አንድ ሰው ወደ ጠፈር ጉዞ ሲያስብ
ምን ያስፈልገዋል ?
ISS- international Space Station-
1. ጉዞው ከመሬት ከ6 ስአት 24 ስአት ይፈጃል::
2. ትንሹ ጠረፍ ላይ ለመቀመጥ ከ8 እስከ 10 ቀን ሲሆን::
ትልቁ ደሞ 1 ወር ይሆናል ::
3.አሁን ላይ 4 ድርጅቶች ሰዎችን በቱሪስትነት ወደ ጠፈር እየወስዱ ይገኛል
እነሱም
* Axiom Space (USA)
* SpaceX (USA)
* Roscosmos (Russia)
* Space Adventures (USA)
ወደፊት ደሞ :-
* Blue Origin (USA – Jeff Bezos)
* Virgin Galactic (USA – Richard Branson )
ሰዎችን ለማጏጏዝ አስበዋል::
ወደ ዋናው ጥያቄ ስንገባ ስንት ብር ያስፍልጋል ወይንም እነዚህ ድርጅቶች ስንት ዶላር ተቀብለው ነው ሰውን ወደ ጠፈር የሚልኩት ሲባል ደሞ
* ከእነ ምግብ
* ትምህርቱ
* Medical cover
* ከእነ ሁሉም ነገር
* VIP treatment
አሁን ላይ ለአንድ ሰው (per person)
* 55 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን
ወደ ብር ሲመነዘር ደሞ በባንክ ምንዛሬ
6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ይሆናል
ነገር ግን እነ Elon Musk ወደፊት በአንድ ሰው ከ5 ሚሊዮን ዶላር እስከ 20 ሚሊዮን ዶላር ለማስከፈል ብዙ ሰራ እየሰሩ ሲሆን
ይህን ነገር እውን የሚሆነው በሚቀጥለው 10 ዓመት ወይንም ከዚህ ቀደም ባሉ ዓመታት ነውም ተብሏል::
ለ14 ቀን ወይንም ለ1 ወር ወደ ጠፈር 6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ከፍለው መሄድ ይፈልጋሉ
እንግዲያው ከላይ ያሉትን ድርጅቶች ያናግሩ::
መልካም ጉዞ::
ምን ያስፈልገዋል ?
ISS- international Space Station-
1. ጉዞው ከመሬት ከ6 ስአት 24 ስአት ይፈጃል::
2. ትንሹ ጠረፍ ላይ ለመቀመጥ ከ8 እስከ 10 ቀን ሲሆን::
ትልቁ ደሞ 1 ወር ይሆናል ::
3.አሁን ላይ 4 ድርጅቶች ሰዎችን በቱሪስትነት ወደ ጠፈር እየወስዱ ይገኛል
እነሱም
* Axiom Space (USA)
* SpaceX (USA)
* Roscosmos (Russia)
* Space Adventures (USA)
ወደፊት ደሞ :-
* Blue Origin (USA – Jeff Bezos)
* Virgin Galactic (USA – Richard Branson )
ሰዎችን ለማጏጏዝ አስበዋል::
ወደ ዋናው ጥያቄ ስንገባ ስንት ብር ያስፍልጋል ወይንም እነዚህ ድርጅቶች ስንት ዶላር ተቀብለው ነው ሰውን ወደ ጠፈር የሚልኩት ሲባል ደሞ
* ከእነ ምግብ
* ትምህርቱ
* Medical cover
* ከእነ ሁሉም ነገር
* VIP treatment
አሁን ላይ ለአንድ ሰው (per person)
* 55 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን
ወደ ብር ሲመነዘር ደሞ በባንክ ምንዛሬ
6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ይሆናል
ነገር ግን እነ Elon Musk ወደፊት በአንድ ሰው ከ5 ሚሊዮን ዶላር እስከ 20 ሚሊዮን ዶላር ለማስከፈል ብዙ ሰራ እየሰሩ ሲሆን
ይህን ነገር እውን የሚሆነው በሚቀጥለው 10 ዓመት ወይንም ከዚህ ቀደም ባሉ ዓመታት ነውም ተብሏል::
ለ14 ቀን ወይንም ለ1 ወር ወደ ጠፈር 6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ከፍለው መሄድ ይፈልጋሉ
እንግዲያው ከላይ ያሉትን ድርጅቶች ያናግሩ::
መልካም ጉዞ::
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
ብሔራዊ ሙዚዬም ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት ይሆናል
ባለፉት ወራት ለእድሳት ተዘግቶ የቆየው ብሔራዊ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት እንደሚሆን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ወራት ለእድሳት ተዘግቶ የቆየው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚዬም ከነገ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ለህዝብ ክፍት ይሆናል፡፡
በ1965 የተሰራው ብሔራዊ ሙዚየሙ የውሃ መፋሰሻ መቀየርና ዙሪያውን ማስተካከል እንዲሁም ሙዚዬሙ ውስጥ ለእይታ የቀረቡ ቅርሶች እንዳይጎዱ መስራት መቻሉን ተናረዋል፡፡
ውስጥ ላይ ያለውን የሙዚዬሙን ቋሚ ኤግዚቢሽን ደረጃን የማሻሻል ሥራ ተሰርቷል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ ቅርብ ዘመን የኢትዮጵያን ታሪክ በሚያሳይ መልኩ እድሳት ተደርጎለታል ብለዋል፡፡
ሙዚዬሙ ቀደም ሲል የሰውን ልጅ አመጣጥና የድንጋይ መሳሪያዎችን ለእይታ ሲቀርቡበት መቆየቱን በመግለጽ፤ አሁን ሥነ ህይወታዊ ዝግመተ ለውጥ በሚያሳይ መልኩ መዘጋጀቱን አመላክተዋል፡፡
ሙዚዬሙ ዛሬ ምሽት ላይ እንደሚመረቅ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት ይደረጋል።
#ኢፕድ
ባለፉት ወራት ለእድሳት ተዘግቶ የቆየው ብሔራዊ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት እንደሚሆን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን አስታወቀ።
የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ወራት ለእድሳት ተዘግቶ የቆየው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚዬም ከነገ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ለህዝብ ክፍት ይሆናል፡፡
በ1965 የተሰራው ብሔራዊ ሙዚየሙ የውሃ መፋሰሻ መቀየርና ዙሪያውን ማስተካከል እንዲሁም ሙዚዬሙ ውስጥ ለእይታ የቀረቡ ቅርሶች እንዳይጎዱ መስራት መቻሉን ተናረዋል፡፡
ውስጥ ላይ ያለውን የሙዚዬሙን ቋሚ ኤግዚቢሽን ደረጃን የማሻሻል ሥራ ተሰርቷል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ ቅርብ ዘመን የኢትዮጵያን ታሪክ በሚያሳይ መልኩ እድሳት ተደርጎለታል ብለዋል፡፡
ሙዚዬሙ ቀደም ሲል የሰውን ልጅ አመጣጥና የድንጋይ መሳሪያዎችን ለእይታ ሲቀርቡበት መቆየቱን በመግለጽ፤ አሁን ሥነ ህይወታዊ ዝግመተ ለውጥ በሚያሳይ መልኩ መዘጋጀቱን አመላክተዋል፡፡
ሙዚዬሙ ዛሬ ምሽት ላይ እንደሚመረቅ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት ይደረጋል።
#ኢፕድ
የኢትዮጵያ አምባሳደር የፓሃልጋም ጥቃትን በማውገዝ ፓኪስታንን ተጠያቂ አደረጉ
የኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር የሆኑት አቶ ፈስሃ ሻወል ፣ በጃሙ እና ካሽሚር በሚገኘው ፓሃልጋም ላይ ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም የተፈፀመውን የሽብር ጥቃት በብርቱ አውግዘው፣ ለጥቃቱ ሙሉ ሃላፊነት ፓኪስታን እንደሆነች በግልጽ አስታውቀዋል።
ይህ ጥቃት 26 ንጹሃን ዜጎችን ለህልፈት የዳረገ ሲሆን፣ የተፈፀመውም በፓኪስታን ድጋፍ ባላቸው አሸባሪዎች መሆኑ በህንድም ሆነ በአለም አቀፍ አጋሮቿ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።
የሽብርተኝነት ኩነና እና የህንድ ምላሽ ምስጋና
አምባሳደር ገብሬ ፣ ህንድ ለዚህ አሰቃቂ ጥቃት የሰጠችውን ምላሽ “በጣም ሃላፊነት የሚሰማው”፣ የተረጋጋ እና ጽኑ ነበር ሲሉ አሞካሽተዋል።
እንደ አኒ ዘገባ በአለም አቀፍ የሽብርተኝነት ትግል ኢትዮጵያ እና ህንድ የጋራ እሴቶች እንዳሏቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።
አምባሳደሩ፣ “ችግር ለመፍጠር ወደ ፓኪስታን የሄዱት ህንዳውያን አይደሉም፤ ችግር ለመፍጠር ወደ ህንድ የመጡት ፓኪስታናውያን ናቸው” በማለት፣ ኢስላማባድ በአጥቂዎቹ ላይ ያላትን ቀጥተኛ ተሳትፎ በግልጽ አውስተዋል።
የኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር የሆኑት አቶ ፈስሃ ሻወል ፣ በጃሙ እና ካሽሚር በሚገኘው ፓሃልጋም ላይ ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም የተፈፀመውን የሽብር ጥቃት በብርቱ አውግዘው፣ ለጥቃቱ ሙሉ ሃላፊነት ፓኪስታን እንደሆነች በግልጽ አስታውቀዋል።
ይህ ጥቃት 26 ንጹሃን ዜጎችን ለህልፈት የዳረገ ሲሆን፣ የተፈፀመውም በፓኪስታን ድጋፍ ባላቸው አሸባሪዎች መሆኑ በህንድም ሆነ በአለም አቀፍ አጋሮቿ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።
የሽብርተኝነት ኩነና እና የህንድ ምላሽ ምስጋና
አምባሳደር ገብሬ ፣ ህንድ ለዚህ አሰቃቂ ጥቃት የሰጠችውን ምላሽ “በጣም ሃላፊነት የሚሰማው”፣ የተረጋጋ እና ጽኑ ነበር ሲሉ አሞካሽተዋል።
እንደ አኒ ዘገባ በአለም አቀፍ የሽብርተኝነት ትግል ኢትዮጵያ እና ህንድ የጋራ እሴቶች እንዳሏቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።
አምባሳደሩ፣ “ችግር ለመፍጠር ወደ ፓኪስታን የሄዱት ህንዳውያን አይደሉም፤ ችግር ለመፍጠር ወደ ህንድ የመጡት ፓኪስታናውያን ናቸው” በማለት፣ ኢስላማባድ በአጥቂዎቹ ላይ ያላትን ቀጥተኛ ተሳትፎ በግልጽ አውስተዋል።
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ሊጓዙ ነው ተባለ‼️ ጠ/ሚኒስትሩ ጠፈር ላይ በመሆን ለአለም ህዝብ የሰላም መልዕክት ለማስተላለፍ አቅደዋል። የጉዞ እቅዱ ከተሳካ ወደ ጠፈር የተጓዙ የመጀመርያው የአለማችን መሪም ያደርጋቸዋል። በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት…
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ሊጓዙ ነው' ዝርዝር ዘገባ...!!!
በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት ግን ጥቂት ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል የዝቅተኛው ንፍቀ ክበብ የጠፈር ጉብኝት አድርገዋል።
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።
በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።
"ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው" ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።
'Project X' የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።
ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።
ለምሳሌ 'Blue Origin' እና 'Virgin Galactic' የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር እስከ 400 ሺህ ዶላር ያስከፍላሉ፣ ራቅ ያሉ እና ከንፍቀ ክበብ ውጪ የሚደረጉ የጠፈር በረራዎችን የሚያከናውኑት እንደ 'Space X' ያሉ ሮኬቶች ደግሞ በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር (7.3 ቢልዮን ብር) እንደሚያስከፍሉ ታውቋል።
ጠ/ሚር አብይ ሊጓዙ እቅድ የያዙት ከንፍቀ ክበብ ውጪ ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ማዕከል (International Space Station) እንደሆነ ታውቋል፣ ወጪውም ከላይ እንደተጠቀሰው በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ እና በኤምሬቶች እንደሚሸፈን ታውቋል።
አንድ ሌላ የስፔስ ባለሙያ ግን የጉብኝቱ አይነት 'lunar' የሚባለው እንደሆነ ሲገለፅ እንደሰሙ ጠቅሰው ይህም ጨረቃ ላይ ሳይታረፍ፣ ዙርያውን በመሄድ የሚደረግ ጉዞ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬት የዛሬ ስድስት አመት ገደማ ሀዛ አል-ማንሱሪ የተባለ ዜጋዋን ወደ ጠፈር ልካ ነበር። ከዛ ወዲህም ከአሜሪካው የጠፈር ድርጅት ናሳ ጋር በመተባበር በመጪው የፈረንጆቹ አመት 2026 ላይ ሰው ወደ ጨረቃ ለመላክ እየተዘጋጀች መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ከጉዞው ጋር በተገናኘ ሂደቱን ተከታትለው እንዲያስፈፅሙ ቢያንስ አምስት የሚሆኑ የመንግስት ሀላፊዎች የቤት ስራ እንደተሰጣቸው የሀገር ቤት ምንጮች አረጋግጠዋል። ይህ የቤት ስራ እስከ ሀምሌ 2017 ዓ/ም ድረስ ንግግሮችን በመጨረስ ከመስከረም በሗላ ጉዞው እንዲከናወን ማድረግ ነው ተብሏል።
ነገር ግን ጠ/ሚሩ ወደ ጠፈር ከመጓዛቸው በፊት ለበርካታ ወራት ልምምድ እና የጤና ሁኔታ ክትትል ማድረግ እንደሚጠብቃቸው አስረድተዋል።
አንድ ስማቸውን የማንጠቅሳቸው የመንግስት ሀላፊን በጉዳዩ ዙርያ መረጃ ጠይቀን "በመጪው አመታት ከተያዙ እቅዶች ውስጥ አንዱ ነው። ለኢትዮጵያ እና ለአለም ሕዝብ የእርቅ እና ሰላም ጥሪ ይደረጋል" ብለው አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
መሠረት ሚዲያ
በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት ግን ጥቂት ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል የዝቅተኛው ንፍቀ ክበብ የጠፈር ጉብኝት አድርገዋል።
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።
በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።
"ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው" ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።
'Project X' የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።
ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።
ለምሳሌ 'Blue Origin' እና 'Virgin Galactic' የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር እስከ 400 ሺህ ዶላር ያስከፍላሉ፣ ራቅ ያሉ እና ከንፍቀ ክበብ ውጪ የሚደረጉ የጠፈር በረራዎችን የሚያከናውኑት እንደ 'Space X' ያሉ ሮኬቶች ደግሞ በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር (7.3 ቢልዮን ብር) እንደሚያስከፍሉ ታውቋል።
ጠ/ሚር አብይ ሊጓዙ እቅድ የያዙት ከንፍቀ ክበብ ውጪ ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ማዕከል (International Space Station) እንደሆነ ታውቋል፣ ወጪውም ከላይ እንደተጠቀሰው በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ እና በኤምሬቶች እንደሚሸፈን ታውቋል።
አንድ ሌላ የስፔስ ባለሙያ ግን የጉብኝቱ አይነት 'lunar' የሚባለው እንደሆነ ሲገለፅ እንደሰሙ ጠቅሰው ይህም ጨረቃ ላይ ሳይታረፍ፣ ዙርያውን በመሄድ የሚደረግ ጉዞ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።
የተባበሩት አረብ ኤምሬት የዛሬ ስድስት አመት ገደማ ሀዛ አል-ማንሱሪ የተባለ ዜጋዋን ወደ ጠፈር ልካ ነበር። ከዛ ወዲህም ከአሜሪካው የጠፈር ድርጅት ናሳ ጋር በመተባበር በመጪው የፈረንጆቹ አመት 2026 ላይ ሰው ወደ ጨረቃ ለመላክ እየተዘጋጀች መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
ከጉዞው ጋር በተገናኘ ሂደቱን ተከታትለው እንዲያስፈፅሙ ቢያንስ አምስት የሚሆኑ የመንግስት ሀላፊዎች የቤት ስራ እንደተሰጣቸው የሀገር ቤት ምንጮች አረጋግጠዋል። ይህ የቤት ስራ እስከ ሀምሌ 2017 ዓ/ም ድረስ ንግግሮችን በመጨረስ ከመስከረም በሗላ ጉዞው እንዲከናወን ማድረግ ነው ተብሏል።
ነገር ግን ጠ/ሚሩ ወደ ጠፈር ከመጓዛቸው በፊት ለበርካታ ወራት ልምምድ እና የጤና ሁኔታ ክትትል ማድረግ እንደሚጠብቃቸው አስረድተዋል።
አንድ ስማቸውን የማንጠቅሳቸው የመንግስት ሀላፊን በጉዳዩ ዙርያ መረጃ ጠይቀን "በመጪው አመታት ከተያዙ እቅዶች ውስጥ አንዱ ነው። ለኢትዮጵያ እና ለአለም ሕዝብ የእርቅ እና ሰላም ጥሪ ይደረጋል" ብለው አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።
መሠረት ሚዲያ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለስራ ጉብኝት ፈረንሳይ ፓሪስ ገቡ!
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ልዑክ ጋር በመሆን ለስራ ጉብኝት ዛሬ ፈረንሳይ ፓሪስ ገብተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓሪስ ሲደርሱ በብሔራዊው የጦር ኃይሎች ሙዚየም የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ተደርጎላቸዋል።
በጉብኝታቸው ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ልዑክ ጋር በመሆን ለስራ ጉብኝት ዛሬ ፈረንሳይ ፓሪስ ገብተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓሪስ ሲደርሱ በብሔራዊው የጦር ኃይሎች ሙዚየም የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ተደርጎላቸዋል።
በጉብኝታቸው ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።
‹‹መንግስት በአድማ ላይ ካሉ የጤና ባለሙያዎች ጋር ድርድር ያድርግ፣ የታሰሩትንም ይፍታ›› ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ
የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው ይህ ተቋም ዛሬ ባወጣው መግለጫ አድማው ከተጀመረ አንስቶ በመላው አገሪቱ 212 የጤና ባለሙያዎች መታሰራቸውን ከጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ መስማቱንና የታሰሩት ሰዎች ስም ዝርዝር እንደተላከለትም አስረድቷል፡፡
የታሰሩት ሰዎች ቤተሰቦችና ጠበቆችን ማነጋገሩን የጠቀሰው አምነስቲ ሰዎቹ ሲታሰሩ ምክንያቱ እንዳልተገለፀላቸው መግለፃቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲሁም ያለ ብርበራ ትእዛዝ የጤና ባለሙያዎቹን ቤት ‹‹ጦር መሳሪያ ይኖራል›› በሚል መፈተሻቸውንና የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶቻቸው መወሰዳቸውን ገልጿል፡፡
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ትግሪ ቻጉታ ሲናገሩ ‹‹ይህ አድማ ምንም አይነት መፍትሄ ሳይገኝለት ወደሁለተኛ ሳምንቱ እየተሸጋገረ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በመላ አገሪቱ ወሳኝ በሆኑ የጤና አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎልን ፈጥሯል፡፡ በመሆኑም መንግስት የታካሚዎችን መብት የሚገድበውን ይህንን ቀውስ ከዚህ በላይ ማራዘም የለበትም፡፡ መንግስትም ሆነ የጤና ባለሙያዎቹ ይህንን አለመግባባት በድርድር ሊፈቱ ይገባል›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹የዘፈቀደ እስር ከዚህ ቀደም ለተለያዩ ጉዳዮች ኢትዮጵያ ውስጥ የታየ ሲሆን አሁን ደግሞ ተገቢ ክፍያና የስራ ሁኔታ በጠየቁ የህክምና ባለሙያዎች ላይ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡›› ብለዋል፡፡ አምነስቲ በመግለጫው በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ማቅረብ መብታቸውን ተግባራዊ ባደረጉ የጤና ባለሙያዎች ላይ እየተደረገ ያለው የእስር ዘመቻ እንዲቆምና ችግሩ በንግግር እንዲፈታ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው ይህ ተቋም ዛሬ ባወጣው መግለጫ አድማው ከተጀመረ አንስቶ በመላው አገሪቱ 212 የጤና ባለሙያዎች መታሰራቸውን ከጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ መስማቱንና የታሰሩት ሰዎች ስም ዝርዝር እንደተላከለትም አስረድቷል፡፡
የታሰሩት ሰዎች ቤተሰቦችና ጠበቆችን ማነጋገሩን የጠቀሰው አምነስቲ ሰዎቹ ሲታሰሩ ምክንያቱ እንዳልተገለፀላቸው መግለፃቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲሁም ያለ ብርበራ ትእዛዝ የጤና ባለሙያዎቹን ቤት ‹‹ጦር መሳሪያ ይኖራል›› በሚል መፈተሻቸውንና የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶቻቸው መወሰዳቸውን ገልጿል፡፡
የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ትግሪ ቻጉታ ሲናገሩ ‹‹ይህ አድማ ምንም አይነት መፍትሄ ሳይገኝለት ወደሁለተኛ ሳምንቱ እየተሸጋገረ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በመላ አገሪቱ ወሳኝ በሆኑ የጤና አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎልን ፈጥሯል፡፡ በመሆኑም መንግስት የታካሚዎችን መብት የሚገድበውን ይህንን ቀውስ ከዚህ በላይ ማራዘም የለበትም፡፡ መንግስትም ሆነ የጤና ባለሙያዎቹ ይህንን አለመግባባት በድርድር ሊፈቱ ይገባል›› ብለዋል፡፡
ጨምረውም ‹‹የዘፈቀደ እስር ከዚህ ቀደም ለተለያዩ ጉዳዮች ኢትዮጵያ ውስጥ የታየ ሲሆን አሁን ደግሞ ተገቢ ክፍያና የስራ ሁኔታ በጠየቁ የህክምና ባለሙያዎች ላይ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡›› ብለዋል፡፡ አምነስቲ በመግለጫው በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ማቅረብ መብታቸውን ተግባራዊ ባደረጉ የጤና ባለሙያዎች ላይ እየተደረገ ያለው የእስር ዘመቻ እንዲቆምና ችግሩ በንግግር እንዲፈታ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የአሜሪካ ኤምባሲ "በራሱ ሕዝብ ላይ" የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶችን የማውገዝ መልዕክት ለወጠ
የአሜሪካ ኤምባሲ አዲስ አበባ፣ ከሰዓታት በፊት አውጥቶት የነበረውንና አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ የፌደራል መንግሥት "በራሱ ሕዝብ ላይ" የሚፈጽማቸውን የድሮን ጥቃቶች "በአፋጣኝ እንዲያቆም" ጥሪ ያቀረቡበትን ልጥፍ ከፌስቡክ እና ከቲውተር ገጾቹ ላይ አንስቶ ለውጥ አድርጓል።
በአዲስ መልክ በወጣው የአምባሳደሩ መልዕክት ላይ፣ የድሮን ጥቃትን በተመለከተ ለፌደራል መንግሥት የቀረበው ጥሪ "መንግሥት ከኃይል ውጪ ያሉ ሰላማዊ አማራጮችን መፈለጉን እንዲቀጥል" በሚጠይቅ ጥሪ ተተክቷል።
አምባሳደር ማሲንጋ ያስተላለፉት የመጀመሪያ መልዕክት በኤምባሲው የፌስቡክ እና ቲውተር ገጾች ላይ የተለጠፈው ዛሬ አርብ ግንቦት 15/2017 ዓ.ም. ከቀኑ 4 ሰዓት ተኩል ገደማ ነበር። በሀገሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማቆምን የተመለከተው የአምባሳደሩ መልዕክት፤ ለፌደራል መንግሥት፣ እንዲሁም ለፋኖ ኃይሎች እና ለኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የተለያዩ ጥሪዎች የቀረቡበት ነበር።
ለፌደራል መንግሥቱ ቀርቦ የነበረው የአምባሳደሩ የመጀመሪያ መልዕክት ሁለት ሀሳቦችን ያዘለ የነበረ ሲሆን፣ አንደኛው በመንግሥት የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች እንዲቆሙ የሚጠይቅ ነበር። የአምባሳደሩ የተጠቀሙት አገላለፅ የመንግሥት የድሮን ጥቃቶች "በራስ ሕዝብ ላይ" የሚፈጸሙ እንደሆኑ የሚያመለክት ነበር።
የአሜሪካ ኤምባሲ አዲስ አበባ፣ ከሰዓታት በፊት አውጥቶት የነበረውንና አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ የፌደራል መንግሥት "በራሱ ሕዝብ ላይ" የሚፈጽማቸውን የድሮን ጥቃቶች "በአፋጣኝ እንዲያቆም" ጥሪ ያቀረቡበትን ልጥፍ ከፌስቡክ እና ከቲውተር ገጾቹ ላይ አንስቶ ለውጥ አድርጓል።
በአዲስ መልክ በወጣው የአምባሳደሩ መልዕክት ላይ፣ የድሮን ጥቃትን በተመለከተ ለፌደራል መንግሥት የቀረበው ጥሪ "መንግሥት ከኃይል ውጪ ያሉ ሰላማዊ አማራጮችን መፈለጉን እንዲቀጥል" በሚጠይቅ ጥሪ ተተክቷል።
አምባሳደር ማሲንጋ ያስተላለፉት የመጀመሪያ መልዕክት በኤምባሲው የፌስቡክ እና ቲውተር ገጾች ላይ የተለጠፈው ዛሬ አርብ ግንቦት 15/2017 ዓ.ም. ከቀኑ 4 ሰዓት ተኩል ገደማ ነበር። በሀገሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማቆምን የተመለከተው የአምባሳደሩ መልዕክት፤ ለፌደራል መንግሥት፣ እንዲሁም ለፋኖ ኃይሎች እና ለኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የተለያዩ ጥሪዎች የቀረቡበት ነበር።
ለፌደራል መንግሥቱ ቀርቦ የነበረው የአምባሳደሩ የመጀመሪያ መልዕክት ሁለት ሀሳቦችን ያዘለ የነበረ ሲሆን፣ አንደኛው በመንግሥት የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች እንዲቆሙ የሚጠይቅ ነበር። የአምባሳደሩ የተጠቀሙት አገላለፅ የመንግሥት የድሮን ጥቃቶች "በራስ ሕዝብ ላይ" የሚፈጸሙ እንደሆኑ የሚያመለክት ነበር።
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉ ባለሙያዎችንና ተማሪዎችን አሰናበተ
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ፣ በቅርቡ በሥራ ማቆም አድማ የተሳተፉ የጤና ባለሙያዎችንና የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪዎችን (ኢንተርን) ለማሰናበት ወስኗል። ኮሌጁ በእነዚህ የሥራ ማቆም አድማ ተሳታፊዎች ምትክ አዲስ ቅጥር እንደሚፈጽምም አስታውቋል።
ኮሌጁ ባወጣው መግለጫ፣ ቅሬታ ያላቸው ባለሙያዎች እስከ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ በአካል ቀርበው ይቅርታ መጠየቅ እንደሚችሉ ገልጿል።
በተመሳሳይ፣ ከግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርትና በሥራ ላይ ባልተገኙ የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪዎች (ኢንተርን) ላይም ውሳኔ ተላልፏል።
የኮሌጁ ሴኔት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፣ እነዚህ ተማሪዎች ከትምህርታቸው እንዲሰናበቱ ተወስኗል። በዚህም ምክንያት፣ በእጃቸው ላይ የሚገኝ ንብረት አስረክበው ከግቢው እንዲወጡ ኮሌጁ አሳስቧል። ይሁን እንጂ፣ ቅሬታ ያለው ኢንተርን ይግባኝ መጠየቅ እንደሚችል ኮሌጁ አስታውቋል።
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ፣ በቅርቡ በሥራ ማቆም አድማ የተሳተፉ የጤና ባለሙያዎችንና የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪዎችን (ኢንተርን) ለማሰናበት ወስኗል። ኮሌጁ በእነዚህ የሥራ ማቆም አድማ ተሳታፊዎች ምትክ አዲስ ቅጥር እንደሚፈጽምም አስታውቋል።
ኮሌጁ ባወጣው መግለጫ፣ ቅሬታ ያላቸው ባለሙያዎች እስከ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ በአካል ቀርበው ይቅርታ መጠየቅ እንደሚችሉ ገልጿል።
በተመሳሳይ፣ ከግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርትና በሥራ ላይ ባልተገኙ የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪዎች (ኢንተርን) ላይም ውሳኔ ተላልፏል።
የኮሌጁ ሴኔት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፣ እነዚህ ተማሪዎች ከትምህርታቸው እንዲሰናበቱ ተወስኗል። በዚህም ምክንያት፣ በእጃቸው ላይ የሚገኝ ንብረት አስረክበው ከግቢው እንዲወጡ ኮሌጁ አሳስቧል። ይሁን እንጂ፣ ቅሬታ ያለው ኢንተርን ይግባኝ መጠየቅ እንደሚችል ኮሌጁ አስታውቋል።
ፌደራል ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ
የፌደራል ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና ምርመራ እያደረገባቸው እንደሚገኝ አስታውቋል።
ፖሊስ እንደገለጸው፣ በምርመራ ላይ ያሉት የጤና ባለሙያዎች ትርምስ እንዲፈጠር ከሚሠሩ ኃይሎች ጋር በመተባበር "ሕገወጥ የሥራ ማቆም አድማ" በማድረግ፣ "ሁከት" በመፍጠር፣ "የታካሚዎችን ሕይወት አደጋ ላይ በመጣል" እና በሥራ ላይ ያሉ የጤና ባለሙያዎች አድማውን እንዲቀላቀሉ "በማነሳሳት" ተጠርጥረዋል።
ፖሊስ በተጨማሪም፣ ተጠርጣሪዎቹ በጤና ተቋማት ውስጥ "የአድማ መረቦችን" በመዘርጋት፣ የጤና ባለሙያ ያልሆኑ ግለሰቦችን ነጭ ጋዋን በማስለበስ በሆስፒታሎች ቅጥር ግቢ "ሁከት" እንዲፈጥሩ በማድረግ፣ እንዲሁም በሥራ ላይ በተገኙ የጤና ባለሙያዎች ላይ "ዛቻ" እና "ማስፈራሪያ" በመፈጸም ጭምር እንደተጠረጠሩ ጠቅሷል።
የፌደራል ፖሊስ በመጨረሻም፣ ሁከትና ብጥብጥ ለማስፋፋት በሚሞክሩ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚቀጥል በማስጠንቀቂያ ገልጿል።
የፌደራል ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና ምርመራ እያደረገባቸው እንደሚገኝ አስታውቋል።
ፖሊስ እንደገለጸው፣ በምርመራ ላይ ያሉት የጤና ባለሙያዎች ትርምስ እንዲፈጠር ከሚሠሩ ኃይሎች ጋር በመተባበር "ሕገወጥ የሥራ ማቆም አድማ" በማድረግ፣ "ሁከት" በመፍጠር፣ "የታካሚዎችን ሕይወት አደጋ ላይ በመጣል" እና በሥራ ላይ ያሉ የጤና ባለሙያዎች አድማውን እንዲቀላቀሉ "በማነሳሳት" ተጠርጥረዋል።
ፖሊስ በተጨማሪም፣ ተጠርጣሪዎቹ በጤና ተቋማት ውስጥ "የአድማ መረቦችን" በመዘርጋት፣ የጤና ባለሙያ ያልሆኑ ግለሰቦችን ነጭ ጋዋን በማስለበስ በሆስፒታሎች ቅጥር ግቢ "ሁከት" እንዲፈጥሩ በማድረግ፣ እንዲሁም በሥራ ላይ በተገኙ የጤና ባለሙያዎች ላይ "ዛቻ" እና "ማስፈራሪያ" በመፈጸም ጭምር እንደተጠረጠሩ ጠቅሷል።
የፌደራል ፖሊስ በመጨረሻም፣ ሁከትና ብጥብጥ ለማስፋፋት በሚሞክሩ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚቀጥል በማስጠንቀቂያ ገልጿል።
ዲሽታ ጊና በሚል ተወዳጅ ዘፈኑ የሚታወቀው ድምጻዊ ታሪኩ ጋንኪሲ ሽልማት ለመቀበል ወደ አሜሪካን ሀገር ለመምጣት የቪዛ ጥያቄ አቅርቦ መከልከሉን መዝናኛ መጽሔት ዘግቧል።
በአሜሪካን ሐገር የሚገኘው ኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ዲቪሎፕመንት ካውንስል የተባለው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የተመሰረተበትን 42ኛ ዓመት ምስረታ በዓል አስመልክቶ፡ ለሰላም እና ለፍትህ የቆሙ ሦስት ግለሰቦችን በደመቀ ስነ ስርዓት የዕውቅና ሽልማት ባለፈው ሀሙስ መስጠቱ ተገልጿል።
"ታሪኩ ጋንጋሲ ለሰላም እና ለፍትህ መስፈን ላበረከተው ላቅ ያለ አስተዋፅዖ እንዲሸለም" ወደ አሜሪካ እንዲመጣ ተቋሙ ለኢምባሲው ደብዳቤ ጽፎ የነበረ ቢሆንም፤ ድምጻዊው ታሪኩ ጋንጋሲም ቪዛ ለመውሰድ ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ፣ አማርኛ ተናጋሪ የሆነው ፈረንጁ የቪዛ ኦፊሰር “ለምንድን ነው ወደ አሜሪካን ሀገር የምትሔደው?” ብሎ በአማርኛ ይጠይቀዋል።
ታሪኩም “በአሜሪካ፡ በቋሚነት ለመኖር” በሚል፡እንደመለሰና በዚህ የተነሳ የቪዛ ኦፊሰሩም ወደ ሃገርህ የመመለስ ዕቅድ የለህም በሚል ቪዛውን እንደከለከለው መጽሔቱ ዘግቦ አንብበናል። በዚህም ምክንያት ታሪኩ በሌለበት ሽልማቱ ተበርክቶለታል።
የዲሽታ ጊና ሙዚቃ አቀንቃኙ ታሪኩ፤ ከሽልማቱ በኋላ በቪዲዮ ተቀድቶ ከጂንካ ባስተላለፈው መልዕክት “ይህንን ሽልማት ስለሸለማችሁኝ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ፣ ወደ አሜሪካን ሀገር ለመምጣት አስቤ አልተሳካም፣ አሁን ጂንካ ተመልሼ በግብርና ሥራዬ ላይ ተሰማርቻለሁ" ብሏል።
በአሜሪካን ሐገር የሚገኘው ኢትዮጵያን ኮሚኒቲ ዲቪሎፕመንት ካውንስል የተባለው መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት የተመሰረተበትን 42ኛ ዓመት ምስረታ በዓል አስመልክቶ፡ ለሰላም እና ለፍትህ የቆሙ ሦስት ግለሰቦችን በደመቀ ስነ ስርዓት የዕውቅና ሽልማት ባለፈው ሀሙስ መስጠቱ ተገልጿል።
"ታሪኩ ጋንጋሲ ለሰላም እና ለፍትህ መስፈን ላበረከተው ላቅ ያለ አስተዋፅዖ እንዲሸለም" ወደ አሜሪካ እንዲመጣ ተቋሙ ለኢምባሲው ደብዳቤ ጽፎ የነበረ ቢሆንም፤ ድምጻዊው ታሪኩ ጋንጋሲም ቪዛ ለመውሰድ ቃለ መጠይቅ ሲያደርግ፣ አማርኛ ተናጋሪ የሆነው ፈረንጁ የቪዛ ኦፊሰር “ለምንድን ነው ወደ አሜሪካን ሀገር የምትሔደው?” ብሎ በአማርኛ ይጠይቀዋል።
ታሪኩም “በአሜሪካ፡ በቋሚነት ለመኖር” በሚል፡እንደመለሰና በዚህ የተነሳ የቪዛ ኦፊሰሩም ወደ ሃገርህ የመመለስ ዕቅድ የለህም በሚል ቪዛውን እንደከለከለው መጽሔቱ ዘግቦ አንብበናል። በዚህም ምክንያት ታሪኩ በሌለበት ሽልማቱ ተበርክቶለታል።
የዲሽታ ጊና ሙዚቃ አቀንቃኙ ታሪኩ፤ ከሽልማቱ በኋላ በቪዲዮ ተቀድቶ ከጂንካ ባስተላለፈው መልዕክት “ይህንን ሽልማት ስለሸለማችሁኝ እጅግ በጣም አመሰግናለሁ፣ ወደ አሜሪካን ሀገር ለመምጣት አስቤ አልተሳካም፣ አሁን ጂንካ ተመልሼ በግብርና ሥራዬ ላይ ተሰማርቻለሁ" ብሏል።
በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የማንኪፖክስ ቫይረስ ተገኘ
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አንድ የ21 ቀን ህፃን ልጅ በMpox ( ማንኪፖክስ) ቫይረስ መያዙን አረጋገጠ። ይህ በአገር ውስጥ የተመዘገበ የመጀመሪያው የቫይረሱ ተጠቂ መሆኑ ተገልጿል ።
ህፃኑን ተከትሎ በተደረገ ምርመራ የእናቱም ለቫይረሱ መጋለጥ ተረጋግጧል። የህፃኑ አባት ወደ ጎረቤት ሀገር ሄዶ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን፣ ከእሱ ጋር የቅርብ ንክኪ የነበራቸው ግለሰቦችን የመለየትና ክትትል የማድረግ ስራ ተጀምሯል ተብሏል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው ህፃኑ እና እናቱ በተዘጋጀ የለይቶ ማከሚያ ክፍል ተገቢው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፣ እስካሁን ከባድ የጤና እክል እንዳልገጠማቸው ሁሉቱ መንግስታዊ የጤና ተቋማት ባወጡት መግለጫ አስታዉቀዋል።
የMpox በሽታ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት እየተከሰተ ያለ ህመም ሲሆን፣ የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል እና የዓለም ጤና ድርጅት በሽታውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በጋራ እየሰሩ መሆናቸው ተጠቁሟል ።
Capital Newspaper
የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በኦሮሚያ ክልል ሞያሌ ከተማ አንድ የ21 ቀን ህፃን ልጅ በMpox ( ማንኪፖክስ) ቫይረስ መያዙን አረጋገጠ። ይህ በአገር ውስጥ የተመዘገበ የመጀመሪያው የቫይረሱ ተጠቂ መሆኑ ተገልጿል ።
ህፃኑን ተከትሎ በተደረገ ምርመራ የእናቱም ለቫይረሱ መጋለጥ ተረጋግጧል። የህፃኑ አባት ወደ ጎረቤት ሀገር ሄዶ እንደነበር የተገለጸ ሲሆን፣ ከእሱ ጋር የቅርብ ንክኪ የነበራቸው ግለሰቦችን የመለየትና ክትትል የማድረግ ስራ ተጀምሯል ተብሏል።
ቫይረሱ የተገኘባቸው ህፃኑ እና እናቱ በተዘጋጀ የለይቶ ማከሚያ ክፍል ተገቢው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፣ እስካሁን ከባድ የጤና እክል እንዳልገጠማቸው ሁሉቱ መንግስታዊ የጤና ተቋማት ባወጡት መግለጫ አስታዉቀዋል።
የMpox በሽታ በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት እየተከሰተ ያለ ህመም ሲሆን፣ የአፍሪካ የበሽታ መከላከልና መቆጣጠር ማዕከል እና የዓለም ጤና ድርጅት በሽታውን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር በጋራ እየሰሩ መሆናቸው ተጠቁሟል ።
Capital Newspaper
Forwarded from Capitalethiopia
#CapitalNews የኢንሹራንስ ዘርፉ ለዉጪ ባለሃብቶች ክፍት እንዲሆን የሚያስችል አዲስ አዋጅ በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተነገረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የሚያደርግ አዲስ አዋጅ በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታውቋል።
ውሳኔው የኢትዮጵያን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ለማዘመን እየተደረገ ካለው ሰፊ ጥረት አንዱ አካል ነው ተብሏል።
ይህ የተገለጸው 51ኛው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ተቋም ዓመታዊ ኮንፈረንስ እና አጠቃላይ ስብሰባ በአዲስ አበባ በተጀመረበት ወቅት ነው።
የብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እንደተናገሩት፣ የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባንኮች ክፍት ያደረገው አዲሱ አዋጅ "የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን በተደረገው ጥረት ትልቅ ምዕራፍ" እንደሆነ ተደርጎ ይታያል። በዚህ ስኬት ላይ በመመስረት፣ ባንኩ አሁን ደግሞ ትኩረቱን የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪውን በማሻሻል ላይ አድርጓል።
ተጨማሪ ያንብቡ
Website | Facebook | X | TikTok | Instagram | Linkedin | Youtube
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የኢንሹራንስ ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት የሚያደርግ አዲስ አዋጅ በዝግጅት ላይ መሆኑን አስታውቋል።
ውሳኔው የኢትዮጵያን የፋይናንስ ኢንዱስትሪ ለማዘመን እየተደረገ ካለው ሰፊ ጥረት አንዱ አካል ነው ተብሏል።
ይህ የተገለጸው 51ኛው የአፍሪካ ኢንሹራንስ ተቋም ዓመታዊ ኮንፈረንስ እና አጠቃላይ ስብሰባ በአዲስ አበባ በተጀመረበት ወቅት ነው።
የብሔራዊ ባንክ ገዢ ማሞ ምህረቱ እንደተናገሩት፣ የባንኩን ዘርፍ ለውጭ ባንኮች ክፍት ያደረገው አዲሱ አዋጅ "የፋይናንስ ዘርፋችንን ለማዘመን በተደረገው ጥረት ትልቅ ምዕራፍ" እንደሆነ ተደርጎ ይታያል። በዚህ ስኬት ላይ በመመስረት፣ ባንኩ አሁን ደግሞ ትኩረቱን የኢንሹራንስ ኢንዱስትሪውን በማሻሻል ላይ አድርጓል።
ተጨማሪ ያንብቡ
Website | Facebook | X | TikTok | Instagram | Linkedin | Youtube
በወተትና መሰል ምርቶች ላይ የአስከሬን
ማድረቂያ የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳሉ ተገለጸ
የወተትና መሰል ምርቶችን የቆይታ ጊዜና መጠናቸውን ለመጨመር ሲባል የአስክሬን ማድረቂያ ጭምር የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳሉ ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
እነዚህ ምግብ ውስጥ የሚጨመሩ ባዕድ ነገሮች ከፍተኛ የሆነ የጤና ችግር በሰዎች ላይ የሚያስከትሉ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለሥልጣን ተናግሯል፡፡
በባለሥልጣኑ የምግብ ኢንስፔክሽንና ህግ ማስፈፀም ስራ አስፈፃሚ ሙላት ተስፋዬ፤ በየጊዜው ክትትል በማድረግ ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶችን ለገበያ በሚያቀርቡት ላይ ህጋዊ እርምጃ እየወሰድን ነው ሲሉ ለጣቢያው ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ በገበያው ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶች መገኘታቸው ቢቀጥልም፣ ከነበረበት መጠን ግን የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ እንደሆነ ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም ድርጊቱን ፈፅመው በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎችንና የቅጣት መጠንን ከፍ ማድረግ እንደሚስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
ምግብ ነክና የመድሐኒት ምርቶች ላይ ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት 14171 የምርመራና ፍተሻ ስራዎችን መስራቱን የባለሥልጣኑ ሪፖርት የሚያሳይ ሲሆን፤በዚህም በአጠቃላይ 3,155ቱ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እንደተወሰደባቸው ተጠቁሟል፡፡
ማድረቂያ የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳሉ ተገለጸ
የወተትና መሰል ምርቶችን የቆይታ ጊዜና መጠናቸውን ለመጨመር ሲባል የአስክሬን ማድረቂያ ጭምር የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳሉ ሸገር ሬዲዮ ዘግቧል፡፡
እነዚህ ምግብ ውስጥ የሚጨመሩ ባዕድ ነገሮች ከፍተኛ የሆነ የጤና ችግር በሰዎች ላይ የሚያስከትሉ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለሥልጣን ተናግሯል፡፡
በባለሥልጣኑ የምግብ ኢንስፔክሽንና ህግ ማስፈፀም ስራ አስፈፃሚ ሙላት ተስፋዬ፤ በየጊዜው ክትትል በማድረግ ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶችን ለገበያ በሚያቀርቡት ላይ ህጋዊ እርምጃ እየወሰድን ነው ሲሉ ለጣቢያው ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ በገበያው ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶች መገኘታቸው ቢቀጥልም፣ ከነበረበት መጠን ግን የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ እንደሆነ ሥራ አስፈጻሚው ጠቁመዋል፡፡
በተጨማሪም ድርጊቱን ፈፅመው በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎችንና የቅጣት መጠንን ከፍ ማድረግ እንደሚስፈልግም አስገንዝበዋል፡፡
ምግብ ነክና የመድሐኒት ምርቶች ላይ ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት 14171 የምርመራና ፍተሻ ስራዎችን መስራቱን የባለሥልጣኑ ሪፖርት የሚያሳይ ሲሆን፤በዚህም በአጠቃላይ 3,155ቱ ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እንደተወሰደባቸው ተጠቁሟል፡፡