በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓል ላይ ተገኙ
በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸውን አናዶሉ እና የኢራን የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።
እስራኤል ከሰኔ 13 ጀምሮ የኢራን የጦር ጀኔራሎችን መግደሏን ያስታወቀች ሲሆን፤ ሦስቱ የኢራን የጦር መሪዎች በትናንትናው ዕለት ኢራን የድል በዓሏን ስታከብር ከህዝቡ ጋር በመገኘት አክብረዋል ብለዋል ምንጮቹ።
ከዚህ ውስጥ አንዱ የሆኑት የእስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፕስ ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኢል ቃኣኒ በዓሉን ከሕብ ጋር ማክበራቸውን የኢራቅ የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።
በኢራን ታስኒም የዜና አገልግሎት የተለጠፈ ቪዲዮ ቃአኒ በዝግጅቱ ላይ ከተሰበሰቡት መካከል አሳይቷል።
በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ቃአኒ በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት የኢራን ጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ዘግቦ እንደነበር የሚታወስ ነው።
በተመሳሳይ የወቅቱ የመከላከያ ሚኒስትር እና የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩ ብርጋዴር ጄኔራል አዚዝ ናስርዛዴህ በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ በመከላከያ ሚኒስቴር ላይ በተፈፀመ የአየር ጥቃት ተገድለዋል ተብለው የነበረ ቢሆንም በሕይወት እንዳሉ እና አሁንም በስልጣን ላይ እንደሚገኙ ተስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የደህንነት ዋና አማካሪ አድሚራል አሊ ሻምካኒ እ.ኤ.አ ሰኔ 13 ቀን 2025 በእስራኤል የአየር ጥቃት መሞታቸው ከተነገሩት አንዱ የነበሩ ናቸው። አድሚራል አሊ ሻምካኒ በድል በዓሉ ላይ በመገኘት የድል በዓሉን አክብረዋል ሲሉ የኢራን የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።
በእስራኤል ጥቃት ተገደሉ የተባሉ 3 የኢራን ጦር መሪዎች የኢራን የድል በዓልን ከሕዝብ ጋር ሲያከብሩ መታየታቸውን አናዶሉ እና የኢራን የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።
እስራኤል ከሰኔ 13 ጀምሮ የኢራን የጦር ጀኔራሎችን መግደሏን ያስታወቀች ሲሆን፤ ሦስቱ የኢራን የጦር መሪዎች በትናንትናው ዕለት ኢራን የድል በዓሏን ስታከብር ከህዝቡ ጋር በመገኘት አክብረዋል ብለዋል ምንጮቹ።
ከዚህ ውስጥ አንዱ የሆኑት የእስላማዊ አብዮታዊ ጥበቃ ኮርፕስ ቁድስ ኃይል አዛዥ ብርጋዴር ጀነራል ኢስማኢል ቃኣኒ በዓሉን ከሕብ ጋር ማክበራቸውን የኢራቅ የሀገር ውስጥ ብዙኃን መገናኛዎች ዘግበዋል።
በኢራን ታስኒም የዜና አገልግሎት የተለጠፈ ቪዲዮ ቃአኒ በዝግጅቱ ላይ ከተሰበሰቡት መካከል አሳይቷል።
በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ቃአኒ በእስራኤል ጥቃት ከተገደሉት የኢራን ጦር መሪዎች መካከል አንዱ እንደሆኑ ዘግቦ እንደነበር የሚታወስ ነው።
በተመሳሳይ የወቅቱ የመከላከያ ሚኒስትር እና የአየር ኃይል አዛዥ የነበሩ ብርጋዴር ጄኔራል አዚዝ ናስርዛዴህ በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ በመከላከያ ሚኒስቴር ላይ በተፈፀመ የአየር ጥቃት ተገድለዋል ተብለው የነበረ ቢሆንም በሕይወት እንዳሉ እና አሁንም በስልጣን ላይ እንደሚገኙ ተስኒም የዜና ወኪል ዘግቧል።
የአያቶላህ አሊ ኻሚኒ ከፍተኛ አማካሪ እና የደህንነት ዋና አማካሪ አድሚራል አሊ ሻምካኒ እ.ኤ.አ ሰኔ 13 ቀን 2025 በእስራኤል የአየር ጥቃት መሞታቸው ከተነገሩት አንዱ የነበሩ ናቸው። አድሚራል አሊ ሻምካኒ በድል በዓሉ ላይ በመገኘት የድል በዓሉን አክብረዋል ሲሉ የኢራን የዜና ወኪሎች ዘግበዋል።
ኢራን ጦርነቱን እንድታቆም ከአሜሪካ የ30 ቢሊየን ዶላር ጉርሻ ቀርቦላታል ተባለ
ኢራን ጦርነቱን እንድታቆም እና ወደ ድርድር እንድትመጣ አሜሪካ የ30 ቢሊዮን ዶላር ጉርሻ እና ማዕቀብ እንዲነሳላት ማድረጓን ሲኤን ኤን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ዘገባው እንደሚለው አሜሪካ ቴህራንን ወደ ድርድር ጠረጴዛው ለመመለስ የተጠናከረ ሙከራ አድርጋለች።
ላለፉት ሁለት ሳምንታት በኢራን እና በእስራኤል ወታደራዊ ጥቃቶች እየተበራከቱ ባለበት ወቅት እንኳን ከመጋረጃው ጀርባ ከኢራናውያን ጋር መነጋገራቸውን ምንጮች ነግረውኛል ሲል ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል።
የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ እነዚያ ውይይቶች በዚህ ሳምንት ቀጥለዋል ብለዋል።
ኢራን ወደ ድርድር ብትመለስም ዩራኒየም ማበልፀግ ላይ የማይወላውል አቋም አሳይታለች ብሏል ዘገባው።
ለኢራን የቀረበው የ30 ቢሊዮን ዶላር ጉርሻ ለሲቪል የኒውክሌር መርሃ ግብር አገልግሎት የሚውል መሆኑን የትራምፕ አስተዳደር ባለስልጣናት እና ሃሳቡን የሚያውቁ ምንጮች ለሲ.ኤን.ኤን ተናግረዋል ብሏል።
ኢራን ጦርነቱን እንድታቆም እና ወደ ድርድር እንድትመጣ አሜሪካ የ30 ቢሊዮን ዶላር ጉርሻ እና ማዕቀብ እንዲነሳላት ማድረጓን ሲኤን ኤን ምንጮችን ጠቅሶ ዘግቧል።
ዘገባው እንደሚለው አሜሪካ ቴህራንን ወደ ድርድር ጠረጴዛው ለመመለስ የተጠናከረ ሙከራ አድርጋለች።
ላለፉት ሁለት ሳምንታት በኢራን እና በእስራኤል ወታደራዊ ጥቃቶች እየተበራከቱ ባለበት ወቅት እንኳን ከመጋረጃው ጀርባ ከኢራናውያን ጋር መነጋገራቸውን ምንጮች ነግረውኛል ሲል ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል።
የተኩስ አቁም ስምምነት ከተደረሰ በኋላ እነዚያ ውይይቶች በዚህ ሳምንት ቀጥለዋል ብለዋል።
ኢራን ወደ ድርድር ብትመለስም ዩራኒየም ማበልፀግ ላይ የማይወላውል አቋም አሳይታለች ብሏል ዘገባው።
ለኢራን የቀረበው የ30 ቢሊዮን ዶላር ጉርሻ ለሲቪል የኒውክሌር መርሃ ግብር አገልግሎት የሚውል መሆኑን የትራምፕ አስተዳደር ባለስልጣናት እና ሃሳቡን የሚያውቁ ምንጮች ለሲ.ኤን.ኤን ተናግረዋል ብሏል።
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
አንጋፋው ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ የጃምቦ ሪል እስቴት ብራንድ አምባሳደር በመሆን ለሦስት ዓመት በጋራ ለመሥራት የሚያስችለውን ስምምነት ትላንት ሰኔ 19 ቀን 2017 ዓ.ም በሂልተን ሆቴል ከድርጅቱ ጋር ተፈራርሟል፡፡
የጃምቦ ሪል ስቴት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ሰይፉ በፊርማ ስነስርአቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ በቅርቡ በሰሜን አሜሪካ በሚካሄደው ዓመታዊ የኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ጃምቦ ሪል ስቴትን ወክሎ በመሳተፍ የመጀመሪያውን የስራ እንቅስቃሴው እንደሚጀምር ገልጸዋል፡፡
ጃምቦ ሪል አስቴት በቅርቡ በተከበረው የጋዜጠኛው የ60ኛ ዓመት ልደት በዓል ላይ፣ ባለ ሦስት መኝታ ክፍል የመኖሪያ ቤት ስጦታ እንዳበረከተለት ይታወሳል፡፡ አንጋፋው ጋዜጠኛ በዕለቱ ከመኖሪያ ቤት በተጨማሪ የመኪና ስጦታ ከታሜሶል እንዲሁም መጠኑ ያልተገለጸ ገንዘብ ከወዳጆቹ እንደተበረከተለት ይታወቃል፡፡
በግራንድ ሃይሌ ሆቴል በተካሄደው የልደት በዓል ላይ ጋዜጠኛው ለጃምቦ ሪል ስቴት በብራንድ አምባሳደርነት መመረጡ መጠቀሱን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የትላንትናው ሥነስርዓት ያስፈለገው ስምምነቱን ለህዝብ ይፋ ለማድረግና ለመፈራረም መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ጃምቦ ለምን ጋዜጠኛ ደረጄን በአምባሳደርነት እንደመረጠው ሲያብራሩም፤ "የመረጥነው በብዙ መስፈርቶች ነው፤ ጃምቦ ካለው ዓላማና እንቅስቃሴ ጋር ተመሳሳይና ትክክለኛ ዓላማ ያለው በመሆኑ ነው፤ ደሞም ምርጫችን ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠናል" ብለዋል።
"ደረጀ ለሥራው ያለው ፍቅር፣ ቁርጠኝነትና ሙያዊ ታማኝነት የድርጅታችን አምባሳደር እንዲሆን ለመምረጥ አስችሎናል" ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ያለው ሰፊ ልምድ፣ እውቅናና ተቀባይነት ለጃምቦ ሪል ስቴት ብራንድ ግንባታና ለድርጅቱን ዕድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት እምነታቸውን ገልጸዋል።
እስከዛሬ ለጋዜጠኝነት ሙያና ለባለሙያዎቹ ትኩረት ሳይሰጣቸው መቆየቱን ያነሱት አቶ ደበበ ሰይፉ፤ "ለመጀመሪያ ጊዜ ጋዜጠኛና የጋዜጠኝነት ሙያ ክብርና ዕውቅና በማግኘታቸው ትልቅ ኩራትና ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡፡
ጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ በበኩሉ፣ በህይወት ዘመኑ ከጋዜጠኝነት ውጭ ሌላ ሥራ ሞክሮ እንደማያውቅና እንደማይችል ተናግሯል፡፡
"የምችለው ጋዜጠኝነትን ብቻ ነው። ጋዜጠኝነት አልከፈለኝም ብዬ አማርሬ ግን አላውቅም" ያለው ጋዜጠኛ ደረጄ ፤ ለተደረገለት ነገር ሁሉ ጃምቦ ሪል እስቴትን አመስግኗል።
ይህ በዚህ እንዳለ፣ ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ በልደቱ ዕለት ቃል የተገባለትን BYD E2 መኪና በዛሬው ዕለት ከታሜሶል ኮሙኒኬሽንስ ተረክቧል፡፡ የመኪና ስጦታው 3.4 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጣ ታውቋል፡፡
ጃምቦ ሪል ስቴት ግሩፕ ከ29 ዓመታት በፊት በወንድማማቾቹ አቶ ደበበ ሰይፉና አቶ ወንድይራድ ሰይፉ አማካኝነት "ጃምቦ ኮንስትራክሽን" በሚል ስያሜ እንደተቋቋመ ይታወቃል። ድርጅቱ ከዚያ ጊዜ አንስቶ በግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ በማካበትና በርካታ ፕሮጀክቶችን በማከናወን በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ገበያ ውስጥ ዋነኛ ተዋናይ ሆኖ ዘልቋል፡፡
የጃምቦ ሪል ስቴት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ደበበ ሰይፉ በፊርማ ስነስርአቱ ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ በቅርቡ በሰሜን አሜሪካ በሚካሄደው ዓመታዊ የኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ጃምቦ ሪል ስቴትን ወክሎ በመሳተፍ የመጀመሪያውን የስራ እንቅስቃሴው እንደሚጀምር ገልጸዋል፡፡
ጃምቦ ሪል አስቴት በቅርቡ በተከበረው የጋዜጠኛው የ60ኛ ዓመት ልደት በዓል ላይ፣ ባለ ሦስት መኝታ ክፍል የመኖሪያ ቤት ስጦታ እንዳበረከተለት ይታወሳል፡፡ አንጋፋው ጋዜጠኛ በዕለቱ ከመኖሪያ ቤት በተጨማሪ የመኪና ስጦታ ከታሜሶል እንዲሁም መጠኑ ያልተገለጸ ገንዘብ ከወዳጆቹ እንደተበረከተለት ይታወቃል፡፡
በግራንድ ሃይሌ ሆቴል በተካሄደው የልደት በዓል ላይ ጋዜጠኛው ለጃምቦ ሪል ስቴት በብራንድ አምባሳደርነት መመረጡ መጠቀሱን ያስታወሱት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ የትላንትናው ሥነስርዓት ያስፈለገው ስምምነቱን ለህዝብ ይፋ ለማድረግና ለመፈራረም መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ጃምቦ ለምን ጋዜጠኛ ደረጄን በአምባሳደርነት እንደመረጠው ሲያብራሩም፤ "የመረጥነው በብዙ መስፈርቶች ነው፤ ጃምቦ ካለው ዓላማና እንቅስቃሴ ጋር ተመሳሳይና ትክክለኛ ዓላማ ያለው በመሆኑ ነው፤ ደሞም ምርጫችን ትክክለኛ መሆኑን አረጋግጠናል" ብለዋል።
"ደረጀ ለሥራው ያለው ፍቅር፣ ቁርጠኝነትና ሙያዊ ታማኝነት የድርጅታችን አምባሳደር እንዲሆን ለመምረጥ አስችሎናል" ያሉት ዋና ሥራ አስፈጻሚው፤ ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ ያለው ሰፊ ልምድ፣ እውቅናና ተቀባይነት ለጃምቦ ሪል ስቴት ብራንድ ግንባታና ለድርጅቱን ዕድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት እምነታቸውን ገልጸዋል።
እስከዛሬ ለጋዜጠኝነት ሙያና ለባለሙያዎቹ ትኩረት ሳይሰጣቸው መቆየቱን ያነሱት አቶ ደበበ ሰይፉ፤ "ለመጀመሪያ ጊዜ ጋዜጠኛና የጋዜጠኝነት ሙያ ክብርና ዕውቅና በማግኘታቸው ትልቅ ኩራትና ደስታ ይሰማናል" ብለዋል፡፡፡
ጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ በበኩሉ፣ በህይወት ዘመኑ ከጋዜጠኝነት ውጭ ሌላ ሥራ ሞክሮ እንደማያውቅና እንደማይችል ተናግሯል፡፡
"የምችለው ጋዜጠኝነትን ብቻ ነው። ጋዜጠኝነት አልከፈለኝም ብዬ አማርሬ ግን አላውቅም" ያለው ጋዜጠኛ ደረጄ ፤ ለተደረገለት ነገር ሁሉ ጃምቦ ሪል እስቴትን አመስግኗል።
ይህ በዚህ እንዳለ፣ ጋዜጠኛ ደረጀ ኃይሌ በልደቱ ዕለት ቃል የተገባለትን BYD E2 መኪና በዛሬው ዕለት ከታሜሶል ኮሙኒኬሽንስ ተረክቧል፡፡ የመኪና ስጦታው 3.4 ሚሊዮን ብር እንደሚያወጣ ታውቋል፡፡
ጃምቦ ሪል ስቴት ግሩፕ ከ29 ዓመታት በፊት በወንድማማቾቹ አቶ ደበበ ሰይፉና አቶ ወንድይራድ ሰይፉ አማካኝነት "ጃምቦ ኮንስትራክሽን" በሚል ስያሜ እንደተቋቋመ ይታወቃል። ድርጅቱ ከዚያ ጊዜ አንስቶ በግንባታ ዘርፍ ከፍተኛ ልምድ በማካበትና በርካታ ፕሮጀክቶችን በማከናወን በኢትዮጵያ የሪል ስቴት ገበያ ውስጥ ዋነኛ ተዋናይ ሆኖ ዘልቋል፡፡
ከኢትዮጵያ ወደ ታንዛኒያ 50 ሜጋ ዋት ኃይል የማስተላለፍ የሙከራ ሂደት በስኬት መከናወኑ ተገለፀ
የኬንያ ኤሌክትሪክ ኩባንያ ሱስዋ-ኢሲንያ ማስተላለፊያ መስመር ከ225 ሜጋ ዋት እስከ 262 ሜጋ ዋት ማስተላለፉን የተቋሙ ሥራ አስፈፃሚ ጆን ማትቪዮ ተናግረዋል፡፡
የማስተላለፊያ መሠረተ ልማት ግንባታው በኬንያ ግምጃ ቤት፣ በዓለም ባንክ፣ በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ በፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ እና በአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎለታል።
ከኢትዮጵያ ወደ ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተላለፍ የሚያስችል የሶስትዮሽ ስምምነት ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ ባለፈው ጥር ወር መፈራረማቸው ይታወሳል።
የኬንያ ኤሌክትሪክ ኩባንያ ሱስዋ-ኢሲንያ ማስተላለፊያ መስመር ከ225 ሜጋ ዋት እስከ 262 ሜጋ ዋት ማስተላለፉን የተቋሙ ሥራ አስፈፃሚ ጆን ማትቪዮ ተናግረዋል፡፡
የማስተላለፊያ መሠረተ ልማት ግንባታው በኬንያ ግምጃ ቤት፣ በዓለም ባንክ፣ በአፍሪካ ልማት ባንክ፣ በፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ እና በአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ የገንዘብ ድጋፍ ተደርጎለታል።
ከኢትዮጵያ ወደ ታንዛኒያ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማስተላለፍ የሚያስችል የሶስትዮሽ ስምምነት ኢትዮጵያ፣ ኬንያ እና ታንዛኒያ ባለፈው ጥር ወር መፈራረማቸው ይታወሳል።
በማዕከላዊ አፍሪካ ሪፐብሊክ የትምህርት ቤት ፈተና ሲወስዱ የነበሩ 29 ህጻናት በአካባቢው በደረሰ ፍንዳታ ሕይወታቸውን አጥተዋል።
የአከባቢው ሆስፒታል ዳይሬክተር ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ ፍንዳታው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማጠናቀቂያ ፈተና እየወሰዱ በሚገኙ ተማሪዎች ላይ የደረሰው በኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ በገጠመው አዳጋ ነው።
የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ፋውስቲን-አርቸንስ ቱዋዴራ በአደጋው ህይወታቸውን ያጡ ተማሪዎችን ለማስታወስ ብሄራዊ የሐዘን ቀን ያወጁ ሲሆን፤ በአደጋው የቆሰሉት ከ280 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች በሆስፒታል ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
አደጋው የደረሰው ከዋና ከተማው ከሚገኙ አምስት የተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች የባካሎሬት የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ለመውሰድ በተሰበሰቡበት አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።
የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤ ፍንዳታው የተፈጠረው በዋናው ህንጻ ወለል ላይ በሚገኘው የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ ጥገና ሲደረግለት የነበረው ኃይል ወደ ቀድሞ ሁኔታው እንዲመለስ በመደረጉ ነው ብሏል።
የትምህርት ሚንስትሩ ኦሬሊን ሲምፕሊስ ኮንግቤሌት ዚምጋስ፤ በአደጋው ልጆቻቸውን ላጡ ወላጆች ሀዘናቸውን ገልፀው ተጨማሪ ፈተናዎች መቋረጣቸውን አስታውቋል።
የአከባቢው ሆስፒታል ዳይሬክተር ጠቅሶ ቢቢሲ እንደዘገበው፣ ፍንዳታው የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ማጠናቀቂያ ፈተና እየወሰዱ በሚገኙ ተማሪዎች ላይ የደረሰው በኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ በገጠመው አዳጋ ነው።
የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ፋውስቲን-አርቸንስ ቱዋዴራ በአደጋው ህይወታቸውን ያጡ ተማሪዎችን ለማስታወስ ብሄራዊ የሐዘን ቀን ያወጁ ሲሆን፤ በአደጋው የቆሰሉት ከ280 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች በሆስፒታል ነፃ ህክምና እንዲያገኙ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል።
አደጋው የደረሰው ከዋና ከተማው ከሚገኙ አምስት የተለያዩ ትምህርት ቤቶች የተውጣጡ ተማሪዎች የባካሎሬት የ2ኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ለመውሰድ በተሰበሰቡበት አካባቢ መሆኑ ተገልጿል።
የሀገሪቱ የትምህርት ሚኒስቴር እንዳስታወቀው፤ ፍንዳታው የተፈጠረው በዋናው ህንጻ ወለል ላይ በሚገኘው የኤሌክትሪክ ትራንስፎርመር ላይ ጥገና ሲደረግለት የነበረው ኃይል ወደ ቀድሞ ሁኔታው እንዲመለስ በመደረጉ ነው ብሏል።
የትምህርት ሚንስትሩ ኦሬሊን ሲምፕሊስ ኮንግቤሌት ዚምጋስ፤ በአደጋው ልጆቻቸውን ላጡ ወላጆች ሀዘናቸውን ገልፀው ተጨማሪ ፈተናዎች መቋረጣቸውን አስታውቋል።
Forwarded from Capitalethiopia
#CapitalNews ኢትዮጵያ የኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ ኤክስፖርት ፕሮጀክት ሰረዘች
👉 በምትኩ የማዕድን ሚኒስትር የተፈጥሮ ጋዝን ለአገር ዉስጥ ፍጆታ ለመጠቀም የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት እያጠና ነዉ
ኢትዮጵያ በኦጋዴን ክልል የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ ፕሮጀክት የገንዘብ እጥረትና የትግበራ መዘግየትን ዋቢ በማድረግ እንደሰረዘች አስታውቃለች። በምትኩ፣ የማዕድን ሚኒስቴር የተፈጥሮ ጋዝን ለአገር ውስጥ ፍጆታ፣ በተለይም ማዳበሪያ ለማምረትና ኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት እያጠና መሆኑን ገልጿል።
የማዕድን ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ኢትዮጵያ በተለይም በኦጋዴን ተፋሰስ፣ በካሉብና ሂላላ አካባቢዎች ከፍተኛ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት ሲሆን፣ ይህም ከ50 ዓመታት በላይ ለሚሆን ጊዜ ማዳበሪያ ለማምረት፣ ኃይል ለማመንጨትና ለተለያዩ የነዳጅ ምርቶች ለማገልገል የሚያስችል እንደሆነ ቢገመትም፣ እስካሁን በጥልቀት አልተጠናም።
የጅቡቲ የቧንቧ መስመር ፕሮጀክት መሰረዝ
በ2022፣ ከኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ አውጥቶ በ767 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው የቧንቧ መስመር ወደ ጅቡቲ በመላክ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ ለመላክ ታቅዶ የነበረው ፕሮጀክት መሰረዙ ተገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ
👉 በምትኩ የማዕድን ሚኒስትር የተፈጥሮ ጋዝን ለአገር ዉስጥ ፍጆታ ለመጠቀም የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት እያጠና ነዉ
ኢትዮጵያ በኦጋዴን ክልል የሚገኘውን የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ የመላክ ፕሮጀክት የገንዘብ እጥረትና የትግበራ መዘግየትን ዋቢ በማድረግ እንደሰረዘች አስታውቃለች። በምትኩ፣ የማዕድን ሚኒስቴር የተፈጥሮ ጋዝን ለአገር ውስጥ ፍጆታ፣ በተለይም ማዳበሪያ ለማምረትና ኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት የሚያስችል አዲስ ፕሮጀክት እያጠና መሆኑን ገልጿል።
የማዕድን ሚኒስቴር እንደገለጸው፣ ኢትዮጵያ በተለይም በኦጋዴን ተፋሰስ፣ በካሉብና ሂላላ አካባቢዎች ከፍተኛ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ያላት ሲሆን፣ ይህም ከ50 ዓመታት በላይ ለሚሆን ጊዜ ማዳበሪያ ለማምረት፣ ኃይል ለማመንጨትና ለተለያዩ የነዳጅ ምርቶች ለማገልገል የሚያስችል እንደሆነ ቢገመትም፣ እስካሁን በጥልቀት አልተጠናም።
የጅቡቲ የቧንቧ መስመር ፕሮጀክት መሰረዝ
በ2022፣ ከኦጋዴን የተፈጥሮ ጋዝ አውጥቶ በ767 ኪሎ ሜትር ርዝመት ባለው የቧንቧ መስመር ወደ ጅቡቲ በመላክ በፈሳሽ የተፈጥሮ ጋዝ ወደ ውጭ ለመላክ ታቅዶ የነበረው ፕሮጀክት መሰረዙ ተገልጿል።
ተጨማሪ ያንብቡ
በጃማይካ የአእምሮ ህመምተኛ የሆኑ ግለሰብ ያለ አግባብ ከ40 አመት በላይ በመታሰራቸው 100 ሚሊዮን ብር ገደማ እንዲከፈላቸው ፍርድ ቤት አዘዘ
ለ50 ዓመታት በእስር ቤት የቆዩት የአእምሮ ህመምተኛ የሆኑት ጆርጅ ዊሊያምስ የፍርድ ቤት ውሳኔን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ሲሆን፣ አሁን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ100ሚሊዮን ዶላር በላይ ካሳ መንግስት እንዲከፍሏቸው አዟል።
ለፍርድ ቤት ለመቅረብ ብቁ እንዳልሆኑ የተቆጠሩት ዊሊያምስ፣ በፈረንጆቹ ሰኔ 2020 ከተለቀቁ በኋላ ለመንግሥት ካሳ ጠይቀው ነበር።
ጉዳዩን የያዙት ዳኛ ሶንያ ዊንት ብሌየር ለዊሊያምስ 78.6 ሚሊዮን ዶላር የማካካሻ ካሳ እና 42 ሚሊዮን ዶላር የቅጣት ካሳ እንዲከፈላቸው ወስነዋል።
መንግሥት ለቤተሰቡ 6 ሚሊዮን ዶላር ካሳ አቅርቦ ነበር።
ዳኛ ዊንት ብሌየር በውሳኔያቸው እንዳብራሩት፣ የ42 ሚሊዮን ዶላር የቅጣት ካሳ የተሰጠው “አስፈጻሚው አካል ተገቢውን ህጋዊ መስፈርቶች ባለማሟላቱ፣ ማለትም ተከሳሹ በእስር ላይ በነበረበት ጊዜ የአእምሮ ጤንነቱ እና ደህንነቱ ታሳቢ ሳይደረግ ለ42 ዓመታት ያህል ደህንነቱ የተጠበቀ ጥበቃ እና እንክብካቤ ባለማግኘቱ ነው” በማለት ነው።
ዊሊያምስ፣ ራስታፋሪያን የሆኑ ግለሰብ ሲሆኑ፣ በሀምሌ 1970 በሴንት ካተሪን በሚገኘው ማውንት ዲያብሎ ማኅበረሰብ ውስጥ በመኪና ሲጓዝ በነበረ ቤተሰብ ላይ ቢላዋ በመውጋት ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በዚያው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ፣ በዚያ ክስተት ወቅት በቢላ ተወግቶ የሞተውን ያን ላውሪን በመግደል ተከሰሱ።
በየካቲት 1971 ተመርምረው ስኪዞፈሪንያ እንዳለባቸው ተረጋግጧል፤ ነገር ግን በከፊል የማገገም ደረጃ ላይ ነበሩ።
ዊሊያምስ በመጋቢት 1971 ለፍርድ ቤት ለመቅረብ ብቁ እንዳልሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በመንግስት እስር እንዲቆዩ ታዘዋል። ጉዳያቸው በየጊዜው ሳይገመገም ለ42 ዓመታት በእስር ላይ ቆይተዋል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ለ50 ዓመታት በእስር ቤት የቆዩት የአእምሮ ህመምተኛ የሆኑት ጆርጅ ዊሊያምስ የፍርድ ቤት ውሳኔን በመጠባበቅ ላይ የነበሩ ሲሆን፣ አሁን ጠቅላይ ፍርድ ቤት ከ100ሚሊዮን ዶላር በላይ ካሳ መንግስት እንዲከፍሏቸው አዟል።
ለፍርድ ቤት ለመቅረብ ብቁ እንዳልሆኑ የተቆጠሩት ዊሊያምስ፣ በፈረንጆቹ ሰኔ 2020 ከተለቀቁ በኋላ ለመንግሥት ካሳ ጠይቀው ነበር።
ጉዳዩን የያዙት ዳኛ ሶንያ ዊንት ብሌየር ለዊሊያምስ 78.6 ሚሊዮን ዶላር የማካካሻ ካሳ እና 42 ሚሊዮን ዶላር የቅጣት ካሳ እንዲከፈላቸው ወስነዋል።
መንግሥት ለቤተሰቡ 6 ሚሊዮን ዶላር ካሳ አቅርቦ ነበር።
ዳኛ ዊንት ብሌየር በውሳኔያቸው እንዳብራሩት፣ የ42 ሚሊዮን ዶላር የቅጣት ካሳ የተሰጠው “አስፈጻሚው አካል ተገቢውን ህጋዊ መስፈርቶች ባለማሟላቱ፣ ማለትም ተከሳሹ በእስር ላይ በነበረበት ጊዜ የአእምሮ ጤንነቱ እና ደህንነቱ ታሳቢ ሳይደረግ ለ42 ዓመታት ያህል ደህንነቱ የተጠበቀ ጥበቃ እና እንክብካቤ ባለማግኘቱ ነው” በማለት ነው።
ዊሊያምስ፣ ራስታፋሪያን የሆኑ ግለሰብ ሲሆኑ፣ በሀምሌ 1970 በሴንት ካተሪን በሚገኘው ማውንት ዲያብሎ ማኅበረሰብ ውስጥ በመኪና ሲጓዝ በነበረ ቤተሰብ ላይ ቢላዋ በመውጋት ጥቃት ከሰነዘሩ በኋላ በቁጥጥር ስር ውለዋል።
በዚያው ዓመት ታህሳስ ወር ላይ፣ በዚያ ክስተት ወቅት በቢላ ተወግቶ የሞተውን ያን ላውሪን በመግደል ተከሰሱ።
በየካቲት 1971 ተመርምረው ስኪዞፈሪንያ እንዳለባቸው ተረጋግጧል፤ ነገር ግን በከፊል የማገገም ደረጃ ላይ ነበሩ።
ዊሊያምስ በመጋቢት 1971 ለፍርድ ቤት ለመቅረብ ብቁ እንዳልሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ በመንግስት እስር እንዲቆዩ ታዘዋል። ጉዳያቸው በየጊዜው ሳይገመገም ለ42 ዓመታት በእስር ላይ ቆይተዋል ሲሉ የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
በህወሓት እና ሻዕቢያ መካከል የተፈጠረው ጥምረትና ግንኙነት በፌደራል መንግሥቱ መቋረጥ አለበት ሲሉ የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ገለጹ!
በቅርቡ ህወሓትና ሻዕቢያ ጥመረት እየፈጠረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ የሁለቱ አካላት ጥምረት በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሊቋረጥ ይገባል ሲሉ የቀድሞ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አሳስበዋል፡፡የቀድሞዋ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም፤ "ይህንን ለጦርነት የተደረገ ጥምረት መንግሥት ሊያቋርጠው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አባልና ከፍተኛ አመራር እንዲሁም የዲሞክራሲ ስምረት ትግራይ ፖርቲ መስራች ውስጥ አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ "የሁለቱ አካላት ጥምረት ዓላማ ግልፅ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሐትና የኤርትራ መንግሥት ጥምረት መፍጠር ለጦርነት ዓላማ የተደረገ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።
በተጨማሪም በትግርኛ "ፅምዶ" ወይንም "ጥምረት ለሀቀኛ ሰላም ለትግራይ እና ኤርትራ" በሚል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተደረገ መሆኑንም መመልከት ተችሏል።ይህንን ጥምረት በሚመለከት ሀሳባቸውን የሰጡት የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም "በግልፅ ለጦርነት የተደረገ ጥምረት ነው" ብለዋል።
"ሕዝብን ከተደቀነበት ጦርነት ማዳን ላይ መስራት አለብን" ያሉ ሲሆን፤ ጦርነቱ የማይቀር እንኳን ቢሆን ዱላው ሕዝብ ላይ እንዳያርፍ መስራት አለብን" ሲሉም ገልጸዋል።"አሁን ላይ በግልፅም ይሁን በድብቅ ጥምረቱ ይታያል" ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ "ይህንን ማስቆምና መቁረጥ ያለበት የትግራይ ሊሂቃንና ፌደራል መንግሥት ነው በማለት ሀሳባቸውን" ሰጥተዋል።
ሌላው ሀሳባቸውን ለአሐዱ የሰጡት የቀድሞ የህወሕት አባልና ከፍተኛ አመራር ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፤ "በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ ከሌላ ሀገር ጋር ማን ግንኙነት መፍጠር እንዳለበት ይታወቃል" ብለዋል፡፡"ሕገ-ወጥ ግነኙነት ሲኖር ደግሞ ማስቆም ያለበት ማን እንደሆነም ግልፅ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።"ይሁን እንጂ ከኤርትራ ጋር ያለው ግንኙነት ያልጠራ ነው፤ ነገር ግን ግንኙነቱ በመርህ ላይ ካልተመሰረተ ትክክል አይለም" ሲሉም ለአሐዱ ገልጸዋል።
በዚህ ጥምረት ዙሪያ የፌደራል መንግሥት በግልፅ ያስታወቀው ነገር ባይኖርም፤ ባለፈው ሳምንት አርብ በትግራይ ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ የሚጠይቅ ወይይት ተካሂዶ ነበር።የፌደራል መንግሥት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከልን በመወከል የተገኙት አቶ መለሰ አለሙ፤ "የፌደራል መንግሥት ኃላፊነት እንዳለ ሆኖ የትግራይ ፖለቲከኞችም ለሰላም ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል" ሲሉ ተደምጠዋል።"የድንበር ጉዳይን በተመለከተ መንግሥት ሉዓላዊነቱን በፍፁም አሳልፎ አይሰጥም" ያሉም ሲሆን፤ የውስጥ ችግሮች ከተፈቱ ሌላውን ማስተካከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
Via Ahadu
በቅርቡ ህወሓትና ሻዕቢያ ጥመረት እየፈጠረ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፤ ይህ የሁለቱ አካላት ጥምረት በመንግሥት ጣልቃ ገብነት ሊቋረጥ ይገባል ሲሉ የቀድሞ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች አሳስበዋል፡፡የቀድሞዋ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም፤ "ይህንን ለጦርነት የተደረገ ጥምረት መንግሥት ሊያቋርጠው ይገባል" ሲሉ ገልጸዋል።
ሌላው የቀድሞ የድርጅቱ አባልና ከፍተኛ አመራር እንዲሁም የዲሞክራሲ ስምረት ትግራይ ፖርቲ መስራች ውስጥ አንዱ የሆኑት ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት በበኩላቸው፤ "የሁለቱ አካላት ጥምረት ዓላማ ግልፅ አይደለም" ሲሉ ተናግረዋል።በምርጫ ቦርድ የተሰረዘው ህወሐትና የኤርትራ መንግሥት ጥምረት መፍጠር ለጦርነት ዓላማ የተደረገ መሆኑ እየተገለጸ ይገኛል።
በተጨማሪም በትግርኛ "ፅምዶ" ወይንም "ጥምረት ለሀቀኛ ሰላም ለትግራይ እና ኤርትራ" በሚል የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት እየተደረገ መሆኑንም መመልከት ተችሏል።ይህንን ጥምረት በሚመለከት ሀሳባቸውን የሰጡት የቀድሞ የህወሓት ከፍተኛ አመራር ወይዘሮ ኬሪያ ኢብራሂም "በግልፅ ለጦርነት የተደረገ ጥምረት ነው" ብለዋል።
"ሕዝብን ከተደቀነበት ጦርነት ማዳን ላይ መስራት አለብን" ያሉ ሲሆን፤ ጦርነቱ የማይቀር እንኳን ቢሆን ዱላው ሕዝብ ላይ እንዳያርፍ መስራት አለብን" ሲሉም ገልጸዋል።"አሁን ላይ በግልፅም ይሁን በድብቅ ጥምረቱ ይታያል" ያሉት ወይዘሮ ኬሪያ፤ "ይህንን ማስቆምና መቁረጥ ያለበት የትግራይ ሊሂቃንና ፌደራል መንግሥት ነው በማለት ሀሳባቸውን" ሰጥተዋል።
ሌላው ሀሳባቸውን ለአሐዱ የሰጡት የቀድሞ የህወሕት አባልና ከፍተኛ አመራር ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረህይወት፤ "በአንድ ሉዓላዊት ሀገር ውስጥ ከሌላ ሀገር ጋር ማን ግንኙነት መፍጠር እንዳለበት ይታወቃል" ብለዋል፡፡"ሕገ-ወጥ ግነኙነት ሲኖር ደግሞ ማስቆም ያለበት ማን እንደሆነም ግልፅ ነው" ሲሉ ተናግረዋል።"ይሁን እንጂ ከኤርትራ ጋር ያለው ግንኙነት ያልጠራ ነው፤ ነገር ግን ግንኙነቱ በመርህ ላይ ካልተመሰረተ ትክክል አይለም" ሲሉም ለአሐዱ ገልጸዋል።
በዚህ ጥምረት ዙሪያ የፌደራል መንግሥት በግልፅ ያስታወቀው ነገር ባይኖርም፤ ባለፈው ሳምንት አርብ በትግራይ ሰላም፣ ልማትና ዲሞክራሲ የሚጠይቅ ወይይት ተካሂዶ ነበር።የፌደራል መንግሥት የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከልን በመወከል የተገኙት አቶ መለሰ አለሙ፤ "የፌደራል መንግሥት ኃላፊነት እንዳለ ሆኖ የትግራይ ፖለቲከኞችም ለሰላም ሚናቸውን ሊወጡ ይገባል" ሲሉ ተደምጠዋል።"የድንበር ጉዳይን በተመለከተ መንግሥት ሉዓላዊነቱን በፍፁም አሳልፎ አይሰጥም" ያሉም ሲሆን፤ የውስጥ ችግሮች ከተፈቱ ሌላውን ማስተካከል እንደሚቻል ተናግረዋል።
Via Ahadu
ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ተወሰነ!
ሦስተኛ ስብሰባውን ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ያካሄደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወሰነ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ዛሬ ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውስኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው።
"አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል።
ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳብ ሌሎች ለብሔራዊ ባንክ ቦርድ ቀርቦ መጽደቁንም መግለጫው አመልክቷል።ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ በሚያስገድደው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ባንኮች መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ 2022 ጀምሮ ከአጠቃላይ ዓመታዊ ብድራቸው አምስት በመቶ የሚሆነውን ለዚህ የቦንድ ግዥ ሲያውሉ ቆይተዋል። በዚህ መመሪያ መሠረት የገዙት ቦንድ የሚመለሰው (ለቦንድ ግዢ ያዋሉት ገንዘብ ተመላሽ የሚደረግላቸው) ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ ሲሆን ፣ ባንኮቹ መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ወር አንስቶ እ.ኤ.አ. እስከ ጁን 30 ቀን 2024 ድረስ የገዙት የቦንድ መጠን 94 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት ዕዳ መግለጫ ያመለክታል።
በገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ያሳለፈው ሌላኛው ውሳኔ በባንኮች ላይ የተጣለውን የብድር ዕቀባ የተመለከተ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ጣሪያ እስከ መጪው መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲቀጠል ኮሚቴው ወስኗል።ለዚህም የሰጠው ምክንያት አሁን ላይ የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ እየተስተዋለ ቢሆንም ይህንን ማስቀጠል አስፈላጊ በመሆኑ በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕድገት ጣሪያ ባለበት እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ የሚገልጽ ነው።
Via Reporter
ሦስተኛ ስብሰባውን ዛሬ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ያካሄደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወሰነ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ዛሬ ባደረገው ውይይት የተለያዩ ውስኔዎችን አሳልፏል። ከእነዚህም ውስጥ አንዱ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ያሳለፈው ወሳኔ ተጠቃሽ ነው።
"አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ሲል መግለጫው ጠቅሷል።
ኮሚቴው ያመነበት ይህ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳብ ሌሎች ለብሔራዊ ባንክ ቦርድ ቀርቦ መጽደቁንም መግለጫው አመልክቷል።ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ በሚያስገድደው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ባንኮች መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ 2022 ጀምሮ ከአጠቃላይ ዓመታዊ ብድራቸው አምስት በመቶ የሚሆነውን ለዚህ የቦንድ ግዥ ሲያውሉ ቆይተዋል። በዚህ መመሪያ መሠረት የገዙት ቦንድ የሚመለሰው (ለቦንድ ግዢ ያዋሉት ገንዘብ ተመላሽ የሚደረግላቸው) ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ ሲሆን ፣ ባንኮቹ መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ወር አንስቶ እ.ኤ.አ. እስከ ጁን 30 ቀን 2024 ድረስ የገዙት የቦንድ መጠን 94 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት ዕዳ መግለጫ ያመለክታል።
በገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴው ያሳለፈው ሌላኛው ውሳኔ በባንኮች ላይ የተጣለውን የብድር ዕቀባ የተመለከተ ሲሆን ፣ በአሁኑ ወቅት በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ጣሪያ እስከ መጪው መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲቀጠል ኮሚቴው ወስኗል።ለዚህም የሰጠው ምክንያት አሁን ላይ የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ እየተስተዋለ ቢሆንም ይህንን ማስቀጠል አስፈላጊ በመሆኑ በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕድገት ጣሪያ ባለበት እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ እንደሆነ የሚገልጽ ነው።
Via Reporter
"በሚቀጥሉት 40 ወራት ውስጥ አፍሪካ በማዳበሪያ እራሷን ትችላለች"- አሊኮ ዳንጎቴ
ናይጄሪያዊው የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ አፍሪካ በመጪዎቹ 40 ወራት ውስጥ በማዳበሪያ ምርት እራሷን ትችላለች አሉ።
ዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካው ላይ የ2.5 ቢሊየን ዶላር ማስፋፊያ ለማድረግ ያቀደ ሲሆን ይህም አፍሪካ ከውጪ የምታስገባውን ምርት በእጅጉ ይቀንሳል ተብሏል።
ቢሊየነሩ" አፍሪካ ከ40 ወራት በኋላ ከየትኛውም ቦታ ማዳበሪያ አታስገባም፤ 40 ወራት ብቻ ስጡኝ፥ ዳንጎቴ ከኳታር የበለጠ የዩራያ አምራች እንዲሆን እናደርገዋለን" ብለዋል።
አፍሪካ በአሁኑ ጊዜ ከ6 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ በላይ በአመት ከሌላው አለም እያስገባች ሲሆን አሁን ያለው የዳንጎቴ ፋብሪካ በአመት 3 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም ገንብቷል።
የዳንጎቴ ፋብሪካ የድርጅቱን 37 በመቶ ምርት ለአሜሪካ ገበያ እያቀረበ መሆኑን ጠቅሶ ከማስፋፊያው በኋላ ምርቱን በእጥፍ በመጨመር የአፍሪካን ፍላጎት ያሟላል ተብሎ ይጠበቃል።
እንደ ግዙፉ የአፍሪካ ኤግዚም ባንክ ሪፖርት አፍሪካ በ2021 ከማዳበሪያ ሽያጭ 8.9 ቢሊየን ዶላር ገቢ ስታገኝ ትልቁን ድርሻ የሰሜን አፍሪካ ሃገራት ይይዛሉ ተብሏል።
ሞሮኮ እና ግብፅ 70 በመቶ የአፍሪካን የማዳበሪያ ሽያጭ ሲይዙ በድምሩ 6.23 ቢሊየን ዶላር አግኝተዋል።
ምንም እንኳን የተወሰኑ ሃገራት በማዳበሪያ እራሳቸውን የቻሉ ቢሆንም አብዛኞቹ አሁንም ከውጪ በሚገባ ምርት ላይ ጥገኛ ናቸው።
የዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካ በሚቀጥሉት ሁለት አመታትም በቀን 7 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን ቢሊየነሩ ገልፀዋል።
በ2022 ስራውን የጀመረው የሌጎሱ የዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካ በናይጄሪያ የምግብ እጥረትን ለመቀነስ በዝቅተኛ ዋጋ እየሸጠ ሲሆን የናይጄሪያን የ1.5 ሚሊየን ቶን አመታዊ የማዳበሪያ ፍጆታም ለመሸፈን እየሰራ ነው።
በአመት ከ400 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ የሚያስመጣው የማዳበሪያ ፋብሪካው የናይጄሪያን የውጪ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው።
የአፍሪካ የማዳበሪያ ዋጋ ከ15 ቢሊየን ዶላር የተሻገረ ሲሆን ይህ ቁጥር በ2030 ወደ 20 ቢሊየን እንደሚያድግ ይገመታል።
በምግብ እጥረት እና በውጪ ምንዛሬ ለምትፈተነው አፍሪካ የዳንጎቴ ፋብሪካ ሁነኛ መፍትሄ እንደሚሆን ሲጠቆም ቢሊየነሩ ዳንጎቴ የአህጉሪቱ መሪዎች የአህጉሪቱን ሃብትና ኢንቨስትመንት ባማከለ መልኩ አፍሪካን ተቀዳሚ አድርገው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት መስማማታቸው በቅርቡ ይፋ መደረጉም ይታወሳል።
Source: Reuters, Africa Fertilizer Watch
ናይጄሪያዊው የአፍሪካ ቁጥር አንድ ቢሊየነር አሊኮ ዳንጎቴ አፍሪካ በመጪዎቹ 40 ወራት ውስጥ በማዳበሪያ ምርት እራሷን ትችላለች አሉ።
ዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካው ላይ የ2.5 ቢሊየን ዶላር ማስፋፊያ ለማድረግ ያቀደ ሲሆን ይህም አፍሪካ ከውጪ የምታስገባውን ምርት በእጅጉ ይቀንሳል ተብሏል።
ቢሊየነሩ" አፍሪካ ከ40 ወራት በኋላ ከየትኛውም ቦታ ማዳበሪያ አታስገባም፤ 40 ወራት ብቻ ስጡኝ፥ ዳንጎቴ ከኳታር የበለጠ የዩራያ አምራች እንዲሆን እናደርገዋለን" ብለዋል።
አፍሪካ በአሁኑ ጊዜ ከ6 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ማዳበሪያ በላይ በአመት ከሌላው አለም እያስገባች ሲሆን አሁን ያለው የዳንጎቴ ፋብሪካ በአመት 3 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን ዩሪያ የማምረት አቅም ገንብቷል።
የዳንጎቴ ፋብሪካ የድርጅቱን 37 በመቶ ምርት ለአሜሪካ ገበያ እያቀረበ መሆኑን ጠቅሶ ከማስፋፊያው በኋላ ምርቱን በእጥፍ በመጨመር የአፍሪካን ፍላጎት ያሟላል ተብሎ ይጠበቃል።
እንደ ግዙፉ የአፍሪካ ኤግዚም ባንክ ሪፖርት አፍሪካ በ2021 ከማዳበሪያ ሽያጭ 8.9 ቢሊየን ዶላር ገቢ ስታገኝ ትልቁን ድርሻ የሰሜን አፍሪካ ሃገራት ይይዛሉ ተብሏል።
ሞሮኮ እና ግብፅ 70 በመቶ የአፍሪካን የማዳበሪያ ሽያጭ ሲይዙ በድምሩ 6.23 ቢሊየን ዶላር አግኝተዋል።
ምንም እንኳን የተወሰኑ ሃገራት በማዳበሪያ እራሳቸውን የቻሉ ቢሆንም አብዛኞቹ አሁንም ከውጪ በሚገባ ምርት ላይ ጥገኛ ናቸው።
የዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካ በሚቀጥሉት ሁለት አመታትም በቀን 7 ሚሊየን ዶላር ገቢ ለማግኘት ማቀዱን ቢሊየነሩ ገልፀዋል።
በ2022 ስራውን የጀመረው የሌጎሱ የዳንጎቴ የማዳበሪያ ፋብሪካ በናይጄሪያ የምግብ እጥረትን ለመቀነስ በዝቅተኛ ዋጋ እየሸጠ ሲሆን የናይጄሪያን የ1.5 ሚሊየን ቶን አመታዊ የማዳበሪያ ፍጆታም ለመሸፈን እየሰራ ነው።
በአመት ከ400 ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ የሚያስመጣው የማዳበሪያ ፋብሪካው የናይጄሪያን የውጪ ምንዛሬ እጥረትን ለመቅረፍ ጉልህ ሚና እየተጫወተ ነው።
የአፍሪካ የማዳበሪያ ዋጋ ከ15 ቢሊየን ዶላር የተሻገረ ሲሆን ይህ ቁጥር በ2030 ወደ 20 ቢሊየን እንደሚያድግ ይገመታል።
በምግብ እጥረት እና በውጪ ምንዛሬ ለምትፈተነው አፍሪካ የዳንጎቴ ፋብሪካ ሁነኛ መፍትሄ እንደሚሆን ሲጠቆም ቢሊየነሩ ዳንጎቴ የአህጉሪቱ መሪዎች የአህጉሪቱን ሃብትና ኢንቨስትመንት ባማከለ መልኩ አፍሪካን ተቀዳሚ አድርገው እንዲሰሩ ጠይቀዋል።
ቢሊየነሩ አሊኮ ዳንጎቴ በኢትዮጵያ የማዳበሪያ ፋብሪካ ለመገንባት መስማማታቸው በቅርቡ ይፋ መደረጉም ይታወሳል።
Source: Reuters, Africa Fertilizer Watch
“በአዲስ አበባ የትግራይ ተወላጆች ላይ ያነጣጠረ የዘፈቀደ እስራት እየተፈጸመ ነው” - ሂዩማን ራይት ፈርስት
ሂዩማን ራይትስ ፈርስት የተሰኘ የሃገር ውስጥ መብት ተሟጋች ድርጅት “በአዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወጣቶች በከተማዋ ባለስለጣናት ኢላማ ተደርገው፣ ያለምንም መደበኛ ክስ እና ፍርድ ሂደት በማንነታቸው ምክንያት “የዘፈቀደ እስራት” እየተፈጸመባቸው ነው” ሲል ክስ አቀረበ።
በተመሳሳይ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ትላንት ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች በፀጥታ ሃይሎች በዘፈቀደ እየታፈሱ እና በህገወጥ መንገድ እየታሰሩ እንደሚገኙ ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል።
ለእስር ተዳርገው በኋላ ላይ መፈታታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ያስታወቁ አንድ በከተማዋ ነዋሪ የሆኑ የትግራይ ተወላጅ ለምን እንደታሰርን ስንጠይቃቸው ምንም አይነት ማብራሪያ አልሰጡንም ብለዋል፤ “ከበላይ አካል የመጣ ትዕዛዝ ነው” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን፤ ክስ አልተመሰረተብንም፣ ፍርድ ቤትም አለቀረብንም” ብለዋል።
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) እንዲሁም ሂዩማን ራይት ፈርስት “ዜጎችን ስማቸውን ወይም ብሄራቸውን መሰረት በማድረግ ለእስር መዳረግ ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ህግጋትን የሚጻረር እና መጣስ ነው” ሲል በመኮነን “ያለ ፍርድ ሂደት ለእስር የታዳረጉት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ” ሲሉ በተናጠል ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።
ሂዩማን ራይትስ ፈርስት የተሰኘ የሃገር ውስጥ መብት ተሟጋች ድርጅት “በአዲስ አበባ የሚገኙ የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወጣቶች በከተማዋ ባለስለጣናት ኢላማ ተደርገው፣ ያለምንም መደበኛ ክስ እና ፍርድ ሂደት በማንነታቸው ምክንያት “የዘፈቀደ እስራት” እየተፈጸመባቸው ነው” ሲል ክስ አቀረበ።
በተመሳሳይ በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሰው ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) ትላንት ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ ነዋሪነታቸው በአዲስ አበባ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች በፀጥታ ሃይሎች በዘፈቀደ እየታፈሱ እና በህገወጥ መንገድ እየታሰሩ እንደሚገኙ ሪፖርት እንደደረሰው አስታውቋል።
ለእስር ተዳርገው በኋላ ላይ መፈታታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ያስታወቁ አንድ በከተማዋ ነዋሪ የሆኑ የትግራይ ተወላጅ ለምን እንደታሰርን ስንጠይቃቸው ምንም አይነት ማብራሪያ አልሰጡንም ብለዋል፤ “ከበላይ አካል የመጣ ትዕዛዝ ነው” የሚል ምላሽ ነው የሰጡን፤ ክስ አልተመሰረተብንም፣ ፍርድ ቤትም አለቀረብንም” ብለዋል።
ሳልሳይ ወያነ ትግራይ (ሳወት) እንዲሁም ሂዩማን ራይት ፈርስት “ዜጎችን ስማቸውን ወይም ብሄራቸውን መሰረት በማድረግ ለእስር መዳረግ ሀገር አቀፍ እና አለም አቀፍ ህግጋትን የሚጻረር እና መጣስ ነው” ሲል በመኮነን “ያለ ፍርድ ሂደት ለእስር የታዳረጉት ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ” ሲሉ በተናጠል ባወጡት መግለጫ ጠይቀዋል።
የቻይና ሰላዮች በአሜሪካ
በአሜሪካ ውስጥ ለቻይና ሲሰልሉ የነበሩ 2 የቻይና ዜግነት ያላቸውን ሠዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአሜሪካን የባህር ሃይል ጣቢያን ፎቶግራፍ በማንሳት፣ አመጽ በገንዘብ በመደገፍና በማስተባበር እንዲሁም የተለያዩ የስለላ ስራዎችን በመስራት በሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የሳን ፍራንሲስኮ የፌደራል ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ እንደገለጹት ፣ የቻይና መንግስት ስለ አሜሪካ ወታደራዊ አቅም በድብቅ መረጃ ለመሰብሰብ የቻይና መንግስት የማያቋርጥ ጥረቶች ማሣያ ነው በማለት አብራርተዋል።
አክለውም "ይህ ጉዳይ የቻይና መንግስት ወታደሮቻችንን ሰርጎ ለመግባት እና ብሄራዊ ደህንነታችንን ከውስጥ ለማዳከም የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ጥረት አጉልቶ ያሳያል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የውጭ ተላላኪዎችን እናጋልጣለን ፣ወኪሎቻቸውን እናያለን እና የአሜሪካን ህዝብ በብሄራዊ ደህንነታችን ላይ ከሚደርሱ ስውር አደጋዎች እንጠብቃለንም" ብለዋል።
እ.ኤ.አ በ2015 ወደ አሜሪካ የገቡት ሠላዮቹ ዩያንስ ቼን እና ሊረን ራያን በመባል ይጠራሉ። የቻይና መንግስት ደህንነት ሚኒስቴርን ወክለው ሚስጥራዊ የስለላ ስራዎችን ለመከታተል የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑም ገልጸዋል።
በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ቃል አቀባይ ሊዩ ፔንግዩ ስለ ጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸው ገልፀው፣ ነገር ግን በቻይና ላይ የተከሰሱ ውንጀላዎች ምንም ዓይነት ማስረጃ የላቸውም እንዲሁም አሜሪካ በቻይና ላይ የምታደርገውን የስለላ ተግባር አላቆመችም ማለታቸውን ኤፒ ዘግቧል።
በአሜሪካ ውስጥ ለቻይና ሲሰልሉ የነበሩ 2 የቻይና ዜግነት ያላቸውን ሠዎች ክስ እንደተመሰረተባቸው የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የአሜሪካን የባህር ሃይል ጣቢያን ፎቶግራፍ በማንሳት፣ አመጽ በገንዘብ በመደገፍና በማስተባበር እንዲሁም የተለያዩ የስለላ ስራዎችን በመስራት በሚል ክስ ተመስርቶባቸዋል።
የሳን ፍራንሲስኮ የፌደራል ፍርድ ቤት አቃቤ ህግ እንደገለጹት ፣ የቻይና መንግስት ስለ አሜሪካ ወታደራዊ አቅም በድብቅ መረጃ ለመሰብሰብ የቻይና መንግስት የማያቋርጥ ጥረቶች ማሣያ ነው በማለት አብራርተዋል።
አክለውም "ይህ ጉዳይ የቻይና መንግስት ወታደሮቻችንን ሰርጎ ለመግባት እና ብሄራዊ ደህንነታችንን ከውስጥ ለማዳከም የሚያደርገውን ያልተቋረጠ ጥረት አጉልቶ ያሳያል" ሲሉ ተናግረዋል።
"የውጭ ተላላኪዎችን እናጋልጣለን ፣ወኪሎቻቸውን እናያለን እና የአሜሪካን ህዝብ በብሄራዊ ደህንነታችን ላይ ከሚደርሱ ስውር አደጋዎች እንጠብቃለንም" ብለዋል።
እ.ኤ.አ በ2015 ወደ አሜሪካ የገቡት ሠላዮቹ ዩያንስ ቼን እና ሊረን ራያን በመባል ይጠራሉ። የቻይና መንግስት ደህንነት ሚኒስቴርን ወክለው ሚስጥራዊ የስለላ ስራዎችን ለመከታተል የተደረገው ጥረት አካል እንደሆኑም ገልጸዋል።
በዋሽንግተን የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ ቃል አቀባይ ሊዩ ፔንግዩ ስለ ጉዳዩ መረጃ እንደሌላቸው ገልፀው፣ ነገር ግን በቻይና ላይ የተከሰሱ ውንጀላዎች ምንም ዓይነት ማስረጃ የላቸውም እንዲሁም አሜሪካ በቻይና ላይ የምታደርገውን የስለላ ተግባር አላቆመችም ማለታቸውን ኤፒ ዘግቧል።
ባልታዛር ተፈረደበት
የቀድሞው የኢኳቶሪያል ጊኒ የብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ ከበርካታ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው የ18 አመት እስራት ተፈረደባቸው።
ባልታዛር ባለፈው አመት መስከረም ወር ላይ ከበርካታ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ማረሚያ ቤት ታስረው ነበር።
የቀድሞ ብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ የፋይናንስ ወንጀሎችን ፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሙስናን የመከላከል ትልቅ ስልጣን ነበራቸው ።
ባልታዛር ኢንጎንጋ ከባለስልጣናቱ ጋር 1ቢሊዮን ፍራንክ ከመንግስት ካዝና አጭበርብረዋል ።
ባልታሳር ኢንጎንጋ ወደ ኪሳቸው 910 ፍራንክ እንዳስገቡ ተገልጿል ።
ከባልታዛር ጋር አገር ሲዘርፉ በነበሩት በሌሎች ባለስልጣናት ላይም ፍርዱ እንደሚቀጥል ተገልጿል
የቀድሞው የኢኳቶሪያል ጊኒ የብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ ከበርካታ የቀድሞ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው የ18 አመት እስራት ተፈረደባቸው።
ባልታዛር ባለፈው አመት መስከረም ወር ላይ ከበርካታ ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር የህዝብን ገንዘብ በማጭበርበር ወንጀል ተከሰው ማረሚያ ቤት ታስረው ነበር።
የቀድሞ ብሄራዊ የፋይናንስ ምርመራ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ባልታዛር ኢንጎንጋ የፋይናንስ ወንጀሎችን ፣ ህገወጥ የገንዘብ ዝውውር እና ሙስናን የመከላከል ትልቅ ስልጣን ነበራቸው ።
ባልታዛር ኢንጎንጋ ከባለስልጣናቱ ጋር 1ቢሊዮን ፍራንክ ከመንግስት ካዝና አጭበርብረዋል ።
ባልታሳር ኢንጎንጋ ወደ ኪሳቸው 910 ፍራንክ እንዳስገቡ ተገልጿል ።
ከባልታዛር ጋር አገር ሲዘርፉ በነበሩት በሌሎች ባለስልጣናት ላይም ፍርዱ እንደሚቀጥል ተገልጿል
ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የወባ በሽታ ጉዳዮችን ሪፖርት አደረገች
በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛው ቁጥርም 8.4 ሚሊዮን ደርሷል
የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሰረት፣ ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ብቻ 520,782 የወባ በሽታ ጉዳዮችን ሪፖርት አድርጋለች። ይህ ቁጥር አሳሳቢ ሲሆን፣ በ2024 በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው የወባ በሽታ ጉዳይ ደግሞ ከ8.4 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገልጿል፤ ይህም እስካሁን ከተመዘገበው ሁሉ ከፍተኛው ነው።
የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ የጤና ክላስተር ቡለቲን ሪፖርቱ ላይ እንዳብራራው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከወባ በተጨማሪ እንደ ኮሌራ፣ ኩፍኝ እና ኤምፖክስ (mpox) የመሳሰሉ በርካታ በሽታዎችን እየተቋቋመች ትገኛለች።
በተለይም በአገሪቱ እየተካሄዱ ያሉት ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ሲሆን፣ ብዙ ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ እጦትና የተገደበ የጤና አገልግሎት በሚያገኙባቸው አካባቢዎች ተይዘው ይገኛሉ።
ወባ በኢትዮጵያ ከባህር ወለል በላይ በ2,000 ሜትር ከፍታ በታች ባሉ አካባቢዎች በስፋት የሚታይ በሽታ ነው። እነዚህ አካባቢዎች የአገሪቱን የመሬት ስፋት ሶስት አራተኛውን የሚሸፍኑ ሲሆን፣ በእነዚህ ስፍራዎች ከሚኖሩት የአገሪቱ ህዝብ ውስጥ 69 በመቶ የሚሆነው በበሽታው የመያዝ ስጋት ተጋርጦበታል።
የወባ በሽታ ስርጭት በተለምዶ ከዋናው የዝናብ ወቅት በኋላ ከመስከረም እስከ ታህሳስ ባሉት ወራት፣ እና ከሁለተኛው የዝናብ ወቅት በኋላ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት ባሉት ወራት ይጨምራል።
Capital
በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው ከፍተኛው ቁጥርም 8.4 ሚሊዮን ደርሷል
የዓለም ጤና ድርጅት ባወጣው ሪፖርት መሰረት፣ ኢትዮጵያ በግንቦት ወር ብቻ 520,782 የወባ በሽታ ጉዳዮችን ሪፖርት አድርጋለች። ይህ ቁጥር አሳሳቢ ሲሆን፣ በ2024 በአንድ ዓመት ውስጥ የተመዘገበው የወባ በሽታ ጉዳይ ደግሞ ከ8.4 ሚሊዮን በላይ መድረሱ ተገልጿል፤ ይህም እስካሁን ከተመዘገበው ሁሉ ከፍተኛው ነው።
የዓለም ጤና ድርጅት በኢትዮጵያ የጤና ክላስተር ቡለቲን ሪፖርቱ ላይ እንዳብራራው፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከወባ በተጨማሪ እንደ ኮሌራ፣ ኩፍኝ እና ኤምፖክስ (mpox) የመሳሰሉ በርካታ በሽታዎችን እየተቋቋመች ትገኛለች።
በተለይም በአገሪቱ እየተካሄዱ ያሉት ግጭቶች በህዝብ ጤና ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እያሳደሩ ሲሆን፣ ብዙ ሰዎች የሰብአዊ እርዳታ እጦትና የተገደበ የጤና አገልግሎት በሚያገኙባቸው አካባቢዎች ተይዘው ይገኛሉ።
ወባ በኢትዮጵያ ከባህር ወለል በላይ በ2,000 ሜትር ከፍታ በታች ባሉ አካባቢዎች በስፋት የሚታይ በሽታ ነው። እነዚህ አካባቢዎች የአገሪቱን የመሬት ስፋት ሶስት አራተኛውን የሚሸፍኑ ሲሆን፣ በእነዚህ ስፍራዎች ከሚኖሩት የአገሪቱ ህዝብ ውስጥ 69 በመቶ የሚሆነው በበሽታው የመያዝ ስጋት ተጋርጦበታል።
የወባ በሽታ ስርጭት በተለምዶ ከዋናው የዝናብ ወቅት በኋላ ከመስከረም እስከ ታህሳስ ባሉት ወራት፣ እና ከሁለተኛው የዝናብ ወቅት በኋላ ከሚያዝያ እስከ ግንቦት ባሉት ወራት ይጨምራል።
Capital
ኢትዮጵያ ከዓለም ባንክ ገቢ ምደባ ዝርዝር ዉጪ መሆኗ ተገለፀ
የ2025 የበጀት ዓመት ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ተብላ የተመደበችው ኢትዮጵያ፣ ለ2026 የበጀት ዓመት የዓለም ባንክ የገቢ ምደባ ዝርዝር ውስጥ አለመካተቷ ካፒታል ተመልክቷል።
የዓለም ባንክ በየዓመቱ ሐምሌ 1 ቀን በሚያወጣው የሀገራት ገቢ ምደባ፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት "ጊዜያዊ ምደባ አልተሰጣትም" ተብሏል። ይህ ማለት ኢትዮጵያ በዝቅተኛ ገቢ ወይም ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ሀገራት ምድብ ውስጥ አልተካተተችም ማለት ነው።
ያልተመደቡ አገሮችን በተመለከተ መረጃው እንደሚያረጋግጠው :- ቬንዙዌላ እስከ 2021 ድረስ የከፍተኛ መካከለኛ ገቢ አገር የነበረች ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መረጃ ባለመኖሩ ምክንያት ከምደባ ውጭ ሆናለች። ኢትዮጵያም በአሁኑ ወቅት ለ 2026 በጀት በጊዜያዊነት ከምደባ ውጭ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።
የዓለም ባንክ የ2025 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ዝርዝር በ2023 የአንድ ሰው አጠቃላይ አገራዊ ገቢ (GNI) 1,195 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከዚያ በታች የሆኑ አገሮችን ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ አንደኛው ነበረች።
ምንም እንኳን የዚህ ምደባ አለመስጠት ትክክለኛ ምክንያቶች ግልጽ ባይሆኑም፣ የሀገር ገቢ ምድብ ለውጦች በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ይገለጻል ።
"በአትላስ" ዘዴ በሚሰላው የነፍስ ወከፍ GNI ላይ በሚከሰቱ ለውጦች (ለምሳሌ የኢኮኖሚ እድገት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የምንዛሪ ተመን እና የህዝብ ብዛት መጨመር ወይም በምደባ ወሰኖቹ ላይ በሚደረጉ ማስተካከያዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
Capital newspaper
የ2025 የበጀት ዓመት ዝቅተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ተብላ የተመደበችው ኢትዮጵያ፣ ለ2026 የበጀት ዓመት የዓለም ባንክ የገቢ ምደባ ዝርዝር ውስጥ አለመካተቷ ካፒታል ተመልክቷል።
የዓለም ባንክ በየዓመቱ ሐምሌ 1 ቀን በሚያወጣው የሀገራት ገቢ ምደባ፣ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት "ጊዜያዊ ምደባ አልተሰጣትም" ተብሏል። ይህ ማለት ኢትዮጵያ በዝቅተኛ ገቢ ወይም ዝቅተኛ መካከለኛ ገቢ ሀገራት ምድብ ውስጥ አልተካተተችም ማለት ነው።
ያልተመደቡ አገሮችን በተመለከተ መረጃው እንደሚያረጋግጠው :- ቬንዙዌላ እስከ 2021 ድረስ የከፍተኛ መካከለኛ ገቢ አገር የነበረች ቢሆንም፣ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ መረጃ ባለመኖሩ ምክንያት ከምደባ ውጭ ሆናለች። ኢትዮጵያም በአሁኑ ወቅት ለ 2026 በጀት በጊዜያዊነት ከምደባ ውጭ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።
የዓለም ባንክ የ2025 ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው አገሮች ዝርዝር በ2023 የአንድ ሰው አጠቃላይ አገራዊ ገቢ (GNI) 1,195 የአሜሪካ ዶላር ወይም ከዚያ በታች የሆኑ አገሮችን ይፋ ሲያደርግ ኢትዮጵያ አንደኛው ነበረች።
ምንም እንኳን የዚህ ምደባ አለመስጠት ትክክለኛ ምክንያቶች ግልጽ ባይሆኑም፣ የሀገር ገቢ ምድብ ለውጦች በሁለት ዋና ዋና ምክንያቶች ሊከሰቱ እንደሚችሉ ይገለጻል ።
"በአትላስ" ዘዴ በሚሰላው የነፍስ ወከፍ GNI ላይ በሚከሰቱ ለውጦች (ለምሳሌ የኢኮኖሚ እድገት፣ የዋጋ ግሽበት፣ የምንዛሪ ተመን እና የህዝብ ብዛት መጨመር ወይም በምደባ ወሰኖቹ ላይ በሚደረጉ ማስተካከያዎች ሊሆኑ እንደሚችሉ ተጠቁሟል።
Capital newspaper
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት ለመጀመሪያ ጊዜ የፊታችን መስከረም ወር ላይ ለገበያ ታቀርባለች - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት የፊታችን መስከረም ወር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለገበያ ታቀርባለች አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው፡፡
በማብራሪያቸውም በለውጡ መንግስት ጋዝ ለማምረት ፋብሪካዎች ለመትከል ስምምነት ተደርጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ጋዝና አካባቢ የሚመጡ የግል ድርጅቶች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የነበራቸው ፍላጎት ፈቃድ መውሰድና በዛ ፈቃድ ብር መፈለግ ነበር ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ አካሄድና መንገድ አያዋጣም ብለን የነበሩትን በመሰረዝ አዳዲስ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ እንዲገቡ አድርገናል ነው ያሉት፡፡
ይህን ተከትሎም ምናልባትም የምክር ቤት አባላት ከእረፍት ሲመለሱ የፊታችን መስከረም ወር ላይ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋዝ ምርት ለገበያ ታቀርባለች ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት የፊታችን መስከረም ወር ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ ለገበያ ታቀርባለች አሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ በምክር ቤቱ 42ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ተገኝተው የመንግስትን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከምክር ቤቱ አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እየሰጡ ነው፡፡
በማብራሪያቸውም በለውጡ መንግስት ጋዝ ለማምረት ፋብሪካዎች ለመትከል ስምምነት ተደርጎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ጋዝና አካባቢ የሚመጡ የግል ድርጅቶች እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ የነበራቸው ፍላጎት ፈቃድ መውሰድና በዛ ፈቃድ ብር መፈለግ ነበር ሲሉም ተናግረዋል፡፡
ይሁን እንጂ ይህ አካሄድና መንገድ አያዋጣም ብለን የነበሩትን በመሰረዝ አዳዲስ ኩባንያዎች ወደ ዘርፉ እንዲገቡ አድርገናል ነው ያሉት፡፡
ይህን ተከትሎም ምናልባትም የምክር ቤት አባላት ከእረፍት ሲመለሱ የፊታችን መስከረም ወር ላይ ኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የጋዝ ምርት ለገበያ ታቀርባለች ብለዋል፡፡