Telegram Web Link
ሱሉልታ መውጫ ፍተሻ ጋር በደረሰ የትራፊክ አደጋ የሰው ህይወት አለፈ

አደጋው የደረሰው ከባድ ተሽከርካሪ በሌላ ተሽከርካሪ ላይ ወድቆ መሆኑን ብስራት ሬዲዮ ሰምቷል።

የተጎጅዎችን አስከሬን ለማውጣት የአደጋ ግዜ ሰሬተኞች ርብርብ እያደረጉ መሆኑን ለማወቅ ችለናል።

ዝርዝር መረጃ እንደደረሰን የምናቀርብ ይሆናል።


በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል
ሚኪያስ ጎማ ፣ ባትሪና ከመነዳሪ አከፋፋይ 

#ለቪትስ
#ለያሪስ
#ለዲዛየርና ስዊፍት
#ለኮሮላ
#3L & 5L እንዲሁም ለከባድ ተሽከርካሪዎች የሚሆኑ ጎማዎች እና ባትሪዎችን ይዘዙን ካሉበት እናደርሳለን

👉የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገራት ጎማዎች (ትሪያንግል ፣ ስፖርትራክ ፣ ኮምፈርሰር ፣ አፖሎ ፣ ብሪጅስቶን እና ሌሎችም)

👉 የተገለገሉበት ጎማ ን ዋጋ ተምነን በአዲስ እንቀይርሎታለን

👉 በስልክ ቁጥር 📞...+251-913-701702 / +251-975293297 ይደውሉልን አልያም ተክለሀይማኖት ከሚገኘው ሱቃችን ይምጡ በደስታ እናስተናግድዎታለን
እስራኤል በፈፀመችው ጥቃት ከኢራናዊው የኒውክሌር ሳይንቲስት ጋር 11 የቤተሰብ አባላት ተገደሉ

የኢራን የእንግሊዘኛ ቋንቋ ስርጭር ጣቢያ ፕሬስ ቲቪ እንደዘገበው የኢራን-እስራኤል የተኩስ አቁም ስምምነት ሰኞ መገባደጃ ላይ ከመጀመሩ ጥቂት ቀደም ብሎ ኢራናዊው የኒውክሌር ሳይንቲስት ሴዲጊ ሳበር ከ11 የቤተሰቡ አባላት ጋር በእስራኤል የግድያ ጥቃት ተገድለዋል። እንደ ፕረስ ቲቪ ዘገባ ከሆነ ጥቃቱ የተፈፀመው በሰሜን ኢራን አስታነህ አሽራፊህ በካስፒያን ባህር አቅራቢያ በምትገኝ ከተማ ነው።

በፕሬስ ቲቪ ይፋ የተደረገው ዘገባ እንደሚያሳየው በሳይንቲስቱ የቤተሰብ ፎቶ ላይ የተገደሉት የቤተሰብ አባላት፣ አዛውንቶችን፣ በርካታ ህፃናትን እና ሴቶች እንደሚገኙበት ያሳያል። እንደ ዘገባው ከሆነ እስራኤል በሀገሪቱ ለ12 ቀናት ባደረገችው ጥቃት ቢያንስ 14 የኢራን የኒውክሌር ሳይንቲስቶችን ኢላማ አድርጋለች። በሌላ በኩል የኢራን የስለላ ሚኒስቴር የተኩስ አቁም ስምምነት ቢደረግም በሀገሪቱ ውስጥ የእስራኤል “ክፉ” እንቅስቃሴዎች ሊቀጥሉ እንደሚችል ማስጠንቀቁን የኢራን የዜና ወኪል ፋርስ ዘግቧል።

ፋርስ ሚኒስቴሩን ጠቅሶ እንደዘገበው የእስራኤል ኦፕሬተሮች “የቴሌፎን ስለላ እና ብሄራዊ መረጃ ለማግኘት” በሚል አላማ ለኢራናውያን “የጅምላ የስልክ ጥሪ” ዘመቻ ጀርባ እንደነበሩ ገልጿል። ሚኒስቴሩ በተጨማሪም ኢራናውያን "በብሄራዊ አንድነት አንድነት ላይ እርምጃ እንዲወስዱ ለማነሳሳት "የሐሰት ዜና" መስፋፋትን አስጠንቅቋል። ከእስራኤል ጋር የተኩስ አቁም ስምምነቱ በቀጠለበት ወቅት የኢራን ባለስልጣናት የጸጥታ ጥቃቶችን እያጠናከሩ እና ለእስራኤል ይሰልላሉ ነበሩ ያላቸውን በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል በሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ላይ ስጋት ፈጥሯል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
ከጁቡቲ እስከ ጋላፊ እና ደወሌ ተሽከርካሪዎች ጉዳት ደርሶባቸዉ ለማስነሳት ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ እንጠየቃለን ሲሉ የፈሳሽ ጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶች ተናገሩ

የጁቡቲ መንገድ ለተሽከርካሪዎችና አሽከርካሪዎች ምቹ አለመሆኑ የተገለፀ ሲሆን በመንገድ ትራንስፖርት ፣በጁቡቲ ባለስልጣናት ፣በኤምባሲ እና በሌሎችም አካላት አከባቢዉን ምቹ ለማድረግ ይሠራል ቢባልም ከ1991 ጀምሮ ምንም የተስተካከለ ነገር አለመኖሩ ተነግሯል ።

በጁቡቲ ማቆሚያ ተርሚናሎች አከባቢ ለአደጋ ለሚጋለጡ አሽከርካሪዎች የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና መስጫ ተቋማት አለመኖራቸው ሌላኛው ችግር ነዉ ተብሏል ።ከብስራት ሬዲዮ ጋር ቆይታ ያደረጉ የፈሳሽ ጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶች እንደተናገሩት ከሆነ አንድ መኪና ጁቡቲ ላይ ብልሽት ሲደርስበት ተሳቢዉንና መኪናዉን ለማስነሳት ወደ 1.2ሚሊዮን ብር የሚጠየቅ ሲሆን ከቦታው ቀና ለማድረግ 500ሺህ ብር ፣የማፃፊያ ፣የጀንደር በሪ ፣የጉምሩክ አበል እና የፖምፕ ኪራይ ተደማምሮ ከ2.5 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚጠየቁ ተናግረዋል ።

ይህም መኪናዉ ያለማቋረጥ በወር አራት ጊዜ ቢሰራ በሁለት ዓመት የማይሰራው ብር መሆኑን የገለፁት ባለንብረቶቹ የምንጠየቁ ገንዘብ መኪናዉን ከመጣል አይተናነስም ብለዋል ። ከዛ ባለፈም ተሽከርካሪዉ የሚነሳበት መንገድ የመኪናዉን ደህንነት በጠበቀ መልኩ ሳይሆን ሀይልና ጉልበትን በመጠቀም የተሽከርካሪውን አካላት  በማዉደምና በይበልጥ በማበላሸት መሆኑ ተጠቁሟል ።

አንድ ተሽከርካሪ በጁቡቲ ጋላፊ ኬላ ከመጣ 200 ኪሎ ሜትር ፣በደወሌ ከመጣ 130 ኪሎ ሜትር ሲሆን ጎትተዉ አምጥተው የሚጠይቁት ክፍያ ከ600 እስከ 700ሺህ ብር ነዉ ብለዋል ። እስከ አዲስ አበባ ለማምጣት ሌላ ተጨማሪ ወጪ እንደሚወጣ ተገልጿል ።

በተጨማሪም ከአዳማ እስከ መተሀራ ባለዉ ተሽርካሪ ላይ ጉዳት ደርሶ እዛዉ ሲቆም በአከባቢዉ ያሉ ሚሊሻ ታጣቂዎች በቀን እስከ 20ሺህ ብር የሚጠይቁ በመሆኑ ይህም ከአቅም በላይ ስለሆነብን የሚመለከተዉ የመንግስት አካል አስፈላጊውን ቁጥጥር እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል ። ከየትኛውም የመኪና ጥበቃ ክፍያ አከባቢዎች ከመተሀራ እስከ አዳማ ያለዉ ከባድ ክፍያ የሚጠየቅበት መሆኑን ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የፈሳሽ ጭነት ተሽከርካሪ ባለንብረቶች ተናግረዋል ።

በመባ ወርቅነህ
#ዳጉ_ጆርናል
አያቶላህ አሊ ካሜኔይ ኢራን በእስራኤል ላይ 'ድል' እንዳገኘች ተናገሩ

የኢራን ጠቅላይ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኒ አሜሪካ በኢራን እና በእስራኤል መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት መደረሱን ካወጀች በኋላ የመጀመሪያ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

ካሜኔይ ንግግር፣ በኤክስ ላይ በለጠፉት መልዕክት የኢራን ህዝብ በእስራኤል ላይ ላገኘዉ “ድል” እንኳን ደስ አለህ ለማለት እወዳለሁ በአስፈሪው የጽዮናዊ አገዛዝ ላይ ስላገኘነዉ ድል እንኳን ደስ አላችሁ ሲሉ ጽፈዋል።አያቶላህ ኸሚኒ ሌላ በቴሌግራም አካውንታቸው በፋርሲ ቋንቋ ባስተላለፉት መልዕክት በኢራን ብሄራዊ አንድነት አሞካሽተዉ በወደ 90 ሚሊዮን የሚጠጋ ህዝብ በአንድ ድምፅ፣ ትከሻ ለትከሻ፣ የታጠቁ ሀይሎችን በመደገፍ በአንድነት ቆሟል ሲሉ ተደምጠዋል።

የአሜሪካን የጦር ሰፈሮች መምታት በጣም ጥሩ ነገር ነው እናም ወደፊት ሊደገም ይችላል ሲሉ ካሜኒ አክለዋል፡፡የኢራን ህዝብ ልዩ ባህሪውን አሳይቷል እናም አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ አንድ ድምጽ ከዚህ ህዝብ እንደሚሰማ አሳይቷል ብለዋል፡፡ወደፊት በኢራን ላይ የሚደረግ ማንኛውም ጥቃት ትልቅ ዋጋ ያስከፍላል።ኢራን ዋና ዋና የአሜሪካን ጦር ሰፈሮችን ማግኘት እና መድረስ መቻሏ ትልቅ ነገር ነው ወደፊትም እንደገና ጥቃት ቢሰነዘርበት ሊደገም ይችላል ሲሉ ተደምጠዋል።የኢራን ጠላቶች እኛን ለማጥቃት እንደ ሚሳኤሎች ወይም የኒውክሌር መርሃ ግብሮች ሰበብ ይጠቀማሉ፣ ነገር ግን  እጅ እንድንሰጥ እየፈለጉ ነው ሲሉ ተደምጠዋል።

ሀገራቸው ከእስራኤል ጋር በነበረችበት ጦርነት በኢራን ውስጥ ወደ ሁለት ሳምንታት የሚጠጋ ሚስጥራዊ ስፍራ ከቆዩ በኋላ የ86 አመቱ የበላይ መሪ የሆኑት አያቶላ አሊ ካሜኒ በእስራኤል እንዳይገደሉ በመፍራት ወደ ጥብቅ ጉድጓድ ውስጥ እንደገቡ ይታመናል። ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ምንም አይነት ግንኙነት እንዳልነበራቸው ተመላክቷል፡፡በጦርነቱ ወቅት እስራኤል የኢራንን የአየር ክልል በፍጥነት የተቆጣጠረች ሲሆን ወታደራዊ መሠረተ ልማቷን አጥቅታለች። የአብዮታዊ ጥበቃ እና የሰራዊቱ ከፍተኛ አዛዦች በፍጥነት ተገድለዋል፡፡

በጦር ኃይሉ ላይ የደረሰው የጉዳት መጠን አሁንም ግልጽ ያልሆነ እና አከራካሪ ቢሆንም በሠራዊቱ እና በአብዮታዊ የጥበቃ ማዕከሎች እና ተቋማት ላይ የሚደርሰው ተደጋጋሚ የቦምብ ጥቃት የኢራንን ወታደራዊ ኃይል በከፍተኛ ደረጃ ማሽቆልቆሉን ያሳያል። ወታደራዊ ሃይል ከፍተኛ መጠን ያለው የሀገር ሀብት ፈሰስ ሲደረግበት ቆይቷል።በ1989 ለመጀመሪያ ጊዜ መሪ የሆኑት አያቶላህ ካሜኔይ ኢራንን ከእስራኤል እና ከአሜሪካ ጋር በፈጠረችዉ ዉዝግብ ተጠቃሽ ሰዉ ተደርገዉ ይወሰዳሉ፡፡

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በደን ወረራ የተከሰሱ 12 ግለሰቦች በፅኑ እስራት እና በገንዘብ ተቀጡ

በኮሬ ዞን ከ100 ዓመታት በላይ ተጠብቆ በቆየዉ የተፈጥሮ ደን ላይ ወረራ ያደረጉ 12 ግለሰቦች መቀጣታቸውን የደቡብ ኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽን ህዝብ ግንኙነት እና ገጽታ ግንባታ ዳይሬክተር ምክትል ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።ግለሰቦቹ  በህገ ወጥ መንገድ  የደን ጭፍጨፋ፣ የመሬት ወረራ፣ መሸጥ እና በሌላቸው ሥልጣን መሬትን ለሌሎች ህገ- ወጦች በመምራት የወንጀል ድርጊት ነው ሊቀጡ የቻሉት።

ተከሳሾቹ  የኢፈዲሪ መንግስት ስለ ደን እና አከባቢ ጥበቃ ያወጣውን አዋጅ ቁጥር 1065/2010 አንቀጽ 26(4) እና መሬት ስለመሸጥ እና መለወጥን ለመከልከል የወጣውን የዚሁ አዋጅ ድንጋጌ ተላልፈው ወንጀል የፈጸሙ መሆናቸውን የክስ መዝገባቸው  ያስረዳል።የምርመራ መዝገቡ የደረሰዉ የጎርካ ወረዳ ፍርድ ቤት የተከሳሾችን የእምነት ቃልና የምስክሮችን ቃል በመስማት ጥፋተኛ መሆናቸውን በማረጋገጥ ብይን ሰጥቷል።

በዚህም መሠረት በ1ኛና 2ኛ ተከሳሾች ላይ የ5 ዓመት እስራት እና 20 ሺህ ብር፣ በ3ኛ ተከሳሽ  አራት ዓመት ጽኑ እስራትና 20 ሺህ ብር፣ አራተኛ ተከሳሽ 3 ዓመት ጽኑ እስራት እና 20 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ዉሳኔ ተላልፎባቸዋል።ሌሎች ተከሳሾችን በተመለከተ በእያንዳንዳቸው ላይ 2 ዓመት ከ6 ወር እና 15 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ በማለት ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ማስተላለፉን ኮማንደር አሸናፊ ኃይሌ ለብስራት ሬዲዮ ተናግረዋል።

በሳምራዊት ስዩም
#ዳጉ_ጆርናል
ሰሜን ኮርያ ቱሪዝምን ለማነቃቃት የባህር ዳርቻዎችን ክፍት አደረገች

የሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ ኡን በሚስጥራዊቷ የኮሚኒስት አገዛዛቸዉ ቱሪዝምን ያሳድጋል ብለው ያሰቡትን የባህር ዳርቻ ሪዞርት እየከፈቱ መሆናቸዉን የመንግስት ሚዲያዎች ዘግበዋል።በምስራቅ የባህር ዳርቻ የሚገኘው ዎንሳን ካልማ ሊጠናቀቅ ከታቀደበት ከስድስት ዓመታት በኋላ ቆይቶ ጁላይ 1 ላይ ለአገር ውስጥ ቱሪስቶች ክፍት ይሆናል። የውጭ ዜጎችን መቼ እንደሚቀበል ግን ግልጽ አይደለም::

ኪም በቅንጦት ያደጉት ዎንሳን ውስጥ ነው፣ በርካታ የሀገሪቱ ልሂቃን የግል ቪላዎች ያሏቸው ሲሆን በአንድ ወቅት የሚሳኤል መሞከሪያ ቦታ የነበረችዉን ከተማዋን ለመለወጥ እየሞከሩ ይገኛል።የመንግስት መገናኛ ብዙሃን የሆነዉ ኬሲኤንኤ እንደዘገበዉ ሪዞርቱ እስከ 20,000 ጎብኝዎችን ማስተናገድ የሚችል ሲሆን 4 ኪሎ ሜትር የባህር ዳርቻ፣ ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የገበያ ማዕከሎች እና የውሃ ፓርክ አላቸዉ ብሏል፡፡

ለአስርት አመታት በኒውክሌር ጦር መሳሪያ መርሃ ግብሯ ምክንያት ከፍተኛ ማዕቀብ የተጣለባት ሰሜን ኮሪያ ከአለም ድሃ ሀገራት ተርታ ትጠቀሳለች። ከ1948 ዓ.ም ጀምሮ አገሪቱን ሲመራ የነበረውን የኪም ቤተሰብ ነዉ፡፡ አብዛኛው ሀብቷን ወደ ወታደራዊ፣ የኪም  ቤተሰብ ሐውልቶች እና ምልክቶች ላይ በፒዮንግያንግ - ፈሰስ ሲደረግ ቆይቷል። አንዳንድ ታዛቢዎች ይህ ለፒዮንግያንግ ገንዘብ የምታገኝበት ቀላል መንገድ ነው ይላሉ። የውጪ ቱሪስቶች ወደ ውስጥ እንዲገቡ ቢፈቀድም፣ የቱሪስት ቡድኖች በአብዛኛው የሚመጡት ከቻይና እና ሩሲያ ነው፣ ፒዮንግያንግ ከረጅም ጊዜ በፊት ወዳጅነት ከሁለቱ ሀገራት ጋር አላት።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
በሱሉልታ ፍተሻ ጣቢያ አካባቢ በደረሰው የትራፊክ አደጋአራት ሰዎች ህይወት አለፈ

ዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም ከረፋዱ 4:50 ገደማ በጉለሌ ክፍለ-ከተማ ወረዳ 7
ሱሉልታ ፍተሻ ጣቢያ ከመድረሱ በፊት ባለዉ ቁልቁለት መንገድ ላይ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን የእሳትና አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል።

አደጋው የደረሰው ከባድ ጭነት ጭኖ ይጓዝ የነበረ ከባድ ተሽከርካሪ የጫነዉ ጭነት ተሳፋሪ ጭኖ ወደ ሱሉልታ ይጓዝ በነበረዉ ሚኒባስ ተሽከርካሪ ላይ በመወደቁ መሆኑን የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ ንጋቱ ማሞ ለብስራት ሬድዮ ተናግረዋል። በአደጋዉ በሚኒባስ ታክሲ ዉስጥ የነበሩ አራት ተሳፋሪዎች ህይወታቸዉ አልፏል።

የኮሚሽኑ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞች ህይወታቸዉ ያለፈዉን ሰዎች ከአራት ሰዓታት ጥረት በኋላ  አስከሬናቸውን ከተጫናቸዉ ጭነትና ከተሽከርካሪ ዉስጥ አዉጥተዉ ለፖሊስ አስረክበዋል።

የሟቾችን አስከሬን ለማዉጣት የኮሚሽኑ እና የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ክሬኖች ጥቅም ላይ የዋሉ ሲሆን በሂደቱም የአዲስ አበባ ፖሊስና ሌሎች የጸጥታ አመራርና አባላት ድጋፍ አድርገዋል።

በትግስት ላቀው
#ዳጉ_ጆርናል
2025/06/30 18:20:08
Back to Top
HTML Embed Code: