በወተት ምርቶች ላይ የአስከሬን ማድረቂያ የሚጠቀሙ ነጋዴዎች እንዳሉ ተገለጸ
አንዳንድ የወተትና መሰል ምርት አምራቾች የምርቶቻቸውን የቆይታ ጊዜና መጠን ለመጨመር ሲሉ የአስክሬን ማድረቂያ (ፎርማሊን) ጭምር እንደሚጠቀሙ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ።
በምግብ ውስጥ የሚጨመሩት እነዚህ ባዕድ ነገሮች በሰው ጤና ላይ ከፍተኛ ችግር እንደሚያስከትሉ የገለጸው ባለሥልጣኑ፣ በየጊዜው ክትትል በማድረግ ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶችን ለገበያ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የምግብ ኢንስፔክሽንና ሕግ ማስፈፀም ሥራ አስፈፃሚ ሙላት ተስፋዬ ለሸገር ሬዲዮ ተናግረዋል።
ሥራ አስፈፃሚው አሁን ላይ በገበያው ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶች መገኘታቸው ቢቀጥልም፣ ከነበረበት መጠን ግን የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም፣ ድርጊቱን ፈጽመው በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎችንና የቅጣት መጠንን ከፍ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።
የባለሥልጣኑ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት በምግብ ነክና የመድኃኒት ምርቶች ላይ 14,171 የምርመራና ፍተሻ ሥራዎች ተከናውነዋል። ከእነዚህም ውስጥ በአጠቃላይ 3,155 የሚሆኑት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እንደተወሰደባቸው ተጠቁሟል።
አንዳንድ የወተትና መሰል ምርት አምራቾች የምርቶቻቸውን የቆይታ ጊዜና መጠን ለመጨመር ሲሉ የአስክሬን ማድረቂያ (ፎርማሊን) ጭምር እንደሚጠቀሙ የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን አስታወቀ።
በምግብ ውስጥ የሚጨመሩት እነዚህ ባዕድ ነገሮች በሰው ጤና ላይ ከፍተኛ ችግር እንደሚያስከትሉ የገለጸው ባለሥልጣኑ፣ በየጊዜው ክትትል በማድረግ ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶችን ለገበያ በሚያቀርቡ ነጋዴዎች ላይ ሕጋዊ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የምግብ ኢንስፔክሽንና ሕግ ማስፈፀም ሥራ አስፈፃሚ ሙላት ተስፋዬ ለሸገር ሬዲዮ ተናግረዋል።
ሥራ አስፈፃሚው አሁን ላይ በገበያው ባዕድ ነገሮች የተቀላቀለባቸው ምርቶች መገኘታቸው ቢቀጥልም፣ ከነበረበት መጠን ግን የመቀነስ አዝማሚያ እያሳየ መሆኑን ጠቁመዋል።
በተጨማሪም፣ ድርጊቱን ፈጽመው በሚገኙ ነጋዴዎች ላይ የሚወሰዱ እርምጃዎችንና የቅጣት መጠንን ከፍ ማድረግ እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።
የባለሥልጣኑ ሪፖርት እንደሚያሳየው፣ ከ2012 እስከ 2016 ዓ.ም ባሉት ጊዜያት በምግብ ነክና የመድኃኒት ምርቶች ላይ 14,171 የምርመራና ፍተሻ ሥራዎች ተከናውነዋል። ከእነዚህም ውስጥ በአጠቃላይ 3,155 የሚሆኑት ላይ አስተዳደራዊ እርምጃዎች እንደተወሰደባቸው ተጠቁሟል።
አሜሪካ ኤምባሲዎቿ የተማሪዎች የቪዛ ቀጠሮ እንዳይሰጡ አዘዘች!
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በውጭ አገሮች የሚገኙ ኤምባሲዎቹ የተማሪዎች የቪዛ ቀጠሮ እንዳይሰጡ አዘዘ።የአመልካቾችን የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የማጣራት ሂደት ለማስፋት በዝግጅት ላይ እንዳለ ያስተዋወቀው አስተዳደሩ፤ ለተማሪዎች የቪዛ ቀጠሮ እንዳይሰጥ በጊዜያዊነት አግዷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ መልዕክት በሰፈረበት ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በተላከ ማስታወሻ ላይ እገዳው "ተጨማሪ መመሪያ እስኪወጣ ድረስ" ይቆያል ተብሏል።አስተዳደሩ የተማሪዎች አመልካቾች የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን የማጣራት ስራ አጠናክሮ የሚሰራ ሲሆን ይህም በኤምባሲዎች እና በቆንስላ ጽ/ቤቶች ላይ ትልቅ አንድምታ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ትራምፕ የግራውን ርዕዮተዓለም እየተከተሉ ናቸው ካሏቸው ታዋቂ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ የተወሰነ ውሳኔ ነው።አንዳንዶቹ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች በግቢያቸው ውስጥ በሚደረገው የፍልስጤም ድጋፎች ለጸረ-ሴማዊነት በር ከፍተዋል ሲል ዋይት ሃውስ ከሷቸዋል።
ዩኒቨርስቲዎች በበኩላቸው የትራምፕ አስተዳደር በነጻነት ሃሳብን የመግለጽ መብቶችን ለመጣስ እየሞከረ ነው ሲሉ ይወቅሳሉ።ፕሬዚዳንት ትራምፕ ታዋቂው ዩኒቨርስቲ ሐርቫርድ የውጭ አገር ተማሪዎችን እንዲሁም ተመራማሪዎችን እንዳይቀበል በሚል ፈቃዱን ቢሰርዙም ይህ ፖሊሲያቸው በፌደራል ዳኛ ታግዷል።ይህ በሐርቫርድ ላይ የጣሉት ውሳኔ ተግባራዊ የሚሆን ከሆነ ሩብ የሚሆኑት ተማሪዎቹ ከውጭ አገር የሆኑት ተቋሙ በከፍተኛ ሁኔታ ሊጎዳ ይችላል ተብሏል።
Via BBC
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በውጭ አገሮች የሚገኙ ኤምባሲዎቹ የተማሪዎች የቪዛ ቀጠሮ እንዳይሰጡ አዘዘ።የአመልካቾችን የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች የማጣራት ሂደት ለማስፋት በዝግጅት ላይ እንዳለ ያስተዋወቀው አስተዳደሩ፤ ለተማሪዎች የቪዛ ቀጠሮ እንዳይሰጥ በጊዜያዊነት አግዷል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ማርኮ ሩቢዮ መልዕክት በሰፈረበት ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰቡ በተላከ ማስታወሻ ላይ እገዳው "ተጨማሪ መመሪያ እስኪወጣ ድረስ" ይቆያል ተብሏል።አስተዳደሩ የተማሪዎች አመልካቾች የማህበራዊ ሚዲያ ገጾችን የማጣራት ስራ አጠናክሮ የሚሰራ ሲሆን ይህም በኤምባሲዎች እና በቆንስላ ጽ/ቤቶች ላይ ትልቅ አንድምታ እንደሚኖረው ተገልጿል።
ትራምፕ የግራውን ርዕዮተዓለም እየተከተሉ ናቸው ካሏቸው ታዋቂ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች ጋር ውዝግብ ውስጥ መግባታቸውን ተከትሎ የተወሰነ ውሳኔ ነው።አንዳንዶቹ የአሜሪካ ዩኒቨርስቲዎች በግቢያቸው ውስጥ በሚደረገው የፍልስጤም ድጋፎች ለጸረ-ሴማዊነት በር ከፍተዋል ሲል ዋይት ሃውስ ከሷቸዋል።
ዩኒቨርስቲዎች በበኩላቸው የትራምፕ አስተዳደር በነጻነት ሃሳብን የመግለጽ መብቶችን ለመጣስ እየሞከረ ነው ሲሉ ይወቅሳሉ።ፕሬዚዳንት ትራምፕ ታዋቂው ዩኒቨርስቲ ሐርቫርድ የውጭ አገር ተማሪዎችን እንዲሁም ተመራማሪዎችን እንዳይቀበል በሚል ፈቃዱን ቢሰርዙም ይህ ፖሊሲያቸው በፌደራል ዳኛ ታግዷል።ይህ በሐርቫርድ ላይ የጣሉት ውሳኔ ተግባራዊ የሚሆን ከሆነ ሩብ የሚሆኑት ተማሪዎቹ ከውጭ አገር የሆኑት ተቋሙ በከፍተኛ ሁኔታ ሊጎዳ ይችላል ተብሏል።
Via BBC
የሀገር ዉስጥ ብድር ክምችት 2.3 ትሪሊዮን ብር መድረሱ ተነገረ
የገንዘብ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ብድር መጠን በተመለከተ የወጡ የተሳሳቱ ዘገባዎችን አስተባብሏል። ሚኒስቴሩ እንደገለጸው፣ እ.ኤ.አ እስከ 2024 መጨረሻ ድረስ የኢትዮጵያ የውጭ ብድር መጠን የመንግሥት ልማት ድርጅቶችን ጨምሮ 31.6 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፣ የሀገር ውስጥ ብድር ክምችት ደግሞ 2.3 ትሪሊዮን ብር ደርሷል ብሏል።
ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር የወጣውን ሪፖርት በማጣቀስ፣ “እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን ከ575 ዶላር መድረሱ ተነገረ” በሚል ርዕስ የወጣው ዘገባ ላይ ግድፈቶች እንዳሉ የገንዘብ ሚኒስቴር ገልጿል። ዘገባው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ የነበራትን የውጭ ዕዳ መጠን 28.5 ቢሊዮን ዶላር ሆኖ ሳለ 62.5 ቢሊዮን ዶላር በማለት ማቅረቡ የተሳሳተ መሆኑን ሚኒስቴሩ አብራርቷል።
ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ የውጭ ብድር በአብዛኛው የተጠራቀመ ውርስ ዕዳ (legacy debt) መሆኑን ጠቁሞ፣ መንግሥት ባለፉት ሰባት ዓመታት ይህንን የክፍያ ጫና ለመቀነስ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል። Capital
የገንዘብ ሚኒስቴር ኢትዮጵያ ያለባትን የውጭ ብድር መጠን በተመለከተ የወጡ የተሳሳቱ ዘገባዎችን አስተባብሏል። ሚኒስቴሩ እንደገለጸው፣ እ.ኤ.አ እስከ 2024 መጨረሻ ድረስ የኢትዮጵያ የውጭ ብድር መጠን የመንግሥት ልማት ድርጅቶችን ጨምሮ 31.6 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን፣ የሀገር ውስጥ ብድር ክምችት ደግሞ 2.3 ትሪሊዮን ብር ደርሷል ብሏል።
ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ማህበር የወጣውን ሪፖርት በማጣቀስ፣ “እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ያለበት የውጭ ዕዳ መጠን ከ575 ዶላር መድረሱ ተነገረ” በሚል ርዕስ የወጣው ዘገባ ላይ ግድፈቶች እንዳሉ የገንዘብ ሚኒስቴር ገልጿል። ዘገባው ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ እስከ 2023 ድረስ የነበራትን የውጭ ዕዳ መጠን 28.5 ቢሊዮን ዶላር ሆኖ ሳለ 62.5 ቢሊዮን ዶላር በማለት ማቅረቡ የተሳሳተ መሆኑን ሚኒስቴሩ አብራርቷል።
ሚኒስቴሩ ባወጣው መግለጫ፣ የኢትዮጵያ የውጭ ብድር በአብዛኛው የተጠራቀመ ውርስ ዕዳ (legacy debt) መሆኑን ጠቁሞ፣ መንግሥት ባለፉት ሰባት ዓመታት ይህንን የክፍያ ጫና ለመቀነስ ጥረቶችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል። Capital
የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች በማራኪ እና ሳቢ በሆኑ ስልቶች ወጣቶችን በሱስ እንዲጠመዱ እያደረጉ መሆኑ ተነገረ
ኢንዱስትሪዎቹ፤ ቄንጠኛ ዲዛይኖች፣ ማራኪ ቀለሞች፣ አሳሳች ንድፎች፣ ጣዕማቸውን የሚያጣፍጡ ቅመሞች እና ንጥረ ነገሮችን በመጨመር በዲጅታል ሚዲያ እና በሌሎች መገናኛ ዘዴዎች ወደ ወጣቶች እያሰራጩ ይገኛሉ ተብሏል፡፡
የተጠቀሱት እና ሌሎች ዘዴዎች ያለማቋረጥ በመጠቀምም የትምባሆ ጎጂነትን ስልታዊ በሆነ መልኩ በመደበቅ ህጻናት እና ወጣቶችን እያማመሉ በሱስ እንዲጠመዱ እያደረጉ ነው መባሉን ሰምተናል፡፡
የአለም ትምባሆ የማይጨስበት ቀን በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ38ኛ ጊዜ ነገ ግንቦት 23 2017 ይከበራል፡፡
እለቱን አስመልክቶም የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ከሌሎች ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል፡፡
በነገው እዕት ለሚከበረው የዓለም ትንባሆ የማይጨስበት ቀንም “በትምባሆ እና በኒኮቲን ምርቶች ላይ፤ የትምባሆ ኢንዱስትሪ አሳሳችና ድብቅ ስልቶችን በማጋለጥ ወጣቶችን እንታደግ” የሚል መሪ ቃል ተመርጦለታል፡፡
የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን የአጮሾች ቁጥር ለመቀነስ እና በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳትም ዝቅ ለማድረግ ለመቀነስ የተለያዩ የግንዛቤ መስጫ እና የቁጥጥር ስራዎችን እየሰራሁ ነው ሲል ተናግሯል፡፡
ባለስልጣኑ ባለፉት 8 ዓመታት የሀገሪቱን ተጠቃሚዎችን በተመለከተ ከሌሎች ከሚመለከታቸው ጋራ ሁለቴ (እ.ኤ.አ በ2016 እና በ2024) የዳሰሳ ጥናት አድርጊያለሁም ብሏል፡፡
ከ8 ዓመት በፊት የተጠናው ጥናት በኢትዮጵያ የትምባሆ ተጠቃሚዎች ቁጥር 5 በመቶ የነበረ ሲሆን ከአንድ ዓመት በፊት የተጠናው ጥናት ደግሞ የተጠቃሚዎች ቁጥር በአንፃራዊነት ቀንሶ 4.6 በመቶ ሆኖ ታይቷል ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፡፡
በ2016ቱ ጥናት 1.2 በመቶ የነበረው የሴት ትምባሆ አጫሾች ቁጥርም በ2024ቱ ጥናት ወደ 0.4 በመቶ ዝቅ እንዳለም ተነግሯል፡፡
በዓለም ዙሪያ 1.3 ቢሊዮን የትምባሆ ተጠቃሚዎች እንዳሉና ከ8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ደግሞ በየዓመቱ በዚሁ የተነሳ ህይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡
በትምባሆ ምክንያት ህወይታቸውን ከሚያጡ ከእነዚህ መካካልም 1 ሚሊዮን ገደማዎቹ የትምባሆ ተጠቃሚ ሳይሆኑ በአካካቢያቸው ሌሎች ሲጠቀሙ በሚያገኛቸው የትምባሆ ጭስ የተነሳ ነው ተብሏል፡፡
በትምባሆ ቅጠል ውስጥ ከ7,000 በላይ ኬሚካሎችን በውስጡ እንደሚይዘና ከእነዚህ ኬሚካሎችም አብዛኞቹ ጎጂ ሲሆኑ በተለይ 70 የሚሆኑ ካንሰር አምጪ ኬሚካል መሆናቸውን ተነግሯል፡፡
ሲጋራ ማጨስ እና ሌሎች የትምባሆ ምርቶችን መጠቀም በሱስ ለመያዝ፣ ለአደገኛ የሳንባ በሽታ፣ ለካንሰር፣ ለልብ በሽታ መዳረግ፣ ለፅንስ መጎዳት፣ በሚጨስበት አካባቢ በሚኖሩ እና በማያጨሱ ሰዎች ላይ ጭምር ከፍተኛ የሆነ የጤና መታወክ እና ሌሎችንም ጉዳቶች እያስከተለ ይገኛል ተብሏል፡፡
በአለም ላይ ካሉት 1.3 ቢሊዮን የትምባሆ ተጠቃሚዎች 80 በመቶ የሚያህሉት የሚኖሩት ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን እና ከጤና ጉዳቱ ባሻገር፤ የቤተሰብ ወጪን እንደ ምግብ እና መጠለያ ካሉት ከመሰረታዊ ፍላጎቶች ወደ ትምባሆ በማዞር ለድህነት አስተዋፅኦ እንደሚደርግም ከጥናቶች ተመልክተናል፡፡
ኢትዮጵያ በ2005 ዓ.ም በአለምጤና ድርጅት አማካኝነት የተዘጋጀውና የትምባሆ ተጠቃሚዎችን ቁጥር ለመቀነስ ታሳቢ ያደረገው እና ዝርዝር ድንዳጌዎችን የያዘ ዓለም አቀፍ የትምባሆ ቁጥጥር ማዕቀፍ ስምምነት ፈርማና በህጓ አካትታ እየሰራችበት እንደሆነ የምግብና መድሀኒት ባለስልጣን አስረድቷል፡፡
ይህ ስምምነት በትምባሆ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ መጣል፣ በምርቶቹ ማሸጊያ ላይ ጎጂነቱን በምስል በተደገፈ መልኩ ማሳየት እንዲሁም ማስታዊያዎችን ሙሉ በሙሉ ማገድ የትምባሆ አጫሾችን ለመቀነስ እንደ መፍትሄ ያስቀምጣል፡፡
በኢትዮጵያ፤ የተከለከለ ይዘት ያለው ትምባሆ፣ ሺሻ፣ የኤልክትሮኒክ ኒኮቲን መስጫ መሳሪያ ወይም ሌላ ተመሳሳይ ምርት ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ያመረተ፣ ያከማቸ፣ ያከፋፈለ እንዲሁም የሸጠ ሰው የተገኘ እንደሆ እስከ ሶስት ዓመት እስር እና ሁለት መቶ ሺህ ብር ድረስ እንደሚቀጣ በህግ ተቀምጧል፡፡
አንድ ትምባሆየሚያጨስ ሰው ከማያጨስ ሰው ጋር ሲነፃፀር በህይወት የመቆየት እድሜው ቢያንስ በ10 ዓመት ያጥራል መባሉንም ሰምተናል፡፡
ኢንዱስትሪዎቹ፤ ቄንጠኛ ዲዛይኖች፣ ማራኪ ቀለሞች፣ አሳሳች ንድፎች፣ ጣዕማቸውን የሚያጣፍጡ ቅመሞች እና ንጥረ ነገሮችን በመጨመር በዲጅታል ሚዲያ እና በሌሎች መገናኛ ዘዴዎች ወደ ወጣቶች እያሰራጩ ይገኛሉ ተብሏል፡፡
የተጠቀሱት እና ሌሎች ዘዴዎች ያለማቋረጥ በመጠቀምም የትምባሆ ጎጂነትን ስልታዊ በሆነ መልኩ በመደበቅ ህጻናት እና ወጣቶችን እያማመሉ በሱስ እንዲጠመዱ እያደረጉ ነው መባሉን ሰምተናል፡፡
የአለም ትምባሆ የማይጨስበት ቀን በኢትዮጵያ ለ33ኛ ጊዜ በዓለም አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ38ኛ ጊዜ ነገ ግንቦት 23 2017 ይከበራል፡፡
እለቱን አስመልክቶም የኢትዮጵያ የምግብና መድሃኒት ባለስልጣን ከሌሎች ከሚመለከታቸው ጋር በመሆን ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል፡፡
በነገው እዕት ለሚከበረው የዓለም ትንባሆ የማይጨስበት ቀንም “በትምባሆ እና በኒኮቲን ምርቶች ላይ፤ የትምባሆ ኢንዱስትሪ አሳሳችና ድብቅ ስልቶችን በማጋለጥ ወጣቶችን እንታደግ” የሚል መሪ ቃል ተመርጦለታል፡፡
የኢትዮጵያ ምግብና መድሀኒት ባለስልጣን የአጮሾች ቁጥር ለመቀነስ እና በሰዎች ላይ የሚያደርሰውን ጉዳትም ዝቅ ለማድረግ ለመቀነስ የተለያዩ የግንዛቤ መስጫ እና የቁጥጥር ስራዎችን እየሰራሁ ነው ሲል ተናግሯል፡፡
ባለስልጣኑ ባለፉት 8 ዓመታት የሀገሪቱን ተጠቃሚዎችን በተመለከተ ከሌሎች ከሚመለከታቸው ጋራ ሁለቴ (እ.ኤ.አ በ2016 እና በ2024) የዳሰሳ ጥናት አድርጊያለሁም ብሏል፡፡
ከ8 ዓመት በፊት የተጠናው ጥናት በኢትዮጵያ የትምባሆ ተጠቃሚዎች ቁጥር 5 በመቶ የነበረ ሲሆን ከአንድ ዓመት በፊት የተጠናው ጥናት ደግሞ የተጠቃሚዎች ቁጥር በአንፃራዊነት ቀንሶ 4.6 በመቶ ሆኖ ታይቷል ብሏል ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ፡፡
በ2016ቱ ጥናት 1.2 በመቶ የነበረው የሴት ትምባሆ አጫሾች ቁጥርም በ2024ቱ ጥናት ወደ 0.4 በመቶ ዝቅ እንዳለም ተነግሯል፡፡
በዓለም ዙሪያ 1.3 ቢሊዮን የትምባሆ ተጠቃሚዎች እንዳሉና ከ8 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ደግሞ በየዓመቱ በዚሁ የተነሳ ህይወታቸውን እንደሚያጡ የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያሳያል፡፡
በትምባሆ ምክንያት ህወይታቸውን ከሚያጡ ከእነዚህ መካካልም 1 ሚሊዮን ገደማዎቹ የትምባሆ ተጠቃሚ ሳይሆኑ በአካካቢያቸው ሌሎች ሲጠቀሙ በሚያገኛቸው የትምባሆ ጭስ የተነሳ ነው ተብሏል፡፡
በትምባሆ ቅጠል ውስጥ ከ7,000 በላይ ኬሚካሎችን በውስጡ እንደሚይዘና ከእነዚህ ኬሚካሎችም አብዛኞቹ ጎጂ ሲሆኑ በተለይ 70 የሚሆኑ ካንሰር አምጪ ኬሚካል መሆናቸውን ተነግሯል፡፡
ሲጋራ ማጨስ እና ሌሎች የትምባሆ ምርቶችን መጠቀም በሱስ ለመያዝ፣ ለአደገኛ የሳንባ በሽታ፣ ለካንሰር፣ ለልብ በሽታ መዳረግ፣ ለፅንስ መጎዳት፣ በሚጨስበት አካባቢ በሚኖሩ እና በማያጨሱ ሰዎች ላይ ጭምር ከፍተኛ የሆነ የጤና መታወክ እና ሌሎችንም ጉዳቶች እያስከተለ ይገኛል ተብሏል፡፡
በአለም ላይ ካሉት 1.3 ቢሊዮን የትምባሆ ተጠቃሚዎች 80 በመቶ የሚያህሉት የሚኖሩት ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት መሆኑን እና ከጤና ጉዳቱ ባሻገር፤ የቤተሰብ ወጪን እንደ ምግብ እና መጠለያ ካሉት ከመሰረታዊ ፍላጎቶች ወደ ትምባሆ በማዞር ለድህነት አስተዋፅኦ እንደሚደርግም ከጥናቶች ተመልክተናል፡፡
ኢትዮጵያ በ2005 ዓ.ም በአለምጤና ድርጅት አማካኝነት የተዘጋጀውና የትምባሆ ተጠቃሚዎችን ቁጥር ለመቀነስ ታሳቢ ያደረገው እና ዝርዝር ድንዳጌዎችን የያዘ ዓለም አቀፍ የትምባሆ ቁጥጥር ማዕቀፍ ስምምነት ፈርማና በህጓ አካትታ እየሰራችበት እንደሆነ የምግብና መድሀኒት ባለስልጣን አስረድቷል፡፡
ይህ ስምምነት በትምባሆ ምርቶች ላይ ከፍተኛ ቀረጥ መጣል፣ በምርቶቹ ማሸጊያ ላይ ጎጂነቱን በምስል በተደገፈ መልኩ ማሳየት እንዲሁም ማስታዊያዎችን ሙሉ በሙሉ ማገድ የትምባሆ አጫሾችን ለመቀነስ እንደ መፍትሄ ያስቀምጣል፡፡
በኢትዮጵያ፤ የተከለከለ ይዘት ያለው ትምባሆ፣ ሺሻ፣ የኤልክትሮኒክ ኒኮቲን መስጫ መሳሪያ ወይም ሌላ ተመሳሳይ ምርት ወደ ሀገር ውስጥ ያስገባ፣ ያመረተ፣ ያከማቸ፣ ያከፋፈለ እንዲሁም የሸጠ ሰው የተገኘ እንደሆ እስከ ሶስት ዓመት እስር እና ሁለት መቶ ሺህ ብር ድረስ እንደሚቀጣ በህግ ተቀምጧል፡፡
አንድ ትምባሆየሚያጨስ ሰው ከማያጨስ ሰው ጋር ሲነፃፀር በህይወት የመቆየት እድሜው ቢያንስ በ10 ዓመት ያጥራል መባሉንም ሰምተናል፡፡
ሳውዲ አረቢያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ14 ሀገራት ላይ የቪዛ እገዳ ጣለች
ሳውዲ አረቢያ በድምሩ በ14 ሀገራት ዜጎች ላይ የብሎክ ቪዛ ማውጣትን በጊዜያዊነት ማገዷን አስታውቃለች። ከነዚህ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ ሀገራት ይገኙበታል።
ይህ የቪዛ እገዳ አዲስ የጊዜያዊ የሥራ ቪዛ ማመልከቻዎችን እና በመጠባበቅ ላይ ያሉትንም የሚመለከት ነው የተባለ ሲሆን በውጭ ዜጎች የሥራ ኃይል ላይ የተመሰረቱ የሳውዲ አረቢያ ዘርፎችን እንደሚጎዳ ተገልጿል።
በእገዳው ሰለባ ሆነዋል ከተባሉት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፣ ግብፅ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ ሱዳን፣ ቱኒዚያ እና ሞሮኮ ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ የመን፣ ህንድ፣ ፓኪስታን እና ባንግላዲሽ ተካትተዋል።
እነዚህ ሀገራት ከሳውዲ አረቢያ ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍልሰትና የገንዘብ ዝውውር ስለሚያገኙ፣ እገዳው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያስከትል እንደሚችል ተዘግቧል።
የብሎክ ቪዛ የሳውዲ አረቢያ ቀጣሪዎች ቀድሞ በተፈቀደላቸው ኮታ የውጭ ሠራተኞችን እንዲቀጥሩ የሚያስችል ነው። የሳውዲ አረቢያ መንግስት የቪዛ እገዳውን የጣለበትን ዝርዝር ምክንያት ባይገልጽም፣ ይህ እርምጃ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ዕጣ ፈንታ አጣብቂኝ ውስጥ ሊጥል ይችላል ተብሏል።
ካፒታል ጋዜጣ
ሳውዲ አረቢያ በድምሩ በ14 ሀገራት ዜጎች ላይ የብሎክ ቪዛ ማውጣትን በጊዜያዊነት ማገዷን አስታውቃለች። ከነዚህ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያን ጨምሮ ሰባት የአፍሪካ ሀገራት ይገኙበታል።
ይህ የቪዛ እገዳ አዲስ የጊዜያዊ የሥራ ቪዛ ማመልከቻዎችን እና በመጠባበቅ ላይ ያሉትንም የሚመለከት ነው የተባለ ሲሆን በውጭ ዜጎች የሥራ ኃይል ላይ የተመሰረቱ የሳውዲ አረቢያ ዘርፎችን እንደሚጎዳ ተገልጿል።
በእገዳው ሰለባ ሆነዋል ከተባሉት የአፍሪካ ሀገራት መካከል ኢትዮጵያ ፣ ግብፅ፣ ናይጄሪያ፣ አልጄሪያ፣ ሱዳን፣ ቱኒዚያ እና ሞሮኮ ይገኙበታል። ከዚህ በተጨማሪ ኢንዶኔዥያ፣ ኢራቅ፣ ዮርዳኖስ፣ የመን፣ ህንድ፣ ፓኪስታን እና ባንግላዲሽ ተካትተዋል።
እነዚህ ሀገራት ከሳውዲ አረቢያ ከፍተኛ የሰው ኃይል ፍልሰትና የገንዘብ ዝውውር ስለሚያገኙ፣ እገዳው ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጫና ሊያስከትል እንደሚችል ተዘግቧል።
የብሎክ ቪዛ የሳውዲ አረቢያ ቀጣሪዎች ቀድሞ በተፈቀደላቸው ኮታ የውጭ ሠራተኞችን እንዲቀጥሩ የሚያስችል ነው። የሳውዲ አረቢያ መንግስት የቪዛ እገዳውን የጣለበትን ዝርዝር ምክንያት ባይገልጽም፣ ይህ እርምጃ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰራተኞችን ዕጣ ፈንታ አጣብቂኝ ውስጥ ሊጥል ይችላል ተብሏል።
ካፒታል ጋዜጣ
በMpox በሽታ የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በኢትዮጵያ የMpox (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) መገኘቱ ከተገለጸ በኃላ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ሚኒስቴሩ ይፋ አድርጓል።
እስካሁን 15 የላብራቶሪ ምርመራ ተካሂዶ 6 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን የ1 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል።
ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የMpox ኬዝ በሞያሌ ከተማ መገኘቱ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
በኢትዮጵያ የMpox (የዝንጀሮ ፈንጣጣ) መገኘቱ ከተገለጸ በኃላ በዛሬው ዕለት የመጀመሪያው ሞት መመዝገቡን ሚኒስቴሩ ይፋ አድርጓል።
እስካሁን 15 የላብራቶሪ ምርመራ ተካሂዶ 6 ሰዎች በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠ ሲሆን የ1 ሰው ህይወት አልፏል ተብሏል።
ከቀናት በፊት በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የMpox ኬዝ በሞያሌ ከተማ መገኘቱ ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
ኬንያ ተጨማሪ 200 ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ሀይል ለመግዛት ልዑኳን ወደ ኢትዮጵያ መላኳን አስታወቀች!
ኬንያ ተጨማሪ 200 ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ለመግዛት ልዑኳን ወደ አዲስ አበባ መላኳን አስታወቀች፤ የኬንያ የኢነርጂ እና ሃይል ሚኒስቴር የቴክኒክ ልዑካን በኤሌክትሪክ ግዢው ዙሪያ ለመደራደር ወደ ኢትዮጵያ ማቅናታቸው ተጠቁሟል።
ወደ ኢትዮጵያ ያቀናው የኬንያ ልዑክ በኤሌክትሪክ ሀይሉ የክፍያ ታሪፍ፣ አቅርቦቱ የሚከናወንበትን ግዜ፣ የማስተላለፊያዎቹ ደህንነት አጠባበቅ መንገዶች ዙሪያ የመጨረሻ ስምምነቱን እንደሚፈጽም ተገልጿል።ለኬንያ የሚቀርበው ተጨማሪ መጠባበቂያ ሀይል ከህዳሴ ግድብ ከሚመነጨው እንደሚሆን ከኬንያው ኬዲአርቲቪ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ከሶስት አመታት በፊት ኬንያ እና ኢትዮጵያ ለ25 አመታት የሚቆይ የሀይል ግዢ ስምምነት መፈጸማቸው የሚታወስ ሲሆን ኢትዮጵያ ለኬንያ ኤሌክትሪክ በማቅረብ በኪሎ ዋት ስድስት ነጥብ አምስት የአሜሪካን ሳንቲም እንደምታስከፍል ተቀምጧል፤ ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታስከፍላት የኬሎዋት ክፍያ ለማምረት ከምታወጣው ወጪ እጅግ ያነሰ ነው ተብሏል።
ኬንያ ከጂኦተርማል ኢነርጂ አንድ ኪሎ ዋት ለማመንጨት 20 የአሜሪካ ሳንቲም ወጪ እንደምታደርግ ተጠቁሟል። ኬንያ አጠቃላይ ከጎረቤቶቿ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን 400 ሜጋ ዋት ለማድረስ እየጣረች መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ይህም አመታዊ 10 ሚሊየን ዶላር እንድታድን ያደርጋታል ተብሏል።በአሁኑ ወቅት በኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል ፍጆታ ከፍተኛ በሚሆንበት ሰዓታት 283 ሜጋዋት እጥረት እንደሚያጋጥማት መረጃዎች አመላክተዋል።
ኬንያ ተጨማሪ 200 ሜጋዋት ኤሌክትሪክ ከኢትዮጵያ ለመግዛት ልዑኳን ወደ አዲስ አበባ መላኳን አስታወቀች፤ የኬንያ የኢነርጂ እና ሃይል ሚኒስቴር የቴክኒክ ልዑካን በኤሌክትሪክ ግዢው ዙሪያ ለመደራደር ወደ ኢትዮጵያ ማቅናታቸው ተጠቁሟል።
ወደ ኢትዮጵያ ያቀናው የኬንያ ልዑክ በኤሌክትሪክ ሀይሉ የክፍያ ታሪፍ፣ አቅርቦቱ የሚከናወንበትን ግዜ፣ የማስተላለፊያዎቹ ደህንነት አጠባበቅ መንገዶች ዙሪያ የመጨረሻ ስምምነቱን እንደሚፈጽም ተገልጿል።ለኬንያ የሚቀርበው ተጨማሪ መጠባበቂያ ሀይል ከህዳሴ ግድብ ከሚመነጨው እንደሚሆን ከኬንያው ኬዲአርቲቪ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።
ከሶስት አመታት በፊት ኬንያ እና ኢትዮጵያ ለ25 አመታት የሚቆይ የሀይል ግዢ ስምምነት መፈጸማቸው የሚታወስ ሲሆን ኢትዮጵያ ለኬንያ ኤሌክትሪክ በማቅረብ በኪሎ ዋት ስድስት ነጥብ አምስት የአሜሪካን ሳንቲም እንደምታስከፍል ተቀምጧል፤ ኢትዮጵያ ለኬንያ የምታስከፍላት የኬሎዋት ክፍያ ለማምረት ከምታወጣው ወጪ እጅግ ያነሰ ነው ተብሏል።
ኬንያ ከጂኦተርማል ኢነርጂ አንድ ኪሎ ዋት ለማመንጨት 20 የአሜሪካ ሳንቲም ወጪ እንደምታደርግ ተጠቁሟል። ኬንያ አጠቃላይ ከጎረቤቶቿ የምታስገባው የኤሌክትሪክ ሀይል መጠን 400 ሜጋ ዋት ለማድረስ እየጣረች መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ይህም አመታዊ 10 ሚሊየን ዶላር እንድታድን ያደርጋታል ተብሏል።በአሁኑ ወቅት በኬንያ የኤሌክትሪክ ሀይል ፍጆታ ከፍተኛ በሚሆንበት ሰዓታት 283 ሜጋዋት እጥረት እንደሚያጋጥማት መረጃዎች አመላክተዋል።
የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እስከ 1.5 ትርሊዮን የሚገመት ሀብት ያስፈልጋል ተባለ
በ #ኢትዮጵያ የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እስከ 1.5 ትርሊዮን የሚገመት ሀብት እንደሚያስፈልግ የገንዝብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ገለጹ።
የገንዝብ ሚኒስትር ደኤታው እዮብ ይህን ያሉት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 33ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
የምክር ቤት አባላቱ በሀገሪቱ ለተጀመሩት የመንገድ ፕሮጀክቶች ትልቅ ማነቆ የሆነውን በጀት መፍታት የሚያስችል የብድር ስምምነቶችን ገንዘብ ሚኒስቴር ሊያመጣ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ከአጋር የልማት ድርጅቶች ሀብት የማሰባሰብ ስራ በስፋት ሊሰራ እንደሚገባ በምክር ቤት አባላቱ አንስተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ከተለያዩ የብድር አቅራቢ ተቋማት በተገኘ ብድርና ከልማት አጋሮች በተገኘ ድጋፍ በርካታ መንገዶች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
ሆኖም በምክር ቤቱ በቂ አይደለም የተባለውን በመውሰድ የሀገር ውስጥ ገቢን ለማሳደግ እና ከልማት አጋሮች ሀብት ማሰባሰቡን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል።
አጠቃላይ እንደሀገር የተጀመሩትን የመንገድ ፕሮጀክቶች ለማጠናቀቅ ከአንድ ነጥብ ሶስት ትሪሊዮን እስከ አንድ ነጥብ አምስት ትሪሊዮን የሚገመት ሀብት እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል።
ችግሩን ለመፍታት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረጉን አንስተው፤ ዘርፉን ለማሳደግ የመንግስትና የግሉን ዘርፍ አጋርነት ያስፈልጋል ብለዋል።
በ #ኢትዮጵያ የተጀመሩ የመንገድ ፕሮጀክቶችን ለማጠናቀቅ እስከ 1.5 ትርሊዮን የሚገመት ሀብት እንደሚያስፈልግ የገንዝብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ገለጹ።
የገንዝብ ሚኒስትር ደኤታው እዮብ ይህን ያሉት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደው 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 33ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው።
የምክር ቤት አባላቱ በሀገሪቱ ለተጀመሩት የመንገድ ፕሮጀክቶች ትልቅ ማነቆ የሆነውን በጀት መፍታት የሚያስችል የብድር ስምምነቶችን ገንዘብ ሚኒስቴር ሊያመጣ እንደሚገባ ጠይቀዋል።
በተጨማሪም የመንገድ መሰረተ ልማቶችን ለማስፋፋት ከአጋር የልማት ድርጅቶች ሀብት የማሰባሰብ ስራ በስፋት ሊሰራ እንደሚገባ በምክር ቤት አባላቱ አንስተዋል።
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ ከምክር ቤት አባላት ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽና ማብራሪያ፤ ከተለያዩ የብድር አቅራቢ ተቋማት በተገኘ ብድርና ከልማት አጋሮች በተገኘ ድጋፍ በርካታ መንገዶች እየተሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
ሆኖም በምክር ቤቱ በቂ አይደለም የተባለውን በመውሰድ የሀገር ውስጥ ገቢን ለማሳደግ እና ከልማት አጋሮች ሀብት ማሰባሰቡን አጠናክረን እንቀጥላለን ሲሉ ተናግረዋል።
አጠቃላይ እንደሀገር የተጀመሩትን የመንገድ ፕሮጀክቶች ለማጠናቀቅ ከአንድ ነጥብ ሶስት ትሪሊዮን እስከ አንድ ነጥብ አምስት ትሪሊዮን የሚገመት ሀብት እንደሚያስፈልግ አስታውቀዋል።
ችግሩን ለመፍታት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት ማድረጉን አንስተው፤ ዘርፉን ለማሳደግ የመንግስትና የግሉን ዘርፍ አጋርነት ያስፈልጋል ብለዋል።
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
“አደባባይ የወጣሁት ሕዝቤ እንዲደርስልኝ ነው”:- አትሌት ገለቴ ቡርቃ
******
በኢቲቪ ኦፋን ኦሮሞ ቴሌቪዥን ከሚቀርበው "ገመዳ ሾው" ጋር ቆይታ ያደረገችው አትሌት ገለቴ ቡርቃ "አደባባይ የወጣሁት ሕዝቤ ያለሁበትን አስቸጋሪ ሁኔታ አውቆ እንዲደርስልኝ ነው" ብላለች፡፡
ከ800 እስከ ማራቶን ኢትዮጵያን ወክላ በተለያዩ መድረኮች የተወዳደረችው አትሌት ገለቴ ሳላውቅ ትዳሬ እየፈረሰ ነውም ብላለች፡፡
"በሩጫ ባገኘሁት ገንዘብ ወደ ኢንቨስትመንት ልገባ ስል ችግር አጋጥሞኛል" የምትለው አትሌቷ.፣ ባለቤቷ በ2009 ዓ.ም ከቤት ጠፍቶ ስምንት ወር ከቆየ በኋላ ፍርድ ቤት እንዳቀረባት እና እስካሁን ክርክር ላይ እንዳሉ ተናግራለች፡፡
ዘጠኝ ዓመታት አብራ የቆየችው ባለቤቷ በ2009 ዓ.ም ለውድድር ከሀገር ውጭ ስትሄድ ከሸኛት በኋላ ውድድሯን ጨርሳ ስትመለስ ባዶ ቤት እንዳገኘች ገልጻለች፡፡
ፍለጋውን ጀምራ ለፖሊስ ስታስታውቅ "ደውሎ ለምን ስሜን ታጠፊያለሽ? አርፈሽ የማትቀመጪ ከሆነ እገድልሻለሁ" እንዳላት የተናገረችው ገለቴ በ2010 ዓ.ም በእርሱ በኩል የክስ መጥሪያ እንደደረሳት ጠቅሳለች፡፡
ፍርድ ቤት ስትቀርብም ባለቤቷ ጋብቻቸው እንዲፈርስ እንደጠየቀ እሷ ደግሞ የተጋቡት በእምነት ተቋም እንደሆነ እና እምነት ደግሞ ጋብቻ እንዲፈርስ እንደማይፈቅድ ጠቅሳ አላፈርስም እንዳለች ነገር ግን በጫና ጋብቻው እንደፈረሰ ትናገራለች፡፡
"ከዚያ ቀደም የወሰደውን ውክልና ተጠቅሞ ያለውን ንብረቴን ሸጦ ስለነበረ ጋብቻው ከፈረሰ በኋላ ንብረቴን ለማሳገድ ብንቀሳቀስም ከአንድ ቤት በስተቀር ሁሉም ስማቸው ዞሮ ነበር ያገኘሁት" ብላለች አትሌት ገለቴ፡፡
አንዷ የቀረችው ቤትም በ2008 ዓ.ም ውክልናው የተነሳባት ቤት እንደሆነ የጠቀሰችው አትሌቷ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ አሥር ቤቶች፣ አራት መኪና እና ሌሎች በርካት ንብረቶችን ተሸጠውባት ባዶ እጇን መቅረቷን ተናግራለች፡፡
"እናቱ እንዲኖሩበት የሰጠሁትን መንግሥት የሰጠኝን ቤት እንኳን ለእናቱ ሸጧል" የምትለው ገለቴ፣ "ከጋብቻ በፊት ያፈራሁት ንብረቴም ሳይመለስ፣ ከጋብቻ በኋላ ያፈራነውንም ሳልካፈል አንዷን የቀረችውን ቤት ለመካፈል ፍርድ ቤት ወስኖብኛል" ስትል ተናግራለች፡፡
እሱ ቀድሞ ሁሉንም አቅዶበት ስለሄደበት ያላትን አቅም ሁሉ ተጠቅማ ፍርድ ቤት ብትከራከርም ውሳኔው ግን ከሷ በተቃራኒ እንደሆነ ተናግራለች፡፡
ከዚህ አልፎም እንደሚያስፋራራት ለፖሊስ ማልከቷን ጠቅሳ፣ ንብረቱም እንዳይገኝ አንድም ገንዘቡን በሱ ስም እንደማያስቀምጥ እንዲሁም ተሸጡ የተባሉ ንብረቶችም ከዋጋቸው እጅግ ባነሰ የተሸጡ መሆናቸው ጉዳዩን ውስብስብ እንዳደረገው ተናግራለች፡፡
ይህን ጉዳይ የማያውቀው የመንግሥት አካል እንደሌለ የጠቀሰችው አትሌት ገለቴ፣ "እስካሁን መፍትሄ ካለማግኘቴም በላይ ወደ ጎዳና ለመውጣት ከዚያም አልፎ ለሕይወቴ አስጊ ሁኔታ ላይ ስለምገኝ የሚመለከተው አካል ይድረስልኝ" ትላለች፡፡
"አደባባይ የወጣሁት ሕዝቤ እንዲደርስልኝ ነው" ያለችው ገለቴ፣ "ወጥቼ የምወደውን ስፖርት እንኳን እንዳልሠራ ማስፋራራት እየደረሰብኝ ቤት ውስጥ ተዘግቼ ተቀምጫለሁ፤ የአቅሜን ያበረከትኩላት ሀገሬ እና ሕዝብ ያለሁበትን ሁኔታ ይወቅልኝ" ብላለች፡፡
በለሚ ታደሰ ( EBC)
******
በኢቲቪ ኦፋን ኦሮሞ ቴሌቪዥን ከሚቀርበው "ገመዳ ሾው" ጋር ቆይታ ያደረገችው አትሌት ገለቴ ቡርቃ "አደባባይ የወጣሁት ሕዝቤ ያለሁበትን አስቸጋሪ ሁኔታ አውቆ እንዲደርስልኝ ነው" ብላለች፡፡
ከ800 እስከ ማራቶን ኢትዮጵያን ወክላ በተለያዩ መድረኮች የተወዳደረችው አትሌት ገለቴ ሳላውቅ ትዳሬ እየፈረሰ ነውም ብላለች፡፡
"በሩጫ ባገኘሁት ገንዘብ ወደ ኢንቨስትመንት ልገባ ስል ችግር አጋጥሞኛል" የምትለው አትሌቷ.፣ ባለቤቷ በ2009 ዓ.ም ከቤት ጠፍቶ ስምንት ወር ከቆየ በኋላ ፍርድ ቤት እንዳቀረባት እና እስካሁን ክርክር ላይ እንዳሉ ተናግራለች፡፡
ዘጠኝ ዓመታት አብራ የቆየችው ባለቤቷ በ2009 ዓ.ም ለውድድር ከሀገር ውጭ ስትሄድ ከሸኛት በኋላ ውድድሯን ጨርሳ ስትመለስ ባዶ ቤት እንዳገኘች ገልጻለች፡፡
ፍለጋውን ጀምራ ለፖሊስ ስታስታውቅ "ደውሎ ለምን ስሜን ታጠፊያለሽ? አርፈሽ የማትቀመጪ ከሆነ እገድልሻለሁ" እንዳላት የተናገረችው ገለቴ በ2010 ዓ.ም በእርሱ በኩል የክስ መጥሪያ እንደደረሳት ጠቅሳለች፡፡
ፍርድ ቤት ስትቀርብም ባለቤቷ ጋብቻቸው እንዲፈርስ እንደጠየቀ እሷ ደግሞ የተጋቡት በእምነት ተቋም እንደሆነ እና እምነት ደግሞ ጋብቻ እንዲፈርስ እንደማይፈቅድ ጠቅሳ አላፈርስም እንዳለች ነገር ግን በጫና ጋብቻው እንደፈረሰ ትናገራለች፡፡
"ከዚያ ቀደም የወሰደውን ውክልና ተጠቅሞ ያለውን ንብረቴን ሸጦ ስለነበረ ጋብቻው ከፈረሰ በኋላ ንብረቴን ለማሳገድ ብንቀሳቀስም ከአንድ ቤት በስተቀር ሁሉም ስማቸው ዞሮ ነበር ያገኘሁት" ብላለች አትሌት ገለቴ፡፡
አንዷ የቀረችው ቤትም በ2008 ዓ.ም ውክልናው የተነሳባት ቤት እንደሆነ የጠቀሰችው አትሌቷ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የሚገኙ አሥር ቤቶች፣ አራት መኪና እና ሌሎች በርካት ንብረቶችን ተሸጠውባት ባዶ እጇን መቅረቷን ተናግራለች፡፡
"እናቱ እንዲኖሩበት የሰጠሁትን መንግሥት የሰጠኝን ቤት እንኳን ለእናቱ ሸጧል" የምትለው ገለቴ፣ "ከጋብቻ በፊት ያፈራሁት ንብረቴም ሳይመለስ፣ ከጋብቻ በኋላ ያፈራነውንም ሳልካፈል አንዷን የቀረችውን ቤት ለመካፈል ፍርድ ቤት ወስኖብኛል" ስትል ተናግራለች፡፡
እሱ ቀድሞ ሁሉንም አቅዶበት ስለሄደበት ያላትን አቅም ሁሉ ተጠቅማ ፍርድ ቤት ብትከራከርም ውሳኔው ግን ከሷ በተቃራኒ እንደሆነ ተናግራለች፡፡
ከዚህ አልፎም እንደሚያስፋራራት ለፖሊስ ማልከቷን ጠቅሳ፣ ንብረቱም እንዳይገኝ አንድም ገንዘቡን በሱ ስም እንደማያስቀምጥ እንዲሁም ተሸጡ የተባሉ ንብረቶችም ከዋጋቸው እጅግ ባነሰ የተሸጡ መሆናቸው ጉዳዩን ውስብስብ እንዳደረገው ተናግራለች፡፡
ይህን ጉዳይ የማያውቀው የመንግሥት አካል እንደሌለ የጠቀሰችው አትሌት ገለቴ፣ "እስካሁን መፍትሄ ካለማግኘቴም በላይ ወደ ጎዳና ለመውጣት ከዚያም አልፎ ለሕይወቴ አስጊ ሁኔታ ላይ ስለምገኝ የሚመለከተው አካል ይድረስልኝ" ትላለች፡፡
"አደባባይ የወጣሁት ሕዝቤ እንዲደርስልኝ ነው" ያለችው ገለቴ፣ "ወጥቼ የምወደውን ስፖርት እንኳን እንዳልሠራ ማስፋራራት እየደረሰብኝ ቤት ውስጥ ተዘግቼ ተቀምጫለሁ፤ የአቅሜን ያበረከትኩላት ሀገሬ እና ሕዝብ ያለሁበትን ሁኔታ ይወቅልኝ" ብላለች፡፡
በለሚ ታደሰ ( EBC)
“አሜሪካ ብትሳተፍም ባትሳተፍም፣ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት በሙሉ የማጥፋት አቅም አላት”
- ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ እንደተናገሩት፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሳተፉም ባይሳተፉም፣ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት በሙሉ የማጥፋት አቅም አላት።
ኔታንያሁ ይህንን የተናገሩት ዋይት ሃውስ ትራምፕ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ጣልቃ መግባት አለመግባታቸውን ይወስናሉ ከማለቱ በፊት ነው።
የወታደራዊ ጉዳይ ተንታኞች፣ እስራኤል የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዋነኛ ክፍል የሆነውን ፎርዶው የነዳጅ ማበልጸጊያ ፋብሪካን ለማጥፋት የአሜሪካ እገዛ ሊያስፈልጋት ይችላል ብለው ያምናሉ።
"በሁሉም ኢላማዎቻችንን፣ ሁሉንም የኒውክሌር ተቋሞቻቸውን የማስወገድ አቅም አለን ያሉት ኔታንያሁ፤ ነገር ግን ፕሬዚዳንቱ ለመቀላቀል ይፈልጉ እንደሆነ ወይም እንደማይፈልጉ የሚወስኑት እርሳቸው ናቸው ብለዋል።"
ኔታንያሁ አክለውም እርሱ (ትራምፕ) ለአሜሪካ የሚበጀውን ያደርጋል፣ እኔም ለእስራኤል መንግስት የሚበጀውን አደርጋለሁ ሲሉ ተደምጠዋል።
- ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ
ጠቅላይ ሚኒስትር ኔታንያሁ እንደተናገሩት፣ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ቢሳተፉም ባይሳተፉም፣ እስራኤል የኢራንን የኒውክሌር ተቋማት በሙሉ የማጥፋት አቅም አላት።
ኔታንያሁ ይህንን የተናገሩት ዋይት ሃውስ ትራምፕ በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ ጣልቃ መግባት አለመግባታቸውን ይወስናሉ ከማለቱ በፊት ነው።
የወታደራዊ ጉዳይ ተንታኞች፣ እስራኤል የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር ዋነኛ ክፍል የሆነውን ፎርዶው የነዳጅ ማበልጸጊያ ፋብሪካን ለማጥፋት የአሜሪካ እገዛ ሊያስፈልጋት ይችላል ብለው ያምናሉ።
"በሁሉም ኢላማዎቻችንን፣ ሁሉንም የኒውክሌር ተቋሞቻቸውን የማስወገድ አቅም አለን ያሉት ኔታንያሁ፤ ነገር ግን ፕሬዚዳንቱ ለመቀላቀል ይፈልጉ እንደሆነ ወይም እንደማይፈልጉ የሚወስኑት እርሳቸው ናቸው ብለዋል።"
ኔታንያሁ አክለውም እርሱ (ትራምፕ) ለአሜሪካ የሚበጀውን ያደርጋል፣ እኔም ለእስራኤል መንግስት የሚበጀውን አደርጋለሁ ሲሉ ተደምጠዋል።
የኢትዮጵያ የባንክ ዘርፍ ከዛሬ ጀምሮ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት ሆነ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።
መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።
ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።
ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።
ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።
ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።
Via Capital Newspaper
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት የሚያደርግ አዲስ መመሪያን ዛሬ ይፋ አድርጓል። ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ዘርፍ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ለማድረግ ሲደረግ የቆየው ጥረት የመጨረሻው ምዕራፍ ተደርጎ እንደሚወሰዱ ተገልጿል።
መመሪያ ቁጥር SBB/94/2025 ባለፉት አንድ ዓመት በተለያዩ ባለድርሻ አካላት በተደረጉ ሰፊ ውይይቶች እና ምክክሮች ግብዓት ተደርጎበት የተዘጋጀ መሆኑ ታውቋል።
ይህ መመሪያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በፀደቀው የባንክ ሥራ አዋጅ መሰረት የወጣ ሲሆን፣ የሚያስፈልገውን የሕግ ማዕቀፍ ማሟላቱ ተገልጿል።
ይህ አዲሱ የፈቃድ አሰጣጥ መመሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ የውጭ ባለሀብቶች፣ ባንኮችን እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ባለሀብቶችን ጨምሮ፣ በኢትዮጵያ የባንክ ሥርዓት ውስጥ እንዲሳተፉ ያስችላል ተብሏል።
ብሔራዊ ባንክ ዛሬ ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም. ባወጣዉ መግለጫ መመሪያው የውጭ ተዋናዮች የባንክ ዘርፉን እንዲቀላቀሉባቸው በርካታ መንገዶችን ያቀርባል፤ ከእነዚህም መካከል ቅርንጫፍ ባንኮችን፣ የውጭ ባንክ ቅርንጫፎችን ወይም የወኪል ቢሮዎችን ማቋቋም ይገኙበታል።
ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ለውጭ ተሳትፎ ክፍት መሆኑን የገለፀ ሲሆን የውጭ ባንኮች እና ባለሀብቶችም ማመልከቻዎቻቸውን ከዛሬ ጀምሮ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ እንደሚችሉ አስታውቋል።
Via Capital Newspaper
በቀጣይ አመት ማስተማር የማይችሉ ት/ቤቶች
በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉ የትምህርት ተቋማትን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ይፋ አድርጓል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ትምህርት ቤቶችን አሳውቋል።
በ2016 ዓ.ም ማጠቃለያ ላይ በተደረገው የእድሳት ፍቃድ ምዘና ለ2017 የትምህርት ዘመን ካሳዩት ዝቅተኛ ውጤት መሻሻል እንዲያሳዩ እስከ 2017 ዓ.ም ታህሳስ ድረስ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፤ በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም በታህሳስ 2017 በተደረገ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው መሻሻል ባለማሳየቱና ዝቅተኛና ከደረጃ በታች በመሆኑ ምክንያት በ2018 የት/ት ዘመን ማስተማር የማይችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም የትምህርት ማህበረሰቡ እና ወላጆች ይህን በማወቅ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እንድታከናውኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር አሳውቋል።
በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉ የትምህርት ተቋማትን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን ይፋ አድርጓል።
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን በ2018 የትምህርት ዘመን ማስተማር የማይችሉና እውቅናቸው የተሰረዘ ትምህርት ቤቶችን አሳውቋል።
በ2016 ዓ.ም ማጠቃለያ ላይ በተደረገው የእድሳት ፍቃድ ምዘና ለ2017 የትምህርት ዘመን ካሳዩት ዝቅተኛ ውጤት መሻሻል እንዲያሳዩ እስከ 2017 ዓ.ም ታህሳስ ድረስ ዝግጅት እንዲያደርጉ ፤ በ2017 የትምህርት ዘመን ላይ በማስጠንቀቂያ እንዲያስተምሩ ጊዜ ቢሰጣቸውም በታህሳስ 2017 በተደረገ የእድሳት ፍቃድ ምዘና ውጤታቸው መሻሻል ባለማሳየቱና ዝቅተኛና ከደረጃ በታች በመሆኑ ምክንያት በ2018 የት/ት ዘመን ማስተማር የማይችሉ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አሳውቋል።
በመሆኑም የትምህርት ማህበረሰቡ እና ወላጆች ይህን በማወቅ የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እንድታከናውኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር አሳውቋል።
በታጣቂዎች ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች መገደላቸው ተነገረ
"ተሳፋሪዎችና አሽከርካሪዎች ታፍነው ተወስደዋል"
በአማራ ክልል በጎንደር መተማ መንገድ ላይ "መቃ" በተባለች ሥፍራ ታጣቂዎች ሰኞ'ለት በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ተገድለው፣ በርካቶች መቁሰላቸውን ዋዜማ ምንጮችን ጠቅሳ ዘግባለች፡፡
በታጣቂዎቹ ከተገደሉት ሾፌሮች በተጨማሪ ተሳፋሪዎችና በርካታ አሽከርካሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
አብዛኞቹ አሽከርካሪዎች የተገደሉት፣ ከጥቃቱ ለማምለጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሳሉ በእሩምታ ተኩስ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ዋዜማ የጥቃቱን ፈጻሚ ታጣቂዎች ማንነት ለጊዜው ባታረጋግጥም፣ የፋኖ ታጣቂዎች ሰሞኑን በመተማ ወረዳ ከቅማንት ብሄረሰብ ታጣቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ግን ምንጮች መናገራቸውን ጠቁማለች፡፡
"ተሳፋሪዎችና አሽከርካሪዎች ታፍነው ተወስደዋል"
በአማራ ክልል በጎንደር መተማ መንገድ ላይ "መቃ" በተባለች ሥፍራ ታጣቂዎች ሰኞ'ለት በፈጸሙት ጥቃት 16 አሽከርካሪዎች ተገድለው፣ በርካቶች መቁሰላቸውን ዋዜማ ምንጮችን ጠቅሳ ዘግባለች፡፡
በታጣቂዎቹ ከተገደሉት ሾፌሮች በተጨማሪ ተሳፋሪዎችና በርካታ አሽከርካሪዎች ታፍነው መወሰዳቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
አብዛኞቹ አሽከርካሪዎች የተገደሉት፣ ከጥቃቱ ለማምለጥ ጥረት በማድረግ ላይ ሳሉ በእሩምታ ተኩስ እንደኾነ ዘገባው አመልክቷል፡፡
ዋዜማ የጥቃቱን ፈጻሚ ታጣቂዎች ማንነት ለጊዜው ባታረጋግጥም፣ የፋኖ ታጣቂዎች ሰሞኑን በመተማ ወረዳ ከቅማንት ብሄረሰብ ታጣቂዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ማድረጋቸውን ግን ምንጮች መናገራቸውን ጠቁማለች፡፡
አሜሪካ በኢራን ላይ የፈጸመችው ጥቃት የኒውክሌር ማብላያ ይዞታዎችን እንዳላወደመ የአሜሪካ መከላከያ ማዕከል (ፔንታጎን) የደህንነት ግምገማ አሳየ።
ቅድመ ግምገማው፤ ጥቃቱ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ምናልባትም በወራት ወደ ኋላ ሊመልሰው እንደሚችል ነው ያሳየው።
ኢራን ያበለጸገችው የዩራኒየም ክምችት አሜሪካ ቅዳሜ፣ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በፈጸመችው ጥቃት አለመውደሙን የአገሪቱ የመከላከያ ደህንነት ኤጀንሲ ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች ለቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ ተናግረዋል።
ዋይት ሃውስ በበኩሉ፤ "ይህ ፍጹም የተሳሳተ ግምገማ" በማይረባ የደህንንት ማህበረሰብ ሾልኮ የወጣ ነው" ሲል ውድቅ አድርጎታል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው፤ የኢራን የኒውክሌር ይዞታዎች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል በማለት በድጋሚ አጽንኦት ሰጥተው፤ "በታሪክ ውስጥ ስኬታማ ከሆኑ ወታደራዊ ጥቃቶች መካከል አንዱ የሆነውን ለማዋረድ", በሚዲያዎች የሚደረግ ሙከራ ሲሉ ከሰዋል።
ነገር ግን የፔንታጎን የደህንነት ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች በበኩላቸው፤ የኢራን ማብላያዎች በአብዛኛው እንዳልተነኩና የጥቃቱ ተጽእኖ ከመሬት በላይ ባለው ብቻ የተወሰነ ነው ይላሉ።
የሁለቱ ኒውክሌር ይዞታዎች መግቢያዎች ተዘግተው እንደነበር የጠቀሰው ግምገማው፣ አንዳንድ መሰረተ ልማቶች ቢወድሙም ወይም ቢጎዱም፤ ከመሬት ስር ያሉት አብዛኛዎቹ ይዞታዎች ግን ከፍንዳታው ቃጠሎ አምልጠዋል ብሏል።
እኚህ ማንነታቸው ያልተገለጹ ምንጮች ለአሜሪካ ሚዲያ እንደተናገሩት፤ ጥቃቱ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በወራት ወደ ኋላ ሊመልሰው እንደሚችል መገመቱን ገልጸዋል።
የኢራን የመንግሥታዊ ሚዲያ ምክትል የፖለቲካ ዳይሬክተር ሃሰን አብደኒ በበኩላቸው፤ አሜሪካ ጥቃት ያደረሰችባቸው ሶስቱ የኒውክሌር ይዞታዎች፣ ከጥቃቱ ቀድሞ ክምችታቸው እንዲዛወር መደረጉን ተናግረዋል።
(ቢቢሲ)
ቅድመ ግምገማው፤ ጥቃቱ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር ምናልባትም በወራት ወደ ኋላ ሊመልሰው እንደሚችል ነው ያሳየው።
ኢራን ያበለጸገችው የዩራኒየም ክምችት አሜሪካ ቅዳሜ፣ ሰኔ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በፈጸመችው ጥቃት አለመውደሙን የአገሪቱ የመከላከያ ደህንነት ኤጀንሲ ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች ለቢቢሲ የአሜሪካ አጋር ሲቢኤስ ተናግረዋል።
ዋይት ሃውስ በበኩሉ፤ "ይህ ፍጹም የተሳሳተ ግምገማ" በማይረባ የደህንንት ማህበረሰብ ሾልኮ የወጣ ነው" ሲል ውድቅ አድርጎታል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በበኩላቸው፤ የኢራን የኒውክሌር ይዞታዎች ሙሉ በሙሉ ወድመዋል በማለት በድጋሚ አጽንኦት ሰጥተው፤ "በታሪክ ውስጥ ስኬታማ ከሆኑ ወታደራዊ ጥቃቶች መካከል አንዱ የሆነውን ለማዋረድ", በሚዲያዎች የሚደረግ ሙከራ ሲሉ ከሰዋል።
ነገር ግን የፔንታጎን የደህንነት ግምገማን የሚያውቁ ምንጮች በበኩላቸው፤ የኢራን ማብላያዎች በአብዛኛው እንዳልተነኩና የጥቃቱ ተጽእኖ ከመሬት በላይ ባለው ብቻ የተወሰነ ነው ይላሉ።
የሁለቱ ኒውክሌር ይዞታዎች መግቢያዎች ተዘግተው እንደነበር የጠቀሰው ግምገማው፣ አንዳንድ መሰረተ ልማቶች ቢወድሙም ወይም ቢጎዱም፤ ከመሬት ስር ያሉት አብዛኛዎቹ ይዞታዎች ግን ከፍንዳታው ቃጠሎ አምልጠዋል ብሏል።
እኚህ ማንነታቸው ያልተገለጹ ምንጮች ለአሜሪካ ሚዲያ እንደተናገሩት፤ ጥቃቱ የኢራንን የኒውክሌር መርሃ ግብር በወራት ወደ ኋላ ሊመልሰው እንደሚችል መገመቱን ገልጸዋል።
የኢራን የመንግሥታዊ ሚዲያ ምክትል የፖለቲካ ዳይሬክተር ሃሰን አብደኒ በበኩላቸው፤ አሜሪካ ጥቃት ያደረሰችባቸው ሶስቱ የኒውክሌር ይዞታዎች፣ ከጥቃቱ ቀድሞ ክምችታቸው እንዲዛወር መደረጉን ተናግረዋል።
(ቢቢሲ)