Telegram Web Link
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
አዲስ አበባ የትራፊክ መጨናነቅን ለማቃለል አዲስ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ አገልግሎት ጀመረች

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ በአንድ ጊዜ 1,000 መኪኖችን የማቆም አቅም ያለውን እና በሾላ ገበያና መገናኛ አካባቢ ያለውን ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ የሚያቃልለውን የየካ ቁጥር 2 የመኪና ማቆሚያ መርቀው አስጀመሩ።

የፕሮጀክቱ ገፅታዎችና አገልግሎቶች

ከንቲባ አዳነች በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ ይህ የመኪና ማቆሚያ ከምድር በላይ ባለ አምስት ወለል እንዲሁም ከመሬት በታች ባለ ሁለት ወለል፣ በአጠቃላይ 8 ወለሎች እንዳሉት ገልጸዋል።

ፕሮጀክቱ ምቹ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ፣ ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት እና የህዝብን እንግልት የሚያቃልል መሆኑንም ጠቁመዋል።

የመኪና ማቆሚያው የህዝብን አገልግሎት ምቾትና ክብርን የጠበቀ፣ ተገልጋዮችን ከዝናብና ጸሀይ የሚከላከል፣ የንጽህና መጠበቂያ ያለው፣ የሰውና የመኪና አሳንሰር የተገጠመለት፣ ለአካል ጉዳተኞች አካታች የሆነ አገልግሎት የሚሰጥ፣ ሶስት የመኪና ማጠቢያ ስፍራዎች ያሉት እንዲሁም ለነዋሪዎች የስራ እድል የሚፈጥር ግዙፍ ፕሮጀክት መሆኑንም ከንቲባዋ አመልክተዋል።

በተጨማሪም፣ በውስጡ ሌሎች አገልግሎቶችን የሚሰጡ ሱቆችና ቢሮዎች በመኖራቸው የኢኮኖሚና የማህበራዊ አገልግሎትን ለማሳለጥ እንዲሁም የትራንስፖርት ስርአቱን ለማዘመን ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው ተገልጿል።

የአዲስ አበባን የፓርኪንግ አቅም ማስፋት

ይህ የተሽከርካሪ ማቆሚያ ለመጀመሪያ ጊዜ በህንጻ ደረጃ የተገነባ ሲሆን፣ መሬት እና በጀት በመመደብ የተሰራው ይህ ስራ ከተማዋን እንደ ስሟ ውብ አበባ የማድረግ አካል ነው ብለዋል ከንቲባዋ።

ከለውጡ በፊት በመንግስት የተገነቡ የፓርኪንግ ቦታዎች ብዛት 2 ብቻ እንደነበሩና 500 መኪኖችን የማቆም አቅም ያልነበራቸው እንዲሁም 1 ተርሚናል ብቻ እንደነበረ የጠቀሱት ከንቲባዋ፣ ከለውጡ በኋላ በተሰራው ስራ 150 የመኪና ማቆሚያ ቦታዎች እንደተገነቡና የዛሬውን ጨምሮ በአንድ ጊዜ 35 ሺሕ ተሽከርካሪዎችን ማቆም የሚችሉ ስፍራዎች መኖራቸውን አስታውቀዋል።

በተጨማሪም፣ 49 የሚደርሱ ተርሚናሎችን ገንብቶ የትራንስፖርት ስርዓቱን ለማዘመን እየተሰራ መሆኑንም ከንቲባ አዳነች አቤቤ አክለዋል።

ይህ አዲስ የመኪና ማቆሚያ የአዲስ አበባን የትራፊክ መጨናነቅ በማቃለል ረገድ ምን ያህል ለውጥ ያመጣል ብለው ያስባሉ?
ብሔራዊ ባንክ ስድስተኛውን የዉጪ ምንዛሪ ጨረታ በ50 ሚሊዮን ዶላር ሊያካሂድ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ ገበያን ለማረጋጋትና የውጭ መረጋጋትን ለመቆጣጠር ያለመ 50 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ ነገ ሐሙስ እንደሚያካሂድ አስታውቋል።

ይህ ጨረታ ለንግድ ባንኮች የቀረበ ሲሆን፣ ባንኩ በየሁለት ሳምንቱ ከሚያካሂዳቸው ተከታታይ ጨረታዎች ስድስተኛው ነው።

ከሁለት ሳምንት በፊት በተካሄደው አምስተኛው ዙር የውጭ ምንዛሪ ጨረታ፣ የአንድ የአሜሪካ ዶላር የመገበያያ ዋጋ 132.96 ብር ሆኖ ተመዝግቦ ነበር። በዚያ ጨረታ ላይ ባንኩ 60 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ያቀረበ ሲሆን፣ በጠቅላላው 16 የንግድ ባንኮች የጠየቁትን የውጭ ምንዛሪ ድልድል ማግኘት ችለው እንደነበር ይታወቃል።

Capital newspaper
👍3
ትራኦሬ

የቡርኪናፋሶው ፕሬዚዳንት ኢብራሂም ትራኦሬ ከዛሬ ጀምሮ በመላው ቡርኪናፋሶ የወሲብ ድረገፆችን ሙሉ ለሙሉ አግደዋቸዋል።

ትራኦሬ ማንኛውንም የብልግና ምስል የሚያሰራጩ ድረገፆችን መዘጋታቸውን ተከትሎ "እንዚህ የብልግና ደረገፆች ህዝባችንን ከማባላግ ባለፈ እሴታችንን በእጅጉ በመሸርሸር ህዝባችንን ብቻ ሳይሆን መላው አፍሪካን እያደነዘዘ የሚገኝ አደገኛ ነገር ነው" ያሉ ሲሆን ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮችም ተመሳሳይ እርምጃ በመውሰድ የሀገራቸውን እና የአፍሪካን እሴት እንዲያስጠብቁ አሳስበዋል።

ይህን የኢብራሂም ትራኦሬን ድፍረት የተሞላበት ውሳኔ በርካቶች አድናቆት እየቸሩት ይገኛሉ።
👏9
245 ሚሊዮን ዶላር የመዘበሩት የቀድሞው የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጠቅላይ ሚኒስትር በሙስና ወንጀል 10 ዓመት ከባድ የግዳጅ የጉልበት ስራ ተፈረደባቸው።

አውግስቲን ማታታ ፖንዮ 245 ሚሊዮን ዶላር የሚጠጋ የህዝብ ገንዘብ በመመዝበር የአገሪቱ ህገ መንግሥታዊ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ሆነው ስላገኛቸው ነው ይህ ብይን የተላለፈው።

ከሳቸው በተጨማሪ የዲሞክራቲክ ኮንጎ ማዕከላዊ ባንክ ገዢ የነበሩት ዲኦግራቲያስ ሙቶምቦም በዚህ ምዝበራ በመሳተፍ ጥፋተኛ ሆነው ተገኝተዋል።

የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ጠበቃ ውሳኔው ኢፍትሃዊ እንዲሁም ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ነው ሲሉ መውቀሳቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

ተመዝብሯል ከተባለው ገንዘብ መካከል የተወሰነው የተወሰደው የአገሪቱን ስር የሰደደ የምግብ እጥረት ለመቅረፍ ከታቀደው ትልቅ የግብርና ልማት ነው።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ሊጓዙ ነው ተባለ‼️

ጠ/ሚኒስትሩ ጠፈር ላይ በመሆን ለአለም ህዝብ የሰላም መልዕክት ለማስተላለፍ አቅደዋል።

የጉዞ እቅዱ ከተሳካ ወደ ጠፈር የተጓዙ የመጀመርያው የአለማችን መሪም ያደርጋቸዋል።

በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት ግን ጥቂት ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል የዝቅተኛው ንፍቀ ክበብ የጠፈር ጉብኝት አድርገዋል።

Via መሠረት ሚዲያ
👍2👎1😁1
97 በመቶ የጤና ሰራተኞች ደመወዛቸው መሰረታዊ ወጪዎችን ለመሸፈን በቂ እንዳልሆነ አዲስ ጥናት አመለከተ

በአፍሪካ የህዝብ ጤና እና ትምህርት አገልግሎቶች ከባድ ችግር ውስጥ መሆናቸውን የሚያሳይ አዲስ ጥናት ይፋ ሆኗል።

በአክሽንኤይድ ኢንተርናሽናል የወጣው “በአፍሪካ የመንግስት ዘርፍ ቅነሳ የሰው ልጅ ዋጋ” የተሰኘው ጥናት፣ በስድስት የአፍሪካ ሀገራት (ኢትዮጵያ፣ ጋና፣ ኬንያ፣ ላይቤሪያ፣ ማላዊ እና ናይጄሪያ) የቁጠባ ፖሊሲዎች በሰው ልጅ ላይ የሚያስከትሉትን ከፍተኛ ዋጋ አጉልቶ አሳይቷል።

የጥናቱ ግኝቶች እንደሚያመለክቱት፣ 97 በመቶ የሚሆኑት የጤና ሰራተኞች ደሞዛቸው የቤት ኪራይ፣ ምግብ እና ሌሎች አስፈላጊ የቤት ወጪዎችን ለመሸፈን በቂ እንዳልሆነ ገልጸዋል።

በተመሳሳይ፣ ከ2020 ወዲህ 84 በመቶ የሚሆኑት አስተማሪዎች እውነተኛ ገቢያቸው ከ10 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ አሳይቷል።

ይህ ደመወዝ በቂ አለመሆን የሰራተኞችን የኑሮ ጫና በእጅጉ እንደጨመረ ተመላክቷል።
እንደ ግኝቱ መሰረት ፣ የመንግስት በጀት ቅነሳ እና እየጨመረ የመጣው የተማሪዎችና የታካሚዎች ቁጥር ከፍተኛ የስራ ጫና ፈጥሯል።

ተጨማሪ ያንብቡ

Capital newspaper
👍3
አንድ ሰው ወደ ጠፈር ጉዞ ሲያስብ
ምን ያስፈልገዋል ?


ISS- international Space Station-

1. ጉዞው ከመሬት ከ6 ስአት 24 ስአት ይፈጃል::

2. ትንሹ ጠረፍ ላይ ለመቀመጥ ከ8 እስከ 10 ቀን ሲሆን::

ትልቁ ደሞ 1 ወር ይሆናል ::

3.አሁን ላይ 4 ድርጅቶች ሰዎችን በቱሪስትነት ወደ ጠፈር እየወስዱ ይገኛል

እነሱም

* Axiom Space (USA)
* SpaceX (USA)
* Roscosmos (Russia)
* Space Adventures (USA)

ወደፊት ደሞ :-
* Blue Origin (USA – Jeff Bezos)
* Virgin Galactic (USA – Richard Branson )

ሰዎችን ለማጏጏዝ አስበዋል::

ወደ ዋናው ጥያቄ ስንገባ ስንት ብር ያስፍልጋል ወይንም እነዚህ ድርጅቶች ስንት ዶላር ተቀብለው ነው ሰውን ወደ ጠፈር የሚልኩት ሲባል ደሞ

* ከእነ ምግብ
* ትምህርቱ
* Medical cover
* ከእነ ሁሉም ነገር
* VIP treatment

አሁን ላይ ለአንድ ሰው (per person)

* 55 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ሲሆን
ወደ ብር ሲመነዘር ደሞ በባንክ ምንዛሬ
6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ይሆናል

ነገር ግን እነ Elon Musk ወደፊት በአንድ ሰው ከ5 ሚሊዮን ዶላር እስከ 20 ሚሊዮን ዶላር ለማስከፈል  ብዙ ሰራ እየሰሩ ሲሆን

ይህን ነገር እውን የሚሆነው በሚቀጥለው 10 ዓመት ወይንም ከዚህ ቀደም ባሉ ዓመታት ነውም ተብሏል::

ለ14 ቀን ወይንም ለ1 ወር ወደ ጠፈር 6 ቢሊዮን 875 ሚሊዮን የኢትዮጵይ ብር ከፍለው መሄድ ይፈልጋሉ

እንግዲያው ከላይ ያሉትን ድርጅቶች ያናግሩ::

መልካም ጉዞ::
👍5
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
Photo
ብሔራዊ ሙዚዬም ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት ይሆናል

ባለፉት ወራት ለእድሳት ተዘግቶ የቆየው ብሔራዊ ሙዚየም ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት እንደሚሆን የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን አስታወቀ።

የኢትዮጵያ ቅርስ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ለኢፕድ እንደተናገሩት፤ ባለፉት ወራት ለእድሳት ተዘግቶ የቆየው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዚዬም ከነገ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓም ጀምሮ ለህዝብ ክፍት ይሆናል፡፡

በ1965 የተሰራው ብሔራዊ ሙዚየሙ የውሃ መፋሰሻ መቀየርና ዙሪያውን ማስተካከል እንዲሁም ሙዚዬሙ ውስጥ ለእይታ የቀረቡ ቅርሶች እንዳይጎዱ መስራት መቻሉን ተናረዋል፡፡

ውስጥ ላይ ያለውን የሙዚዬሙን ቋሚ ኤግዚቢሽን ደረጃን የማሻሻል ሥራ ተሰርቷል ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፤ ከጥንት ጀምሮ እስከ ቅርብ ዘመን የኢትዮጵያን ታሪክ በሚያሳይ መልኩ እድሳት ተደርጎለታል ብለዋል፡፡

ሙዚዬሙ ቀደም ሲል የሰውን ልጅ አመጣጥና የድንጋይ መሳሪያዎችን ለእይታ ሲቀርቡበት መቆየቱን በመግለጽ፤ አሁን ሥነ ህይወታዊ ዝግመተ ለውጥ በሚያሳይ መልኩ መዘጋጀቱን አመላክተዋል፡፡

ሙዚዬሙ ዛሬ ምሽት ላይ እንደሚመረቅ የሚጠበቅ ሲሆን፤ ከነገ ጀምሮ ለጎብኝዎች ክፍት ይደረጋል።
#ኢፕድ
👍1
የኢትዮጵያ አምባሳደር የፓሃልጋም ጥቃትን በማውገዝ ፓኪስታንን ተጠያቂ አደረጉ

የኢትዮጵያ የህንድ አምባሳደር የሆኑት አቶ ፈስሃ ሻወል ፣ በጃሙ እና ካሽሚር በሚገኘው ፓሃልጋም ላይ ሚያዝያ 14 ቀን 2017 ዓ.ም የተፈፀመውን የሽብር ጥቃት በብርቱ አውግዘው፣ ለጥቃቱ ሙሉ ሃላፊነት ፓኪስታን እንደሆነች በግልጽ አስታውቀዋል።

ይህ ጥቃት 26 ንጹሃን ዜጎችን ለህልፈት የዳረገ ሲሆን፣ የተፈፀመውም በፓኪስታን ድጋፍ ባላቸው አሸባሪዎች መሆኑ በህንድም ሆነ በአለም አቀፍ አጋሮቿ ዘንድ ከፍተኛ ቁጣን ቀስቅሷል።

የሽብርተኝነት ኩነና እና የህንድ ምላሽ ምስጋና
አምባሳደር ገብሬ ፣ ህንድ ለዚህ አሰቃቂ ጥቃት የሰጠችውን ምላሽ “በጣም ሃላፊነት የሚሰማው”፣ የተረጋጋ እና ጽኑ ነበር ሲሉ አሞካሽተዋል።

እንደ አኒ ዘገባ በአለም አቀፍ የሽብርተኝነት ትግል ኢትዮጵያ እና ህንድ የጋራ እሴቶች እንዳሏቸውም አጽንኦት ሰጥተዋል።

አምባሳደሩ፣ “ችግር ለመፍጠር ወደ ፓኪስታን የሄዱት ህንዳውያን አይደሉም፤ ችግር ለመፍጠር ወደ ህንድ የመጡት ፓኪስታናውያን ናቸው” በማለት፣ ኢስላማባድ በአጥቂዎቹ ላይ ያላትን ቀጥተኛ ተሳትፎ በግልጽ አውስተዋል።
😁1🖕1
Hule Addis Media ( ሁሌ አዲስ ሚዲያ)
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ሊጓዙ ነው ተባለ‼️ ጠ/ሚኒስትሩ ጠፈር ላይ በመሆን ለአለም ህዝብ የሰላም መልዕክት ለማስተላለፍ አቅደዋል። የጉዞ እቅዱ ከተሳካ ወደ ጠፈር የተጓዙ የመጀመርያው የአለማችን መሪም ያደርጋቸዋል። በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት…
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ሊጓዙ ነው' ዝርዝር ዘገባ...!!!

በአለም ታሪክ ወደ ጠፈር (space) የተጓዙ ሰዎች ቁጥር 721 እንደሆነ የታሪክ ድርሳናት ያሳያሉ፣ ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹ የጠፈር ተመራማሪዎች ሲሆኑ ከቅርብ አመታት ግን ጥቂት ሰዎች ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል የዝቅተኛው ንፍቀ ክበብ የጠፈር ጉብኝት አድርገዋል።

መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።

በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።

"ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው" ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።

'Project X' የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።

ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።

ለምሳሌ 'Blue Origin' እና 'Virgin Galactic' የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር እስከ 400 ሺህ ዶላር ያስከፍላሉ፣ ራቅ ያሉ እና ከንፍቀ ክበብ ውጪ የሚደረጉ የጠፈር በረራዎችን የሚያከናውኑት እንደ 'Space X' ያሉ ሮኬቶች ደግሞ በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር (7.3 ቢልዮን ብር) እንደሚያስከፍሉ ታውቋል።

ጠ/ሚር አብይ ሊጓዙ እቅድ የያዙት ከንፍቀ ክበብ ውጪ ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ማዕከል (International Space Station) እንደሆነ ታውቋል፣ ወጪውም ከላይ እንደተጠቀሰው በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ እና በኤምሬቶች እንደሚሸፈን ታውቋል።

አንድ ሌላ የስፔስ ባለሙያ ግን የጉብኝቱ አይነት 'lunar' የሚባለው እንደሆነ ሲገለፅ እንደሰሙ ጠቅሰው ይህም ጨረቃ ላይ ሳይታረፍ፣ ዙርያውን በመሄድ የሚደረግ ጉዞ ሊሆን እንደሚችል ጠቁመዋል።

የተባበሩት አረብ ኤምሬት የዛሬ ስድስት አመት ገደማ ሀዛ አል-ማንሱሪ የተባለ ዜጋዋን ወደ ጠፈር ልካ ነበር። ከዛ ወዲህም ከአሜሪካው የጠፈር ድርጅት ናሳ ጋር በመተባበር በመጪው የፈረንጆቹ አመት 2026 ላይ ሰው ወደ ጨረቃ ለመላክ እየተዘጋጀች መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ከጉዞው ጋር በተገናኘ ሂደቱን ተከታትለው እንዲያስፈፅሙ ቢያንስ አምስት የሚሆኑ የመንግስት ሀላፊዎች የቤት ስራ እንደተሰጣቸው የሀገር ቤት ምንጮች አረጋግጠዋል። ይህ የቤት ስራ እስከ ሀምሌ 2017 ዓ/ም ድረስ ንግግሮችን በመጨረስ ከመስከረም በሗላ ጉዞው እንዲከናወን ማድረግ ነው ተብሏል።

ነገር ግን ጠ/ሚሩ ወደ ጠፈር ከመጓዛቸው በፊት ለበርካታ ወራት ልምምድ እና የጤና ሁኔታ ክትትል ማድረግ እንደሚጠብቃቸው አስረድተዋል።

አንድ ስማቸውን የማንጠቅሳቸው የመንግስት ሀላፊን በጉዳዩ ዙርያ መረጃ ጠይቀን "በመጪው አመታት ከተያዙ እቅዶች ውስጥ አንዱ ነው። ለኢትዮጵያ እና ለአለም ሕዝብ የእርቅ እና ሰላም ጥሪ ይደረጋል" ብለው አጭር ምላሽ ሰጥተዋል።

መሠረት ሚዲያ
👍7👎1👏1😁1
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለስራ ጉብኝት ፈረንሳይ ፓሪስ ገቡ!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው ከከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ልዑክ ጋር በመሆን ለስራ ጉብኝት ዛሬ ፈረንሳይ ፓሪስ ገብተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፓሪስ ሲደርሱ በብሔራዊው የጦር ኃይሎች ሙዚየም የአቀባበል ሥነ ሥርዓት ተደርጎላቸዋል።

በጉብኝታቸው ከፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት መረጃ አመላክቷል።
👎2👍1👏1
‹‹መንግስት በአድማ ላይ ካሉ የጤና ባለሙያዎች ጋር ድርድር ያድርግ፣ የታሰሩትንም ይፍታ›› ሲል አምነስቲ ኢንተርናሽናል ጠየቀ

የሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆነው ይህ ተቋም ዛሬ ባወጣው መግለጫ አድማው ከተጀመረ አንስቶ በመላው አገሪቱ 212 የጤና ባለሙያዎች መታሰራቸውን ከጤና ባለሙያዎች ንቅናቄ መስማቱንና የታሰሩት ሰዎች ስም ዝርዝር እንደተላከለትም አስረድቷል፡፡

የታሰሩት ሰዎች ቤተሰቦችና ጠበቆችን ማነጋገሩን የጠቀሰው አምነስቲ ሰዎቹ ሲታሰሩ ምክንያቱ እንዳልተገለፀላቸው መግለፃቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲሁም ያለ ብርበራ ትእዛዝ የጤና ባለሙያዎቹን ቤት ‹‹ጦር መሳሪያ ይኖራል›› በሚል መፈተሻቸውንና የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶቻቸው መወሰዳቸውን ገልጿል፡፡

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል የምስራቅ አፍሪካ ዳይሬክተር ትግሪ ቻጉታ ሲናገሩ ‹‹ይህ አድማ ምንም አይነት መፍትሄ ሳይገኝለት ወደሁለተኛ ሳምንቱ እየተሸጋገረ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በመላ አገሪቱ ወሳኝ በሆኑ የጤና አገልግሎቶች ላይ መስተጓጎልን ፈጥሯል፡፡ በመሆኑም መንግስት የታካሚዎችን መብት የሚገድበውን ይህንን ቀውስ ከዚህ በላይ ማራዘም የለበትም፡፡ መንግስትም ሆነ የጤና ባለሙያዎቹ ይህንን አለመግባባት በድርድር ሊፈቱ ይገባል›› ብለዋል፡፡

ጨምረውም ‹‹የዘፈቀደ እስር ከዚህ ቀደም ለተለያዩ ጉዳዮች ኢትዮጵያ ውስጥ የታየ ሲሆን አሁን ደግሞ ተገቢ ክፍያና የስራ ሁኔታ በጠየቁ የህክምና ባለሙያዎች ላይ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡›› ብለዋል፡፡ አምነስቲ በመግለጫው በሰላማዊ መንገድ ጥያቄ ማቅረብ መብታቸውን ተግባራዊ ባደረጉ የጤና ባለሙያዎች ላይ እየተደረገ ያለው የእስር ዘመቻ እንዲቆምና ችግሩ በንግግር እንዲፈታ ጥሪ አቅርቧል፡፡
የአሜሪካ ኤምባሲ "በራሱ ሕዝብ ላይ" የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶችን የማውገዝ መልዕክት ለወጠ

የአሜሪካ ኤምባሲ አዲስ አበባ፣ ከሰዓታት በፊት አውጥቶት የነበረውንና አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ የፌደራል መንግሥት "በራሱ ሕዝብ ላይ" የሚፈጽማቸውን የድሮን ጥቃቶች "በአፋጣኝ እንዲያቆም" ጥሪ ያቀረቡበትን ልጥፍ ከፌስቡክ እና ከቲውተር ገጾቹ ላይ አንስቶ ለውጥ አድርጓል።

በአዲስ መልክ በወጣው የአምባሳደሩ መልዕክት ላይ፣ የድሮን ጥቃትን በተመለከተ ለፌደራል መንግሥት የቀረበው ጥሪ "መንግሥት ከኃይል ውጪ ያሉ ሰላማዊ አማራጮችን መፈለጉን እንዲቀጥል" በሚጠይቅ ጥሪ ተተክቷል።

አምባሳደር ማሲንጋ ያስተላለፉት የመጀመሪያ መልዕክት በኤምባሲው የፌስቡክ እና ቲውተር ገጾች ላይ የተለጠፈው ዛሬ አርብ ግንቦት 15/2017 ዓ.ም. ከቀኑ 4 ሰዓት ተኩል ገደማ ነበር። በሀገሪቱ ያሉ ግጭቶችን ማቆምን የተመለከተው የአምባሳደሩ መልዕክት፤ ለፌደራል መንግሥት፣ እንዲሁም ለፋኖ ኃይሎች እና ለኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት የተለያዩ ጥሪዎች የቀረቡበት ነበር።

ለፌደራል መንግሥቱ ቀርቦ የነበረው የአምባሳደሩ የመጀመሪያ መልዕክት ሁለት ሀሳቦችን ያዘለ የነበረ ሲሆን፣ አንደኛው በመንግሥት የሚፈጸሙ የድሮን ጥቃቶች እንዲቆሙ የሚጠይቅ ነበር። የአምባሳደሩ የተጠቀሙት አገላለፅ የመንግሥት የድሮን ጥቃቶች "በራስ ሕዝብ ላይ" የሚፈጸሙ እንደሆኑ የሚያመለክት ነበር።
የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ የሥራ ማቆም አድማ ያደረጉ ባለሙያዎችንና ተማሪዎችን አሰናበተ

የቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ፣ በቅርቡ በሥራ ማቆም አድማ የተሳተፉ የጤና ባለሙያዎችንና የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪዎችን (ኢንተርን) ለማሰናበት ወስኗል። ኮሌጁ በእነዚህ የሥራ ማቆም አድማ ተሳታፊዎች ምትክ አዲስ ቅጥር እንደሚፈጽምም አስታውቋል።

ኮሌጁ ባወጣው መግለጫ፣ ቅሬታ ያላቸው ባለሙያዎች እስከ ግንቦት 16 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 6 ሰዓት ድረስ በአካል ቀርበው ይቅርታ መጠየቅ እንደሚችሉ ገልጿል።

በተመሳሳይ፣ ከግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በትምህርትና በሥራ ላይ ባልተገኙ የመጨረሻ ዓመት የህክምና ተማሪዎች (ኢንተርን) ላይም ውሳኔ ተላልፏል።

የኮሌጁ ሴኔት ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት፣ እነዚህ ተማሪዎች ከትምህርታቸው እንዲሰናበቱ ተወስኗል። በዚህም ምክንያት፣ በእጃቸው ላይ የሚገኝ ንብረት አስረክበው ከግቢው እንዲወጡ ኮሌጁ አሳስቧል። ይሁን እንጂ፣ ቅሬታ ያለው ኢንተርን ይግባኝ መጠየቅ እንደሚችል ኮሌጁ አስታውቋል።
👍2
ፌደራል ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ሥር አውሎ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አስታወቀ

የፌደራል ፖሊስ 47 የጤና ባለሙያዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋሉንና ምርመራ እያደረገባቸው እንደሚገኝ አስታውቋል።

ፖሊስ እንደገለጸው፣ በምርመራ ላይ ያሉት የጤና ባለሙያዎች ትርምስ እንዲፈጠር ከሚሠሩ ኃይሎች ጋር በመተባበር "ሕገወጥ የሥራ ማቆም አድማ" በማድረግ፣ "ሁከት" በመፍጠር፣ "የታካሚዎችን ሕይወት አደጋ ላይ በመጣል" እና በሥራ ላይ ያሉ የጤና ባለሙያዎች አድማውን እንዲቀላቀሉ "በማነሳሳት" ተጠርጥረዋል።

ፖሊስ በተጨማሪም፣ ተጠርጣሪዎቹ በጤና ተቋማት ውስጥ "የአድማ መረቦችን" በመዘርጋት፣ የጤና ባለሙያ ያልሆኑ ግለሰቦችን ነጭ ጋዋን በማስለበስ በሆስፒታሎች ቅጥር ግቢ "ሁከት" እንዲፈጥሩ በማድረግ፣ እንዲሁም በሥራ ላይ በተገኙ የጤና ባለሙያዎች ላይ "ዛቻ" እና "ማስፈራሪያ" በመፈጸም ጭምር እንደተጠረጠሩ ጠቅሷል።

የፌደራል ፖሊስ በመጨረሻም፣ ሁከትና ብጥብጥ ለማስፋፋት በሚሞክሩ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ መውሰድ እንደሚቀጥል በማስጠንቀቂያ ገልጿል።
2025/07/09 01:23:15
Back to Top
HTML Embed Code: