Telegram Web Link
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሐምሌ ቡሩክ፤ ወአመ ፮፦

ተዝካረ ጻማ ንግደታ ለእግዝእትነ ማርያም ድንግል፥ ወላዲተ አምላክ (ደብረ ቁስቋም)

ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ካህን ወነቢይ፥ ዕዝራ ሱቱኤል (ዘቦአ ብሔረ ሕያዋን)
✿መርቄሎስ ሐዋርያ፥ ዘተሰምየ ጳውሎስሃ፥ ዘእም፸ወ፪ቱ አርድእት (ዘገነዞ ለጴጥሮስ ርዕሰ አርድእት)
✿በርተሎሜዎስ ሐዋርያ (ዘእም፲ወ፪ቱ አበዊነ)
✿ቴዎዳስያ ሰማዕት (እሙ ለአብሮኮሮንዮስ)
✿፪ቱ መኳንንት፥ ሰማዕታት (ማኅበራኒሃ)
✿፲ወ፪ አንስት (ሰማዕታት)
✿ንስተሮኒን እመ ምኔት (ዘእምሰብአ ኢየሩሳሌም)
✿ከላድያኖስ ሊቀ ጳጳሳት (ታስዕ እማርቆስ ወንጌላዊ)
✿፲፻ ሰማዕታት

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
=>+"+ እንኩዋን ለአጋእዝተ ዓለም #ሥላሴ እና ለቅዱሳን
አበው #አብርሃም: #አባ_ሲኖዳ እና #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋሥጫ
ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ +"+

+"+ #ሥሉስ_ቅዱስ +"+

=>በአንድነቱ ምንታዌ (ሁለትነት): በሦስትነቱ ርባዔ (አራትነት)
የሌለበት የዘለዓለም አምላክ: የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ
#እግዚአብሔር ነው:: #አብ : #ወልድ : #መንፈስ_ቅዱስ
በስም: በአካል: በግብር ሦስትነት: በባሕርይ: በሕልውናና
በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው:: በዚህ ጊዜ ተገኙ: በዚህ ጊዜ
ያልፋሉ አይባሉም:: መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና::

+ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት " #ቅድስት_ሥላሴ "
እንላቸዋለን:: የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም::
የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል:: በቤቱም መጥተው
ያድራሉ::

+ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል
በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም:: አባታችን
#ቅዱስ_አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን
በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል:: ሥላሴ
አኀዜ ዓለም (ዓለምን በእጁ የያዘ) ነው:: ነገር ግን በፍቅር
ለሚሻው በፍቅር ይመጣል::

+አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ: እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ
ሥላሴን በድንኩዋናቸው አስተናገዱ:: አብርሃም እግራቸውን
አጠበ:: (ወይ መታደል!) በጀርባውም አዘላቸው:: (ድንቅ አባት!)
ምሳቸውንም አቀረበላቸው:: እንደሚበሉ ሆኑለት:: በዚያው
ዕለትም የይስሐቅን መወለድ አበሠሩት:: #ቅድስት_ሣራ ሳቀች::
እንደ ዘንድሮ ወገኖቻችን የማሾፍ አይደለም:: ደስታና ጉጉት
የፈጠረው እንጂ:: ሥላሴ "ምንት አስሐቃ ለሣራ በባሕቲታ"
ብለው ነበርና በዚህም ምክንያት ነው " #ይስሐቅ" የተባለው::

+ሥላሴን ያስተናገደች ድንኩዋን (ሐይመት) የድንግል
እመቤታችን ማርያም ምሳሌ ናት:: በድንግል ላይ #አብ
ለአጽንኦ: #መንፈስ_ቅዱስ ለአንጽሖ: #ወልድ በተለየ አካሉ
ለሥጋዌ በእርሷ ላይ አርፈዋል / አድረዋልና::

+"+ #ታላቁ_አባ_ሲኖዳ +"+

=>የባሕታውን ሁሉ አለቃቸው ታላቁ ቅዱስ ሲኖዳ:-
¤በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የተወለደ
¤በእናቱ ማሕጸን ሳለ መላእክት በሰይፈ እሳት ይጠብቁት የነበረ
¤የታላቅነት ትንቢት የተነገረለት
¤ገና ሳይወለድ ሥውራን አበው የሰገዱለት
¤በሕጻን ሰውነቱ ጾምና ጸሎትን የጀመረ
¤የልጅነት ቁርስና ምሳውን ለነዳያን ያካፍል የነበረ
¤በ9 ዓመቱ ወደ በርሃ የመነነ
¤የአባ አብጐል ደቀ መዝሙር የሆነ አባት ነው::

+ሲመነኩስም በእግዚአብሔር ትእዛዝ #የሠለስቱ_ደቂቅ
አስኬማ: #የኤልያስ ቆብዕ እና የመጥምቁ #ዮሐንስ ቅናትን
(መታጠቂያ) ከያሉበት መላእክት አምጥተውለት የመነኮሰ
¤ዓለምን በሙሉ በጸሎቱ ይጠብቅ የነበረ
¤የግብፅን በርሃ በብርሃን የሞላ
¤በርካታ ድርሰቶችን የደረሰ
¤ያለ ማቇረጥ በየቀኑ ከ100 ዓመታት በላይ ከጌታችን ክርስቶስ
ጋር የተነጋገረ
¤ደመናትን ተጭኖ ይሔድ የነበረና
¤ያለ ዕረፍት ለ111 ዓመታት ከ2 ወራት ፈጣሪውን ያገለገለ
አባት ነው::

+በዚህም ምክንያት አንድ ቀን ገዳማውያን ሁሉ እየሰሙ
እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ መጣ:: "ሲኖዳ ተሠይመ
#አርሲመትሪዳ " (ሲኖዳ አርሲመትሪዳ ሆኗል:: ማለትም
ለባሕታውያን ሁሉ አለቃ ሁኖ ተመርጧል ማለት ነው:: )

+ቅዱሱ የጌታችንን እግር እያጠበም ይጠጣ ነበር::
+በዚህች ዕለት በ120 ዓመቱ ጌታችን ወርዶ ሲያሳርገው
#አቡነ_ኪሮስ "ታላቅ ምሰሶ (ታላቅ ዛፍ) ወደቀ" ብለው
አልቅሰዋል:: #ሲኖዳ ማለት "ደግ ሰው" ማለት ነው::

+"+ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ ( #GIYORGIS_OF_SEGLA )
+"+

=>ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ #ጋስጫ
ውስጥ በ1358 ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ
ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ
"ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው "የእግዚአብሔር
ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት:: መገፋቱን የተመለከተ
#አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን ከልቡ ይወዳት ነበረና
ይማጸናት ገባ::

+ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም
ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል
እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና #ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ
መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም ነገረችው::
"ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን አጠጥታው
ተሠወረችው::

+ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ:: በጽድቁ
ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተነትናቸው:
መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ:: የተረጐማቸውና
ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን ደረሰ:: (መጽሐፈ
ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን: ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ
መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች ነበሩ)

+ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው የኢ/
ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1. #ሊቀ_ሊቃውንት
2. #በላዔ_መጻሕፍት
3. #ዓምደ_ሃይማኖት
4. #ዳግማዊ_ቄርሎስ
5. #ጠቢብ_ወማዕምር

+ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 ዓ/ም በዚህች ቀን
ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ 7 ቀን
ነው::

=>የሥላሴ ቸርነት: የአብርሃም ደግነት: የአበው አባ ጊዮርጊስና
አባ ሲኖዳ በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን::

=>ሐምሌ 7 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱሳን አብርሃምና ሣራ (ሥላሴን ያስተናገዱ)
2.ብሥራተ ልደተ ይስሐቅ
3.ታላቁ አባ ሲኖዳ (የባሕታውያን ሁሉ አለቃ)
4.አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (ሊቀ ሊቃውንት: ኢትዮዽያዊ
የሃይማኖት ምሰሶ)
5.ቅዱስ አግናጥዮስ ዘአንጾኪያ (ምጥው ለአንበሳ)
6.አባ መቃቢስ
7.አባ አግራጥስ

=>ወርሐዊ በዓላት
1.አባ ዳንኤል ዘገዳመ ሲሐት
2.አባ ባውላ ገዳማዊ
3.ቅዱስ አትናቴዎስ ሐዋርያዊ

=>+"+ እግዚአብሔርም ለአብርሃም ተስፋ በሰጠው ጊዜ:-
'በእውነት እየባረክሁ እባርክሃለሁ:: እያበዛሁም አበዛሃለሁ'
ብሎ ከእርሱ በሚበልጥ በማንም ሊምል ስላልቻለ በራሱ ማለ::
እንዲሁም እርሱ ከታገሠ በሁዋላ ተስፋውን አገኘ:: +"+ (ዕብ.
6:13)
=>+"+ የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ: የእግዚአብሔርም ፍቅር:
የመንፈስ ቅዱስም ሕብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን:: አሜን:: +"+
(ቆሮ. 13:14)

<<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
Memhir Esuendale:
#Feasts of #Hamle_7

✞✞✞On this day we commemorate the Rulers of the World the Holy Trinity, and the Holy Fathers Abraham, Abba Shenouda and Abba Giorgis of Gascha✞✞✞

✞✞✞In the name of the Father, the Son and the Holy Spirit, one God. Amen!✞✞✞

✞✞✞The Holy Trinity✞✞✞
=>The eternal God, Who doesn’t have duality in His oneness/unity and Who doesn’t have an addition (a fourthness/quadrality) to His Threeness/Trinity, is the maker of all creation. The Father, the Son and the Holy Spirit exist eternally as three in Their hypostatic names, hypostases and hypostatic attributes while They are one in essence, being and will. One cannot say/ask about Them saying, “When did They come to be? Or when will They pass?” as They are the beginning and the end.


✞And as They are compassionate as a mother, we call Them as “Qedest Selassie” (Qedest being a feminine adjective). They do not abhor the person who hates (does not believe in) Them. But They love with many folds he/she who loves Them and dwell in his/her abode.

✞There is none from creation that was loved as Abraham except for our Lady before the Holy Trinity. Our holy father Abraham as he was the father of all kindness, received the Holy Trinity at the tree of Mamre in Hebron and served Them. The Holy Trinity has the world in the palm of His hand but to him who seeks Him in love, He goes to in love.

✞Our father Abraham at the age of 99 and our mother Sarah at the age of 89 served the Holy Trinity in their tent. Abraham washed Their feet (What a fortune!). And he carried Them with his back. (A wondrous father!) He brought Them lunch. They seemed as if They ate, for him. And They announced to him on that day that Isaac would be born. St. Sarah laughed but not in ridicule like today, rather she laughed from joy and anticipation. And because the Holy Trinity had said, “Wherefore did Sarah laugh” (Gen.18:13), for this reason he, Sarah’s son, was called Isaac.

✞The tent that served the Holy Trinity is the symbol of our Lady the Virgin Mary. And that’s because the Father to preserve her, the Holy Spirit to prepare her and the Son for incarnation and in His incarnate body have resided upon/in her.

✞✞✞Saint Abba Shenouda/Shenoute the Archimandrite✞✞✞
=>The chief of all hermits, the Great Abba Shenouda was a father
- who was born in the 4th century
-who was protected by flaming swords of angels in his mother’s womb
-about whom was foretold a prophecy of greatness
-to whom prostrated the sowah (invisible fathers/ anchorites) before he was born
-who began prayer and fasting as a child – with a child’s physique
-who distributed his breakfast and lunch to the destitute in his childhood
-who became an ascetic and left for the desert at the age of 9
-and who was the disciple of Abba Abgol (Bgoul/Bigal)

✞And when he became a monk, he was garbed by the order of God, by the schema of the Three Children, the hood/kolonsowa of Elijah and the girdle of St. John the Baptist that were brought by the angels from where they were.

✞The Saint was a father
-who protected the whole world by his prayers
-who filled the desert of Egypt with light
-who wrote many homilies
-who conversed with our Lord Christ daily for a 100 years without interlude
-who traveled upon clouds
-and who served his Creator for 111 years and 2 months without ceasing.

✞And for these reasons one day while all the monastics listened, a voice, which said, “Shenouda has become an Archimandrite (the chief of all the hermits)” came from heaven.

✞The Saint also used to drink from what was left of washing the Lord’s feet.

✞On this day, at the age of 120 years when our Lord descended and took up his soul, Abune Kiros (Karas/Cyrus) wept saying, “A great pillar has fallen”. The name Shenouda has the meaning “kind person/man”.
✞✞✞Abba Giyorgis/Giorgis of Segla/Gesecha/Gascha✞✞✞
=>This great Ethiopian scholar and saint was born in Gesecha/Gascha, Wello in 1358 (1357) E.C. Even though he could not grasp what he was taught in his childhood, he was sincere and obedient. However, his teacher sent him to his parents saying, “Since he can’t comprehend what he is taught, take him.” But they responded with, “As he is God’s, let him serve you” and sent him back. Abba Giyorgis, who saw that he was pushed away, started beseeching our Lady, as he loved her from the depths of his heart.

✞He spent the day helping in the monastery, fetching water, grinding and crushing grains until he was soaked in his sweat, and prayed during the night until dawn. Because our Lady the Virgin heard his plea, she came with St. Uriel. Then she blessed him with her pure hands and told him mysteries. As it says, “She told him five words.” Then she gave him from the grail of wisdom to drink and left.

✞Starting from that moment, Abba Giyorgis was completely changed. Upon his righteousness, he added the cloak of scholarship. He started exegeting the scriptures and silencing heretics. He wrote 41 works, not including those he translated and expounded. (Masehafa Sa'atat (Horologium), Masehafa Mestir (The Book of Mystery), Arganon (Hymns of Praise to Mary), Hohite Birhan (The Gate/ Portal of Light), Wedasae Mesqel (Praise of the Cross) and the like…were his writings).

✞He was also an apologist of the faith. For his holiness and contribution, the church calls him as;
1. Head of the Scholars
2. Learned (‘Belae Mesehaft’-Devourer of Books)
3. Pillar of Faith
4. Cyril II (the Second)
5. Wise and Insightful

✞The righteous scholar passed away on this day at the age of 60 in the year 1418 (1417) E.C. He was born and departed on the same day, Hamle 7 (July 14).

✞✞✞ May the Goodness of the Trinity, the kindness of Abraham and the blessings of the fathers Abba Giorgis and Abba Shenouda be with us all.

✞✞✞ Annual feasts celebrated on the 7th of Hamle
1. Sts. Abraham and Sarah (The Day they served the Holy Trinity)
2. Annunciation of the Birth of Isaac
3. The Great Abba Shenouda/Shenoute the Archimandrite
4. Abba Abba Giyorgis/Giorgis of Segla/Gesecha/Gascha (Chief of the Scholars, Ethiopian Pillar of Faith)
5. St. Ignatius of Antioch (the one given to lions)
6. Abba Maccabaeus
7. Abba Agrates


✞✞✞ Monthly Feasts
1. Abba Daniel of the Monastery of Scete
2. Abba Paula the Monastic
3. St. Athanasius the Apostolic

✞✞✞ “For when God made promise to Abraham, because He could swear by no greater, He sware by Himself, Saying, Surely blessing I will bless thee, and multiplying I will multiply thee. And so, after he had patiently endured, he obtained the promise.”✞✞✞
Heb. 6:13-15

✞✞✞ “The grace of the Lord Jesus Christ, and the love of God, and the communion of the Holy Ghost, be with you all. Amen.”✞✞✞
2Cor. 13:14

✞✞✞ Salutations to God ✞✞✞

(Translated by Mhr. Esuendale Shemeles with the permission of Dn. Yordanos Abebe)
+"+ #አባ_ጊዮርጊስ_ዘጋስጫ ( #GIYORGIS_OF_SEGLA )
+"+

=>ታላቁ ኢትዮዽያዊ ሊቅና ጻድቅ የተወለደው ወሎ #ጋስጫ
ውስጥ በ1358 ዓ/ም ነው:: ከልጅነቱ ትምሕርት አልገባሕ
ቢለውም በልቡናው ግን ቅን እና ታዛዥ ነበር:: መምሕሩ
"ትምሕርት አይገባውምና ውሰዱት" ቢላቸው "የእግዚአብሔር
ነውና ያገልግላችሁ" ብለው መለሱት:: መገፋቱን የተመለከተ
#አባ_ጊዮርጊስ #እመቤታታችንን ከልቡ ይወዳት ነበረና
ይማጸናት ገባ::

+ቀን ቀን ገዳሙን ሲረዳ: እሕል ሲፈጭና ሲከካ: ላቡንም
ሲያፈስ ውሎ ሌሊት ደግሞ ሲጸልይ ያነጋ ነበር:: ድንግል
እመቤታችን ጸሎቱን ሰምታለችና #ቅዱስ_ዑራኤልን አስከትላ
መጣችለት:: በንጹሐት እጆቿ ባርካው ምሥጢርንም ነገረችው::
"ወነገረቶ ሐምስተ ቃላተ" እንዲል:: ጽዋዐ ልቡናን አጠጥታው
ተሠወረችው::

+ከዚህች ሰዓት ጀምሮ አባ ጊዮርጊስ ፍጹም ተለወጠ:: በጽድቁ
ላይ የሊቅነትን ካባ ደረበ:: ቅዱሳት መጻሕፍትን ይተነትናቸው:
መናፍቃንንም ምላሽ ያሳጣቸው ገባ:: የተረጐማቸውና
ያተታቸውን ሳይጨምር 41 ድርሰቶችን ደረሰ:: (መጽሐፈ
ሰዓታት: መጽሐፈ ምሥጢር: አርጋኖን: ኆኅተ ብርሃን: ውዳሴ
መስቀል: ወዘተ . . . የእርሱ ድርሰቶች ነበሩ)

+ስለ ሃይማኖትም ጠበቃ ነበር:: ስለ ቅድስናውና ውለታው የኢ/
ኦ/ተ/ቤ እንዲህ ትጠራዋለች:-
1. #ሊቀ_ሊቃውንት
2. #በላዔ_መጻሕፍት
3. #ዓምደ_ሃይማኖት
4. #ዳግማዊ_ቄርሎስ
5. #ጠቢብ_ወማዕምር

+ጻድቁ ሊቅ በተወለደ በ60 ዓመቱ በ1418 ዓ/ም በዚህች ቀን
ዐርፏል:: አባ ጊዮርጊስ የተወለደውም ያረፈውም ሐምሌ 7 ቀን
ነው::

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
ታላቁ_አባ_ሲኖዳ +"+

=>የባሕታውን ሁሉ አለቃቸው ታላቁ ቅዱስ ሲኖዳ:-
¤በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን የተወለደ
¤በእናቱ ማሕጸን ሳለ መላእክት በሰይፈ እሳት ይጠብቁት የነበረ
¤የታላቅነት ትንቢት የተነገረለት
¤ገና ሳይወለድ ሥውራን አበው የሰገዱለት
¤በሕጻን ሰውነቱ ጾምና ጸሎትን የጀመረ
¤የልጅነት ቁርስና ምሳውን ለነዳያን ያካፍል የነበረ
¤በ9 ዓመቱ ወደ በርሃ የመነነ
¤የአባ አብጐል ደቀ መዝሙር የሆነ አባት ነው::

+ሲመነኩስም በእግዚአብሔር ትእዛዝ #የሠለስቱ_ደቂቅ
አስኬማ: #የኤልያስ ቆብዕ እና የመጥምቁ #ዮሐንስ ቅናትን
(መታጠቂያ) ከያሉበት መላእክት አምጥተውለት የመነኮሰ
¤ዓለምን በሙሉ በጸሎቱ ይጠብቅ የነበረ
¤የግብፅን በርሃ በብርሃን የሞላ
¤በርካታ ድርሰቶችን የደረሰ
¤ያለ ማቇረጥ በየቀኑ ከ100 ዓመታት በላይ ከጌታችን ክርስቶስ
ጋር የተነጋገረ
¤ደመናትን ተጭኖ ይሔድ የነበረና
¤ያለ ዕረፍት ለ111 ዓመታት ከ2 ወራት ፈጣሪውን ያገለገለ
አባት ነው::

+በዚህም ምክንያት አንድ ቀን ገዳማውያን ሁሉ እየሰሙ
እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ መጣ:: "ሲኖዳ ተሠይመ
#አርሲመትሪዳ " (ሲኖዳ አርሲመትሪዳ ሆኗል:: ማለትም
ለባሕታውያን ሁሉ አለቃ ሁኖ ተመርጧል ማለት ነው:: )

+ቅዱሱ የጌታችንን እግር እያጠበም ይጠጣ ነበር::
+በዚህች ዕለት በ120 ዓመቱ ጌታችን ወርዶ ሲያሳርገው
#አቡነ_ኪሮስ "ታላቅ ምሰሶ (ታላቅ ዛፍ) ወደቀ" ብለው
አልቅሰዋል:: #ሲኖዳ ማለት "ደግ ሰው" ማለት ነው::

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት ጉባኤ ዘጎንደር
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል:: አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሳችሁ!

አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ማኅቶት፤
ዘባረክዎ ለአብርሃም በዊኦሙ በድርገት፤
ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በላዔ መጻሕፍት ወሊቀ ሊቃውንት፤
አግናጥዮስ ሐዋርያ ሊቀ ጳጳሳት ወሰማዕት፤
አርሲመትሪዳ ሲኖዳ በዓለ ሥልጣት ብሑት፤
እህተ ጴጥሮስ ወእንድርያስ ዘአብርሁ በውስተ ጽልመት!

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርሃ ሐምሌን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መታው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
          

🌿ዝክረ ቅዱሳንን ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!


1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, አላማ

    2 ,እምነት

    3,ጥረት

    4 ጥንቃቄ
=>እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸዉ ኑሯቸው።


🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
✞እንኳን አደረሰን !

"እንበለ ጽርዓት ወትረ፥ ጊዜ ትሴብሕ ሥላሴ፤
ሱራፌልሃ ትመስል፥ ወአኮ ብእሴ፤
#ጊዮርጊስ ነቅዓ ቅዳሴ!
ሰላም ለከ።" (ሰላምታ ዘቅዱስ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ)

መሐሪ ሥላሴ፦ ከአባ ጊዮርጊስ፥ ከአባ ሲኖዳ፥ ከአባ አግናጥዮስ፥ ከአባ እንድርያስ (ዘደብረ ሊባኖስ)፥ ከአበዊነ አብርሃም ወይስሐቅ፥ ከቅዱሳት ሣራ ወእኅተ ጴጥሮስ፥ ከሊቃውንት (ስብሐት ለአብ፥ ድንቁ፥ ክፍለ ዮሐንስ፥ ሲኖዳ . . .) ፥ ከንጉሡ አድያም ሰገድ ሐፄ ኢያሱ . . . በረከትን ያሳትፈን!

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
መንክር ትእግስትከ፤
ወዐቢይ ትኅትናከ፤
ግሩም ግብርከ፤
ወንጹሕ ኅሊናከ፤
ጽድቅ ትምህርትከ፤
ወጥዑም ውዳሴከ፤
. . .

ሠግላዊ ጻድቅ፥ ወሐዋርያዊ መምህር፤
የዋህ ብእሴ እግዚአብሔር፤
ቡሩክ ብእሲሁ፤
አፈ መዓር ወሶከር፤
አፈ በረከት ወሊቀ ሊቃውንት፤
ጠቢብ ወማእምር፤
ቄርሎስ ዳግማዊ ዘብሔረ ኢትዮጵያ . . .

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (ዘኮነ ልደቱ ወዕረፍቱ በዛቲ ዕለት)

በረከቱ ቅድስት፤
ወሀብተ ረድኤቱ ንጽሕት፤
ወጸሎቱ ውክፍት፤
ትብጽሐነ ወትረ፤
አሜን!

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሳችሁ!!!

ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ዜና እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)

🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

🔗https://www.tg-me.com/zikirekdusn
▶️
https://www.youtube.com/@ZikereKedusan
Audio
"" ስንክሳር - ሐምሌ ፯/7 ""


ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://www.tg-me.com/zikirekdusn
እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ ሐምሌ ቡሩክ፤ ወአመ ፯፦

በዓል ዐቢይ ወክቡር፥ ዘሥሉስ ቅዱስ (አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ)

አስተርአዮ እግዚአብሔር ለአብርሃም ርዕሰ አበው (ጊዜ ቀትር፥ ታሕተ ዕጸ ድርስ)
ወአብሰሮ ልደተ ይስሐቅ ንጹሕ
ሐይመተ ሣራ ቅድስት፥ ወአብርሃም አብ

ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ጊዮርጊስ ጻድቅ፥ መምህረ ጋስጫ፥ በላዔ መጻሕፍት፥ ወሊቀ ሊቃውንት (ጠቢብ ወማዕምር፥ ዓምደ ሃይማኖት)

✿ዐቢይ ወክቡር፥ አባ ሲኖዳ ጻድቅ፥ አርሲመትሪዳ (ርዕሰ ኲሎሙ ባሕታወውያን)

✿ዐቢይ ወክቡር፥ አግናጥዮስ ሐዋርያ፥ ሰማዕት ወሊቀ ጳጳሳት (ምጥው ለአንበሳ)

✿እንድርያስ ጻድቅ ወመምህር (ዘደብረ ሊባኖስ)

✿እኅተ ጴጥሮስ እምነ (ኢትዮጵያዊት)

✿መቃቢስ ወጊዮርጊስ ወአግራጥስ

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡

https://www.tg-me.com/zikirekdusn
2025/07/14 08:43:00
Back to Top
HTML Embed Code: