፒታል ገበያ ልማት ትረስት ፈንድ ተጠቃሚ የሆነች የመጀመሪያዋ የምስራቅ አፍሪካ ሀገር ሆናለች።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
📌ግልፅ የሆነ የህግና በቂ ማብራሪያ የመስጠት ክፍተት የታየበት፤ጋዜጠኞችን ያላጠገበው በ"ጨርሻለሁ"የተዘጋው ጋዜጣዊ መግለጫ

#Ethiopia | የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ውሳኔ ያስተላለፈባቸውን ተጠባቂ ጉዳዮች ዙሪያ ለመገናኛ ብዙሃን አካላት ሲሠጥ የነበረው ጋዜጣዊ መግለጫ ከደቂቃዎች በፊት ክቡር ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ መጨረሻ ላይ "ጨርሻለሁ" ባሉት መሠረት ተጠናቋል።

ጋዜጠኛውን ያላጠገበ፣ለስፖርት ቤተሠቡ በተለይ ውሳኔው ላረፈባቸው አካላት አጥጋቢ ምላሽ የሠጠ የማይመስለው መግለጫ ከጋዜጠኞች ለቀረበው ጥያቄ ፕሬዝዳንቱ ያልተብራራና የህግ ክፍተት በግልፅ የተስተዋለበት አሁንም ጉዳዩ በቀጣይም ማወዛገቡንና የተዳፈነ እሳት ሆኖ እንደሚቀጥል በጠቆመ፣ ሁሉንም ባላረካ በተለይ የወላይታ ዲቻና የሲዳማ ቡናን የኢትዮጵያ ዋንጫን በተመለከተ ግልፅ ያለ የህግ ማብራሪያ ባልተሠማበት መልኩ ተጠባቂው መግለጫ ተጠናቋል።

ክቡር ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ጅራ በመግለጫው ከሠጧቸው ምላሾች የተመረጡትን ከዚህ በታች አስቀምጠናል።

📌"ፊፋ መሄድ መብታቸው ነው፤ ይሄንን ህግ ጥሠው ነው ወደ 20 ያሳደጉት ካለ መልስ እንሠጣለን"

📌"ወደ 20 ክለብ ለምን አደገ ከተባለ ወደ ፊፋ መሄድ ይቻላል፤ፊፋ ምክረ ሃሳብ ይሠጣል እንጂ ይሄን ቁጥር አድርጉ የሚል አስገዳጅ ህግ የለውም"

📌"በፕሪሚየር ሊጉ መሳተፍ አልፈልግም ያለ ክለብ ካለ ደግሜ ነው የምነግርህ መውጣት ይችላል"

📌""መብቴን አስከብራለሁ የኢትዮጵያ እግር ኳስ በድሎኛል ካለ ወደ Governing Body ወደ መንግስት አካል መውሠድ ይችላል"

📌"ብሄራዊ ፌዴሬሽኑ በአንድ ግለሠብ ላይ የደሞዝ ጣሪያ መጣል አይችልም፤ የደሞዝ ጣሪያ መከታተል ይችላል"

📌"ገንዘብ ካልመለሱ ህጉ ተግባራዊ ይሆናል፤ የወጣ ህግ ተግባራዊ ይሆናል"

✍️በጋዜጠኛ ይስሀቅ በላይ
በመዲናዋ 95 በመቶ የሚሆኑ የ6ኛ ክፍል ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ማስመዝገባቸው ተገለጸ!

በ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል ከተፈተኑ 79 ሺሕ 34 ተማሪዎች መካከል 75 ሺሕ 85 ተማሪዎች ከ50 በመቶ በላይ ውጤት በማስመዝገብ ወደ ቀጣዩ ክፍል መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።የትምህርት ቢሮው የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላት በዛሬው ዕለት ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ በከተማ አስተዳደሩ ሥር ፈተናውን ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 95 በመቶ የሚሆኑት የማለፊያ ነጥብ በማምጣት ወደ ቀጣይ ክፍል ማለፋቸውን ገልጸዋል።

አያይዘዉ የአካል ጉዳተኞች ተማሪዎች የማለፊያ ነጥብ ከ45 በመቶ በላይ መሆኑን ተናግረዋል።ቢሮው ላለፉት ተከታታይ ሦስት ዓመታት የ6ኛ ክፍል ፈተና በመንግሥትና በግል ትምህርት ቤቶች በቀን እና በማታ የትምህርት መርሃግብር መስጠቱን ገልጸው፤ "የተያዘው ዓመት አፈጻጸም ከቀደሙት አንጻር ሲታይ ጥሩ የሚባል ነው" ብለዋል።

የትምህርት አሰጣጥ ስርአቱ ቴክኖሎጂን ጨማሮ ሬድዮ እና በቴሌቪዥንን በመጠቀም ሲሰጥ መቆየቱ ተማሪዎች ውጤታማነት እንዳገዘ ተገልጿል።የትምህርት ቢሮው የቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም አክለውም፤ ዘንድሮው በከተማ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ1 እስከ 4 የሚሆኑት ከመንግሥት ትምህርት ቤቶች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ተፈታኝ ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት እንደሚችሉም በጋዜጣዊ መግለጫው ተጠቁሟል።

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa
የቻይና ሰላዮች በአሜሪካ

በአሜሪካ ውስጥ ለቻይና ሲሰልሉ የነበሩ 2 የቻይና ዜግነት ያላቸውን ሠዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።

የአሜሪካን የባህር ሃይል ጣቢያን ፎቶግራፍ በማንሳት፣ አመጽ በገንዘብ በመደገፍና በማስተባበር እንዲሁም የተለያዩ የስለላ ስራዎችን በመስራት በሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል።

የሳን ፍራንሲስኮ የፌደራል ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ እንደገለጹት ፣ የቻይና መንግስት ስለ አሜሪካ ወታደራዊ አቅም በድብቅ መረጃ ለመሰብሰብ የቻይና መንግስት የማያቋርጥ ጥረቶች ማሣያ ነው በማለት አብራርተዋል።

አክለውም "ይህ ጉዳይ የቻይና መንግስት ወታደሮቻችንን ሰርጎ ለመግባት እና ብሄራዊ ደህንነታችንን ከውስጥ ለማዳከም የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ጥረት አጉልቶ ያሳያል" ሲሉ ተናግረዋል።

"የውጭ ተላላኪዎችን እናጋልጣለን ፣ወኪሎቻቸውን እናያለን እና የአሜሪካን ህዝብ በብሄራዊ ደህንነታችን ላይ ከሚደርሱ ስውር አደጋዎች እንጠብቃለንም" ብለዋል።

እ.ኤ.አ በ2015 ወደ አሜሪካ የገቡት ሠላዮቹ ዩያንስ ቼን እና ሊረን ራያን በመባል ይጠራሉ። የቻይና መንግስት ደህንነት ሚኒስቴርን ወክለው ሚስጥራዊ የስለላ ስራዎችን ለመከታተል የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑም ገልጸዋል።

በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ቃል አቀባይ ሊዩ ፔንግዩ ስለ ጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸው ገልፀው፣ ነገር ግን በቻይና ላይ የተከሰሱ ውንጀላዎች ምንም ዓይነት ማስረጃ የላቸውም እንዲሁም አሜሪካ በቻይና ላይ የምታደርገውን የስለላ ተግባር አላቆመችም ማለታቸውን ኤፒ ዘግቧል።

@Yenetube @Fikerassefa
2025/07/03 01:07:26
Back to Top
HTML Embed Code: