Telegram Web Link
የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አዲሱን ሞዴል ትምህርት ቤት ጎበኙ

ጥቅምት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. የድሬዳዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሱልጣን አልይ በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በቅርቡ ሥራ የጀመረውን የሁለተኛ ደረጃ ሞዴል ትምህርት ቤት ዛሬ ጉብኝት አደረጉ።

ይህ በዓይነቱ ልዩ የሆነው ሞዴል ትምህርት ቤት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እና በአስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ትብብር የተቋቋመ ሲሆን በከተማዋ የትምህርት ጥራት ማሻሻያ ጉዞ ላይ አዲስ ምዕራፍ ይከፍታል ተብሎ ከፍተኛ ተስፋ ተጥሎበታል።

ኃላፊው በቆይታቸው ወቅት የመማሪያ ክፍሎችን ተዘዋውረው በመመልከት የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚከናወንበትን ሁኔታ በቅርበት ተከታትለዋል። ከዚህም ባሻገር ከተማሪዎች ጋር በቀጥታ በመገናኘት የማበረታቻ መልዕክት አስተላልፈዋል።

አቶ ሱልጣን ለተማሪዎቹ ባደረጉት ንግግር ትምህርት ቤቱ በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ መገኘቱ በራሱ ትልቅና ልዩ ዕድል መሆኑን ገልጸዋል። "ይህንን ታሪካዊ ዕድል በአግባቡ በመጠቀም ጊዜያችሁን ለትምህርት ብቻ በማዋልና በትጋት በማጥናት ለውጤት መብቃት አለባችሁ" ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
6👍5🥰2🤣1
2025/10/21 16:44:28
Back to Top
HTML Embed Code: