Telegram Web Link
Huawei Smart 4G LTE Wi-Fi Router -- SIM card Supported --High speed Up to 300mbps -- For home and office use -- Dual 2.4 & 5GHZ Band -- Can connect up to 64 Devices -- Can accept external antenna --4 Gigabit Ethernet port --Controlled by Its own Application --High security features --Additional Geust Wi-Fi with additional 1Km wide external indoor and outdoor antenna with free delivery
8,000 birr
@el_piko
" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል " - ትምህርት ሚኒስቴር

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ  ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል።

በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር  ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ በይፋ አሳውቋል።

#ትምህርት_ሚኒስቴር

https://www.tg-me.com/Ethio_Entrance_preparation
https://www.tg-me.com/Ethio_Entrance_preparation
Entrance pinned «" የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል " - ትምህርት ሚኒስቴር የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ  ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል። በዚህም ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴር  ነገ መስከረም 28/2016 ዓ.ም ከ ቀኑ ስድስት ሰዓት ላይ ጋዜጣዊ መግለጫ እንደሚሰጥ በይፋ አሳውቋል። #ትምህርት_ሚኒስቴር https://www.tg-me.com/Ethio_Entrance_preparation https://t.m…»
እንደሚታወቀው ነገ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ውጤት ነገ ይፋ ይሆናል ስለዚህ የኔትወርክ መጨናነቅ ሊኖር ስለሚችል ውጤት እንዲታይላችሁ የምትፈልጉ ልጆች በ @Ethio_Entrance_preparation_bot የፈተና ውጤት የሚታይበትን ቁጥራችሁን ላኩልን እንዲሁም ቻናሉን ሼር አርጉ

መልካም እድል
ውጤቱ እንዴት ነው ?

ከፍተኛ ውጤት ተፈጥሮ ሳይንስ 649 ፤ የማህበራዊ ሳይንስ 533 ሆኖ ተመዝግቧል።

649 ያመጣችው የአዲስ አበባ ልደታ ክሩዝ ትምህርት ቤት ስትሆን 533 ያመጣው ከደ/ማርቆስ አዲስ አለማየሁ ትምህርት ቤት ነው።
#Update

በአጠቃላይ በ2015 ዓ/ም ከተፈተኑ ተማሪዎች ውስጥ 3.2 በመቶ ብቻ ናቸው 50 በመቶ እና ከዛ በላይ ያስመዘገቡት።
#Update

27,267 ተማሪዎች ብቻ ናቸው ያለፉት፤ 3.2 በመቶ ማለት ነው።
#Update

ትምህርት ሚኒስቴር ዘንድሮም የሬሜዲያል ፕሮግራም እንደሚኖር አስታወቀ።

በቀጥታ ያለፉ ተማሪዎች ውስን ስለሆኑ ዘንድሮም የሬሜዲያል ፕሮግራም ይኖራል ተብሏል።

ፕ/ር ብርሃኑ አምና የገባሁትን ቃሌን በማጠፌ ይቅርታ ብለዋል።

ሚኒስትሩ አምና የሬሜዲያል ፕሮግራም ለአንድ ጊዜ የተሰጠ እድል ብቻ እንደሆነ መግለቸው ይታወሳል።
#Update

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በመግለጫቸው " 5 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል፡፡ " ብለዋል።

ሌሎች 5 ትምህርት ቤቶች ድግሞ ካስፈተኗቸው ውስጥ 95 ከመቶ ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉ ገልጸዋል።

ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦

1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት (ደብረማርቆስ)
2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት
3. ባህርዳር ስቴም ትምህርት ቤት
4. ሀይራንዚ አዳሪ ትምህርት ቤት (ስልጤ ዞን)
5. ሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት (ሀድያ)
6. ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት (አዳማ)
7. ኮተቤ ሼርድ ካምፓስ
8. የኔታ አካዳሚ
9. ወላይታሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት
10. ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት
ውጤት በምን ይታያል ?

" ነገ ጥዋት 12 ሰዓት ላይ በዌብሳይት እና በSMS ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት ይቻላሉ። " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ
Entrance pinned «ውጤት በምን ይታያል ? " ነገ ጥዋት 12 ሰዓት ላይ በዌብሳይት እና በSMS ተማሪዎች ውጤታቸውን ማየት ይቻላሉ። " - ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ»
ውጤት እንዴት መመልከት ይቻላል ?

የ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች መገ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ።

በዌብ ሳይት 👉 https://eaes.edu.et/

በአጭር የጽሑፍ መልዕክት 👉 6284

በቴሌግራም 👉 https://www.tg-me.com/eaesbot

#MoE
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ውጤታቸውን ማክሰኞ በ29/01/2016 ዓ.ም ከጥዋቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ ማየት ይችላሉ ብሏል።

ተፈታኞች የሚከተሉትን 3 አማራጭ አድራሻዎችን #ብቻ በመጠቀም ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ፡፡ 
    
👉 በዌብ ሳይት፡- eaes.et
👉 በአጭር የጽሁፍ መልዕክት፡- 6284
👉 ቴሌግራም አድራሻ፡- @eaesbot

አገልግሎቱ ከላይ ከተገለጹት የውጤት መግለጫ አማራጮች ውጪ ሌላ የውጤት መግለጫ መንገዶች የሌሉ መሆኑን አሳውቋል።
ተማሪዎች በማመሳሰል " ውጤት እንገልጻለን " ከሚሉ ከማንኛውም አጭበርባሪዎች እራሳቸውን እንዲጠብቁ መልዕክት ተለልፏል።

በተጨማሪ ተቋሙ ውጤት ለማሳየት ምንም ክፍያ የማይጠይቅ መሆኑን አስገንዝቧል።

እንዴት ውጤት ልመልከት ?

በዌብ ሳይት ለማየት ፦

1. eaes.et ብለው ብሮውዘር ላይ ይጻፉ
2. በመቀጠልም በሚመጣው ገጽ ላይ የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) እና የመጀመሪያ ስም ይጻፉ
3. Check Result የሚለውን በመጫን ውጤትዎን ማግኘት ይችላሉ።

በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ፦

1. 6284 የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ብቻ ጽፎ አንዴ ብቻ በመላክ መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ።

በቴሌግራም ቦት ፦

1. @eaesbot ይፈልጉ

2. የሚመጡ አማራጮችን በመከተል የአድሚሽን ቁጥር (ሬጅስትሬሽን ቁጥር) ያስገቡ በመቀጠልም መልስ እስኪያገኙ ይጠብቁ፡፡
አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ
በ2015ዓ.ም ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ!

በመሆኑም በ2016ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲተያችን ገብተው በአፕላድ ተፈጥሮ ሳይንስ እና በኢንጂነሪንግ የትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን መከታተል ለሚፈልጉ በ2015ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ወስዳችሁ ከ50% አና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጡትን ተማሪዎች ተቀብሎ ማተማር ይፈልጋል ፡፡

ዩኒቨርሲቲያችን ልዩ ከሚያደርጉት ነገሮች ውስጥ፡👇
• ተማሪዎች የራሳቸው ካሪኩለም (Curriculum)መቅረጽ መቻላቸው

• አቅም ያላቸው ተማሪዎችን በአንድ ጊዜ በሁለት ሜጀር (Dual Major /minor) መመረቅ መቻላቸው

• አቅም ያላቸውን ተማሪዎች በተፋጠነ ጊዜ የመጀመሪያና ሁለተኛ ዲግሪ የማግኘ ትዕድል (Fast track) ማግኘት

• ያሉን ፕሮግራሞች በሙሉ አለማአቀፍ እውቅና ያላቸው እንድሆኑ እየተሰራ መሆኑን እየገለፅን ፡-

በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ መማር የምትፈልጉ ተማሪዎች በትምህርት ሚኒስቴር ዌብሳይት ውስጥ ገብታችሁ ዩኒቨርሲቲያችንን መምረጥ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን በመጀመሪያ ድግሪ የሚሰጡ ፕሮግራሞች የሚከተሉት መሆኑን እንገልጻለን፡፡

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ👇
በኢንጂነሪንግ                               

Architecture
Civil Engineering
Water Resource Engineering
Chemical engineering
Mechanical engineering
Material science engineering
Electrical power &Control Engine..
Electronics & Communication eng
Computer science engineering
Software Engineering

Applied science

Applied Natural Biology
Applied Chemistry
Industrial Chemistry
Pharmacy & Applied Mathematics
Applied Physics
Applied Geology
እናት ፓርቲ የ2015 ዓ፣ም የ12ኛ ክፍል አገር ዓቀፍ ብሄራዊ ፈተና ተፈታኞች በድጋሚ ለፈተናው እንዲቀመጡ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠይቋል። የፈተናው ውጤት፣ የትምህርት ሥርዓቱ የትምህርት ሚንስቴር ውድቀት ማሳያና የሚንስቴሩን የአሠራር ሂደት፣ የፈተና አወጣጥ፣ የግምገማና መለኪያ መንገዶች ተዓማኒነት ጥያቄ ውስጥ ያስገባ እንደኾነ ፓርቲው ገልጧል። የፈተናው ውጤት፣ በተፈታኝ ተማሪዎች ላይ "ከፍተኛ ተስፋ መቁረጥ" እና "የማይሽር ሥነ ልቡናዊ ተጽዕኖ" እንዳሳደረም ፓርቲው በመግለጫው አውስቷል። ፓርቲው፣ ከተፈታኞች መካከል 97 በመቶዎቹ ወድቀዋል መባሉ "ትምህርት ሚንስቴር ከመንግሥት ጋር የተዋዋለው ድብቅ አጀንዳ እንዳለ ያመለክታል" በማለትም ጥርጣሬውን ገልጧል። ፓርቲው አያይዞም፣ ያለ በቂ ምክክር፣ ምርምርና ግምገማ "በፖለቲካዊ ውሳኔ" ተግባራዊ የተደረገው አዲስ የትምህርት ፍኖተ ካርታ ትልቅ ኪሳራ ፈጥሯል ብሏል። የትምህርት ሚንስቴር አሠራር ከፖለቲካ ጥገኝነት እንዲላቀቅም እናት ፓርቲ ጠይቋል።
2025/07/05 20:22:35
Back to Top
HTML Embed Code: