#ዳግም_ልደት
@Mgetem
እሳት ወይስ ውሀ
ሀዘን ወይ ፍስሀ
አንዱን የግድ ምረጥ
ልብህ ባንዱ ይቁረጥ
ወይ ብረድ ወይ ተኩስ ፡በመሀል አትልፋ
ለብ ብለህ ካፉ ላይ፡ ውጭ እንዳትተፋ
ጨለማ ወይ ብርሀን
አንዱን ምረጥ ዝገን
ሞት ወይስ ህይወት
ሀሰት ወይስ እውነት
መዝሙር ወይስ ኮንሰርት
(አንዱን የግድ ምረጥ...)
ጣዖት ወይስ ታቦት
ሲዖል ወይስ ገነት
ይሄኔ አስተውለህ
አስበህ መርምረህ
ካላወክ ጠየቀህ
በውነት በቅንነት ፡ በበጎ ህሊና
አንዱን ምረጥና ፡ በንፁህ ልቦና
ተወለድ ወንድሜ ዳግም እንደገና ፡፡
🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹
🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹
🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸
@Mgetem
እሳት ወይስ ውሀ
ሀዘን ወይ ፍስሀ
አንዱን የግድ ምረጥ
ልብህ ባንዱ ይቁረጥ
ወይ ብረድ ወይ ተኩስ ፡በመሀል አትልፋ
ለብ ብለህ ካፉ ላይ፡ ውጭ እንዳትተፋ
ጨለማ ወይ ብርሀን
አንዱን ምረጥ ዝገን
ሞት ወይስ ህይወት
ሀሰት ወይስ እውነት
መዝሙር ወይስ ኮንሰርት
(አንዱን የግድ ምረጥ...)
ጣዖት ወይስ ታቦት
ሲዖል ወይስ ገነት
ይሄኔ አስተውለህ
አስበህ መርምረህ
ካላወክ ጠየቀህ
በውነት በቅንነት ፡ በበጎ ህሊና
አንዱን ምረጥና ፡ በንፁህ ልቦና
ተወለድ ወንድሜ ዳግም እንደገና ፡፡
🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹
🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹
🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹🔸
👍1
#አገልግሎትና_መኪና
ከሕሊና በለጠ ዘኖኅተ ብርሃን
በአገልግሎት ጋሪ በልኡክ መኪና
ነዳጁ #ፍቅር ነው ፍሬኑ #ትሕትና።
መኪና በመንገድ ፍሬን ከሌለው፣
አገልጋይም እንዲሁ ትሕትና ካነሰው፣
መፃኢ ዕጣቸው መጋጨት ብቻ ነው።
ነዳጅና ፍቅርም ይመሳሰላሉ፣
ፍቅር ይኽኛውን ነዳጅም ያኛውን ያንቀሳቅሳሉ።
#ተስፋ መስታወት ነው #ትውፊት ስፖኪዮ፣
#እምነት ደግሞ መሪው የአቅጣጫ መለዮ፤
በእምነት መሪነት በተስፋ መስታወት ወደፊት እያሉ፣
በአዕምሮ ማኅደር በትውፊት 'ሚታዩ ኋላዎችም አሉ።
'ሚንቀሳቀሱበት 'ሚሽከረከሩበት #ትግኃት ይባላል የመኪናው ጎማ፣
#ትግኃት ቅንዓትም ጡሩምባው 'ጲጵ' የሚያደርጉበት ከሃይማኖት መንገድ ዞር እንዲል ጠማማ።
ከእነዚህ ዕቃዎች አንዱ ከጎደለ ወይ ከተጣመመ ወይም ከተበሳ፣
መኪናው አሮጌ ይባላል ከርካሳ።
ጥገናና ሰርቪስ መለዋወጫ ዕቃ ለሚያስፈልገው ሰው፣
መካኒኩ ካህን ፣ ላቫጆው ንስሐ ፣ ጋራጁ መቅደስ ነው።
ሕግ አስከባሪዎች ፖሊሶችስ ካሉ፣
ሥርዐት ቀኖና ተብለው 'ሚጠሩ ትራፊኮች አሉ።
በሃይማኖት መንገድ ሲወጡ ሲወርዱ፣
መጠመቅ ብቻ ነው የመንጃ ፈቃዱ።
መልካም መንገድ!
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@AskBoaBot
ከሕሊና በለጠ ዘኖኅተ ብርሃን
በአገልግሎት ጋሪ በልኡክ መኪና
ነዳጁ #ፍቅር ነው ፍሬኑ #ትሕትና።
መኪና በመንገድ ፍሬን ከሌለው፣
አገልጋይም እንዲሁ ትሕትና ካነሰው፣
መፃኢ ዕጣቸው መጋጨት ብቻ ነው።
ነዳጅና ፍቅርም ይመሳሰላሉ፣
ፍቅር ይኽኛውን ነዳጅም ያኛውን ያንቀሳቅሳሉ።
#ተስፋ መስታወት ነው #ትውፊት ስፖኪዮ፣
#እምነት ደግሞ መሪው የአቅጣጫ መለዮ፤
በእምነት መሪነት በተስፋ መስታወት ወደፊት እያሉ፣
በአዕምሮ ማኅደር በትውፊት 'ሚታዩ ኋላዎችም አሉ።
'ሚንቀሳቀሱበት 'ሚሽከረከሩበት #ትግኃት ይባላል የመኪናው ጎማ፣
#ትግኃት ቅንዓትም ጡሩምባው 'ጲጵ' የሚያደርጉበት ከሃይማኖት መንገድ ዞር እንዲል ጠማማ።
ከእነዚህ ዕቃዎች አንዱ ከጎደለ ወይ ከተጣመመ ወይም ከተበሳ፣
መኪናው አሮጌ ይባላል ከርካሳ።
ጥገናና ሰርቪስ መለዋወጫ ዕቃ ለሚያስፈልገው ሰው፣
መካኒኩ ካህን ፣ ላቫጆው ንስሐ ፣ ጋራጁ መቅደስ ነው።
ሕግ አስከባሪዎች ፖሊሶችስ ካሉ፣
ሥርዐት ቀኖና ተብለው 'ሚጠሩ ትራፊኮች አሉ።
በሃይማኖት መንገድ ሲወጡ ሲወርዱ፣
መጠመቅ ብቻ ነው የመንጃ ፈቃዱ።
መልካም መንገድ!
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@AskBoaBot
👍2
#እንጠይቅ_ተዓምሯን
@Mgetem
፦ዮሐ ፦2 ፥1-11
፦ሉቃ ፦1 ፥ --
እንጠይቅ ስለሷ እውነታው ያልገባችሁ
ከምትናገሩ እንደመጣላችሁ
አበዉን እንጠይቅ ይንገሩን ባካችሁ ።
ብዙ አባቶች አሉ የለበሱ ፍቅሯን እነሱን እንጠይቅ የንገሩን ታምሯን ።
ታምራቱዋን ያየው የተደረገለት
ዶኪማስ ይመስክር ይናገር ስለ እውነት ፦
በዛ በሰረጉ ቤት ቃና ዘገሊላ
ሰርገኛዉ ታድሞ ሲጠጣ ሲበላ ፦
ድንገት በመሀከል ወይኑ በመጥፋቱ
ዶኪማስ ተጨንቆ ሲርድ ሰዉነቱ
የነበረው ደስታ ሁሉም ሲሆን ከንቱ
መቋቋም አቅቶት ሲዝል ጉልበቱ
ተዋረድኩኝ ብሎ ሲታየዉ ሽንፈቱ
እማምላክ አንብባ ጭንቀቱን ከፊቱ ።
እሩህሩህ ናትና እናቴ አዛኚቱ
የዶኪማስ ጭንቀት ሀዘኑ እንዲፈታ
ድንግል ልታማልድ ሄደች ወደ ጌታ
ተዓምር የሚያደርግ ስላላት ቃልኪዳን
"ወይንኪ ዓልቦሙ "አለችው ልጇን ።
ልጇም ሰማና የናቱን ልመና
ውሃውን ቀየረዉ ወደ ወይን ቃና ።
ትናገር ኤልሳቤጥ ትመስክር ታምሯን
የሰላምታዋን ቃል ስትሰማዉ ድምጿን
በምንፈስ ተሞልታ ለክብሯ መስገዷን
በማሕፀኗ ያለዉን ፅንስ ማዘለሏን ።
ልቧ ሀሴት አርጎ መጮኋን በደስታ
ፅንሱም እደዘለለ በድንግል ሰላምታ ።
ምድራዉያንን እኛን ወክላ
ለክብሯ ሰገደች "ሰላም ለኪ "ብላ
ሰማያዉያንን ሁሉ ወክሎ
ገብረኤል አበሰራት" ሰላም ለኪ "ብሎ
ታደያ በኛም ዘመን አሁን ባለንበት
የድንግል ተዓምር በሚገለጥበት
ዓለም በምልጃዋ ድህነት ባገኝበት
ታድያ ለምን ካዱ ጠፋባቸው እውነት ።
አይናቸው እያየ ገድል ታምራቷን
ጆሮአቸውም ሰምቶ ሙታን ማስነሳቱዋን
ታድያ ለምን ይሆን ሰው ናት ማልታቸዉ
ስላልተፃፈ እንጂ ፍቅሯ በልባቸው ።
ከዚህ ሓጥያት ለመዉጣት ለመቅመስ ፍቅሯን
እንጠይቅ ስለሷ ይንገሩን ታምሯን ።
እውነትን ተማሩ ግቡ ወደ በረቱ
የእውነት አማላጅ ናት ድንግል አዛኚቱ ።
✍ያለዉ ተሾመ
[][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][]
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
፦ዮሐ ፦2 ፥1-11
፦ሉቃ ፦1 ፥ --
እንጠይቅ ስለሷ እውነታው ያልገባችሁ
ከምትናገሩ እንደመጣላችሁ
አበዉን እንጠይቅ ይንገሩን ባካችሁ ።
ብዙ አባቶች አሉ የለበሱ ፍቅሯን እነሱን እንጠይቅ የንገሩን ታምሯን ።
ታምራቱዋን ያየው የተደረገለት
ዶኪማስ ይመስክር ይናገር ስለ እውነት ፦
በዛ በሰረጉ ቤት ቃና ዘገሊላ
ሰርገኛዉ ታድሞ ሲጠጣ ሲበላ ፦
ድንገት በመሀከል ወይኑ በመጥፋቱ
ዶኪማስ ተጨንቆ ሲርድ ሰዉነቱ
የነበረው ደስታ ሁሉም ሲሆን ከንቱ
መቋቋም አቅቶት ሲዝል ጉልበቱ
ተዋረድኩኝ ብሎ ሲታየዉ ሽንፈቱ
እማምላክ አንብባ ጭንቀቱን ከፊቱ ።
እሩህሩህ ናትና እናቴ አዛኚቱ
የዶኪማስ ጭንቀት ሀዘኑ እንዲፈታ
ድንግል ልታማልድ ሄደች ወደ ጌታ
ተዓምር የሚያደርግ ስላላት ቃልኪዳን
"ወይንኪ ዓልቦሙ "አለችው ልጇን ።
ልጇም ሰማና የናቱን ልመና
ውሃውን ቀየረዉ ወደ ወይን ቃና ።
ትናገር ኤልሳቤጥ ትመስክር ታምሯን
የሰላምታዋን ቃል ስትሰማዉ ድምጿን
በምንፈስ ተሞልታ ለክብሯ መስገዷን
በማሕፀኗ ያለዉን ፅንስ ማዘለሏን ።
ልቧ ሀሴት አርጎ መጮኋን በደስታ
ፅንሱም እደዘለለ በድንግል ሰላምታ ።
ምድራዉያንን እኛን ወክላ
ለክብሯ ሰገደች "ሰላም ለኪ "ብላ
ሰማያዉያንን ሁሉ ወክሎ
ገብረኤል አበሰራት" ሰላም ለኪ "ብሎ
ታደያ በኛም ዘመን አሁን ባለንበት
የድንግል ተዓምር በሚገለጥበት
ዓለም በምልጃዋ ድህነት ባገኝበት
ታድያ ለምን ካዱ ጠፋባቸው እውነት ።
አይናቸው እያየ ገድል ታምራቷን
ጆሮአቸውም ሰምቶ ሙታን ማስነሳቱዋን
ታድያ ለምን ይሆን ሰው ናት ማልታቸዉ
ስላልተፃፈ እንጂ ፍቅሯ በልባቸው ።
ከዚህ ሓጥያት ለመዉጣት ለመቅመስ ፍቅሯን
እንጠይቅ ስለሷ ይንገሩን ታምሯን ።
እውነትን ተማሩ ግቡ ወደ በረቱ
የእውነት አማላጅ ናት ድንግል አዛኚቱ ።
✍ያለዉ ተሾመ
[][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][][]
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍7❤2
#የአምላኬ ስራ እንጂ
🔖🔖🔖🔖🔖🔖🔖
እሲቲ ለአንድ አፍታ ስሙኝ ወገኖቼ
አሁን የምታዩኝ እንደዚ ፈክቼ
ደስታዬ ወሰን አጥቶ ከመጠን በላይ
የምረቃ ቆቡን ድፍቼ የምታይ
በጥናት ተግቼ እንቅልፌን አጥቼ
ፕሮጀክት አሳይመንት ሁሉንም ሰርቼ
ከቶ አንዳይመስላቹ የቆምኩኝ በደስታ
ያበቃኝ እሱ ነው የጌቶቹ ጌታ።
እናም እወቁልኝ የስኬቴን ምስጢር
የመቆሜን ነገር እንደዚህ በክብር
የኔ ስራ አይደለም በአንዳቸውም ቦታ
የአምላኬ ስራ እንጂ ያቆመኝ ከፍታ።
➴ ከቃልኪዳን ተፈራ
🔖🔖🔖🔖🔖🔖🔖
እሲቲ ለአንድ አፍታ ስሙኝ ወገኖቼ
አሁን የምታዩኝ እንደዚ ፈክቼ
ደስታዬ ወሰን አጥቶ ከመጠን በላይ
የምረቃ ቆቡን ድፍቼ የምታይ
በጥናት ተግቼ እንቅልፌን አጥቼ
ፕሮጀክት አሳይመንት ሁሉንም ሰርቼ
ከቶ አንዳይመስላቹ የቆምኩኝ በደስታ
ያበቃኝ እሱ ነው የጌቶቹ ጌታ።
እናም እወቁልኝ የስኬቴን ምስጢር
የመቆሜን ነገር እንደዚህ በክብር
የኔ ስራ አይደለም በአንዳቸውም ቦታ
የአምላኬ ስራ እንጂ ያቆመኝ ከፍታ።
➴ ከቃልኪዳን ተፈራ
👍2
#እውነት_አለቀሰች
@Mgetem
ልብ ያለህ አስተውል ጆሮ ያለህ ስማ
እግርህ እንዳይገባ ከክህደት ከተማ።
የያዝከውን አጽና ልብህ አይጨነቅ
ለጥያቄህ መልስም ሊቃውንትን ጠይቅ።
ለእውነት የቆመ ሃይማኖቱን የሚያውቅ
ንባብ ትርጓሜን ጠንቅቆ የሚዘልቅ
ተናገር ዩሐንስ አንተ ልሳነ ወርቅ።
ቄርሎስን ጠይቀው የተዋህዶን ምስጢር
የክርስቶስ ነገር እንዴት እንደነበር
ከብሉይ ከሐዲስ በማቀነባበር
እንዳመሰጠረው በብዙ ምስክር።
ነቢዩ ኢሳያስ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ
መዝሙረኛው ዳዊት ሐዋርያው ሉቃስ
አባ ዝክረ ማርያም ወአባ ጴጥሮስ
የስነ ዘፍጥረት ሊቅ ኤጲፋኒዮስ
ዝም አትበል ተናገር ቅዱስ ሳዊሮስ
በሥጋው ማክበሩን አምላክ ክርስቶስ።
ጊዮርጊስ ተናገር አንተ የጥዋት ጮራ
ክርስቶስ መሲሕም ተብሎ እንደሚጠራ።
ወልድ ቅብዕ በማለት ክህደት አስተማሩ
የሥግው ቃል ነገር መች ገባቸው ዳሩ
የተዋሕዶ ምስጢር ሳይገባቸው ቅሉ
ሃይማኖት ከምስጢር ይደባልቃሉ።
ክርስቶስ በሥጋ እንደሞተ ሲያውቁ
በሥጋስ መክበሩን እንዴት አላወቁ
ሊቃውንት እያሉ ለምን አይጠይቁ
በተዋሕዶ ከበረ ብለው ሲናገሩ
ለዚህ ብሂላቸው የታል ምስክሩ።
ግብርን በማፋለስ አንድ ገጽ ካለው ከሰባልዮስ
አንድነትን ትቶ ሁለት አካል ካለው ከእርጉም ንስጥሮስ
መንፈስ ቅዱስ ሕጸፅ ካለው ከመቅዶንዮስ
ወልድ ፍጡር ካለው ከእርጉም ከአርዮስ
የዚህ ክህደቱ በምንም አያንስ።
ፈላጊዋ ጠፍቶ እውነት አለቀሰች
ግብራቸው ተቃርኖ ሀሰት ጥላት ሄደች።
ዳሩ ግን ወገኔ ይህ ክህደት ነውና
ቀኑ ሳይመሽብህ መንገድህን አቅና
እውነትን ከፈለክ ታገኛለህና
እረፍት ስላላት የህይወት ጎዳና
የያዝከውን ይዘህ በሃይማኖት ጽና።
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ልብ ያለህ አስተውል ጆሮ ያለህ ስማ
እግርህ እንዳይገባ ከክህደት ከተማ።
የያዝከውን አጽና ልብህ አይጨነቅ
ለጥያቄህ መልስም ሊቃውንትን ጠይቅ።
ለእውነት የቆመ ሃይማኖቱን የሚያውቅ
ንባብ ትርጓሜን ጠንቅቆ የሚዘልቅ
ተናገር ዩሐንስ አንተ ልሳነ ወርቅ።
ቄርሎስን ጠይቀው የተዋህዶን ምስጢር
የክርስቶስ ነገር እንዴት እንደነበር
ከብሉይ ከሐዲስ በማቀነባበር
እንዳመሰጠረው በብዙ ምስክር።
ነቢዩ ኢሳያስ ብርሃነ ዓለም ጳውሎስ
መዝሙረኛው ዳዊት ሐዋርያው ሉቃስ
አባ ዝክረ ማርያም ወአባ ጴጥሮስ
የስነ ዘፍጥረት ሊቅ ኤጲፋኒዮስ
ዝም አትበል ተናገር ቅዱስ ሳዊሮስ
በሥጋው ማክበሩን አምላክ ክርስቶስ።
ጊዮርጊስ ተናገር አንተ የጥዋት ጮራ
ክርስቶስ መሲሕም ተብሎ እንደሚጠራ።
ወልድ ቅብዕ በማለት ክህደት አስተማሩ
የሥግው ቃል ነገር መች ገባቸው ዳሩ
የተዋሕዶ ምስጢር ሳይገባቸው ቅሉ
ሃይማኖት ከምስጢር ይደባልቃሉ።
ክርስቶስ በሥጋ እንደሞተ ሲያውቁ
በሥጋስ መክበሩን እንዴት አላወቁ
ሊቃውንት እያሉ ለምን አይጠይቁ
በተዋሕዶ ከበረ ብለው ሲናገሩ
ለዚህ ብሂላቸው የታል ምስክሩ።
ግብርን በማፋለስ አንድ ገጽ ካለው ከሰባልዮስ
አንድነትን ትቶ ሁለት አካል ካለው ከእርጉም ንስጥሮስ
መንፈስ ቅዱስ ሕጸፅ ካለው ከመቅዶንዮስ
ወልድ ፍጡር ካለው ከእርጉም ከአርዮስ
የዚህ ክህደቱ በምንም አያንስ።
ፈላጊዋ ጠፍቶ እውነት አለቀሰች
ግብራቸው ተቃርኖ ሀሰት ጥላት ሄደች።
ዳሩ ግን ወገኔ ይህ ክህደት ነውና
ቀኑ ሳይመሽብህ መንገድህን አቅና
እውነትን ከፈለክ ታገኛለህና
እረፍት ስላላት የህይወት ጎዳና
የያዝከውን ይዘህ በሃይማኖት ጽና።
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍12🤬1
#ያኔ_እመረቃለሁ
@Mgetem
ሀሁ ABCD ፊደላት ቆጥሬ
ጥበብን ለመማር መፃሕፍት ደርድሬ
ሀገሬን ወገኔን እናቴን ለመርዳት
ድንቁርናን ጥዬ ከችግር ለመውጣት
ጋራውን ስወጣ ቁልቁለት ወርጄ
ከአንድ ወደ ሌላ ማለፍ ተላምጄ
ነገን ለማሸነፍ እቅድ እነድፋአለሁ
ተስፋ ስንቅ ሆኖልኝ እሩቅ አልማለሁ፡፡
ደግሞ
መቼነው የማያት ያቺን የብርሃን ቀን?
ነፃ ምወጣባት ከቴንሽን ሰቀቀን
መች ትሆን እያልኩኝ አማትሬ ሳያት
ያቺን የቀናት ቀን እንዲሁ ስናፍቃት
ቀናት ተሰብስበው ወራት አቀናጁ
ወራትም አብረው አመታት አበጁ
የዘመን ባለቤት ጊዜያት አቀዳጅቶ
ጉዞና መንገዴን ጥርጊያዬን አቅንቶ
በጊዜው ውብ አርጎ ሁሉን አስተካክሎ
የምርቃቴን ቀን ለገሰኝ በቶሎ፡፡
የእናት የአባቴ ህልም የተስፋ ቀናቸው
የብርሃን ቀን መጣች ሀሴት ልትሞላቸው
የምመረቅባት....የልፋት ካባዬን የምደርብባት
ራዕይ ዓላማዬ ግብ የሚመታባት፡፡
ነገ!
ሀገሬን ወገኔን የምጠቅም ዜጋ
ለእውነት ለቅንነት ጦር ይዜ ምዋጋ
የማይነቃነቅ ብርቱ ትውልድ ሆኜ
ለጥፋት የማልቆም የማልቀር ባክኜ
አንድነት ሰላምን ፍቅርን ተነቅሼ
የዳዊትን ትምክህት የምጓዝ ለብሼ
እንድሆን ብሩህ ትውልድ ሥላሴ ድረሱ
መላ ማንነቴን ህይወቴን ቀድሱ፡፡
የአብርሃምን ቤት እንደባረካችሁ
ትውልዱንም ታላቅ እንዳደረጋችሁ
ብርቱ መጠለያ ዋስ ድጋፍ ሁኑልኝ
ዓጋዕዝተ ዓለም ቀኔን መርቁልኝ፡፡
እንደ ያዕቆብ ሌሊት ይባረክ ህይወቴ
ሙሉ ሀሴት ይሁን የምርቃት ለቴ፡፡
ባላቅን ልካችሁ
ሰዓታት ዕለታት ቀኔን መርቁልኝ
በጴጥሮስ መክፈቻ
የገዛ ሀጥያቴን አጥባችሁ አጥሩልኝ፡፡
መልአከ ምክራችሁን ወደኔ ላኩልኝ
ዲግሪዬን በትንፋሹ እንዲቀድስልኝ
አብሳሪውን መልአክ ጠርታችሁ ላኩልኝ
የምስራች ነግሮ ደስታ እንዲበዛልኝ፡፡
ጆሮዬ ይሰማው የድንግል ሰላምታ
ይታጠፍ ጉልበቴ ይስገድ ለአንተ ጌታ
ጉዞዬን በሙሉ ባንተ ላይ ስጥለው
መቻል እስቂያቅተኝ ያኔ እመረቃለሁ፡፡
___________________________
ለ2011ዓ.ም የተዋህዶ ልጆች በሙሉ እንኳን ለመርቃ ቀናቹ አደረሳቹ እንላለን።
✍ገጣሚ ረዳኢ ሃዱሽ
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
ሀሁ ABCD ፊደላት ቆጥሬ
ጥበብን ለመማር መፃሕፍት ደርድሬ
ሀገሬን ወገኔን እናቴን ለመርዳት
ድንቁርናን ጥዬ ከችግር ለመውጣት
ጋራውን ስወጣ ቁልቁለት ወርጄ
ከአንድ ወደ ሌላ ማለፍ ተላምጄ
ነገን ለማሸነፍ እቅድ እነድፋአለሁ
ተስፋ ስንቅ ሆኖልኝ እሩቅ አልማለሁ፡፡
ደግሞ
መቼነው የማያት ያቺን የብርሃን ቀን?
ነፃ ምወጣባት ከቴንሽን ሰቀቀን
መች ትሆን እያልኩኝ አማትሬ ሳያት
ያቺን የቀናት ቀን እንዲሁ ስናፍቃት
ቀናት ተሰብስበው ወራት አቀናጁ
ወራትም አብረው አመታት አበጁ
የዘመን ባለቤት ጊዜያት አቀዳጅቶ
ጉዞና መንገዴን ጥርጊያዬን አቅንቶ
በጊዜው ውብ አርጎ ሁሉን አስተካክሎ
የምርቃቴን ቀን ለገሰኝ በቶሎ፡፡
የእናት የአባቴ ህልም የተስፋ ቀናቸው
የብርሃን ቀን መጣች ሀሴት ልትሞላቸው
የምመረቅባት....የልፋት ካባዬን የምደርብባት
ራዕይ ዓላማዬ ግብ የሚመታባት፡፡
ነገ!
ሀገሬን ወገኔን የምጠቅም ዜጋ
ለእውነት ለቅንነት ጦር ይዜ ምዋጋ
የማይነቃነቅ ብርቱ ትውልድ ሆኜ
ለጥፋት የማልቆም የማልቀር ባክኜ
አንድነት ሰላምን ፍቅርን ተነቅሼ
የዳዊትን ትምክህት የምጓዝ ለብሼ
እንድሆን ብሩህ ትውልድ ሥላሴ ድረሱ
መላ ማንነቴን ህይወቴን ቀድሱ፡፡
የአብርሃምን ቤት እንደባረካችሁ
ትውልዱንም ታላቅ እንዳደረጋችሁ
ብርቱ መጠለያ ዋስ ድጋፍ ሁኑልኝ
ዓጋዕዝተ ዓለም ቀኔን መርቁልኝ፡፡
እንደ ያዕቆብ ሌሊት ይባረክ ህይወቴ
ሙሉ ሀሴት ይሁን የምርቃት ለቴ፡፡
ባላቅን ልካችሁ
ሰዓታት ዕለታት ቀኔን መርቁልኝ
በጴጥሮስ መክፈቻ
የገዛ ሀጥያቴን አጥባችሁ አጥሩልኝ፡፡
መልአከ ምክራችሁን ወደኔ ላኩልኝ
ዲግሪዬን በትንፋሹ እንዲቀድስልኝ
አብሳሪውን መልአክ ጠርታችሁ ላኩልኝ
የምስራች ነግሮ ደስታ እንዲበዛልኝ፡፡
ጆሮዬ ይሰማው የድንግል ሰላምታ
ይታጠፍ ጉልበቴ ይስገድ ለአንተ ጌታ
ጉዞዬን በሙሉ ባንተ ላይ ስጥለው
መቻል እስቂያቅተኝ ያኔ እመረቃለሁ፡፡
___________________________
ለ2011ዓ.ም የተዋህዶ ልጆች በሙሉ እንኳን ለመርቃ ቀናቹ አደረሳቹ እንላለን።
✍ገጣሚ ረዳኢ ሃዱሽ
___________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
👍8❤1
Forwarded from መንፈሳዊ ግጥም ብቻ
❗️ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ
➤በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል
➤ከሐምሌ 5 ( ከአርብ) አስከ ሐምሌ 7 (እሁድ)
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
#Share ሼር ያድርጉት
➤በአሰላ ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም ካቴድራል
➤ከሐምሌ 5 ( ከአርብ) አስከ ሐምሌ 7 (እሁድ)
ሁላችሁም ተጋብዛችኋል
#Share ሼር ያድርጉት
#የአምላክ_መገኛ
@Mgetem
አንድ እለት አንድ ወጣት
አንድን የበቁ አባት
በማለት ጠየቀ በጣም ፈልጋለሁ አምላኬን ለማየት
ከልብህ ከፈለክ አምላክን ለማግኘት
ልምራህ ወዳለበት ተነስ ተከተለኝ
ታዲያ ግን አደራ ልመለስ አትበለኝ
አምላክን ለማየት ከልብህ ከፈለግክ
እርሱ ወዳለበት ስንሄድ ታየዋለክ
ካሉት በኋላማ ተነሱ በአንድነት ወደ አምላክ ሊሄዱ
ከጠበቀው በላይ ሩቅ ሲሆንበት ወጣቱ መንገዱ
እስኬት ነዉ ምንሄደው አምላክ የት ነው ያለው
እርሱ አምላክ ሳለ በዚህ በበረሃ ለምን ነው ሚኖረው
እኔ ግን አባቴ ልሞት ነው ደክሞኛል
ከምነግሮት በላይ ጉሮሮዬ ደርቋል
አባቴ ይንገሩኝ አምላክ የት ይገኛል
እኔስ ሄድኩ እንበል እርሱ ግን ያውቀኛል
አሁን ተቃርበናል ልንደርስ ነው አምላክ ጋ
እዚሁ ጠብቀኝ እኔ ግን ልሄድ ነው ሚጠጣ ፍለጋ
አሉትና እኚያ አባት ፈጥነው ተራመዱ
ወጣቱም በድካም ተንጋሎ አያቸው በፍጥነት ሲሄዱ
እራሱን ጠየቀ እጅጉን ተገርሞ
እኚህ አባት ጥንካሬያቸውን ኬት አመጡት ደግሞ
እኚያ አባት ሄደው ትንሽ እንደቆዩ
ወጣቱ ዞረበት ምድርና ሰማዩ
አምላኬን ሳላየው ልሞት ይሆን እንዴ
ምነው ግን ቢያቆየኝ እስካገኘው አንዴ
ብሎ ሳይጨርሰው እዚያው ራሱን ሳተ ተንጋሎ ሜዳ ላይ
ልክ እንደ ነቃ ዙሪያ ገባውን ሲያይ
እኚያ አባት ተቀምጠው ይፀልዩ ነበር
እሱም ቀና ብሎ የሚፀልዩትን ይሰማቸው ጀመር
ይስሙኝማ አባቴ
አምላኬን አየሁት ለዚያውም ሁለቴ
ወዴት አገኘኸው እንዴትስ ለየኸው
ባገኘኸው ጊዜስ ምንድን ነበር ያልከው
እኔ ወጣት ሆኜ በድካም ስሰቃይ
እርሶ ግን ሸምግለው ጥንካሬዎትን ሳይ
ያን ጊዜ አየሁት አምላኬን በእርሶ ላይ
ውሃ ጠምቶኝ ደክሞኝ ህሊናዬን ስቼ
ስነቃ ለየሁት ፀሎቶን ሰምቼ
በል አድምጠኝ ልጄ ታዲያ አሁንስ ገባህ
አምላክ ሁሌም አለ በዙሪያ በደጅህ
ይገለፅልህ ዘንድ
የትም ሳትሰደድ
በተስፋ ጠብቀው ልቦናህን ከፍተህ
ይህንን ስትፈፅም ያኔ ታየዋለህ
➴በሰላማዊት ጌቱ
___________________________
@mgetem
@Mgetem
@Kal002
@Mgetem
አንድ እለት አንድ ወጣት
አንድን የበቁ አባት
በማለት ጠየቀ በጣም ፈልጋለሁ አምላኬን ለማየት
ከልብህ ከፈለክ አምላክን ለማግኘት
ልምራህ ወዳለበት ተነስ ተከተለኝ
ታዲያ ግን አደራ ልመለስ አትበለኝ
አምላክን ለማየት ከልብህ ከፈለግክ
እርሱ ወዳለበት ስንሄድ ታየዋለክ
ካሉት በኋላማ ተነሱ በአንድነት ወደ አምላክ ሊሄዱ
ከጠበቀው በላይ ሩቅ ሲሆንበት ወጣቱ መንገዱ
እስኬት ነዉ ምንሄደው አምላክ የት ነው ያለው
እርሱ አምላክ ሳለ በዚህ በበረሃ ለምን ነው ሚኖረው
እኔ ግን አባቴ ልሞት ነው ደክሞኛል
ከምነግሮት በላይ ጉሮሮዬ ደርቋል
አባቴ ይንገሩኝ አምላክ የት ይገኛል
እኔስ ሄድኩ እንበል እርሱ ግን ያውቀኛል
አሁን ተቃርበናል ልንደርስ ነው አምላክ ጋ
እዚሁ ጠብቀኝ እኔ ግን ልሄድ ነው ሚጠጣ ፍለጋ
አሉትና እኚያ አባት ፈጥነው ተራመዱ
ወጣቱም በድካም ተንጋሎ አያቸው በፍጥነት ሲሄዱ
እራሱን ጠየቀ እጅጉን ተገርሞ
እኚህ አባት ጥንካሬያቸውን ኬት አመጡት ደግሞ
እኚያ አባት ሄደው ትንሽ እንደቆዩ
ወጣቱ ዞረበት ምድርና ሰማዩ
አምላኬን ሳላየው ልሞት ይሆን እንዴ
ምነው ግን ቢያቆየኝ እስካገኘው አንዴ
ብሎ ሳይጨርሰው እዚያው ራሱን ሳተ ተንጋሎ ሜዳ ላይ
ልክ እንደ ነቃ ዙሪያ ገባውን ሲያይ
እኚያ አባት ተቀምጠው ይፀልዩ ነበር
እሱም ቀና ብሎ የሚፀልዩትን ይሰማቸው ጀመር
ይስሙኝማ አባቴ
አምላኬን አየሁት ለዚያውም ሁለቴ
ወዴት አገኘኸው እንዴትስ ለየኸው
ባገኘኸው ጊዜስ ምንድን ነበር ያልከው
እኔ ወጣት ሆኜ በድካም ስሰቃይ
እርሶ ግን ሸምግለው ጥንካሬዎትን ሳይ
ያን ጊዜ አየሁት አምላኬን በእርሶ ላይ
ውሃ ጠምቶኝ ደክሞኝ ህሊናዬን ስቼ
ስነቃ ለየሁት ፀሎቶን ሰምቼ
በል አድምጠኝ ልጄ ታዲያ አሁንስ ገባህ
አምላክ ሁሌም አለ በዙሪያ በደጅህ
ይገለፅልህ ዘንድ
የትም ሳትሰደድ
በተስፋ ጠብቀው ልቦናህን ከፍተህ
ይህንን ስትፈፅም ያኔ ታየዋለህ
➴በሰላማዊት ጌቱ
___________________________
@mgetem
@Mgetem
@Kal002
👍4
የእሳት ትንታግ ፍንጣሪ
የድል ዜማ ወገን አኩሪ
የክብር ጥግ ማማ
የደስታ ውበት ቄጤማ
የመስቀሉን ሀይል ከግሽን የጠበሉን በረከት ዘግና
ይኸው አየኋት በለንደን የእሳት ልጅ እሳት ሆና
የደም አዙሪት ምሬቱ
የእሳት ትግል ሽረቱ
እየፈላባት አሞቷ እየታገላት ሲቃ
ታቦቷን ከራሷ ሳይሆን ከደረቷ ላይ ደብቃ
ተሻገረችው ያን ጉድ አስለቀሰችን ነፍርቃ
ጀመረች አግዢኝ ብላ
ድንግልን በደረቷ አዝላ
ታሪክ ናት ይህች ማሪያም ለተማፀናት በብርቱ
ልጇን ላመነ በልቡ ፍቅሯን ላሰረ በአንገቱ
ረሳችውና ድካሟን የልፋት ውጤት ወርቋን
ከፍ አደረገች በሥዕሏ የድንግልን ማሪያምን ስሟን
ግሸን ሆነች አሉ ለንደን ተቀይራ
መሰረተ ሕይወት ድንግል ተዘምራ
እምነት ከጉያ ውስጥ ድንገት ፈለቀና
ሃሌ ሃሌ ሆነ ድካም ተረሳና
የእኛ እርግብ አማኝቷ
የኢትዮጵያ ልጅ መሰረቷ
ቢላላባት ያሰረችው ቢበጣጠስ መቀነቷ
ተወራርዳ አሸነፈች በጌታ እናት በአዛኚቷ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
በቀሲስ ማሞ በዕለቱ የተፃፈ
@Mgetem
@Mgetem
@Bahraan
የድል ዜማ ወገን አኩሪ
የክብር ጥግ ማማ
የደስታ ውበት ቄጤማ
የመስቀሉን ሀይል ከግሽን የጠበሉን በረከት ዘግና
ይኸው አየኋት በለንደን የእሳት ልጅ እሳት ሆና
የደም አዙሪት ምሬቱ
የእሳት ትግል ሽረቱ
እየፈላባት አሞቷ እየታገላት ሲቃ
ታቦቷን ከራሷ ሳይሆን ከደረቷ ላይ ደብቃ
ተሻገረችው ያን ጉድ አስለቀሰችን ነፍርቃ
ጀመረች አግዢኝ ብላ
ድንግልን በደረቷ አዝላ
ታሪክ ናት ይህች ማሪያም ለተማፀናት በብርቱ
ልጇን ላመነ በልቡ ፍቅሯን ላሰረ በአንገቱ
ረሳችውና ድካሟን የልፋት ውጤት ወርቋን
ከፍ አደረገች በሥዕሏ የድንግልን ማሪያምን ስሟን
ግሸን ሆነች አሉ ለንደን ተቀይራ
መሰረተ ሕይወት ድንግል ተዘምራ
እምነት ከጉያ ውስጥ ድንገት ፈለቀና
ሃሌ ሃሌ ሆነ ድካም ተረሳና
የእኛ እርግብ አማኝቷ
የኢትዮጵያ ልጅ መሰረቷ
ቢላላባት ያሰረችው ቢበጣጠስ መቀነቷ
ተወራርዳ አሸነፈች በጌታ እናት በአዛኚቷ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖
በቀሲስ ማሞ በዕለቱ የተፃፈ
@Mgetem
@Mgetem
@Bahraan
👍2
#የታወረ_ትውልድ
@Mgetem
ከእናቱ አፈንግጦ እምነት ወዲያ ብሎ በአለም የታለለ
በዚህ በእኔ ዘመን ልበ ስውር ወጣት እጂግ ብዙ አለ
ዶግማና ቀኖና መፈፀም ሲያቅተው በስጋው ሲታለል
ይችን ቅድስት እምነት መፍትሄ ነው ብሎ ትታደስ ይላታል
የመለውጥ ትርጉም ጠንቅቆ ያልገባው ልበ ስውር ጓዴ
በኃጢያት ያደፈ እሱነቱን ይዞ ትታደስ ይለኛል ያላረጀ ነገር ይታደሳል እንዴ?
እነዲዎስቆሮስ ፂም የተነጩላት የፀናች ሀይማኖት
ቆዳቸው እንደ ድንች በአህዛብ ጭካኔ ያኔ የተላጡላት
በሚያስፈራ እሳት ነጎድጓድ በላበት
ለኛ ያቆዩልን ህይወትን ሰውተው
ተዋህዶ እምነቴ ምኗ ነው ያረጀው
በሀጥያት አረንቋ የተቆሳቆለ እርሱ ተቀምጦ
ፍርሀት እንኳን አያውቅ ትታደስ ይለኛል ካፉ ቃል አውጥቶ
መላ በሉት'ማ ምከሩት ይህን ስው
የመታደስ ትርጉም ምን አልባት ቢገባው!!!የናቁሽ ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይበረከካሉ
ያከበሩሽም የከበሩ ናቸው
ማሪያምን የጠላ የለውም ከለላ
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ከእናቱ አፈንግጦ እምነት ወዲያ ብሎ በአለም የታለለ
በዚህ በእኔ ዘመን ልበ ስውር ወጣት እጂግ ብዙ አለ
ዶግማና ቀኖና መፈፀም ሲያቅተው በስጋው ሲታለል
ይችን ቅድስት እምነት መፍትሄ ነው ብሎ ትታደስ ይላታል
የመለውጥ ትርጉም ጠንቅቆ ያልገባው ልበ ስውር ጓዴ
በኃጢያት ያደፈ እሱነቱን ይዞ ትታደስ ይለኛል ያላረጀ ነገር ይታደሳል እንዴ?
እነዲዎስቆሮስ ፂም የተነጩላት የፀናች ሀይማኖት
ቆዳቸው እንደ ድንች በአህዛብ ጭካኔ ያኔ የተላጡላት
በሚያስፈራ እሳት ነጎድጓድ በላበት
ለኛ ያቆዩልን ህይወትን ሰውተው
ተዋህዶ እምነቴ ምኗ ነው ያረጀው
በሀጥያት አረንቋ የተቆሳቆለ እርሱ ተቀምጦ
ፍርሀት እንኳን አያውቅ ትታደስ ይለኛል ካፉ ቃል አውጥቶ
መላ በሉት'ማ ምከሩት ይህን ስው
የመታደስ ትርጉም ምን አልባት ቢገባው!!!የናቁሽ ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይበረከካሉ
ያከበሩሽም የከበሩ ናቸው
ማሪያምን የጠላ የለውም ከለላ
@Mgetem
@Mgetem
👍1
መንፈሳዊ ግጥም ብቻ via @like
ውድ የመንፈሳዊ ግጥም ብቻ ቻናላችን ተከታታዮች አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን፡፡ 🙏🙏
🖼አዲስ ፕሮፋይል....
#Profile_design Credit to
Sc graphics 📩 @Scgpx
🖼አዲስ ፕሮፋይል....
#Profile_design Credit to
Sc graphics 📩 @Scgpx
#ሁሉም_በምክንያት_ነው
@Mgetem
ለስራ ሲሄዱ አባት ከልጁ ጋር
ሲደክማቸው አረፉ በአንድ የሾላ ዛፍ ስር
ትንሽም ሳይቆዩ ልጅየው ለማረፍ መሬት ላይ ተንጋሎ
አባቱን አላቸው የሾላውን ፍሬ በደንቡ አስተውሎ
አባቴ ተመልከት አምላክ ግን ሞኝ ነው
እንዴት ባክህ ልጄ ምን እያልከኝ ነው
ይህንን በሚያህል ትልቅ ዛፍ
የጥበቡን ስራ ሲያሳርፍ
እፍኝ የማይሞላ ትንሽዬ ፍሬ እንዲያፈራ ፈጥሮ
ግን ለአቅመ ቢሱ ዱባ ትልቅ ፍሬን ፈጥሮ ታዲያ ሞኝ አይደለም ብሎ ሳይጨርሰው
አባት ጣልቃ ገብቶ ልጁን አቋረጠው
አምላክ አላማ አለው ሲፈጥረው6 ሁሉንም በም/ክ ነው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም
መቼም እንዳትገባ በፈጣሪ ስራ
ከዛሬ በኋላ እንዲህም አታውራ
ቢሆንም አባቴ አምላክ ልክ አይደለም
ብሎ ተናገረ ሳያስበው ምንም
ትክክል መሆኑን ሊያስረዳ ሲቃጣው
አንዲት ፍሬ ወድቃ ግንባሩን መታችው
አባትም አየና ይናገር ጀመረ
አልሰማም አልክ እንጂ ነግሬህ ነበረ
ልክ አንተ እንዳልከው ይሄ የሾላ ፍሬ ዱባን ቢያክል ኖሮ
ዛሬ ሞተህ ነበር አብቅቶልህ ኑሮ
ስለዚህ አትግባ በሱ ስራ ድንገት
ምክንያቱ ከገባህ ይከተላል ቅጣት
➴
ከሰላማዊት ጌቱ
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
@Mgetem
ለስራ ሲሄዱ አባት ከልጁ ጋር
ሲደክማቸው አረፉ በአንድ የሾላ ዛፍ ስር
ትንሽም ሳይቆዩ ልጅየው ለማረፍ መሬት ላይ ተንጋሎ
አባቱን አላቸው የሾላውን ፍሬ በደንቡ አስተውሎ
አባቴ ተመልከት አምላክ ግን ሞኝ ነው
እንዴት ባክህ ልጄ ምን እያልከኝ ነው
ይህንን በሚያህል ትልቅ ዛፍ
የጥበቡን ስራ ሲያሳርፍ
እፍኝ የማይሞላ ትንሽዬ ፍሬ እንዲያፈራ ፈጥሮ
ግን ለአቅመ ቢሱ ዱባ ትልቅ ፍሬን ፈጥሮ ታዲያ ሞኝ አይደለም ብሎ ሳይጨርሰው
አባት ጣልቃ ገብቶ ልጁን አቋረጠው
አምላክ አላማ አለው ሲፈጥረው6 ሁሉንም በም/ክ ነው እንጂ በአጋጣሚ አይደለም
መቼም እንዳትገባ በፈጣሪ ስራ
ከዛሬ በኋላ እንዲህም አታውራ
ቢሆንም አባቴ አምላክ ልክ አይደለም
ብሎ ተናገረ ሳያስበው ምንም
ትክክል መሆኑን ሊያስረዳ ሲቃጣው
አንዲት ፍሬ ወድቃ ግንባሩን መታችው
አባትም አየና ይናገር ጀመረ
አልሰማም አልክ እንጂ ነግሬህ ነበረ
ልክ አንተ እንዳልከው ይሄ የሾላ ፍሬ ዱባን ቢያክል ኖሮ
ዛሬ ሞተህ ነበር አብቅቶልህ ኑሮ
ስለዚህ አትግባ በሱ ስራ ድንገት
ምክንያቱ ከገባህ ይከተላል ቅጣት
➴
ከሰላማዊት ጌቱ
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
👍5
#አልችልም_አስችለኝ
@Mgetem
እየደነገጠ እየፈራ ልቤ
አንድነት አቅቶት ቅጥልጥል ሃሳቤ
ኮሽ ባለ ቁጥር እየፈራች ነፍሴ
አስጨንቀዋለሁ ራሴን በራሴ
አይኖቼ ተስፋዬን ማየት ተስኗቸው
እግሮቼ ጉዞዬን መጓዝ አቅቷቸው
ይቅበዘበዛሉ መሪ ጠፍቶባቸው
ዝም ባለ ጎጆ ጭጭ ባለ ሌሊት
ጩኸት ይሰማኛል ምንም በሌለበት
የሚያሳርፍ ጌታ እንዳለኝ ይወቀው
የሚያስጨንቀኝን አምላኬ አስጨንቀው
አንተ ድረስና የጭንቄን ውል ፍታ
አልችልም አስችለኝ እንዳልጠፋ ጌታ !
🔶🔷🔶🔷🔸🔹🔸🔹🔶🔷🔶
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
@Mgetem
እየደነገጠ እየፈራ ልቤ
አንድነት አቅቶት ቅጥልጥል ሃሳቤ
ኮሽ ባለ ቁጥር እየፈራች ነፍሴ
አስጨንቀዋለሁ ራሴን በራሴ
አይኖቼ ተስፋዬን ማየት ተስኗቸው
እግሮቼ ጉዞዬን መጓዝ አቅቷቸው
ይቅበዘበዛሉ መሪ ጠፍቶባቸው
ዝም ባለ ጎጆ ጭጭ ባለ ሌሊት
ጩኸት ይሰማኛል ምንም በሌለበት
የሚያሳርፍ ጌታ እንዳለኝ ይወቀው
የሚያስጨንቀኝን አምላኬ አስጨንቀው
አንተ ድረስና የጭንቄን ውል ፍታ
አልችልም አስችለኝ እንዳልጠፋ ጌታ !
🔶🔷🔶🔷🔸🔹🔸🔹🔶🔷🔶
@Mgetem
@Mgetem
@Menfesawi_getem_bot
#ፍቅር_ማለት
@Mgetem
#ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
#ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ #በደሙ_ታጥቤ
ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
#ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
#የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
#ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
#የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
#ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
#ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
#ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
#ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
#ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
#ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
#ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
እ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#ያን_ሁሉ መስዋእት ያን ሁሉ ግርፋት
#ልጅን_ከአባት ጋር አባትን ከልጅ ጋር
አስታርቆ ለማየት ፤
እኔ ያያ ሰው ነኝ የከበረ ዋጋ የተከፈለበት
እኔ ያ. ሰው ነኝ #በደሙ_ታጥቤ
ነፃ የሆንኩበት ፤
ታድያ ለዚህ ከንቱ አለም ላልወደደው
በትንሽነቱ ሰው ሁሉ ለናቀው ፤
እንዴትስ ተገብቶት ጌታ ሊሞትለት
እንዴትስ ተደርጎ ክብሩን ሊተውለት ፤
#ይህ_ፍጡር ማን ቢሆን ነው ከቶ
#የሰማዩን_ንጉስ ግዛቱን አስትቶ
በሀጥያቷ ክርፋት ወደ ገማች ምድር
ጠርቶና ጎትቶ ፤
#ሞትን_ያቀመሰው የትኛው ፍቅር ነው
#የቱ ቅድስና የቱ ማንነቴ የቱ ንፅህና ፤
#ንፁህ_የሆነውን ፅድቅ የለበሰውን
ስጋ ያለበሰው ሀጥያት ያደረገው
የቱ እኔነቴ እሱነቱን ትቶ እንዲያ
ሚያዋርደው ? ፤
#ያንን_ፍቅርማ ቃላት ተቆፍረው
#ያንን_መውደድማ ፊደላት ተጣምረው ፤
#ከቶ አይገልፁትም ፍፁም አይደርሱትም
ብርሀን አያደምቀው ጨለማ አይጋርደው
የቀናት መገስገስ የአመታት መንጎድ
ዘመን የማይሽረው ፤
#ፍ ቅ ር ማለት ያ ያ ነው
#ፍቅር_ውልደቱ ነው ፍቅር መከራው ነው
#ፍቅር_መሞቱ_ነው ፍቅር ትንሳኤው ነው ፤
በዘመን ጅማሬ በዘመን ፍፃሜም
የፍቅር ስንኙ የፍቅር ሀረጉ
እ የ ሱ ስ ብቻ ነው !
__________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍9
Forwarded from Daregot Media
daregot magazine vol 5 for mobile.pdf
4.5 MB
የዳረጎት መጽሔት አምስተኛ እትም።
አስተያየት በመስጠት፥ ለሌሎች በማጋራት የአገልግሎት ድርሻዎን ይወጡ። መልካም ንባብ
አስተያየት በመስጠት፥ ለሌሎች በማጋራት የአገልግሎት ድርሻዎን ይወጡ። መልካም ንባብ