እንደ እመቤታችን ይህ ዓለም ያልተገባው ማን ነው? የእርሷ ስደት የሚጀምረው ገና በእናቷ ማኅጸን ሳለች ነው። ከተወለደችም በኋላ ሰይጣን ዕረፍት አልሰጣትም። ክፉ መንፈስ ባደረባቸው አይሁድ ምክንያት ብዙ መከራ ተቀብላለች። ከወለደችው የበኩር ልጇ የተነሣ እንደ ሰይፍ የሚወጉ ብዙ የልብ ኃዘኖች ደርሰውባታል። ልጇ የተሰደባቸው ስድቦች በላይዋ ወድቀዋል። በጅራፍ መገረፉ፣ በዘንግ መመታቱ፣ በጦር መወጋቱ የእናትነት አንጀቷን እንደ እሳት አቃጥለዉታል። የማዳን ሥራውን ፈጽሞ ከዐረገ በኋላም የትንሣኤው ጠላት የነበሩት አይሁድ የትንሣኤን እናት ድንግልን አሳድደዋታል። ይህች ዓለም ለአንዲት ደቂቃ እንኳን ለእመቤታችን ተገብታት አታውቅም ነበር።
ስለዚህ ከምድራዊቷ ወደ ሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም ሊያሸጋግራት፣ ከክፉው ወደ መልካሙ ዓለም ሊጠራት ልጇ በታላቅ ልዕልና ወደ እርሷ ወረደ። ጌታ ወደ ማኅጸኗ እቅፍ በገባ ጊዜ "ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች። መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች። የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና" ስትል እንዳመሰገነችው፣ ዳግመኛም እናቲቱ ወደ ልጇ እቅፍ በገባች ጊዜ በዚህ ቃል መልሳ አመስግናዋለች።
እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሰን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
ስለዚህ ከምድራዊቷ ወደ ሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም ሊያሸጋግራት፣ ከክፉው ወደ መልካሙ ዓለም ሊጠራት ልጇ በታላቅ ልዕልና ወደ እርሷ ወረደ። ጌታ ወደ ማኅጸኗ እቅፍ በገባ ጊዜ "ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች። መንፈሴም በአምላኬ በመድኃኒቴ ሐሴት ታደርጋለች። የባሪያይቱን ውርደት ተመልክቶአልና" ስትል እንዳመሰገነችው፣ ዳግመኛም እናቲቱ ወደ ልጇ እቅፍ በገባች ጊዜ በዚህ ቃል መልሳ አመስግናዋለች።
እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሰን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
https://www.tg-me.com/Dnabel
“በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ። ጌታ እግዚአብሔር የዘላለም አምባ ነውና ለዘላለም በእግዚአብሔር ታመኑ”
ኢሳ 26:3-4
ኢሳ 26:3-4
ዝምታ ራሳችንን የምናይበት ጥሩ መጽሔት(መስታወት) ነው። አብዛኛውን ሰዓት በወሬ ተጠምዶ የሚውል ሰው ራሱን የሚመለከትበት እድል አይኖረውም። በሌሎች ኃጢአት ሲፈርድ፣ ሲተችና ሲያማ ስለሚውል የራሱን ስህተትና ውድቀት ለማወቅ ይቸገራል። ቀኑን ሙሉ እንዲሁ ሲያወራ የሚውል ሰው የሚያሳዝነው ዝም አለማለቱ ብቻ ሳይሆን የሚጠቅም ነገር የማይናገር መሆኑም ጭምር ነው። ነገር ግን ማር ይስሐቅ እንደሚለው "አንድ ሰው ከሰዎች ጋር ብዙ ማውራት ባቆመ ጊዜ ወደ ራሱ ይመለሳል። በእግዚአብሔርም ፊት ምግባሩን ማቅናት ይጀምራል"
የሥጋ አንደበታችንን መቆጣጠርና ዝም ማስባል ስንችል የነፍስ ጆሮአችን ንቁህ መሆን ይጀምራል። ስለዚህም ነፍሳችን ሳይሰለች ከልባችን ደጅ ቆሞ የሚያንኳኳውን የመልካሙን እረኛ ድምጽ ትሰማለች። ደጇንም ከፍታ ታስገባዋለች። ከእርሱም ጋር ለእራት ትሰየማለች።(ራእይ 3፥20) በእውነት ይህ እንደ ምን ያለ መታደል ነው? ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር "የዝምተኛ ሰው ጆሮ የእግዚአብሔርን ድንቆች ትሰማለች" ያለው ለዚህ ይሆን?!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
የሥጋ አንደበታችንን መቆጣጠርና ዝም ማስባል ስንችል የነፍስ ጆሮአችን ንቁህ መሆን ይጀምራል። ስለዚህም ነፍሳችን ሳይሰለች ከልባችን ደጅ ቆሞ የሚያንኳኳውን የመልካሙን እረኛ ድምጽ ትሰማለች። ደጇንም ከፍታ ታስገባዋለች። ከእርሱም ጋር ለእራት ትሰየማለች።(ራእይ 3፥20) በእውነት ይህ እንደ ምን ያለ መታደል ነው? ቅዱስ ዮሐንስ ሐጺር "የዝምተኛ ሰው ጆሮ የእግዚአብሔርን ድንቆች ትሰማለች" ያለው ለዚህ ይሆን?!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ብዙ ሰው "ያሰብኹት ሁሉ ምንም ሊሳካልኝ አልቻለም" እያለ ያጉረመርማል፤ "እግዚአብሔርማ እኔን ሳይተወኝ አልቀረም!" እያለ ፈጣሪውን ያማርራል። "ይሰጠኛል" ሳይሆን "አገኘዋለሁ" ብሎ ይጀምርና ሳይሆን ሲቀር በእጁ የነበረውን የነጠቀው ያህል አምላኩ ላይ ያለቅሳል። ስታቅድ ያላስታወስከውን አምላክ ያቀድከው ሲፈርስ ስሙን እየጠራህ ስለምን ትወቅሰዋለህ? በሕይወትህ መቼ ቦታ ሰጠኸው? እንደ ፈቃዴ ካልሆነ አልህ እንጂ መቼ "እንደ ፈቃድህ ይሁን" ብለህ ጸለይህ? ባላማከርከው ለምን ተከሳሽ ታደርገዋለህ?
ልሥራ ብለህ በተነሣህበትም ቀን እንዲሁ በግዴለሽነት ስሙን ጠርተህ እንደ ሆነም ራስህን መርምር? በትክክል ጸልየህና በመንገድህ ሁሉ ይመራህ ዘንድ ፈቅደህ ከጀመርህ ግን ግድ የለም እረኛህን እመነው። አንተ እንደ ሎጥ ከመረጥኸው እና ለጊዜው የገነት አምሳል ሆኖ ከሚታይህ ነገር ግን እግዚአብሔር ከማይከብርበት ከለምለሙ ሰዶምና ገሞራ ይልቅ፣ አሁን ብዙም ለአይን የማይስበው በኋላ ግን ወተትና ማር የሚያፈሰው ለልጅ ልጆችህም ርስት የሚሆነው እግዚአብሔር የሚሰጥህ ከነአን ይሻልሃል።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ልሥራ ብለህ በተነሣህበትም ቀን እንዲሁ በግዴለሽነት ስሙን ጠርተህ እንደ ሆነም ራስህን መርምር? በትክክል ጸልየህና በመንገድህ ሁሉ ይመራህ ዘንድ ፈቅደህ ከጀመርህ ግን ግድ የለም እረኛህን እመነው። አንተ እንደ ሎጥ ከመረጥኸው እና ለጊዜው የገነት አምሳል ሆኖ ከሚታይህ ነገር ግን እግዚአብሔር ከማይከብርበት ከለምለሙ ሰዶምና ገሞራ ይልቅ፣ አሁን ብዙም ለአይን የማይስበው በኋላ ግን ወተትና ማር የሚያፈሰው ለልጅ ልጆችህም ርስት የሚሆነው እግዚአብሔር የሚሰጥህ ከነአን ይሻልሃል።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ኃጢአት ጸሎት የማቋረጥ ውጤት ነው። እውነተኛ ጸሎት ኃጢአትን የማቆም ምልክት ነው። ሰው ኃጢአትን ልምዱ ካላደረገ በቀር እየጸለየ የሚበድል፣ ከአምላኩ ጋር እየተነጋገረ የሚያምጽ የለም። አዳም እጸ በለስን የቆረጠው ከአምላኩ ጋር የነበረውን ንግግር (ጸሎቱን) በማቋረጡ ነው። ይኸውም አዳምን ጠርቶ "ወዴት ነህ?" ባለው በፈላጊው ድምጽ ተረጋግጧል።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
https://www.tg-me.com/Dnabel
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
https://www.tg-me.com/Dnabel
+++ ልሸፈንላችሁ? +++
ሙሴ ከሲና ተራራ ወርዶ ከሕዝቡ ጋር ሲገናኝ የፊቱን ማንጸባረቅ አይተው "ተሸፈንልን" ያሉት ሕዝቡ ናቸው። እርሱ "ከእግዚአብሔር ጋር ስነጋገር ቆይቼ እኮ አሁን መውረዴ ነው? ምነው የፊቴ ብርሃን አስቸገራችሁ? ልሸፈንላችሁ እንዴ?" አላለም። እንዲያውም ቅዱስ መጽሐፍ "ሙሴም ከተራራው በወረደ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ተነጋገረ የፊቱ ቁርበት እንዳንጸባረቀ አላወቀም ነበር" ነው የሚለው።(ዘጸ 34፥29) ለቅዱሳን እግዚአብሔር በፊታቸው የሚሥለው የክብር ብርሃን እነርሱን ለሚመለከታቸው እንጂ ለራሳቸው አይታወቃቸውም። እውነተኞቹ ቅዱሳን "ተሸፈኑልን" የሚባሉ እንጂ "ልሸፈንላችሁ" የሚሉ አይደሉም።
ጥቂት በጎ ሥራ ሠርተህ ጻድቅነትህን በግድ ለማሳየት አትሞክር። ሌሎች ተሸፈንልን ይበሉህ እንጂ፣ አንተ ራስህ "ልሸፈንላችሁ" እያልህ የዋሐንን አታስጨንቅ።
በአገራችን የሚታወቅ ተረት አለ። አንድ ጊዜ ትንኝ በሬ ቀንድ ላይ ቆመችና "ከብጄህ እንደ ሆነ ንገረኝና ልነሣልህ" አለችው። በሬውም "እንኳን ልትከብጅኝ መኖርሽንም አላወቅሁም" አላት።
"ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው" ሉቃስ 18፥9
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
ሙሴ ከሲና ተራራ ወርዶ ከሕዝቡ ጋር ሲገናኝ የፊቱን ማንጸባረቅ አይተው "ተሸፈንልን" ያሉት ሕዝቡ ናቸው። እርሱ "ከእግዚአብሔር ጋር ስነጋገር ቆይቼ እኮ አሁን መውረዴ ነው? ምነው የፊቴ ብርሃን አስቸገራችሁ? ልሸፈንላችሁ እንዴ?" አላለም። እንዲያውም ቅዱስ መጽሐፍ "ሙሴም ከተራራው በወረደ ጊዜ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ስለ ተነጋገረ የፊቱ ቁርበት እንዳንጸባረቀ አላወቀም ነበር" ነው የሚለው።(ዘጸ 34፥29) ለቅዱሳን እግዚአብሔር በፊታቸው የሚሥለው የክብር ብርሃን እነርሱን ለሚመለከታቸው እንጂ ለራሳቸው አይታወቃቸውም። እውነተኞቹ ቅዱሳን "ተሸፈኑልን" የሚባሉ እንጂ "ልሸፈንላችሁ" የሚሉ አይደሉም።
ጥቂት በጎ ሥራ ሠርተህ ጻድቅነትህን በግድ ለማሳየት አትሞክር። ሌሎች ተሸፈንልን ይበሉህ እንጂ፣ አንተ ራስህ "ልሸፈንላችሁ" እያልህ የዋሐንን አታስጨንቅ።
በአገራችን የሚታወቅ ተረት አለ። አንድ ጊዜ ትንኝ በሬ ቀንድ ላይ ቆመችና "ከብጄህ እንደ ሆነ ንገረኝና ልነሣልህ" አለችው። በሬውም "እንኳን ልትከብጅኝ መኖርሽንም አላወቅሁም" አላት።
"ጻድቃን እንደ ሆኑ በራሳቸው ለሚታመኑና ሌሎቹን ሁሉ በጣም ለሚንቁ ይህን ምሳሌ ነገራቸው" ሉቃስ 18፥9
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
ቅዱስ ማርቆስ ወንጌላዊው እንደሚነግረን ጌታችን የተፈተነው በአርባኛው ቀን ብቻ ሳይሆን አርባውን ቀን በሰይጣን እየተፈተነ ነው የሰነበተው፡፡(ማር 1:13) መጻሕፍት በአርባኛው ቀን የተፈተናቸውን ፈተናዎች ብቻ ይዘው መገኘታቸው በሚበልጠው ለመናገር ነው እንጂ እነዚህን ብቻ ነው የተፈተነው ማለታቸው አይደለም፡፡ በፈተና የሚያልፉ ክርስቲያኖች በደል ሳይገኝበት ‹በነገር ሁሉ የተፈተነ› እና በድካማቸው የሚራራላቸው አምላክ እንዳላቸው አውቀው ይጽናኑ ዘንድ እርሱ በበጎ ለሚፈተኑ ሁሉ በኩር ሆነ፡፡ (ዕብ 4:15)
ጌታ የተፈተነው ከተጠመቀ በኋላ ነበር፡፡ ይህ ለእኛ ምን ያስተምረናል? ምዕመናን ሁል ጊዜ የእግዚአብሔርን ኃይል ፣ልጅነትን በጥምቀት ከተቀበሉ በኋላ የሚያስተናግዱት የፈተና ሕይወት እንዳለ ነው፡፡ ሰይጣን ደስ የሚሰኝበት ምንም ዓይነት የጽድቅ ሥራ ባለመኖሩ ፣የፈተና ወጥመዱን የሚዘረጋው ፈቃዱን ለሚፈጽሙ ደካሞች ሳይሆን በጥምቀት የእግዚአብሔርን ልጅነት ላገኙ እና የዲያቢሎስን ክፋት በመልካም ተጋድሎ ለሚቃወሙት ጽኑዓን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹ኃይልን የምንታጠቀው እኮ ለመዋጋት ነው እንጂ ለመቀመጥ አይደለም› ይለናል! እውነት ነው!፡፡ እግዚአብሔር በጥምቀት መንፈሳዊውን ኃይል የሚያስታጥቀን ከጠላት ዘንድ ፋታ የሌለው ውጊያ ስላለብን አይደለምን? ታዲያ ለምን ለፈተና ሁል ጊዜ እንግዶች እንሆናለን?
አምላካችን በወንጌል በምሳሌ እንዳስተማረው ኢየሩሳሌም ከተባለች ልዕልና ኢያሪኮ ወደ ተሰኘች ትሕትና አንድ ሰው የተባለ አዳም ሲወርድ በመንገድ አጋንንት አግኝተው ፈትነው ፣ልጅነቱን ቀምተው ፣በኃጢአት ቁስል አቁስለው በሞትና በሕይወት መካከል ጥለውት እንደሄዱ ፤ የአዳምና የሔዋንን እዳ ለመክፈል ሰው የሆነ ክርስቶስም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ሲወርዱ በሚያገኙት የቆሮንቶስ በረሃ አዳምን ያቆሰሉትን አጋንንት ድል ነስቶለታል፡፡ (ሉቃ 10)
መልካም ጾም ይሁንልን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ጌታ የተፈተነው ከተጠመቀ በኋላ ነበር፡፡ ይህ ለእኛ ምን ያስተምረናል? ምዕመናን ሁል ጊዜ የእግዚአብሔርን ኃይል ፣ልጅነትን በጥምቀት ከተቀበሉ በኋላ የሚያስተናግዱት የፈተና ሕይወት እንዳለ ነው፡፡ ሰይጣን ደስ የሚሰኝበት ምንም ዓይነት የጽድቅ ሥራ ባለመኖሩ ፣የፈተና ወጥመዱን የሚዘረጋው ፈቃዱን ለሚፈጽሙ ደካሞች ሳይሆን በጥምቀት የእግዚአብሔርን ልጅነት ላገኙ እና የዲያቢሎስን ክፋት በመልካም ተጋድሎ ለሚቃወሙት ጽኑዓን ነው፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ‹ኃይልን የምንታጠቀው እኮ ለመዋጋት ነው እንጂ ለመቀመጥ አይደለም› ይለናል! እውነት ነው!፡፡ እግዚአብሔር በጥምቀት መንፈሳዊውን ኃይል የሚያስታጥቀን ከጠላት ዘንድ ፋታ የሌለው ውጊያ ስላለብን አይደለምን? ታዲያ ለምን ለፈተና ሁል ጊዜ እንግዶች እንሆናለን?
አምላካችን በወንጌል በምሳሌ እንዳስተማረው ኢየሩሳሌም ከተባለች ልዕልና ኢያሪኮ ወደ ተሰኘች ትሕትና አንድ ሰው የተባለ አዳም ሲወርድ በመንገድ አጋንንት አግኝተው ፈትነው ፣ልጅነቱን ቀምተው ፣በኃጢአት ቁስል አቁስለው በሞትና በሕይወት መካከል ጥለውት እንደሄዱ ፤ የአዳምና የሔዋንን እዳ ለመክፈል ሰው የሆነ ክርስቶስም ከኢየሩሳሌም ወደ ኢያሪኮ ሲወርዱ በሚያገኙት የቆሮንቶስ በረሃ አዳምን ያቆሰሉትን አጋንንት ድል ነስቶለታል፡፡ (ሉቃ 10)
መልካም ጾም ይሁንልን!
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
በንጽሕና ለመኖር እየታገለ የሚወድቅን እግዚአብሔር አያዝንበትም። ድካሙን እና ያልተቋረጠ ጥረቱን አይቶ ድል የሚነሣበትን መንፈሳዊ ጸጋ ይሰጠዋል እንጂ። እንድትኖር በታዘዝከው ልክ ለመኖር ሞክረህ ስላልሆነልህ በራስህ ተስፋ አትቁረጥ። መሆንህን ብቻ ሳይሆን ፈልገህ መሞከርህን እግዚአብሔር ይቆጥርልሃል። ሰይጣን አቁስሎህ ስለሻረው ጠባሳህ አትቆጭ። ብዙ ጠባሳ እኮ ለሚዋደቅ ጀግና ወታደር የክብር ምልክቱ ነው። አፈ ወርቅ ዮሐንስ እንደሚለው የማይቆስለው የማይዋጋ ብቻ ነው።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
+++ ጸልየህ ልታደርገው ትችላለህ? +++
ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ። በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"
በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
ማልዶ ቤተ ክርስቲያን ተሳልሞ ወደ ሥራ የሚሄድ አንድ መንፈሳዊ ሰው በጉዞው ከሌላ መንገደኛ ሰው ጋር ይገናኛል። ጥቂት እንደ ተጨዋወቱ ይህ በመንገድ ያገኘው ሰው ከደረት ኪሱ የሲጋራ ፓኮ በማውጣት አንዱን መዝዞ እንዲወስድ ይጋብዘዋል። ያም መንፈሳዊ ሰው "አይ ይቅርብኝ" ሲል እምቢታውን ገለጸ። ባለ ሲጋራውም "ኃጢአት ነው ብለህ ስላሰብህ ነው እምቢ ያልከኝ? ማጨስ እኮ ከአስጨናቂዋ ሕይወት ፋታ ለመውሰድና ራስን ዘና ለማድረግ ይረዳል። ግድ የለህም አንዱን ሞክር" እያለ ሊያግባባው ጣረ። በመጨረሻም መንፈሳዊው ሰው "ግድ የለም ለእኔ ይቅርብኝ። ባይሆን አንተ ይጠቅመኛል ካልህ በቃ ሲጋራውን ከመለኮስህ በፊት አንድ "አባታችን ሆይ" ጸልይና ጀምር" አለው። በዚህ ጊዜ ያ መንገደኛ ደንግጦ እንዲህ ሲል መለሰ "ጸሎት ጸልዬማ እንዴት እንዲህ አደርጋለሁ?!"
በጸሎት ልትጀምር የማትችላቸው ማናቸውም ነገሮች ለአንተ መልካም አይደሉም። በልብህ ኃጢአት እንድታደርግ የሚገፉፉህ ክፉ ሐሳብ ሲመጣ "ይህን ጸልዬ ማድረግ እችላለሁ?" ብለህ ራስህን ጠይቅ። ከጸሎት ጋር የማይጣጣም ከመሰለህ እርሱ ኃጢአት ነውና ተወው። ጸልዮ የሚዘሙት፣ ጸልዮ የሚሰርቅ፣ ጸልዮ ባልንጀራውን የሚሳደብ፣ ጸልዮ በወንድሙ ላይ ክፉ የሚያደርግ ማን ነው?
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
[email protected]
አዲስ አበባ
ሰላም እንዴት አመሻችሁ ክቡራን፣
ከዚህ በፊት የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርታት ጀምረን ለዐሥር ክፍላት መማራችን ይታወቃል። ይሁን እንጂ ትምህርቱ ይሰጥ የነበረበት ሰዓት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ላሉ ብዙም አመቺ ስላልነበር የሰዓት ማስተካከያ ቢደረግ የሚሉ አስተያየቶች ሲደርሱን ቆይተዋል። በዚህ መሠረት የonline ትምሀእርቱን በኢትዮጵያ አቆጣጠር አርብ ከምሽቱ 4:00 እስከ 5:00 ድረስ ለማድረግ አስበናል።
ከላይ ባስቀመጥነው poll ላይ የተባለው ሰዓት የሚመች መሆኑን እና አለመሆኑን እንድትገልጹልን እንዲሁም ተጨማሪ የሰዓት ማስተካከያ አስተያየት ካላችሁም ሐሳባችሁን በcomment section እንድትሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን!
=) ትምህርቱ እዚሁ Telegram Channel ላይ በlive stream ነው የሚሰጠው።
ከዚህ በፊት የዕብራውያን መልእክት ሐተታ ትምህርታት ጀምረን ለዐሥር ክፍላት መማራችን ይታወቃል። ይሁን እንጂ ትምህርቱ ይሰጥ የነበረበት ሰዓት ኢትዮጵያ እና አውሮፓ ላሉ ብዙም አመቺ ስላልነበር የሰዓት ማስተካከያ ቢደረግ የሚሉ አስተያየቶች ሲደርሱን ቆይተዋል። በዚህ መሠረት የonline ትምሀእርቱን በኢትዮጵያ አቆጣጠር አርብ ከምሽቱ 4:00 እስከ 5:00 ድረስ ለማድረግ አስበናል።
ከላይ ባስቀመጥነው poll ላይ የተባለው ሰዓት የሚመች መሆኑን እና አለመሆኑን እንድትገልጹልን እንዲሁም ተጨማሪ የሰዓት ማስተካከያ አስተያየት ካላችሁም ሐሳባችሁን በcomment section እንድትሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን!
=) ትምህርቱ እዚሁ Telegram Channel ላይ በlive stream ነው የሚሰጠው።
ሰላም እንዴት ቆያችሁ፣
በብዙዎቻችሁ ድምፅ መሠረት “የዕብራውያን መልእክት ሐተታ” ትምህርታችን አርብ ከምሽቱ 4:00-5:00 ባለው እንዲደረግ ተወስኗል። ስለዚህም ነገ የካቲት 21 ልክ 4፡00 ሰዓት ላይ ትምህርታችንን የምንጀምር ይሆናል። ትምህርቱ ከክፍል አንድ ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ከዚህ ቀደም የመማር ዕድል ላልነበራቸው ምንም የሚያመልጣቸው ነገር አይኖርም። እስከ ክፍል ዐሥር የተማሩትም ቢሆኑ አቀራረቡ እና ይዘቱ ካለፈው ይልቅ ሰፋ ስለሚል የተሻለ ተጠቃሚዎች ያደርጋቸዋል።
እስከዚያው ትምህርቱ የሚተላለፍበትን ይህን የTelegram Channel link ለብዙዎች እያጋራን እንቆይ።
“ብዙ ምርኮ እንዳገኘ በቃልህ ደስ አለኝ” መዝ 119:162
https://www.tg-me.com/Dnabel
በብዙዎቻችሁ ድምፅ መሠረት “የዕብራውያን መልእክት ሐተታ” ትምህርታችን አርብ ከምሽቱ 4:00-5:00 ባለው እንዲደረግ ተወስኗል። ስለዚህም ነገ የካቲት 21 ልክ 4፡00 ሰዓት ላይ ትምህርታችንን የምንጀምር ይሆናል። ትምህርቱ ከክፍል አንድ ጀምሮ የሚሰጥ ሲሆን ከዚህ ቀደም የመማር ዕድል ላልነበራቸው ምንም የሚያመልጣቸው ነገር አይኖርም። እስከ ክፍል ዐሥር የተማሩትም ቢሆኑ አቀራረቡ እና ይዘቱ ካለፈው ይልቅ ሰፋ ስለሚል የተሻለ ተጠቃሚዎች ያደርጋቸዋል።
እስከዚያው ትምህርቱ የሚተላለፍበትን ይህን የTelegram Channel link ለብዙዎች እያጋራን እንቆይ።
“ብዙ ምርኮ እንዳገኘ በቃልህ ደስ አለኝ” መዝ 119:162
https://www.tg-me.com/Dnabel
“እንዲህም የተወደደው ወንድማችን ጳውሎስ ደግሞ እንደ ተሰጠው ጥበብ መጠን ጻፈላችሁ” 2 ጴጥ 3:15
ዛሬ ልክ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ላይ በዚህ https://www.tg-me.com/Dnabel የቴሌግራም ቻናል በlive stream ትምህርቱ ይሰጣል።
ለአማራጭ እንዲሆን የzoom meeting የተዘጋጀ ሲሆን፣ ይህን ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ደግሞ በzoom ልትቀላቀሉን ትችላላችሁ።
https://us05web.zoom.us/j/84709079682?pwd=obn6Rc8YrJjSTaAAeRwKmNbMC2kY8n.1
ዛሬ ልክ በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከምሽቱ 4:00 ሰዓት ላይ በዚህ https://www.tg-me.com/Dnabel የቴሌግራም ቻናል በlive stream ትምህርቱ ይሰጣል።
ለአማራጭ እንዲሆን የzoom meeting የተዘጋጀ ሲሆን፣ ይህን ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ደግሞ በzoom ልትቀላቀሉን ትችላላችሁ።
https://us05web.zoom.us/j/84709079682?pwd=obn6Rc8YrJjSTaAAeRwKmNbMC2kY8n.1
+++ የጀማሪ ጠባይ +++
መንፈሳዊ ሕይወትን ገና ስትጀምረው ለፍጹምነት ጥቂት የቀረህ ያህል ይሰማሃል። አንተ ጋር ያለው ደስታ እና ሰላም ሌሎች ጋር የሌለ ይመስልሃል። በዚህች ሁከት በሞላባት ዓለም አንተ ብቻ ክርስቶስን እንዳገኘኸው ታስባለህ። የቀረው ሕዝበ አዳም እንዲሁ በከንቱ ሲርመሰመስ የሚውል ባካና ሆኖ ይታይሃል። ታዝንለታለህ፣ አይይይ ይህ ኃጢአተኛ ሕዝብ ምን ይሻለዋል? ትላለህ።
የእውነተኛ መንፈሳዊ እድገት መገለጫ ግን ይህ አይደለም። ሰው ወደ እግዚአብሔር እየቀረበ ሲመጣ ከሌላው ሰው ይልቅ የራሱ ጉድለት ይታየዋል። መንፈሳዊነት የሚገልጥልህ ሰዎችን ተመልክተህ የምትፈርድበትን ውጫዊ ዓይንህን ሳይሆን ራስህን አይተህ የምትወቅስበት የውስጥ ዓይንህን ነው። መንፈሳዊ ሕይወትህ ሲጎመራ "አይ ሰው" ሳይሆን "አይ እኔ!" ያሰኝሃል። አባ ማቴዎስም እንዲህ ይላል "ሰው የበለጠ ወደ እግዚአብሔር ሲቀርብ ይበልጥ ኃጢአተኛ መሆኑ እየታየው ይመጣል። ነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ካየ በኋላ ከንፈሮቼ የረከሱብኝና የጠፋሁ ሰው ነኝ እንዳለ።"
ከብቃት ደርሰህ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ቢታዩህ እንኳን ሁሉ እንዳንተ ስለሚመስልህ እንደ ዮሐንስ ሐጺር "ሚካኤል ይበልጣል ወይስ ገብርኤል?" እያልህ ከአጠገብህ የቆመውን ትጠይቃለህ እንጂ "አይይ አንተ እንኳን ገና አልበቃህም። ብዙ ይቀርሃል" ብለህ ወዳጅህን አታናንቅም። ይልቅ "ለእኔ ብቻ ገልጦ ለሌላው እንዲሰውር የሚያደርገው ምንም ቁም ነገር የለኝም" በማለት ከወንድምህ የተሻልህ እንዳልሆንክ በፍጹም ልብህ ታምናለህ።
ለመንፈሳዊ ሕይወት አዲስ ስትሆን ገና ጥቂት ጸልየህ፣ ጥቂት ጾመህ፣ ጥቂት መጽውተህ ሳለ ግን ሩጫህን ወደ መጨረሱ የተቃረብህ ይመስልሃል። ጉዞህን በግማሽ እርምጃ ከመጀመርህ ከፍጻሜው ላይ የደረስህ ያህል ይሰማሃል። "እኔን ምሰሉ" ማለት ያምርሃል። ነገር ግን መንፈሳዊ ሕይወት የቱንም ያህል ብትሮጥበት ሁል ጊዜ እንደ ጀማሪ የሚያደርግ ረጅም ጎዳና ነው። ሰማንያ ዓመት በገዳም ሲጋደል የነበረው አባ ሲሶይ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በቀረበች ጊዜ ብዙ መነኮሳት በአልጋው ዙሪያ ከበውት ሳለ ቅዱሱ "አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ለንስሐ የሚሆን ጥቂት ጊዜን ስጠኝ?" እያለ በልቅሶ ሲማጸን ሰሙት። በዚህ የተገረሙት መነኮሳቱ አባ ሲሶይን "አባታችን አንተ እድሜ ልክህን በንስሐ የኖርህ መምህረ ንስሐ ሆነህ ሳለ እንዴት አሁን ጥቂት የንስሐ ጊዜን ትለምናለህ?" ቢሉት፣ ቅዱሱም "ልጆቼ ይህን መንፈሳዊ ጥበብ (ንስሐን) ገና አሁን መጀመሬ ነው" አላቸው።
ጌታ ሆይ መንፈሳዊ ሕይወት እኖር ዘንድ አስጀምረኝ፤ ገና ጀማሪ ሳለሁ ደርሻለሁ ከማለትም ሰውረኝ። እንድቆም አትፍቀድልኝ፤ ወደ አንተ ሳበኝ፣ አሳድገኝ።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ሰኔ 22፣ 2014 ዓ.ም.
አዲስ አበባ
መንፈሳዊ ሕይወትን ገና ስትጀምረው ለፍጹምነት ጥቂት የቀረህ ያህል ይሰማሃል። አንተ ጋር ያለው ደስታ እና ሰላም ሌሎች ጋር የሌለ ይመስልሃል። በዚህች ሁከት በሞላባት ዓለም አንተ ብቻ ክርስቶስን እንዳገኘኸው ታስባለህ። የቀረው ሕዝበ አዳም እንዲሁ በከንቱ ሲርመሰመስ የሚውል ባካና ሆኖ ይታይሃል። ታዝንለታለህ፣ አይይይ ይህ ኃጢአተኛ ሕዝብ ምን ይሻለዋል? ትላለህ።
የእውነተኛ መንፈሳዊ እድገት መገለጫ ግን ይህ አይደለም። ሰው ወደ እግዚአብሔር እየቀረበ ሲመጣ ከሌላው ሰው ይልቅ የራሱ ጉድለት ይታየዋል። መንፈሳዊነት የሚገልጥልህ ሰዎችን ተመልክተህ የምትፈርድበትን ውጫዊ ዓይንህን ሳይሆን ራስህን አይተህ የምትወቅስበት የውስጥ ዓይንህን ነው። መንፈሳዊ ሕይወትህ ሲጎመራ "አይ ሰው" ሳይሆን "አይ እኔ!" ያሰኝሃል። አባ ማቴዎስም እንዲህ ይላል "ሰው የበለጠ ወደ እግዚአብሔር ሲቀርብ ይበልጥ ኃጢአተኛ መሆኑ እየታየው ይመጣል። ነቢዩ ኢሳይያስ እግዚአብሔርን ካየ በኋላ ከንፈሮቼ የረከሱብኝና የጠፋሁ ሰው ነኝ እንዳለ።"
ከብቃት ደርሰህ መላእክት ሲወጡና ሲወርዱ ቢታዩህ እንኳን ሁሉ እንዳንተ ስለሚመስልህ እንደ ዮሐንስ ሐጺር "ሚካኤል ይበልጣል ወይስ ገብርኤል?" እያልህ ከአጠገብህ የቆመውን ትጠይቃለህ እንጂ "አይይ አንተ እንኳን ገና አልበቃህም። ብዙ ይቀርሃል" ብለህ ወዳጅህን አታናንቅም። ይልቅ "ለእኔ ብቻ ገልጦ ለሌላው እንዲሰውር የሚያደርገው ምንም ቁም ነገር የለኝም" በማለት ከወንድምህ የተሻልህ እንዳልሆንክ በፍጹም ልብህ ታምናለህ።
ለመንፈሳዊ ሕይወት አዲስ ስትሆን ገና ጥቂት ጸልየህ፣ ጥቂት ጾመህ፣ ጥቂት መጽውተህ ሳለ ግን ሩጫህን ወደ መጨረሱ የተቃረብህ ይመስልሃል። ጉዞህን በግማሽ እርምጃ ከመጀመርህ ከፍጻሜው ላይ የደረስህ ያህል ይሰማሃል። "እኔን ምሰሉ" ማለት ያምርሃል። ነገር ግን መንፈሳዊ ሕይወት የቱንም ያህል ብትሮጥበት ሁል ጊዜ እንደ ጀማሪ የሚያደርግ ረጅም ጎዳና ነው። ሰማንያ ዓመት በገዳም ሲጋደል የነበረው አባ ሲሶይ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በቀረበች ጊዜ ብዙ መነኮሳት በአልጋው ዙሪያ ከበውት ሳለ ቅዱሱ "አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ለንስሐ የሚሆን ጥቂት ጊዜን ስጠኝ?" እያለ በልቅሶ ሲማጸን ሰሙት። በዚህ የተገረሙት መነኮሳቱ አባ ሲሶይን "አባታችን አንተ እድሜ ልክህን በንስሐ የኖርህ መምህረ ንስሐ ሆነህ ሳለ እንዴት አሁን ጥቂት የንስሐ ጊዜን ትለምናለህ?" ቢሉት፣ ቅዱሱም "ልጆቼ ይህን መንፈሳዊ ጥበብ (ንስሐን) ገና አሁን መጀመሬ ነው" አላቸው።
ጌታ ሆይ መንፈሳዊ ሕይወት እኖር ዘንድ አስጀምረኝ፤ ገና ጀማሪ ሳለሁ ደርሻለሁ ከማለትም ሰውረኝ። እንድቆም አትፍቀድልኝ፤ ወደ አንተ ሳበኝ፣ አሳድገኝ።
ዲያቆን አቤል ካሳሁን
ሰኔ 22፣ 2014 ዓ.ም.
አዲስ አበባ