This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
†
[ አ ን ድ ቀ ን ...... ! ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። ❞
[ ፩ ዮሐ . ፪ ፥ ፲፯ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
[ አ ን ድ ቀ ን ...... ! ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
❝ ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። ❞
[ ፩ ዮሐ . ፪ ፥ ፲፯ ]
† † †
▬▬▬▬ ▬▬▬▬▬ ▬▬▬▬
🕊
[ † እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንጸተ ቤታ [ ሕንጸታ ] በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † በዓለ ሕንጸታ † 🕊
† በዚሕች ቀን : በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በአምላክ እናት ስም ታንጻለች::
ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን "ሑሩ ወመሐሩ ኩሎ አሕዛበ" [አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ] [ማቴ.፳፰፥፲፱] (28:19) ባላቸው ቃል መሠረት ዓለምን በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል::
የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና [ዮሐ.፮፥፶፮] (6:56) አበው ሐዋርያት ቁርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር::
በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን: ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲሕ ይከናወን ነበር:: ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኩራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቁጥር እጅጉን በዛ::
በተለይ ቅዱስ ጳውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ:: በዚሕ ምክንያት መምሕራን ሕዝቡን "ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?" ቢሏቸው "እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት እንደሆን የለን" ሲሉ መለሱላቸው::
ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ጳውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች "ለምን አናንጽም" ብለው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ግን "ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም" አለ:: [ለዚሕ ነው ዛሬም ሊቀ ጳጳስ ካልፈቀደ ቤተ ክርስቲያን የማይታነጸው::]
ከዚያ ቅዱሳን ጳውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ጴጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱም "የጌታችን ፈቃዱ መሆኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ" ብሎ አዋጅ ነገረ::
በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔአቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ::
ሁሉንም ሐዋርያት በደመና ጭኖ ፊልጵስዩስ አደረሳቸው:: ከከተማ ወጣ ብሎ ባለ መሬት ላይም "ቤተ ክርስቲያንን በእናቴ ስም አንጹ" ብሎ አዘዛቸው:: ለቅዱስ ጴጥሮስም ሦስት ዓለቶችን ሰጠው::
እነዚያን መሬት ላይ ተክሎ : ጌታችን ቆሞለት : ሐዋርያቱ እየተራዱት : ግርምት የምትሆን ሦስት ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን በ52 ዓ/ም በዚህች ቀን አንጿል::
ቤተ ክርስቲያኗን ነገ ጌታችን ቀደሳት የምንል ነንና ይቆየን::
† አምላካችን የድንግል እናቱን ፍቅር : የተቀደሰች ቤቱን ጸጋ : የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን::
🕊
[ † ሰኔ ፳ [ 20 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ [ ዕረፍቱ ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት [ሰማዕት]
፪. ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
፫. ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
፬. ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ [ ንጉሠ ኢትዮጵያ ]
፭. አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
፮. ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
† " በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር : አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት : ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . . የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው:: " † [፪ቆሮ. ፲፩፥፳፫-፳፰]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
[ † እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ሕንጸተ ቤታ [ ሕንጸታ ] በሰላም አደረሳችሁ ፣ አደረሰን። † ]
† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †
🕊 † በዓለ ሕንጸታ † 🕊
† በዚሕች ቀን : በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን በአምላክ እናት ስም ታንጻለች::
ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ :-
ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን "ሑሩ ወመሐሩ ኩሎ አሕዛበ" [አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ] [ማቴ.፳፰፥፲፱] (28:19) ባላቸው ቃል መሠረት ዓለምን በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል::
የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና [ዮሐ.፮፥፶፮] (6:56) አበው ሐዋርያት ቁርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው ያቆርቡ ነበር::
በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን: ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲሕ ይከናወን ነበር:: ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኩራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቁጥር እጅጉን በዛ::
በተለይ ቅዱስ ጳውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ:: በዚሕ ምክንያት መምሕራን ሕዝቡን "ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?" ቢሏቸው "እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት እንደሆን የለን" ሲሉ መለሱላቸው::
ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ጳውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች "ለምን አናንጽም" ብለው ነበር:: ቅዱስ ጳውሎስ ግን "ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም" አለ:: [ለዚሕ ነው ዛሬም ሊቀ ጳጳስ ካልፈቀደ ቤተ ክርስቲያን የማይታነጸው::]
ከዚያ ቅዱሳን ጳውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ጴጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱም "የጌታችን ፈቃዱ መሆኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ" ብሎ አዋጅ ነገረ::
በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔአቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ::
ሁሉንም ሐዋርያት በደመና ጭኖ ፊልጵስዩስ አደረሳቸው:: ከከተማ ወጣ ብሎ ባለ መሬት ላይም "ቤተ ክርስቲያንን በእናቴ ስም አንጹ" ብሎ አዘዛቸው:: ለቅዱስ ጴጥሮስም ሦስት ዓለቶችን ሰጠው::
እነዚያን መሬት ላይ ተክሎ : ጌታችን ቆሞለት : ሐዋርያቱ እየተራዱት : ግርምት የምትሆን ሦስት ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተ ክርስቲያን በ52 ዓ/ም በዚህች ቀን አንጿል::
ቤተ ክርስቲያኗን ነገ ጌታችን ቀደሳት የምንል ነንና ይቆየን::
† አምላካችን የድንግል እናቱን ፍቅር : የተቀደሰች ቤቱን ጸጋ : የቡሩካን ሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን::
🕊
[ † ሰኔ ፳ [ 20 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ኤልሳዕ ነቢይ [ ዕረፍቱ ]
[ † ወርኀዊ በዓላት ]
፩. ቅዱስ ቴዎድሮስ ሊቀ ሠራዊት [ሰማዕት]
፪. ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር
፫. ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ
፬. ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ [ ንጉሠ ኢትዮጵያ ]
፭. አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና
፮. ቅድስት ሳድዥ የዋሒት
† " በድካም : አብዝቼ በመገረፍ : አብዝቼ በመታሠር : አትርፌ በመሞት ብዙ ጊዜ ሆንሁ:: በድካምና በጥረት : ብዙ ጊዜም እንቅልፍ በማጣት : በራብና በጥም : ብዙ ጊዜም በመጦም : በብርድና በራቁትነት ነበርሁ . . . የቀረውን ነገር ሳልቆጥር ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው:: " † [፪ቆሮ. ፲፩፥፳፫-፳፰]
† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †
† ወለወላዲቱ ድንግል †
† ወለመስቀሉ ክቡር †
[ ዲ/ን ዮርዳኖስ አበበ ]
† † †
▬▬▬▬▬ ▬▬▬ ▬▬▬▬▬
💖 🕊 💖
❤6
ስለ አንተ ቀኑን ሁሉ እንገደላለን፥ እንደሚታረዱ በጎች ተቆጠርን ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው ፤ በዚህ ሁሉ ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች እንበልጣለን ፤ ሞት ቢሆን፥ ሕይወትም ቢሆን፥ መላእክትም ቢሆኑ፥ ግዛትም ቢሆን፥ ያለውም ቢሆን፥ የሚመጣውም ቢሆን፥ ኃይላትም ቢሆኑ፥
፤ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።
ወ.ሮ ሰዎች ምዕ. 8፣36_39
#_ሰናይ__ቀን🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
፤ ከፍታም ቢሆን፥ ዝቅታም ቢሆን፥ ልዩ ፍጥረትም ቢሆን በክርስቶስ ኢየሱስ በጌታችን ካለ ከእግዚአብሔር ፍቅር ሊለየን እንዳይችል ተረድቼአለሁ።
ወ.ሮ ሰዎች ምዕ. 8፣36_39
#_ሰናይ__ቀን🙏
ለመቀላቀል 👇👇👇👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤6😢4🙏3👍1
🕊 † 🕊
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትንሣኤውንም እናምናለን ! ]
🕊 💖 🕊
❝ እኛ ግን የዳንበትን አዳኛችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለውን ሕማሙን በፈቃዱ ስለእኛ በሥጋ ያደረገውን ሞቱን እናስተምራለን ፤ ትንሣኤውንም እናምናለን ወደ ሰማይ ማረጉንም እናስተምራለን ፤ በሙታን በሕያዋን ይፈርድ ዘንድ የሚመጣበትን ዳግመኛ ምጽአቱን ፤ እርሱ የሚያወርሳት ለዘለዓለም የማታልፍ መንግሥተ ሰማያት እንዳለች እናምናለን። [ ማቴ.፲፥፳፰-፮ ። ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ]
በኦሪት የተጻፈውን ቃል ምክንያት አድርገው ለእግዚአብሔር ቀድሞ ሥጋ እንደ ነበረው የሚናገሩ ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን በእኛ አምሳል እንፍጠር አለ በእኛ አምሳል ያለውም ስለሰው ሥጋ ነው የሚሉ አሉ። [ዘፍ.፩፥፳፮ ]
ነገር ግን እንዲህ አይደለም እርሱ ስለ ውሳጣዊ ሰውነታችን [ ነፍስ ] ተናገረ እንጂ እርሱ ሁልጊዜ በመታደስ ጸንቶ ይኖራልና። አፍአዊ ሰውነታችን [ ሥጋ ] ይሞት ዘንድ እስኪነሣ ድረስም ይፈርስ ይበሰብስ ዘንድ እንዳለው ነገሩ የታወቀ ነው ፤ ውሳጣዊው ግን አይሞትም አይፈርስም አይበሰብስም። [ ፪ቆሮ.፬፥፲፮ ]
የበቃ ቢሆን ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስዱታል ፤ መውጣት ሳይኖር ሁል ጊዜ በዚያ ይኖራል።የበቃ ባይሆን ግን ወደገሀነም ይወስዱታል ፤ ፍጻሜ ሳይኖረው ለዘለዓለም በዚያ ይኖራል። [ ማቴ.፳፭፥፵፮ ]
ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ በጎ ሥራን ቢሠራ እግዚአብሔርን እንደሚመስል እግዚአብሔር ገልጦልን ይኸን ቃል እንተረጕማለን ፤ ምድራዊ አዳምን መምሰል ገንዘብ እንደ አደረግን ሰማያዊ ክርስቶስን መምሰልን ገንዘብ እናደርጋለን ተብሎ እንደ ተጻፈ። [ ፩ቆሮ.፲፭፥፮-፵፱ ]
ውሳጣዊ ሰውነት ግን የማይለወጥ ዕውቀት ያለው ነፍስ ነው ፤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በሥጋ ተሰውሮ ያለ ነፍስን በቸርነቱ እግዚአብሔርን የሚመስል አድርጎ ፈጠረው ፤ እግዚአብሔር ጥንቱን ሥጋ አይደለምና አይወሰንምና ጌታ እሳት ነው ፤ ብርሃንም ነው ፤ ማንም ማን አይቀርበውም ፤ ሕሊናም መርምሮ አያገኘውም አይመረመርም ከላይ ሆኖ ሰማይን ፡ ይሸፍናል ፤ ከታች ሆኖ ምድርን ይሸፍናል።
ፍጥረት ሁሉ ፤ ሰማያት በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ፤ ምድርም ፤ በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ከብቱም አውሬውም ሁሉ የሚንቀሳቀሱትም ወፎችም ፤ የምድረ በዳ ዛፎችም ሁሉ ባሕርም ፤ ፈሳሾችም በውስጣቸውም ያሉ ሁሉ በእርሱ ጸንተው ይኖራሉ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ሁሉም በእርሱ ተፈጥሮአልና። [ መዝ.፻፵፰፥፩—፲፬ ። ዮሐ.፩፥፫ ቆላ.፩፥፲፭-፲፰ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
[ ተዋሕዶ ፍጽምት የቅዱሳን ሃይማኖት ]
▬▬▬▬▬▬ † ▬▬▬▬▬▬
[ ትንሣኤውንም እናምናለን ! ]
🕊 💖 🕊
❝ እኛ ግን የዳንበትን አዳኛችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተቀበለውን ሕማሙን በፈቃዱ ስለእኛ በሥጋ ያደረገውን ሞቱን እናስተምራለን ፤ ትንሣኤውንም እናምናለን ወደ ሰማይ ማረጉንም እናስተምራለን ፤ በሙታን በሕያዋን ይፈርድ ዘንድ የሚመጣበትን ዳግመኛ ምጽአቱን ፤ እርሱ የሚያወርሳት ለዘለዓለም የማታልፍ መንግሥተ ሰማያት እንዳለች እናምናለን። [ ማቴ.፲፥፳፰-፮ ። ግብ.ሐዋ.፩፥፲፩ ]
በኦሪት የተጻፈውን ቃል ምክንያት አድርገው ለእግዚአብሔር ቀድሞ ሥጋ እንደ ነበረው የሚናገሩ ስለዚህም እግዚአብሔር ሰውን በእኛ አምሳል እንፍጠር አለ በእኛ አምሳል ያለውም ስለሰው ሥጋ ነው የሚሉ አሉ። [ዘፍ.፩፥፳፮ ]
ነገር ግን እንዲህ አይደለም እርሱ ስለ ውሳጣዊ ሰውነታችን [ ነፍስ ] ተናገረ እንጂ እርሱ ሁልጊዜ በመታደስ ጸንቶ ይኖራልና። አፍአዊ ሰውነታችን [ ሥጋ ] ይሞት ዘንድ እስኪነሣ ድረስም ይፈርስ ይበሰብስ ዘንድ እንዳለው ነገሩ የታወቀ ነው ፤ ውሳጣዊው ግን አይሞትም አይፈርስም አይበሰብስም። [ ፪ቆሮ.፬፥፲፮ ]
የበቃ ቢሆን ወደ መንግሥተ ሰማያት ይወስዱታል ፤ መውጣት ሳይኖር ሁል ጊዜ በዚያ ይኖራል።የበቃ ባይሆን ግን ወደገሀነም ይወስዱታል ፤ ፍጻሜ ሳይኖረው ለዘለዓለም በዚያ ይኖራል። [ ማቴ.፳፭፥፵፮ ]
ሰው እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ በጎ ሥራን ቢሠራ እግዚአብሔርን እንደሚመስል እግዚአብሔር ገልጦልን ይኸን ቃል እንተረጕማለን ፤ ምድራዊ አዳምን መምሰል ገንዘብ እንደ አደረግን ሰማያዊ ክርስቶስን መምሰልን ገንዘብ እናደርጋለን ተብሎ እንደ ተጻፈ። [ ፩ቆሮ.፲፭፥፮-፵፱ ]
ውሳጣዊ ሰውነት ግን የማይለወጥ ዕውቀት ያለው ነፍስ ነው ፤ ዳግመኛም እግዚአብሔር በሥጋ ተሰውሮ ያለ ነፍስን በቸርነቱ እግዚአብሔርን የሚመስል አድርጎ ፈጠረው ፤ እግዚአብሔር ጥንቱን ሥጋ አይደለምና አይወሰንምና ጌታ እሳት ነው ፤ ብርሃንም ነው ፤ ማንም ማን አይቀርበውም ፤ ሕሊናም መርምሮ አያገኘውም አይመረመርም ከላይ ሆኖ ሰማይን ፡ ይሸፍናል ፤ ከታች ሆኖ ምድርን ይሸፍናል።
ፍጥረት ሁሉ ፤ ሰማያት በውስጣቸውም ያለው ሁሉ ፤ ምድርም ፤ በምድር ላይ ያለ ሰው ሁሉ ከብቱም አውሬውም ሁሉ የሚንቀሳቀሱትም ወፎችም ፤ የምድረ በዳ ዛፎችም ሁሉ ባሕርም ፤ ፈሳሾችም በውስጣቸውም ያሉ ሁሉ በእርሱ ጸንተው ይኖራሉ መጽሐፍ እንደ ተናገረ ሁሉም በእርሱ ተፈጥሮአልና። [ መዝ.፻፵፰፥፩—፲፬ ። ዮሐ.፩፥፫ ቆላ.፩፥፲፭-፲፰ ] ❞
[ 🕊 ቅዱስ ቄርሎስ 🕊 ]
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፤ ወለወላዲቱ ድንግል ፤ ወለመስቀሉ ክቡር። አሜን።
† † †
💖 🕊 💖
🕊 💖 🕊
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ ! ]
❝ ሰላም ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ማኅደረ ስብሐት ምዕዋደ መላእክት እም ኩሉ ሕዝብ ❞
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] የምስጋና ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላምታ ይገባል። ] [አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ]
" በመላእክት ፊት እዘምርልኻለሁ ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ። " [መዝ.፻፴፯፥፪ ]
🕊 💖 🕊
ቤተ ክርስቲያንን “ ቅድስት ” አላት ስለምን ቢሉ ?
የቅድስት ሥላሴ አንድነት ሦስትነት ይነገርባታልና ፤ አንድም ክርስቶስ በቅዱስ ደሙ አክብሯታልና። አንድም የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ደሙ ለምእመናን ይሰጥባታልና፡፡ አንድም በኀጢአት የረከሰ ሰው በንስሓ ከእግዚአብሔር ጋር ታርቆባት ይቀደስባታልና።
“ ማኅደረ ስብሐት ” [ የምስጋና ማደሪያ ] አላት ፦
የልዑል እግዚአብሔር ምስጋና በጸሎተ ኪዳን ፣ በስብሐተ ነግህ ፣ በጸሎተ ቅዳሴ ፣ በማሕሌት ፣ በሰዓታት ፣ በሰባቱ ጊዜያት ኹሉ ይነገርባታልና።
“ የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] ” አላት ፦
የመንግሥቱ ወንጌል በሚነገርበት ፣ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ በሚፈተትበት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የጸለዩትን ጸሎት ለማሳረግ በቀን ስድስት መቶ በሌሊት ስድስት መቶ መላእክት ይጠብቋታልና።
“ እመ ኵሉ ሕዝብ ” የሕዝብ ኹሉ እናት ይላታል ፦
እናት ልጆቿን እንድታሳድግ ፣ እንድትጠብቅ ፣ ወደ ቀና ጐዳና መርታ እንድታደርስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በምስጢረ ቤተ ክርስቲያን ይልቁኑ በሥጋውና በደሙ እናድግባታለን ፤ በርቱዕ ትምህርቷ ከክሕደት እንጠበቅባታለን ፤ በመጨረሻም ወደ አምሳያዋ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት መርታ ታደርስናለችና። [ ገላ.፬፥፳፮-፳፯ ] ❞
🕊 † በዓለ ሕንጸታ † 🕊
💖 🕊 💖
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ ! ]
❝ ሰላም ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ማኅደረ ስብሐት ምዕዋደ መላእክት እም ኩሉ ሕዝብ ❞
[ የሕዝብ ኹሉ እናት የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] የምስጋና ማደሪያ ለኾነችው ለቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላምታ ይገባል። ] [አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ]
" በመላእክት ፊት እዘምርልኻለሁ ወደ ቅዱስ መቅደስህ እሰግዳለሁ። " [መዝ.፻፴፯፥፪ ]
🕊 💖 🕊
ቤተ ክርስቲያንን “ ቅድስት ” አላት ስለምን ቢሉ ?
የቅድስት ሥላሴ አንድነት ሦስትነት ይነገርባታልና ፤ አንድም ክርስቶስ በቅዱስ ደሙ አክብሯታልና። አንድም የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋውና ደሙ ለምእመናን ይሰጥባታልና፡፡ አንድም በኀጢአት የረከሰ ሰው በንስሓ ከእግዚአብሔር ጋር ታርቆባት ይቀደስባታልና።
“ ማኅደረ ስብሐት ” [ የምስጋና ማደሪያ ] አላት ፦
የልዑል እግዚአብሔር ምስጋና በጸሎተ ኪዳን ፣ በስብሐተ ነግህ ፣ በጸሎተ ቅዳሴ ፣ በማሕሌት ፣ በሰዓታት ፣ በሰባቱ ጊዜያት ኹሉ ይነገርባታልና።
“ የመላእክት መዘዋወሪያ [ ቦታ ] ” አላት ፦
የመንግሥቱ ወንጌል በሚነገርበት ፣ ቅዱስ ሥጋው ክቡር ደሙ በሚፈተትበት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን የጸለዩትን ጸሎት ለማሳረግ በቀን ስድስት መቶ በሌሊት ስድስት መቶ መላእክት ይጠብቋታልና።
“ እመ ኵሉ ሕዝብ ” የሕዝብ ኹሉ እናት ይላታል ፦
እናት ልጆቿን እንድታሳድግ ፣ እንድትጠብቅ ፣ ወደ ቀና ጐዳና መርታ እንድታደርስ ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም በምስጢረ ቤተ ክርስቲያን ይልቁኑ በሥጋውና በደሙ እናድግባታለን ፤ በርቱዕ ትምህርቷ ከክሕደት እንጠበቅባታለን ፤ በመጨረሻም ወደ አምሳያዋ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት መርታ ታደርስናለችና። [ ገላ.፬፥፳፮-፳፯ ] ❞
🕊 † በዓለ ሕንጸታ † 🕊
💖 🕊 💖
❤2
💛
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🕊
▷ " ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ! "
[ 💖 አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖 ]
[ 🕊 ]
-------------------------------------------------
❝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ፥ አቤቱ ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች ፤ መቼ እደርሳለሁ ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ ?
ዘወትር። አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ። ❞
[ መዝ . ፵፪ ፥ ፩ - ፫ ]
🕊 💖 🕊
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🕊 [ ምክረ ቅዱሳን ] 🕊
▷ " ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ! "
[ 💖 አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ 💖 ]
[ 🕊 ]
-------------------------------------------------
❝ ዋላ ወደ ውኃ ምንጭ እንደሚናፍቅ ፥ አቤቱ ፥ እንዲሁ ነፍሴ ወደ አንተ ትናፍቃለች። ነፍሴ ወደ ሕያው አምላክ ተጠማች ፤ መቼ እደርሳለሁ ? የአምላክንስ ፊት መቼ አያለሁ ?
ዘወትር። አምላክህ ወዴት ነው? ሲሉኝ እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ። ❞
[ መዝ . ፵፪ ፥ ፩ - ፫ ]
🕊 💖 🕊
❤4
ሰኔ____21
እንኳን #ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ ሰኔ ጐልጐታና ሕንጸተ ቤተ ቤተክርስቲያን (ሕንጸታ) በሰላም አደረሳችኹ
#ድንግል_ሆይ_ዝም_አትበይ🙏😢😢
ጨለማችን ጨልሟል ውስጣችን ቃል በሌለው #ኃዘን ውስጥ ወድቋል ። አሰገራሚው መድኃኒት በውስጥሸ የተገኘ ፡ ምድርን የሸፈነ ፀሐይ የተገለጠብሽ #የዳዊት ልጅ እናታችን ማርያም ሆይ ዝም አትበይ በእውነት ዝም አትበይ ። ትላንት ልመናሽ እንደጋረደን ዛሬም #ቃል_ኪዳንሽ ጥላ ይሁነን ።
#ድንግል_ሆይ....የመጣብንን እሳት ፡ከፊታችን
የቆመውን ደንቃራ በቃህ እንዲለው #በልጅሽ ፈት ቁሚልን ።
#እናታችን__ሆይ ...አለማችን የዶኪማስን ቤት ሆኗል ፡ ሠርጉ ወደ ሙሾ ጠጁም ወደ መርዝነት ተቀይሯልና ....እንደ ልማድሽ ልጄ ሆይ በይልን ።
ከቀኝ ከግራ የሌለው የቃል ኪዳን ሕዝብሽን ሞት እንዳይበላው መድኃኒት ተብሎ ከተጠራው ልጅሽ ለምኚልን ። አንቺ #በሥላሴ ፊት ሞገስ ያለሽ ሙሽራ ማርያም ሆይ ሠዓሊ ለነ እያልን በፊትሽ የመረረ #እንባችንን እናፈሳላን ። ሚረዳን የልጅሽ እጅ ሚፈውሰንም እርሱ ብቻ ነውና ዝም አትበይ ።
ኢየሩሳሌምን ስለ ዳዊት የጋረድካት ጌታ ሆይ ስለ እናትህ ብለህ የሚሮጠውን መልአከ ሞት ያዘው። ደምህ ይጋርደን #ሐጢአታችንን_አታስብብን
የእናታችን እረድኤት በረከት ፍቅር አይለየን አሜን 🙏🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
እንኳን #ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም ዓመታዊ ሰኔ ጐልጐታና ሕንጸተ ቤተ ቤተክርስቲያን (ሕንጸታ) በሰላም አደረሳችኹ
#ድንግል_ሆይ_ዝም_አትበይ🙏😢😢
ጨለማችን ጨልሟል ውስጣችን ቃል በሌለው #ኃዘን ውስጥ ወድቋል ። አሰገራሚው መድኃኒት በውስጥሸ የተገኘ ፡ ምድርን የሸፈነ ፀሐይ የተገለጠብሽ #የዳዊት ልጅ እናታችን ማርያም ሆይ ዝም አትበይ በእውነት ዝም አትበይ ። ትላንት ልመናሽ እንደጋረደን ዛሬም #ቃል_ኪዳንሽ ጥላ ይሁነን ።
#ድንግል_ሆይ....የመጣብንን እሳት ፡ከፊታችን
የቆመውን ደንቃራ በቃህ እንዲለው #በልጅሽ ፈት ቁሚልን ።
#እናታችን__ሆይ ...አለማችን የዶኪማስን ቤት ሆኗል ፡ ሠርጉ ወደ ሙሾ ጠጁም ወደ መርዝነት ተቀይሯልና ....እንደ ልማድሽ ልጄ ሆይ በይልን ።
ከቀኝ ከግራ የሌለው የቃል ኪዳን ሕዝብሽን ሞት እንዳይበላው መድኃኒት ተብሎ ከተጠራው ልጅሽ ለምኚልን ። አንቺ #በሥላሴ ፊት ሞገስ ያለሽ ሙሽራ ማርያም ሆይ ሠዓሊ ለነ እያልን በፊትሽ የመረረ #እንባችንን እናፈሳላን ። ሚረዳን የልጅሽ እጅ ሚፈውሰንም እርሱ ብቻ ነውና ዝም አትበይ ።
ኢየሩሳሌምን ስለ ዳዊት የጋረድካት ጌታ ሆይ ስለ እናትህ ብለህ የሚሮጠውን መልአከ ሞት ያዘው። ደምህ ይጋርደን #ሐጢአታችንን_አታስብብን
የእናታችን እረድኤት በረከት ፍቅር አይለየን አሜን 🙏🙏
አጫጭር ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች
•➢ 👇 ለማግኘት // 👇
@Enatachn_mareyam
@Enatachn_mareyam
❤18
† † †
[ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን ፥ አደረሳችሁ ! ]
🕊 ሰኔ ጎለጎታ 🕊
💖
" ምሕረትን የምትለምኚ ድንግል እናቱ ፤
አንድያው ልጅሽ አያጥፋን በከንቱ ! "
"በእንቲአነ በሊዮ ሰአሊተ ምሕረት እሙ ፤
ኢታማስን ግብረ እዴከ እንተ ለሐኮ ቀዲሙ ! " [ አርኬ ]
[ ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፭. ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ
፮. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፯. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፰. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘምስር [ሰማዕት]
፱. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ዻዻሳት
† † †
💖 🕊 💖
[ እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን ፥ አደረሳችሁ ! ]
🕊 ሰኔ ጎለጎታ 🕊
💖
" ምሕረትን የምትለምኚ ድንግል እናቱ ፤
አንድያው ልጅሽ አያጥፋን በከንቱ ! "
"በእንቲአነ በሊዮ ሰአሊተ ምሕረት እሙ ፤
ኢታማስን ግብረ እዴከ እንተ ለሐኮ ቀዲሙ ! " [ አርኬ ]
[ ሰኔ ፳፩ [ 21 ] ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት ]
፩. እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም
፪. ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
፫. ቅዱሳን ሐዋርያት
፬. ቅዱስ ዼጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት
፭. ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ
፮. ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ
፯. ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ
፰. ቅዱስ ጢሞቴዎስ ዘምስር [ሰማዕት]
፱. አባ ከላድያኖስ ሊቀ ዻዻሳት
† † †
💖 🕊 💖
❤4