#አዳም_ሆይ_የት_አለህ?
(ዲ/ን ዐብይ ሙሉቀን)
@Mgetem
@Mgetem
አትብላ ስትባል በለሲቱን በላህ
አምላክ መሆን ስትሻ ከክብርህ ተዋርደህ
ከገነት ኮብልለህ ወዴት ነው የገባህ?
አዳም ሆይ የት አለህ?
ዛሬም እንደ ጥንቱ መብላትን ትሻለህ?
አንተን የፈለገህ ላንተ የሞተልህ
በለሲቱን ሳይሆን ዕፅ ህይወት ሰጠህ
አዳም ሆይ የት አለህ?
ብላ ይኸውልህ።
@Yohannes_mariyam
(ዲ/ን ዐብይ ሙሉቀን)
@Mgetem
@Mgetem
አትብላ ስትባል በለሲቱን በላህ
አምላክ መሆን ስትሻ ከክብርህ ተዋርደህ
ከገነት ኮብልለህ ወዴት ነው የገባህ?
አዳም ሆይ የት አለህ?
ዛሬም እንደ ጥንቱ መብላትን ትሻለህ?
አንተን የፈለገህ ላንተ የሞተልህ
በለሲቱን ሳይሆን ዕፅ ህይወት ሰጠህ
አዳም ሆይ የት አለህ?
ብላ ይኸውልህ።
@Yohannes_mariyam
👍5
አምስተኛ ሰንበት(ሳምንት)
፨፨፨፨፨፨፨፨✞፨፨፨፨፨፨፨
ደብረ ዘይት ተብሎ ይታወቃል።
በዚህ ቀን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር ስለመምጣቱ (ዳግም
ምፅአቱ) ይሰበካል። ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ
መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል ደ/ሰ/መ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤ/ት/ክ
የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ
የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸው ክፉም ላደረጉ
የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል። ጌታም የአባቴ ቡሩካን የተዘጋጀላችሁን
የክብር ቦታ ውረሱ በማለት ወዳጆቹን እንደሚጠራ ይነገራል።
ምስባኩም፦ መዝ.፵፱፡፫ ነው።
እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽዕ እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል
ወአምላክነሂ ኢያረምም አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ እሳት በፊቱ ይቃጠላል
ወንጌሉም ማቴ.፳፬፡፩-፴፮ ነው።
በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡት ጥቅሶችም፦
፩ተሰ.፬፡-፲፫-እስከ ፍጻሜ፤
፪ጴጥ.፫፡፯-፲፭፤
የሐዋ.ሥራ ፳፬፡፩-፳፪ ።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
፨፨፨፨፨፨፨፨✞፨፨፨፨፨፨፨
ደብረ ዘይት ተብሎ ይታወቃል።
በዚህ ቀን ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግም ወደ ምድር ስለመምጣቱ (ዳግም
ምፅአቱ) ይሰበካል። ይህን ዓለምንም አሳልፎ ለመረጣቸውና ላከበራቸው ዘላለማዊ
መንግሥትን ሊያወርሳቸው እንደሚመጣ ይነገርበታል። ይህ ቀንም እኩለ ፆም በመባል ደ/ሰ/መ/ኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ/ሰ/ት/ቤ/ት/ክ
የሚታወቅ ሲሆን በዚህች በተለየች ቀንም ሁሉም እንደ የሥራው ፍርዱን ከአምላክ
የሚቀበልበት መሆኑ፤ መልካም ላደረጉ መልካም እንደሚመለስላቸው ክፉም ላደረጉ
የክፋታቸውን ዋጋ እንደሚያገኙ ይሰበካል። ጌታም የአባቴ ቡሩካን የተዘጋጀላችሁን
የክብር ቦታ ውረሱ በማለት ወዳጆቹን እንደሚጠራ ይነገራል።
ምስባኩም፦ መዝ.፵፱፡፫ ነው።
እግዚአብሔርሰ ገሀደ ይመጽዕ እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል
ወአምላክነሂ ኢያረምም አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም
እሳት ይነድድ ቅድሜሁ እሳት በፊቱ ይቃጠላል
ወንጌሉም ማቴ.፳፬፡፩-፴፮ ነው።
በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡት ጥቅሶችም፦
፩ተሰ.፬፡-፲፫-እስከ ፍጻሜ፤
፪ጴጥ.፫፡፯-፲፭፤
የሐዋ.ሥራ ፳፬፡፩-፳፪ ።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍3❤1
🔔ቅዱስ ፓትርያርኩ ኮሮናን በተመለከተ ሃይማኖታዊ መመሪያ ሰጡ
--------------
ፓትርያርኩ በዓለም ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ለመቋቋም እንዲያስችል ምእመናንም ሆኑ ካህናት ማድረግ ያለባቸውን እና ማድረግ የሌለባቸውን ተግባራት የለየ ዝርዝር መመሪያ ሰጡ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊቀ ጳጳስ ዘአኩሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተ/ሃይማኖት ዛሬ ባስተላለፉት አባታዊ መመሪያ ቋሚ ሲኖዶስ ተወያይቶ ያስተላለፈው ነው ያሏቸውን 13 ነጥቦች በጽሑፍ አቅርበዋል።
የትኛውም ዓይነት መንፈሳዊ ጉዞዎች፣ የትምህርት እና የስብከት ጉባኤዎች የተከለከሉ ሲሆን በቅዳሴ እና በሌሎች የቤተ መቅደስ አገልግሎቶች ሊኖር ስለሚገባው የሰዎች መቀራረብም መመሪያ ሰጥቷል።
(የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን
+++++++++++++++++
በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ፤
በሀገራችን ኢትዮጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!
ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝብን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡
ስለዚህ ቋሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-
1. በሰሙነ ሕማማት እንደምናደርገው የእርስ በርስ መሳሳም ቀርቶ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ እጅ በመንሳት ወይም በእማሄ ሰላምታ በማቅረብ እንዲፈጸም፣
2. ወረርሽኙ በሰዎች መሰባሰብ የሚስፋፋ ስለሆነ ማናቸውም መንፈሳዊ ጉባኤያት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት፣ ወደ ገዳማትና አድባራት የሚደረጉ ጉዞዎች እና ምዕመናን የሚሳተፉባቸው ታላላቅ መርሐ ግብሮች ለጊዜው እንዲቋረጡ፣
3. ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባም ሆነ አሰፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ እጆቻንን በመታጠብና ዘርዘር ብሎ በመቆም ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጸም፣
4. ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት በቅዳሴና በማኅሌት ታስበው ክብረ በዓላቱ በሌላ ጊዜ እንዲከበሩ፣
5. የጉንፋን ምልክት ያለባቸው ለሌሎች እንዳያስተላልፉ በቤታቸው በጥንቃቄ ተለይተው በጸሎትና በሕክምና እንዲቆዩ፣ ከቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን መንፈሳዊ አገልግሎትም በልዩ ሁኔታ እንዲያገኙ፣
6. በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የተስፋ ልዑክ በመሆን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ተደራጅቶ ተልዕኮውን በአስቸኳይ እንዲጀምር
7. ሥርዓተ ቅዳሴን በተመለከተ፡-
• በቤተ መቅደስ ቀዳስያን በሆኑት ልዑካን ብቻ ሥርዓተ ቅዳሴው እንዲፈጸምና ሌሎች አገልጋዮች በቅድስቱ ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያገለግሉ፣
• በዕለቱ ለሚቆርቡ ምዕመናን ለአረጋውያን፣ ለወጣቶችና ለሕፃናት የፈረቃ ተራ በማዘጋጀት ቆራቢዎች ብቻ ወደ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያስቀድሱ፣
• ሌሎች ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ቢያንስ ሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ያህል በመራራቅ ቆመው እንዲያስቀድሱ፣
• የቅዳሴ ጠበል በየግል መጠቀሚያ ምእመናን በየቆሙበት ቦታ በጥንቃቄ እንዲሰጥ፣
• ሌሎች ከቅዳሴ ጋር የተያያዙ ዝርዝር የአፈፃፀም ጉዳዮችን ግብረ ኃይሉ አዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለአህጉረ ስብከት በሚልከው መመሪያ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ፤
8. ከሥርዓተ ቅዳሴ በተጨማሪ እንደ ስብሐተ ነግሕ፣ ሰዓታት፣ ቁመተ ማኅሌት፣ ጥምቀተ ክርስትና፣ ጸሎተ ፍትሐት፣ የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለሥርዓቱ በሚያስፈልገው ቁጥር ብቻ እና በውሱን ሊቃውንት በተራ እንዲፈፀም፣
9. ወረርሽኙ ከዓለም እንዲጠፋ ካህናት ብቻ በቤተ መቅደስ፣ በዐውደ ምኅረትና በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ጸሎተ እጣን በማድረስ ማዕጠንት እንዲፈጽሙ፣
10. በማኅበራዊ ግንኙነት በደስታ፣ በሐዘን፣ በእድር፣ በሥርዓተ ቀብር አፈፃፀምና በመሳሰሉት መሰባሰቦች በሽታው እንዳይሠራጭ አገልግሎቱ በውስን የሰው ቁጥር በጥንቃቄ እንዲፈፀም፤
11. ምዕመናን ራሳቸውን እየጠበቁ በቫይረሱ የተጠቁና አገግመው የወጡ ወገኖችን፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ከሃይማኖትና ከምግባር የወጣ መገለልና ጥቃት እንዳይደርስባቸው በክርስቲያናዊ ፍቅርና በኢትጵያዊ ጨዋነት እንክብካቤ እንዲደረግላቸው፣
12. ለነዳያን እና ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊው ማኅበራዊ እና ቁሳዊ እገዛ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲደረግ፣
13. ቤተ ክርስቲያንን ከማይወክሉና ቀኖናዊ ካልሆኑ አሳሳች መረጃዎች በመቆጠብ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ መምህራን፣ ሰባክያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መመሪያዎችን በየአጥቢያችሁና አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ እንድትፈጽሙ እና እንድታስፈጽሙ ተወስኗል፡፡
በአጠቃላይ በበሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምህረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፤
በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፤
በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠበቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ/ም
አዲስ አበባ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
--------------
ፓትርያርኩ በዓለም ላይ እየተስፋፋ የመጣውን የኮሮና ቫይረስ ለመቋቋም እንዲያስችል ምእመናንም ሆኑ ካህናት ማድረግ ያለባቸውን እና ማድረግ የሌለባቸውን ተግባራት የለየ ዝርዝር መመሪያ ሰጡ።
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊቀ ጳጳስ ዘአኩሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተ/ሃይማኖት ዛሬ ባስተላለፉት አባታዊ መመሪያ ቋሚ ሲኖዶስ ተወያይቶ ያስተላለፈው ነው ያሏቸውን 13 ነጥቦች በጽሑፍ አቅርበዋል።
የትኛውም ዓይነት መንፈሳዊ ጉዞዎች፣ የትምህርት እና የስብከት ጉባኤዎች የተከለከሉ ሲሆን በቅዳሴ እና በሌሎች የቤተ መቅደስ አገልግሎቶች ሊኖር ስለሚገባው የሰዎች መቀራረብም መመሪያ ሰጥቷል።
(የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ይነበባል)
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡ አሜን
+++++++++++++++++
በመላው ዓለም የተስፋፋውን የኮሮና ወረርሽኝ ለመግታት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የተሰጠ መግለጫ፤
በሀገራችን ኢትዮጵያ በገጠር፣ በከተማና በመላው ዓለም ለምትገኙ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን በሙሉ!
ወቅታዊ የሰው ልጅ ሥጋት በመሆን በመላው ዓለም በፍጥነት በተስፋፋው የኮሮና ወረርሽኝ ምክንያት ዓለም አቀፍ ሥጋት ስለተከሰተ መንግሥታት ሀገርን ከጥፋት፣ ሕዝብን ከሞት ለመጠበቅ አዋጆችን እያወጡ ይገኛሉ፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ሕይወት ለመታደግ እምነትና ቀኖናን ጠብቆ ሃይማኖታዊ መመሪያ የመስጠት ሐዋርያዊ ኃላፊነት አለባት፡፡
ስለዚህ ቋሚ ሲኖዶስ የጉዳዩን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት መሠረተ እምነትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ጠብቆ ለሁሉም ካህናትና ለሕዝበ እግዚአብሔር ደኅንነት ሲባል የሚከተሉትን መመሪያዎች አስተላልፏል፡-
1. በሰሙነ ሕማማት እንደምናደርገው የእርስ በርስ መሳሳም ቀርቶ ራስን ዝቅ በማድረግ፣ እጅ በመንሳት ወይም በእማሄ ሰላምታ በማቅረብ እንዲፈጸም፣
2. ወረርሽኙ በሰዎች መሰባሰብ የሚስፋፋ ስለሆነ ማናቸውም መንፈሳዊ ጉባኤያት፣ የትምህርት ክፍለ ጊዜያት፣ ወደ ገዳማትና አድባራት የሚደረጉ ጉዞዎች እና ምዕመናን የሚሳተፉባቸው ታላላቅ መርሐ ግብሮች ለጊዜው እንዲቋረጡ፣
3. ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲገባም ሆነ አሰፈላጊ በሆነበት ጊዜ ሁሉ እጆቻንን በመታጠብና ዘርዘር ብሎ በመቆም ሥርዓተ አምልኮ እንዲፈጸም፣
4. ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት በቅዳሴና በማኅሌት ታስበው ክብረ በዓላቱ በሌላ ጊዜ እንዲከበሩ፣
5. የጉንፋን ምልክት ያለባቸው ለሌሎች እንዳያስተላልፉ በቤታቸው በጥንቃቄ ተለይተው በጸሎትና በሕክምና እንዲቆዩ፣ ከቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋቸውን መንፈሳዊ አገልግሎትም በልዩ ሁኔታ እንዲያገኙ፣
6. በቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ የተቋቋመው ግብረ ኃይል የተስፋ ልዑክ በመሆን እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ተደራጅቶ ተልዕኮውን በአስቸኳይ እንዲጀምር
7. ሥርዓተ ቅዳሴን በተመለከተ፡-
• በቤተ መቅደስ ቀዳስያን በሆኑት ልዑካን ብቻ ሥርዓተ ቅዳሴው እንዲፈጸምና ሌሎች አገልጋዮች በቅድስቱ ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያገለግሉ፣
• በዕለቱ ለሚቆርቡ ምዕመናን ለአረጋውያን፣ ለወጣቶችና ለሕፃናት የፈረቃ ተራ በማዘጋጀት ቆራቢዎች ብቻ ወደ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገብተው ዘርዘር ብለው በመቆም እንዲያስቀድሱ፣
• ሌሎች ምእመናን በአጸደ ቤተክርስቲያን ቢያንስ ሁለት የትልቅ ሰው እርምጃ ያህል በመራራቅ ቆመው እንዲያስቀድሱ፣
• የቅዳሴ ጠበል በየግል መጠቀሚያ ምእመናን በየቆሙበት ቦታ በጥንቃቄ እንዲሰጥ፣
• ሌሎች ከቅዳሴ ጋር የተያያዙ ዝርዝር የአፈፃፀም ጉዳዮችን ግብረ ኃይሉ አዘጋጅቶ በቅዱስ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለአህጉረ ስብከት በሚልከው መመሪያ መሠረት ተግባራዊ እንዲደረግ፤
8. ከሥርዓተ ቅዳሴ በተጨማሪ እንደ ስብሐተ ነግሕ፣ ሰዓታት፣ ቁመተ ማኅሌት፣ ጥምቀተ ክርስትና፣ ጸሎተ ፍትሐት፣ የመሳሰሉ አገልግሎቶች ለሥርዓቱ በሚያስፈልገው ቁጥር ብቻ እና በውሱን ሊቃውንት በተራ እንዲፈፀም፣
9. ወረርሽኙ ከዓለም እንዲጠፋ ካህናት ብቻ በቤተ መቅደስ፣ በዐውደ ምኅረትና በአጸደ ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ ጸሎተ እጣን በማድረስ ማዕጠንት እንዲፈጽሙ፣
10. በማኅበራዊ ግንኙነት በደስታ፣ በሐዘን፣ በእድር፣ በሥርዓተ ቀብር አፈፃፀምና በመሳሰሉት መሰባሰቦች በሽታው እንዳይሠራጭ አገልግሎቱ በውስን የሰው ቁጥር በጥንቃቄ እንዲፈፀም፤
11. ምዕመናን ራሳቸውን እየጠበቁ በቫይረሱ የተጠቁና አገግመው የወጡ ወገኖችን፣ እንዲሁም በውጭ ሀገር ዜጎች ላይ ከሃይማኖትና ከምግባር የወጣ መገለልና ጥቃት እንዳይደርስባቸው በክርስቲያናዊ ፍቅርና በኢትጵያዊ ጨዋነት እንክብካቤ እንዲደረግላቸው፣
12. ለነዳያን እና ለተቸገሩ ወገኖች አስፈላጊው ማኅበራዊ እና ቁሳዊ እገዛ በሁሉም አጥቢያዎች እንዲደረግ፣
13. ቤተ ክርስቲያንን ከማይወክሉና ቀኖናዊ ካልሆኑ አሳሳች መረጃዎች በመቆጠብ ሊቃውንት፣ ካህናት፣ መምህራን፣ ሰባክያን፣ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች ከቅዱስ ሲኖዶስ የሚሰጡ መመሪያዎችን በየአጥቢያችሁና አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ሁሉ እንድትፈጽሙ እና እንድታስፈጽሙ ተወስኗል፡፡
በአጠቃላይ በበሽታው እስካሁን ለተያዙት፣ በጊዜያዊ ማቆያ ለሚገኙት በሙሉ እግዚአብሔር አምላካችን ምህረቱን እንዲሰጥልን እንጸልያለን፤
በመላው ዓለም ዜጎቻቸውን በበሽታው ለተነጠቁ ሁሉ መጽናናቱን እንዲሰጥልን ያረፉትንም እንዲምርልን እግዚአብሔርን በጸሎት እንጠይቃለን፤
በመላው ዓለም የምትገኙ ወገኖቻችን የራሳችሁና የሌሎች ሕይወት ከወረርሽኙ እንዲጠበቅ እንዲሁም የበሽታው ሥርጭት እንዲቆም መንፈሳዊና ማኅበራዊ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እያሳሰብን የተሰጡት መመሪያዎች ወረርሽኙ እስኪጠፋ ድረስ የጸኑ እንዲሆኑ በጥብቅ እናስታውቃለን፡፡
ልዑል እግዚአብሔር በቸርነቱና በይቅርታው ብዛት ዓለማችንን ከጥፋት የሰውን ልጅ ሁሉ ከመከራ ሞት ይጠብቅልን፡፡ አሜን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
መጋቢት 14 ቀን 2012 ዓ/ም
አዲስ አበባ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
👍8🤬2
ለሙሴ የተጻፈ ደብዳቤ
አንተ የእግዚአብሔር ወዳጅ ነቢዩ ሙሴ ሆይ ለጤናህ እንዴት ነህ?
ለነገሩ አንተ ጤነኛ ነህ በሰማይ ቤት ሁነህ ደግሞ ምን ያገኝህ።እኔ ምልህ ሙሴ ባለቤትህ ሲጳራ ደህናናት አማትህስ ዮቶር እንዴት ናቸው?ሰሞኑን በሀገራቸው ኢትዮጵያ በተሰማው ወሬ ምን ተሰምቷቸው ይሆን?መቼም ሲያስነጥሱ ይበክሉናል ብለው ፊታቸውን አላዞሩብንም አይደል?ስማኝማ ሙሴ ቆይ ያኔ እስራኤልን ከፈርኦን መንጋጋ በ10 መቅሰፍት በ 11ኛ ስምጠተ ባህር ስትታደግ በበኩር ልጅ ሞት ግብጻውያን ሲያልቁ እስራኤላውያን ግን በፍሲካ በግ ደም መቃንና ጉበኑን ረጭተው ከሞት እንደተረፋችሁ፤ፍርኦን ሊገድላችሁ ኪትላዎቹን አስከትሎ ሲመጣ በብትርህ ባህር ከፍለህ እንደተሻገራችሁ፤በዛ በበረሀ እባብ ተነስቶ ህዝቡን ሲጨርሰው የእባብ ምስል ሰርተህ እንደታደግሀቸው እናውቃለን።እግዚአብሔርም እንዴት እንዳከበረህ እንደወደደህ በፈርኦን ላይ አምላክ ዘበጸጋ አድርጎ ሲያሰለጥንህ ተርድተናል።ሙሴ ሆይ ከእህትህ ከማርያም ጋር በተቀያየምህባት በሚስትህ በሲጳራ ሀገር የመጣውን ውርጅብኝ እንደሰማህ እንዳየህ ተስፍ አደርጋለሁ።ስማኝማ ሙሴ እስራኤል ዘነፍስ የተባሉ ኢትዮጵያዊው ሁሉ ተሸብሯል።እንደዚህም ሁኗል፦
1 ሰላም በጠፍባት ሀገር ሰላምታተከልክሏል።ይሄ መከልከልስ በሰሙነ ህማማት በሆነ ጥሩ ነበር
2 ህዝቡ እንዳይቀራረብ በ 2 ሜትር እርቀት እንዲጓዝ ተወስኗል
3 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከግቢ መውጣት ተከልክለው ቤተ እግዚአብሔር ናፍቋቸዋል።
4 ህዝቡ በወሬ ብቻ ሳይታመም ታሟል።
ሙሴ ሆይ መቸም በነፍስም በስጋም ተዛምደናል እና ታዲያ ዝምድናችን በችግር ጊዜ መረዳጃ ካልሆነ ምኑን ዝምድና ሆነ።እባክህ መፍትሄ ንገረን ያደረግንልህን እንክብካቤ መቼም አትረሳም።ምን እናድርግ ንገረን መቼም በግ አርዳችሁ ደም እርጩ በትሬንም እንኩ የኮሮና ምልክት ስቀሉ አትለንም።ምክንያቱም እንኳን በምሳሌው እውነተኛ የክስቶስን ደም የአፍችንን እና የልባችንን መቃንና ጉበን ቀብተን እምነት ጎድሎን ውሃ ላይ እንዳለች ኩበት ሁነናል፤በትርህንም አንፈልግም ምክንያቱም እውነተኛው የክርስቶስ መስቀል በእጃችን ነው።ለነገሩ ትንሽ ከሰነበትን ሥጋ እና ደሙን የምንቀበልበት ከቤታችን እናምጣ የሚያቀብሉን መስቀል የሚያሳልሙን ካህናትና ዲያቆናት አፍቸውንና እጃቸውን ይሸፍኑ ማለታችን አይቀርም።አሜሪካ እና ቻይና የሆኑትን ነበር መሆን ምንፈልግ ይሄው እዛ ሳንሄድ እዚሁ መሰልናቸው።በብልጽግናቸው ባንመስላቸው እግዚአብሄር ይመስገን ኮሮና አመሳስሎናል።እባክህ እነሱን አንምሰል ጤነኛ እንድንሆን ምን እናድርግ ንገረን።ወይ ከእግዚአብሔር ተማክረህ ሀኪም ሉቃስን ላክልን አልያም እኔን ከህይወት መጽሐፍ ሰርዘኝ እንጅ ህዝቡን አትንካ የሚል እረኛ ይነሳልን።ምንደኛው እኮ በዛብን።በዛውም አማትህ ዮቶርን ላክልን ህዝብ እንዴት እንደሚመራ መሪያችንን ያስተምርልንን።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨@Mgetem_bot
አንተ የእግዚአብሔር ወዳጅ ነቢዩ ሙሴ ሆይ ለጤናህ እንዴት ነህ?
ለነገሩ አንተ ጤነኛ ነህ በሰማይ ቤት ሁነህ ደግሞ ምን ያገኝህ።እኔ ምልህ ሙሴ ባለቤትህ ሲጳራ ደህናናት አማትህስ ዮቶር እንዴት ናቸው?ሰሞኑን በሀገራቸው ኢትዮጵያ በተሰማው ወሬ ምን ተሰምቷቸው ይሆን?መቼም ሲያስነጥሱ ይበክሉናል ብለው ፊታቸውን አላዞሩብንም አይደል?ስማኝማ ሙሴ ቆይ ያኔ እስራኤልን ከፈርኦን መንጋጋ በ10 መቅሰፍት በ 11ኛ ስምጠተ ባህር ስትታደግ በበኩር ልጅ ሞት ግብጻውያን ሲያልቁ እስራኤላውያን ግን በፍሲካ በግ ደም መቃንና ጉበኑን ረጭተው ከሞት እንደተረፋችሁ፤ፍርኦን ሊገድላችሁ ኪትላዎቹን አስከትሎ ሲመጣ በብትርህ ባህር ከፍለህ እንደተሻገራችሁ፤በዛ በበረሀ እባብ ተነስቶ ህዝቡን ሲጨርሰው የእባብ ምስል ሰርተህ እንደታደግሀቸው እናውቃለን።እግዚአብሔርም እንዴት እንዳከበረህ እንደወደደህ በፈርኦን ላይ አምላክ ዘበጸጋ አድርጎ ሲያሰለጥንህ ተርድተናል።ሙሴ ሆይ ከእህትህ ከማርያም ጋር በተቀያየምህባት በሚስትህ በሲጳራ ሀገር የመጣውን ውርጅብኝ እንደሰማህ እንዳየህ ተስፍ አደርጋለሁ።ስማኝማ ሙሴ እስራኤል ዘነፍስ የተባሉ ኢትዮጵያዊው ሁሉ ተሸብሯል።እንደዚህም ሁኗል፦
1 ሰላም በጠፍባት ሀገር ሰላምታተከልክሏል።ይሄ መከልከልስ በሰሙነ ህማማት በሆነ ጥሩ ነበር
2 ህዝቡ እንዳይቀራረብ በ 2 ሜትር እርቀት እንዲጓዝ ተወስኗል
3 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ከግቢ መውጣት ተከልክለው ቤተ እግዚአብሔር ናፍቋቸዋል።
4 ህዝቡ በወሬ ብቻ ሳይታመም ታሟል።
ሙሴ ሆይ መቸም በነፍስም በስጋም ተዛምደናል እና ታዲያ ዝምድናችን በችግር ጊዜ መረዳጃ ካልሆነ ምኑን ዝምድና ሆነ።እባክህ መፍትሄ ንገረን ያደረግንልህን እንክብካቤ መቼም አትረሳም።ምን እናድርግ ንገረን መቼም በግ አርዳችሁ ደም እርጩ በትሬንም እንኩ የኮሮና ምልክት ስቀሉ አትለንም።ምክንያቱም እንኳን በምሳሌው እውነተኛ የክስቶስን ደም የአፍችንን እና የልባችንን መቃንና ጉበን ቀብተን እምነት ጎድሎን ውሃ ላይ እንዳለች ኩበት ሁነናል፤በትርህንም አንፈልግም ምክንያቱም እውነተኛው የክርስቶስ መስቀል በእጃችን ነው።ለነገሩ ትንሽ ከሰነበትን ሥጋ እና ደሙን የምንቀበልበት ከቤታችን እናምጣ የሚያቀብሉን መስቀል የሚያሳልሙን ካህናትና ዲያቆናት አፍቸውንና እጃቸውን ይሸፍኑ ማለታችን አይቀርም።አሜሪካ እና ቻይና የሆኑትን ነበር መሆን ምንፈልግ ይሄው እዛ ሳንሄድ እዚሁ መሰልናቸው።በብልጽግናቸው ባንመስላቸው እግዚአብሄር ይመስገን ኮሮና አመሳስሎናል።እባክህ እነሱን አንምሰል ጤነኛ እንድንሆን ምን እናድርግ ንገረን።ወይ ከእግዚአብሔር ተማክረህ ሀኪም ሉቃስን ላክልን አልያም እኔን ከህይወት መጽሐፍ ሰርዘኝ እንጅ ህዝቡን አትንካ የሚል እረኛ ይነሳልን።ምንደኛው እኮ በዛብን።በዛውም አማትህ ዮቶርን ላክልን ህዝብ እንዴት እንደሚመራ መሪያችንን ያስተምርልንን።
✨✨✨✨✨✨✨✨✨@Mgetem_bot
👍5❤2
"የቤተ ክርስትያን መመሪያ ከእምነት መጉደል ቆጥሮ የሚተች ሰው ካለ በጠንካራ እምነቱ ኮሮናን በማስወገድ እንዲገላግለን በትሕትና እንማፀናለን"
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#stayathome
#በቤትመሆንመልካምነው
#Manaturuungaaridha
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_Bot
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
#stayathome
#በቤትመሆንመልካምነው
#Manaturuungaaridha
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_Bot
👍1
Forwarded from Daregot Media
ውድ የዳረጎት መጽሔት አንባቢዎች
እነሆ ዳረጎታችን በቁጥር 6 ዕትሟ ወደ እናንተ ልትደርስ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርቷታል፡፡ ዳረጎትን ለመቋደስና ከማዕዷ ለመካፈል የምትሹ ሁሉ እጃችሁን ታጥባችሁ፣ ማህበራዊ ርቀታችሁን ጠብቃችሁና እንደው ግድ ካላለ በቀር ከቤት ሳይወጡ በጸሎት ተግተው እንዲጠብቁን እያልን ከቀናት በኀላ ዳረጎታችንን ይዘን እንቀርባለን፡፡
ከጥንቱም ተካፍሎ መብላት ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነውና በዚህ ሰዓት ሥጋዊ መብል ላጡት ካለን እያካፈልን ለመንፈሳዊው መብል ደግሞ ዳረጎት ይዛ የቀረበችውን መጽሔታችንን ለሚወዱት እንዲያጋሩና ከገበታችን እንዲሰየሙ ( ገጻችንን እንዲቀላቀሉ ) ከወዲሁ በክርስቶስ ፍቅር እንለምናችኀለን፡፡
Join Us @daregot
እነሆ ዳረጎታችን በቁጥር 6 ዕትሟ ወደ እናንተ ልትደርስ ጥቂት ቀናት ብቻ ቀርቷታል፡፡ ዳረጎትን ለመቋደስና ከማዕዷ ለመካፈል የምትሹ ሁሉ እጃችሁን ታጥባችሁ፣ ማህበራዊ ርቀታችሁን ጠብቃችሁና እንደው ግድ ካላለ በቀር ከቤት ሳይወጡ በጸሎት ተግተው እንዲጠብቁን እያልን ከቀናት በኀላ ዳረጎታችንን ይዘን እንቀርባለን፡፡
ከጥንቱም ተካፍሎ መብላት ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነውና በዚህ ሰዓት ሥጋዊ መብል ላጡት ካለን እያካፈልን ለመንፈሳዊው መብል ደግሞ ዳረጎት ይዛ የቀረበችውን መጽሔታችንን ለሚወዱት እንዲያጋሩና ከገበታችን እንዲሰየሙ ( ገጻችንን እንዲቀላቀሉ ) ከወዲሁ በክርስቶስ ፍቅር እንለምናችኀለን፡፡
Join Us @daregot
👍4
#ሚካኤል
@Mgetem
ከአለቆች መካከል አንዱ እና ነው ዋና፤
መሰረት የሆነ ለኔ ህልውና፤
አይርቅም ፈፅሞ ላፍታ ከአጠገቤ፤
የህይወቴ ዋልታ አዋቂ የልቤ።
ሚቀድም ሚከተለኝ በሄድሁበት ሁሉ፤
የሚንከባከበኝ ዘመኔን በሙሉ፤
ጠባቂዬ ለኔ እሱ ነው ሀያሉ።
አልጠራጠርም አልፈራም ፈተና፤
ለጥማቴ እርካታ ለእራቤ መና፤
አዳኝ ጠባቂዬ አለኝታዬ አለና።
...... ምንም ባስቸግረው በሃጢአት ስራዬ፤
ነፍሴን እረስቼ ብኖር ለስጋዬ፤
አሁንም አራቀኝ ሁኗል ጠበቃዬ።
በተሰበረ ልብ ስሙን ለሚጠራ፤
በፈጠነ እርዳታው ልቦናን ሚያበራ፤
በትህትና ግርማ በፍቅር የሚመራ፤
ለፍጥረት በሙሉ የሚያዝን የሚራራ፤
የእርህራሄ አባት የማይዘገይ መልሱ፤
ለድህነት ተልኮ ሚፈጥን ከንፋሱ፤
ዋሴ ጠበቃዬ ሚካኤል ነው እሱ።
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
✍ ከ @duksha
@Mgetem
ከአለቆች መካከል አንዱ እና ነው ዋና፤
መሰረት የሆነ ለኔ ህልውና፤
አይርቅም ፈፅሞ ላፍታ ከአጠገቤ፤
የህይወቴ ዋልታ አዋቂ የልቤ።
ሚቀድም ሚከተለኝ በሄድሁበት ሁሉ፤
የሚንከባከበኝ ዘመኔን በሙሉ፤
ጠባቂዬ ለኔ እሱ ነው ሀያሉ።
አልጠራጠርም አልፈራም ፈተና፤
ለጥማቴ እርካታ ለእራቤ መና፤
አዳኝ ጠባቂዬ አለኝታዬ አለና።
...... ምንም ባስቸግረው በሃጢአት ስራዬ፤
ነፍሴን እረስቼ ብኖር ለስጋዬ፤
አሁንም አራቀኝ ሁኗል ጠበቃዬ።
በተሰበረ ልብ ስሙን ለሚጠራ፤
በፈጠነ እርዳታው ልቦናን ሚያበራ፤
በትህትና ግርማ በፍቅር የሚመራ፤
ለፍጥረት በሙሉ የሚያዝን የሚራራ፤
የእርህራሄ አባት የማይዘገይ መልሱ፤
ለድህነት ተልኮ ሚፈጥን ከንፋሱ፤
ዋሴ ጠበቃዬ ሚካኤል ነው እሱ።
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
✍ ከ @duksha
👍10❤1👎1
ቦሌ መድሐኔዓለም የሆሳሕና በዓል ተከብሯል ህዝብ ክርስቲያኑ ርቀቱን መጠበቁን የተላከልን ፎቶ ያመለክታል።
Via~Yenetube
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_Bot
Via~Yenetube
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_Bot
የመንፈሳዊ ግጥም ቻናል ቤተሰቦች
የመንፈሳዊ ግጥም ግሩፕ ስለከፈትን ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀላሉ
👇
https://www.tg-me.com/joinchat-GvI-gxt-0dfDVv6kx2QYNg
የመንፈሳዊ ግጥም ግሩፕ ስለከፈትን ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀላሉ
👇
https://www.tg-me.com/joinchat-GvI-gxt-0dfDVv6kx2QYNg
✞የተባረከች.........✞
የተባረከች አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች
👁📖👁📖👁📖👁📖👁
የተባረከች ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች
🗣👂🗣👂🗣👂🗣👂
የተባረከ ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል
💧💧💧💧💧💧💧💧💧
የተባረከች ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች
👑👑👑👑👑👑👑👑👑
የተባረከ አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም
🗣🙏🗣🙏🗣🗣🙏🗣🙏
የተባረከች አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች
✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞
የተባረከች ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የተባረከች እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች
👐👐👐👐👐👐👐👐👐
የተባረከች እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች
⛪🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶
"እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44
https://youtu.be/75GFp4SBUEg
የተባረከች አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች
👁📖👁📖👁📖👁📖👁
የተባረከች ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች
🗣👂🗣👂🗣👂🗣👂
የተባረከ ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል
💧💧💧💧💧💧💧💧💧
የተባረከች ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች
👑👑👑👑👑👑👑👑👑
የተባረከ አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም
🗣🙏🗣🙏🗣🗣🙏🗣🙏
የተባረከች አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች
✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞ ✞
የተባረከች ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የተባረከች እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች
👐👐👐👐👐👐👐👐👐
የተባረከች እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች
⛪🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶🚶
"እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44
https://youtu.be/75GFp4SBUEg
👍1
የመንፈሳዊ ግጥም ቻናል ቤተሰቦች
የመንፈሳዊ ግጥም ግሩፕ ስለከፈትን ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀላሉ
👇
https://www.tg-me.com/joinchat-GvI-gxt-0dfDVv6kx2QYNg
የመንፈሳዊ ግጥም ግሩፕ ስለከፈትን ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን ይቀላቀላሉ
👇
https://www.tg-me.com/joinchat-GvI-gxt-0dfDVv6kx2QYNg
📌የመዝሙር ግብዣ
#በርባን_እኔ_ነኝ
ዘማሪት :- ትዕግሥት¶ ስለሺ
በርባን ይፈታ በርባን ይፈታ
ይሰቀል ክርስቶስ ይሰቀል ጌታ
የሚለው ጩኸት ሆነ መዳኛዬ
በርባን እኔ ነኝ ማረኝ ጌታዬ
በአንተ መታሰር እስሬ ተፈትቶ
በአንተ መጎተት ቀንበሬ ላልቶ
ነጻ የወጣሁ ኃጢአተኛ
እኔ ነኝ የዓለም ክፉ ወንጀለኛ
አንተ ተጠልተህ የተወደድሁት
አንተ ተዋርደህ የተከበርኩት
በርባን እኔ ነኝ ውለታ ቢስዋ
የዋልክልኝን ሁሌ የምረሳ
ዘውድ እንድቀዳጅ እሾኽ ደፍተሃል
ለነጻነቴ ተቸንክረሃል
እኔ ግን ተመለስኩ ወደ ኃጢአቴ
መች ተወኝና በርባንነቴ
ግጥም :- ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ዜማ :- ዘውዱ ጌታቸው
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
https://m.youtube.com/watch?reload=9&feature=youtu.be&v=mP5jWCOwyI8&fbclid=IwAR3m5ZQGcNfyAExazS23IVarEVBQ9eJfN2SbXMQLpB4gS4OarLtSDU2hLL8
#በርባን_እኔ_ነኝ
ዘማሪት :- ትዕግሥት¶ ስለሺ
በርባን ይፈታ በርባን ይፈታ
ይሰቀል ክርስቶስ ይሰቀል ጌታ
የሚለው ጩኸት ሆነ መዳኛዬ
በርባን እኔ ነኝ ማረኝ ጌታዬ
በአንተ መታሰር እስሬ ተፈትቶ
በአንተ መጎተት ቀንበሬ ላልቶ
ነጻ የወጣሁ ኃጢአተኛ
እኔ ነኝ የዓለም ክፉ ወንጀለኛ
አንተ ተጠልተህ የተወደድሁት
አንተ ተዋርደህ የተከበርኩት
በርባን እኔ ነኝ ውለታ ቢስዋ
የዋልክልኝን ሁሌ የምረሳ
ዘውድ እንድቀዳጅ እሾኽ ደፍተሃል
ለነጻነቴ ተቸንክረሃል
እኔ ግን ተመለስኩ ወደ ኃጢአቴ
መች ተወኝና በርባንነቴ
ግጥም :- ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ዜማ :- ዘውዱ ጌታቸው
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem_bot
https://m.youtube.com/watch?reload=9&feature=youtu.be&v=mP5jWCOwyI8&fbclid=IwAR3m5ZQGcNfyAExazS23IVarEVBQ9eJfN2SbXMQLpB4gS4OarLtSDU2hLL8
YouTube
*NEW* | "በርባን እኔ ነኝ" | ዘማሪት ትዕግስት ስለሺ
Ethiopian Orthodox Tewahedo Song By Zemarit Tigist Sileshi "Berban Ene Negn"
© Mahtot Tube is the only Channel that has exclusive rights for all Lyrics produced by Zemarit Tigist Sileshi
#ይህ_ቪዲዮ_በFacebook_ኮፒ_ራይት_የተመዘገበ_ስለሆነ_አካውንትዎ_እንዳይዘጋ_በFacebook_አይልቀቁት
© Mahtot Tube is the only Channel that has exclusive rights for all Lyrics produced by Zemarit Tigist Sileshi
#ይህ_ቪዲዮ_በFacebook_ኮፒ_ራይት_የተመዘገበ_ስለሆነ_አካውንትዎ_እንዳይዘጋ_በFacebook_አይልቀቁት
👍5