አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር ብሄራዊ ባንክ ገለፀ‼️
አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ እስመለአለም ምህረቱ ገለፁ።
እንደ ገዥው ገለፃ የውህደቱ ዋነኛ አላማ ችግር ያለባቸውን ባንኮች ለማዳን ነው ብለዋል።
በቅርቡ የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅ የባንኮችን ውህደት በተመለከተ የገለፀ ሲሆን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ እየተጠበቀ ነው።
ብሄርን መሰረት አድርገው ስለተመሰረቱ ባንኮች በውህደት ወቅት ስለ ሚያጋጥም ተግዳሮት የተጠየቁት አቶ ማሞ ውህደትን ጨምሮ አጠቃላይ የባንክ ስራ በህግ እንደሚመራ አስታውሰው፣ "ከዚህ አኳያ ከብሄር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ በተለይ በአስገዳጅነት የሚፈፀም ውህደት ላይ የሚኖረው ተፅእኖ አናሳ ነው፣" ብለዋል።
Via:- #ቅዳሜገበያ
አስገዳጅ የባንኮች ውህደት እንደሚኖር የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ እስመለአለም ምህረቱ ገለፁ።
እንደ ገዥው ገለፃ የውህደቱ ዋነኛ አላማ ችግር ያለባቸውን ባንኮች ለማዳን ነው ብለዋል።
በቅርቡ የፀደቀው የባንክ ስራ አዋጅ የባንኮችን ውህደት በተመለከተ የገለፀ ሲሆን ዝርዝር የአፈፃፀም መመሪያ እየተጠበቀ ነው።
ብሄርን መሰረት አድርገው ስለተመሰረቱ ባንኮች በውህደት ወቅት ስለ ሚያጋጥም ተግዳሮት የተጠየቁት አቶ ማሞ ውህደትን ጨምሮ አጠቃላይ የባንክ ስራ በህግ እንደሚመራ አስታውሰው፣ "ከዚህ አኳያ ከብሄር ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ በተለይ በአስገዳጅነት የሚፈፀም ውህደት ላይ የሚኖረው ተፅእኖ አናሳ ነው፣" ብለዋል።
Via:- #ቅዳሜገበያ
የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ መቃረቡን ተከትሎ አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑ ታወቀ
- መርዙ ወንዝ ዳር የሚበቅል ምግብ ሊበክል እንደሚችል ተሰግቷል
በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።
በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ፒያሳ እና ካዛንችስ ያሉ ቦታዎች መፍረሳቸውን ተከትሎ መንገድ ላይ የቀሩ በርካታ ውሻዎች መኖራቸው ይታወቃል።
ይሁንና ቀጣዩን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች "ጎዳና ላይ እንዳያዩዋቸው" በሚል ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሺህ ውሻዎች በመርዝ እየተገደሉ እንደሆነ ታውቋል።
ባለፈው ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊመጡ ሲልም ሲባልም በተመሳሳይ ብዙ ውሻዎችን በመርዝ መገደላቸው ታውቋል።
"መርዙ በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል የታገደ ነው፣ እንዴትስ ወደ ሀገራችን ገባ የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ ነው" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ ግለሰብ መርዙ ሰዎች እጅ ቢገባ በአንድ የሻይ ማንኪያ እሩብ በታች ሆነ መጠን ሺህ ህዝብ ሊጨርስ ይችላል ብለዋል።
"መርዙ ሽታ የሌለው በመሆኑ በምግብም ሆነ መጠጥ ውስጥ ሊገባና ሰዎችን ለመጉዳት ሊውል ይችላል። በዚህ መርዝ ያለ ሃጢያታቸው እየተገደሉ ያሉ ውሾች የሚጣሉበት ቦታ ሌላው አውሬ ምግብ ያገኘ መስሎት የሞተውን በድን ሲበላ እንደሚሞት፣ ተያይዞም አሞራዎች በልተውት የተረፋቸውን ወንዝ ላይ ቢጥሉት ውሃው የሚመረዝ መሆኑ ሊታወቅ ይሀገባል" በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።
አክለውም ውሃው የከተማም ሆነ የገጠር የወንዝ ዳር አትክልት ልማት ላይ ሊውል ስለሚችል ተያያዥነቱ ረጅም በመሆኑ ህዝብ ሁሉ ይህንን ድርጊት እንዲኮንን ተማፅነዋል።
መሠረት ሚዲያ
- መርዙ ወንዝ ዳር የሚበቅል ምግብ ሊበክል እንደሚችል ተሰግቷል
በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል በታገደ መርዝ በርካታ ሺህ ውሻዎች አዲስ አበባ ውስጥ እየተገደሉ መሆኑን ከተለያዩ ቦታዎች የሚደርሱን ጥቆማዎች ያሳያሉ።
በኮሪደር ልማት ምክንያት እንደ ፒያሳ እና ካዛንችስ ያሉ ቦታዎች መፍረሳቸውን ተከትሎ መንገድ ላይ የቀሩ በርካታ ውሻዎች መኖራቸው ይታወቃል።
ይሁንና ቀጣዩን የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ለመሳተፍ የሚመጡ እንግዶች "ጎዳና ላይ እንዳያዩዋቸው" በሚል ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በርካታ ሺህ ውሻዎች በመርዝ እየተገደሉ እንደሆነ ታውቋል።
ባለፈው ወር የፈረንሳዩ ፕሬዝደንት ኢማኑኤል ማክሮን ሊመጡ ሲልም ሲባልም በተመሳሳይ ብዙ ውሻዎችን በመርዝ መገደላቸው ታውቋል።
"መርዙ በአለም ጤና ድርጅት አገልግሎት ላይ እንዳይውል የታገደ ነው፣ እንዴትስ ወደ ሀገራችን ገባ የሚለው ጉዳይ አጠያያቂ ነው" ያሉት አንድ ጉዳዩን የሚከታተሉ ግለሰብ መርዙ ሰዎች እጅ ቢገባ በአንድ የሻይ ማንኪያ እሩብ በታች ሆነ መጠን ሺህ ህዝብ ሊጨርስ ይችላል ብለዋል።
"መርዙ ሽታ የሌለው በመሆኑ በምግብም ሆነ መጠጥ ውስጥ ሊገባና ሰዎችን ለመጉዳት ሊውል ይችላል። በዚህ መርዝ ያለ ሃጢያታቸው እየተገደሉ ያሉ ውሾች የሚጣሉበት ቦታ ሌላው አውሬ ምግብ ያገኘ መስሎት የሞተውን በድን ሲበላ እንደሚሞት፣ ተያይዞም አሞራዎች በልተውት የተረፋቸውን ወንዝ ላይ ቢጥሉት ውሃው የሚመረዝ መሆኑ ሊታወቅ ይሀገባል" በማለት ስጋታቸውን ገልፀዋል።
አክለውም ውሃው የከተማም ሆነ የገጠር የወንዝ ዳር አትክልት ልማት ላይ ሊውል ስለሚችል ተያያዥነቱ ረጅም በመሆኑ ህዝብ ሁሉ ይህንን ድርጊት እንዲኮንን ተማፅነዋል።
መሠረት ሚዲያ
👍3
አሜሪካ ውስጥ በመወለድ ዜግነት ከሚያሰጠው ሕግ ጋራ በተያያዘ ትረምፕ የፈረሙት ፕሬዝደንታዊ ትዕዛዝ በሦስተኛ ዳኛ ታገደ
አሜሪካ ውስጥ በመወለድ ዜግነት የሚያሰጠው ሕግ፣ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በገቡ ሰዎች ለተወለዱ ልጆች ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚያደርገውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የፈረሙትን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ በማገድ የኒው ሃምፕሸር ክፍለ ግዛቱ የፌዴራል ዳኛ ጆሴፍ ኤን ላፕላንት በትላንትናው ዕለት በሰጡት ብይን ሦስተኛው ዳኛ ሆኑ።
በዩናይትድ ስቴትስ የሲቪል መብት ማሕበራት ባቀረቧቸው ክሶች፤ ትረምፕ የፈረሙትን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ሕገ መንግስቱን የሚጥስ እና "ከዋነኞቹ የአሜሪካ ሕገ-መንግሥታዊ እሴቶች ውስጥ አንዱን ለመለወጥ የተደረገ ሙከራ ነው” ሲሉ ተከራክረዋል።
አሜሪካ ውስጥ በመወለድ ዜግነት የሚያሰጠው ሕግ፣ ያለ ሕጋዊ ፈቃድ ወደ ዩናይትድ ስቴትስ በገቡ ሰዎች ለተወለዱ ልጆች ተፈጻሚ እንዳይሆን የሚያደርገውን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትረምፕ የፈረሙትን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ በማገድ የኒው ሃምፕሸር ክፍለ ግዛቱ የፌዴራል ዳኛ ጆሴፍ ኤን ላፕላንት በትላንትናው ዕለት በሰጡት ብይን ሦስተኛው ዳኛ ሆኑ።
በዩናይትድ ስቴትስ የሲቪል መብት ማሕበራት ባቀረቧቸው ክሶች፤ ትረምፕ የፈረሙትን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ሕገ መንግስቱን የሚጥስ እና "ከዋነኞቹ የአሜሪካ ሕገ-መንግሥታዊ እሴቶች ውስጥ አንዱን ለመለወጥ የተደረገ ሙከራ ነው” ሲሉ ተከራክረዋል።
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
በአየር መንገድ ግቢ ውስጥ ከአመራሮች እውቅና ውጪ ተነሳ የተባለው ፎቶ በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ወጣ
ከቀናት በፊት ሲያነጋግር የነበረው የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የተነሳው ፎቶ እንደተባለው "ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጪ" ሳይሆን በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል።
የአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግሩም አበበ ለሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም በፃፉት ደብዳቤ አርቲስት ምህረት ታደሰ በአየር መንገድ የአየር ክልል ውስጥ የፎቶ ፕሮግራም እንድታደርግ መጠየቋን ያሳያል።
ደብዳቤው አክሎም የፎቶ ፕሮግራሙ ለአየር መንገዱ ማስታወቂያነት ስለሚጠቅም ታህሳስ 27/2017 ዓ/ም ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተው ፎቶ እንዲነሱ ይጠይቃል።
የፎቶ ፕሮግራሙ በዚህ ሁኔታ በተቋሙ እውቅና ቢካሄድም ተቋሙ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ገፁ "የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" ማለቱ ግርታን ፈጥሯል።
በተጨማሪም የፎቶ ፕሮርግራሙ የግል የልደት ፕሮግራም መሆኑን አርቲስቷ በሶሻል ሚድያ ገጿ ላይ የገለፀች ቢሆንም ይህ በምን መልኩ ለአየር መንገዱ በማስታወቂያነት እንደሚጠቅም ግልፅ አልሆነም።
ተቋሙ ለፎቶ ፕሮግራሙ ከአርቲስቷ ገንዘብ አለመቀበሉን እና ምንም አይነት ውል እንደሌለው በመግለጫው ላይ ገልፆ ነበር።
በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ከአየር የበረራ ክልል ደህንነት ጋር በማንሳት ጥያቄ ሲያቀርቡ ሌሎች ደግሞ በምን መስፈርት አንድ ግለሰብ የግል ልደት ከፍ ያለ ደህንነት በሚያስፈልገው አውሮፕላን ላይ ዲኮር በመስራት ተከበረ የሚል ጥያቄ አንስተዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክስተቱ ለአየር መንገዱ ጥሩ ማስታወቂያነት ውሏል ብለው ሀሳብ የሰጡም አልጠፉም።
መሰረት ሚዲያ
ከቀናት በፊት ሲያነጋግር የነበረው የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የተነሳው ፎቶ እንደተባለው "ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጪ" ሳይሆን በእውቅና መደረጉን የሚያሳይ ደብዳቤ ለመሠረት ሚድያ ደርሷል።
የአየር መንገዱ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ዳይሬክተር አቶ ግሩም አበበ ለሲቪል አቪዬሽን ደህንነት ዋና መምሪያ ዳይሬክተር ታህሳስ 25/2017 ዓ/ም በፃፉት ደብዳቤ አርቲስት ምህረት ታደሰ በአየር መንገድ የአየር ክልል ውስጥ የፎቶ ፕሮግራም እንድታደርግ መጠየቋን ያሳያል።
ደብዳቤው አክሎም የፎቶ ፕሮግራሙ ለአየር መንገዱ ማስታወቂያነት ስለሚጠቅም ታህሳስ 27/2017 ዓ/ም ቅጥር ግቢ ውስጥ ገብተው ፎቶ እንዲነሱ ይጠይቃል።
የፎቶ ፕሮግራሙ በዚህ ሁኔታ በተቋሙ እውቅና ቢካሄድም ተቋሙ ከትናንት በስቲያ በፌስቡክ ገፁ "የግለሰቧ የአየር መንገድ ግቢ ውስጥ የልደት ምስል ቀረጻ ከተቋሙ አመራሮች እውቅና ውጭ የተደረገ ነው" ማለቱ ግርታን ፈጥሯል።
በተጨማሪም የፎቶ ፕሮርግራሙ የግል የልደት ፕሮግራም መሆኑን አርቲስቷ በሶሻል ሚድያ ገጿ ላይ የገለፀች ቢሆንም ይህ በምን መልኩ ለአየር መንገዱ በማስታወቂያነት እንደሚጠቅም ግልፅ አልሆነም።
ተቋሙ ለፎቶ ፕሮግራሙ ከአርቲስቷ ገንዘብ አለመቀበሉን እና ምንም አይነት ውል እንደሌለው በመግለጫው ላይ ገልፆ ነበር።
በርካታ የማህበራዊ ሚድያ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ከአየር የበረራ ክልል ደህንነት ጋር በማንሳት ጥያቄ ሲያቀርቡ ሌሎች ደግሞ በምን መስፈርት አንድ ግለሰብ የግል ልደት ከፍ ያለ ደህንነት በሚያስፈልገው አውሮፕላን ላይ ዲኮር በመስራት ተከበረ የሚል ጥያቄ አንስተዋል፣ በሌላ በኩል ደግሞ ክስተቱ ለአየር መንገዱ ጥሩ ማስታወቂያነት ውሏል ብለው ሀሳብ የሰጡም አልጠፉም።
መሰረት ሚዲያ
የአየር መንገዱን አሠራር ጥሰዋል በተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሮ ሠራተኞች ላይ ዕርምጃ መወሰዱ ተገለጸ
- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ ቀረፃዎች እንዲካሄዱ ፈቃድ ሰጥተዋል የተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች መወሰዱ ተገለጸ።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በአየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ነው።
ኢትዮጵያ እያስተናገደችው ስለምትገኘው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔን ጨምሮ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን፣ በቅርቡ ለተዋናይትና ሞዴል ምሕረት ታደሰ (ፒፒሎ) የልደት በዓል አየር መንገዱ ፈቃድ ሰጥቶ ተቀርጿል በሚል ስለተሠራጩት የግለሰቧ ቪድዮዎችና ምሥሎች፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ስለጉዳዩ መረጃ አልነበራቸውም በሚል ስለተሰጠው ምላሽ ጉዳዩን በዝርዝር እንዲያብራሩ ከጋዜጠኞች ጥያቄዎች ቀርቦላቸዋል።
አቶ መስፍን፣ ‹‹ቪድዮው መቀረፁ ትክክል ነው። ለግለሰቧ ሕጋዊ ፈቃድ ተሰጥቶ የፀጥታ መምርያ ሒደቱን ተከትሎ ጥገና ወደሚደረግበት የአየር መንገዱ ቅጥር ግቢ ገብታ የተከናወነ ነው፤›› ብለው፣ ‹‹የፀጥታ ፕሮሲጀሩን አሟልታ ነው ቪድዮው የተቀረፀው። ለአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሯችን ታኅሳስ 27 ጥያቄ ያቀረበችበት ቀን ሲሆን፣ ከሁለት ቀን በኋላ ፈቃድ ተሰጥቶ ቀረፃው ተካሂዷል፤›› ሲሉ ገልጸዋል።
- የሕግ ክፍሉ ክስ መመሥረት የሚቻልባቸውን ሁኔታዎች እየተመለከተ ነው ተብሏል
ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት የሥራ ክፍሎች ዕውቅና ውጪ፣ በቅጥር ግቢው ውስጥ የፎቶና የቪዲዮ ቀረፃዎች እንዲካሄዱ ፈቃድ ሰጥተዋል የተባሉ የአዲስ አበባ ሽያጭ ክፍል ሠራተኞች ላይ አስተዳደራዊ ዕርምጃዎች መወሰዱ ተገለጸ።
ይህ የተገለጸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ የንግድ ዘርፍ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ለማ ያደቻ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በአየር መንገዱ ዋና መሥሪያ ቤት ጋዜጣዊ መግለጫ ሲሰጡ ነው።
ኢትዮጵያ እያስተናገደችው ስለምትገኘው የአፍሪካ ኅብረት ጉባዔን ጨምሮ በተለያዩ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ የሰጡት ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን፣ በቅርቡ ለተዋናይትና ሞዴል ምሕረት ታደሰ (ፒፒሎ) የልደት በዓል አየር መንገዱ ፈቃድ ሰጥቶ ተቀርጿል በሚል ስለተሠራጩት የግለሰቧ ቪድዮዎችና ምሥሎች፣ እንዲሁም የአየር መንገዱ ከፍተኛ አመራሮች ስለጉዳዩ መረጃ አልነበራቸውም በሚል ስለተሰጠው ምላሽ ጉዳዩን በዝርዝር እንዲያብራሩ ከጋዜጠኞች ጥያቄዎች ቀርቦላቸዋል።
አቶ መስፍን፣ ‹‹ቪድዮው መቀረፁ ትክክል ነው። ለግለሰቧ ሕጋዊ ፈቃድ ተሰጥቶ የፀጥታ መምርያ ሒደቱን ተከትሎ ጥገና ወደሚደረግበት የአየር መንገዱ ቅጥር ግቢ ገብታ የተከናወነ ነው፤›› ብለው፣ ‹‹የፀጥታ ፕሮሲጀሩን አሟልታ ነው ቪድዮው የተቀረፀው። ለአዲስ አበባ ሽያጭ ቢሯችን ታኅሳስ 27 ጥያቄ ያቀረበችበት ቀን ሲሆን፣ ከሁለት ቀን በኋላ ፈቃድ ተሰጥቶ ቀረፃው ተካሂዷል፤›› ሲሉ ገልጸዋል።
#NewsAlert
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሱሉልታ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ የሆኑት አበበ ወርቁ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው አማጺ ቡድን በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት መገደላቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች።
ታጣቂ ቡድኑ ጥቃቱን የፈጸመው ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ መሆኑን የገለጹት የዋዜማ ምንጮች፣ ከወረዳ አሥተዳዳሪው ጋር የነበረ የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በቡድኑ ታፍኖ መወሰዱን አስረድተዋል።
ዋና አሥተዳዳሪው፣ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው እና በርካታ የጸጥታ ኃይሎች ታጣቂ ቡድኑ በስፋት ይንቀሳቀስበታል ወደተባለው "ሞዬ ጋጆ" በተባለው ስፍራ ሲደርሱ አማጺ ቡድኑ ድንገተኛ የእሩምታ ተኩስ እንደከፈተባቸው ተጠቁሟል።
በዚህም ዋዜማ ለጊዜው ቁጥራቸውን ማጣራት ያልቻለችው የጸጥታ ኃይሎች ሲገደሉ፣ በርካቶች ደግሞ ቆስለው ጫንጮ ሆስፒታል መግባታቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
ከጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው በተጨማሪ በርካታ የጸጥታ ኃይሎች በቡድኑ ታፍነው መወሰዳቸውንም ዋዜማ ባደረገችው ማጣራት መረዳት ችላለች።
ከወራት በፊትም በተመሳሳይ በዚሁ ታጣቂ ቡድን ጥቃት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ለገሰ ሥዩም መገደላቸውን ዋዜማ መዘገቧ ይታወሳል።
ሟቹ አበበ ከሁለት ዓመት በፊት የወረዳው ዋና አሥተዳዳሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት፣ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እንደነበሩ ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመለክታል።
ዋዜማ
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን የሱሉልታ ወረዳ ዋና አሥተዳዳሪ የሆኑት አበበ ወርቁ ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ብሎ በሚጠራው አማጺ ቡድን በደረሰባቸው ድንገተኛ ጥቃት መገደላቸውን ዋዜማ ከምንጮቿ ሰምታለች።
ታጣቂ ቡድኑ ጥቃቱን የፈጸመው ዛሬ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 9 ሰዓት አካባቢ መሆኑን የገለጹት የዋዜማ ምንጮች፣ ከወረዳ አሥተዳዳሪው ጋር የነበረ የወረዳው የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊ በቡድኑ ታፍኖ መወሰዱን አስረድተዋል።
ዋና አሥተዳዳሪው፣ የጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው እና በርካታ የጸጥታ ኃይሎች ታጣቂ ቡድኑ በስፋት ይንቀሳቀስበታል ወደተባለው "ሞዬ ጋጆ" በተባለው ስፍራ ሲደርሱ አማጺ ቡድኑ ድንገተኛ የእሩምታ ተኩስ እንደከፈተባቸው ተጠቁሟል።
በዚህም ዋዜማ ለጊዜው ቁጥራቸውን ማጣራት ያልቻለችው የጸጥታ ኃይሎች ሲገደሉ፣ በርካቶች ደግሞ ቆስለው ጫንጮ ሆስፒታል መግባታቸውን ምንጮች ተናግረዋል።
ከጸጥታ ዘርፍ ኃላፊው በተጨማሪ በርካታ የጸጥታ ኃይሎች በቡድኑ ታፍነው መወሰዳቸውንም ዋዜማ ባደረገችው ማጣራት መረዳት ችላለች።
ከወራት በፊትም በተመሳሳይ በዚሁ ታጣቂ ቡድን ጥቃት የወረዳው ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ለገሰ ሥዩም መገደላቸውን ዋዜማ መዘገቧ ይታወሳል።
ሟቹ አበበ ከሁለት ዓመት በፊት የወረዳው ዋና አሥተዳዳሪ ሆነው ከመሾማቸው በፊት፣ የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እንደነበሩ ዋዜማ የደረሳት መረጃ ያመለክታል።
ዋዜማ
👍2
የፋይዳ አገልግሎቶችን የያዘ የሞባይል መተግበሪያ ይፋ ሆነ
የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ የፋይዳ አገልግሎቶችን የያዘ የሞባይል መተግበሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ አደረገ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የስራቴጂክ ኮሙኒኬሽን አማካሪ አቶ አቤነዘር ፈለቀ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት፤ የፋይዳ ሞባይል መተግበሪያ በተቁሙ የውስጥ ሀይል ተገንብቶ በአንድሮይድና በኣይኦኤስ (OS) ኦፐሬቲንግ ሲስተሞች ይፋ ተደርጓል።
ይህም ነዋሪዎች የሚያገኟቸውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶች ቀላል ፈጣንና ለአጠቃቀም ምቹ በሆነ መንገድ የሚያገኙበትን መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑም ነዋሪዎች ይህን የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም በተለያየ ምክንያት የጠፋባቸውን ወይም ያልደረሳቸውን የፋይዳ ቁጥር ወዲያው መልሰው ማስላክ ይችላሉ።
እንዲሁም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያቸውን በዲጂታል መልኩ ለማግኘት እንዲሁም አውርዶ ለመያዝና መታወቂያውን በካርድ መልክ አሳትሞ ለመያዝ የካርድ ህትመት ለማዘዝ የሚያስችል መሆኑን አንተስዋል።
በቀጣይም እየተሻሻለ እና የዘመነ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ነዋሪዎች ደህንነቱ የተጠበቀ ፣ ቀልጣፋ እና ዘመናዊ አገልግሎትን እንዲያገኙበት መሆኑንም ጠቅሰዋል።
መተግበሪያውን ከአፕ ስቶር እንዲሁም ከፕሌይ ስቶር ላይ በማውረድ መጠቀም ይቻላል።
የበለጠ መረጃ ድረገጻችን id.gov.et ላይ በመግባት ማግኘት ይችላሉ ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ የፋይዳ አገልግሎቶችን የያዘ የሞባይል መተግበሪያ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ አደረገ።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ መታወቂያ ፕሮግራም የስራቴጂክ ኮሙኒኬሽን አማካሪ አቶ አቤነዘር ፈለቀ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለፁት፤ የፋይዳ ሞባይል መተግበሪያ በተቁሙ የውስጥ ሀይል ተገንብቶ በአንድሮይድና በኣይኦኤስ (OS) ኦፐሬቲንግ ሲስተሞች ይፋ ተደርጓል።
ይህም ነዋሪዎች የሚያገኟቸውን የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ አገልግሎቶች ቀላል ፈጣንና ለአጠቃቀም ምቹ በሆነ መንገድ የሚያገኙበትን መሆኑን ገልፀዋል።
በመሆኑም ነዋሪዎች ይህን የሞባይል መተግበሪያ በመጠቀም በተለያየ ምክንያት የጠፋባቸውን ወይም ያልደረሳቸውን የፋይዳ ቁጥር ወዲያው መልሰው ማስላክ ይችላሉ።
እንዲሁም የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያቸውን በዲጂታል መልኩ ለማግኘት እንዲሁም አውርዶ ለመያዝና መታወቂያውን በካርድ መልክ አሳትሞ ለመያዝ የካርድ ህትመት ለማዘዝ የሚያስችል መሆኑን አንተስዋል።
በቀጣይም እየተሻሻለ እና የዘመነ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ነዋሪዎች ደህንነቱ የተጠበቀ ፣ ቀልጣፋ እና ዘመናዊ አገልግሎትን እንዲያገኙበት መሆኑንም ጠቅሰዋል።
መተግበሪያውን ከአፕ ስቶር እንዲሁም ከፕሌይ ስቶር ላይ በማውረድ መጠቀም ይቻላል።
የበለጠ መረጃ ድረገጻችን id.gov.et ላይ በመግባት ማግኘት ይችላሉ ብለዋል።
👍3
ሰበር ዜና‼️
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ለሶስት ወራት ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለሶስት ወራት “በምንም አይነት” ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳይሳተፍ አገደ።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የሚያስችል “የእርምት እርምጃ” ካልወሰደ የፓርቲው ምዘገባ በቀጥታ እንደሚሰረዝ ቦርዱ አስታውቋል።
ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ ህወሓትን በተመለከተ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 6፤ 2017 ባወጣው መግለጫ ነው። ቦርዱ ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱን የገለጸው፤ በነሐሴ 2016 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ ነበር።
ይህ እርምጃ በጥር 2013 ዓ.ም. በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ከፓርቲነት የተሰረዘው ህወሓትን፤ ወደ “ህጋዊ ሰውነት” የመለሰ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ቦርዱ ህወሓትን ከፓርቲነት ሰርዞ የነበረው፤ “ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሳተፉን” እንዳረጋገጠ በመጥቀስ ነበር።
ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማጣት በምክንያትነት ተጠቅሶ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተካሄደ የግጭት ማቆም ስምምነት በጥቅምት 2015 ዓ.ም. መቋጨቱ ይታወሳል። ስምምነቱን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈራረመው ህወሓት፤ ህጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ለቦርዱ ያቀረበው ጥያቄ “በህግ የተደገፈ አይደለም” በሚል ውድቅ ተደርጎ ነበር።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህወሓትን ለሶስት ወራት ከፖለቲካዊ እንቅስቃሴ አገደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) ለሶስት ወራት “በምንም አይነት” ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ እንዳይሳተፍ አገደ።
በዚህ ጊዜ ውስጥ ህወሓት ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ የሚያስችል “የእርምት እርምጃ” ካልወሰደ የፓርቲው ምዘገባ በቀጥታ እንደሚሰረዝ ቦርዱ አስታውቋል።
ብሔራዊው ምርጫ ቦርድ ይህን ያስታወቀው፤ ህወሓትን በተመለከተ ዛሬ ሐሙስ የካቲት 6፤ 2017 ባወጣው መግለጫ ነው። ቦርዱ ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት “በልዩ ሁኔታ” መስጠቱን የገለጸው፤ በነሐሴ 2016 ዓ.ም. መጀመሪያ ላይ ነበር።
ይህ እርምጃ በጥር 2013 ዓ.ም. በምርጫ ቦርድ አማካኝነት ከፓርቲነት የተሰረዘው ህወሓትን፤ ወደ “ህጋዊ ሰውነት” የመለሰ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር። ቦርዱ ህወሓትን ከፓርቲነት ሰርዞ የነበረው፤ “ኃይልን መሠረት ባደረገ የአመጻ ተግባር ላይ መሳተፉን” እንዳረጋገጠ በመጥቀስ ነበር።
ለህወሓት ህጋዊ ሰውነት ማጣት በምክንያትነት ተጠቅሶ የነበረው የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት፤ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በተካሄደ የግጭት ማቆም ስምምነት በጥቅምት 2015 ዓ.ም. መቋጨቱ ይታወሳል። ስምምነቱን ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የተፈራረመው ህወሓት፤ ህጋዊ ሰውነቱ እንዲመለስ ለቦርዱ ያቀረበው ጥያቄ “በህግ የተደገፈ አይደለም” በሚል ውድቅ ተደርጎ ነበር።
👍4❤1
በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ 13 መምህራን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናገሩ!
በሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት 13 መምህራን ፋኖ ታጣቂዎች ናቸው ባሏቸው ታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ።
ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸውን በይፋ እንዳንጠቅስ የጠየቁን የታጋች ቤተሰቦች ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በአካባቢው ትምህርት ከተከፈተ አንድ ወር እንዳለፈው ገልጸው ባለፈው ዕረቡ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ትምህርት ቤቱ የሄዱ መምሕራንን ታጣቂዎቹ አግተው ወደ በርሃ ይዘዋቸው እንደሄዱ መስማታቸውን ተናግረዋል።
ታጣቂዎቹ ከዚህ በፊትም ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ መምህራንን ሥራ እንዳይጀምሩ ማስጠንቀቃቸውን እና ሥራ ለመጀመር ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ መምሕራንን በማገት እስከ 50 ሺሕ ብር አስከፍለው እንደሚለቁ ተናግረዋል።በአሁኑ ሰዓት ወረዳው በመንግሥት ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት “መምህራኑን ሥራ ጀምሩ ጥበቃ ይደረግላችኋል” ብለዋቸው እንደነበርም አክለዋል።
የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ተረፈ አበጀ በስልክ አግኝተናቸው መምህራኑ መታገታቸውን አምነው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል።ለጎንጂ ቆለላ ወረዳ አስተዳዳሪ ለአቶ ጌታቸው ደገፋው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ የፋኖ ታጣቂዎች ምላሽ ለማግኘትም ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
Via VoA
በሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት 13 መምህራን ፋኖ ታጣቂዎች ናቸው ባሏቸው ታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ።
ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸውን በይፋ እንዳንጠቅስ የጠየቁን የታጋች ቤተሰቦች ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በአካባቢው ትምህርት ከተከፈተ አንድ ወር እንዳለፈው ገልጸው ባለፈው ዕረቡ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ትምህርት ቤቱ የሄዱ መምሕራንን ታጣቂዎቹ አግተው ወደ በርሃ ይዘዋቸው እንደሄዱ መስማታቸውን ተናግረዋል።
ታጣቂዎቹ ከዚህ በፊትም ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ መምህራንን ሥራ እንዳይጀምሩ ማስጠንቀቃቸውን እና ሥራ ለመጀመር ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ መምሕራንን በማገት እስከ 50 ሺሕ ብር አስከፍለው እንደሚለቁ ተናግረዋል።በአሁኑ ሰዓት ወረዳው በመንግሥት ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት “መምህራኑን ሥራ ጀምሩ ጥበቃ ይደረግላችኋል” ብለዋቸው እንደነበርም አክለዋል።
የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ተረፈ አበጀ በስልክ አግኝተናቸው መምህራኑ መታገታቸውን አምነው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል።ለጎንጂ ቆለላ ወረዳ አስተዳዳሪ ለአቶ ጌታቸው ደገፋው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ የፋኖ ታጣቂዎች ምላሽ ለማግኘትም ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
Via VoA
በአቃቂ ቃሊቲ ቤቶችን በማኅበር የተቀበሉ ነዋሪዎች ከሕግ አግባብ ውጭ ታግደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቀረቡ!
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሕጋዊ መንገድ በማኅበር ተደራጅተው የመሬት ባለንብረት መሆን የቻሉ ማኅበራት ከ4 ዓመታት ወዲህ በክፍለ ከተማውና በከተማ አስተዳደሩ 'የኦዲት ግኝት ችግር ያሉባቸው ማኅበራት አሉ' በማለት፤ ማንኛውንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳይችሉ ያለአግባብ መታገዳቸውን ለአሐዱ ባቀረቡት ቅሬታ ገልጸዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ 1997 ዓ.ም ሕጋዊ አሠራሩን በጠበቀ መልኩ በመደራጀት የቤት ባለንብረት መሆን መቻላቸውን ጠቁመው፤ አንድ ማኅበር ውስጥ 12 አባወራ አባላት መኖራቸውን ተናግረዋል።ሁሉም አባላት 94 ካሬ መሬት ይዞታ እንዳላቸውና ሕጋዊ ሰነድ ያሟሉ መሆናቸውን የገለጹም ሲሆን፤ "ነገር ግን በወቅቱ የተለያዩ ግርግሮች በመፈጠራቸው ምክንያት ይህንን አጋጣሚ ተገን በማድረግ 'በሕገወጥ መንገድ ባለንብረት የሆኑ ግለሰቦች አሉ' ተብሎ እግዱ ተጥሎብናል" ብለዋል።
አክለውም ለጉዳያቸው መፍትሔ ፍለጋ ወደሚመለከታቸው ተቋማት ቢሄዱም፤ መፍትሔ ማግኘት እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።በዚህም "ቤቶችን መሸጥ መለወጥ እንዳችል እንዲሁም ግብር እንዳንከፍል አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ታግደናል" ብለዋል።ለተጠቀሱት ችግሮች ባለፉት 4 ዓመታት እልባት እንዳልተሰጣቸው የገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በዚህም ምክንያት ለአላስፈላጊ ወጪ እና ለእንግልት መዳረጋቸውን አብራርተዋል።
አሐዱ የቅሬታ አቅራቢዎችን አቤቱታ በማድመጥ ምላሽ ለማግኘት በጉዳዩ ዙሪያ የከተማ አስተዳዳሩን አነጋግሯል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትአለም መለሰ በሰሰጡት ምላሽ ከተማ አስተዳደሩ ከክፍለ ከተማ የሚመጡ ችግሮችን እልባት በመስጠት መልሶ ወደ ክፍለ ከተማ እንደሚልክ አንስተው፤ ጉዳዩን በዋናነት ክፍለ ከተማውን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡
አሐዱም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዓለማየሁ ሚጀናን አነጋግሯል። ሥራ አስኪያጁም በምላሻቸው ማህበራቱ እንደታገዱ አምነው፤ የኦዲት ችግር ያለባቸው በመኖራቸው የማጣራት ሥራው ብዙ ጊዜ እንደሚፈጅ ተናግረዋል።
አያይዘውም በሕገ-ወጥ መንገድ ሕጋዊነት ያላቸው የሚመስሉ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫዎች የሚሰጡ ግለሰቦች በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ሥራው አጽንኦት ተሰጥቶት እየተሰራበት መሆኑን አብራርተዋል፡፡አክለውም ከ900 በላይ ማህበራት በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ጊዜው መጓተቱን አስረድተው፤ "ምላሹን በቅርቡ ለመስጠት እየተሠራ ይገኛል" ሲሉ ገልጸዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎች እንደገለጹት በተለያዩ ጊዜያት ወደ ከተማ አስተዳደሩ እና ክፍለ ከተማ በሚሄዱበት ወቅት የሚሰጣቸው ምላሽ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ለችግሩ እልባት እንደሚሰጥ ነው።ነገር ግን ላለፉት 4 ዓመታት ምላሻ እንዳላገኙ አሳስበዋል።የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ አቤቱታዎችን ሲያሰሙ ይደመጣል።
Via Ahadu
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሕጋዊ መንገድ በማኅበር ተደራጅተው የመሬት ባለንብረት መሆን የቻሉ ማኅበራት ከ4 ዓመታት ወዲህ በክፍለ ከተማውና በከተማ አስተዳደሩ 'የኦዲት ግኝት ችግር ያሉባቸው ማኅበራት አሉ' በማለት፤ ማንኛውንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳይችሉ ያለአግባብ መታገዳቸውን ለአሐዱ ባቀረቡት ቅሬታ ገልጸዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎቹ 1997 ዓ.ም ሕጋዊ አሠራሩን በጠበቀ መልኩ በመደራጀት የቤት ባለንብረት መሆን መቻላቸውን ጠቁመው፤ አንድ ማኅበር ውስጥ 12 አባወራ አባላት መኖራቸውን ተናግረዋል።ሁሉም አባላት 94 ካሬ መሬት ይዞታ እንዳላቸውና ሕጋዊ ሰነድ ያሟሉ መሆናቸውን የገለጹም ሲሆን፤ "ነገር ግን በወቅቱ የተለያዩ ግርግሮች በመፈጠራቸው ምክንያት ይህንን አጋጣሚ ተገን በማድረግ 'በሕገወጥ መንገድ ባለንብረት የሆኑ ግለሰቦች አሉ' ተብሎ እግዱ ተጥሎብናል" ብለዋል።
አክለውም ለጉዳያቸው መፍትሔ ፍለጋ ወደሚመለከታቸው ተቋማት ቢሄዱም፤ መፍትሔ ማግኘት እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።በዚህም "ቤቶችን መሸጥ መለወጥ እንዳችል እንዲሁም ግብር እንዳንከፍል አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ታግደናል" ብለዋል።ለተጠቀሱት ችግሮች ባለፉት 4 ዓመታት እልባት እንዳልተሰጣቸው የገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በዚህም ምክንያት ለአላስፈላጊ ወጪ እና ለእንግልት መዳረጋቸውን አብራርተዋል።
አሐዱ የቅሬታ አቅራቢዎችን አቤቱታ በማድመጥ ምላሽ ለማግኘት በጉዳዩ ዙሪያ የከተማ አስተዳዳሩን አነጋግሯል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትአለም መለሰ በሰሰጡት ምላሽ ከተማ አስተዳደሩ ከክፍለ ከተማ የሚመጡ ችግሮችን እልባት በመስጠት መልሶ ወደ ክፍለ ከተማ እንደሚልክ አንስተው፤ ጉዳዩን በዋናነት ክፍለ ከተማውን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡
አሐዱም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዓለማየሁ ሚጀናን አነጋግሯል። ሥራ አስኪያጁም በምላሻቸው ማህበራቱ እንደታገዱ አምነው፤ የኦዲት ችግር ያለባቸው በመኖራቸው የማጣራት ሥራው ብዙ ጊዜ እንደሚፈጅ ተናግረዋል።
አያይዘውም በሕገ-ወጥ መንገድ ሕጋዊነት ያላቸው የሚመስሉ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫዎች የሚሰጡ ግለሰቦች በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ሥራው አጽንኦት ተሰጥቶት እየተሰራበት መሆኑን አብራርተዋል፡፡አክለውም ከ900 በላይ ማህበራት በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ጊዜው መጓተቱን አስረድተው፤ "ምላሹን በቅርቡ ለመስጠት እየተሠራ ይገኛል" ሲሉ ገልጸዋል።
ቅሬታ አቅራቢዎች እንደገለጹት በተለያዩ ጊዜያት ወደ ከተማ አስተዳደሩ እና ክፍለ ከተማ በሚሄዱበት ወቅት የሚሰጣቸው ምላሽ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ለችግሩ እልባት እንደሚሰጥ ነው።ነገር ግን ላለፉት 4 ዓመታት ምላሻ እንዳላገኙ አሳስበዋል።የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ አቤቱታዎችን ሲያሰሙ ይደመጣል።
Via Ahadu
የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር # ''ጥቅማ ጥቅሞች'' !!
👉 የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን መቀመጫው የኅብረቱ ጽህፈት ቤት ሲሆን፣ የኅብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎችን ይመራል ይቆጣጠራል።
👉 የአህጉራዊው ድርጅት ሊቀመንበር ኃላፈነቱን ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ የአፍሪካ ኅብረት ዋነኛው ዲፕሎማት በመሆን በአባል አገራት፣ በዓለም አገራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ተቋማት የተለያ ተሰሚነት እና ቦታን ያገኛል።
👉 ኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር መቀመጫው አዲስ አበባ ሲሆን፣ በኃላፊነቱ ከሚያገኘው ስም እና ዝና ባሻገር ለሚያከናውነው ተግባር ለእራሱ እና ለቤተሰቦቹ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ከኅብረቱ ያገኛል።
👉 የኅብረቱ ሊቀመንበር በወር ከ15 ሺህ 500 የአሜሪካ ዶላር በላይ ደሞዝ የሚያገኝ ሲሆን፣ ልጅ ካለ በእያንዳንዱ ልጅ ስም የ250 ዶላር ድጎማ፣ በተጨማሪ ለቤት ኪራይ፣ ለመብራት እና ለውሃ የሚውል በየወሩ 6000 ዶላር ተመድቦለታል።
👉 እንዲሁም የኅብረቱ ሊቀመንበር ልጆች በአፍሪካ ውስጥ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከሆነ የትምህርት ወጪያቸው ሙሉ ለሙሉ ይሸፈንላቸዋል። ከአውሮፓ እና ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከሆነ ሙሉ በሙሉ ወጪያቸው እንደሚሸፈን የኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ ያሳያል።
👉 የሊቀመንበሩ ልጆች በአውሮፓው ወይም በሰሜን አሜሪካ የሚማሩ ከሆነ ለእያንዳንዳቸው የትምህርት ወጪያቸውን የሚሸፍን 15 ሺህ ዶላር ክፍያ በዓመት ያገኛሉ። በተጨማሪም ከአህጉሪቱ ውጪ ለሚኖሩት ልጆች ለቤት ኪራይ ስድስት ሺህ ብር ድጎማ እንዳላቸው የቢቢሲ መረጃ ያሳያል ።
👉 የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን መቀመጫው የኅብረቱ ጽህፈት ቤት ሲሆን፣ የኅብረቱን የዕለት ተዕለት ሥራዎችን ይመራል ይቆጣጠራል።
👉 የአህጉራዊው ድርጅት ሊቀመንበር ኃላፈነቱን ከተረከበበት ጊዜ አንስቶ የአፍሪካ ኅብረት ዋነኛው ዲፕሎማት በመሆን በአባል አገራት፣ በዓለም አገራት እንዲሁም በዓለም አቀፍ እና አህጉራዊ ተቋማት የተለያ ተሰሚነት እና ቦታን ያገኛል።
👉 ኅብረቱ ኮሚሽን ሊቀመንበር መቀመጫው አዲስ አበባ ሲሆን፣ በኃላፊነቱ ከሚያገኘው ስም እና ዝና ባሻገር ለሚያከናውነው ተግባር ለእራሱ እና ለቤተሰቦቹ የተለያዩ ጥቅማጥቅሞችን ከኅብረቱ ያገኛል።
👉 የኅብረቱ ሊቀመንበር በወር ከ15 ሺህ 500 የአሜሪካ ዶላር በላይ ደሞዝ የሚያገኝ ሲሆን፣ ልጅ ካለ በእያንዳንዱ ልጅ ስም የ250 ዶላር ድጎማ፣ በተጨማሪ ለቤት ኪራይ፣ ለመብራት እና ለውሃ የሚውል በየወሩ 6000 ዶላር ተመድቦለታል።
👉 እንዲሁም የኅብረቱ ሊቀመንበር ልጆች በአፍሪካ ውስጥ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከሆነ የትምህርት ወጪያቸው ሙሉ ለሙሉ ይሸፈንላቸዋል። ከአውሮፓ እና ከሰሜን አሜሪካ ውጪ ትምህርታቸውን የሚከታተሉ ከሆነ ሙሉ በሙሉ ወጪያቸው እንደሚሸፈን የኅብረቱ መተዳደሪያ ደንብ ያሳያል።
👉 የሊቀመንበሩ ልጆች በአውሮፓው ወይም በሰሜን አሜሪካ የሚማሩ ከሆነ ለእያንዳንዳቸው የትምህርት ወጪያቸውን የሚሸፍን 15 ሺህ ዶላር ክፍያ በዓመት ያገኛሉ። በተጨማሪም ከአህጉሪቱ ውጪ ለሚኖሩት ልጆች ለቤት ኪራይ ስድስት ሺህ ብር ድጎማ እንዳላቸው የቢቢሲ መረጃ ያሳያል ።
👍2❤1
Forwarded from Capitalethiopia
የጅቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ የሱፍ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ
የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ነው።
የሱፍ የተመረጡት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነዉ።
55 አባል አገራት ያሉትን ህብረቱን እኤአ ከ 2017 ጀምሮ በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ሙሳ ፋኪን በመተካት ያገለግላሉ።
የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ ላይ ነው።
የሱፍ የተመረጡት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነዉ።
55 አባል አገራት ያሉትን ህብረቱን እኤአ ከ 2017 ጀምሮ በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ሙሳ ፋኪን በመተካት ያገለግላሉ።
👍2
ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ከሲሚንቶ አልፎ ወደ ስኳር ምርት ላይ አመራ!
በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን ግዙፉን የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካን ካስጀመረ በኋላ፣ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አይነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያሰፋ መሆኑን አስታውቋል።
የግሪፑ ለቀመንበርና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ የአገሪቱ እየተሻሻለ የመጣውን የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ እና በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረጓቸውን ውጤታማ ውይይቶች ተከትሎ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍ ማቀዱን ገልጿል።
በናይጄሪያ የ 60,000 ሄክታር ስኳር እርሻ በማልማት ያገኘውን ልምድ በመጠቀም ኩባንያው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ውስጥ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ጠቁሟል።
ወደፊትም ዳንጎቴ ግሩፕ የአገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ልማት ላይ በመመስረት የእርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ያለመ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ለመመስረት እንቅድ እንዳለው ካፒታል ሰምታለች።
Via Capital
በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን ግዙፉን የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካን ካስጀመረ በኋላ፣ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አይነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያሰፋ መሆኑን አስታውቋል።
የግሪፑ ለቀመንበርና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ የአገሪቱ እየተሻሻለ የመጣውን የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ እና በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረጓቸውን ውጤታማ ውይይቶች ተከትሎ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍ ማቀዱን ገልጿል።
በናይጄሪያ የ 60,000 ሄክታር ስኳር እርሻ በማልማት ያገኘውን ልምድ በመጠቀም ኩባንያው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ውስጥ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ጠቁሟል።
ወደፊትም ዳንጎቴ ግሩፕ የአገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ልማት ላይ በመመስረት የእርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ያለመ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ለመመስረት እንቅድ እንዳለው ካፒታል ሰምታለች።
Via Capital
#CapitalNews የኢትዮጵያ የአበባ የወጪ ንግድ በቫለንታይን ቀን በ7% መቀነሱ ተነገረ
በተለምዶ ንቁ የሆነው የኢትዮጵያ የአበባ በወጪ ንግድ ዘርፍ፣ ወሳኝ በሆነው የቫለንታይን ( የፍቅረኞች) ቀን ወቅት ማለትም ከጥር 24 እስከ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የተላከዉ ምርት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ7% ቅናሽ አሳይቷል።
ካፒታል ከኢትዮጵያ የሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማኅበር ያገኘችዉ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የወጪ ንግድ መጠኑ በ2016 ከነበረው 2,913,178.50 ኪሎ ግራም በ207 ወደ 2,696,069 ኪሎ ግራም ቀንሷል።
ይህንን ዝቅተኛ አፈፃፀም ሊመጣ የቻለዉ በዋነኝነት በቁልፍ የአበባ ማምረቻ ክልሎች ውስጥ እየቀጠለ ባለዉ አለመረጋጋት ምክንያት መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።
በአካባቢው ያለው አለመረጋጋት የምርትና የሎጂስቲክስ ሂደቶችን በማስተጓጎል ኢትዮጵያ የፍቅረኞች ቀን አበባዎች ከፍተኛ ፍላጎት መጠቀም እንዳትችል አድርጓታል ተብሏል።
የቫለንታይን ቀን ወቅት በተለምዶ ለአበባ እርሻዎች ወሳኝ ወቅት ሲሆን ከፍተኛ ገቢ እና የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል። የ7% ቅናሽ መሰረታዊ ችግሮች ካልተፈቱ ለኢንዱስትሪው ሰፋ ያለ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል የሚያሳስብ አዝማሚያ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል።
መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከጥር 13 እስከ የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ከ4,500 ቶን በላይ አበባዎችን ለዓለም አቀፋዊ ገበያዎች የላከች ሲሆን የእነዚህ ጭነት ዋና መዳረሻዎች አውሮፓ፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ መካከለኛው ምሥራቅ እና ሩቅ ምሥራቅን እንደሚያካትቱ ይታወቃል።
በተለምዶ ንቁ የሆነው የኢትዮጵያ የአበባ በወጪ ንግድ ዘርፍ፣ ወሳኝ በሆነው የቫለንታይን ( የፍቅረኞች) ቀን ወቅት ማለትም ከጥር 24 እስከ የካቲት 6 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የተላከዉ ምርት ካለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ7% ቅናሽ አሳይቷል።
ካፒታል ከኢትዮጵያ የሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማኅበር ያገኘችዉ መረጃ እንደሚያመለክተው፣ የወጪ ንግድ መጠኑ በ2016 ከነበረው 2,913,178.50 ኪሎ ግራም በ207 ወደ 2,696,069 ኪሎ ግራም ቀንሷል።
ይህንን ዝቅተኛ አፈፃፀም ሊመጣ የቻለዉ በዋነኝነት በቁልፍ የአበባ ማምረቻ ክልሎች ውስጥ እየቀጠለ ባለዉ አለመረጋጋት ምክንያት መሆኑን ለመረዳት ተችሏል።
በአካባቢው ያለው አለመረጋጋት የምርትና የሎጂስቲክስ ሂደቶችን በማስተጓጎል ኢትዮጵያ የፍቅረኞች ቀን አበባዎች ከፍተኛ ፍላጎት መጠቀም እንዳትችል አድርጓታል ተብሏል።
የቫለንታይን ቀን ወቅት በተለምዶ ለአበባ እርሻዎች ወሳኝ ወቅት ሲሆን ከፍተኛ ገቢ እና የውጭ ምንዛሬ ያስገኛል። የ7% ቅናሽ መሰረታዊ ችግሮች ካልተፈቱ ለኢንዱስትሪው ሰፋ ያለ አንድምታ ሊኖረው እንደሚችል የሚያሳስብ አዝማሚያ እንደሚያሳይ ተጠቁሟል።
መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ከጥር 13 እስከ የካቲት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ ኢትዮጵያ ከ4,500 ቶን በላይ አበባዎችን ለዓለም አቀፋዊ ገበያዎች የላከች ሲሆን የእነዚህ ጭነት ዋና መዳረሻዎች አውሮፓ፣ እንግሊዝ፣ አሜሪካ፣ መካከለኛው ምሥራቅ እና ሩቅ ምሥራቅን እንደሚያካትቱ ይታወቃል።
👍5
የፕሪቶሪያውን ስምምነት በሚመለከት በአፍሪካ ሕብረት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ
በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም
በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።
ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት <<የዛሬው መድረክ እስካሁን የሄድንበት ርቀት መገምገም ነው። ከጀመርነው ፍጥነት አንፃር ገና ያላለቁ ነገሮች አሉ። ግን በተሻለ ፍጥነት መጨረስ የምንችልበት እድል ለማግኘት ነው የመጣነው" ብለዋል። አክለውም ሰላምን ከመስበክ ፣ ሰላምን ከመተግበርም ሆነ ከምንም ነገር በላይ ግን ተፈናቃዮች ወደወትሮ ህይወታቸው የሚመለሱበትና ህገመንግስቱ በሚያስቀምጠው መሰረት የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጉዳይ ላይ ነው ሀሳብ የተለዋወጥነው። በቀጣይም በዚህ መሰረት የምንቀጥል ይመስለኛል" ብለዋል።
Reporter
በትግራይ ክልል የነበረውን ግጭት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት ሂደትን በተመለከተና ከስምምነቱ "ሌሎች ምን እንማር?" በሚል ርዕስ ዛሬ የካቲት 9ቀን 2017ዓ.ም
በአፍሪካ ህብረት ሪፓርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።
በዚህ ውይይት ላይም የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ እና የህወሓት ሊቀመንበር ደብረ ጽዮን ገብረሚካኤል(ዶ/ር) የተገኙ ሲሆን ከኢትዮጵያ መንግሥት በኩል ደግሞ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ጌድዮን ጢሞቲዎስ (ዶ/ር) ፣ የሰላም ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ እድሪስ እና ሌሎች ተገኝተዋል።
የፕሪቶሪያውን ስምምነትና አፈፃፀም የተመለከተውን ሪፓርት ደግሞ ተሰናባቹ የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ሙሳ ፉኪ ማህማት፣ የቀድሞ የናይጀሪያ ፕሬዚዳንትና የአፍሪካ ህብረት አደራዳሪ ቡድን ሰብሳቢ ኡሊሲንጎን ኦባሳንጆ እና ከፍተኛ ኮሚሽነሮች አቅርበዋል።
ከአንድ ሰአት በላይ የዘለቀ ውይይት ከተካሄደ በኋላ አቶ ጌታቸው ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥተዋል።
የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዚዳንት <<የዛሬው መድረክ እስካሁን የሄድንበት ርቀት መገምገም ነው። ከጀመርነው ፍጥነት አንፃር ገና ያላለቁ ነገሮች አሉ። ግን በተሻለ ፍጥነት መጨረስ የምንችልበት እድል ለማግኘት ነው የመጣነው" ብለዋል። አክለውም ሰላምን ከመስበክ ፣ ሰላምን ከመተግበርም ሆነ ከምንም ነገር በላይ ግን ተፈናቃዮች ወደወትሮ ህይወታቸው የሚመለሱበትና ህገመንግስቱ በሚያስቀምጠው መሰረት የፕሪቶሪያ ውል ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሚሆንበት ጉዳይ ላይ ነው ሀሳብ የተለዋወጥነው። በቀጣይም በዚህ መሰረት የምንቀጥል ይመስለኛል" ብለዋል።
Reporter
👍2