Telegram Web Link
Forwarded from Kesatebirhan Ze Tewahdo (Kesatebirhan)
ተአምረ 27
፨፨፨፨፨

መውለድና መወለድ በአንድ ዕለት!

- እሳቸው 27 ዓመት ባገለገሉበት ቤት፣

-እኔም 27 ዓመቴን በሚይዝበት ዋዜማ ዕለት፣

- በመጋቢት 27 በዓለ ጥንተ ስቅለት፣

- "መጽሐፈ መሠረት" በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን በይፋ ገበያ ላይ ይውላል። የቁጥሩ መገጣጠም ወይ ግሩም ያሰኛል። በአንድ ዕለት የበኩር ልጅን ልደትና የራስን ልደት ማክበር ያለውን ስሜት እንዴት ልንገራችሁ? ለማንኛውም በበዓለ ንግሡ ማንጊያው እስከ ማብቂያው ማታ በተሰናዱት የዳስ Stationoch "መጽሐፈ መሠረት"ን ታገኟታላችሁ። ዋጋዋ ሦስት መቶ ብር ነው። ሰማይ በደረሰ የወረቀት ዋጋ ፣ በሌለ ገንዘብ የታተመ ጥቂት ፍሬ ስለሆነ የማለቅ እድሉ ሰፊ ነው። ቶሎ ግዙና የአባታችሁን ዘለዓለማዊ ታሪክ አስቀሩ። የመጽሔቱ ዕጣ እንዳይደርሳችሁ!

በተረፈ መጽሐፉን የምትፈልጉ አዲስ አበቤዎች እኚህን ወዶ ገብ አከፋፋዮች ደውሉና መጽሐፉን አግኙ።

1.አስቻለው አሸናፊ
+251922705082

2.በረከት ጉዲሣ
+251913134524

3.ሳባ ሰሎሞን
+251931527516

4.ሜሮን ገነነ
+251936290305

መልካም ንባብ ለእናንተ! መልካም ልደት ለእኔ!
https://www.instagram.com/p/CqlPK1bI-X8/?igshid=MDJmNzVkMjY=
ፊርማ ለወዳጅ

ለመላው አብሮ አደጎች ፣ አብሮ አገልጋዮች ፣ ክላስ ሜቶች ፣ ወዳጆችና የመንፈስ ልጆች በሙሉ።

አንዳንዶቻችሁ በቅርብ ለገበያ የቀረበውን መጽሐፌን " አዘጋጁ ካልፈረመበት አንገዛም ሙተን እንገኛለን" ማለታችሁን ሰምቻለሁ። ሌሎቻችሁ ደግሞ "ለበዓል መጥተን ሰኞ ፣ ማክሰኞ ሂያጅ ነን። መጽሐፉን አስቀምጥልን" እያላችሁ በውስጥ መስመር እየወተወታችሁኝ ነው። እኔ የሺህ ወዳጅ ወንድማችሁ ወገቤ እስቲንቀጠቀጥ ጥፌ ማዘጋጀቴ አንሶ እናንተን እግር በእግር እየተከተልኩ መጣፍ ማቀብልበት ጊዜውም ጉልበቱም የለኝምና የግቢ ጉባኤ ፣ የዓለም ት/ቤት ፣ የፕሪፕ ፣ የሚካኤልና የሌላም ሌላም የሰፈር ወዳጅ ፣ ጓደኛ ፣ ደቀ መዝሙርና ደቂቀ መዝሙር ሁሉ በትንሣኤ ዋዜማ በቀዳም ሥዑር ዕለት በደብረ መድኃኒት ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ከ4 ሰዓት ጀምሮ ከትተህ ላግኝህ። ማኅተምና ፊርማዬን ከስምህ ጋር ከትቤ እንዳስፈላጊነቱም በሥዕል አስውቤ ዘላለማዊ የወዳጅነት ማስታወሻ ይሆን ዘንድ መጽሐፈ መሠረትን አበረክትልሃለሁ። መርኃ ግብር አይደለም ደግሞ መጥቶ መሄድ ነው። አንድ የጋራ መገናኛ ለመፍጠር ያመች ዘንድ ነው። ማን ያውቃል በስንት እግዚኦታ ፣ ሠርግና ምርቃት መገናኘት ያልሆነለትን ጀማ ማገናኛ ሰበብ ይሆናል። ዘር ፣ ቀለም ፣ ጾታ ፣ እድሜ ፣ ባች ፣ ጸባይ ፣ የአመራርነትና የሥራ እርከን አይለይም። "ከሣችን አውቀዋለሁ" የሚል ሁሉ ጎራ ይበል።
https://www.instagram.com/p/Cq8b-10oXh8/?igshid=MDJmNzVkMjY=
Forwarded from Daregot Media
ዜና ሕይወቱ
ለቅዱስ ያሬድ
'ማኅሌታይ'
ግንቦት 11 በዓለ ስዋሬው ነው፡፡ እንኳን አደረሳችሁ!

ለአስተያየት
👉 @DaregotMediaComment_bot

ቴሌግራም ገጻችንን ይቀላቀሉ
👉 https://www.tg-me.com/daregot
ነገ ጠዋት በቤተ ቅኔ tube ይጠብቁ!
እሁድ ሰኔ 4 ከቀኑ 6 ሰዓት ጀምሮ አሰላ በርሔ ሆቴል በይፋ ይመረቃል።

መግቢያ የጥሪ ካርድ አልያም መጽሐፋን መያዝ

መጽሐፋን በሀገር ውስጥ በአዲስ አበባ ፣ አዳማ ፣ እና አሰላ ታገኙታላችሁ ፤ በውጪው ሀገር ደግሞ ቤሩት ፣ ካናዳ ፣ ቱርክ ታገኙታላችሁ። ለተጨማሪ መረጃ በ @buchula36 - 0936290305 ላይ አልያም 0975177166 ላይ መደወል ይችላሉ ።
                                የመፅሐፋ አዘጋጅ
Watch "የሰኔ ሚካኤል ወረብ ጥናት part 2 - ባሕራንኒ ይቤ" on YouTube
https://youtu.be/qmOJvPB4r7I
መኑ ከመ ከንተ?[እንዳንተ ያለ ማነው?]
@Mgetem
🌟🌟🌟🌟🌟

እንዳንተ ያለ ማነው
ከፍጥረታት ወገን ከዓለመ መላእክት
ከምድር እስከ አርያም ሠማየ ሠማያት
ከረቂቃን ወገን እጅግ ከከበሩ
ኃያል ከመ አንተ? ቅሩበ መንበሩ

እንዳንተ ያለ ማነው

ነፃ የሚያወጣ ከግዞት ከተማ
ህዝቡን የጠበቀ በተዓምረ ግርማ
ባህር የብስ የሚያደርግ ዝማሬን የመላ
ፈርዖንን የጣለ ከእስራኤል ኋላ
መኑ ከመ አንተ? ሠዳዴ አጋንንት
የሞትን ደብዳቤ የሚቀይር በህይወት
ፍጡነ ረድኤት ምዕራገ ጸሎት
መኑ ከመ አንተ? ሚካኤል አቡነ
አጽናኝ ለተከዘ ከልቡ ላዘነ
ዛሬም በጠላት እጅ የሞቷን ደብዳቤ ይዛ ለምትጓዝ ባህራን ሀገሬ
ደርሰህ ቀይርላት በትንሳኤ ብስራት ትቁም ለዝማሬ

                📝 አክሊለ ማርያም

🌟🌟🌟🌟🌟🌟
   እንኳን ለሊቀ መላዕክት ቅ/ሚካኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን
🌟🌟🌟🌟🌟🌟

▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
#ጎጆ_ቀለስኩልህ
@Mgetem
(በሰመረ ፍስሃ)

በአውላላ ሜዳ በጠራራ ፀሐይ
ከአስፓልቱ አጠገብ ስኖር ጎዳና ላይ
የበጋውን ንፋስ በዙሪያዬ ከቦኝ
እንደ ዥዋዥዌ ወዲያ ሲወስደኝ፡፡
...................ወዲህ ሲመልሰኝ

ዝናቡ በተራው ጉዴን ተመልክቶ
...................ጉድፌን አፅድቶ
ይወደኝ ይመስል ልብሴን ያጥብልኛል
ጎጆዬን አፈራርሶ በብርድ ይገርፈኛል፡፡

ከዚህ የባሰ ግን ሰዉ ነው 'ሚገርመኝ
በነጋ በጠባ መተንፈሻ ያሳጣኝ፡፡

ስለተናገርኩኝ ማጣት መከፋቴ
የእውነት ስለኖርኩኝ ውሸትን ጠልቼ
አፋቸውን ሞልተው እብድ ነው ይሉኛል
አንዳንዴ ሲያሻቸውም ድሃ ነው ይሉኛል፡፡

የሆነው ሆነና ቅር አላለኝም
አጣሁኝ ብዬም አላማረርኩም
ጌታ እንዳስተማረኝ ለበጎ ነው ብዬ
የማይቻል የለም እኖራሎህ ችዬ፡፡

ይሄውልህ ግን ሚካኤል ሆይ...
የሰው ልጅ ሲሸሸኝ ማንነቴን አይቶ
ሰላምታ ሲነፍገኝ ኑሮዬን ተመልክቶ
አንተ ግን አንተ ነህ የአምላክ መልእክተኛ
ሁሌ 'ምትጠብቀኝ መቼም የማተኛ፡፡
ምንም ሳይገድብህ ከቤቴ ገብተሀል
ድሃዋን ጎጆዬ በፍቅር ጎብኝተሀል፡፡

እናም ሚካኤል ሆይ....
ከኔ እንዳትርቅ ስለሳሳሁልህ
በንፁህ ልቤ ውስጥም ጎጆ ቀለስኩልህ፡፡
_____________
@Mgetem
@Mgetem_group
@Solasc12
2025/06/30 20:09:47
Back to Top
HTML Embed Code: