Telegram Web Link
የደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ መሐል ሜዳ ካምፓስ የ2018 ዓመት መደበኛ ተማሪዎች ለመቀበል ሙሉ ዝግጅት መጨረሱን አስታወቀ::

የደብረ ብርሐን ዩንቨርስቲ የመሐል ሜዳ ካምፓስ የ 2018 ዓመት የመደበኛ ተማሪዎችን ለመቀበል ሙሉ ዝግጅቱን መጨረሱን የካምፓሱ ማኔጂንግ ዳሬክተር አቶ ሰለሞን ገሰሰ ለዲጂታል ሚዲያችን ገልፀዋል::

በካምፓሱ ቅጥር ግቢ ተገኝተን እንደዘገብነው በ 2017 የትምህርት ዘመን : የሪሜዲያል ተማሪዎችን በመቀበል የትምህርት ዘመኑን የጀመረው ካምፓሱ ፣ ከመጀመሪያው የተማሪዎች የመማር ማስተማር ሂደት በርካታ ልምዶችን መውሰዱን ማኔጂንግ ዳሬክተሩ ገልፀዋል::

በ 2018 የተማሪዎች ቅበላን ለማድረግ በየትምህርት ዘርፋ እና በሌሎች የትብብር ኮሚቴዎችን በማቋቋም ሰፊ ስራ መሰራቱን አሳውቀው ፤ በተለይም ቅጥር ግቢውን ለተማሪዎች ሳቢ እና ማራኪ ለማድረግ በክረምቱ በርካታ ሀገር በቀል ችግኞችን በመትከልና በግቢው ባሉ የዶርሚታሪ እና የመማሪያ ክፍሎችን በማስተካከል ሰፊ ስራ ተሰርቷል ብለዋል::

በተለይም የግቢው የውበት ስራ እንደተጠበቀ ሆኖ ፣ ለግቢው የውስጥ ገቢ የሚያስገኙ ለግንባታ የማይውሉ መሬቶችን ለአካባቢው ማህበረሰብ በኪራይ ጨረታ በመስጠት የካምፓሱ የማህበራዊ ዘርፍ ግዴታዎችን ለመወጣት ጥረት ተደርጓል ብለዋል::

ማኔጂንግ ዳሬክተሩም በገለፃቸው እንደተናገሩት በ 2018 የአዲስና የነባር ተማሪዎችን ለመቀበል የነበሩትን ችግሮች ከዋናው የደብረ ብርሐን ዩኒቨርስቲ ግቢ አስተዳደር አካላት ጋር በመነጋገር የቤተ - መፅሐፍት ፣ የመመገቢያ ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ ግንባታ ፣ የመፀዳጃ ቤትና ሌሎች ተያያዥ የተማሪዎች መሰረታዊ አስፈላጊ ሁኔታዎችን ፈትተን ተማሪዎቻችንን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን ብለዋል::

@DBU11
@DBU111
🤔3😢3🤬1
በደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል የአለም የህሙማን ደህንነት ቀን ተከበረ

-“የታካሚዎች ደህንነት ከውልደት” በሚል መሪ ቃል መስከረም 9 ቀን 2018 ዓ.ም የአለም የህሙማን ደህንነት ቀን በዩኒቨርሲቲው አስራት ወልደየስ ጤና ሳይንስ ካምፓስ ሀኪም ግዛው ሆስፒታል ለመጀመሪያ ጊዜ ተከበረ።

- በበዓሉ ላይ የከተማው ም/ከንቲባ እና የሆስፒታሉ ቦርድ አባል አቶ ወርቃለማሁ ኮስትሬ በንግግራቸው የታካሚዎች ደህንነት ሊያደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን (የመድሃኒት ስህተት፣ ኢንፌክሽን፣ መውደቅ፣ የተሳሳተ መለያ መጠቀም፣ ያልተጠበቀ ደም መውሰድ ወዘተ) በማስወገድ የታካሚዎችን ደህንነት ማረጋገጥ እንዳለበት ጠቅሰዋል።

- ዶ/ር ዘመድ ገለታ ይህ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የጉዳት አሰራሮችን ማስወገድ ላይ የተሰማራ መሆኑን ገልጸዋል።

- ዶ/ር ቴዎድሮስ ክፍለዮሐንስ ደግሞ የታካሚ ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ መሆኑን እና ታካሚዎች በትክክለኛ ሰዓት በትክክለኛ መመሪያ መታከም አስፈላጊ መሆኑን አሳስበዋል።

- በመድረኩ ላይ የተሰጠ ምስክርነት ውስጥ አቶ ሳሙኤል ጌታቸው ከ2 ዓመት በፊት በ1 ኪ.ግ ክብደት የተወለደችው ልጃቸው በሆስፒታሉ የተሻለ ክብካቤ ተቀብላ አሁን በጤና መሆኗን አስረው ምስጋና አቀረቡ።

- በመጨረሻ የታካሚ ደህንነት መሠረት፣ የIPC ተግባር በአዲስ የተወለዱ ሕፃናት ሞት ላይ ያለው ተፅዕኖ እና የአዲስ የተወለዱ ህፃናት እንክብካቤ ላይ የተዘጋጀ ውይይት ተካሂዷል።

- ከበዓሉ በተጨማሪ ሆስፒታሉ የጥራት ማሻሻያ ትግበራዎችንና የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎችን እየተካሄዱ መሆናቸውን አሳውቋል።

@DBU11
@DBU111
🤔1
የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ
@DBU11
@DBU11
የደብረ ብርሀን ዩኒቨርሲቲ መሀል ሜዳ ካምፖስ የባቄላ ፣የምስርና የስንዴ ሰብልን
ከ10 ሄክታር በላይ በሆነ መሬት እያመረተ ይገኛል ።

የሀገራችን አንዳንድ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ፍጆታ ሰብል ፍላጎታቸውን ለሟሟላት በራስ አቅም የተለያዩ ሰብሎችን እንደሚያመርቱ ይታወቃል ።



@DBU11
@DBU11
👏13👌5🤔4🤬4😢2
2025/10/24 11:33:48
Back to Top
HTML Embed Code: