መስጂዶችን ለቀብር አገልግሎት ማዋል
~
የመስጂድ ግቢዎች ለሶላት እና ሌሎች ዒባዳዎች የተዘጋጁ ቦታዎች ናቸው። እነዚህ ቦታዎች ለግለሰቦች መቀበሪያ ማዋል አይፈቀድም። ምክንያቱም የግለሰብ ንብረቶች አይደሉምና። ሌላው ቀርቶ ለመስጂድነት ወቅፍ ያደረገው አንድ ግለሰብ ቢሆን እንኳ ቦታው ወቅፍ ከተደረገ በኋላ ከሱ የግል ንብረትነት ይወጣል።
የመስጂድ ግቢዎች ደግሞ ለመስጂዱ ማስፋፊያ፣ የውዱእና መፀዳጃ ቦታዎች፣ ወዘተ ስለሚያስፈልጉ ቦታውን ለግለሰባዊ አገልግሎት ማዋል ይህንን መጋፋት ነው የሚሆነው።
በሌላ በኩል የመስጂድ ግቢዎችን ለቀብር አገልግሎት መጠቀም የሺርክ በር መክፈት ነው። ይህንን የሚያረጋግጡ ብዙ ማሳያዎች አሉ። ብዙዎች እንዲፈተኑበት፣ በሟቹ ላይ ድንበር እንዲያልፉ እና ከኢስላም ያፈነገጡ ተግባራት እንዲፈጽሙ ማመቻቸት ከጉዳት በስተቀር አንዳች ፋይዳ የለውም። ደግሞም አሁን ቀብር ከተጀመረ ዶሪሕ የመግገንባቱ እድል ሰፊ ነው።
ይሄ እንግዲህ መስጂድ ውስጥ ሳይሆን ግቢው ውስጥ መቅበርን በተመለከተ ነው። ከዚያም አልፎ ቀጥታ መስጂድ ውስጥ መቅበር ከተፈፀመ ጥፋቱ የከፋ የነብዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሐዲሥ የሚቃረን ተግባር ነው።
እንዲህ አይነት ጥፋት በጊዜ ማስቆም ካልተቻለ ሌሎች አካላት የሚከተሉት መጥፎ ሱና ነው የሚሆነው። ይሄ ተግባር በአንዳንድ ሃገራት እንዳለው መስጂዶች እና ግቢዎቻቸው በቀብር እንዲጥለቀለቁ በር ሊከፍት ይችላል።
ማሳሰቢያ፦
የነብዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቀብር ለተሳሳተ አካሄድ ማስረጃ የሚያደረጉ እንዳሉ ይታወቃል።
1. እሳቸው ከቤታቸው ውስጥ ነው የተቀበሩት። መስጂዱ ሲሰፋ ነው ባንድ ጣራ ስር የሆነው። ይህም ሆኖ በዘመኑ የነቀፉ ዓሊሞች ነበሩ።
2. ከቤታቸው የተቀበሩበትም ምክንያት አንደኛ ነብያት በሞቱበት ቦታ ስለሚቀበሩ ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ እናታችን ዓኢሻ እንደገለፀችው በቀብራቸው ላይ ሰዎች ድንበር አልፈው እንዳይፈተኑ ነው። ዛሬ ሰዎችን በመሳጂድ ግቢ ውስጥ መቅበር ግን እንዲያውም ሰዎችን እንዲፈተኑ ማመቻቸት ነው የሚሆነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
የመስጂድ ግቢዎች ለሶላት እና ሌሎች ዒባዳዎች የተዘጋጁ ቦታዎች ናቸው። እነዚህ ቦታዎች ለግለሰቦች መቀበሪያ ማዋል አይፈቀድም። ምክንያቱም የግለሰብ ንብረቶች አይደሉምና። ሌላው ቀርቶ ለመስጂድነት ወቅፍ ያደረገው አንድ ግለሰብ ቢሆን እንኳ ቦታው ወቅፍ ከተደረገ በኋላ ከሱ የግል ንብረትነት ይወጣል።
የመስጂድ ግቢዎች ደግሞ ለመስጂዱ ማስፋፊያ፣ የውዱእና መፀዳጃ ቦታዎች፣ ወዘተ ስለሚያስፈልጉ ቦታውን ለግለሰባዊ አገልግሎት ማዋል ይህንን መጋፋት ነው የሚሆነው።
በሌላ በኩል የመስጂድ ግቢዎችን ለቀብር አገልግሎት መጠቀም የሺርክ በር መክፈት ነው። ይህንን የሚያረጋግጡ ብዙ ማሳያዎች አሉ። ብዙዎች እንዲፈተኑበት፣ በሟቹ ላይ ድንበር እንዲያልፉ እና ከኢስላም ያፈነገጡ ተግባራት እንዲፈጽሙ ማመቻቸት ከጉዳት በስተቀር አንዳች ፋይዳ የለውም። ደግሞም አሁን ቀብር ከተጀመረ ዶሪሕ የመግገንባቱ እድል ሰፊ ነው።
ይሄ እንግዲህ መስጂድ ውስጥ ሳይሆን ግቢው ውስጥ መቅበርን በተመለከተ ነው። ከዚያም አልፎ ቀጥታ መስጂድ ውስጥ መቅበር ከተፈፀመ ጥፋቱ የከፋ የነብዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ሐዲሥ የሚቃረን ተግባር ነው።
እንዲህ አይነት ጥፋት በጊዜ ማስቆም ካልተቻለ ሌሎች አካላት የሚከተሉት መጥፎ ሱና ነው የሚሆነው። ይሄ ተግባር በአንዳንድ ሃገራት እንዳለው መስጂዶች እና ግቢዎቻቸው በቀብር እንዲጥለቀለቁ በር ሊከፍት ይችላል።
ማሳሰቢያ፦
የነብዩን ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ቀብር ለተሳሳተ አካሄድ ማስረጃ የሚያደረጉ እንዳሉ ይታወቃል።
1. እሳቸው ከቤታቸው ውስጥ ነው የተቀበሩት። መስጂዱ ሲሰፋ ነው ባንድ ጣራ ስር የሆነው። ይህም ሆኖ በዘመኑ የነቀፉ ዓሊሞች ነበሩ።
2. ከቤታቸው የተቀበሩበትም ምክንያት አንደኛ ነብያት በሞቱበት ቦታ ስለሚቀበሩ ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ እናታችን ዓኢሻ እንደገለፀችው በቀብራቸው ላይ ሰዎች ድንበር አልፈው እንዳይፈተኑ ነው። ዛሬ ሰዎችን በመሳጂድ ግቢ ውስጥ መቅበር ግን እንዲያውም ሰዎችን እንዲፈተኑ ማመቻቸት ነው የሚሆነው።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
መቃብር ላይ ቤት/ ዶሪሕ መገንባት
~
በኢትዮጵያም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታዋቂ ሰዎች መቃብር ላይ የተገነቡ ህልቆ መሳፍርት ዶሪሆች አሉ። ይሄ ተግባር አላዋቂ ሰዎች መቃብሮቹን እንዲያመልኳቸው በር ከፍቷል። ይሄ ደግሞ ችግሩ ተከስቶ ሲታይ ብቻ ሳይሆን ስጋት ሲኖር ራሱ ቀድመን በጥብቅ ልንተዋወስበት የሚገባ ጉዳይ ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል:-
اللَّهُمَّ لَا تَجْعَلْ قَبْرِي وَثَنًا يُعْبَدُ اشْتَدَّ غَضَبُ اللَّهِ عَلَى قَوْمٍ اتَّخَذُوا قُبُورَ أَنْبِيَائِهِمْ مَسَاجِدَ
{ጌታዬ ሆይ! ቀብሬን የሚመለክ ጣኦት አታድርገው። የነብዮቻቸውን መቃብር የአምልኮት ቦታዎች አድርገው የያዙ ሰዎች ላይ የአላህ እርግማን በረታ!} [ሚሽካቱል መሷቢሕ፡ 750]
ይህን ያሉት እነዚያዎቹ የሰሩት ጥፋት በሳቸው ቀብር ላይ እንዳይደገም ስለሰጉ ለማስጠንቀቅ ነው። ይሄ ባይሆን ኖሮ ቀብራቸው ውጭ ላይ በግላጭ ይሆን እንደነበር እናታችን ዓኢሻ - ረዲየላሁ ዐንሃ - ተናግራለች። [ቡኻሪ፡ 1390] [ሙስሊም፡ 529]
ሶሐቦች አደራቸውን ተወጥተዋል። የነብዩ ﷺ ቀብር የአምልኮት ቦታ እንዳይሆን በመስጋት ከሞቱበት ቤት ከጓዳቸው ቀብረዋቸዋል። ኢማም ኢብኑ ተይሚያ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦ “የነብዩ ﷺ ቀብር ምድር ላይ ካሉ ቀብሮች ሁሉ በላጭ ነው። ሆኖም ግን መመላለሻ ተደርጎ እንዳይያዝ ከልክለዋል። ስለዚህ ከሳቸው ቀብር ውጭ ያለው ማንም ይሁን ምን ይበልጥ ለክልከላ የተገባ ነው።” [አልኢቅቲዷእ፡ 2/172]
አንዳንዶች ግን የነብዩን ﷺ ኑዛዜ ጥሰው፣ አደራቸውን በልተው፣ አጥብቀው የከለከሉትን ጉዳይ በተቃራኒው አጥብቀው ያዘዙት በሚመስል ሁኔታ በታላላቅ ሰዎችና በሱፊያ ቁንጮዎች መቃብር ላይ ምን የመሳሰለ ቤት ይገነባሉ። ከዚያም የተለያዩ ሺርኮችን ለመፈፀም ቀብራቸው ዘንድ ይመላለሳሉ። ኢስላም ማለት የመቃብር አምልኮት ማለት እስከሚመስል ድረስ የሙስሊሙ አለም በዶሪሕ ተጥለቅልቋል።
በሶሪያ ደማስቆ ከተማ ውስጥ ብቻ መቶ ዘጠና አራት ዶሪሖች አሉ። ግብፅ ውስጥ ከስድስት ሺህ በላይ የሚመለኩ ዶሪሖች አሉ። በዒራቅ፣ በሱዳን፣ በሊቢያ፣ በህንድ፣ በፓኪስታን፣ በአፍጋኒስታን፣ በየመን፣ ... በሌሎችም የሙስሊም ሃገራት ያለው ነገር የከፋ እንጂ የተሻለ አይደለም።
የበለጠ የሚያሸማቅቀው ደግሞ ቀላል የማይባሉ ዶሪሖች ከነ ጭራሹ ቀብርም ሆነ የተቀበረ ነገር የሌላቸው ባዶ መሆናቸው ነው። ለምሳሌ የሑሰይን ጭንቅላት የተቀበረበት ነው ተብሎ ካይሮ ውስጥ እርድ የሚፈፀምበት፣ ስለት የሚቀረብበት፣ ጠዋፍ የሚደረግበት፣ ሌሎችም ዘግናኝ የሺርክ ተግባራት የሚፈፀሙበት ዶሪሕ አለ። በተመሳሳይ ሶሪያ ውስጥ ደማስቆና ሐለብ (አሌፖ) ከተማ አቅራቢያ የሑሰይን ዶሪሕ አለ። ምን ይሄ ብቻ! ዒራቅ ውስጥ ከርበላእና ነጀፍ ከተሞች ውስጥ የሑሰይን ዶሪሕ አለ። በ“እ $ራኤል” ስር ባለችው በፍልስጤማዊቷ የዐስቀላን ከተማም የሑሰይን ዶሪሕ ይገኛል። ይህ ሁሉ እንግዲህ የሑሰይን ጭንቅላት የተቀበረበት የሚባል ነው። ለመሆኑ ሑሰይን ስንት ጭንቅላት ነው የነበራቸው?
የዐሊይ ልጅ ዘይነብ የሞተችው መዲና የተቀበረችውም በቂዕ ነው። ነገር ግን ሶሪያ ደማስቆ ውስጥ እና ግብፅ ካይሮ ውስጥ በስሟ የተገነባ ዶሪሕ አለ። ግብፅ አሌክሳንድሪያ ከተማ ውስጥ የአቡ ደርዳእ ዶሪሕ አለ። ዓሊሞች ግን እርግጠኛ ሆነው እዚያ እንዳልተቀበሩ ይናገራሉ። ዐብዱረሕማን ብኑ ዐውፍ የተቀበሩት መዲና በቂዕ ውስጥ ነው። በዒራቋ የበስራ ከተማ ግን በስማቸው የተገነባ ዶሪሕ አለ። የነብዩ ﷺ ልጅ ሩቀያ የሞተችውም የተቀበረችውም መዲና ውስጥ ነው፣ ነብዩ በህይወት እያሉ። በሚገርም ሁኔታ ሶሪያ ውስጥም ግብፅ ውስጥም በስሟ ዶሪሕ አለ።
ወደ ሀገራችን ስንመጣም በተመሳሳይ በርካታ የታወቁ ሰዎች መቃብር በላያቸው ላይ ዶሪሕ ተገንብቶባቸዋል። ከዚያም ዶሪሑ ዘንድ የሚፈፀሙ ብዙ ዘግናኝ ሺርኮች አሉ። ይሄ ሁሉ ኢስላም የሚያዘው ነው ወይ? በፍፁም! መረጃውስ? አቡል ሀያጅ አል አሰዲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
قَالَ لِي عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ : أَلَا أَبْعَثُكَ عَلَى مَا بَعَثَنِي عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ ﷺ؟ ( ... وَلَا قَبْرًا مُشْرِفًا إِلَّا سَوَّيْتَهُ)
"0ሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ እንዲህ ብለውኛል፦ 'አላህ መልእክተኛ ﷺ በላኩብኝ አምሳያ አልክህምን? { ...ከፍ ያለ ቀብር አይተህ (ከሌሎች ቀብሮች ጋር እኩል) ሳታስተካክለው እንዳታልፍ!}' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 969]
ኢብኑ ዑመር - ረዲየላሁ ዐንሁማ - ከዐብዱረሕማን ቀብር ላይ ቤት ተሰርቶ ቢመለከቱ “አስወግደው አንተ ልጅ። የሚያጠልለው ስራው ነው” ብለዋል። [ተሕዚሩ ሳጂድ፡ 130]
ስለነዚህ ጉዳዮች የምንማማረው ወገናችን በሺርክ እንዳይፈተን በማሰብ ቀድሞ ለማስታወስ እንጂ አንዳንዶች እንደሚመስላችሁ ለእልህና ለብሽሽቅ አይደለም። ደግሞም ሁሉ ይቀበላል ብለን አንጠብቅም። ነገር ግን በኛ ላይ ያለው ሐቁን ማድረስ ብቻ ነው። እስትንፋሳችን እስካለ ድረስ ይህንን ማድረግ ይጠበቅብናል። አላህ ያለለት ለመረጃ እጅ ይሰጣል ኢንሻአላህ። በእልህ በመነሳሳት ብዙ ርቀት አልፈው ለሚሄዱት ወገኖቻችን በዚህ የአላህ ቃል ለማስታወስ እንሞክራለን፦
{ یَـٰۤأَیُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّمَا بَغۡیُكُمۡ عَلَىٰۤ أَنفُسِكُمۖ مَّتَـٰعَ ٱلۡحَیَوٰةِ ٱلدُّنۡیَاۖ ثُمَّ إِلَیۡنَا مَرۡجِعُكُمۡ فَنُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ }
"እናንተ ሰዎች ሆይ! ወሰን ማለፋችሁ (ጥፋቱ) በነፍሶቻችሁ ላይ ብቻ ነው። (እርሱም) የቅርቢቱ ሕይወት መጠቀሚያ ነው። ከዚያም መመለሻችሁ ወደኛ ነው። ትሠሩት የነበራችሁትንም ሁሉ እንነግራችኋለን።" [ዩኑስ፡ 23]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
በኢትዮጵያም ይሁን በዓለም አቀፍ ደረጃ በታዋቂ ሰዎች መቃብር ላይ የተገነቡ ህልቆ መሳፍርት ዶሪሆች አሉ። ይሄ ተግባር አላዋቂ ሰዎች መቃብሮቹን እንዲያመልኳቸው በር ከፍቷል። ይሄ ደግሞ ችግሩ ተከስቶ ሲታይ ብቻ ሳይሆን ስጋት ሲኖር ራሱ ቀድመን በጥብቅ ልንተዋወስበት የሚገባ ጉዳይ ነው። ነብያችን ﷺ እንዲህ ብለዋል:-
اللَّهُمَّ لَا تَجْعَلْ قَبْرِي وَثَنًا يُعْبَدُ اشْتَدَّ غَضَبُ اللَّهِ عَلَى قَوْمٍ اتَّخَذُوا قُبُورَ أَنْبِيَائِهِمْ مَسَاجِدَ
{ጌታዬ ሆይ! ቀብሬን የሚመለክ ጣኦት አታድርገው። የነብዮቻቸውን መቃብር የአምልኮት ቦታዎች አድርገው የያዙ ሰዎች ላይ የአላህ እርግማን በረታ!} [ሚሽካቱል መሷቢሕ፡ 750]
ይህን ያሉት እነዚያዎቹ የሰሩት ጥፋት በሳቸው ቀብር ላይ እንዳይደገም ስለሰጉ ለማስጠንቀቅ ነው። ይሄ ባይሆን ኖሮ ቀብራቸው ውጭ ላይ በግላጭ ይሆን እንደነበር እናታችን ዓኢሻ - ረዲየላሁ ዐንሃ - ተናግራለች። [ቡኻሪ፡ 1390] [ሙስሊም፡ 529]
ሶሐቦች አደራቸውን ተወጥተዋል። የነብዩ ﷺ ቀብር የአምልኮት ቦታ እንዳይሆን በመስጋት ከሞቱበት ቤት ከጓዳቸው ቀብረዋቸዋል። ኢማም ኢብኑ ተይሚያ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦ “የነብዩ ﷺ ቀብር ምድር ላይ ካሉ ቀብሮች ሁሉ በላጭ ነው። ሆኖም ግን መመላለሻ ተደርጎ እንዳይያዝ ከልክለዋል። ስለዚህ ከሳቸው ቀብር ውጭ ያለው ማንም ይሁን ምን ይበልጥ ለክልከላ የተገባ ነው።” [አልኢቅቲዷእ፡ 2/172]
አንዳንዶች ግን የነብዩን ﷺ ኑዛዜ ጥሰው፣ አደራቸውን በልተው፣ አጥብቀው የከለከሉትን ጉዳይ በተቃራኒው አጥብቀው ያዘዙት በሚመስል ሁኔታ በታላላቅ ሰዎችና በሱፊያ ቁንጮዎች መቃብር ላይ ምን የመሳሰለ ቤት ይገነባሉ። ከዚያም የተለያዩ ሺርኮችን ለመፈፀም ቀብራቸው ዘንድ ይመላለሳሉ። ኢስላም ማለት የመቃብር አምልኮት ማለት እስከሚመስል ድረስ የሙስሊሙ አለም በዶሪሕ ተጥለቅልቋል።
በሶሪያ ደማስቆ ከተማ ውስጥ ብቻ መቶ ዘጠና አራት ዶሪሖች አሉ። ግብፅ ውስጥ ከስድስት ሺህ በላይ የሚመለኩ ዶሪሖች አሉ። በዒራቅ፣ በሱዳን፣ በሊቢያ፣ በህንድ፣ በፓኪስታን፣ በአፍጋኒስታን፣ በየመን፣ ... በሌሎችም የሙስሊም ሃገራት ያለው ነገር የከፋ እንጂ የተሻለ አይደለም።
የበለጠ የሚያሸማቅቀው ደግሞ ቀላል የማይባሉ ዶሪሖች ከነ ጭራሹ ቀብርም ሆነ የተቀበረ ነገር የሌላቸው ባዶ መሆናቸው ነው። ለምሳሌ የሑሰይን ጭንቅላት የተቀበረበት ነው ተብሎ ካይሮ ውስጥ እርድ የሚፈፀምበት፣ ስለት የሚቀረብበት፣ ጠዋፍ የሚደረግበት፣ ሌሎችም ዘግናኝ የሺርክ ተግባራት የሚፈፀሙበት ዶሪሕ አለ። በተመሳሳይ ሶሪያ ውስጥ ደማስቆና ሐለብ (አሌፖ) ከተማ አቅራቢያ የሑሰይን ዶሪሕ አለ። ምን ይሄ ብቻ! ዒራቅ ውስጥ ከርበላእና ነጀፍ ከተሞች ውስጥ የሑሰይን ዶሪሕ አለ። በ“እ $ራኤል” ስር ባለችው በፍልስጤማዊቷ የዐስቀላን ከተማም የሑሰይን ዶሪሕ ይገኛል። ይህ ሁሉ እንግዲህ የሑሰይን ጭንቅላት የተቀበረበት የሚባል ነው። ለመሆኑ ሑሰይን ስንት ጭንቅላት ነው የነበራቸው?
የዐሊይ ልጅ ዘይነብ የሞተችው መዲና የተቀበረችውም በቂዕ ነው። ነገር ግን ሶሪያ ደማስቆ ውስጥ እና ግብፅ ካይሮ ውስጥ በስሟ የተገነባ ዶሪሕ አለ። ግብፅ አሌክሳንድሪያ ከተማ ውስጥ የአቡ ደርዳእ ዶሪሕ አለ። ዓሊሞች ግን እርግጠኛ ሆነው እዚያ እንዳልተቀበሩ ይናገራሉ። ዐብዱረሕማን ብኑ ዐውፍ የተቀበሩት መዲና በቂዕ ውስጥ ነው። በዒራቋ የበስራ ከተማ ግን በስማቸው የተገነባ ዶሪሕ አለ። የነብዩ ﷺ ልጅ ሩቀያ የሞተችውም የተቀበረችውም መዲና ውስጥ ነው፣ ነብዩ በህይወት እያሉ። በሚገርም ሁኔታ ሶሪያ ውስጥም ግብፅ ውስጥም በስሟ ዶሪሕ አለ።
ወደ ሀገራችን ስንመጣም በተመሳሳይ በርካታ የታወቁ ሰዎች መቃብር በላያቸው ላይ ዶሪሕ ተገንብቶባቸዋል። ከዚያም ዶሪሑ ዘንድ የሚፈፀሙ ብዙ ዘግናኝ ሺርኮች አሉ። ይሄ ሁሉ ኢስላም የሚያዘው ነው ወይ? በፍፁም! መረጃውስ? አቡል ሀያጅ አል አሰዲይ - ረሒመሁላህ - እንዲህ ይላሉ፦
قَالَ لِي عَلِيُّ بْنُ أَبِي طَالِبٍ : أَلَا أَبْعَثُكَ عَلَى مَا بَعَثَنِي عَلَيْهِ رَسُولُ اللهِ ﷺ؟ ( ... وَلَا قَبْرًا مُشْرِفًا إِلَّا سَوَّيْتَهُ)
"0ሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ እንዲህ ብለውኛል፦ 'አላህ መልእክተኛ ﷺ በላኩብኝ አምሳያ አልክህምን? { ...ከፍ ያለ ቀብር አይተህ (ከሌሎች ቀብሮች ጋር እኩል) ሳታስተካክለው እንዳታልፍ!}' " [ሶሒሕ ሙስሊም፡ 969]
ኢብኑ ዑመር - ረዲየላሁ ዐንሁማ - ከዐብዱረሕማን ቀብር ላይ ቤት ተሰርቶ ቢመለከቱ “አስወግደው አንተ ልጅ። የሚያጠልለው ስራው ነው” ብለዋል። [ተሕዚሩ ሳጂድ፡ 130]
ስለነዚህ ጉዳዮች የምንማማረው ወገናችን በሺርክ እንዳይፈተን በማሰብ ቀድሞ ለማስታወስ እንጂ አንዳንዶች እንደሚመስላችሁ ለእልህና ለብሽሽቅ አይደለም። ደግሞም ሁሉ ይቀበላል ብለን አንጠብቅም። ነገር ግን በኛ ላይ ያለው ሐቁን ማድረስ ብቻ ነው። እስትንፋሳችን እስካለ ድረስ ይህንን ማድረግ ይጠበቅብናል። አላህ ያለለት ለመረጃ እጅ ይሰጣል ኢንሻአላህ። በእልህ በመነሳሳት ብዙ ርቀት አልፈው ለሚሄዱት ወገኖቻችን በዚህ የአላህ ቃል ለማስታወስ እንሞክራለን፦
{ یَـٰۤأَیُّهَا ٱلنَّاسُ إِنَّمَا بَغۡیُكُمۡ عَلَىٰۤ أَنفُسِكُمۖ مَّتَـٰعَ ٱلۡحَیَوٰةِ ٱلدُّنۡیَاۖ ثُمَّ إِلَیۡنَا مَرۡجِعُكُمۡ فَنُنَبِّئُكُم بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ }
"እናንተ ሰዎች ሆይ! ወሰን ማለፋችሁ (ጥፋቱ) በነፍሶቻችሁ ላይ ብቻ ነው። (እርሱም) የቅርቢቱ ሕይወት መጠቀሚያ ነው። ከዚያም መመለሻችሁ ወደኛ ነው። ትሠሩት የነበራችሁትንም ሁሉ እንነግራችኋለን።" [ዩኑስ፡ 23]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
حقيقة المراقبة في السر والعلن
الشيخ أنيس المهندس اليافعي
📖 العنوان: حقيقة المراقبة في السر والعلن
محاضرة علميَّة نافعة عبر البث المباشر على تيليجرام، موجَّهة إلى طلاب العلم في بلاد الحبشة
🎙ألقاها فضيلة الشيخ: أبي عبدالرحمن أنيس المهندس اليافعي -حفظه الله تعالى-
🗓 يوم السبت بتاريخ ٢٦ ربيع الآخر ١٤٤٧هـ
وقد تولّى الترجمة الفورية إلى اللغة الأمهرية الأستاذ أبو العباس – وفّقه الله –
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/wmzxbn
محاضرة علميَّة نافعة عبر البث المباشر على تيليجرام، موجَّهة إلى طلاب العلم في بلاد الحبشة
🎙ألقاها فضيلة الشيخ: أبي عبدالرحمن أنيس المهندس اليافعي -حفظه الله تعالى-
🗓 يوم السبت بتاريخ ٢٦ ربيع الآخر ١٤٤٧هـ
وقد تولّى الترجمة الفورية إلى اللغة الأمهرية الأستاذ أبو العباس – وفّقه الله –
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/wmzxbn
ብዙ ክርስቲያኖች ወሃቢያ ወሃቢያ እያሉ ነው። ለምን በማያገባችሁ የሙስሊሞች የውስጥ ጉዳይ ትገባላችሁ? መካነ ሰላም ውስጥ ኢማም እና ሙአዚኑን ጨምሮ አራት ሙስሊሞች በመስጂዳቸው ውስጥ ከተ7ደሉኮ ገና ወር እንኳ አልሞላቸውም። ያኔ የነበረው ድምፅ ዛሬ ከምናየው ፍፁም የተለየ ነበር። "ይቺ ጩኸት ከፍየሏ በላይ ናት!"
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from قناة دروس فضيلة الشيخ محمد زين بن آدم الحبشي - Sheikh Muhammed Zain Adam - ሸይኽ ሙሐመድ ዘይን ኣደም (عبد السلام عبد الله)
የተውሒድ ጉዳይ ለሚያሳስባችሁ ሁሉ!
~
የማንም ጩኸት ሳይበግራችሁ መሬት የረገጠ ስራ አጥብቃችሁ ስሩ። የተውሒድ ሙቱኖችን በስፋት ማስቀራት፣ በተውሒድ ርእስ ላይ ደጋግሞ ደዕዋ ማድረግ፣ መሳጂዶችን፣ የማህበራዊ መገናኛዎች ፕላትፎርሞችን፣ መራኪዞችን በሚገባ መጠቀም ያስፈልጋል። በድምፅ፣ በፅሁፍ፣ በራሳችንም፣ የሌሎችንም በማሰራጨት በሁሉም አይነት መንገዶች ሰሞንኛ ሆይ ሆይታ ሳይሆን ዘላቂነት ያለው ስራ እንስራ። አንዳንድ ጩኸቶች ማንቂያ ደወል ሊሆኑን ይገባል። እንጂ ፈፅሞ ለአሕባሽና መሰሎቻቸው ግርግር የምንደናገጥ ልፍስፍሶች ልንሆን አይገባም። የተውሒድ ዳዒያህ የኹራፋት እና የኹራፊዮች ግርግር የማያስደናብረው ጀግና ሊሆን ይገባል። ጀግና ማለት ለፈተና ሳይደነግጥ እንደ አለት የሚፀና ነው። ወደፊት ብቻ!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
የማንም ጩኸት ሳይበግራችሁ መሬት የረገጠ ስራ አጥብቃችሁ ስሩ። የተውሒድ ሙቱኖችን በስፋት ማስቀራት፣ በተውሒድ ርእስ ላይ ደጋግሞ ደዕዋ ማድረግ፣ መሳጂዶችን፣ የማህበራዊ መገናኛዎች ፕላትፎርሞችን፣ መራኪዞችን በሚገባ መጠቀም ያስፈልጋል። በድምፅ፣ በፅሁፍ፣ በራሳችንም፣ የሌሎችንም በማሰራጨት በሁሉም አይነት መንገዶች ሰሞንኛ ሆይ ሆይታ ሳይሆን ዘላቂነት ያለው ስራ እንስራ። አንዳንድ ጩኸቶች ማንቂያ ደወል ሊሆኑን ይገባል። እንጂ ፈፅሞ ለአሕባሽና መሰሎቻቸው ግርግር የምንደናገጥ ልፍስፍሶች ልንሆን አይገባም። የተውሒድ ዳዒያህ የኹራፋት እና የኹራፊዮች ግርግር የማያስደናብረው ጀግና ሊሆን ይገባል። ጀግና ማለት ለፈተና ሳይደነግጥ እንደ አለት የሚፀና ነው። ወደፊት ብቻ!
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#ማነው_ተKፊሩ?
#ክፍል_1
ኢብኑ ተይሚያ እና ኢብኑል ቀይም ሙስሊሞች አይደሉም ይላል ይሄ አሕ ^ ባሽ። እነዚህና መሰሎቻቸው ናቸው እንግዲህ ስለ አደብ ሊሰብኩ የሚሞክሩት። "ጅ^ብ የማያውቁት ሃገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ።"
በደንብ "ሼር" እያደረጋችሁ ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
#ክፍል_1
ኢብኑ ተይሚያ እና ኢብኑል ቀይም ሙስሊሞች አይደሉም ይላል ይሄ አሕ ^ ባሽ። እነዚህና መሰሎቻቸው ናቸው እንግዲህ ስለ አደብ ሊሰብኩ የሚሞክሩት። "ጅ^ብ የማያውቁት ሃገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ አለ።"
በደንብ "ሼር" እያደረጋችሁ ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Forwarded from ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ.. እና አካባቢዋ 《ፈትህ መስጂድ》
بسم الله الرحمان الرحيم
በ2018 E.C ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ!!!
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
በአላህ ፈቃድ በ 2017 ዓ.ል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና እና የሪሚዲያል ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ በ2018 ዓ.ል ዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ላደረጋችሁ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ እንኳ ደስ አላችሁ እያልን እነሆ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እናንተን ለመቀበል ዝግጅቱ አጠናቆ እናንተን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል :: በመቀጠልም ዩኒቨርስቲያችን የተማሪዎች ቅበላ መርሃ ግብር ከጥቅምት (21-22) 2018 ዓ.ል መሆኑ ይታወቃል በእለቱ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረትም (ጀመዐም) ደማቅ አቀባበል የሚያደርግላችሁ ይሆናል :: እናንተም ውድ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ማንነታችሁን(ሙስሊም መሆናችሁን) ለማሳወቅ የቀና ትብብራችሁን በአክብሮት እንጠይቃለን:: #እንዲሁም _ከምናደርግላችሁ_መስተግዶዎች_ከዩኒቨርሲቲው_ማህበርሰብ_ጋር_ማስተዋወቅ_እና_የሚያስፈልጓችሁን_ነገሮች_ሁሉ_ማሟላት ይሆናል ።ይህንንም የምናረግበት ምክንያት፡-
1. ኢስላማዊ ወንድማማችነትን ለማጠናከር፤ እና ሸሪአችን እንግዶቻችንን እንድናከብር ስለሚያዘን
2.ዲንን ለመርዳት እና የሙስሊሞችን ችግሮች በጋራ ለመቀነስ /ለመዋጋት።
3.ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ አካባቢ ላይ ካሉ ከዲን እና ከዱንያ እጭበርባሪዎች እናንተን ለመታደግ ነዉ ::
~ ~~
🤳የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች (ተማሪዎችን ለመቀበል የተወከሉ)ስልክ ቁጥር 📱📲፡-
#1_ወንድም አብዱረሺድ ሙሀመድ
0918742346
#2_ወንድም አብዱረህማን አህመድ
0916263025
#3_ወንድም ዑመር ሙደሲር
0935251136
#4_ወንድም ቢላል ተማም
0953328296
#5_ወንድም ሙባረክ ምስጋናው
0922817219
#4_ወንድም ኸይረዲን ሻፊ
0904846672
#5_ወንድም በድሩ ሁሴን
0979874293
⏭አማርኛ ለምትቸገሩ ጉራጌ እና ስልጤ ወንድሞች🫛
#7_ወንድም ሃያቱ ነስሩ
0904366714
#8_ወንድም አሊ ሙሀመድ
0987247510
#9_ወንድም ቶፊቅ ሱሩር
0905060964
⤴⤴⤴⤴⤴⤴⤴⤴
#For all affaan oromo language speakers who can't speak Amharic fluently.
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
#9_ወንድም ሙሳ አህመድ
0941486725
#10_ ወንድም ቤካም ገመዳ
0964106353
ማሳሰቢያ:-
#1.የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ [ሰለፊይ ] ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ ከዚህ በታች ካሉት የቴሌግራም ቻናል እና ግሩፕ ውጪ ምንም አይነት የሚዲያ ቻናል የለውም !!!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🫛የወ.ሶ.ዩ.ሙስሊም(ሰለፍዮች) ተማሪዎች ጀመዐ... (Wolaita sodo university Muslim(Selefyoch) students jemea')
https://www.tg-me.com/WSU_Muslim1SelefyStudents/2263
⬆⬆⬆
#2.የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ [ሰለፊይ ] ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ ፈትሕ መስጂድ መሆኑን አትርሱ !!!
#3.ለማንኛውም ተማሪ ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለሚመጡ ይህንን መልዕክት ማሰራጨትን እንዳይረሱ!!!
#4. ማንነታችውን ደብቀው እሚንቀሳቀሱ የዲን አጭበርባሪዎች ስላሉ አቅማችሁ በፈቀደው ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግን እንዳትረሱ !!
#5 በዩንቨርሲቲያችን የተማሪዎች የቅበላ መርሃ- ግብር ወቅት ዩንቨርሲቲው ደርሳችሁ ከትራንስፖርት ስትወርዱ ካላይ በቅደም ተከተል ስማቸው ከነ-ስልክ ቁጥራቸው የተዘረዘሩት ወንድሞች ጋር በመደወል እነሱ እንዲቀበሉዋቹ አልያም በነሱ በኩል ሌሎች ወንድሞች እንዲመድቡላችሁ መጠየቅን እንዳትረሱ!!
#6.አድራሻ ከቴክኖ ካምፓስ ፊት ለፊት የተማሪዎች መስጂድ ብለው ቢጠይቁ ማንም ሰው ይነግሮታል የዲን አጭበርባሪዎች ሲቀሩ !!!
#7.የሙስሊም ሴት እህቶቻችንን ስልክ ለምትፈልጉ ሙስሊም ሴት እህቶች ወንድም በድሩ ሁሴን(0979874293) እና ወንድም አብዱረሺድ ሙሀመድ (0918742346) በኩል ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ፤ እንዲሁም affaan oromo ዐብዱልሐኪም ከድር(0909879173)።
✍የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ ተወካይ
ሃያቱ ሸረፋ : 0936780125
#share
#Share
#share and
#Join
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/WSU_Muslim1SelefyStudents/2263
⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐
በ2018 E.C ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ለተመደባችሁ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ!!!
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
በአላህ ፈቃድ በ 2017 ዓ.ል የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና እና የሪሚዲያል ፈተና ወስዳችሁ ማለፊያ ውጤት አምጥታችሁ በ2018 ዓ.ል ዩኒቨርስቲ ምርጫችሁን ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ላደረጋችሁ ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ እንኳ ደስ አላችሁ እያልን እነሆ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እናንተን ለመቀበል ዝግጅቱ አጠናቆ እናንተን በመጠባበቅ ላይ ይገኛል :: በመቀጠልም ዩኒቨርስቲያችን የተማሪዎች ቅበላ መርሃ ግብር ከጥቅምት (21-22) 2018 ዓ.ል መሆኑ ይታወቃል በእለቱ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረትም (ጀመዐም) ደማቅ አቀባበል የሚያደርግላችሁ ይሆናል :: እናንተም ውድ አዲስ ገቢ ተማሪዎች ማንነታችሁን(ሙስሊም መሆናችሁን) ለማሳወቅ የቀና ትብብራችሁን በአክብሮት እንጠይቃለን:: #እንዲሁም _ከምናደርግላችሁ_መስተግዶዎች_ከዩኒቨርሲቲው_ማህበርሰብ_ጋር_ማስተዋወቅ_እና_የሚያስፈልጓችሁን_ነገሮች_ሁሉ_ማሟላት ይሆናል ።ይህንንም የምናረግበት ምክንያት፡-
1. ኢስላማዊ ወንድማማችነትን ለማጠናከር፤ እና ሸሪአችን እንግዶቻችንን እንድናከብር ስለሚያዘን
2.ዲንን ለመርዳት እና የሙስሊሞችን ችግሮች በጋራ ለመቀነስ /ለመዋጋት።
3.ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ አካባቢ ላይ ካሉ ከዲን እና ከዱንያ እጭበርባሪዎች እናንተን ለመታደግ ነዉ ::
~ ~~
🤳የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች (ተማሪዎችን ለመቀበል የተወከሉ)ስልክ ቁጥር 📱📲፡-
#1_ወንድም አብዱረሺድ ሙሀመድ
0918742346
#2_ወንድም አብዱረህማን አህመድ
0916263025
#3_ወንድም ዑመር ሙደሲር
0935251136
#4_ወንድም ቢላል ተማም
0953328296
#5_ወንድም ሙባረክ ምስጋናው
0922817219
#4_ወንድም ኸይረዲን ሻፊ
0904846672
#5_ወንድም በድሩ ሁሴን
0979874293
⏭አማርኛ ለምትቸገሩ ጉራጌ እና ስልጤ ወንድሞች🫛
#7_ወንድም ሃያቱ ነስሩ
0904366714
#8_ወንድም አሊ ሙሀመድ
0987247510
#9_ወንድም ቶፊቅ ሱሩር
0905060964
⤴⤴⤴⤴⤴⤴⤴⤴
#For all affaan oromo language speakers who can't speak Amharic fluently.
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
#9_ወንድም ሙሳ አህመድ
0941486725
#10_ ወንድም ቤካም ገመዳ
0964106353
ማሳሰቢያ:-
#1.የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ [ሰለፊይ ] ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ ከዚህ በታች ካሉት የቴሌግራም ቻናል እና ግሩፕ ውጪ ምንም አይነት የሚዲያ ቻናል የለውም !!!
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
🫛የወ.ሶ.ዩ.ሙስሊም(ሰለፍዮች) ተማሪዎች ጀመዐ... (Wolaita sodo university Muslim(Selefyoch) students jemea')
https://www.tg-me.com/WSU_Muslim1SelefyStudents/2263
⬆⬆⬆
#2.የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ [ሰለፊይ ] ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ ፈትሕ መስጂድ መሆኑን አትርሱ !!!
#3.ለማንኛውም ተማሪ ወደ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለሚመጡ ይህንን መልዕክት ማሰራጨትን እንዳይረሱ!!!
#4. ማንነታችውን ደብቀው እሚንቀሳቀሱ የዲን አጭበርባሪዎች ስላሉ አቅማችሁ በፈቀደው ሁሉ ጥንቃቄ ማድረግን እንዳትረሱ !!
#5 በዩንቨርሲቲያችን የተማሪዎች የቅበላ መርሃ- ግብር ወቅት ዩንቨርሲቲው ደርሳችሁ ከትራንስፖርት ስትወርዱ ካላይ በቅደም ተከተል ስማቸው ከነ-ስልክ ቁጥራቸው የተዘረዘሩት ወንድሞች ጋር በመደወል እነሱ እንዲቀበሉዋቹ አልያም በነሱ በኩል ሌሎች ወንድሞች እንዲመድቡላችሁ መጠየቅን እንዳትረሱ!!
#6.አድራሻ ከቴክኖ ካምፓስ ፊት ለፊት የተማሪዎች መስጂድ ብለው ቢጠይቁ ማንም ሰው ይነግሮታል የዲን አጭበርባሪዎች ሲቀሩ !!!
#7.የሙስሊም ሴት እህቶቻችንን ስልክ ለምትፈልጉ ሙስሊም ሴት እህቶች ወንድም በድሩ ሁሴን(0979874293) እና ወንድም አብዱረሺድ ሙሀመድ (0918742346) በኩል ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ፤ እንዲሁም affaan oromo ዐብዱልሐኪም ከድር(0909879173)።
✍የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዐ ተወካይ
ሃያቱ ሸረፋ : 0936780125
#share
#Share
#share and
#Join
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://www.tg-me.com/WSU_Muslim1SelefyStudents/2263
⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
የቀብር ዚያራ
~
የቀብር ዚያራ ብለው የሚያራግቡ ሰዎችን እያየን ነው። የቀብር ዚያራን የሚቃወም ሙስሊም የለም። የቀብር አምልኮን የሚነቅፉ አካላትን ልክ የቀብር ዚያራ እንደሚቃወሙ እያደረጉ ማቅረብ ከእውነት የራቀ የተለመደ የሱፍያ ክስ ነው። ችግሩ ያለው ከሙታንና ከመቃብር ጋር ያላቸውን አጉል ቁርኝት የሸሪዐ መሰረት ባለው የቀብር ዚያራ ሊያሻሽጡ መሞከራቸው ላይ ነው።
ለማንኛውም የቀብር ዚያራ ሶስት መልክ አለው። እነሱም፦
ሀ. ሸሪዐዊ የቀብር ዚያራ፡-
ኣኺራን ለማስታወስ ወይም ለሟቾቹ ዱዓእ ለማድረግ ታስቦ የሚደረግ ሲሆን ሸሪዐው የሚያበረታታውና ነብዩ ﷺ የፈፀሙት ነው። ሸሪዐዊ የቀብር ዚያራ ሶስት መስፈርቶችን ያሟላ ነው።
1. አገር አቋርጦ አለመጓዝ፡-
ምክንያቱም ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لا تُشَدُّ الرِّحالُ إلَّا إلى ثلاثةِ مساجدٍ : المسجدُ الحرامُ ، و مسجدي هذا ، والمسجدُ الأقصى
{ወደ ሶስት መስጂዶች ካልሆነ በስተቀር ለጉዞ (የግመል) መጫኛዎች አይጠበቁም። (አገር አቋርጦ መጓዝ አይቻልም።) (እነሱም) ይሄ መስጂዴ (መዲና የሚገኘው የሳቸው መስጂድ)፣ መስጂደል ሐራም እና መስጂደል አቅሷ ናቸው።} [ቡኻሪ፡ 1189] [ሙስሊም፡ 1397]
2. ሄዶ መጥፎ ነገር አለመናገር፣ አለመፈፀም፡-
ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
كنتُ نهيتُكم عن زيارَةِ القبورِ ألا فزورُوها ، فإِنَّها تُرِقُّ القلْبَ ، و تُدْمِعُ العينَ ، وتُذَكِّرُ الآخرةَ ، ولا تقولوا هُجْرًا
{ቀብሮችን እንዳትጎበኙ ከልክያችሁ ነበር። ከዚህ በኋላ ግን ጎብኟቸው። ምክንያቱም ልብን ያለሰልሳሉ፤ አይንን ያረሰርሳሉ እንዲሁም ኣኺራን ያስታውሳሉና። መጥፎ ነገር ግን እንዳትናገሩ።} [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4584]
ሟቹን መለመን፣ በጀነት መመስከር፣ ሙሾ ማወረድና መሰል አላህን የሚያስቆጡ ንግግሮችን መራቅ የግድ ይላል።
3. ገደብ አለማስቀመጥ፡-
የቀብር ጉብኝት ዒባዳ ወይም አምልኮት ነው። አምልኮት ውስጥ ደግሞ ሸሪዐው ያላስቀመጠውን የአፈፃፀም ልዩ ገደብ ማስቀመጥ አይፈቀድም። ስለሆነም የሆነን ጊዜ ጠብቆ ወይም የሆነን ቀብር ለይቶ በቋሚነት መጎብኘት አይፈቀድም። ነብዩም ﷺ {ቀብሬን መመላለሻ አድጋችሁ አትያዙት} ማለታቸው ይህን የሚገልፅ መልእክት አለው። [አሕካሙል ጀናኢዝ፡ 280]
ለ. ቢድዐዊ የቀብር ዚያራ፡-
ሌላኛው ዚያራ አይነት ደግሞ ከቀብሩ ዘንድ ቁርኣን ለመቅራት፣ ሶላት ለመስገድ ወይም እዚያ ለአላህ ለማረድ ታስቦ የሚፈፀመው ሲሆን ይህኛው ጉብኝት መሰረት የሌለው መጤ ፈሊጥ ነው። ምክንያቱም እነኚህን አምልኮቶች ለመፈፀም በማሰብ ነብዩም ﷺ ይሁኑ ሶሐቦች ወደ መቃብር ስፍራ የሚመላለሱ አልነበሩምና። እንዲያውም ይሄኛው ዚያራ ወደ ሺርክ የሚያሻግር መንገድ ነው። ከቀብር አካባቢ ዘወትር አምልኮት የሚፈፅም ሰው ወደ ቀብሩ በአምልኮት የማዘንበል እድሉ ሰፊ ነው።
ሐ. ሺርክ ያለበት የቀብር ዚያራ፡-
ሌላኛው የቀብር ዚያራ አይነት ለሟቹ ለማረድ፣ ሟቹን ለመለመን፣ በሱ ወደ አላህ ለመቃረብ፣ ከሟቹ ልጅ፣ ዝናብ፣ ፈውስ ወይም ሌላ እርዳታ ለመጠየቅ፣ ስለት ለመሳል ታስቦ የሚፈፀመው ሲሆን ብይኑም ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ ነው። [አልቀውሉል ሙፊድ፣ ወሷቢይ፡ 192-194]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
የቀብር ዚያራ ብለው የሚያራግቡ ሰዎችን እያየን ነው። የቀብር ዚያራን የሚቃወም ሙስሊም የለም። የቀብር አምልኮን የሚነቅፉ አካላትን ልክ የቀብር ዚያራ እንደሚቃወሙ እያደረጉ ማቅረብ ከእውነት የራቀ የተለመደ የሱፍያ ክስ ነው። ችግሩ ያለው ከሙታንና ከመቃብር ጋር ያላቸውን አጉል ቁርኝት የሸሪዐ መሰረት ባለው የቀብር ዚያራ ሊያሻሽጡ መሞከራቸው ላይ ነው።
ለማንኛውም የቀብር ዚያራ ሶስት መልክ አለው። እነሱም፦
ሀ. ሸሪዐዊ የቀብር ዚያራ፡-
ኣኺራን ለማስታወስ ወይም ለሟቾቹ ዱዓእ ለማድረግ ታስቦ የሚደረግ ሲሆን ሸሪዐው የሚያበረታታውና ነብዩ ﷺ የፈፀሙት ነው። ሸሪዐዊ የቀብር ዚያራ ሶስት መስፈርቶችን ያሟላ ነው።
1. አገር አቋርጦ አለመጓዝ፡-
ምክንያቱም ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لا تُشَدُّ الرِّحالُ إلَّا إلى ثلاثةِ مساجدٍ : المسجدُ الحرامُ ، و مسجدي هذا ، والمسجدُ الأقصى
{ወደ ሶስት መስጂዶች ካልሆነ በስተቀር ለጉዞ (የግመል) መጫኛዎች አይጠበቁም። (አገር አቋርጦ መጓዝ አይቻልም።) (እነሱም) ይሄ መስጂዴ (መዲና የሚገኘው የሳቸው መስጂድ)፣ መስጂደል ሐራም እና መስጂደል አቅሷ ናቸው።} [ቡኻሪ፡ 1189] [ሙስሊም፡ 1397]
2. ሄዶ መጥፎ ነገር አለመናገር፣ አለመፈፀም፡-
ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
كنتُ نهيتُكم عن زيارَةِ القبورِ ألا فزورُوها ، فإِنَّها تُرِقُّ القلْبَ ، و تُدْمِعُ العينَ ، وتُذَكِّرُ الآخرةَ ، ولا تقولوا هُجْرًا
{ቀብሮችን እንዳትጎበኙ ከልክያችሁ ነበር። ከዚህ በኋላ ግን ጎብኟቸው። ምክንያቱም ልብን ያለሰልሳሉ፤ አይንን ያረሰርሳሉ እንዲሁም ኣኺራን ያስታውሳሉና። መጥፎ ነገር ግን እንዳትናገሩ።} [ሶሒሑል ጃሚዕ፡ 4584]
ሟቹን መለመን፣ በጀነት መመስከር፣ ሙሾ ማወረድና መሰል አላህን የሚያስቆጡ ንግግሮችን መራቅ የግድ ይላል።
3. ገደብ አለማስቀመጥ፡-
የቀብር ጉብኝት ዒባዳ ወይም አምልኮት ነው። አምልኮት ውስጥ ደግሞ ሸሪዐው ያላስቀመጠውን የአፈፃፀም ልዩ ገደብ ማስቀመጥ አይፈቀድም። ስለሆነም የሆነን ጊዜ ጠብቆ ወይም የሆነን ቀብር ለይቶ በቋሚነት መጎብኘት አይፈቀድም። ነብዩም ﷺ {ቀብሬን መመላለሻ አድጋችሁ አትያዙት} ማለታቸው ይህን የሚገልፅ መልእክት አለው። [አሕካሙል ጀናኢዝ፡ 280]
ለ. ቢድዐዊ የቀብር ዚያራ፡-
ሌላኛው ዚያራ አይነት ደግሞ ከቀብሩ ዘንድ ቁርኣን ለመቅራት፣ ሶላት ለመስገድ ወይም እዚያ ለአላህ ለማረድ ታስቦ የሚፈፀመው ሲሆን ይህኛው ጉብኝት መሰረት የሌለው መጤ ፈሊጥ ነው። ምክንያቱም እነኚህን አምልኮቶች ለመፈፀም በማሰብ ነብዩም ﷺ ይሁኑ ሶሐቦች ወደ መቃብር ስፍራ የሚመላለሱ አልነበሩምና። እንዲያውም ይሄኛው ዚያራ ወደ ሺርክ የሚያሻግር መንገድ ነው። ከቀብር አካባቢ ዘወትር አምልኮት የሚፈፅም ሰው ወደ ቀብሩ በአምልኮት የማዘንበል እድሉ ሰፊ ነው።
ሐ. ሺርክ ያለበት የቀብር ዚያራ፡-
ሌላኛው የቀብር ዚያራ አይነት ለሟቹ ለማረድ፣ ሟቹን ለመለመን፣ በሱ ወደ አላህ ለመቃረብ፣ ከሟቹ ልጅ፣ ዝናብ፣ ፈውስ ወይም ሌላ እርዳታ ለመጠየቅ፣ ስለት ለመሳል ታስቦ የሚፈፀመው ሲሆን ብይኑም ከኢስላም የሚያስወጣው ትልቁ ሺርክ ነው። [አልቀውሉል ሙፊድ፣ ወሷቢይ፡ 192-194]
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Forwarded from Wolkite University Muslim students jeme'a official channel
ውድ ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ freshman ሙስሊም ተማሪዎች በሙሉ!!
الســـــلام عليـــــكم ورحــــمة الله وبركــــــاته
እንደሚታወቀው በ2018 ዓ.ል በአላህ ፍቃድ ወደ ግቢ መግቢያ ቀናችሁ ጥቅምት 15 እና 16 ነው ።
ስለሆነም ይህን በማስመልከት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እናንተን ሙስሊም ወንድምና እህቶቹን ተቀብሎ ማንኛውንም ዲናዊም ሆነ አካዳሚክ መረጃዎችን ለመስጠት እና ለመተባበር በጉጉት እየጠበቅናችሁ እንገኛለን፡፡
ስለዚህ ስለሚያስፈልጋችሁ ማንኛውም አይነት ጥያቄም ይሁን ትብብር ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ስልኮች ደውላችሁ ሙሉ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።
1, ነጃ ሰዒድ
ስ'ቁ +251927528715
2,አሚር አብድል ቋድር
ስ'ቁ +251960116848
3.ቢላል ሺከታ
ስ'ቁ +251968510115 (የእህቶችን ቁጥር ለምትፈልጉ በዚህ ቁጥር ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ።)
አላህ በሰላም ያገናኘን።
https://www.tg-me.com/Wku_ms_Official_Channel
@Wku_ibnuabbas_bot
الســـــلام عليـــــكم ورحــــمة الله وبركــــــاته
እንደሚታወቀው በ2018 ዓ.ል በአላህ ፍቃድ ወደ ግቢ መግቢያ ቀናችሁ ጥቅምት 15 እና 16 ነው ።
ስለሆነም ይህን በማስመልከት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ እናንተን ሙስሊም ወንድምና እህቶቹን ተቀብሎ ማንኛውንም ዲናዊም ሆነ አካዳሚክ መረጃዎችን ለመስጠት እና ለመተባበር በጉጉት እየጠበቅናችሁ እንገኛለን፡፡
ስለዚህ ስለሚያስፈልጋችሁ ማንኛውም አይነት ጥያቄም ይሁን ትብብር ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ስልኮች ደውላችሁ ሙሉ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።
1, ነጃ ሰዒድ
ስ'ቁ +251927528715
2,አሚር አብድል ቋድር
ስ'ቁ +251960116848
3.ቢላል ሺከታ
ስ'ቁ +251968510115 (የእህቶችን ቁጥር ለምትፈልጉ በዚህ ቁጥር ደውላችሁ ማግኘት ትችላላችሁ።)
አላህ በሰላም ያገናኘን።
https://www.tg-me.com/Wku_ms_Official_Channel
@Wku_ibnuabbas_bot
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
ሁድሁድ፡ ተአምረኛው ወፍ!
~
ነብዩ ሱለይማን ብኑ ዳውድ ﷺ እጅግ አስደናቂ በሆነ መልኩ አላህ ሁሉን ነገር የገራላቸው ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡ ከቁርኣን ጥቂት ቀንጨብ ላድርግማ፡-
وَلَقَدْ آتَيْنَا دَاوُودَ وَسُلَيْمَانَ عِلْمًا ۖ وَقَالَا الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي فَضَّلَنَا عَلَىٰ كَثِيرٍ مِنْ عِبَادِهِ الْمُؤْمِنِينَ
{ለዳውድና ለሱለይማንም እውቀትን በእርግጥ ሰጠናቸው፡፡ አሉም፡- “ምስጋና ለአላህ ይገባው፡፡ ለዚያ ከምእምናን ባሮቹ በብዙዎቹ ላይ ላበለጠን፡፡”}
وَوَرِثَ سُلَيْمَانُ دَاوُودَ ۖ وَقَالَ يَا أَيُّهَا النَّاسُ عُلِّمْنَا مَنْطِقَ الطَّيْرِ وَأُوتِينَا مِنْ كُلِّ شَيْءٍ ۖ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْفَضْلُ الْمُبِينُ
{ሱለይማንም ዳውድን ወረሰ፡፡ አለም፡ “ሰዎች ሆይ! የወፍን ቋንቋ ተስተማርን፡፡ ከነገሩ ሁሉም ተሰጠን፡፡ ይህ እርሱ በእርግጥ ግልጽ የሆነ ችሮታ ነው!”}
وَحُشِرَ لِسُلَيْمَانَ جُنُودُهُ مِنَ الْجِنِّ وَالْإِنْسِ وَالطَّيْرِ فَهُمْ يُوزَعُونَ
{ለሱለይማንም ሰራዊቶቹ ከጂን፣ ከሰውም፣ ከወፍም የሆኑት ተሰበሰቡ፡፡ እነሱም በስርኣት ይደራጃሉ፡፡}
حَتَّىٰ إِذَا أَتَوْا عَلَىٰ وَادِ النَّمْلِ قَالَتْ نَمْلَةٌ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ لَا يَحْطِمَنَّكُمْ سُلَيْمَانُ وَجُنُودُهُ وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ
{በጉንዳንም ሸለቆ በመጡ ጊዜ አንዲት ጉንዳን “እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ፡፡ ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲሆኑ እንዳይሰባብሩዋችሁ” አለች፡፡}
فَتَبَسَّمَ ضَاحِكًا مِنْ قَوْلِهَا وَقَالَ رَبِّ أَوْزِعْنِي أَنْ أَشْكُرَ نِعْمَتَكَ الَّتِي أَنْعَمْتَ عَلَيَّ وَعَلَىٰ وَالِدَيَّ وَأَنْ أَعْمَلَ صَالِحًا تَرْضَاهُ وَأَدْخِلْنِي بِرَحْمَتِكَ فِي عِبَادِكَ الصَّالِحِينَ
{(ሱለይማን) ከንግግርዋም እየሳቀ ፈገግ አለ፡፡ “ጌታዬ ሆይ! ያቺን በእኔና በወላጆቼ ላይ የለገስካትን ጸጋህን እንዳመሰግን፣ የምትወደውንም በጎ ሥራ እንድሰራ ምራኝ፡፡ በችሮታህም በመልካሞቹ ባሮችህ ውስጥ አግባኝ” አለ፡፡}
وَتَفَقَّدَ الطَّيْرَ فَقَالَ مَا لِيَ لَا أَرَى الْهُدْهُدَ أَمْ كَانَ مِنَ الْغَائِبِينَ
{ወፎቹንም ተመለከተ፤ አለም፡ “ምነው ሁድሁድን አላየውም?! ወይስ (በቦታው) ከሌሉት ሆኗልን?”}
لَأُعَذِّبَنَّهُ عَذَابًا شَدِيدًا أَوْ لَأَذْبَحَنَّهُ أَوْ لَيَأْتِيَنِّي بِسُلْطَانٍ مُبِينٍ
{“በእርግጥ ብርቱ ቅጣትን እቀጣዋለሁ፡፡ ወይም በእርግጥ አርደዋለሁ!! ወይም (ለመጥፋቱ አሳማኝ የሆነ) ግልፅ የሆነን ማስረጃ ያመጣልኛል” (አለ፡፡)}
فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍ فَقَالَ أَحَطْتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِ وَجِئْتُكَ مِنْ سَبَإٍ بِنَبَإٍ يَقِينٍ
{(ሁድሁድ ግን) ሩቅ ያልሆነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም፡ “ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ፡፡”}
إِنِّي وَجَدْتُ امْرَأَةً تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِنْ كُلِّ شَيْءٍ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌ
{“እኔ የምትገዛቸው (ሰዎች ያሏት) የሆነችን፣ ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችን ሴት አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡}
وَجَدْتُهَا وَقَوْمَهَا يَسْجُدُونَ لِلشَّمْسِ مِنْ دُونِ اللَّهِ وَزَيَّنَ لَهُمُ الشَّيْطَانُ أَعْمَالَهُمْ فَصَدَّهُمْ عَنِ السَّبِيلِ فَهُمْ لَا يَهْتَدُونَ
{“እርሷንም ሕዝቦችዋንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም፡፡”}
أَلَّا يَسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي يُخْرِجُ الْخَبْءَ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَيَعْلَمُ مَا تُخْفُونَ وَمَا تُعْلِنُونَ
{“ለዚያ በሰማያትና በምድር የተደበቀውን ለሚያወጣው፣ የምትሸሽጉትንና የምትገልፁትንም ሁሉ ለሚያውቀው አላህ እንዳይሰግዱ (ሰይጣን አግዷቸዋል)፡፡”}
اللَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ
{“አላህ ከርሱ ሌላ (የእውነት) አምላክ የለም፡፡ የታላቁ ዐርሽ (ዙፋን) ጌታ ነው፡፡”}
قَالَ سَنَنْظُرُ أَصَدَقْتَ أَمْ كُنْتَ مِنَ الْكَاذِبِينَ
{(ሱለይማንም) አለ፡- “እውነት እንደ ተናገርክ ወይም ከውሸታሞቹ እንደ ሆንክ ወደፊት እናያለን፡፡”}
اذْهَبْ بِكِتَابِي هَٰذَا فَأَلْقِهْ إِلَيْهِمْ ثُمَّ تَوَلَّ عَنْهُمْ فَانْظُرْ مَاذَا يَرْجِعُونَ
{“ይህንን ደብዳቤዬን ይዘህ ሂድ፡፡ ወደ እነርሱም ጣለው፡፡ ከዚያም ከእነሱ ዘወር በል፡፡ ምን አንደሚመልሱም ተመልከት፡፡”}
ሁድሁድ የታዘዘውን ፈፀመ፡፡ ደብዳቤውንም ከሱለይማን ወስዶ የመን ደርሶ የሰበእ (ሳባ) ንግስት ከምትገኝበት ስፍራ ጣለው፡፡ ተልእኮው ግቡን መቷል፡፡ ደብዳቤው ከንግስቲቷ እጅ ገባ፡፡ ይህኔም፡
قَالَتْ يَا أَيُّهَا الْمَلَأُ إِنِّي أُلْقِيَ إِلَيَّ كِتَابٌ كَرِيمٌ
{አለች፡ “እናንተ መማክርቶች ሆይ! እኔ የተከበረ ደብዳቤ ወደኔ ተጣለ፡፡”}
إِنَّهُ مِنْ سُلَيْمَانَ وَإِنَّهُ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
{“እነሆ እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” (የሚል መክፈቻ አለው፡፡)}
أَلَّا تَعْلُوا عَلَيَّ وَأْتُونِي مُسْلِمِينَ
{“በእኔ ላይ አትኩሩ፡፡ ታዛዦችም ሆናችሁ ወደኔ ኑ” (የሚል ነው)፡፡} [አነምል፡ 15 - 31]
ይህን ልብ አንጠልጣይ ታሪክ መጨረስ የፈለገ ጥሩ የሆነ ተፍሲር ይዞ እስከመጨረሻው መከታተል ይችላል፡፡ እኔ ግን አንድ ጥያቄ ጠይቄ ፅሁፌን ልቋጭ፡፡ ሁድሁድ፡ ንግስተ-ሳባ የታደለችውን ሀብትና ድሎት ከገለፀ በኋላ ፀሀይ አምላኪ የሆኑትን ንግስቷን እና ህዝቦቿን ከእውነተኛው የተውሒድ መስመር ያፈነገጡ እንደሆኑ በሚደንቅ ሁኔታ እንዲህ ሲል ገልፁዋቸዋል፡-
“እርሷንም ሕዝቦቿንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም!”
አላሁ አክበር! ዛሬም ልክ እንዲሁ ሸይጧን ጥፋታቸውን አስውቦላቸው በአላህ ላይ ማጋራታቸውን እንደ ተውሒድ፣ እንደ ፅድቅ የሚቆጥሩት ስንትና ስንት ናቸው?! ህሊና ያላችሁ አስተውሉ! ሁድሁድ ቀጠለ፣ የሰዎቹ ምግባር ማስተዋሉን ላልተነፈገ ከህሊና ጋር የሚጋጭ እንደሆነ እንዲህ ገለፀው፡-
~
ነብዩ ሱለይማን ብኑ ዳውድ ﷺ እጅግ አስደናቂ በሆነ መልኩ አላህ ሁሉን ነገር የገራላቸው ታላቅ ሰው ነበሩ፡፡ ከቁርኣን ጥቂት ቀንጨብ ላድርግማ፡-
وَلَقَدْ آتَيْنَا دَاوُودَ وَسُلَيْمَانَ عِلْمًا ۖ وَقَالَا الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي فَضَّلَنَا عَلَىٰ كَثِيرٍ مِنْ عِبَادِهِ الْمُؤْمِنِينَ
{ለዳውድና ለሱለይማንም እውቀትን በእርግጥ ሰጠናቸው፡፡ አሉም፡- “ምስጋና ለአላህ ይገባው፡፡ ለዚያ ከምእምናን ባሮቹ በብዙዎቹ ላይ ላበለጠን፡፡”}
وَوَرِثَ سُلَيْمَانُ دَاوُودَ ۖ وَقَالَ يَا أَيُّهَا النَّاسُ عُلِّمْنَا مَنْطِقَ الطَّيْرِ وَأُوتِينَا مِنْ كُلِّ شَيْءٍ ۖ إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ الْفَضْلُ الْمُبِينُ
{ሱለይማንም ዳውድን ወረሰ፡፡ አለም፡ “ሰዎች ሆይ! የወፍን ቋንቋ ተስተማርን፡፡ ከነገሩ ሁሉም ተሰጠን፡፡ ይህ እርሱ በእርግጥ ግልጽ የሆነ ችሮታ ነው!”}
وَحُشِرَ لِسُلَيْمَانَ جُنُودُهُ مِنَ الْجِنِّ وَالْإِنْسِ وَالطَّيْرِ فَهُمْ يُوزَعُونَ
{ለሱለይማንም ሰራዊቶቹ ከጂን፣ ከሰውም፣ ከወፍም የሆኑት ተሰበሰቡ፡፡ እነሱም በስርኣት ይደራጃሉ፡፡}
حَتَّىٰ إِذَا أَتَوْا عَلَىٰ وَادِ النَّمْلِ قَالَتْ نَمْلَةٌ يَا أَيُّهَا النَّمْلُ ادْخُلُوا مَسَاكِنَكُمْ لَا يَحْطِمَنَّكُمْ سُلَيْمَانُ وَجُنُودُهُ وَهُمْ لَا يَشْعُرُونَ
{በጉንዳንም ሸለቆ በመጡ ጊዜ አንዲት ጉንዳን “እናንተ ጉንዳኖች ሆይ! ወደ መኖሪያዎቻችሁ ግቡ፡፡ ሱለይማንና ሰራዊቱ እነርሱ የማያውቁ ሲሆኑ እንዳይሰባብሩዋችሁ” አለች፡፡}
فَتَبَسَّمَ ضَاحِكًا مِنْ قَوْلِهَا وَقَالَ رَبِّ أَوْزِعْنِي أَنْ أَشْكُرَ نِعْمَتَكَ الَّتِي أَنْعَمْتَ عَلَيَّ وَعَلَىٰ وَالِدَيَّ وَأَنْ أَعْمَلَ صَالِحًا تَرْضَاهُ وَأَدْخِلْنِي بِرَحْمَتِكَ فِي عِبَادِكَ الصَّالِحِينَ
{(ሱለይማን) ከንግግርዋም እየሳቀ ፈገግ አለ፡፡ “ጌታዬ ሆይ! ያቺን በእኔና በወላጆቼ ላይ የለገስካትን ጸጋህን እንዳመሰግን፣ የምትወደውንም በጎ ሥራ እንድሰራ ምራኝ፡፡ በችሮታህም በመልካሞቹ ባሮችህ ውስጥ አግባኝ” አለ፡፡}
وَتَفَقَّدَ الطَّيْرَ فَقَالَ مَا لِيَ لَا أَرَى الْهُدْهُدَ أَمْ كَانَ مِنَ الْغَائِبِينَ
{ወፎቹንም ተመለከተ፤ አለም፡ “ምነው ሁድሁድን አላየውም?! ወይስ (በቦታው) ከሌሉት ሆኗልን?”}
لَأُعَذِّبَنَّهُ عَذَابًا شَدِيدًا أَوْ لَأَذْبَحَنَّهُ أَوْ لَيَأْتِيَنِّي بِسُلْطَانٍ مُبِينٍ
{“በእርግጥ ብርቱ ቅጣትን እቀጣዋለሁ፡፡ ወይም በእርግጥ አርደዋለሁ!! ወይም (ለመጥፋቱ አሳማኝ የሆነ) ግልፅ የሆነን ማስረጃ ያመጣልኛል” (አለ፡፡)}
فَمَكَثَ غَيْرَ بَعِيدٍ فَقَالَ أَحَطْتُ بِمَا لَمْ تُحِطْ بِهِ وَجِئْتُكَ مِنْ سَبَإٍ بِنَبَإٍ يَقِينٍ
{(ሁድሁድ ግን) ሩቅ ያልሆነንም ጊዜ ቆዬ፡፡ አለም፡ “ያላወቅከውን ነገር አወቅኩ፡፡ ከሰበእም እርግጠኛን ወሬ አመጣሁልህ፡፡”}
إِنِّي وَجَدْتُ امْرَأَةً تَمْلِكُهُمْ وَأُوتِيَتْ مِنْ كُلِّ شَيْءٍ وَلَهَا عَرْشٌ عَظِيمٌ
{“እኔ የምትገዛቸው (ሰዎች ያሏት) የሆነችን፣ ከነገሩም ሁሉ የተሰጠችን ሴት አገኘሁ፡፡ ለእርሷም ታላቅ ዙፋን አልላት፡፡}
وَجَدْتُهَا وَقَوْمَهَا يَسْجُدُونَ لِلشَّمْسِ مِنْ دُونِ اللَّهِ وَزَيَّنَ لَهُمُ الشَّيْطَانُ أَعْمَالَهُمْ فَصَدَّهُمْ عَنِ السَّبِيلِ فَهُمْ لَا يَهْتَدُونَ
{“እርሷንም ሕዝቦችዋንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም፡፡”}
أَلَّا يَسْجُدُوا لِلَّهِ الَّذِي يُخْرِجُ الْخَبْءَ فِي السَّمَاوَاتِ وَالْأَرْضِ وَيَعْلَمُ مَا تُخْفُونَ وَمَا تُعْلِنُونَ
{“ለዚያ በሰማያትና በምድር የተደበቀውን ለሚያወጣው፣ የምትሸሽጉትንና የምትገልፁትንም ሁሉ ለሚያውቀው አላህ እንዳይሰግዱ (ሰይጣን አግዷቸዋል)፡፡”}
اللَّهُ لَا إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ رَبُّ الْعَرْشِ الْعَظِيمِ
{“አላህ ከርሱ ሌላ (የእውነት) አምላክ የለም፡፡ የታላቁ ዐርሽ (ዙፋን) ጌታ ነው፡፡”}
قَالَ سَنَنْظُرُ أَصَدَقْتَ أَمْ كُنْتَ مِنَ الْكَاذِبِينَ
{(ሱለይማንም) አለ፡- “እውነት እንደ ተናገርክ ወይም ከውሸታሞቹ እንደ ሆንክ ወደፊት እናያለን፡፡”}
اذْهَبْ بِكِتَابِي هَٰذَا فَأَلْقِهْ إِلَيْهِمْ ثُمَّ تَوَلَّ عَنْهُمْ فَانْظُرْ مَاذَا يَرْجِعُونَ
{“ይህንን ደብዳቤዬን ይዘህ ሂድ፡፡ ወደ እነርሱም ጣለው፡፡ ከዚያም ከእነሱ ዘወር በል፡፡ ምን አንደሚመልሱም ተመልከት፡፡”}
ሁድሁድ የታዘዘውን ፈፀመ፡፡ ደብዳቤውንም ከሱለይማን ወስዶ የመን ደርሶ የሰበእ (ሳባ) ንግስት ከምትገኝበት ስፍራ ጣለው፡፡ ተልእኮው ግቡን መቷል፡፡ ደብዳቤው ከንግስቲቷ እጅ ገባ፡፡ ይህኔም፡
قَالَتْ يَا أَيُّهَا الْمَلَأُ إِنِّي أُلْقِيَ إِلَيَّ كِتَابٌ كَرِيمٌ
{አለች፡ “እናንተ መማክርቶች ሆይ! እኔ የተከበረ ደብዳቤ ወደኔ ተጣለ፡፡”}
إِنَّهُ مِنْ سُلَيْمَانَ وَإِنَّهُ بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَٰنِ الرَّحِيمِ
{“እነሆ እርሱ ከሱለይማን ነው፡፡ እርሱም በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው” (የሚል መክፈቻ አለው፡፡)}
أَلَّا تَعْلُوا عَلَيَّ وَأْتُونِي مُسْلِمِينَ
{“በእኔ ላይ አትኩሩ፡፡ ታዛዦችም ሆናችሁ ወደኔ ኑ” (የሚል ነው)፡፡} [አነምል፡ 15 - 31]
ይህን ልብ አንጠልጣይ ታሪክ መጨረስ የፈለገ ጥሩ የሆነ ተፍሲር ይዞ እስከመጨረሻው መከታተል ይችላል፡፡ እኔ ግን አንድ ጥያቄ ጠይቄ ፅሁፌን ልቋጭ፡፡ ሁድሁድ፡ ንግስተ-ሳባ የታደለችውን ሀብትና ድሎት ከገለፀ በኋላ ፀሀይ አምላኪ የሆኑትን ንግስቷን እና ህዝቦቿን ከእውነተኛው የተውሒድ መስመር ያፈነገጡ እንደሆኑ በሚደንቅ ሁኔታ እንዲህ ሲል ገልፁዋቸዋል፡-
“እርሷንም ሕዝቦቿንም ከአላህ ሌላ ለፀሐይ ሲሰግዱ አገኘኋቸው፡፡ ሰይጣንም ለእነሱ (መጥፎ) ስራዎቻቸውን ሸልሞላቸዋል፡፡ ከእውነተኛውም መንገድ አግዷቸዋል፡፡ ስለዚህ እነሱ (ወደ እውነት) አይምመሩም!”
አላሁ አክበር! ዛሬም ልክ እንዲሁ ሸይጧን ጥፋታቸውን አስውቦላቸው በአላህ ላይ ማጋራታቸውን እንደ ተውሒድ፣ እንደ ፅድቅ የሚቆጥሩት ስንትና ስንት ናቸው?! ህሊና ያላችሁ አስተውሉ! ሁድሁድ ቀጠለ፣ የሰዎቹ ምግባር ማስተዋሉን ላልተነፈገ ከህሊና ጋር የሚጋጭ እንደሆነ እንዲህ ገለፀው፡-
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Photo
“ለዚያ በሰማያትና በምድር የተደበቀውን ለሚያወጣው፣ የምትሸሽጉትንና የምትገልፁትንም ሁሉ ለሚያውቀው አላህ እንዳይሰግዱ (ሰይጣን አግዷቸዋል።)”
ዛሬ ግን የተደበቀውን ስውሩን ሁሉ ከዘመናት በፊት የሞቱ ሰዎች ያውቃሉ በሚል በጥፋት ላይ የሚዋልሉት ስንቶች ናቸው?! ከዚያም እንዲህ ሲል ንግግሩን በተውሒድ አሳረገው፡
“አላህ ከርሱ ሌላ (የእውነት) አምላክ የለም፡፡ የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው፡፡”
ሱብሓነላህ! ምንኛ የሚደንቅ ነው። ሁድሁድ (hoopoe)፣ እንድር ማርዬ፣ ሽንብር ጉትያ።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 11/2008)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
ዛሬ ግን የተደበቀውን ስውሩን ሁሉ ከዘመናት በፊት የሞቱ ሰዎች ያውቃሉ በሚል በጥፋት ላይ የሚዋልሉት ስንቶች ናቸው?! ከዚያም እንዲህ ሲል ንግግሩን በተውሒድ አሳረገው፡
“አላህ ከርሱ ሌላ (የእውነት) አምላክ የለም፡፡ የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው፡፡”
ሱብሓነላህ! ምንኛ የሚደንቅ ነው። ሁድሁድ (hoopoe)፣ እንድር ማርዬ፣ ሽንብር ጉትያ።
(ኢብኑ ሙነወር፣ ጥቅምት 11/2008)
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Hisnul Muslim #02
Ibnu Munewor
ደርስ
~
• ኪታቡ፦ ሒስኑል ሙስሊም
• ክፍል:-0️⃣ 2️⃣
• ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor/8340
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 10፣ أذكار الاستيقاظ من النوم
~
• ኪታቡ፦ ሒስኑል ሙስሊም
• ክፍል:-
• ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂድ
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor/8340
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 10፣ أذكار الاستيقاظ من النوم
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
በተውሒድ ደዕዋ ላይ አደራ
~
* አስተማሪዎች ከተውሒድ / ዐቂዳ ኪታቦች አትራቁ። የተለያየ ፈን እያስተማራችሁ ባጠናቀቃችሁ ቁጥር በየ መሀሉ የተውሒድ / የዐቂዳ ኪታቦችን አስገቡ። የቃል በቃል ትርጉም ሳይሆን በሚገባ ሸርሕ አይታችሁ በመቅረብ አብጠርጥራችሁ አድምታችሁ አስተምሩ።
* ለመስጂድ ኮሚቴዎች ወይም ሌሎች የሚመለከታችሁ ሁሉ የተውሒድ ትምህርት ተጠናክሮ ለህዝባችን እንዲስሰጥ የድርሻችሁን ተወጡ።
* ነጋዴዎች፣ ባለ ሀብቶች ብትሞቱ እንኳ የማይቋረጥ እጅግ የገዘፈ ሶደቀቱን ጃሪያ እንዲኖራችሁ ተውሒድን በማሰራጨት ላይ ድርሻ ይኑራችሁ። የተውሒድ ኪታቦችን፣ ሹሩሓትን በመግዛት በተለይም ወደ ገጠር አሰራጩ። ደረሶችን አግዙ። ተውሒድ ላይ ትኩረት የሚሰጡ መሻይኾችን፣ ዱዓቶችን ከጎናቸው ቁሙ።
* ሁሉም በየዘርፉ የተውሒድን ደዕዋ በማገዝ ላይ ሊረባረብ ይገባል። አደራ አደራ! ለወገናችን ከዚህ በላይ የምንውለው ውለታ የለም። አላህ ያበርታችሁ፣ ልፋታችሁንም ይቀበላችሁ።
ሼር አድርጉት ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
* አስተማሪዎች ከተውሒድ / ዐቂዳ ኪታቦች አትራቁ። የተለያየ ፈን እያስተማራችሁ ባጠናቀቃችሁ ቁጥር በየ መሀሉ የተውሒድ / የዐቂዳ ኪታቦችን አስገቡ። የቃል በቃል ትርጉም ሳይሆን በሚገባ ሸርሕ አይታችሁ በመቅረብ አብጠርጥራችሁ አድምታችሁ አስተምሩ።
* ለመስጂድ ኮሚቴዎች ወይም ሌሎች የሚመለከታችሁ ሁሉ የተውሒድ ትምህርት ተጠናክሮ ለህዝባችን እንዲስሰጥ የድርሻችሁን ተወጡ።
* ነጋዴዎች፣ ባለ ሀብቶች ብትሞቱ እንኳ የማይቋረጥ እጅግ የገዘፈ ሶደቀቱን ጃሪያ እንዲኖራችሁ ተውሒድን በማሰራጨት ላይ ድርሻ ይኑራችሁ። የተውሒድ ኪታቦችን፣ ሹሩሓትን በመግዛት በተለይም ወደ ገጠር አሰራጩ። ደረሶችን አግዙ። ተውሒድ ላይ ትኩረት የሚሰጡ መሻይኾችን፣ ዱዓቶችን ከጎናቸው ቁሙ።
* ሁሉም በየዘርፉ የተውሒድን ደዕዋ በማገዝ ላይ ሊረባረብ ይገባል። አደራ አደራ! ለወገናችን ከዚህ በላይ የምንውለው ውለታ የለም። አላህ ያበርታችሁ፣ ልፋታችሁንም ይቀበላችሁ።
ሼር አድርጉት ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
Video
"ወሃBያ ተከትሎ መስገድ አይቻልም፣ ያረ ^ዱት ስጋ አይብበላም፣ ኒካሕ የላቸውም"
#ማነው_ተKፊሩ?
#ክፍል_2
~
ሰሞኑን ኢኽዋንና አሕ ^ ባሽ በሰለፊያ ደዕዋ ላይ የጋራ ዘመቻ እንደከፈቱ እያየን ነው። በቀዳሚነት እያራገቡት ያለው ነጥብ ተKፊሪዮች ናቸው የሚል ነው። ሙስሊሞችን በጅምላ ከኢስላም በማውጣት ላይ የተሰማራው ማን እንደሆነ በተከታታይ በማስረጃ አቀርባለሁ። ክፍል አንድን አሳልፌያለሁ።
በዚህኛው ክፍል ያቀረብኩት መረጃ የአሕ ^ ባሹን ዑመር ይማምን ንግግር ነው። በቅድሚያ አንድ ነጥብ ላስቀድም። አላህ ከፍጡራን በላይ ነው የሚለው እምነት በቁርኣንም፣ በሐዲሥም የተረጋገጠ የሰለፎች ኢጅማዕ ያለበት ጉዳይ ነው። በዚህ ላይ ተደጋጋሚ መረጃዎችን ያቀረብኩ ቢሆንም ለቅምሻ ያክል ብቻ ጠቆም ላድርግ፦
1. ታላቁ ዓሊም ዐብዱላህ ብኑል ሙባረክ (181 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡-
فَإِنَّ أَهْلَ الْإِثْبَاتِ مِنْ أَهْلِ السُّنَّةِ يُجْمِعُونَ ... وَأَنَّ اللَّهَ عَلَى عَرْشِهِ بَائِنٌ مِنْ خَلْقِهِ
“የአላህን መገለጫዎች የሚያፀድቁት የሱና ሰዎች … አላህ ከፍጡሩ ተለይቶ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ኢጅማዕ አድርገዋል።” [አልኢባና፣ ኢብኑ በጧህ፡ ቁ. 694]
2. አቡ ዙርዐ አራዚይ (264 ሂ.) እና ሓቲም አራዚይ (277 ሂ.) የአህሉ ሱናን ዐቂዳ ሲተነትኑ እንዲህ ብለዋል፡-
أَدْرَكْنَا الْعُلَمَاءَ فِي جَمِيعِ الْأَمْصَارِ حِجَازًا وَعِرَاقًا وَشَامًا وَيَمَنًا فَكَانَ مِنْ مَذْهَبِهِمُ: … وَأَنَّ اللَّهَ عَزَّ وَجَلَّ عَلَى عَرْشِهِ بَائِنٌ مِنْ خَلْقِهِ كَمَا وَصَفَ نَفْسَهُ فِي كِتَابِهِ , وَعَلَى لِسَانِ رَسُولِهِ ﷺ بِلَا كَيْفٍ
“በሁሉም ሃገራት - በሒጃዝ፣ በዒራቅ፣ በሻም፣ በየመን፣… ያሉ ዑለማዎችን አግኝተናል። ከመዝሀባቸው ውስጥ … አላህ - ዐዘ ወጀል - እራሱን በቁርኣኑ፣ እንዲሁም በመልእክተኛው ﷺ አንደበት እንደተገለፀው - ያለ እንዴት - ከፍጡሩ ተለይቶ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ማመን ነው። [ላለካኢ፡ ቁ. 321]
3. ታላቁ ኢማም ኢብኑ ቁተይባህ (276 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡-
وَالْأُمَمُ كُلُّهَا - عَرَبِيُّهَا وَعَجَمِيُّهَا - تَقُولُ: إِنَّ اللَّهَ تَعَالَى فِي السَّمَاءِ مَا تُرِكَتْ عَلَى فِطَرِهَا وَلَمْ تُنْقَلْ عَنْ ذَلِكَ بِالتَّعْلِيمِ
“ህዝቦች በሙሉ ዐረቡም ሌላውም አላህ በሰማይ ነው ይላሉ። በተፈጥሯቸው ላይ እስከተተውና ከዚህ ላይ በስብከት እስካልተወሰዱ ድረስ።” [ተእዊሉ ሙኽተሊፊል ሐዲሥ፡ 395]
በዚህ ላይ ያሉ የሰለፎች ንግግሮች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ድምፁን ያያያዝኩት ዑመር ይማም የተባለው አሕ ^ባሽስ ምን ይላል?
አላህን ከፍጡራን በላይ ከዐርሹ በላይ ነው የሚሉ ሙስሊሞችን በሙሉ ከኢስላም ያስወጣል። ሙስሊሞች አይደሉም፣ እነሱን በሶላት ተከትሎ መስገድ አይቻልም፣ ያረ ^ዱት ስጋ አይብበላም፣ ኒካሕም የላቸውም ይላል። ይሄ የሱ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው የአሕ ^ባሽ ቡድን አቋም ነው። ዛሬ ያሉ ሙስሊሞችን ከተራው ህዝብ አልፈው እስከ ዑለማእ ከእስልምና ያስወጣሉ። ለሐጅ እና ለዑምራ ወደ ሳዑዲ ሲሄዱ ኢማሞቹ ሙስሊሞች አይደሉም በሚል አብረው አይሰግዱም።
እንደ ዑመር ይማም ሃይማኖት አላህ ከዐርሹ በላይ ነው በማለት ከሶሐቦች ጀምሮ ያለፉ የጥንት ሰለፎች በሙሉ ሙስሊሞች አይደሉም ማለት ነው። እንግዲህ ተመልከቱ! ከዚህ በላይ ተKፊነት ኖሮ አይናቸውን በጨው አጥበው ሌሎችን በተK ፊርነት እየከሰሱ ነው። በሺርክ እየጨፈሩ ሌሎችን ከኢስላም ሲያስወጡ ማየት ስላቅ ነው መቼም። እኮ ማነው ተKፊሩ ?
በደንብ "ሼር" እያደረጋችሁ ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
#ማነው_ተKፊሩ?
#ክፍል_2
~
ሰሞኑን ኢኽዋንና አሕ ^ ባሽ በሰለፊያ ደዕዋ ላይ የጋራ ዘመቻ እንደከፈቱ እያየን ነው። በቀዳሚነት እያራገቡት ያለው ነጥብ ተKፊሪዮች ናቸው የሚል ነው። ሙስሊሞችን በጅምላ ከኢስላም በማውጣት ላይ የተሰማራው ማን እንደሆነ በተከታታይ በማስረጃ አቀርባለሁ። ክፍል አንድን አሳልፌያለሁ።
በዚህኛው ክፍል ያቀረብኩት መረጃ የአሕ ^ ባሹን ዑመር ይማምን ንግግር ነው። በቅድሚያ አንድ ነጥብ ላስቀድም። አላህ ከፍጡራን በላይ ነው የሚለው እምነት በቁርኣንም፣ በሐዲሥም የተረጋገጠ የሰለፎች ኢጅማዕ ያለበት ጉዳይ ነው። በዚህ ላይ ተደጋጋሚ መረጃዎችን ያቀረብኩ ቢሆንም ለቅምሻ ያክል ብቻ ጠቆም ላድርግ፦
1. ታላቁ ዓሊም ዐብዱላህ ብኑል ሙባረክ (181 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡-
فَإِنَّ أَهْلَ الْإِثْبَاتِ مِنْ أَهْلِ السُّنَّةِ يُجْمِعُونَ ... وَأَنَّ اللَّهَ عَلَى عَرْشِهِ بَائِنٌ مِنْ خَلْقِهِ
“የአላህን መገለጫዎች የሚያፀድቁት የሱና ሰዎች … አላህ ከፍጡሩ ተለይቶ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ኢጅማዕ አድርገዋል።” [አልኢባና፣ ኢብኑ በጧህ፡ ቁ. 694]
2. አቡ ዙርዐ አራዚይ (264 ሂ.) እና ሓቲም አራዚይ (277 ሂ.) የአህሉ ሱናን ዐቂዳ ሲተነትኑ እንዲህ ብለዋል፡-
أَدْرَكْنَا الْعُلَمَاءَ فِي جَمِيعِ الْأَمْصَارِ حِجَازًا وَعِرَاقًا وَشَامًا وَيَمَنًا فَكَانَ مِنْ مَذْهَبِهِمُ: … وَأَنَّ اللَّهَ عَزَّ وَجَلَّ عَلَى عَرْشِهِ بَائِنٌ مِنْ خَلْقِهِ كَمَا وَصَفَ نَفْسَهُ فِي كِتَابِهِ , وَعَلَى لِسَانِ رَسُولِهِ ﷺ بِلَا كَيْفٍ
“በሁሉም ሃገራት - በሒጃዝ፣ በዒራቅ፣ በሻም፣ በየመን፣… ያሉ ዑለማዎችን አግኝተናል። ከመዝሀባቸው ውስጥ … አላህ - ዐዘ ወጀል - እራሱን በቁርኣኑ፣ እንዲሁም በመልእክተኛው ﷺ አንደበት እንደተገለፀው - ያለ እንዴት - ከፍጡሩ ተለይቶ ከዐርሹ በላይ እንደሆነ ማመን ነው። [ላለካኢ፡ ቁ. 321]
3. ታላቁ ኢማም ኢብኑ ቁተይባህ (276 ሂ.) እንዲህ ብለዋል፡-
وَالْأُمَمُ كُلُّهَا - عَرَبِيُّهَا وَعَجَمِيُّهَا - تَقُولُ: إِنَّ اللَّهَ تَعَالَى فِي السَّمَاءِ مَا تُرِكَتْ عَلَى فِطَرِهَا وَلَمْ تُنْقَلْ عَنْ ذَلِكَ بِالتَّعْلِيمِ
“ህዝቦች በሙሉ ዐረቡም ሌላውም አላህ በሰማይ ነው ይላሉ። በተፈጥሯቸው ላይ እስከተተውና ከዚህ ላይ በስብከት እስካልተወሰዱ ድረስ።” [ተእዊሉ ሙኽተሊፊል ሐዲሥ፡ 395]
በዚህ ላይ ያሉ የሰለፎች ንግግሮች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ድምፁን ያያያዝኩት ዑመር ይማም የተባለው አሕ ^ባሽስ ምን ይላል?
አላህን ከፍጡራን በላይ ከዐርሹ በላይ ነው የሚሉ ሙስሊሞችን በሙሉ ከኢስላም ያስወጣል። ሙስሊሞች አይደሉም፣ እነሱን በሶላት ተከትሎ መስገድ አይቻልም፣ ያረ ^ዱት ስጋ አይብበላም፣ ኒካሕም የላቸውም ይላል። ይሄ የሱ ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው የአሕ ^ባሽ ቡድን አቋም ነው። ዛሬ ያሉ ሙስሊሞችን ከተራው ህዝብ አልፈው እስከ ዑለማእ ከእስልምና ያስወጣሉ። ለሐጅ እና ለዑምራ ወደ ሳዑዲ ሲሄዱ ኢማሞቹ ሙስሊሞች አይደሉም በሚል አብረው አይሰግዱም።
እንደ ዑመር ይማም ሃይማኖት አላህ ከዐርሹ በላይ ነው በማለት ከሶሐቦች ጀምሮ ያለፉ የጥንት ሰለፎች በሙሉ ሙስሊሞች አይደሉም ማለት ነው። እንግዲህ ተመልከቱ! ከዚህ በላይ ተKፊነት ኖሮ አይናቸውን በጨው አጥበው ሌሎችን በተK ፊርነት እየከሰሱ ነው። በሺርክ እየጨፈሩ ሌሎችን ከኢስላም ሲያስወጡ ማየት ስላቅ ነው መቼም። እኮ ማነው ተKፊሩ ?
በደንብ "ሼር" እያደረጋችሁ ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
Telegram
Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
كناشة ابن منور
የሒስኑል ሙስሊም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
~
• ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂደል ዋሊደይን
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor/8340
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ 10፣ 4ኛ ሐዲሥ
• ደርሱ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፣ ኢንሻአላህ፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
~
• ደርሱ የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ፣ ጉቱ ሪል እስቴት መስጂደል ዋሊደይን
• ጊዜ፦ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
• የኪታቡን pdf ፋይል በዚህ ማግኘት ይቻላል:-
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor/8340
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ 10፣ 4ኛ ሐዲሥ
• ደርሱ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፣ ኢንሻአላህ፦
https://www.tg-me.com/IbnuMunewor
