Telegram Web Link
እንኳን አደረሰነ!

☞ሠረቀ ወርኀ ሐምሌ ቡሩክ፤ በሰላመ እግዚአብሔር፤ አሜን።
ወአመ ፩፦

ተዝካረ በዓለ ልደታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል (ወለተ ኢያቄም ወሐና)
ቅድስት ጾመ ሐዋርያት (ንጹሐን)

ወበዓለ ቅዱሳን፦

✿ቅፍሮንያ ድንግል ወሰማዕት (ዘብሔረ ንጽቢን)
✿ኦርያና መነኮሳይት፥ ወእመ ምኔት (እኅታ)
✿ብዮክ ወብንያሚን መስተጋድላን (ጻድቃን ካህናት)
✿አግናጥዮስ ክቡር ሊቀ ጳጳሳት (ወሰማዕት)
✿ቶማስ ሐዋርያ፥ ገባሬ መንክራት (ዘሕንደኬ)
✿ገብረ መድኅን መነኮስ ጻድቅ (ኢትዮጵያዊ)
✿ክልዮስ ሊቀ ጳጳሳት (ዘሮሜ)
✿ወበርተሎሜዎስ ክቡር

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞

✞✞✞ እንኩዋን ለሐዋርያው #ቅዱስ_ታዴዎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞

+"+ #ቅዱስ_ታዴዎስ_ሐዋርያ +"+

=>#ቅዱሳን_ሐዋርያት አባቶቻችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በተከተሉበት ሰዓት እድሜአቸው በ3 ደረጃ የተከፈለ እንደ ነበር የቤተ ክርስቲያን ትውፊት ያሳያል::

¤እንደ #ዮሐንስ_ወንጌላዊ ያሉት በ20ዎቹ ውስጥ:
¤#ቅዱስ_ታዴዎስን የመሰሉት ደግሞ በ30ና በ40ዎቹ ውስጥ የነበሩ ሲሆን
¤እነ #ቅዱስ_ዼጥሮስ ደግሞ በ50ዎቹ ውስጥ የሚገኙ ነበሩ:: ደቀ መዛሙርቱ ከወጣቶችም: ከጐልማሶችም ከአረጋውያንም የተዋቀሩ ነበሩ ማለት ነው::

+ቅዱስ ታዴዎስ በቀደመ ስሙ #ልብድዮስ ይባል የነበረ ሲሆን በአንዳንድ መጻሕፍት ውስጥ (በተለይ በምሥራቅ ኦርቶዶክሶች) #ስምዖን እና #ይሁዳ እየተባለም ተጠርቷል::

+ቅዱሱ ጌታችን ተከትሎ:
¤ከ12ቱ አንዱ ሆኖ በፈጣሪው ተመርጦ:
¤3 ዓመት ከ3 ወር ከጌታ እግር ተምሮ:
¤በዕርገቱ ተባርኮ:
¤በበዓለ ሃምሳም 71 ልሳናትን ተቀብሎ:
¤#ሐዋርያት ዕጣ ሲጣጣሉ የበኩሉን አሕጉረ ስብከት ተካፍሎ ዓለምን ዙሯል::

+ቅዱስ ታዴዎስ አንድ ቀን ከሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ጋር ወደ አንዲት ሃገር ይገባሉ:: ታዲያ ለቀናት ያለ ምግብ ወንጌልን ሲሰብኩ ቆይተው ነበርና ደጐቹ ሐዋርያት ራባቸው:: ወደ ከተማዋ ሳይገቡ አንድ ሽማግሌ ሲያርስ አይተው ሰላምታን ሰጡትና "እባክህ እርቦናልና አብላን" አሉት:: እርሱም ምንም ወገኑ ከአሕዛብ ቢሆነ አሳዝነውት በሬዎቹን ሳይፈታ እየሮጠ ሄደ::

+ያን ጊዜ ቅዱስ ታዴዎስ ሊቀ ሐዋርያትን "እርሱ እስኪመጣ ለምን አናርስም" አለው:: 2ቱ ተነስተው ታዴዎስ ሞፈር: ዼጥሮስ ደግሞ ስንዴውን ያዘ:: ቅዱሳኑ እየዘሩ ያረሱት ሰውየው ምግብ ይዞ እስኪመጣ አድጐ: አፍርቶ: እሸት ሆኖ ቆየው::

+ገበሬው የተደረገውን ተአምራት ባየ ጊዜ ደነገጠ:: ሊያመልካቸውም ወደደ:: እነርሱ ግን "እኛ የልዑል ባሮች ነን" ብለው በክርስቶስ ማመንን አስተማሩት:: "ልከተላችሁ" ቢላቸው "የለም! ከእሸቱ ይዘህ ወደ ከተማ ግባና ራት አዘጋጅልን:: እኛ እንመጣለን" አሉት::

+እርሱ ወደ ቤቱ ሲመለስ አሕዛብ ነገሩን ተረዱ:: ተሠብሥበውም "እነዚህ የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት እሳትም ሰይፍም አይበግራቸውም" ብለው ወደ ከተማ እንዳይገቡ ከበሩ ላይ ራቁቷን የሆነች ዘማ አቆሙ::

+ቅዱስ ታዴዎስ ገና ከርቀት ስላያት ቀና ብሎ #ቅዱስ_ሚካኤልን "እርዳን" አለው:: ሊቀ መላእክትም ድንገት ወርዶ ዘማዋን ሴት በጸጉሯ በዓየር ላይ ሰቀላት:: በከተማዋ ያሉ አሕዛብም ይህንና ሌሎች ተአምራትን አይተው ሁሉም በጌታችን አምነው ተጠመቁ:: ለሐዋርያቱም ሰገዱላቸው::

+አንድ ቀን ግን አንድ ጐረምሳ ባለ ጠጋ ቅዱስ ታዴዎስ "ሀብት ንብረታችሁን መጽውቱ" ሲል ሰምቶት ዘሎ የሐዋርያውን ጉሮሮ አንቆ ከሞት አድርሶት ነበር:: ያን ጊዜ "ጌታየ! ለካ ሀብታም ከሚጸድቅ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል ያልክ ለዚህ ነው!" ብሏል:: ባለ ጠጋው "እንዴት ይሆናል?" ቢለው መርፌ አሠርቶ ግመሉን ከነ ባለቤቱ በሰው ሁሉ ፊት 3 ጊዜ አሳልፎታል::

+ያም ማለት ጌታችን እንዳለው "በሰው ዘንድ የማይቻለው በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል::" (ማር. 10:23) በዚህ ምክንያትም ያ ክፉ ባለ ጸጋ ወደ ልቡናው ተመልሶ ከቅዱስ ታዴዎስ እግር ሥር ወደቀ:: ሐዋርያውም አለው "ሀብትህን ለነዳያን ስጥ:: ይህንንም በትር እንካና እየዞርክ ወንጌለ መንግስትን ስበክ::" ባለ ጸጋውም የተባለውን ሁሉ ፈጽሞ በክብር ዐርፏል::

+ቅዱሳኑ ታዴዎስና ዼጥሮስ ግን በሃገሪቱ አብያተ ክርስቲያናትን አንጸው: ካህናትን ሹመው: ያቺን በዓየር ላይ የሰቀሏትን ዘማም የተባረከች መበለት አድርገው: በሌሎች አሕጉራት ወንጌልን ለማዳረስ ወጥተዋል::

+ቅዱስ ታዴዎስም እስከ እርጅናው ድረስ ለወንጌል ሲተጋ ኑሯል:: ጌታችንም በየጊዜው በአካል እየተገለጸ አጽናንቶታል:: ከብዙ የድካምና የመከራ ዘመናት በሁዋላም በዚህች ቀን ዐርፏል::

=>ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከቅዱሱ ሐዋርያ በረከት ይክፈለን::

=>ሐምሌ 2 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ (ከ12ቱ ሐዋርያት)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቀ መለኮት
2.ቅዱስ ኢዮብ ጻድቅ ተአጋሲ
3.ቅዱስ አቤል ጻድቅ
4.ቅዱስ አባ ዻውሊ ገዳማዊ (ታላቁ)
5.ቅዱስ ሳዊሮስ ዘአንጾኪያ
6.አባ ሕርያቆስ ዘሃገረ ብሕንሳ

=>+"+ ጌታ ኢየሱስም ዘወር ብሎ አይቶ ደቀ መዛሙርቱን "ገንዘብ ላላቸው ወደ እግዚአብሔር መንግስት መግባት እንዴት ጭንቅ ይሆናል!" አላቸው:: ደቀ መዛሙርቱም እነዚህን ቃሎች አደነቁ:: ጌታ ኢየሱስም ደግሞ መልሶ "ልጆች ሆይ! በገንዘብ ለሚታመኑ ወደ #እግዚአብሔር መንግስት መግባት እንዴት ጭንቅ ነው! ባለ ጠጋ ወደ እግዚአብሔር መንግስት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢያልፍ ይቀላል" አላቸው:: +"+ (ማር. 10:23-28)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
#Feasts of #Hamle_2

✞✞✞On this day we commemorate the departure of Saint Thaddeus (Thaddaeus/Lebbaeus) the Apostle ✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞Saint Thaddeus (Thaddaeus/Lebbaeus) the Apostle ✞✞✞
=>The Tradition of the Church shows us that when our fathers, the Holy Apostles, followed our Lord Jesus Christ their ages were of 3 categories.
*The likes of John the Evangelist were in their 20s,
*The likes of Thaddeus were in their 30s and 40s,
*And the likes of St. Peter were in their 50s. Hence, the disciples were comprised of youths, adults, and older ones.

✞St. Thaddeus was formerly called Lebbaeus and in some texts (particularly in Eastern Orthodox writings), he is called as Simeon and Judah.

✞The Saint after following the Lord,
*was chosen as one of the 12 by his Creator,
*learned from the Lord for 3 years and 3 months,
*was blessed by His ascension,
*received 71 tongues (languages) on the day of Pentecost
*and preached by going around the world after the Apostles drew lots and he received his own diocese.

✞One day St. Thaddeus entered a city with the Arch-apostle St. Peter. And because they were preaching the Gospel without food for days, the kind Apostles were famished. And before entering the city, they saw an old man plowing a field, greeted him, and said, “We are hungry, could you give us food, please.” And the man, though a gentile, feeling empathetic, and without untying his oxen, went running. 

✞At that moment, St. Thaddeus said to the Arch-apostle, “Why do not we till [the field] until he comes back.” Thus, both rose, Thaddeus held the plow handle while Peter carried the grains of wheat. And what the Saints cultivated and sowed, awaited the man miraculously grown, bearing seeds, and ripe until he came back with food.
 
✞The farmer was shocked when he saw the wonder and wished to worship them. However, the Apostles said, “We are servants of the Almighty,” and taught him to believe in Christ. And when he said, “Let me follow you” the replied, “No! Take from the ripe wheat, go in the city, and prepare us dinner. We will come.”

✞And when he returned to his home, the gentiles heard of what had occurred. Then, they gathered and said, “These disciple of Christ will not be stopped by flames nor the sword.” Thereafter, they placed a naked adulterous woman at the gate of the city so the Apostles could not enter.

✞And because St. Thaddeus had seen her from afar, he raised his head and said to St. Michael, “Help us!” Suddenly, the Archangel descended, and suspended the adulterous woman in the air by means of her hair. Hence, the gentiles of the city and others seeing this miracle believed in our Lord, and all were baptized. They then bowed down to the Apostles [in veneration].
 
✞Nonetheless, on another day, one wealthy youth herd St. Thaddeus preach, “Give your riches and material wealth as alms” and he strangled the Apostle to the extent killing him. At that moment, the Saint said, “My Lord! This is why You said, ‘It is easier for a camel to go through the eye of a needle, than for a rich man to become holy.’” (Matt. 19:24/Mark 10:23) And the rich youth hearing this inquired, “How could it be?” Thence, Thaddeus had a needle made, and miraculously enabled a camel with its proprietor to pass through its eye trice before everyone.
 
✞And that came to pass per what our Lord had said, “The things which are impossible with men are possible with God” Luke 18:27/ Mark 10:23-27 And for this reason, that wicked rich man came to himself (came to his senses) and fell under the feet of the Apostle. Then, the Apostle instructed him, “Give your riches to the destitute. Take this staff, and go around preaching the Gospel.” The rich man executed all what he was told, and departed [from this world] in glory.
✞However, the Saints, Thaddeus and Peter, after they erected churches, ordained priests, made that adulterous woman whom they suspended on air a servant in that land, they left for other countries to evangelize.
 
✞St. Thaddeus lived laboring for the Gospel until his old age. And our Lord has appeared to him at different times to console him. And after many years of boundless toils, and tribulations, he departed on this day.

✞✞✞May our Lord Jesus Christ grant us from the blessing of the Holy Apostle.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 2nd of Hamle
1. St. Thaddeus (Thaddaeus/Lebbaeus) (One of the 12 Apostles)

✞✞✞ Monthly Feasts
1. St. John the Baptist
2. The Righteous and Longsuffering St. Job
3. St. Abel the Righteous
4. St. Abba Paul the Hermit (the Great)
5. St. Severus of Antioch
6. Abba Heryakos of Behensa

✞✞✞“And Jesus looked round about, and saith unto his disciples, How hardly shall they that have riches enter into the kingdom of God! And the disciples were astonished at his words. But Jesus answereth again, and saith unto them, Children, how hard is it for them that trust in riches to enter into the kingdom of God! It is easier for a camel to go through the eye of a needle, than for a rich man to enter into the kingdom of God.”✞✞✞
Mark 10:23-25

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርሃ ሐምሌን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
          

🌿ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!


1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, አላማ

    2 ,እምነት

    3,ጥረት

    4 ጥንቃቄ
=>እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።


🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Audio
"" ስንክሳር - ሐምሌ ፪/2 ""

❖ቅዱስ ታዴዎስ ሐዋርያ

(ሐምሌ 1 - 2017)

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሐምሌ ቡሩክ፤ ወአመ ፪፦

ቅድስት ጾመ ሐዋርያት (ንጹሐን)

ወበዓለ ቅዱሳን፦

✿ዐቢይ ወክቡር ሐዋርያ፥ ታዴዎስ ልብድዮስ (፩ እም፲ወ፪ቱ ሐዋርያት አጋዕዝቲነ)

✿እምነ ቅድስት ዜና ድንግል ገዳማዊት፥ ዘቡልጋ (ተላዊቱ ለአቡነ ታዴዎስ ዘጽላልሽ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
ታዴዎስ ሐዋርያ ብእሲ ሔር፤
ወበዓለ ዐቢይ መንክር፤
በእንተ ዘረድኦ በፍኖት ሚካኤል ክቡር፤
ምስለ ዜና ድንግል ጻድቅት ተዝካሮ ንገብር!

እንኳን አደረሰነ !

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
††† እንኳን ለዓምደ ሃይማኖት ቅዱስ ቄርሎስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ †††

††† ቅዱስ ቄርሎስን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን " #ዓምደ_ሃይማኖት- የሃይማኖት ምሰሶ" ይሉታል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:-

ሊቁ የተወለደው በእስክንድርያ (ግብጽ) በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን ነው:: እናቱ የወቅቱ ፓትርያርክ #ቅዱስ_ቴዎፍሎስ እህቱ ነበረችና አጎቱ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ወስዶ አሳድጐታል:: ገና በልጅነቱ ወደ #አባ_ሰራብዮን ገዳም ገብቶ ቅዱሳት መጻሕፍትንና ገዳማዊ ሕይወትን ተምሯል:: በጾም: በጸሎትና በትሕትና የታሸ ነውና ሲማር አንድ ጊዜ ካነበበው በሕሊናው ተስሎ ይቀር ነበር::

ቅዱስ ቴዎፍሎስ "ምዕመናንን አስተምርልኝ" ብሎ ወደ ከተማ አመጣው:: #መንፈስ_ቅዱስ አድሮበታልና ሲያስተምር ወይ ደግሞ መጻሕፍትን ሲያነብ ከምዕመናን ወገን ስንኩዋን የሚያወራና የሚንቀሳቀስ ቀርቶ የሚቀመጥም አልነበረም:: ጣዕመ ስብከቱም ብዙዎችን ለወጠ::

ከዚያም በ412 ዓ/ም አጎቱ የነበረው ፓትርያርክ አባ ቴዎፍሎስ ሲያርፍ ዻዻሳትና ሊቃውንት በአንድነት ቅዱስ ቄርሎስን መረጡ:: የእስክንድርያም 24ኛ ሊቀ ዻዻሳት ሆኖ ተሾመ:: በዘመኑ #ቤተ_ክርስቲያን አበራች:: በቅድስናው: በሊቅነቱ: በስብከቱ: በድርሰቶቹና በትጋቱ በፍጹም አገለገላት::

በወቅቱ ስመ ክፉ መናፍቅ ንስጥሮስ ተነስቶ የእስያ አብያተ ክርስቲያናትን አወካቸው:: ትምሕርቱ ክርስቶስን "2 አካል: ባሕርይ ነው" (ሎቱ ስብሐት!) የሚል ነበር:: በእውነት እንየው ከተባለ ግን ጠቡና ጥላቻው ከድንግል ማርያም ጋር ነበር:: ምክንያቱም ጌታችንን ወደ 2 የከፈለው #እመቤታችንንየአምላክ እናት አይደለሽም ለማለት ነው:: (ላቲ ስብሐት!)

ነገሩን #ቅዱስ_ቄርሎስ በሰማ ጊዜ ወዳለበት ሒዶ ቢመክረውም ንስጥሮስ ሊሰማ አልፈለገም:: በዚህ ምክንያት በትንሹ ቴዎዶስዮስ (የቁስጥንጥንያ ንጉሥ) ትዕዛዝ በኤፌሶን ታላቅ ጉባኤ እንዲሰበሰብ ሆነ:: ይህ ጉባዔ በቤተ ክርስቲያናችን የመጨረሻው የተቀደሰ ጉባዔ ነው:: በ431 ዓ/ም #በኤፌሶን ከተማ የመናፍቃኑን ጥርቅም ሳንቆጥር ሃይማኖታቸው የቀና 200 #ቅዱሳን_ሊቃውንት ተገኙ::

የሚገባው ጸሎትና ሱባዔ ከተፈጸመ በሁዋላ ጉባዔው ተጀመረ:: አፈ ጉባዔው ሊቀ ማሕበር ማር (ቅዱስ) ቄርሎስ ነበርና በጉባዔ ፊት ንስጥሮስን ተከራክሮ ረታው:: ምላሽም አሳጣው:: ከቅዱሳት መጻሕፍት #ክርስቶስ አንድ ባሕርይ መሆኑን: #ድንግል_ማርያምም #ወላዲተ_አምላክ መሆኗን እየጠቀሰ: በምሳሌም እያሳየ አስረዳ::

የሰይጣን ማደሪያ ንስጥሮስ ግን እንቢ: አላምንም በማለቱ ተወግዞ ተለየ:: ቅዱሳን ሊቃውንቱም በቅዱስ ቄርሎስ አርቃቂነት 12 አንቀጾችን አዘጋጅተው ወደ ዓለም ሁሉ ላኩ:: እሊህ አንቀጾች ዛሬም በሊቃውንቱ እጅ አሉ:: ይነበባሉ: ይተረጎማሉ::

††† ከእነዚህም አንዱ ድንግል ማርያም " #ታኦዶኮስ(የእግዚአብሔር እናቱ) ናት" የሚል ነው:: እመቤታችንን:-
¤የአምላክ እናት:
¤ዘላለማዊት ድንግል:
¤ፍጽምት:
¤ንጽሕትና አማላጅ ብሎ ማመን ለሰማያዊ ርስት የሚያበቃ በጐ ሃይማኖት ነውና::

ጉባዔው ከተጠናቀቀ በሁዋላ ቅዱስ ቄርሎስ ንስጥሮስን ጠርቶ "በድንግል ማርያም እመን:: እርሷ ከልጇ ታስታርቅሃለች" ቢለው በድጋሚ "እንቢ" አለው:: ያን ጊዜ ሊቁ "ለአምላክ እናት ያልታዘዘ ምላስህ ላንተም አይታዘዝህ" ብሎ ረገመው:: ወዲያው ምላሱ ተጐልጉሎ ወጥቶ ደረቱ ላይ ወደቀ::

እንደ ውሻ እየተዝረከረከ ሒዶ ከወዳጆቹ ጋር ቁሞ ሳለ መሬት ተከፍታ ውጣዋለች::
ቅዱስ ቄርሎስ ግን ለ32 ዘመናት በመንበሩ ላይ አገልግሎ: ፍሬ ትሩፋት አፍርቶ: ብዙ ድርሰቶችንም ደርሶ በ444 ዓ/ም በዚህች ቀን ዐርፏል:: ከድርሰቶቹም ቅዳሴው: ድርሳነ ቄርሎስና ተረፈ ቄርሎስ ይጠቀሳሉ::

††† ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአባቶቻችን ጸሎት ቤተ ክርስቲያንን ይጠብቅልን:: ከሊቁም በረከቱን ይክፈለን::

††† ሐምሌ 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ ቄርሎስ ሊቅ (ዓምደ ሃይማኖት)
2.ቅዱስ ክልስቲያኖስ ዘሮሜ (ታላቅ ጻድቅ ሊቀ ዻዻሳት)
3.አባ ሉቅያስ ኤዺስ ቆዾስ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.በዓታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል ወላዲተ አምላክ
2.ቅዱሳን ኢያቄም ወሐና
3.ቅዱሳን ሊቃነ ካህናት አበው (ዘካርያስና ስምዖን)
4.አባ ሊባኖስ ዘመጣዕ
5.አቡነ ዜና ማርቆስ
6.አቡነ መድኃኒነ እግዚእ ዘደብረ በንኮል

††† "የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ:: የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው:: ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ: እስከ ዘለዓለምም ያው ነው:: ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምሕርት አትወሰዱ:: ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም:: በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና::" †††
(ዕብ. 13:7)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

'
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
#Feasts of #Hamle_3

✞✞✞On this day we commemorate the departure of Saint Cyril of Alexandria✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞ Saint Cyril the Scholar✞✞✞
=>The scholars of the Church call St. Cyril as “A Pillar of Faith.” And if asked how that came to be, it was as follows.

✞The Scholar was born in Alexandria (Egypt) in the 4th century. And because his mother was the sister of the then Patriarch St. Theophilus, his uncle took, and raised him. While he was just a child, he entered into the Monastery of Abba Sarapion, and studied Holy Scripture and the ascetic life. Because he was kneaded by prayer, fasting, and humility, when he learned something and read it for the first time the content used to be instilled in his mind.

✞Thereafter, St. Theophilus brought him to the city saying, “Teach the faithful for me.” Because the Holy Spirit had dwelt in Cyril, when he taught or read the Holy Books, the faithful did not sit let alone make a sound or move. And the tang of his sermon changed many.

✞Then, in the year 412 A.D when the Patriarch, Abba Theophilus, his uncle, departed, the bishops and the scholars together chose St. Cyril. And he was appointed as the 24th Archbishop of Alexandria. And in his day, the Church shone. And he served Her wholly in holiness, as a scholar, by his sermons, by his writings, and his diligence.

✞During that period, a heretic named Nestorius (who was the Archbishop of Constantinople) disturbed the Churches of Asia. His heretical teaching stated, “Christ (glory be to His name) was ‘two persons/hypostases, and two natures/physes.’” But if we want to see it truly, his conflict and hate was with and towards the Virgin Mary. And that is why he divided our Lord (glory be to Him) to two, to say, “Our Lady is not the Mother of God (Theotokos).” (Glory be to her).

✞And when St. Cyril heard the matter, he went to Nestorius (sent letters) and spoke to him to correct his errors, but Nestorius did not want to hear it. And for this reason, by the order of Theodosius II (Theodosius the Younger), a great council (an Ecumenical Council) was convened at Ephesus. This council was the last Holy Ecumenical Council in our Church. Not counting the heretics, there were 200 holy scholars gathered in the City of Ephesus in 431 A.D for the council.

✞After the proper prayers and vigils were concluded, the Council started. Because the chairman was Mar St. Cyril, he debated and overcame Nestorius before the gathered. He silenced and made him responseless as well. The Saint showed by quoting the Holy Bible and by providing examples that Christ was one [united] nature (Miaphysis) and that the Virgin Mary was Theotokos (God-bearer).

✞Nevertheless, because Nestorius the abode of Satan did not agree, and said he will not believe that (the correct teaching), he was excommunicated from the Church. The holy scholars on the other hand sent 12 anathemas to all the world after they were drafted by St. Cyril. These anathemas are still in the hands of the scholars of the Church and are read and exegeted.

✞✞✞And one of the anathemas states that the Virgin Mary is “Theotokos – the Mother of God” (Anathema 1). Believing that our Lady
*is the Mother of God (Theotokos)
*is ever-virgin
*is perfect
*is pure, and an intercessor is a good faith that will enable one to receive the heavenly inheritance.

✞After the Council concluded, St. Cyril called Nestorius, and said to him, “Believe in the Virgin Mary [that she is the Theotokos]. She will reconcile you with her Son.” However, Nestorius as previous said, “No.” Hence, at that moment, the Scholar cursed him saying, “May your tongue which is not obedient to the Mother of God may it not obey you as well.” And immediately after, Nestorius’ tongue protruded and reached his chest.
✞While he moved like a slobbering dog, and stood with his friends, the earth opened up and swallowed him whole (though some say he was banished to a desert).

✞St. Cyril, on the other hand, for 32 years upon his See served, bore fruits of virtues, wrote many texts and departed on this day in the year 444 A.D. From his works his liturgy, his homilies/commetaries, and his dialogue with Palladius are mentionable.

✞✞✞ May our Lord Jesus Christ safeguard the Church by the prayers of our fathers. And may He grant us from the Scholar’s blessing.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 3rd of Hamle
1. St. Cyril of Alexandria the Scholar (Pillar of Faith)
2. St. Celestine of Rome (A great righteous Archbishop)
3. Abba Lucius the Bishop

✞✞✞ Monthly Feasts
1. The Entrance of our Lady the Virgin Saint Mary the God-bearer into the Temple
2. Sts. Joachim and Anna
3. Sts. The Arch-Priests (Zacharias and Simeon)
4. Abba Libanos of Mata
5. Abune Zena Markos
6. Abune Medhanine Egzi of Debre Benkol

✞✞✞“Remember them which have the rule over you, who have spoken unto you the word of God: whose faith follow, considering the end of their conversation. Jesus Christ the same yesterday, and to day, and for ever. Be not carried about with divers and strange doctrines. For it is a good thing that the heart be established with grace; not with meats, which have not profited them that have been occupied therein.”✞✞✞
Heb. 13:7-9

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርሃ ሐምሌን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
          

🌿ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!


1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, አላማ

    2 ,እምነት

    3,ጥረት

    4 ጥንቃቄ
=>እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።


🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
ቀዳማይ ምኒልክ

የቅዱስ ሰሎሞን እና የንግሥት ሳባ ልጅ።

የቅዱስ ዳዊት የልጅ ልጅ።

ከክርስቶስ ልደት 900 ዓመት በፊት ታቦተ ጽዮንን ወደ ኢትዮጵያ ያመጣ።

አምልኮተ እግዚአብሔርን ያስፋፋ።

ሥርዓተ ኦሪትን ያመጣልን ደግ ሰው።

ሐምሌ 3 ዕረፍቱ ይከበራል።
ከበረከቱ ይክፈለን።

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
2025/07/10 14:41:10
Back to Top
HTML Embed Code: