Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
አሰላሙ አለይኩም ወረሕመቱሏሂ ወበረካቱህ
~
ይቺ እህታችን ዘህራ 0ብዱ ትባላለች። እኔም አውቃታለሁ። የደም ካንሰር በሽታ ታማሚ ናት። ህመሟ በፍጥነት እየተባባሰ ነው። ውጭ ሄዳ እንድትታከም ተነግሯታል። እስከ 6 ሚሌየን ለህክምናው የሚያስፈልግ ቢሆንም እስካሁን የተገኘው 800ሺ ብቻ ነዉ። እባካችሁ በምንችለው ብናግዛት ባረከላሁ ፊኩም።
አካውንት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000705606203
Kalid Mohammed
~
ይቺ እህታችን ዘህራ 0ብዱ ትባላለች። እኔም አውቃታለሁ። የደም ካንሰር በሽታ ታማሚ ናት። ህመሟ በፍጥነት እየተባባሰ ነው። ውጭ ሄዳ እንድትታከም ተነግሯታል። እስከ 6 ሚሌየን ለህክምናው የሚያስፈልግ ቢሆንም እስካሁን የተገኘው 800ሺ ብቻ ነዉ። እባካችሁ በምንችለው ብናግዛት ባረከላሁ ፊኩም።
አካውንት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
1000705606203
Kalid Mohammed
ክርስቲያን የሆነ ሰው ወደ ኢስላም ሲገባ የሚኖረው ዋጋ!
~
አይሁድና ክርስቲያኖች በኢስላም የመፅሐፍ ሰዎች (አህለል ኪታብ) በመባል ይታወቃሉ። በዚህ ስም የተጠሩበት ምክንያቱ እንደ ጥቅል ተውራት (ኦሪት) እና ኢንጂልን (ወንጌልን) በመቀበላቸው ነው። ተውራትና ኢንጂል ምንም እንኳ በዘመናት ሂደት ውስጥ የሰው እጅ ቢገባባቸውም የአላህ ታላላቅ ነቢያት ለሆኑት ሙሳ እና ዒሳ የተሰጡ መለኮታዊ መፃህፍት ናቸው። በዚህ የተነሳ ኢስላም ለአይሁድና ክርስቲያኖች ከሌሎች ሙስሊም ያልሆኑ ህዝቦች ይልቅ የተሻለ ቦታ ይሰጣል። ይሄ እውነታ የሚንፀባረቁባቸው የተለያዩ ጉዳዮች ሲኖሩ ከነዚህ ውስጥ አንዱ የምንዳ (ሽልማት) ጉዳይ ነው። አንድ አይሁድ ወይም ክርስቲያን የሆነ ሰው ወደ ኢስላም ሲገባ የሚኖረው የመልካም ስራ ሽልማት (ምንዳ) ከሌሎች በተለየ ሁለት እጥፍ ነው። ጌታችን አላህ ስለነሱ ባወሳበት መልእክት ላይ እንዲህ የሚል እናገኛለን፦
( أُولَئِكَ يُؤْتَوْنَ أَجْرَهُمْ مَرَّتَيْنِ بِمَا صَبَرُوا )
{እነዚያ በመታገሳቸው የተነሳ ዋጋቸውን ሁለት ጊዜ ይስሰጣሉ፡፡}
[አልቀሶስ፡ 52-54]
ነብዩ ሙሐመድም صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ "ሶስት አይነት ሰዎች የመልካም ስራቸውን ዋጋ ሁለት እጥፍ ነው የሚስሰጡት" ካሉ በኋላ አንዱ የጠቀሱት "የመፅሐፍ ሰዎች ከሆኑት ውስጥ ያመነ ነው" የሚል ነው። [ቡኻሪ፡ 3011] [ሙስሊም፡ 154]
በሌላ ንግግራቸውም ላይ እንዲህ ብለዋል፦
( مَنْ أَسْلَمَ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابَيْنِ فَلَهُ أَجْرُهُ مَرَّتَيْنِ ، وَلَهُ مَا لَنَا وَعَلَيْهِ مَا عَلَيْنَا )
"ከሁለቱ መፃህፍት ባለቤቶች ውስጥ የሰለመ ሰው ለሱ ሁለት ጊዜ ምንዳ አለው። ከዚያም ለኛ ያለን ለሱ አለው። በኛ ላይ ያለብንም በሱ ላይ አለበት።" [አሶሒሐ፡ 304]
በሃገራችን እውነቱን በሆነ መንገድ ካወቁ በኋላ ልባቸው መስለም እየፈለገ በቤተሰብ፣ በይሉኝታ፣ በተለያዩ ስጋቶች መወሰን አቅቷቸው እያመነቱ ሳይሰልሙ የሚቆዩ ብዙ ሰዎች አሉ። ግዴላችሁም ዛሬ ነገ አትበሉ። ሞት በቀጠሮ አይመጣም። ከፊት ለፊታችን ዘላለማዊ ህይወት አለ። ዛሬ ብትወስኑ በእጥፍ የምትሸለሙበትን እድል ብታሳልፉ ነገ መቋጫ የሌለው ፀፀት ይከተላችኋል። "ብልጥ ማለት ነፍሱን ተቆጣጥሮ ከሞት በኋላ ላለው (ህይወቱ) የሰራ ነው። ሰነፍ ማለት ነፍሱን ዝንባሌዋን እያስከተላት በአላህ ላይ አጉል የተመኘ ነው።"
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
አይሁድና ክርስቲያኖች በኢስላም የመፅሐፍ ሰዎች (አህለል ኪታብ) በመባል ይታወቃሉ። በዚህ ስም የተጠሩበት ምክንያቱ እንደ ጥቅል ተውራት (ኦሪት) እና ኢንጂልን (ወንጌልን) በመቀበላቸው ነው። ተውራትና ኢንጂል ምንም እንኳ በዘመናት ሂደት ውስጥ የሰው እጅ ቢገባባቸውም የአላህ ታላላቅ ነቢያት ለሆኑት ሙሳ እና ዒሳ የተሰጡ መለኮታዊ መፃህፍት ናቸው። በዚህ የተነሳ ኢስላም ለአይሁድና ክርስቲያኖች ከሌሎች ሙስሊም ያልሆኑ ህዝቦች ይልቅ የተሻለ ቦታ ይሰጣል። ይሄ እውነታ የሚንፀባረቁባቸው የተለያዩ ጉዳዮች ሲኖሩ ከነዚህ ውስጥ አንዱ የምንዳ (ሽልማት) ጉዳይ ነው። አንድ አይሁድ ወይም ክርስቲያን የሆነ ሰው ወደ ኢስላም ሲገባ የሚኖረው የመልካም ስራ ሽልማት (ምንዳ) ከሌሎች በተለየ ሁለት እጥፍ ነው። ጌታችን አላህ ስለነሱ ባወሳበት መልእክት ላይ እንዲህ የሚል እናገኛለን፦
( أُولَئِكَ يُؤْتَوْنَ أَجْرَهُمْ مَرَّتَيْنِ بِمَا صَبَرُوا )
{እነዚያ በመታገሳቸው የተነሳ ዋጋቸውን ሁለት ጊዜ ይስሰጣሉ፡፡}
[አልቀሶስ፡ 52-54]
ነብዩ ሙሐመድም صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ "ሶስት አይነት ሰዎች የመልካም ስራቸውን ዋጋ ሁለት እጥፍ ነው የሚስሰጡት" ካሉ በኋላ አንዱ የጠቀሱት "የመፅሐፍ ሰዎች ከሆኑት ውስጥ ያመነ ነው" የሚል ነው። [ቡኻሪ፡ 3011] [ሙስሊም፡ 154]
በሌላ ንግግራቸውም ላይ እንዲህ ብለዋል፦
( مَنْ أَسْلَمَ مِنْ أَهْلِ الْكِتَابَيْنِ فَلَهُ أَجْرُهُ مَرَّتَيْنِ ، وَلَهُ مَا لَنَا وَعَلَيْهِ مَا عَلَيْنَا )
"ከሁለቱ መፃህፍት ባለቤቶች ውስጥ የሰለመ ሰው ለሱ ሁለት ጊዜ ምንዳ አለው። ከዚያም ለኛ ያለን ለሱ አለው። በኛ ላይ ያለብንም በሱ ላይ አለበት።" [አሶሒሐ፡ 304]
በሃገራችን እውነቱን በሆነ መንገድ ካወቁ በኋላ ልባቸው መስለም እየፈለገ በቤተሰብ፣ በይሉኝታ፣ በተለያዩ ስጋቶች መወሰን አቅቷቸው እያመነቱ ሳይሰልሙ የሚቆዩ ብዙ ሰዎች አሉ። ግዴላችሁም ዛሬ ነገ አትበሉ። ሞት በቀጠሮ አይመጣም። ከፊት ለፊታችን ዘላለማዊ ህይወት አለ። ዛሬ ብትወስኑ በእጥፍ የምትሸለሙበትን እድል ብታሳልፉ ነገ መቋጫ የሌለው ፀፀት ይከተላችኋል። "ብልጥ ማለት ነፍሱን ተቆጣጥሮ ከሞት በኋላ ላለው (ህይወቱ) የሰራ ነው። ሰነፍ ማለት ነፍሱን ዝንባሌዋን እያስከተላት በአላህ ላይ አጉል የተመኘ ነው።"
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ሙስሊሞች ከዚህ ትምህርት ውሰዱ
~
እነሱ የሰው ጩኸት ለመቀማት ምንም አይነት ይሉኝታ የላቸውም። እንኳን ሙስሊሙ ላይ የደረሰውን ጥፋት ሊያምኑ ጭራሽ ከመስጊድ ውስጥ ሆነው ጥይት በተኮሱ የብልፅግና ሹሞች ህይወት ጠፍቶብናል እያለ ነው። የጥላቸውም፣ የንቀቱም ጥግ የት ድረስ እንደሆነ እንደሆነ ተመልከቱ።
"ጥላቻው ከአፎቻቸው በእርግጥ ገሀድ ወጣ። ልቦቻቸውም የሚደብቁት ይበልጥ ትልቅ ነው" ይላል ጀሊሉ። [ኣሉ ዒምራን፡ 118]
ሙስሊሞች ከዚህ ትምህርት ውሰዱ።
1- ሐቅ ይዛችሁ፣ ተበድላች አትሽኮርመሙ። እነሱ በዳይ ሆነውም እያፈሩ አይደለም።
2- ሁሉም የሚያውቀውን ሳምንት ያልሞላው ክስተት እንዲህ ሲሸመጥጡ ፣ የዘመናት ታሪክ እንዴት ሆኖ እንደሚፃፍ ማሰብ ነው።
3- የደረሰውን ነውረኛ ጥፋት አምነው ይቅርታ ይላሉ ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው። እንዲያውም እንደተበዳይ ነው እየተወኑ ያሉት። ይሄ ማለት በፈፀሙት አልረኩም ማለት ነው። ገና ብዙ ሊያደርጉ ይችላሉ ማለት ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
እነሱ የሰው ጩኸት ለመቀማት ምንም አይነት ይሉኝታ የላቸውም። እንኳን ሙስሊሙ ላይ የደረሰውን ጥፋት ሊያምኑ ጭራሽ ከመስጊድ ውስጥ ሆነው ጥይት በተኮሱ የብልፅግና ሹሞች ህይወት ጠፍቶብናል እያለ ነው። የጥላቸውም፣ የንቀቱም ጥግ የት ድረስ እንደሆነ እንደሆነ ተመልከቱ።
"ጥላቻው ከአፎቻቸው በእርግጥ ገሀድ ወጣ። ልቦቻቸውም የሚደብቁት ይበልጥ ትልቅ ነው" ይላል ጀሊሉ። [ኣሉ ዒምራን፡ 118]
ሙስሊሞች ከዚህ ትምህርት ውሰዱ።
1- ሐቅ ይዛችሁ፣ ተበድላች አትሽኮርመሙ። እነሱ በዳይ ሆነውም እያፈሩ አይደለም።
2- ሁሉም የሚያውቀውን ሳምንት ያልሞላው ክስተት እንዲህ ሲሸመጥጡ ፣ የዘመናት ታሪክ እንዴት ሆኖ እንደሚፃፍ ማሰብ ነው።
3- የደረሰውን ነውረኛ ጥፋት አምነው ይቅርታ ይላሉ ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው። እንዲያውም እንደተበዳይ ነው እየተወኑ ያሉት። ይሄ ማለት በፈፀሙት አልረኩም ማለት ነው። ገና ብዙ ሊያደርጉ ይችላሉ ማለት ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
"አማራ ክልል ኮሽ ሲል ብዙ ትጮሀላችሁ" የሚሉበትን በተደጋጋሚ እያየሁ ነው።
* መስጂድ ውስጥ እየገቡ ነፍስ ማጥፋት ነው ኮሽታ እየተባለ የሚገለፀው? ችግራችሁ ግን የጤና ወይስ የንቀት?
* አላማችሁስ ምንድነው? ብንገድልም ብናፈናቅልም አትናገሩን ነው? እና እናጨብጭብላችሁ? ወይስ ሽልማትም ያስፈልጋችኋል?
መቼስ እናንተ የግdያዎቹ ፈፃሚና ደጋፊ እንጂ ተቃዋሚ አይደላችሁም። እናንተ በተደጋጋሚ እንዳየነው ሟችን ነው ወንጀለኛ የምታደርጉት። እኛንም ዝም እንድንል ትወተውታላችሁ። ያሻንን ብንፈፅምም ማንም ኮሽታ እንዳያሰማ እያላችሁ እንደሆነ ግልፅ ነው። ነው ወይስ እንዳናስከፋችሁ በምን ያህል መጠን መቃወም እንዳለብን ፅፋችሁ ብትሰጡን ይሻላል?
እኔ የነዚህ ሰዎች ሁኔታ የሚገርመኝ ሁሉም ለማለት በሚቀርብ አንድ አይነት መሆናቸው ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
* መስጂድ ውስጥ እየገቡ ነፍስ ማጥፋት ነው ኮሽታ እየተባለ የሚገለፀው? ችግራችሁ ግን የጤና ወይስ የንቀት?
* አላማችሁስ ምንድነው? ብንገድልም ብናፈናቅልም አትናገሩን ነው? እና እናጨብጭብላችሁ? ወይስ ሽልማትም ያስፈልጋችኋል?
መቼስ እናንተ የግdያዎቹ ፈፃሚና ደጋፊ እንጂ ተቃዋሚ አይደላችሁም። እናንተ በተደጋጋሚ እንዳየነው ሟችን ነው ወንጀለኛ የምታደርጉት። እኛንም ዝም እንድንል ትወተውታላችሁ። ያሻንን ብንፈፅምም ማንም ኮሽታ እንዳያሰማ እያላችሁ እንደሆነ ግልፅ ነው። ነው ወይስ እንዳናስከፋችሁ በምን ያህል መጠን መቃወም እንዳለብን ፅፋችሁ ብትሰጡን ይሻላል?
እኔ የነዚህ ሰዎች ሁኔታ የሚገርመኝ ሁሉም ለማለት በሚቀርብ አንድ አይነት መሆናቸው ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የወለጋ ካርድ
~
የወለጋ ካርድ ያልኩት በአማራ አክቲቪስቶችና አጋፋሪዎቻቸው ክልሉ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችን የሚያጋልጡ ድምፆችን ለማፈን የሚጠቀሙበትን አፍ ማስያዣ ስልት ነው። እያንዳንዱ ሙስሊሞች ላይ የሚደርስ ጥቃት በተዘገበ ቁጥር "ወለጋ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ሲፈፀም የት ነበራችሁ?" ይላሉ።
* በጎንደር ሙስሊሞች ላይ የደረሰ ጥቃት ሲዘገብ "ወለጋ ..." ይላሉ።
* በባህርዳር ሙስሊሞች ላይ የተፈፀመ ግድያ ሲወራ ይህንኑ የወለጋ ካርድ ይመዛሉ።
* የሞጣ ግድያ ቢዘገብ "ወለጋ ..." ይላሉ።
* የእንፍራንዝ ደረሶች ግድያ ቢዘገብ የተለመደውን የወለጋ ካርድ ይመዛሉ።
በክልሉ ሙስሊሞች ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ መቆሚያ የለውም።
በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ግድያዎች፣ ዝርፊያዎች፣ እገታዎች፣ ማሳደዶች፣ መስጂዶችን ማቃጠል በተዘገቡ ቁጥር ያለ መታከት ይህንኑ ካርድ ይመዛሉ። ሂሳባቸው አጭር ነው። ወለጋ ላይ የደረሰው ጥቃት በቂ ሽፋን ስላልተሰጠው እኛ ስንገድልም፣ ስናፈናቅልም፣ ስናግትም፣ ስንዘርፍም ተቃውሞ ቀርቶ ኮሽታ ሊሰማ አይገባም ነው። እንዲያውም እንደ ተበዳይ ነው የሚተውኑት። "የኛ ማጥቃት ለምንድን ነው የሚራገበው? ደመ መራራ ነን። ነገር ይገንብናል" አይነት ነው ጨዋታው። "አማራ ክልል ኮሽ ሲል ይራገባል" ይላሉ። ያ ሁሉ በጎንደር፣ በደባርቅ፣ በእንፍራንዝ፣ በእስቴ ፣ በቢቸና፣ በሞጣ፣ በባህር ዳር፣ (ሰሞኑን ደግሞ በመካነ ሰላም) ... የደረሰው መስጂዶችን ማቃጠል፣ የበርካታ ሙስሊም ግድያ፣ እገታ፣ ... ሁሉ ያን ያህል ሊራገብ የማይገባው እንዲሁ ጢኒኒጥ ኮሽታ ብቻ ናት። መስጂድ እንደ ደመራ አንድደው መጨፈራቸው ራሱ እዚህ ግባ የማይባል ተራ ነገር ነው ፣ እንዲሁ ኮሽታ ብቻ። የትኛውም ነገር ይድረስ "አማራ ክልል ውስጥ ኮሽ ሲል... " እያሉ ጥቃቱን ተራ ኮሽታ አድርገው ነው የሚገልፁት። አላህ አናታቸው ኮሽ ያድርገውና።
ከዚያ እኛ ብንበድልም የወለጋው ከኛ ስለሚበልጥ የኛን ብዙም አታስጩሁት ነው የሚሉት። በክልሉ ሙስሊሞች ያነጣጠሩ ጥቃቶች በተዘገቡ ቁጥር ይህንን ካርድ መምዘዝን በቃ ንቃት አድርገውታል። አላማው የተቃውሞ ድምፆችን ማፈን ነው። ሳይወራ፣ ሳይዘገብ መፍጀት። በዚህ አይነት የማንሰማቸው ስንት በደሎች እንደሚኖሩ ማሰብ ይቻላል።
በነዚህ መሰሪዎች ለተሸወዳችሁ ሙስሊሞች ሁሉ! ለመሆኑ በደሉ ምን ሲደርስ ነው "አሁንስ በዛ!" የምትሉት? ነው ወይስ እንዲሁ እያሉ ሁሉንም በየተራ ቢጨርሱም አትነቁም? ለይቶ ማራገብ አለ ካላችሁ የጎደለውን በመሙላት ላይ ስሩ እንጂ በሙስሊም ደም ቁማር ለሚሰራ እባB ለምን ትወግናላችሁ? የኦሮሚያው ችግር ሽፋን ካላገኘ እናንተ ዘግቡት። "ለምን የኦሮሚያ ሲሆን ...?" የሚላችሁ ሲኖር ነው "ምነው የአማራ ብቻ..." የሚባለው። እንጂ እንዴት በዘር መሰላል ተንጠላጥላችሁ እምነታችሁን ለሚያረክስ፣ ወገኖቻችሁን ለይቶ ለሚያጠቃ አካል ጠበቃ ትሆናላችሁ?! ወላሂ ይሄ የሞኝነት ጥግ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 11/2016)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
የወለጋ ካርድ ያልኩት በአማራ አክቲቪስቶችና አጋፋሪዎቻቸው ክልሉ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችን የሚያጋልጡ ድምፆችን ለማፈን የሚጠቀሙበትን አፍ ማስያዣ ስልት ነው። እያንዳንዱ ሙስሊሞች ላይ የሚደርስ ጥቃት በተዘገበ ቁጥር "ወለጋ ውስጥ ሙስሊሞች ላይ ጥቃት ሲፈፀም የት ነበራችሁ?" ይላሉ።
* በጎንደር ሙስሊሞች ላይ የደረሰ ጥቃት ሲዘገብ "ወለጋ ..." ይላሉ።
* በባህርዳር ሙስሊሞች ላይ የተፈፀመ ግድያ ሲወራ ይህንኑ የወለጋ ካርድ ይመዛሉ።
* የሞጣ ግድያ ቢዘገብ "ወለጋ ..." ይላሉ።
* የእንፍራንዝ ደረሶች ግድያ ቢዘገብ የተለመደውን የወለጋ ካርድ ይመዛሉ።
በክልሉ ሙስሊሞች ላይ የሚደርሰው ሰቆቃ መቆሚያ የለውም።
በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች ሙስሊሞች ላይ ያነጣጠሩ ግድያዎች፣ ዝርፊያዎች፣ እገታዎች፣ ማሳደዶች፣ መስጂዶችን ማቃጠል በተዘገቡ ቁጥር ያለ መታከት ይህንኑ ካርድ ይመዛሉ። ሂሳባቸው አጭር ነው። ወለጋ ላይ የደረሰው ጥቃት በቂ ሽፋን ስላልተሰጠው እኛ ስንገድልም፣ ስናፈናቅልም፣ ስናግትም፣ ስንዘርፍም ተቃውሞ ቀርቶ ኮሽታ ሊሰማ አይገባም ነው። እንዲያውም እንደ ተበዳይ ነው የሚተውኑት። "የኛ ማጥቃት ለምንድን ነው የሚራገበው? ደመ መራራ ነን። ነገር ይገንብናል" አይነት ነው ጨዋታው። "አማራ ክልል ኮሽ ሲል ይራገባል" ይላሉ። ያ ሁሉ በጎንደር፣ በደባርቅ፣ በእንፍራንዝ፣ በእስቴ ፣ በቢቸና፣ በሞጣ፣ በባህር ዳር፣ (ሰሞኑን ደግሞ በመካነ ሰላም) ... የደረሰው መስጂዶችን ማቃጠል፣ የበርካታ ሙስሊም ግድያ፣ እገታ፣ ... ሁሉ ያን ያህል ሊራገብ የማይገባው እንዲሁ ጢኒኒጥ ኮሽታ ብቻ ናት። መስጂድ እንደ ደመራ አንድደው መጨፈራቸው ራሱ እዚህ ግባ የማይባል ተራ ነገር ነው ፣ እንዲሁ ኮሽታ ብቻ። የትኛውም ነገር ይድረስ "አማራ ክልል ውስጥ ኮሽ ሲል... " እያሉ ጥቃቱን ተራ ኮሽታ አድርገው ነው የሚገልፁት። አላህ አናታቸው ኮሽ ያድርገውና።
ከዚያ እኛ ብንበድልም የወለጋው ከኛ ስለሚበልጥ የኛን ብዙም አታስጩሁት ነው የሚሉት። በክልሉ ሙስሊሞች ያነጣጠሩ ጥቃቶች በተዘገቡ ቁጥር ይህንን ካርድ መምዘዝን በቃ ንቃት አድርገውታል። አላማው የተቃውሞ ድምፆችን ማፈን ነው። ሳይወራ፣ ሳይዘገብ መፍጀት። በዚህ አይነት የማንሰማቸው ስንት በደሎች እንደሚኖሩ ማሰብ ይቻላል።
በነዚህ መሰሪዎች ለተሸወዳችሁ ሙስሊሞች ሁሉ! ለመሆኑ በደሉ ምን ሲደርስ ነው "አሁንስ በዛ!" የምትሉት? ነው ወይስ እንዲሁ እያሉ ሁሉንም በየተራ ቢጨርሱም አትነቁም? ለይቶ ማራገብ አለ ካላችሁ የጎደለውን በመሙላት ላይ ስሩ እንጂ በሙስሊም ደም ቁማር ለሚሰራ እባB ለምን ትወግናላችሁ? የኦሮሚያው ችግር ሽፋን ካላገኘ እናንተ ዘግቡት። "ለምን የኦሮሚያ ሲሆን ...?" የሚላችሁ ሲኖር ነው "ምነው የአማራ ብቻ..." የሚባለው። እንጂ እንዴት በዘር መሰላል ተንጠላጥላችሁ እምነታችሁን ለሚያረክስ፣ ወገኖቻችሁን ለይቶ ለሚያጠቃ አካል ጠበቃ ትሆናላችሁ?! ወላሂ ይሄ የሞኝነት ጥግ ነው።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ሚያዚያ 11/2016)
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ahbash #07
Ibnu Munewor
ደርስ
~
• ኪታቡ፦ ዶላሉ ጀማዐቲል አሕባሽ
• ክፍል:- 7️⃣
• ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor/8025
• የእለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 21፦ الفصل السادس
~
• ኪታቡ፦ ዶላሉ ጀማዐቲል አሕባሽ
• ክፍል:- 7️⃣
• ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor/8025
• የእለቱ ደርስ መነሻ ገፅ 21፦ الفصل السادس
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የሙስሊሙ ህመም ያምሀል?
~
እንግዲያው በቁጭት ከምትብሰለሰል የድርሻህን ተወጣ።
1. ቢያንስ ቢያንስ ከራስህ ጀምሮ ቤተሰብህን በዲን፣ በስነ ምግባር ኮትኩት። አላማ እንዲሰንቁ አድርጋቸው። ቢቻል ከቤተሰብ አልፎ ሌሎችንም ለመለወጥ ጥረት እናድርግ።
2. ቅንጦትና ድሎት ቀንስ። አደጋ እንደተጋረጠበት ሰው አስብ። ትንሽም ቢሆን ወገንህን ለማጠንከር፣ ለማንቃት፣ ከመከራው ለማውጣት ትጋት ይኑርህ።
3. ከሱስ ራቅ። ጫትን ተፀየፍ። የእለት ቁጭቱን የሚተርክ እንጂ ለአላማው ቆራጥ የሆነ ሰው ከጫት ጋር አይርመጠመጥም። ሌሎችም ሱሶች ካሉ እንዲሁ።
4. ለዲንህ አስተዋጽኦ ይኑርህ። በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበት፣ ብዙ ማገዝ የምትችላቸው ነገሮች አሉ። ዋናው ቁም ነገር ከእንቅልፋችን ልንነቃ ይገባል።
5. ተማር፣ አስተምር፣ የሚማሩትን አግዝ። ትምህርት ትልቅ ጉልበት አለው።
6. ዘካ ትሰጣለህ? ካልሆነ ይሄ ሞት ነው። ከአምስቱ የኢስላምህ ምሰሶዎች አንዱን ንደህ፣ በዙሪያህ ያሉ ምስኪኖችን ሐቅ ነፍገህ ፣ ከዚያ ስለ ሙስሊም ወገኖችህ መገፋት ማውራት ሰከን ብሎ ለሚያይ ሰው ብዙም ስሜት አይሰጥም።
7. በኢኮኖሚ ለመጠንከር ታትረህ ስራ። ሌሎችንም ወደ ስራ እንዲገቡ አግዝ። መተዛዘን ይኑር። የመተጋገዝ፣ እጅ ለእጅ ተያይዞ የማደግን ስነ ልቦና እናዳብር። ሃብት በዚህ ዘመን ትልቅ ጉልበት ነው። ጉልበቱ ብዙ ትርጉም ያለው ነው።
ያያያዝኩት ምስል እንዲሁ ለቁጭት ያክል ነው፦
ንፅፅሩ በጀርመን እና በሀያ ሁለቱ የዐረብ ሊግ ሃገራት መካከል ነው። በያዝነው የፈረንጆቹ 2025 ዓ. ል
* የጀርመን ህዝብ ብዛት 84.4 ሚሊዮን ሲሆን፣ የዐረብ ሊግ ሃገራት ህዝብ ብዛት ደግሞ 478 ሚሊዮን አካባቢ ነው።
* በቆዳ ስፋት :- ጀርመን 357,582 ኪ.ሜ² ስትሆን፣ የዐረብ ሊግ ሃገራት ድምር ስፋት ደግሞ ~13.1 ሚሊዮን ኪ.ሜ² ነው።
* በኢኮኖሚስ? የጀርመን Nominal GDP $4.74 ትሪሊዮን ሲሆን፣ የጠቅላላው የዐረብ ሊግ ሃገራት GDP ደግሞ ~$3.55 ትሪሊዮን ነው።
በነዳጅ ዘይት እና በተፈጥሮ ጋዝ የታደሉት ሃገራት ድምር GDP ከአንዲት ጀርመን ያነሰ ነው። በዚያ ላይ የጀርመን ኢኮኖሚ ትልልቅ ማሽኖችን፣ ትልልቅ ተሽከርካሪዎችን፣ ኬሚካሎችን፣ ወዘተ. አምራች ነው። እውቀት ላይ፣ ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ነው። የዐረቡ ዓለምስ? በአብዛኛው የተፈጥሮ ሃብት ሽያጭ ላይ ጥገኛ ነው። ቴክኖሎጂ የለም። የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተጠቃሚ እንጂ አምራች አይደለም። ይሄ በኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በብዙ ማይል ገና ወደ ኋላ የቀረ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
እንግዲያው በቁጭት ከምትብሰለሰል የድርሻህን ተወጣ።
1. ቢያንስ ቢያንስ ከራስህ ጀምሮ ቤተሰብህን በዲን፣ በስነ ምግባር ኮትኩት። አላማ እንዲሰንቁ አድርጋቸው። ቢቻል ከቤተሰብ አልፎ ሌሎችንም ለመለወጥ ጥረት እናድርግ።
2. ቅንጦትና ድሎት ቀንስ። አደጋ እንደተጋረጠበት ሰው አስብ። ትንሽም ቢሆን ወገንህን ለማጠንከር፣ ለማንቃት፣ ከመከራው ለማውጣት ትጋት ይኑርህ።
3. ከሱስ ራቅ። ጫትን ተፀየፍ። የእለት ቁጭቱን የሚተርክ እንጂ ለአላማው ቆራጥ የሆነ ሰው ከጫት ጋር አይርመጠመጥም። ሌሎችም ሱሶች ካሉ እንዲሁ።
4. ለዲንህ አስተዋጽኦ ይኑርህ። በገንዘብ፣ በእውቀት፣ በጉልበት፣ ብዙ ማገዝ የምትችላቸው ነገሮች አሉ። ዋናው ቁም ነገር ከእንቅልፋችን ልንነቃ ይገባል።
5. ተማር፣ አስተምር፣ የሚማሩትን አግዝ። ትምህርት ትልቅ ጉልበት አለው።
6. ዘካ ትሰጣለህ? ካልሆነ ይሄ ሞት ነው። ከአምስቱ የኢስላምህ ምሰሶዎች አንዱን ንደህ፣ በዙሪያህ ያሉ ምስኪኖችን ሐቅ ነፍገህ ፣ ከዚያ ስለ ሙስሊም ወገኖችህ መገፋት ማውራት ሰከን ብሎ ለሚያይ ሰው ብዙም ስሜት አይሰጥም።
7. በኢኮኖሚ ለመጠንከር ታትረህ ስራ። ሌሎችንም ወደ ስራ እንዲገቡ አግዝ። መተዛዘን ይኑር። የመተጋገዝ፣ እጅ ለእጅ ተያይዞ የማደግን ስነ ልቦና እናዳብር። ሃብት በዚህ ዘመን ትልቅ ጉልበት ነው። ጉልበቱ ብዙ ትርጉም ያለው ነው።
ያያያዝኩት ምስል እንዲሁ ለቁጭት ያክል ነው፦
ንፅፅሩ በጀርመን እና በሀያ ሁለቱ የዐረብ ሊግ ሃገራት መካከል ነው። በያዝነው የፈረንጆቹ 2025 ዓ. ል
* የጀርመን ህዝብ ብዛት 84.4 ሚሊዮን ሲሆን፣ የዐረብ ሊግ ሃገራት ህዝብ ብዛት ደግሞ 478 ሚሊዮን አካባቢ ነው።
* በቆዳ ስፋት :- ጀርመን 357,582 ኪ.ሜ² ስትሆን፣ የዐረብ ሊግ ሃገራት ድምር ስፋት ደግሞ ~13.1 ሚሊዮን ኪ.ሜ² ነው።
* በኢኮኖሚስ? የጀርመን Nominal GDP $4.74 ትሪሊዮን ሲሆን፣ የጠቅላላው የዐረብ ሊግ ሃገራት GDP ደግሞ ~$3.55 ትሪሊዮን ነው።
በነዳጅ ዘይት እና በተፈጥሮ ጋዝ የታደሉት ሃገራት ድምር GDP ከአንዲት ጀርመን ያነሰ ነው። በዚያ ላይ የጀርመን ኢኮኖሚ ትልልቅ ማሽኖችን፣ ትልልቅ ተሽከርካሪዎችን፣ ኬሚካሎችን፣ ወዘተ. አምራች ነው። እውቀት ላይ፣ ቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ነው። የዐረቡ ዓለምስ? በአብዛኛው የተፈጥሮ ሃብት ሽያጭ ላይ ጥገኛ ነው። ቴክኖሎጂ የለም። የቴክኖሎጂ ውጤቶች ተጠቃሚ እንጂ አምራች አይደለም። ይሄ በኢኮኖሚ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ላይ በብዙ ማይል ገና ወደ ኋላ የቀረ እንደሆነ የሚያሳይ ነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from 𝐀𝐛𝐮 𝐒𝐮𝐟𝐲𝐚𝐧~𝐂𝐡𝐚𝐧𝐧𝐞𝐥
ታላቅ የምስራች በኬንቴሪ እና አካባቢዋ ለምትገኙ ወንድሞች እና እህቶች በሙሉ!
ለጀማሪዎች፤ከቃዒዳ ጀምሮ፣ነዘር፣ሂፍዝ እንድሁም ሀፍዘው ለጨረሱ ሙሉ ሙራጀዓህ ማሰማት
አቂዳ፣ተጅዊድ፣ፊቅህ፣ሲራ፣አዳብ
ለአዋቂዎች (ለወንዶች እና ለሴቶች):
ኬንቴሪ፣ ማማ መስጂድ ፊት ለፊት በሚያስገባው መንገድ ገባ ብሎ።
ስልክ: 0913291117 ወይም 0969688568
https://www.tg-me.com/MERKEZ_ABU_UBEYDAH
https://www.tg-me.com/ABUUBEYDAH_ALWAN
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ለዱዓት
~
የዝሙትን አስከፊነት እና መጠበቂያ ሰበቦችን አስመልክቶ በተለይ ለወጣቱ ደጋግሞ ማስተማር ላይ ትኩረት መስጠት ይገባል። ወጣቱ መሀል በጣም ደስ የማይሉ ነገሮች በብዛት አሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
የዝሙትን አስከፊነት እና መጠበቂያ ሰበቦችን አስመልክቶ በተለይ ለወጣቱ ደጋግሞ ማስተማር ላይ ትኩረት መስጠት ይገባል። ወጣቱ መሀል በጣም ደስ የማይሉ ነገሮች በብዛት አሉ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ለመስጂድ ኮሚቴዎች
~
መስጂዳችሁ ደርስ እና ደዕዋ ይሰጥበታል ወይ? የሰፈሩ ልጆች በተሻለ መልኩ ቁርኣን ለመቅራት የተመቻቸ ሁኔታ አላቸው ወይ? ወጣቱ አልባሌ ቦታ እንዳይውል ትኩረት አግኝቷል ወይ? ሴቶቻችንን ያማከለ ትምህርት አለ ወይ? በሰፈሩ እርዳታ የሚያሻቸውን አቅመ ደካሞች ተረባርቦ ለማገዝ የሚውልበት ጊዜ አለ ወይ?
መስጂድ ማለት ማህበረሰብን ለመለወጥ እጅግ ወሳኝ ቦታ ነው። ከሶላት ባሻገር እንደ ህዝብ ያሉብንን ፈተናዎች ለመወጣት የምንመካከርበት እጅግ ሁነኛ ቦታ ነው። የምንፈልገውን ግብ ለማሳካት የምንጥርበት ማዕከል ይሆን ዘንድ ግን የኮሚቴዎች ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። በዚህ ኃላፊነት ላይ ያላችሁ አካላት ለወገናችሁ ውለታ የምታውሉበት፣ ለኣኺራችሁ የምትሰሩበት ትልቅ እድል ነው እጃችሁ ላይ ያለው። እንደ ዋዛ አትመልከቱት። በክፋትም ይሁን በእዝህላልነት ኃላፊነታችሁን የማትወጡ ከሆነ ግን ለኣኺራችሁ ስትሉ ኃላፊነቱን ለሌሎች ለሚሰሩ አካላት ብትለቁ ይሻላችኋል።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
መስጂዳችሁ ደርስ እና ደዕዋ ይሰጥበታል ወይ? የሰፈሩ ልጆች በተሻለ መልኩ ቁርኣን ለመቅራት የተመቻቸ ሁኔታ አላቸው ወይ? ወጣቱ አልባሌ ቦታ እንዳይውል ትኩረት አግኝቷል ወይ? ሴቶቻችንን ያማከለ ትምህርት አለ ወይ? በሰፈሩ እርዳታ የሚያሻቸውን አቅመ ደካሞች ተረባርቦ ለማገዝ የሚውልበት ጊዜ አለ ወይ?
መስጂድ ማለት ማህበረሰብን ለመለወጥ እጅግ ወሳኝ ቦታ ነው። ከሶላት ባሻገር እንደ ህዝብ ያሉብንን ፈተናዎች ለመወጣት የምንመካከርበት እጅግ ሁነኛ ቦታ ነው። የምንፈልገውን ግብ ለማሳካት የምንጥርበት ማዕከል ይሆን ዘንድ ግን የኮሚቴዎች ቁርጠኝነት ያስፈልጋል። በዚህ ኃላፊነት ላይ ያላችሁ አካላት ለወገናችሁ ውለታ የምታውሉበት፣ ለኣኺራችሁ የምትሰሩበት ትልቅ እድል ነው እጃችሁ ላይ ያለው። እንደ ዋዛ አትመልከቱት። በክፋትም ይሁን በእዝህላልነት ኃላፊነታችሁን የማትወጡ ከሆነ ግን ለኣኺራችሁ ስትሉ ኃላፊነቱን ለሌሎች ለሚሰሩ አካላት ብትለቁ ይሻላችኋል።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
"መንግስት ድምፅ ያፍናል"፣ "ጋዜጠኞችን ያስራል"፣ "ሃሳብን የመግለፅ ነፃነት የለም" እያሉ የሚተቹ አካላት፣ የተቃወማቸውን ሁሉ "አራት ኪሎን ስንቆጣጠር እናሳያችኋለን!" እያሉ ግለሰቦች ላይ ብቻ ሳይሆን ድፍን ብሄር ላይ ሲዝቱ ማየት የሚገርም ነው። ከህወሓት ጋር በነበረው ጦርነት ጊዜም በጣም እየተጠጉ ሲመጡ እርምጃ የሚወሰድባቸው ሰዎች ብለው የስም ዝርዝር የሚለቁ ታጋዮች ነበሩ። በ1997 ምርጫ ቅስቀሳ ወቅት የተቃዋሚው ቅንጅት ፓርቲ ተወካይ ብርሃኑ ነጋ ገና ስልጣን ሳይዙ የሙስሊም ሴቶች አለባበስ ላይ ገደብ እንደሚያደርጉ የሰጠው ሃሳብ መነጋገሪያ ሆኖ ነበር። ግራ የሆነ 'ሜንታሊቲ!'
እዚች ሃገር ላይ በህዝብ ስም እየማለ መንግስትን የሚታገለው ሁላ ተረኛ ጨቋኝ ለመሆን እንጂ የተሻለ ስርአት ለመዘርጋት፣ ወገንን ከድህነት አረንቋ ለማውጣት፣ ለሃገር ሰላምና እድገት አልሞ አለመሆኑ የሚያሳዝን እውነታ ነው። "የኢትዮጵያ ህዝብ ጨቋኝን እንጅ ጭቆናን አይጠላም" የሚለው አባባል እውነትነት እንዳለው የሚያረጋግጡ ብዙ ምሳሌዎች ታይተዋል። እንዲያውም ዛሬ ላይ ቆመን ስናይ ጣልያንን ራሱ የተቃወሙት ለሃገር አስበው ነው ለማለት ያስጠረጥራል።
* ከስር ያያያዝኩት አይነት ዛቻዎች ከሰሞኑ በሰፊው ሲንሸራሸሩ ነበር። በርግጥ ከብዙ ደጋፊዎች ተመሳሳይ ሐሳብ ሲሰነዘር ስላየሁ እንጂ የቡድኑ እውነተኛ ፔጅ አይደለም።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
እዚች ሃገር ላይ በህዝብ ስም እየማለ መንግስትን የሚታገለው ሁላ ተረኛ ጨቋኝ ለመሆን እንጂ የተሻለ ስርአት ለመዘርጋት፣ ወገንን ከድህነት አረንቋ ለማውጣት፣ ለሃገር ሰላምና እድገት አልሞ አለመሆኑ የሚያሳዝን እውነታ ነው። "የኢትዮጵያ ህዝብ ጨቋኝን እንጅ ጭቆናን አይጠላም" የሚለው አባባል እውነትነት እንዳለው የሚያረጋግጡ ብዙ ምሳሌዎች ታይተዋል። እንዲያውም ዛሬ ላይ ቆመን ስናይ ጣልያንን ራሱ የተቃወሙት ለሃገር አስበው ነው ለማለት ያስጠረጥራል።
* ከስር ያያያዝኩት አይነት ዛቻዎች ከሰሞኑ በሰፊው ሲንሸራሸሩ ነበር። በርግጥ ከብዙ ደጋፊዎች ተመሳሳይ ሐሳብ ሲሰነዘር ስላየሁ እንጂ የቡድኑ እውነተኛ ፔጅ አይደለም።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
ለጦለበተል ዒልም
~
ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደምን ተጠቀሙባቸው። የምትችሉ በአካል እየተገኛችሁ፣ ካልቻላችሁ የተቀዱ ትምህርቶቻቸውን ብትከታተሉ ትጠቀማላችሁ ኢንሻአላህ።
ዱሩሶቻቸው የሚቀርቡበት የቴሌግራም ቻናል ይሄ ነው :-
ቴሌግራም - https://www.tg-me.com/Sheikhmuhammedzainadam
https://www.tg-me.com/SheikhMuhammedZainAdam
ሼር አድርጉት ባረከላሁ ፊኩም።
~
ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደምን ተጠቀሙባቸው። የምትችሉ በአካል እየተገኛችሁ፣ ካልቻላችሁ የተቀዱ ትምህርቶቻቸውን ብትከታተሉ ትጠቀማላችሁ ኢንሻአላህ።
ዱሩሶቻቸው የሚቀርቡበት የቴሌግራም ቻናል ይሄ ነው :-
ቴሌግራም - https://www.tg-me.com/Sheikhmuhammedzainadam
https://www.tg-me.com/SheikhMuhammedZainAdam
ሼር አድርጉት ባረከላሁ ፊኩም።
Forwarded from ●መርከዝ አቡ ሙሳ አል-አሽዐሪ●
መርከዝ አቡ ሙሳ አል አሽዓሪ የቁርኣን ሒፍዝ ማዕከል ለ2018 ዓ.ል የትምህርት ዘመን በ አዳሪና በተመላላሽ መርኃግብር ተማሪዎችን ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቆ በምዝገባ ላይ ይገኛል።
ጾታ፡ ለሁለቱም (ለወንድም ለሴትም)
እድሜ: ለወንድ ከ10 - 25 ዓመት
ለሴት ከ 10 አመት በላይ
ፆታ: ለሁለቱም
እድሜ: ከ 4 አመት በላይ ለሁሉም የእድሜ ክልል
+251913939993 /+251928844757
+251911119260 /+251930547776
https://www.tg-me.com/merkezabumussa1
https://www.tg-me.com/merkezabumussa1
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
Telegram
●መርከዝ አቡ ሙሳ አል-አሽዐሪ●
ለመርከዝ አቡ ሙሳ የቦታ ግዢ ገቢ ማሰባሰቢያ የተከፈቱ አካዉንቶች
Hijra :1008798290001
ZamZam: 0055632820101
Awash: 014381538447400
Commercial bank: 1000683751301
የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን ባንኮች እንድትጠቀሙ እናበረታታለን ።
ገቢ ማሰባሰቢያ ግሩፕ ⤵️
https://www.tg-me.com/merkezabumussa1
https://t.m
Hijra :1008798290001
ZamZam: 0055632820101
Awash: 014381538447400
Commercial bank: 1000683751301
የመጀመሪያዎቹን ሁለቱን ባንኮች እንድትጠቀሙ እናበረታታለን ።
ገቢ ማሰባሰቢያ ግሩፕ ⤵️
https://www.tg-me.com/merkezabumussa1
https://t.m
ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሷሊህ ኢብኑ ፈውዛን አል-ፈውዛን (አላህ ይጠብቃቸው) እንዲህ ይላሉ፦
"الله نهانا عن الجلوس مع القوم الظالمين، ومِن أظلم الظالمين دعاةُ الفتنة، لا تجلس معهم، لا تستمع لهم، لا تقل أنا أعرف، ولا يمكن لهم أن يخدعوني، لا، لا تُزكِّ نفسك، يا أخي".
"አላህ ከበደለኞች ሕዝቦች ጋር መቀመጥን ከልክሎናል። ከበደለኞች ሁሉ ደግሞ እጅግ በዳይ የሆኑት የፈተና (የብጥብጥ) ጠሪዎች ናቸው።
ከእነሱ ጋር አትቀመጥ። አትስማቸውም። 'እኔ አውቃለሁ፤ እነሱም ሊያታልሉኝ አይችሉም' አትበል። በፍጹም! ራስህን አታጥራራ፣ ወንድሜ ሆይ!"
በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የምንከተላቸው ወይም የምንጎዳኛቸው አካላት ዲናችንን የሚጎዱ፣ አመለካከታችን ላይ ተፅእኖ የሚያሳድሩ፣ ስነ ምግባርን የሚያበላሹ፣ በዘር የሚያናክሱ ከሆነ ዛሬ ነገ ሳንል እንራቃቸው። Unfriend, unfollow, unsubscribe, unlike እናድርግ። የሆነ የሚስብ ይዘት ቢኖራቸው እንኳ እሱን ስናስብ ሌላ ጉዳት እንዳንሸምት። ጎመን በጤና።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
"الله نهانا عن الجلوس مع القوم الظالمين، ومِن أظلم الظالمين دعاةُ الفتنة، لا تجلس معهم، لا تستمع لهم، لا تقل أنا أعرف، ولا يمكن لهم أن يخدعوني، لا، لا تُزكِّ نفسك، يا أخي".
"አላህ ከበደለኞች ሕዝቦች ጋር መቀመጥን ከልክሎናል። ከበደለኞች ሁሉ ደግሞ እጅግ በዳይ የሆኑት የፈተና (የብጥብጥ) ጠሪዎች ናቸው።
ከእነሱ ጋር አትቀመጥ። አትስማቸውም። 'እኔ አውቃለሁ፤ እነሱም ሊያታልሉኝ አይችሉም' አትበል። በፍጹም! ራስህን አታጥራራ፣ ወንድሜ ሆይ!"
በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ የምንከተላቸው ወይም የምንጎዳኛቸው አካላት ዲናችንን የሚጎዱ፣ አመለካከታችን ላይ ተፅእኖ የሚያሳድሩ፣ ስነ ምግባርን የሚያበላሹ፣ በዘር የሚያናክሱ ከሆነ ዛሬ ነገ ሳንል እንራቃቸው። Unfriend, unfollow, unsubscribe, unlike እናድርግ። የሆነ የሚስብ ይዘት ቢኖራቸው እንኳ እሱን ስናስብ ሌላ ጉዳት እንዳንሸምት። ጎመን በጤና።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
ወላጆች፣ ት/ቤቶች ጥንቃቄ አድርጉ
~
ሰው እያገቱ፣ ህፃናት እየሰረቁ ከፍተኛ መጠን ያለው ብር መጠየቅ በጣም የተንሰራፋ ባህል እየሆነ ነው። ሰላም ሲጠፋ፣ ጠንካራና አስተማሪ ቅጣት ሳይኖር ሲቀር የሰው ልጅ እንዲህ አይነት የተደበቀ አመሉን ያወጣል።
ብቻ ልጆቻችንን እንጠብቅ። ለራሳችንም ቢሆን አጉል ሰዓት ላይ ወይም ራቅ ያለ አካባቢ ብቻችንን አንጓዝ። እንዲሁ ሰበብ ለማድረስ ያህል እንጂ አንዳንድ አካባቢ ቤት ሰብረው፣ ተሳፋሪ አስወርደው ነው ሰው እያገቱ ያሉት። የሃገራችን ነገር እጅግ አሳዛኝ ደረጃ ደርሷል። አላህ ሰላማችንን ይመልስልን።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
ሰው እያገቱ፣ ህፃናት እየሰረቁ ከፍተኛ መጠን ያለው ብር መጠየቅ በጣም የተንሰራፋ ባህል እየሆነ ነው። ሰላም ሲጠፋ፣ ጠንካራና አስተማሪ ቅጣት ሳይኖር ሲቀር የሰው ልጅ እንዲህ አይነት የተደበቀ አመሉን ያወጣል።
ብቻ ልጆቻችንን እንጠብቅ። ለራሳችንም ቢሆን አጉል ሰዓት ላይ ወይም ራቅ ያለ አካባቢ ብቻችንን አንጓዝ። እንዲሁ ሰበብ ለማድረስ ያህል እንጂ አንዳንድ አካባቢ ቤት ሰብረው፣ ተሳፋሪ አስወርደው ነው ሰው እያገቱ ያሉት። የሃገራችን ነገር እጅግ አሳዛኝ ደረጃ ደርሷል። አላህ ሰላማችንን ይመልስልን።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
