Telegram Web Link
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
🤭🤭

ለ7 ደቂቃ ከ17 ሰከንድ ብቻ የሚቆይ ፖስት
“በመካከላችሁ ሳለሁ ከኢየሱስ ክርስቶስ በቀር እርሱም እንደተሰቀለ ሌላ ነገር እንዳላውቅ ቆርጬ ነበርና።”
[1ኛ ቆሮንቶስ 2: 2]


በነገራችን ላይ አገልግሎት ማለት አገልጋዩ ያለውን እውቀት ለማሳየት ከሰሚዎቹ የመረዳት አቅም የራቀ ነገርን መናገር ማለት አይደለም.. እንዲያ ቢደረግ ማንም አይጠቀምም.. አስባችሁታል ቅዱስ ጳውሎስ በእውቀቱ ደረጃ ብቻ የሚሰብክ ቢሆን አልቆልን ነበር😁😁 ስለዛ እንደቦታው ነው መሆን ያለብን አለበለዚያ ብቻችንን ለንፋስ የምናወራ እንሆናለን

ጌታችንንም ካያችሁት ሲያስተምር በሰዎቹ ዙሪያ ያለውን እያጣቀሰ እነርሱ በሚገባቸው መልኩ ነበር.. የተወሳሰበ ነገር አታዩም..

ሰሚአኑ እየበሰለ ሲሄድ አልያም በበሰሉት ዘንድ ደግሞ ተለቅ እና ረቀቅ ስላለው ነገር ይወራል ነው..

@Apostolic_Answers
እኔኮ ተስፋ የቆረጥኩት.. የቦሌ መድኃኔዓለም አውደ ምህረት ላይ ከኔ ቀድሞ ደምረው ሲወጣ ነው😭😭
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ኧረ እነዚህ ሰዎች በአክሊለ እንዳያብዱ🙄🙄 በየሰዓቱ አካሉ..?? ሯ!
“የምንበላው ሥጋና ደም የማርያም ነው” አሉ አንዱ አባት.. ከዛ ጴንጤዎች ኡኡ እያሉ ነው.. እሺ አሁን እናንተ ኡኡ ያስባላችሁ ያ ሥጋና ደም የኢየሱስ ነው ለማለት ነው..?? እሱን ደግሞ አታምኑም ቅዱስ ቁርባን ለእናንተ ምሳሌ ብቻ ነው😁😁

ለማንኛውም ያ ሥጋና ደም የመለኮት ሥጋና ደም መለኮት የራሱ አድርጎታል..

የማርያም ሥጋና ደም ሲጀምር ያድናልም አንልም.. የሚያድነው የመለኮት ሥጋና ደም ነው..

እኛ ቢያንስ በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጳጳስን ሳይቀር እንመዝናለን.. ፕሮቴስታንቶች ግን በቃ እንደ ግሌ መረዳት እንደሆነ ልብ ይለዋል

@Apostolic_Answers
ያዝ እንግዲህ.. ባለፈው ኢየሱስ ለዓለም ሁሉ ቤዛ ነው በሚለው ላይ አሁን ደግሞ በቅዱስ ቁርባን ላይ ልንሄድባቸው ነው መሰለኝ ሎል

https://vm.tiktok.com/ZMBo9YANp/

This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
የቦሌ መድኃኔዓለም ሲከነክነኝ ጭራሽ የልደታ አውደ ምህረት ላይም ቀደምከኝ..??😭😭

እንኳን አደረሳችሁ ለማንኛውም ለወላዲተ አምላክ የልደት ቀን
ትናንት በሰራሁት ቪዲዮ ላይ አንዳንድ ፕሮቴስታንቶች ሲያለቅሱ አየሁ እና በተለይ “ሉተራኖች” እኛኮ በቅዱስ ቁርባን እናምናለን እና ጨፍልቀህ ፕሮቴስታንት ያልከን በጥላቻ ነው እያሉ ነው😁😁

ሲጀመር እዛው ቪዲዮው ላይ “በተለይ ጴንጤ” ብዬ ለይቻለሁ.. ስለዛ እናቱ ጥላው እንደሄደችበት ሕጻን የማልቀሻ ምክንያት ፈልጋችሁ ነው ምትለቅሱት ማለት ነው.. ምክንያቱም እንዳልኩትም እዛው ቪዲዮ ላይ “በተለይ ጴንጤ” ብዬ ለይቻለሁ😁😁

ሲቀጥል ደግሞ የእናንተን ስም እየለየን የግድ መጥራት አይጠበቅብንም.. ሃገሪቱ ጠቅላላ ከፕሮቴስታንት ውስጥ ጴንጤዎች አይደሉ እንዴ😁😁 በግል ቸርቾች ተጥለቅልቀህ ደግሞ ሌላ ሥራ ይሁንብኝ እንዴ የእናንተ የጥቂቶቹ..??

ለማንኛውም ከጴንጤዎች እና ከፕሮቴስታንቶች መጽሐፍ ቅዱስን በትክክል የተረዳው ማን ነው በሚለው ልግባ መሰለኝ ሎል😁😁
ፕሮቴስታንቶች ክርስቲያን ናቸው..??

አንድ ወንድም ዛሬ ምን አለኝ:- “በጥንት ቤተ ክርስቲያን በመናፍቃን የተጠመቁትን ዳግም ሳያጠምቁ የተቀበሉ ነበሩ እናም እነዛ መናፍቃን ራሱ ክርስቲያን ካልሆኑ እንዴት ጥምቀታቸው ተቀባይነት ኖረው..?? እንደው ዋናው ነገር የኒቂያውን እምነት ማመን ቢሆን ነው እንጂ..”

አከሲ..?? ሎል

ለምሳሌ አርዮሳውያንን ሳይቀር ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመለሱ በአንድ ወቅት ላይ ዳግም ሳያጠምቁ በቅብአ ሜሮን ይቀበሏቸው ነበር.. ይህ ማለት ግን አርዮሳውያን ክርስቲያኖች ናቸው ማለት ነው..?? ገና ከጅምሩስ የኒቂያውን አንቀጸ ሃይማኖት ስለተቀበሉ ነው ዳግም ያላጠመቋቸው..??😭😭 ወፍ።

ምንም እንኳን አርዮሳውያንን ያለ ዳግም ጥምቀት ቢቀበሏቸውም ግን ደግሞ አባታችን አትናቴዎስ "እኛም ክርስቲያን ነን" የሚሉትን አርዮሳውያንን ምን እንዳላቸው ላሳይህ..??

"ሁላችን በክርስቶስ ክርስቲያኖች ስንባል፤ መርቅያኖስ የምንፍቅና ትምሕርትን አነሳ ተወገዘም፤ መርቅያኖስን ያወገዘውን የተከተለ ክርስቲያን እንደሆነ ሲቀጥል ከመርቅያኖስ ጋር አብሮ የወጡት ግን ክርስቲያን መባላቸው ቀርቷል ይልቁንም መርቅያኖሳዊ(Marcionites) ይባላሉ እንጂ። ልክ እንዲሁ ሌሎች መናፍቃንም ስማቸውን ለተከታዮቻቸው ሰጥተዋል። እንዲሁ እስክንድሮስ(Alexander) አርዮስን ሲያወግዝ ከእስክንድሮስ ጋር የቀሩት በክርስቲያንነታቸው ሲቀጥሉ ከአርዮስ ጋር የተለዩት ግን የጌታችንን ስም ለእኛ በመተው እነሱ አርዮሳውያን(Arians) ይባላሉ"
[Against the Arians: Discourse 1, chap. 1: 3]

ክርስቲያን መባልንና አለመባልን ያገናኘው ከቤተ ክርስቲያን ውጪ ከመሆን እና ካለመሆን ጋር ነው ብራዘርዬ ሎል

@Apostolic_Answers
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ እኔን ሃጢአተኛውን ማረኝ

👇👇👇👇

ጌታ - ጌትነቱን ምንመሰክርበት

ኢየሱስ - ከስም ሁሉ በላይ ስሙን ምንጠራበት

ክርስቶስ - ኢየሱስ እርሱ ይጠበቅ የነበረው መሲሕ(ክርስቶስ) እንደሆነ ምንመሰክርበት

የሕያው እግዚአብሔር ልጅ - ኢየሱስ እርሱ ክርስቶስ ብቻ ሳይሆን የእግዚአብሔር የባህሪ ልጁ እንደሆነ ምንመሰክርበት

እኔን ሃጢአተኛውን - ሃጢአተኛ መሆናችንን አምነን ምንናዘዝበት

ማረኝ - ምህረት የሚቀዳው ከጌታ እንደሆነ አምነን ምህረትን የምንለምንበት

መልካም ውሎ.. ለጸሎት ካነሳሳችሁ በሚለው የተለቀቀ😁😁

@Apostolic_Answers
—————
ሰሞኑን ከፕሮቴስታንቶች የደረሰኝ ሁለት ትችት..??

https://vm.tiktok.com/ZMSJGk7Mn/

—-
“ከዝሙት ሽሹ” - [1ቆሮ 6:18]

የትኛውም ክርስቲያን ማግባት ካለበት ወይ ያገባል እንጂ በሌላ ነገር ብንደክም እንኳን ከተለያየ ሴት ጋር እየዘሞትን ግን ልንኖር አይገባም..

እውነቱን ለመናገር ይሄ አይመጥንምም.. የኢየሱስ ነን.. ስለዛ እንዲህ የምናደርግ በጊዜ በንስሐ እና ቅዱስ ቁርባን መመለስ ይኖርብናል..

አንዳንድ ልጅ ባለጌ ከሆነ “ቤተሰብ አሰዳቢ” ይባላል.. እኛ ደግሞ እግዚአብሔር አባታችንን እንዳናሰድብ በጣም ጥንቃቄ ይፈልጋል..

@Apostolic_Answers
ወላጆች ልጃቸውን በተሳካ ሁኔታ ያሳደጉ ሚመስላቸው ያው አሳድገው አስተምረው ምናምን ከዛ ሲመረቅ ነው😁😁

ግን ትልቁ ድል ልጅን ከቅዱስ ቁርባን ሳያርቁ የእግዚአብሔርን ቃል እያስተማሩ በመንፈሳዊ ሕይወቱ አሳድጎ ቅዱስ ልጅ ሲያደርግ ነው..

ለዘላለም የሚኖረው የዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሳይሆን የእግዚአብሔር መንግሥት ነው.. ስለዛ እሱ ላይ በጣም ይሠራ..

@Apostolic_Answers
አንዱ “ጊዮርጊስ ለአጃው/ለራሱ ጉዳይ ነው የተገዘገዘው ምን አገባኝ እኔ” እያለ በንዴት ሲደነፋ አየሁት.. ማለት ሌላው ቢቀር አሁን ይሄ እሱን ምን አናደደው..?? ጳውሎስ ለራሱ ነው የተሰየፈው ምን አገባኝ እያሉ እንደመደንፋት ማለት ነው ይሄ.. ቢያንስ እንደሱ መታመን አለብኝ አይባልም..??

ጋይስ ማርያምን በጣም ነው ሚሰለቸው ግን ሁሉም ነገር.. ብቻ ጌታ ይርዳን እንጂ በስመአብ..
አንድ ታዋቂ መምህር በየዋሕነት ለእመቤታችን ካለው ፍቅር የተነሳና ያው ሰዎች የጠፋባቸውን የእግዚአብሔርን ምሳሌ በጌታ በኩል ከማግኘታቸውም አንጻር በማለት እንደው እንዲህ አሉ:-

[ማርያም የጌታ ባሪያ አይደለችም.. ለትህትና ነው ራሷን “እነሆኝ የጌታ ባሪያ” ያለቸውም..]

ጋይስ ያው ግን ወላዲተ አምላክ እውነተኛ የእግዚአብሔር ባርያ ናት.. ለእርሷ ይህም ክብሯ ነው.. ጌታችን ራሱ ራሱን ዝቅ አድርጎ በሥጋ ስለመምጣቱ እንደዛ ተብሏል.. ብቻ ያው እንደዛ ነው..

@Apostolic_Answers
😆😆 ከክርስቲያን ኤዲተሮች ማንም አያመልጥም

https://vm.tiktok.com/ZMSRLeQuD/

———
እንዲህም ያለ ደግሞ ጥሩ አሳብ ያለው ፕሮቴስታንት አለ..

https://vm.tiktok.com/ZMSRhPLmn/

2025/07/01 16:02:54
Back to Top
HTML Embed Code: