Telegram Web Link
፨ትንቢተ ዮናስ፨
ክፍል ፩
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በሕዝቡ መካከል አመጽ ስለ ጸና
በጣም ተቆጥቼ አዝኛለሁ እና
ይህንን ለነነዌ ንገራት በአዋጅ
አለና ለዮናስ ለአሚታይ ልጅ
እግዚአብሔር አዘዘው እንዲሄድ በቶሎ
ዮናስ እቢተኛው አሰበ ኮብልሎ
ከአምላኩ ተደብቆ አምልሎ ሊጠፋ
ወደ ተረሲስ ሲጓዝ የሄደ ወደ ያፋ።
ዋጋ ክፍልና ከመርከብ ተሳፍሮ
እያጉረመረመ ባሕሩን ተሻግሮ
ዮናስ ተደብቆ ሲሄድ በግስገሳ
ከእግዚአብሔር ተልዕኮ ማዕበል ተነሳ
ታላቅ ሞገድ ሆነ ባሕሩ ተቆጣ
መርከበኞች ፈሩ ታላቅ ሽብር መጣ
መርከቡ እንዲቃለል እናድርግ እያሉ
አንስተው ብዙ ዕቃ ወደ ባሕር ጣሉ
ባህሩም ባሰበት በጣም ተናወጠ
መረከቡ መሰለ የተገለበጠ
ሰው ሁሉ ተነሳ ጸሎት ለማድረስ
ይኽ ሁሉ ሲሆን ተኝቷል ዮናስ
ወደ ዮናስ ሄዶ የመርከቡ አለቃ
ቀሰቀሰው እና ከእንቅልፉ ሲነቃ
እግዜር እንዲያድነን ከዚህ ክፉ ጥፋት
ተነስ ጸልይ አለው ይብቃህ ማንቀላፋት
በመርከቡ ውስጥ ያሉ ሰዎች ተሰብስበው
ተመካከሩ እና ቢናገሩ አስበው
አለው ኃጢአት ሰርቶ ከእኛ ጋር የመጣ
ለይተን ለማወቅ እንጣጣል ዕጣ
አለዚያ አንድንም ስለተባባሉ
ተሰባሰቡና ዕጣ ቢጣጣሉ
እውነትም እንዳሉት አጥፊው ሰው ታወቀ
በእንቢተኛው ነብይ በዮናስ ወደቀ
በዮናስ ተረዳና እጁ እንደ ተያዘ
ያጠፋውን ጥፋት ገልጦ ተናዘዘ
ምነው ባትመጣ ተጣልተክ ከጌታ
እየው መርከባችን እንደሚንገላታ
ቁጣውን እንዲታገስ ለማግኘት ጸጥታ
በል አንተው ፍረደን ምን ይበጃል ቢሉ
ዮናስ መለሰና እዚህ ያለ ሁሉ
ስለምን ይጠፋል በእኔ የተነሳ
ወደ ባሕር ጣሉኝ አለብኝ አበሳ
ተመልከቱ እንሆ ስራውን ዐወቀ
ጥፋቱን ገለጠ ይኽው መች ደበቀ
እሱ ከፈረደ መልሶ በራሱ
ምን እናድርግ ብለው ሊጥሉት ተነሱ
ከደሙ አንጻን ሲሉ ለእግዜር አመልክተው
ወደ ባሕር ጣሉት ዮናስን አውጥተው
በዮናስ ላይ ኖር የመጣው ይህ ጥፋት
ባሕሩ ጸጥ አለ ልክ በዛው ሰዓት


ይቀጥላል.....

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ትንቢተ ዮናስ
ክፍል ፪
ዮናስም ተውጦ በእግዚአብሔር ፍቃድ
ሶስት ቀን ሶስት ለሊት ሊያድር በዓሣ ሆድ
ተቀይመህ ኖረህ ከላይ ብትቆጣ
እንዲህ ያለ መአት በራሴ ላይ መጣ
የባሕሩ ሞገድ እኔን አዋከበኝ
ውኃና ጨለማ ሲኦልም ከበበኝ
እያለ በአሳ ሆድ ዮናስ ሲቀመጥ
አምላኩን ለመነው በመለማመጥ
የታዛዥነትም ጠባይ እያሳየ
አዝኖ ተጸጽቶ ከልቡ ጸለየ
ምንጊዜም ቢቆጣ ነውና መሓሪ
ፊቱን መልሶለት ታረቀው ፈጣሪ
ዓሣውም ዮናስን ውጦ ሳያስቀረው
ከባሕር ተፋና መሬት ወረወረው

ይቀጥላል.....

@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ትንቢተ ዮናስ
ምዕራፍ፫
ይህንን የኔን ቃል ስማና በቶሎ
ሄደህ ለነነዌ እንድትነግራት ብሎ
ደገመና እግዚአብሔር ዮናስን አዘዘ
ነነዌ ሊገባ ዮናስም ተጓዘ
ድምጹን ከፍ አድርጎ ነቢዩ ዮናስም
ከዛሬ ጀምሮ አርባ ቀን ድረስ
ነነዌ ጠፊነች ከስር ተገልብጣ
አለና ለፈፈ የእግዚአብሔርን ቁጣ
ሳያንገራግሩ ሁሉም ቢለምኑ
የነነዌ ሰዎች ተጨንቀው አዘኑ
ከትልቅ ጀምሮ ሕፃኑ ድረስ
ሕይወቱ የቆመች በሥጋ በነፍስ
ሰውም ሆነ እንስሳ ይቀበል ንስሐ
ፍጡር ሁሉ ይጸልይ ይጹም ከእህል ውሃ
ሁሉም ከልብ አዝኖ ማቅ እየለበሰ
ከክፉ ወደ ደግ እየተመለሰ
መቼም ወሰን የለው የእግዚአብሔር ምሕረቱ
ይጸልይ አለና ይለምን በብርቱ
ንጉሡ አሳወጀ ከነ መኳንንቱ
የነነዌ ሰዎች በእውነት ከልቦና
መፀፀታቸውን እግዚአብሔር አየና
ፍጡር ቢለምነው እምባ እያፈሰሰ
ምሕረቱን አውርዶ መአቱን መለሰ።
ይቀጥላል...

@Mgetem

@Mgetem
#_የፍቅር_ቀን#

እኔ የማከብረው ሁሌ ምዘክረው
አለኝ የፍቅር ቀን አለኝ የማረሳው
ልቤን አሸንፎት በእንባ የማወሳው
የኔ ውድ አፍቃሪ በቀጠሮው ሰአት በቀጠሮው ቦታ
ሳያረፍድ ተገኝቶ በዛች በከፍታ
በደሙ ቀለበት ገብቶልኝ ቃልኪዳን
በእውነተኛ ፍቅር ለእውነተኛ መዳን
ልሙትልሽ ብሎ በፅኑ መሀላ
መውደዱን ገልጦልኝ እንድኖር በተድላ
በዛች በለተ አርብ በፍቅር ቀናችን
ፍቅሩን ገልጦልኛል
ቀይ አበባ ሳይሆን ቀይ ደም ሰቶኛል
ስለዚህ ያቺ ናት እርሷ ናት
የኛ ቀን የኔና የውዴ
ለአለም የታየበት በርሱ መወደዴ።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!


፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ክብርና ምስጋና ይግባው በእለተ አርብ ለተሰቀለው

@Mgetem
አንተ ሰው! ወንበዴ፣ ሌባ፣ ዘማዊም ፡ ብታይ ፡ አትፍረድበት! እንደ ፡ ፈያታዊ ፡ ዘየማን ፡ እኔን ፡ ቀድሞ ፡ መንግሥተ ፡ ሰማያት ፡ ይገባ ፡ እንደ ፡ ሆነ ፡ ምን ፡ አውቃለሁ ፡ ብለህ ፡ እለፍ ፡ እንጂ። “ትዳር አለኝ፤ ልጆችን አሳድጋለሁ፤ የቤት አባወራ ስለኾንኩኝ ይኽንን ማድረግ አልችልም” አትበሉኝ፡፡ ከእናንተ የሚፈለገው ፈቃዳችኁ ብቻ ነውና፡፡ ዕድሜም ቢኾን፣ ባለጸግነትም ቢኾን፣ ማጣትም ቢኾን ሌላም ቢኾን ይኽን ኹሉ ከማድረግ አይከለክላችሁምና፡፡ ምክንያቱም ሽማግሌዎችም፣ ወጣቶችም፣ ሚስቶችም፣ ሕፃናት አሳዳጊዎችም፣ ዕደ ጥበቦኞችም፣ ወታደሮችም ይኽን ኹሉ ፈጽመውታልና፡፡ ዳንኤል ወጣት ነበር፤ ሠለስቱ ደቂቅ ሕፃናት ነበሩ፤ ዮሴፍ ባርያ ነበር፤ ሉቃስ ሐኪም ነበር፤ ሊድያም ሐር ሻጭ ነጋዴ ነበረች፤ ጳውሎስንና ሲላስን በወኅኒ ሲጠብቅ የነበረውም ፖሊስ ነበር፤ ቆርነሌዎስ ደግሞ ዐሥራ አለቃ ነበር፤ ጢሞቴዎስ በሽተኛ ነበር… ነገር ግን ይኽን ከማድረግ የከለከላቸው አንዳችም ምክንያት የለም፡፡ እነዚኽ ኹሉ እንደ እኛ ሴቶች፣ እንደ እኛ ወጣቶች፣ እንደ እኛ ሽማግሎች፣ እንደ እኛ ነጋዴዎች፣ እንደ እኛ አሠሪዎች፣ እንደ እኛ ሠራተኞች፣ እንደ እኛ ወታደሮችና ሲቪል ነበሩ፡፡”
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ኦፍጡነ ረድኤት/2/
የእግዚአብሔር አገልጋይ ቅዱስ ሰማዕት
አዝ…………………………………………………………….
ሰላም ላንተ ይሁን ፍጡነ ረድኤት
የልዳው ፀሐይ ‘’ ‘’
በጨካ ንጉስ ፊት ቆምክ አደባባይ
ታማኝ አገልጋይ ነህ ፍጡነ ረድኤት
ስቃይ ያልበገረህ ‘’ ‘’
አክሊል አገኘህ መከራን ታግሰህ
አዝ…………………………………………………………….
የፈጣሪውን ስም ፍጡነ ረድኤት
ስለመሰከረ ‘’ ‘’
ጊዮርጊስ ሰማዕት በሰይፍ ተመተረ
የስቃይ መሳሪያ ፍጡነ ረድኤት
ያላዘናጋህ ‘’ ‘’
መንፈሳዊ አርበኛ ጊዮርጊስ አንተነህ
አዝ…………………………………………………………….
የጌታ ተጋዳይ ፍጡነ ረድኤት
ታማኝ ወታደር ‘’ ‘’
ቢነገር አያልቅም የተሰጠህ ክብር
ስቃይ ሲደርስብህ ፍጡነ ረድኤት
በመታገስህ ‘’ ‘’
ሲወሳ ይኖራል ዘላለም ስምህ
አዝ…………………………………………………………….
ለሰማው ይደንቃል ፍጡነ ረድኤት
ያንተ ሰማዕትነት ‘’ ‘’
ምሳሌ ይሆናል በሁሉ ፍጥረት
ገድሉ ይናገራል ፍጡነ ረድኤት
ክብር እንደተሰጠው ‘’ ‘’
ጊዜ የማይሽረው ምግባር ሃማኖት

💚 @yeorthodoxmezmur 💚
💛 @yeorthodoxmezmur 💛
❤️ @yeorthodoxmezmur ❤️
🌺❖በልዑል እግዚአብሔር ስም ይቅርታ❖🌺

ሰላመ እግዚአብሔር ይብዛላች የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦ በክርቶስ ክርስትያ በወልድ ውሉድ በመንፈስ ቅዱስ መንፈሳዊያን የሆናችው የድግል ማርያም ለጆች እንኳን ለታላቁ የአብይ ፆም በሰላም ቤጤና አደረጋች ፆሙ የበረከት የረድኤት የነብሳችን ድህነት የዳቢሎስ ድል መንሻ የአጥያት መደምሰሻ ይሁንልን ❖🌺ዘወረደ🌺

ሳላውቅ በስህተት አውቄም ሆነ በድፍረት በንፈሳዊ ማህበሮቼም ሆነ በጉደኝነት በኮሜን በማህበራዊ ሚድያም ብሆን ብበድል ባስከፋ ያስቀየምኳች ካላች በእግዚአብሔር ስም ይቅርታ አድርጉልኝ እወዳችዋለው 😰
ይቅርታ ውዴ ሆይ
ይቅርታ እህቴ ሆይ
ይቅርታ ወንድሜ ሆይ
ይቅርታ ወዳጄ ሆይ
ይቅርታ 🌺🌺
ይቅርታ 🌺🌺
https://youtu.be/dMoqfYGoPE8
የንስሀ መዝሙርነው

@Mgetem

@Mgetem

@Mgetem
    🍟🎂ተጠቃሚ ያጡ መድኃኒቶች🍛🍧🍟

🍡🍢1/ ቃለ እግዚአብሔር
               🌕🌒ጠዋት አንድ
               🌒🌙ማታ አንድ

🍢🍡2/ ንስሐ
           🌺በየሳምንቱ አንድ አንድ

🍢🍡3/ ስጋወ ደሙ
        🌹🌺🌼 ቢያንስ በ40 ቀን አንዴ

🍢🍡4/ ጸበል
      ከምግብ በፊት በየቀኑ አንዴ

🍢🍡5/ እምነት
         ❤️ዘወትር በየሰከንዱ ያለማቋረጥ

🍢🍡6/ ፍቅር
         💔ዘወትር ያለማቋረጥ ለሁሉም

🍢🍡7/ ሰላም
      🍁ለተከታታይ ሰዓታት እስከ ዘላለም

🍢🍡8/ጸሎት
 📕📗🙏 በቀን ሰባት ግዜ ያለማቋረጥ

🍢🍡9/ ፆም
   😒☺️ ከምግብ በፊት

🍬🍢10/ ምፅዋት
💰💷 በየቀኑ ከምታገኘው ጥቂቱን

🍢🍡11/ ስግደት
🙇🙇‍♀ ጠዋት 21
🙇‍♀🙇 ማታ 20

☞☞ማሳሰቢያ፡- ሁሉም መድኃኒቶች ተስፋ በተባለ ውሃ ማወራረጃነት መዋጥ ይኖርባቸዋል።
https://youtu.be/dMoqfYGoPE8
@Mgetem
Forwarded from Daregot Media
ተዋሕድዋ
የዓድዋ ድልና ተዋሕዷዊ ገድል

በዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ

፩.የእግዚአብሔርና የምኒልክ ሰይፍ

፪.ጣይቱ ምዕመኒቱ

፫. ካህናት፣ ታቦታት ፣መነኮሳት ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር

፬. የኢትዮጵያ ገበዝ በዓድዋ ጦሩን ሲመዝ

፭.የወታደሩ ሃይማኖት ይባስ!

፮. ቤተ ክርስቲያን ግን ለምን በጦርነቱ ተሳተፈች?

እንኳን ለሰማዕቱ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ክብረ በዓልና ለ124ኛው የአደዋ በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን ተከታዩን ጹሑፍ ታነቡት ዘንድ ዳረጎት ማዕዷን አቅርባለች፡፡

ሙሉ ጹሑፉን ያንብቡ 👉 https://telegra.ph/ተዋሕድዋ-03-01

©ዳረጎት ዘተዋሕዶ

Join us @daregot
፨የልቤ ማድጋ፨

ዘወትር ጠዋት ማታ
ስለፋ ስተጋ
እሞላለሁ ብዬ
የልቤን ማድጋ
ዛሬ በንስሐ
ሞላችልኝ ብዬ
በሐሰት ስቦርቅ
አይሎ ደስታዬ
ነገ ደግም ባዶ
ወና ሆና ሳያት
ኀዘኔ በርትቶ
ስሞክር ልሞላት
ጠብም ላይልላት
ደግም እየሞላች
ዳግም ስትጎድል
ምሬቴ አይሎ
ደክሜ እንዳልዝል
ከዚያ ከምንጩ ዳር
አግኝቼ አምላኬን
ዳግም ላይጎድልብኝ
ሞልተህ ማድጋዬን
ለስምህ ልዘምር
ላብዛ ምስጋናዬን።
@Mgetem
ይህቺ ጥፊ የኔ ናት"
መነኮስ አባ አርሳንዮስ በገባበት ገዳም ዉስጥ፣ እግዚአብሔርን
እያገለገለ ሲኖር አንድ ቀን ከገዳሙ ሕግ ዉጭ የሆነ ነገር
ይፈጽማል፡፡ ጥፋቱ ከገዳሙ አበምኔት ይደርስና አበምኔቱ አስበዉ
ብገስጸዉ ያፍራል፣ ዝም ብል ጥፋቱ ጥፋት ሳይመስለዉ ሊቀር ነዉ
አሉና፡፡ የሱን ረድዕ ጠርተዉ እንዲህ አሉት፡፡ "አርሳንዮስ ያጠፋዉን
ጥፋት እኔ እያየሁህ በእርሱ ፊት አንተ አጥፋ ከዛ በጥፊ
እመታሃለሁ፡፡ ያኔ እርሱ በአንተ ጥፊ ይማራል አሉት፡፡"
እንደተመካከሩት በአርሳንዮስ ፊት ረድኡ የእርሱን ጥፋት አጠፋ
አበምኔቱም ተቆጥተዉ በጥፊ መቱት በዚህ ጊዜ ነገሩን የተከታተለዉ
አርሳንዮስም "ይህች ጥፊ የኔ ናት" ብሎ ተናገረ፡፡
እግዚአብሔር እኛን ባጠፋነዉ ቅጣት የግድ እስከሚቀጣን ቁጭ
ብለን መጠበቅ የለብንም ፣ከሌላዉ ጥፋት፣ ከሌላዉ ቅጣት መማር
አለብን፡፡ ከሌላዉ ጥፋት መማር ትልቅ ዕዉቀት፣ ታላቅ ማስተዋል
ነዉ፡፡ አርሳንዮስ ጓደኛዉ በጥፊ ሲመታ፣ ይች ጥፊ የኔ ናት አለ እንጂ
ባጠፋዉ ጥፋት ነዉ የተቀጣዉ ብሎ አልፈረደበትም፡፡ እኛም ቁጣ፣
መቅሰፍት፣ እኛ ጋር እስኪመጣ መጠበቅ የለብንም ከጓደኞቻችን
ከጎረቤቶቻችን በሌላም ሀገር ከምናየዉ ከምንሰማዉ ተምረን ንስሓ
መግባት አለብን ጾም ማለትም ይህ ነዉ፡፡ ንስሐ የምንገባዉም
ኃጢአታችንን ስናስተዉል ነዉ፡፡ ማስተዋል ከሌለን ኃጢአቱን እንደ
ጽድቅ ቆጥረን ለንስሐ አንበቃም፡፡
ማስተዋልን ገንዘብ ያደረገ ምዕመን በሌላ ላይ የተደረገ ቅጣት
በርሱ ላይ እንደመጣ ይጠነቀቃል፡፡ እንደ ርግብ የዋህ እንደ እባብ
ብልህ በመሆን የነገሮችን ሁኔታ በማስተዋል ይከታተላል፡፡ ከሰብአ
ትካት ከሰዶም ይማራል ሎጥ የዳነበትን መንገድ ይከተላል ቃሉን
በመስማት በኖህ መርከብ በተመሰለች ቅድስት ቤተክርስቲያን
ይገኛል እራሱን በንስሐ በሥጋ ወደሙ በጸሎት በእግዚአብሔር
ቸርነት ከሚመጣዉ መቅሰፍት ያድናል፡፡
የአባቶቻችን በረከታቸው ይደርብን አሜን፡፡
https://youtu.be/dMoqfYGoPE8
@Mgetem
የአብይ ፆም
፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ሦስተኛ ሰንበት(ሳምንት)

ምኩራብ ተብሎ ይታወቃል።
በዚህ ቀን ቤተ መቅደስን አስመልክቶ ትምህርት ይሰጣል። ጌታችንም በምኩራብ ገብቶ
ስለማስተማሩ በሰፊው ይነገራል።
ምስባኩም፦ መዝ.፷፰፡፱ ነው።
እስመ ቅንዐተ ቤትከ በልዐኒ የቤትህ ቅናት በልቶኛል
ትዕይርቶሙ ለእለይትዔየሩከ ወድቀ ላዕሌየ የሚሰድቡህምስድብ በላዬ ወድቆብኛልና
ወቀጻዕክዋ በጾም ለነፍስየ ነፍሴን በጾም አስመረርኩአት
ወንጌሉም ዮሐ.፪፡፲፪-እስከ ፍጻሜ ነው።
በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡት ጥቅሶችም፦
ቆላ.፪፡፲፮-እስከ ፍጻሜ፤
ያዕ.፪፡፲፬-እስከ ፍጻሜ፤
የሐዋ.ሥራ ፲፡፩-፱ ።
@Mgetem
Forwarded from Daregot Media
​​​​​​​​#ሕፃን_መፃጕዕ
(ውርስ ትርጉም)
ከሣቴብርሃን ገብረኢየሱስ
@Mgetem

“ብላቴና” የሚል፤
ከግብሩ የተነሣ የተሰጠው ቅፅል፤
በትርጓሜ ወንጌል የሚነበብ ሰፍሮ፤
መፃጕዕ መፃጕዕ ሕፃነ አእምሮ፤
ጨቅላ ነው ፤ ትክክል!
ምንም ነፍስ የማያውቅ፤
እሳትና ውሃን መለየት የማይችል።

ቢለይማ ኖሮ፤
ከእሳተ መለኮት ፤ እጁን ይልክ ነበር ፤ ለጥፊ ሰንዝሮ ?
......................................................
መነሻ ቅኔ ፦ ዕዝል ጉባዔ ቃና
ዘመሪጌታ ጥበበ ደስታ

 ሕፃን ኢያእመሬ ነፍስ ዓዲ፤ 
አኮኑ ፈነወ እዴሁ መንገለ እሳት ነዳዲ

.......................................................
መፃጕዕ ለ 38 ዓመት ሲማቅቅበት ከነበረ ደዌው የፈወሰው ክርስቶስን በቤተመቅደስ በጥፊ ስለ መምታቱ መሪጌታ ጥበበ ደስታ የተቀኙትን ቅኔ መነሻ በማድረግ የተገጠመ
ከሣቴብርሃን ገብረኢየሱስ
.......................................................
@Mgetem
@Mgetem
@Scgpx9
2025/07/07 12:48:50
Back to Top
HTML Embed Code: