Telegram Web Link
ንጉሱ ሲጠሩት መጣ በፈረሱ
ለራስ መኮንን ኢትዮጵያ ናት ነፍሱ!
ራስ መኮንን ወልደሚካኤል ጉግሳ የአፄ ሀይለ ስላሴ አባት በኢትዮጵያ ታሪክ ከታዩ ሩሩህ ፣ ብልህ ፣ አስተዋይ እና ታማኝ መሪ ነበሩ። በአደዋ ጦርነት ታላቅ ጀብድ የፈፀሙ የጦር መሪ ነበሩ።
#አደዋ

@Bookfor
@Bookfor
ወላይታም አለኝ እንደ ካኦ ጦና
ደፍረው በነኩኝ ላይ የሚሆን ፈተና!
ንጉስ ካኦ ጦና የወላይታን ጦር አስከትለው በአደዋ ድል ታላቅ ጀብድ የፈፀሙ ጀግና ናቸው። ብልሀት እንደ ጦና እንዲሉ ታሪክ አዋቂዎች። ኢትዮጵያ ከንጉስ ጦና ብልሀት ብብዙ እንደተጠቀመች ጳውሎስ ኞኞ "ሚኒሊክና ወላይታ" በሚል ባሰፈሩት ፅሑፍ ላይ ተገልጿል።
#አደዋ
#ክብር_ለጀግኖቻችን

@Bookfor
@Bookfor
ወላይታም አለኝ እንደ ካኦ ጦና
ደፍረው በነኩኝ ላይ የሚሆን ፈተና!
ንጉስ ካኦ ጦና የወላይታን ጦር አስከትለው በአደዋ ድል ታላቅ ጀብድ የፈፀሙ ጀግና ናቸው። ብልሀት እንደ ጦና እንዲሉ ታሪክ አዋቂዎች። ኢትዮጵያ ከንጉስ ጦና ብልሀት ብብዙ እንደተጠቀመች ጳውሎስ ኞኞ "ሚኒሊክና ወላይታ" በሚል ባሰፈሩት ፅሑፍ ላይ ተገልጿል።
#አደዋ
#ክብር_ለጀግኖቻችን
@Bookfor
@Bookfor
ቀና በል አትበሉት!!!
:
የዛለ መዳፉ
ሰውኛ ተስፋውን መሸከም ያቃተው
ማጣት ይሉት ህመም ቃሉ እያቃተተው
አሻግሮ ለማየት
ባልታደሉ አይኖቹ ጎንብሶ ቢማትር
ለካስ ቀን ሲያጎድል
በጠራራ ጠሀይ ይጨልማል ቀትር።

ከመረገም ይሁን ወይ ካለመታደል
ህሊና ሲደማ
ልብ እያለቀሰ ባልፈፀመው በደል
በየ ጥርጊያው ጥጋት
በየጎዳናው ዳር መሄጃው የጠፋው
ከሱነቱ ጎጆ
ይህ ስግብግብ አለም አርቆ የገፋው
እልፍ ሰው ይታያል በኑረት የከፋው።

ተመልከት ቀዬውን
ያዘኔታን ከንፈር ከሚመጠው እኩል
እልፍ አሳዛኝ አለ ባ'ሳዛኞች በኩል።

አጋድሏል ሚዛኑ
ቀን እየፈረደ ተ'በዳይ ይቀጣል
በተራማጅ እግሮች
የተሻለው ሲሄድ የባሰው ይመጣል
ምንም የሌለው ሰው የሌለውን ያጣል።

እንዲህ ናት ሀገሬ
በማለዳ ጀንበር የምትታይ መሽታ
ክርስቶስን አስራ በርባንን ምትፈታ።

እንዲህ ነው የኛ ቤት
አእላፉን ምስኪን ከኑሮ ሚያኳርፍ
በሁሉም ጎዳና
ተመፅዋች አይሄድም መፅዋች ነው የሚያልፍ።
@Bookfor
#ባለውለታ

"ሰውነት አልሞተም"

በዚህ ግዜ እኛ ኢትዮጵያውያን ብሎም በአለም ላይ የሚታየው የሚሰማው ሁሉ ሰው ሰውነቱን በቃ አጣ? ዓለም ለመኖር አስፈሪ እየሆነች ይሆን? የሚያስብሉ ሰው የሰው ስጋት እየሆነ የመጣበት አስከፊ ነገሮች ተከስተዋል እየተከሰቱም ሰብዓዊነትም እየተሸረሸረ የመጣበት ጊዜ ነው።
ነገር ግን አሁንም በጨለማ ውስጥ ብርሃን የሆኑ እና ለመኖር እንድንጓጓ የሚያደርጉን ጥቂት የማይባሉ ለነብሳቸው ያደሩ ልበ ብሩሃን መልካም ሰዎች ዛሬም አሉ።
👉ለአብነት ያህል ከሰሞኑ በልበ ብሩሁ ቢኒያም አማካኝነት ለተቋቋመው መቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል የማስፋፊያ ህንፃ ግንባታው ተጠናቆ ነገር ግን ያላለቁ የበር እና የመስኮት እንዲሁም አንዳንድ የፊኒሺንግ ስራዎች ለማጠናቀቅ የሚውል ገንዘብ አሰባስቤ ሳልጨርስ ከዚች ወንበር ንቅንቅ አልልም ብሎ ራሱን ለመልካምነት አሳልፎ የሰጠውን በበጎ ስራዎቹ የምናውቀው ኮሜድያን ዕሸቱ መለሰን መጥቀስ ይቻላል። እንደዚህ ያሉ መልካም ሰዎች ያብዛልን እያልን ፤
ለዚህ በጎ ዓላማ መሳካት ከጎኑ የሆኑ ቅን ልብ ያላቸው መልካም ሰዎች ሁሉ ክብር ይገባቸዋል።

👉የሀገር ባለውለታው ኮሜዲያን እሸቱ መለሰ ላደረከው፤እያደረክ ላለኸው እና ወደፊት ለምታደርገው ሁሉ ክብር ይገባሃል

"ሰውነት!ሰብዐዊነት አሁንም አልሞተም"
@Bookfor
Dear girls❤️

Never remove your clothes to prove your love.

Get a boy who can buy safety pads for you, not condoms. Get a boy who can take you to his home, not to the hotels. Get a boy who ask about your period pain, not for nudes. Get a boy who choosed your soul & heart, not the body.

Respect is one of the greatest expression of love. A real man never hurt a woman. She isn't just a housewife who cooks your meal & washes clothes. She is a homemaker who holds together the family & make sure that everything is as perfect as it can be once you get home. Respect for women is one of the greatest gift a man can show.

Be a real man & respect women.

Happy International Woman's Day!

@Bookfor
@Bookfor
ለአንድ ሴት በተለይ "ቆንጆ ሴት ነን" ብለን ለምናስብ ሴቶች ፥ አቅማችንን እንዳንጠቀም እስር ቤት የሚሆንብን፤ የራሳችን ቁንጅና ነው። የራሳችን ቆዳ የራሳችን እስር ቤት ነው።

በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ሴትነት እና ቁንጅና የሚባል የእስር ፍርግርጋችንን እያስዋብን ፥ ተሟሙቀን የወንዶችን ጭብጨባና አድናቆት እየጠበቅን እንድንኖር ሆነናል።

ማኅብረሰቡ አንዲትን ሴት "የብረት መዝጊያ" የሚሆን አማች የምትመጣ እንጂ ፥ የብረት መዝጊያ መሆን የምትችል አድርጎ አያስብም፤ ስለዚህ የነሱን የምኞት በር የሚዘጋ የብረት መዝጊያ ለማምጣት ፥ አንዲት ሴት ዓይኗን፤ አዕምሮዋን፤ ሳይሆን እግሯን እንድትከፍት ከህፃንነቷ ጀምሮ ሲያዘጋጃት ይኖራል።

እግር የተፈጠረበት የመጀመሪያ ዓላማው መራመድ ነው፤ ለሴት ልጅ ግን ከመራመድ በላይ እግር ውበት እንደሆነ እንድታስብ ፥ በስነ-ጽሁፍ፣ በፊልሙ፤ አዕምሮዋ ውስጥ ሲታጨቅባት ኖሯል።

ከመራመዷ በላይ የአረማመዷን እና የእግሯን ውበት ፥ እንድታስብ ስትሰበክ ኖራለች። ለዚህም ነው ከፊትሽ የተነጠፈውን እሾህም ይሁን ጠጠር ፥ ረግጠውና ዋጋ ከፍለው አዳሰቡበት ከሚራመዱ ሴቶች ይልቅ፤ ከየትም ባገኟት ሳንቲም በየውበት ሳሎኑ ተጎልተው ፥ እግራቸውን የጥፍር ቀለም ሲያስቀቡና ተረከዛቸውን ሲያስፈገፍጉ የሚውሉ ዘመነኞች የሚበዙት። እግራቸው ከለሰለሰ በኃላ ፥ አዝሎ የሚያሻግር ወንድ ሲጠብቁ ቁጭ ብለው ይኖራሉ።

ገጽ 182-183
(ከእለታት ግማሽ ቀን)
@Bookfor
@Bookfor
ከእርጋታውዋ ጋር በፍቅር ወድቄያለሁ ! ድምጿን እወደዋለሁ ። መቀራረባችን ባህርያችንን አሳስቦታል ።

በተደጋጋሚ ስንገናኝ ረጅም ሰዓት ተቃቅፈን ፤ ትከሻችንን ተነካክሰን ፤ እጆቼን ስማ ፂሜን በጣቶቿ አበላሽታ ነው ሰላምታችን፤

አረፍ ስንል ነው እንዴት ነሽ ? እንዴት አለህ ? የምንባባለው በዕይታችን ውስጥ መነፋፈቅ አለ ! በዕይታችን ውስጥ መፈላለግ አለ ! መሸነፋችንን ግን ማሳበቅ አንፈልግም ስንገናኝ ተፈጥሮ ሚዛን ይስታል መሰለኝ ሰዓቱ አይበረክትም።  ከሷ ጋ ስሆን ምቾት ይሰማኛል ። ከኔ ጋ ስትሆን ደስ እንደሚላት አውቃለሁ። ምን እንደተሰማኝ አልነገርኳትም ።

ለሁኔታዎች እድል መስጠት ፈልገናል ድልድዩን ስንደርስ እንሻገረዋለን አይነት ድፍረት ….. በነዚህ ሁኔታዎች ውስጥ ሰባት ወራት አለፉ፡፡  ባሉን የእረፍት ጊዜያት ሁሉ  መገናኘት ግድ ሆነ ካልሆነ ሁለታችንም መነጫነጭ ይታይብናል ግን ማመን አንፈልግም፤

ሁላችንም ድክመታችን ይለያይ የለ...

የተገናኘን ሰሞን የምንግባባ አይነት ሰዎች አንመስልም…. ዝምታ የምታበዛና እርጋታዋ ትዕግስት የሚያስጨርስ አይነት… ሴት ነች እሷ፤

እሷ ግልፅነት የህይወት መርኋ የሆነ። የማታወሳስብ ያየችውን ፣ያስተዋለችውን ቀለል አርጋ የምታጋራ አይነት ሴት ነች።

መላመድ ያሳስብ የለ....ማንነታችን እየተወራረሰ ነበር ።

ያገናኘን የአንድ ወቅት ስራ ነበር ስራውን ማዕከል አድርገን ዘለግ ያለ ጊዜ አብረን እናሳልፋለን.. ከስራው አረፍ ስንል ስለ ህይወት እናወራለን፡፡ ጠንከር ባሉ የተለያዩ ሀሳቦች ላይ ስንሟገት ላየን አንዳች የምንፈታው ችግር ከፊት ያለ ያስመስልብናል፡፡

ስብዕናዋ ደስ ይላል አዲስ አይነት ባህሪን የምታለማምድ አይነት ሰው ነች፡፡ የተገናኘንበት ስራ ተጠናቀቀ፡፡ አልፎ አልፎ መደዋወል እና ስለሰሞነኛ ጉዳይ መጠያየቅ ጀምረናል፡፡

ሁለታችንም ጋር መገናኘትን መፈለጋችን በብዙ መንገድ ያስታውቅ ነበር የምንደዋወልበት ድግግሞች ከሁለትና ከሶስት ጊዜ አለፈ፡፡ አንዴ ስንደዋወል የወሬያችን የቆይታ ጊዜ ከደቂቃዎች ለሰዓት እየተጠጋ ሆነ…. ሳይደዋወሉ መዋል የማይታሰብ ነው፡፡ ጠዋት በሷ ድምፅ መቀስቀስ ማታ በኔ ድምፅ መተኛት የተፈጥሮ ህግ  እስኪመስል….

በእንዲ ያለ ስሜት ውስጥ ሆኖ መገናኘት ያስፈራል..

በተደጋጋሚ እየተገናኘን እናወጋለን፡፡ የምንወዳቸው ቦታዎች አብረን እንሄዳለን በስራ እየተደጋገፍን የአንዳችንን ሸክም አንዳችን እናቀላለን፡፡ በጣም እየተቀራረብን እየተላመድን ሆነ... እንደ ሱስ አይነት ነገር  ...

አንዳንዴ እንዳናጣቸው የምንፈራቸው ሰዎች አሉ ሁሉን በአንድ የያዙ ልክ ጓደኛ ፤ቤተሰብ፤ ሚስጥረኛ ባልደረባ ፍቅረኛ አይነት የሆኑ … ግን ደግሞ ሁሉንም በአንዴ ማድረግም መፈለግም ይከብዳል፡፡ ከነዚህ ሁሉ የአንዱን መስመር ለመምረጥ ያለ ትግል …… ፈታኝ ጉዳይ ነው፡፡

ግን አሁንም ለግንኙነታችን ስምም፤ መልክም፤ ቅርፅም ፤ አልሰጠነውም እንዲሁ መዋደድ ብቻ መራራቅን መፍራት ብቻ፤

የኔ ሴት እሷ ነበረች ... ያሳለፍነው የህይወት ምልልስ ያቀራረበን የልቤ ሰው…

@Bookfor
@Bookfor
በዜማ ማንሰፍሰፍ፤ አበበ ብርሃኔ
(ዮናስ ታምሩ ገብሬ)
‹‹ሰደድ ነው አንገቷ፤
እንደ ዥንጉርጉሩ፣ እንደ መቀነቷ፤ [አበበ ብርሃኔ]

የኢትዮጵያ ሙዚቃ ወንዴው ባሕርይ የተጫነው እንዲሆን ዕሙን ነው፤ በሀገራችን የተቀነቀኑ የበርካታ ዘፈኖች ግጥም እና ዜማቸው ወንዳዊ ጠባይ በጉልህ የሚንጸባረቅባቸው ናቸው። ለአብነት እንኳን ከተባእት ጾታ ድግምግሞሻዊ መገለጫዎች መካከል፡- መደለቅ፣ መርገጥ፣ መጋለብ፣ ማካለብ እና ሌሎችም ተጠቃሾች ናቸው፤ የተጠቀሱ ባሕርያት በሙዚቃችን ገላ ውስጥ ጥላ ጥለው ከርመዋል። አሁን፣ አሁን በመጠኑም ቢሆን ሙዚቃችን ሴቴአዊነትን እየተላበሰ መጥቷል - ከ1980-81 ዓ.ም. ወዲህ፤ ከመደለቅ፣ ከመርገጥ እና ከመጋለብ አልፎ ወደ ሴቴአዊ መንሰፍሰፍ እያደላ መጣ ሙዚቃችን - በአበበ መለሠ። ስፓኛዊው ሰዓሊ ፐብሎ ፒካሶ ጥበብ ከውስጥ ስትመነጭ ጣዕመኛ ነች የሚላት ይትባሃል አለቺው፤ አቤም እንዲያ ነው - በሥራዎቹ የውስጣችንን ድብቅ ሚስጥር ጫር አድርጎ ያልፋል፤ በእንስፍስፍ ስልት የተብሰለሰለ ውስጣችንን ጎብኝቶ ለሌላ ተመስጦ አምነሽንሾን ሸርተት ይላል፤ ማሳተፍ ጠባዩ ሆነ ማለት ነው።

የሴት ሥነ-ልቡና የዘለቀው ሙዚቀኛ ነው አቤ፤ ወንድ ሆኖ ሳለ በሴት ይትባሃል የማንሰፍሰፍ ክኅሎት ያደለው ደራሲ። የሚደርሳቸው የዘፈን ዜማዎች ብርክ የማድረግና የማራድ ጉልበት አላቸው። ኩልል ያለ የቆለኛ ድምጽ ዓይነት ዜማዎች እና ስርቅርቅ ስልቶች በድርሰቶቹ ገላ ውስጥ ይስተዋላሉ። ከስምንት መቶ (800) በላይ የዜማ ድርሰቶችን ጀባ ብሏል። አመለ ሸጋ እና ተጫዋች ነው፤ ከዘፈን ዜማ አልፎ ክራር እና ኪቦርድ በወጉ ይጫወታል። 1978 ዓ.ም. መገባደጃ አካባቢ ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ ተከተተ - ከፋሲለደስ የኪነት ቡድን ጋር ለወጣቶች ፌስቲቫል ወደ ኮሪያ ሊዘምት። አልሆነም ነበር ታዲያ፤ በአዲስ አበባ ቲያትር ቤቶች ሲያንዣብብ እያዩ ማንያዘዋል (የ‹‹ዕድሌ ጠማማ›› ዘፈን አቀንቃኝ) ጋር ይገናኛሉ። የ‹‹ልቤ ገራገሩ››ን ዘፈን ግጥም በአንድ ምሽት ደርሶ ጀባ ካለው በኋላ ወደ ጎንደር ይተማል - ብዙም ሳይቆይ ወደ አዲስ አበባ ተመለሰ…

…ከግጥም እና ዜማ ደራሲው ከጸጋዬ ደቦጭ ጋር ለጸጋዬ እሸት፣ ለኬኔዲ መንገሻ እና ለአሠፉ ደባልቄ በሠራቸው ሥራዎች ተወዳጅነትን አተረፈ። አቤ በግጥምና ዜማ ድርሰቶቹ ማንሰፍሰፍ ያውቅበታል፤ ወንድ ደራሲ የሴት ዓይነት ማራድን በሙዚቃ ሥራዎቹ…

…የእናት ዓይነት የአንጀት መንሰፍሰፍ እና ተብሰልስሎት በዋናነት በዜማ ድርሰቶቹ ውስጥ ይንጸባረቃሉ፤ አዚሞ ማንሰፍሰፍን ተክኖበታል። እውስጥ የሚቀሩ ዜማዎችን ለበርካታ ድምጻዊያን አበርክቷል፤ ለማሳያ ያህል፡-

1. ለጌታቸው ካሳ፡- ‹‹ቀና ብዬ ሳየው›› (ዜማ) (ግጥም ጸጋዬ ደቦጭ)
2. ለኤፍሬም ታምሩ፡- ‹‹ቢልልኝ›› (ዜማ)
3. ለሂሩት በቀለ፡- ‹‹የእኔ ዓለም››፣ ‹‹ጠላኝ እንዳልለው›› (ዜማ)
4. ለባለቤቱ/ፍቅርአዲስ፡- ‹‹እርሳኝ›› (ዜማ)፣ ‹‹አልገባኝም›› (ግጥምና ዜማ)፣ ‹‹ዝም እላለሁ›› (ዜማ) - ካሴት 1984 ዓ.ም.፣ ‹‹ላባብለው›› 1989፣ ‹‹ሳብ በለው›› 1993 ካሴቶች
5. ለአሠፉ ደባልቄ፡- ‹‹የሆዴን›› (ግጥምና ዜማ)
6. ለሰርጉዓለም ተገኝ፡- ‹‹ሳላያት አመሸሁ›› (ዜማ)
7. ለየሺእመቤት ዱባለ፡- ‹‹ለዚህ በቃሁ››፣ ‹‹ትዝ አለኝ›› (ዜማ)
8. ለጸጋዬ እሸቱ፡- ‹‹ሆዴ ክፉ ዕዳዬ›› (ዜማ)፣ ‹‹መሸ›› (ግጥምና ዜማ)፣ ‹‹ያየ አለ›› (ዜማ)፣ ‹‹ተከለከለ አሉ›› (ዜማ)
9. ለማሐሙድ አሕመድ፡- ‹‹ስንቱን አሳለፍኩት›› (ዜማ)
10. ለኬኔዲ መንጋሻ፡- ‹‹ፋንታዬ›› ካሴት - ‹‹ፋንታዬ›› ‹‹አንቺ ዓለም›› ‹‹እንግባ ሀገራችን/ከየሺእመቤት ጋር›› (ግጥምና ዜማ)
11. ለቴዎድሮስ ታደሠ እና አሠፉ ደባልቄ፡- ‹‹ላጉርስሽ›› (ዜማ)
12. ለአበበ ተካ፡- ‹‹ወፍዬ››፣ ‹‹ሰው ጥሩ/ማን አላት ሰው ሐገር›› - ካሴት ሙሉውን ዜማ (ግጥሙ የአያ ሙሌ - ሙሉጌታ ተስፋዬ ነው)
13. ለሐመልማል አባተ፡- ‹‹ይዳኘኝ ያየ›› (ዜማ)
14. ለጎሳዬ ተስፋዬ፡- ‹‹የሐመሯ›› (ዜማ)
15. ለሞኒካ ሲሳይ፡- ‹‹ቀኑ አጠረ›› (ዜማ)
16. ለይርዳው ጤናው፡- ‹‹ላፍ አርጋት›› ሙሉ ካሴት (ሶስና ታደሠ ደግሞ ሙሉ ግጥም)
17. ለጸደኒያ ገ/ማርቆስ ሙሉ ካሴት፡- ከ‹‹ላፍ አርጋት›› ካሴት ዕኩል (ሶስና ታደሠ ደግሞ ሙሉ ግጥም)
18. ለይሁኔ በላይ፡- ‹‹የሰው ሐገር›› (ግጥምና ዜማ)
19. አሁንም ለባለቤቱ፡- ‹‹ምስክር›› - ካሴት፤ ይልማ ገ/አብ እና ቢኒአሚር አሕመድ ታክለውበታል
20. ለዳዊት ጽጌ፡- ‹‹እትቱ›› (ዜማ) - ግጥም፡- ናትናኤል ግርማቸው
21. ለተመስገን ተስፋዬ፡- ‹‹ሳቢዬ›› (ዜማ) - ግጥም፡- ናትናኤል ግርማቸው

እና ሌሎች ተጠቃሾች ናቸው። ለዛሬ የሰርጉዓለም ተገኝን

‹‹ሳላያት አመሸሁ፣ ሳላያት፤
እመጣለሁ እያልኩ - እየዋሸሁ፤
ነገር አበላሸሁ - እያመሸሁ፤›› ተጋበዙልኝ።

አቤ ዕድሜና ጤና ይስጥህ፤ አመሰግናለሁ!
@Bookfor
@Bookfor
ታላቁ ሰው አረፉ !

ለሃገር ትልቅ ባለ ውለታ የነበሩት ታዋቂው የአካባቢ ጉዳይ ሳይንቲስት ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ።

ዶክተር ተወልደ ለሃገራቸው ሲደክሙ ከኖሩ ታላላቅ ሰዎች አንዱ ነበሩ ።

ደራሲ ዘነበ ወላ "የምድራችን ጀግና" በሚለው መፅሃፉ የዶክተር ተወልደን ንግግር እንዲህ ሲል አስፍሮታል ።

“ሰው ሁሉ ሰው ነው። ሰው ሁሉ የትም ይፈጠር እኩል ነው የሚለውን እምነት … በተጨባጭ እያሳዩ ነው ወላጆቼ ያሳደጉኝ።

አሁን ባለሁበት ሁኔታ ሕይወቴን ሳስበውና የተጓዝኩበትን መንገድ ዞሬ ሳየው የቤተሰቦቼ አመራር የምወደውና የምቀበለው ነው። የሰው ልጆች እምነት እምነቴ ነው። የሕዝቦች ሁሉ ተፈጥሮአዊ ዕውቀትን የገበየሁት በዚህ ዓይነት መንገድ ነው። ማንንም ሰው በእኔ ሕይወት ውስጥ እምነቱን አከብርለታለሁ። እኔም እንዲሁ አመለካከቴን እንዲያከብሩልኝ እፈልጋለሁ። በዚህም አመለካከት ዓለምን ሀገሬ አድርጌያለሁ። ”
ዶ/ር ተወልደ ብርሃን ገብረ እግዚአብሔር

ነፍስዎ በሰላም ትረፍ🙏

@Bookfor
@Bookfor
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ ቤተሰቦች እንኳን ለታላቁ የረመዳን ፆም በሰላም አደረሳችሁ።

@Bookfor
ዒላማህን ምታ
__________________
ውሃ በተሞላ ድስት አንዲት እንቁራሪት ብንጨምር እና ከዛም ውሃውን ማፍላት ብንጀምር ፤ ውሃው እየፈላ በሄደ ቁጥር እንቁራሪቷም የሰውነት ሙቀቷን ማስተካከል ትጀምራለች።

የውሃው ሙቀት ከፍተኛ እየሆነ ሲሄድ እሷም የሰውነቷን ሙቀት በዛው ልክ ማስተካከሉን ትቀጥላለች። የውሃው ሙቀት ጨምሮ የመፍላት ደረጃ (boiling point) ላይ ሲደርስ ግን ማስተካከል ማትችልበት ደረጃ ስለሚደርስ እራሷን ለማዳን ከድስቱ ዘላ ለመውጣት ትፈልጋለች ፤ ትሞክራለችም ፤ ግን ዘላ መውጣት አቅም አይኖራትም አትችልም። ምክንያቱም ያላትን አቅም ሁሉ ሙቀቷን በማስተካከል የውሃውን ቃጠሎ ለመከላከልና ለመላመድ ባደረገችው ተጋድሎ ጨርሳዋለችና ወድያው ትሞታለች፡፡

እንቁራሪቷን ምን ገደላት ???

አብዛኞቻቸችን የፈላ ውሃ እንል ይሆናል ፤ እውነታው ግን ይህ አይደለም። እንቁራሪቷን የገደላት የፈላው ውሃ ሳይሆን መች መዝለል እንዳለባት የመወሰን እቅም ማጣቷ ነው።

አብዛኞቻችን ከሰዎችም ይሁን ከነገሮች ጋር ያለንን ነገር ለማስተካከልና ለመላመድ እንሞክር ይሆናል፤ ግን እስከ መች ማስተካከል እንዳለብንና መች መወሰን እንዳለብን ማውቅ ይሳነናል።

አንዳንዴ ነገሮችን እንለምዳቸውና ለኛ የማይጎዱ መስለው ይታዩናል፤ በመጨረሻው ቅፅበት ግን እንዳለመድናቸው ቢገባንም ማመልጥና መውጣት የማይቻለን ሰአት ይሆናል።

በጥፋት/ወንጀል መንገድ ውሰጥም ስንሆን እንዲሁ ነው፤ ትንሹን ወንጀል እንለምደዋለን የሚጎዳን አይመስለንም፤ ደስታ ውስጥ ያለን ይመስለናል፤ ደስታው ሙቀት ይፈጥርልናል፡፡

ሙቀቱ ወደ እሳት የተቀየረ ጊዜ ግን ፍፃሜው ግልፅ ነው፡፡ ከሙቀቱ መውጣት ካልቻልን ከእሳት እንደማንወጣ ግልፅ ነው። እናም ለውሳኔ አንዘግይ !!!

ምንጭ | ከመጻሕፍት ዓለም ገጽ
sometimes later became never! አንዳድ ግዜ ቦሀላ ወይም ነገ መቼም ላይሆን ይችላል!
ብዙ የሰው ልጅ በኪሱና በባንክ አካውንቱ ካለው ገንዘብ ምን ያክል እንደቀረው ያውቃል ነገር ግን ከህይወት አካውንቱ የቀረውን ግዜ ማንም አያቅም፡፡ ለዚህም ነው መልካም ትሩፋቶችን ለመተው ቀጠሮ መስጠት የሌለብን ይቅር ማለት ካለብን ዛሬ እንባባል ፣ መርዳት ካሰብን ዛሬ እናድርገው ፣ ሰውን መውደድም ዛሬ ላይ ሆኖ ነው፡፡ ይህንን ስናረግ ብቻ ነው ከጸጸት የምንድነው አለበለዛ የቢሆንስ ኖሮ እስረኞች እንሆናል፡፡

መባ

@Bookfor
@Bookfor
የደራሲ እንዳለ ጌታ ከበደ (ዶ/ር) አዲሱ መፅሐፍ ለገበያ ቀርቧል።

እስረኞቹ
@Bookfor
@Bookfor
እባክሽ ፥

በትካሻዬ በኩል ነይ ፥
ልብ የማይችልሽ ሸክም ነሽና.....

-

ቴዎድሮስ ካሳ 🤎
@Bookfor
2024/05/17 18:58:05
Back to Top
HTML Embed Code: