#ፍልሰታ
@Mgetem
ትፈራው ነበረ ያን መልአከሞት
የልጅሽን ፅዋ ቅመሽው አላት
ይጠፋል ኩነኔ ይጠፋል አበሳ
እንደ ፈጣሪያችን ማርያም ስትነሳ
እየባረከቻት ኢትዮጵያን በእጆቿ
በይባቤ አረገች እሷም እንደ ልጇ
ከሰው የተለየች መሆኗን ሲያበስር
ሞት በጥር ሆነ ነሃሴ መቃብር
አይሁዳዊው ቀንቶ ሲሰርቅ ሥጋዋን
የመለኮቱ ሰይፍ ቆርጠው እጁን
ብዙው ይጾመዋል የፍልሰታን ፆም
ከእህል ተከልክሎ ከሥጋ ከደም
ሐዋርያው ፊሊጶስ ትንሣኤዋን ሲሻ
ከወንድሞቹ ጋር ዕርገቷንም ሲሻ
በስሟ ተነሱ ሊፆሙ በጋራ።
የበረከት ፆም ያድርግልን!
@Mgetem
@Mgetem
@Ask_Boa_Bot
@Mgetem
ትፈራው ነበረ ያን መልአከሞት
የልጅሽን ፅዋ ቅመሽው አላት
ይጠፋል ኩነኔ ይጠፋል አበሳ
እንደ ፈጣሪያችን ማርያም ስትነሳ
እየባረከቻት ኢትዮጵያን በእጆቿ
በይባቤ አረገች እሷም እንደ ልጇ
ከሰው የተለየች መሆኗን ሲያበስር
ሞት በጥር ሆነ ነሃሴ መቃብር
አይሁዳዊው ቀንቶ ሲሰርቅ ሥጋዋን
የመለኮቱ ሰይፍ ቆርጠው እጁን
ብዙው ይጾመዋል የፍልሰታን ፆም
ከእህል ተከልክሎ ከሥጋ ከደም
ሐዋርያው ፊሊጶስ ትንሣኤዋን ሲሻ
ከወንድሞቹ ጋር ዕርገቷንም ሲሻ
በስሟ ተነሱ ሊፆሙ በጋራ።
የበረከት ፆም ያድርግልን!
@Mgetem
@Mgetem
@Ask_Boa_Bot
👍3❤1
#ፆመኛ_ነኝ!
@Mgetem
ከምግብ እርቄ
ሰዓቷን ጠንቅቄ
ሥርዓት አከብራለሁ
ከሥጋ ከወተት ንክች አላደርግም በደንብ እጾማለሁ
በእርግጥ ወዳፍ ሚገባ ነውና የማያረክስው
ጾምን ባልበላበት ሰዶቤበታለሁ
እጄ ሥጋም ባይዝ ሰውን ይጠቁማል
ሰው ይወነጅላል
እግሬ አመድ ሆኖበቅቤ ባዮወዛም
ወደ ጥፋት መንገድ መሮጡ አልቀረም
የውስጡ አካሌ ያ ድብቁ ነገር
ያ የልቤ ወዳጄ ቅቤና ቅባቱ
አልፎ ባይነካካው እዚያ ተደብቆ
ሰዎች ላይ ለማሴር
ክፋት ለማውጠንጠን
እንደምን ይሳነው!
አዎን ይሄ ሳይቆጠር
በርግጥ እጾማለሁ
ነጠላ አድርጌ
ቅዳሴ አስቀድሼ
በአንድ እግሬ ቆሜ
ጸሎት አደርሳለሁ
አዎን ጾመኛ ነኝ
በደንብ አከፍላለሁ
ሩጫዬን ያለግብ እደመድማለሁ።
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
@Mgetem
ከምግብ እርቄ
ሰዓቷን ጠንቅቄ
ሥርዓት አከብራለሁ
ከሥጋ ከወተት ንክች አላደርግም በደንብ እጾማለሁ
በእርግጥ ወዳፍ ሚገባ ነውና የማያረክስው
ጾምን ባልበላበት ሰዶቤበታለሁ
እጄ ሥጋም ባይዝ ሰውን ይጠቁማል
ሰው ይወነጅላል
እግሬ አመድ ሆኖበቅቤ ባዮወዛም
ወደ ጥፋት መንገድ መሮጡ አልቀረም
የውስጡ አካሌ ያ ድብቁ ነገር
ያ የልቤ ወዳጄ ቅቤና ቅባቱ
አልፎ ባይነካካው እዚያ ተደብቆ
ሰዎች ላይ ለማሴር
ክፋት ለማውጠንጠን
እንደምን ይሳነው!
አዎን ይሄ ሳይቆጠር
በርግጥ እጾማለሁ
ነጠላ አድርጌ
ቅዳሴ አስቀድሼ
በአንድ እግሬ ቆሜ
ጸሎት አደርሳለሁ
አዎን ጾመኛ ነኝ
በደንብ አከፍላለሁ
ሩጫዬን ያለግብ እደመድማለሁ።
@Mgetem
@Mgetem
@MENFESAWItsufoche
👍3
#ተዋህዶ_አትፈርስም
@Mgetem
ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነፀ፣
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ፣
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላት የማይበቃዉ፣
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ መስቀል ላይ የወጣዉ።
በደም ታንፀናል በማይጠፋ ቀለም፣
ለእኛ ብሎ እርሱ ጌታ ቢሰቀልም፣
መሠረቱ ኢየሱስ ግድግዳዉ ቅዱሳን፣
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምዕመናን።
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ፀንተን፣
እግዚአብሔርን ይዘን ማን ይሆን የሚከሰን?
መሃመዳዊያን ወይም ጅሆቫ ዊትነስ፣
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደግሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ፣
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ።
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል፣
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል።
ስንሞት እንበዛለን መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንፀናለን፣
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን።
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና፣
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና።
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የእኛ ብቻ፣
እንደ አሸዋ የበዛን እስከዓለም ዳርቻ።
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ፣
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ፣
እናንተ ስትጠፉ በገሀነም እሳት፣
ሰማዕታት በአባታቸዉ እቤት
ይሰበሰባሉ መንግስተ ሰማያት።
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም፣
በፍፁም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን።
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀ፣
ድል ላታደርግ እንደዉ ራስህን አታስጨንቀዉ፣
ሃሰት እዉነትን መቼ ነዉ አሸንፎ የሚያቀዉ?
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ፣
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን ሴራ በእምነታችሁ ናዱ።
በእምነት እንሞላ በፅናት እንቁም በተስፋ እንዉጣ፣
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻም እንዲያጣ።
የጦር ዕቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ፣
ዘመቻዉን አፅኑት ቅድስቲቷ ምድር አርዮስ እንዳይገባ።
የጦር ሠልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም፣
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም።
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ፣
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ።
መምቻው ክርስቶስ ነው የእሳት መዶሻ፣
ምሽጋችን ቅድስት የኃጥአን መሸሻ።
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
@Mgetem
@Mgetem
@AskBoaBot
@Mgetem
ድርጅት አይደለም በሰዉ የታነፀ፣
ፖለቲካም አይደል ዘርን ያጣቀሰ፣
ሚስጥሩ ፍቅር ነዉ ቃላት የማይበቃዉ፣
እኛን ስለመዉደድ በፍቅር ተስቦ መስቀል ላይ የወጣዉ።
በደም ታንፀናል በማይጠፋ ቀለም፣
ለእኛ ብሎ እርሱ ጌታ ቢሰቀልም፣
መሠረቱ ኢየሱስ ግድግዳዉ ቅዱሳን፣
ግንቦቹ እኛ ነን የእርሱ ምዕመናን።
ልንወድቅ አንችልም በእርሱ ፍቅር ፀንተን፣
እግዚአብሔርን ይዘን ማን ይሆን የሚከሰን?
መሃመዳዊያን ወይም ጅሆቫ ዊትነስ፣
ፕሮቴስታንትም ሁን ወይ ደግሞ ካቶሊክ
አለቱን ላታፈርስ የሰዉ ደም አታፍስስ፣
ምንጩንም ላታደርቅ ከመቅደሱ እራቅ።
ካህኑ ቢታረድ መቅደሱ ቢቃጠል፣
እንበዛለን እንጂ የለም የሚጎድል።
ስንሞት እንበዛለን መከራዉ ሲበዛ በፍቅር እንፀናለን፣
በእሳት ስንቃጠል እንለመልማለን።
ከማይደክም አባት ተፈጥረናልና፣
አርዮስ አትልፋ እንላለን ቀና።
ሰልፉ የእኛ ነዉ ድልም የእኛ ብቻ፣
እንደ አሸዋ የበዛን እስከዓለም ዳርቻ።
ካህኑን ግደሉ መቅደሱን አቃጥሉ፣
ቅጥሩንም አፍርሱ ልጆቹን በትኑ፣
እናንተ ስትጠፉ በገሀነም እሳት፣
ሰማዕታት በአባታቸዉ እቤት
ይሰበሰባሉ መንግስተ ሰማያት።
ይህ ነዉ ክርስትና የማይጠፋ ቀለም፣
በፍፁም ማይጨልም ሁሌ ሚሰጥ ብርሃን።
እናማ አርዮስ ቁርጥህን እወቀ፣
ድል ላታደርግ እንደዉ ራስህን አታስጨንቀዉ፣
ሃሰት እዉነትን መቼ ነዉ አሸንፎ የሚያቀዉ?
ባንድነት ተነሱ የእምነትን ሰይፍ ያዙ፣
በፍቅር ማርኩና የዲያቢሎስን ሴራ በእምነታችሁ ናዱ።
በእምነት እንሞላ በፅናት እንቁም በተስፋ እንዉጣ፣
ጠላት አፍሮ እንዲቀር መድረሻም እንዲያጣ።
የጦር ዕቃችሁን ልበሱ እንደ ካባ፣
ዘመቻዉን አፅኑት ቅድስቲቷ ምድር አርዮስ እንዳይገባ።
የጦር ሠልፍ አንሻም ቀስት አንወረዉርም፣
ደም እያፈሰስን እርሱ የፈጠረዉን እኛ አንገድልም።
ቀስትና ጦር ይዘን አንወጣም ዘመቻ፣
ጠጠርም አንለቅምም አሳዳጁን መምቻ።
መምቻው ክርስቶስ ነው የእሳት መዶሻ፣
ምሽጋችን ቅድስት የኃጥአን መሸሻ።
🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸🔸
@Mgetem
@Mgetem
@AskBoaBot
👍2❤1
++ ልብሱ ዘመብረቅ ++
@Mgetem
ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
(ውርስ ትርጉም)
ሊቀ ነቢይ ሙሴ፤
ከሲና ሲመለስ ፥ሕጉን ተቀብሎ፤
ካ’ምላክ ተነጋግሮ፤
ብርሃነ ገጹ አንፀባርቆ ኖሮ፤
የሰናፍጭ ታህል ቅንጣተ ፀዳሉ፤
በፊቱ መሳሉ፤
አሮን ፣ እስራኤልን ፍጹም አስፈራቸው፤
ሊያዩትም አልቻሉ።
ስለዚህ ለመኑት፤
“ፊትህን በበፍታ ሸፍንልን” አሉት።
ዛሬ ግን ብርሃኑ እንደሙሴ ያይደለ፤
ቅንጣት ሳይሆን ምሉዕ፤
“የዓለም ብርሃን” ፣ “ፀሐይ” የተባለ፤
የሙሴ ፈጣሪ፤
በታቦር ተራራ ከሙሴ ጋር ሳለ፤
ብርሃነ መለኮት ክብሩን መመልከቱ፤
ከብዷቸው ሲወድቁ ፤
ከእርሱ ጋራ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ፤
በምን ይሸፍነው?
ተለውጦ ፀሐይ የሆነውን ፊቱ’።
ምክንያቱማ ልብሱ ፤ ይሸፍናል ሲባል፤
ፀአዳም ከመሆን፤
ሊያዩ እስኪሳናቸው ፤
እንደ መብረቅ ባርቋል።
መነሻ ቅኔ፦ ሥላሴ
ዘመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ
ሰአልዎ ፡እስራኤል፤
ለሙሴ፡ ይትገልበብ ፡በሰንዱናት፤
ኅጠተ-ብርሃን ንስቲተ ፡በገጹ ፥
አመ ነጽሮተ ፈርሁ፤
ይእዜሰ እምኀበ -ኢኮነ፥ ብርሃኑ ከማሁ፤
እግዚአ- ሙሴ ክርስቶስ፥
ለዘሀለዉ ምስሌሁ፤
በምንት ይትገልበብ ፥ገጸ ዚአሁ?
እስመ -ከመ -መብረቅ በረቀ አልባሲሁ፤
እስከ ስዕኑ ነጽሮ ኪያሁ።
________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
ዲ/ን ከሣቴብርሃን ገ/ኢየሱስ
(ውርስ ትርጉም)
ሊቀ ነቢይ ሙሴ፤
ከሲና ሲመለስ ፥ሕጉን ተቀብሎ፤
ካ’ምላክ ተነጋግሮ፤
ብርሃነ ገጹ አንፀባርቆ ኖሮ፤
የሰናፍጭ ታህል ቅንጣተ ፀዳሉ፤
በፊቱ መሳሉ፤
አሮን ፣ እስራኤልን ፍጹም አስፈራቸው፤
ሊያዩትም አልቻሉ።
ስለዚህ ለመኑት፤
“ፊትህን በበፍታ ሸፍንልን” አሉት።
ዛሬ ግን ብርሃኑ እንደሙሴ ያይደለ፤
ቅንጣት ሳይሆን ምሉዕ፤
“የዓለም ብርሃን” ፣ “ፀሐይ” የተባለ፤
የሙሴ ፈጣሪ፤
በታቦር ተራራ ከሙሴ ጋር ሳለ፤
ብርሃነ መለኮት ክብሩን መመልከቱ፤
ከብዷቸው ሲወድቁ ፤
ከእርሱ ጋራ ያሉት ደቀ መዛሙርቱ፤
በምን ይሸፍነው?
ተለውጦ ፀሐይ የሆነውን ፊቱ’።
ምክንያቱማ ልብሱ ፤ ይሸፍናል ሲባል፤
ፀአዳም ከመሆን፤
ሊያዩ እስኪሳናቸው ፤
እንደ መብረቅ ባርቋል።
መነሻ ቅኔ፦ ሥላሴ
ዘመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬ
ሰአልዎ ፡እስራኤል፤
ለሙሴ፡ ይትገልበብ ፡በሰንዱናት፤
ኅጠተ-ብርሃን ንስቲተ ፡በገጹ ፥
አመ ነጽሮተ ፈርሁ፤
ይእዜሰ እምኀበ -ኢኮነ፥ ብርሃኑ ከማሁ፤
እግዚአ- ሙሴ ክርስቶስ፥
ለዘሀለዉ ምስሌሁ፤
በምንት ይትገልበብ ፥ገጸ ዚአሁ?
እስመ -ከመ -መብረቅ በረቀ አልባሲሁ፤
እስከ ስዕኑ ነጽሮ ኪያሁ።
________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍4
#ስውር_ቅኔ
@Mgetem
#የቤተ_ክርስትያን ደጅ ዕለት ተለት ስሜ
#በፆም_በፀሎት በስግደት ደክሜ
አምላኬን ለመንኩት
የሚያስፈልገኝን ዘርዝሬ ነገርኩት
የሚያስፈልገኝ ነገር ቢዘገይ ጊዜ
ነፈከኝ ብዬ በምሬት አንካሴ
#ፈጣሪን_ወጋሁት
#ልቡን_አደማሁት
#በስርዓት_አጥ_ምሬቴ
በአጉል እምነቴ
ልቡ ስለቆሰለ
#በደመና_መሀል ጌታዬ እንዲህ አለ
‹‹ ሁሉን የማቀው እኔ ሆኘ ሳለ
ነፈከኝ ለማለት ምነው ልቦናህ ቸኮለ
ዘርዝረህ የላከውን የልመና ፀሎት
ይመለከት ዘንድ ዐይኔ ተተከለ
የምትፈልገው እንጅ የሚያስፈልግህ አንድም እንደሌሌ
የታዘበው እጄ የጠየከኝን ከማድረግ ተከለከለ
ግና ልጄ አዕምሮህ በደንብ ካሰተዋለ
ባለማድረግ ውስጥም ታላቅ ማድረግ አለ>>
_________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
#የቤተ_ክርስትያን ደጅ ዕለት ተለት ስሜ
#በፆም_በፀሎት በስግደት ደክሜ
አምላኬን ለመንኩት
የሚያስፈልገኝን ዘርዝሬ ነገርኩት
የሚያስፈልገኝ ነገር ቢዘገይ ጊዜ
ነፈከኝ ብዬ በምሬት አንካሴ
#ፈጣሪን_ወጋሁት
#ልቡን_አደማሁት
#በስርዓት_አጥ_ምሬቴ
በአጉል እምነቴ
ልቡ ስለቆሰለ
#በደመና_መሀል ጌታዬ እንዲህ አለ
‹‹ ሁሉን የማቀው እኔ ሆኘ ሳለ
ነፈከኝ ለማለት ምነው ልቦናህ ቸኮለ
ዘርዝረህ የላከውን የልመና ፀሎት
ይመለከት ዘንድ ዐይኔ ተተከለ
የምትፈልገው እንጅ የሚያስፈልግህ አንድም እንደሌሌ
የታዘበው እጄ የጠየከኝን ከማድረግ ተከለከለ
ግና ልጄ አዕምሮህ በደንብ ካሰተዋለ
ባለማድረግ ውስጥም ታላቅ ማድረግ አለ>>
_________________________
@Mgetem
@Mgetem
@Mgetem
👍2
#ይህችን_ዓመት_ተወኝ 🌼
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@MGETEM
ከዓመት እስከ ዓመት - ፍሬን ሳላፈራ - ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ - ሁለቱንም ሳልሆን - እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ
አለሁኝ በቤትህ - ለሙን መሬትህን - እያጎሳቆልኩኝ
አውቃለሁ አምላኬ - ፍሬዬን ለመልቀም - እንዳመላለስኩህ
ዛሬም ሳላፈራ - እሾህን አብቅዬ - ደርቄ ጠበቅሁህ
ያልተደረገልኝ - ያላፈሰሰክብኝ - ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ - አላርምህ አለኝ - አልለየኝም ከዓለም
የማትሰለቸኝ ሆይ - ተነሥቼ እስክቆም - እባክህ ታገሠኝ
የእኔን ክፋት ተወው - መልአክህን ሰምተህ - ይህችን ዓመት ተወኝ!
አውቃለሁ ታውቃለህ - ቀጠሮን ሰጥቼ - እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ - ብዙ ጊዜ ዝቼ - በወሬ እንደምቀር
‹ዘንድሮስ…!› እንዳልኩኝ - አምና ይሄን ጊዜ - ሰምተኸኝ ነበረ
ምንም ሳልለወጥ - ‹ዘንድሮዬ› አልፎ - በአዲስ ተቀየረ
ፍሬ የማይወጣኝ - እኔን በመኮትኮት - እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ - ዛሬም አልበቃኝም - በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውኃ - በድንጋይ ልጅህ ላይ - ሳትታክት ስታፈስስ -
ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ - ሕይወቴን ሳይለውጥ - እንዲያው ፈስሶ ቀረ
ቃልህን ጠግቤ - እያገሳሁት ነው - ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን - አልያዝህ አለኝ - ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘሁ - ከቅዱስ መጽሐፍህ - ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ - አንድ ጥቅስ አጣሁኝ - በበደል ተኝቼ
ውጤቴ ደካማ - ትምህርት የማይሠርጸኝ - ተማሪ ብሆንም
ይህችን ዓመት ተወኝ - ደግሞ ትንሽ ልማር - ታገሠኝ አሁንም!
እባክህ አልቆረጥ - በቅዱስ መሬትህ - ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን - የፍሬያቸው ሽታ - መዓዛ እንዲደርሰኝ
የተሸከምከኝ ሆይ - ዛሬም ተሸከመኝ - አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሠኛል - ጠላት እየሆንኩት - አይሠሩ ስሠራ!
አታውጣኝ ከቤትህ - ብዙ ቦታ አልይዝም - ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ - ቤት የማላጣብብ - ፍሬ አልባ በለስ ነኝ!
ቦታስ የሚይዙት - ባለ ምግባሮቹ - ቅዱሳንህ ናቸው
ልክ እንደ ዘንባባ - የተንዠረገገ - ተጋድሎ ጽድቃቸው!
ከሊባኖስ ዝግባ - እጅጉን የበዛ - ገድል ትሩፋታቸው!
እኔ አይደለሁም - ቦታስ የምትይዘው - የአንተው እናት ናት
ሥሮቿ በምድር - ጫፎቿ በሰማይ - ሲደርሱ ያየናት
ይሀችን ዓመት ተወኝ - ከሥርዋ እሆናለሁ - ባፈራ ምናልባት!..
ይህችን ዓመት ተወኝ - እባክህ አምላኬ - አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺህ ዓመት አንድ ቀን - አይደለም ወይ ለአንተ - ዓመት ኢምንት ናት!
ይሄ ዓመት አልፎ - ዳግም ‹ዓመት ሥጠኝ› - እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ - ይህችን ዓመት ተወኝ - የወጉን እንዳደርስ!
🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸
@Mgetem
@Mgetem
@AlewROBOT
ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
@MGETEM
ከዓመት እስከ ዓመት - ፍሬን ሳላፈራ - ደረቅ እንደሆንኩኝ
በራድ ወይም ትኩስ - ሁለቱንም ሳልሆን - እንዲያው ለብ እንዳልኩኝ
አለሁኝ በቤትህ - ለሙን መሬትህን - እያጎሳቆልኩኝ
አውቃለሁ አምላኬ - ፍሬዬን ለመልቀም - እንዳመላለስኩህ
ዛሬም ሳላፈራ - እሾህን አብቅዬ - ደርቄ ጠበቅሁህ
ያልተደረገልኝ - ያላፈሰሰክብኝ - ያልሰጠኸኝ የለም
ነገር ግን ይህ ሁሉ - አላርምህ አለኝ - አልለየኝም ከዓለም
የማትሰለቸኝ ሆይ - ተነሥቼ እስክቆም - እባክህ ታገሠኝ
የእኔን ክፋት ተወው - መልአክህን ሰምተህ - ይህችን ዓመት ተወኝ!
አውቃለሁ ታውቃለህ - ቀጠሮን ሰጥቼ - እንደማላከብር
ብዙ ጊዜ አቅጄ - ብዙ ጊዜ ዝቼ - በወሬ እንደምቀር
‹ዘንድሮስ…!› እንዳልኩኝ - አምና ይሄን ጊዜ - ሰምተኸኝ ነበረ
ምንም ሳልለወጥ - ‹ዘንድሮዬ› አልፎ - በአዲስ ተቀየረ
ፍሬ የማይወጣኝ - እኔን በመኮትኮት - እጆችህ ደከሙ
እኔ ግን አለሁኝ - ዛሬም አልበቃኝም - በኃጢአት መታመሙ
የቃልህን ውኃ - በድንጋይ ልጅህ ላይ - ሳትታክት ስታፈስስ -
ዘመን ተቆጠረ
ወደ ልቤ ሳይሰርግ - ሕይወቴን ሳይለውጥ - እንዲያው ፈስሶ ቀረ
ቃልህን ጠግቤ - እያገሳሁት ነው - ሌሎች እስኪሰሙ
በቃልህ መኖር ግን - አልያዝህ አለኝ - ከበደኝ ቀለሙ
ብዙ ጥቅስ አገኘሁ - ከቅዱስ መጽሐፍህ - ገልጬ አይቼ
ከራሴ ላይ ብቻ - አንድ ጥቅስ አጣሁኝ - በበደል ተኝቼ
ውጤቴ ደካማ - ትምህርት የማይሠርጸኝ - ተማሪ ብሆንም
ይህችን ዓመት ተወኝ - ደግሞ ትንሽ ልማር - ታገሠኝ አሁንም!
እባክህ አልቆረጥ - በቅዱስ መሬትህ - ልቆይ ፍቀድልኝ
ያፈሩት ቅዱሳን - የፍሬያቸው ሽታ - መዓዛ እንዲደርሰኝ
የተሸከምከኝ ሆይ - ዛሬም ተሸከመኝ - አትሰልቸኝ አደራ
ማን ይታገሠኛል - ጠላት እየሆንኩት - አይሠሩ ስሠራ!
አታውጣኝ ከቤትህ - ብዙ ቦታ አልይዝም - ፍሬ ስለሌለኝ
ስፍራ የማያሻኝ - ቤት የማላጣብብ - ፍሬ አልባ በለስ ነኝ!
ቦታስ የሚይዙት - ባለ ምግባሮቹ - ቅዱሳንህ ናቸው
ልክ እንደ ዘንባባ - የተንዠረገገ - ተጋድሎ ጽድቃቸው!
ከሊባኖስ ዝግባ - እጅጉን የበዛ - ገድል ትሩፋታቸው!
እኔ አይደለሁም - ቦታስ የምትይዘው - የአንተው እናት ናት
ሥሮቿ በምድር - ጫፎቿ በሰማይ - ሲደርሱ ያየናት
ይሀችን ዓመት ተወኝ - ከሥርዋ እሆናለሁ - ባፈራ ምናልባት!..
ይህችን ዓመት ተወኝ - እባክህ አምላኬ - አንድ ዓመት ምንህ ናት
ሺህ ዓመት አንድ ቀን - አይደለም ወይ ለአንተ - ዓመት ኢምንት ናት!
ይሄ ዓመት አልፎ - ዳግም ‹ዓመት ሥጠኝ› - እስከምልህ ድረስ
እባክህን ጌታ - ይህችን ዓመት ተወኝ - የወጉን እንዳደርስ!
🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸🌼🌸
@Mgetem
@Mgetem
@AlewROBOT
👍7❤2
Forwarded from የorthodox መዝሙር ብቻ
🌼የእንቁጣጣሽ መዝሙር🌼
🌼🌼
እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ሉቃስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)ጌቶች አሉ ብለን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)እሜቴ አሉ ብለን
አበባዮሽ 🌼 ለምለም አበባዮሽ 🌼 ለምለም
እንቆቅልሽ - - ንግሥት ልትፈትል ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - - ንግሥት እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን - ንግሥት አጫወታቸው - - ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ🌼 ንግሥት እያሳየችው - - ንግሥት
መአዛው የሚሸት - - ከሁለቱ የቱ ነው አለቸው - - ለንጉሥ
ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ(፪)
🌼የአገር አምባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ
እንቆቅልሹ - - የሳባ ከበድም ቢለው - -🌼 የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - - ሰለሞን ቢለው ለሎሌው - -ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ - - ሊቀስሙ🌼 ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ - - መለሠ ለተጠየቀው - - በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - - አለ አልተሠወረው 🌼 በእውነት
🌼አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (፪)
🌼 ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (፪)
🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት ምስጋና አቅርባ - - ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት ንግስተ ሣባ 🌼 ንግሥት
ጥበቡን አይታ - - ንግሥት አደነቀችው - - ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - - ንግሥት ዕንቁ ሰጠችው - - ንግሥት
ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)🌼🌼
የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (፪)🌼🌼
የኢትዮጵያ ሠዎች - -ለንግሥት ቆሙ በተራ - -ለንግሥት
እደጅ ሆነው 🌼 ለንግሥት ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - - ለንግሥት ሀገር ስትገባ - - ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - - ለንግሥት የፈካ አበባ 🌼ለንግሥት
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)🌼🌼
ኢየሩሳሌም - - ንግሥት ደርሠሽ መጣሽ - - ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - - ንግሥት ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት
🌼ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)🌼🌼
🌼ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)🌼🌼
🌼የአባቶች ተስፋ - - ለፃድቃን የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - - ለፀሎት የአሮን በትር - - ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት ይዘሸ የመጣሽ - - ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ ለሀገር መሠረት - በእውነት🌼🌼
🌼 አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)🌼🌼
በህገ ልቦና - - ህጉን ፈጣሪን አውቀሽ - - ህጉን
ህገ ነቢያትን - - ከዓለም ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን 🌼ለጌታ መስዋዕት አቅርበሽ - - ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን- -በፊት ይዘሽ ተገኘሽ 🌼 በፊት
🌼ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)🌼🌼
🌼ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)🌼🌼
ካለፈው ሰህተት - - ሁላችን እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት - - ለሁሉም መጣ ማቴዎስ- -ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - - በጊዜው ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ - - በጊዜው 🌼 ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት - - በጊዜው ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ - - መጥምቁ ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው🌼🌼
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)🌼🌼
🌼 ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)🌼🌼
ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ እያለች እማማ አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)
አበባ ለምለም ቀጤማ ለምለም
ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)
አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)
ከበረው ይቆዩ ከብረው
አመት አወደ አመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
የፍቅር ሸማን ለብሰው
ንስሐ ገብተው ቆርበው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
❤@yeorthodoxmezmur💝
💝@yeorthodoxmezmur❤
💖@yeorthodoxmezmur💖
🌼🌼
እሰይ /ደስ ደስ ይበላችሁ/(፪)
ቅዱስ ሉቃስ መጣላችሁ
ደስ ደስ ይበላችሁ
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)ጌቶች አሉ ብለን
ደስ ብሎን መጣን ደስ ብሎን(፪)እሜቴ አሉ ብለን
አበባዮሽ 🌼 ለምለም አበባዮሽ 🌼 ለምለም
እንቆቅልሽ - - ንግሥት ልትፈትል ሄዳ - - ንግሥት
ንግስተ አዜብ - - ንግሥት እናት ማክዳ - - ንግሥት
በልቧ ያለውን - ንግሥት አጫወታቸው - - ንግሥት
አሰቀምጣ አበባ🌼 ንግሥት እያሳየችው - - ንግሥት
መአዛው የሚሸት - - ከሁለቱ የቱ ነው አለቸው - - ለንጉሥ
ንግስት ሆይ ለጥያቄሽ ጥበብ አለሽ(፪)
🌼የአገር አምባር የሚሆነው ከልብ ሽተሽ
እንቆቅልሹ - - የሳባ ከበድም ቢለው - -🌼 የሳባ
ጥበብ ሰላለው - - ንጉሡ ሚሥጥሩን ሊያውቀው - - ንጉሡ
ክፈት መስኮቱን - - ሰለሞን ቢለው ለሎሌው - -ሰለሞን
ገቡ ንቦቹ - - ሊቀስሙ🌼 ከአባባው አርፈው - - ሊቀስሙ
ብልህ ጠቢቡ - - መለሠ ለተጠየቀው - - በእውነት
ንጉስ ሰለሞን - - አለ አልተሠወረው 🌼 በእውነት
🌼አደይ ቅድስት ሀገሬ እልል በይ (፪)
🌼 ኢትዩዮጲያ የዝና ስሟ በዓለም ተሠማ (፪)
🌼
ለፈጣሪዋ - - ንግሥት ምስጋና አቅርባ - - ንግሥት
ኢትዮጲያዊቷ - - ንግሥት ንግስተ ሣባ 🌼 ንግሥት
ጥበቡን አይታ - - ንግሥት አደነቀችው - - ንግሥት
ወርቅ ሸቶውን - - ንግሥት ዕንቁ ሰጠችው - - ንግሥት
ንግስት ሆይ ምስክር ሆንሽ ለሀገርሽ (፪)🌼🌼
የአምላክን የፈጣሪያችን ስሙን ጠርተሽ (፪)🌼🌼
የኢትዮጵያ ሠዎች - -ለንግሥት ቆሙ በተራ - -ለንግሥት
እደጅ ሆነው 🌼 ለንግሥት ለዙፋን ክብሯ - - ለንግሥት
በመስከረም ወር - - ለንግሥት ሀገር ስትገባ - - ለንግሥት
ይዘው ሥጦታ - - ለንግሥት የፈካ አበባ 🌼ለንግሥት
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በኢትዮጵያ በራ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጲያ በታሪክሽ ጥንታዊት ነሽ (፪)🌼🌼
ኢየሩሳሌም - - ንግሥት ደርሠሽ መጣሽ - - ንግሥት
እንኳን በክብር - - ንግሥት ለዚህ አበቃሽ - - ንግሥት
ከአምላክ በረከት - - ንግሥት ፍሬ አግኝተሽ - - ንግሥት
የዘሽ ስጦታ - - ንግሥት ዕንቁ ለጣጣሽ - - ንግሥት
🌼ንግስት ሆይ ለታሪክሽ ክብር አለሽ (፪)🌼🌼
🌼ልጆችሽ አበባዮሽ እያልን እናስታውስሽ (፪)🌼🌼
🌼የአባቶች ተስፋ - - ለፃድቃን የነቢያት ትንቢት - - ለፅናት
የሙሴ ፅላት - - ለፀሎት የአሮን በትር - - ለፅናት
የዳዊት መንግስት - - ለፅናት ይዘሸ የመጣሽ - - ከጥንት
አምስቱን አውታር - - ለሠጠሽ ለሀገር መሠረት - በእውነት🌼🌼
🌼 አደይ ቅድስት ኢትዮጵያ እልል በይ (፪)🌼🌼
🌼ኢትዮጵያ በልጆችሽ ደስ ይበልሽ (፪)🌼🌼
በህገ ልቦና - - ህጉን ፈጣሪን አውቀሽ - - ህጉን
ህገ ነቢያትን - - ከዓለም ፈጥነሽ ተቀበልሽ - - ከዓለም
በብሉይ ኪዳን 🌼ለጌታ መስዋዕት አቅርበሽ - - ለጌታ
ተስፋ ካረጉት - - ከአይሁድ ከአስራኤል - - ከአይሁድ
ህገ ወንጌልን- -በፊት ይዘሽ ተገኘሽ 🌼 በፊት
🌼ኢትዮጵያ ደስ ይበልሽ ትልቅ ፀጋ አለሽ(፪)🌼🌼
🌼ስለፈፀምሽ ሦስቱን ህግጋት ለፈጣሪሽ (፪)🌼🌼
ካለፈው ሰህተት - - ሁላችን እንድንመለስ - - ሁላችን
አዲሱ ዓመት - - ለሁሉም መጣ ማቴዎስ- -ለሁሉም
ይህም ያልፍና - - በጊዜው ይመጣል ማርቆስ - - በጊዜው
ሌላው ይተካል - - በጊዜው ዘመነ ሉቃስ - - በጊዜው
ወልደነጓድጓድ - - በጊዜው 🌼 ሲደርስ ዮሐንስ - - በጊዜው
በየአራት ዓመት - - በጊዜው ለሁሉም ሲደርስ - - በጊዜው
በየዓመቱ - - መጥምቁ ቅዱስ ዩሐንስ - - በጊዜው🌼🌼
🌼አደይ የብርሃን ጮራ በዮሐንስ በራ(፪)🌼🌼
🌼 ኢትዮጵያ ባሕል ቋንቋሽ የሚያኮራሽ (፪)🌼🌼
ልጅ አበባ ልጅ አበባዬ አዬ ውዲቷ እናቴ
ልጅ አበባ እያለች እማማ አዬ ውዲቷ እናቴ
ምክሯን ሁሌ እኔ እንድሰማ አዬ ውዲቷ እናቴ
እያሻሸች እንድሆን ጤናማ አዬ ውዲቷ እማማ
አዬ ውዲቷ እናቴ (፪)
አበባ ለምለም ቀጤማ ለምለም
ኢትዮጵያ እንዳንቺ የለም (፪)
አብዬ ኧኸ ደግሞም እማምዬ
መጣሁ ለሰላምታ ከቤት አሉ ብዬ
እንኳን ለቅዱስ ዮሐንስ አደረሰዎት ብዬ (፪)
ይሸታል ዶሮ ዶሮ (፪) ከማምዬ ጓሮ (፪)
ይሸታል የወይን ጠጅ (፪) ከጋሽዬ ደጅ (፪)
ከበረው ይቆዩ ከብረው
አመት አወደ አመት ደርሰው
ቅን ታዛዥ ልጅን ወልደው
ትሁት ሰው አክባሪ ሆነው
የፍቅር ሸማን ለብሰው
ንስሐ ገብተው ቆርበው
ከብረው ይቆዩ ከብረው
❤@yeorthodoxmezmur💝
💝@yeorthodoxmezmur❤
💖@yeorthodoxmezmur💖
👍6
#እሰይ_የምስራች
@Mgetem
እሰይ የምስራች ዘመን ተሻገርን
አምናን አሳልፎ ለዘንድሮ አበቃን
ይመስገን ፈጣሪ ለንስሀ ህይወት እድሜ ጨመረልን
አሁን ካካፈለን ከዚህ አዲስ አመት
ሳይሆን መዋተቱ ለስጋ ፍላጎት
ልክ እንደ አበቦቹ አፍርተን አሽተን
ደግሞ እንደ አዕዋፉቱ ለእርሱ ዘምረን
ዘመን ለንስሀ ዕድሜ ለፍስሀ አምላክ ካቀናጀን
ተመስገን እንበለው ምን አለ የሌለን
Nani girma
@Mgetem
@Mgetem
@Sulamatiz
እንኳን አደረሳችሁ
@Mgetem
እሰይ የምስራች ዘመን ተሻገርን
አምናን አሳልፎ ለዘንድሮ አበቃን
ይመስገን ፈጣሪ ለንስሀ ህይወት እድሜ ጨመረልን
አሁን ካካፈለን ከዚህ አዲስ አመት
ሳይሆን መዋተቱ ለስጋ ፍላጎት
ልክ እንደ አበቦቹ አፍርተን አሽተን
ደግሞ እንደ አዕዋፉቱ ለእርሱ ዘምረን
ዘመን ለንስሀ ዕድሜ ለፍስሀ አምላክ ካቀናጀን
ተመስገን እንበለው ምን አለ የሌለን
Nani girma
@Mgetem
@Mgetem
@Sulamatiz
እንኳን አደረሳችሁ
".ይህንን አልስማ "
@Mgetem
የኖህ መሸሸጊያ አምሳለ ሐመሩ
የሙሴ ሰገነት የምስጢር ደብሩ
አማሌቅ ሊያጠፋሽ ሲመክር ሲሰማማ
አኔ ልቅደም ካአንቺ ይህንስ አልስማ
...............................ይህንን አልስማ
ክርስቶስ የዘራሽ የስንዴዋ አዝመራ
የማጠፊው መብራት ያለሽ በተራራ
የጴጥሮስ መሠረት አለት ሽልማቱ
አይስማ ጆሮዬ ሲያሳዱሽ በከንቱ
የአትናቴዎስ እርሻ የቄርሎስ ቡቃያ
የዴስቆርዮስ ፍሬ የጽናት ማሳያ
የዮሐንስ ትምህርት አፈ ወርቅነቱ
አልይሽ እናቴ ሲበላሽ እሳቱ
...........................ይህንስ አልስማ
ከ Biruk Asamere
@Mgetem
@Mgetem
@sulamatiz
@Mgetem
የኖህ መሸሸጊያ አምሳለ ሐመሩ
የሙሴ ሰገነት የምስጢር ደብሩ
አማሌቅ ሊያጠፋሽ ሲመክር ሲሰማማ
አኔ ልቅደም ካአንቺ ይህንስ አልስማ
...............................ይህንን አልስማ
ክርስቶስ የዘራሽ የስንዴዋ አዝመራ
የማጠፊው መብራት ያለሽ በተራራ
የጴጥሮስ መሠረት አለት ሽልማቱ
አይስማ ጆሮዬ ሲያሳዱሽ በከንቱ
የአትናቴዎስ እርሻ የቄርሎስ ቡቃያ
የዴስቆርዮስ ፍሬ የጽናት ማሳያ
የዮሐንስ ትምህርት አፈ ወርቅነቱ
አልይሽ እናቴ ሲበላሽ እሳቱ
...........................ይህንስ አልስማ
ከ Biruk Asamere
@Mgetem
@Mgetem
@sulamatiz
👍6
#መስከረም_ሲታጠን
(ዲ/ን ሕሊና በለጠ)
@Mgetem
ከብሶት አድማስ ሥር - ከጽልመቱ ማዶ - የብርሃን ጎህ ሲቀድ፣
በሃይማኖት ፍቅር - ሀገር ልቡ ነዶ - ፍርሐት ሲቀረደድ፣
የእማትን ልቅሶ - የአበውን እንባ - የውርዛዌን ወኔ፣
የአንድነትን እርሾ - የአትንኩንን ካባ - የፍትሕን ጠኔ፣
ከእግዚኦታው ማዕድ - ከካህናቱ ዕድ - ይህን ኹሉ ይዞ፣
ዕጣኑ ዐረገ - ወጣ ወደ ሰማይ - ሺ ጸሎት አርግዞ።
በታደለች ሰንበት - ዣን ተከል ሥር ያለው - ወዲህም ከጦሳ፣
በሃይማኖት እሳት - ልቡ የተቃጠለው - የመንፈሱን እንጂ - የምድሩን
ቢረሳ፣
ይግባኙን ወደ ላይ - በእግዚኦታ ሊያደርስ - በአንድነት ሲነሣ፣
ምድር ሰማይ ሆነች - ሰውም መልአክ ሆነ - ግዙፋን ረቀቁ፣
ሰላማዊ ብለው - በሰማያዊ ሰልፍ - ከሰማይ ታረቁ።
በዚህችስ ሰንበት - ግዙፍ አይደለች ምድር - አፈርም የለባት፣
ከኢዮር ከኤረር - ከራማ የተለየ - ምንስ ተሠራባት?
በዚህችስ ሰንበት.....
የመላእክት ሀገር - ኢዮር ኤረርና - ራማ ብቻ አይደሉ፣
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ - መሐረነ ክርስቶስ - እግዚኦ እያሉ፣
ማዕጠንቱን ይዘው - ጎንደርና ወሎም - ለሦስቱ ሰማያት - ራብዓይ
ሆነው ዋሉ።
እኛስ የምናውቀው - በዕለተ መልአኩ - በ12ኛው ቀን - ኅዳር ሲታጠን
ነው፣
ሀገር መልአክ ኾኖ - በ12ኛ ዓመት (2012) - ወሎና ጎንደር ላይ -
መስክዬን አጠነው።
መስከረም ሲታጠን...
ከልቡና ደጃፍ - ብሔር ሚሉት ዕድፍ፣
በማዕጠንት ምድጃ - ተጠርጎ ሲራገፍ፣
ጎጥ ሚሉት ቆሻሻ - ዘር የሚሉት ትቢያ፣
ነዶ ሲቀጣጠል - በፍቅር ማራገቢያ፤
መስከረም ሲታጠን - ከኦርቶዶክስ አድማስ ሥር፣
የምድሩ ያየሩ - የሲዖሉ ጋኔን - በጢሱ ሲታወር፣
ወዶ የታወረው - የጋኔኑ ቢጤም - ተባሉ ተጣሉን - በትግኃት ሲዘክር፣
ይህን ለመመስከር - አላየሁ አልሰማሁ - ብሎ ሲግደረደር፣
ያደለው ዐይናማ - የመላእክቱን ዐይን - ዐይኑ ያደረገ
ከሰልፈኞቹ ጋር - ያየውን መስክሮ - በክብር ዐረገ።
መስከረም ሲታጠን....
የተስፋ ብርሃን - በአቅሌስያ ደጃፍ - ጭል ጭል እያለ፣
የበሯ ላይ ጽልመት - በአንድነቱ ክንድ - የሚናድ መሰለ።
መስከረም ሲታጠን - የዕጣኑ መዓዛ - ደቡብ ላይም ሔደ፣
ሰሜንና ምሥራቅ - ምዕራብ ላይም ሔደ፣
ለሃይማኖት የመሞት - ሰማዕት የመሆን - ጥብዓት እያወደ።
መስከረም ሲታጠን....
ጥቅምትና ኅዳር - ታኅሣሥና ጥር - መጋቢት ሚያዝያም - ፈክተው
ይውላሉ፣
ቤተ ክርስቲያን ሆይ - ክረምትሽ አለፈ - በጋ ነው እያሉ።
@Mgetem
@Mgetem
@Solasc
(ዲ/ን ሕሊና በለጠ)
@Mgetem
ከብሶት አድማስ ሥር - ከጽልመቱ ማዶ - የብርሃን ጎህ ሲቀድ፣
በሃይማኖት ፍቅር - ሀገር ልቡ ነዶ - ፍርሐት ሲቀረደድ፣
የእማትን ልቅሶ - የአበውን እንባ - የውርዛዌን ወኔ፣
የአንድነትን እርሾ - የአትንኩንን ካባ - የፍትሕን ጠኔ፣
ከእግዚኦታው ማዕድ - ከካህናቱ ዕድ - ይህን ኹሉ ይዞ፣
ዕጣኑ ዐረገ - ወጣ ወደ ሰማይ - ሺ ጸሎት አርግዞ።
በታደለች ሰንበት - ዣን ተከል ሥር ያለው - ወዲህም ከጦሳ፣
በሃይማኖት እሳት - ልቡ የተቃጠለው - የመንፈሱን እንጂ - የምድሩን
ቢረሳ፣
ይግባኙን ወደ ላይ - በእግዚኦታ ሊያደርስ - በአንድነት ሲነሣ፣
ምድር ሰማይ ሆነች - ሰውም መልአክ ሆነ - ግዙፋን ረቀቁ፣
ሰላማዊ ብለው - በሰማያዊ ሰልፍ - ከሰማይ ታረቁ።
በዚህችስ ሰንበት - ግዙፍ አይደለች ምድር - አፈርም የለባት፣
ከኢዮር ከኤረር - ከራማ የተለየ - ምንስ ተሠራባት?
በዚህችስ ሰንበት.....
የመላእክት ሀገር - ኢዮር ኤረርና - ራማ ብቻ አይደሉ፣
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ - መሐረነ ክርስቶስ - እግዚኦ እያሉ፣
ማዕጠንቱን ይዘው - ጎንደርና ወሎም - ለሦስቱ ሰማያት - ራብዓይ
ሆነው ዋሉ።
እኛስ የምናውቀው - በዕለተ መልአኩ - በ12ኛው ቀን - ኅዳር ሲታጠን
ነው፣
ሀገር መልአክ ኾኖ - በ12ኛ ዓመት (2012) - ወሎና ጎንደር ላይ -
መስክዬን አጠነው።
መስከረም ሲታጠን...
ከልቡና ደጃፍ - ብሔር ሚሉት ዕድፍ፣
በማዕጠንት ምድጃ - ተጠርጎ ሲራገፍ፣
ጎጥ ሚሉት ቆሻሻ - ዘር የሚሉት ትቢያ፣
ነዶ ሲቀጣጠል - በፍቅር ማራገቢያ፤
መስከረም ሲታጠን - ከኦርቶዶክስ አድማስ ሥር፣
የምድሩ ያየሩ - የሲዖሉ ጋኔን - በጢሱ ሲታወር፣
ወዶ የታወረው - የጋኔኑ ቢጤም - ተባሉ ተጣሉን - በትግኃት ሲዘክር፣
ይህን ለመመስከር - አላየሁ አልሰማሁ - ብሎ ሲግደረደር፣
ያደለው ዐይናማ - የመላእክቱን ዐይን - ዐይኑ ያደረገ
ከሰልፈኞቹ ጋር - ያየውን መስክሮ - በክብር ዐረገ።
መስከረም ሲታጠን....
የተስፋ ብርሃን - በአቅሌስያ ደጃፍ - ጭል ጭል እያለ፣
የበሯ ላይ ጽልመት - በአንድነቱ ክንድ - የሚናድ መሰለ።
መስከረም ሲታጠን - የዕጣኑ መዓዛ - ደቡብ ላይም ሔደ፣
ሰሜንና ምሥራቅ - ምዕራብ ላይም ሔደ፣
ለሃይማኖት የመሞት - ሰማዕት የመሆን - ጥብዓት እያወደ።
መስከረም ሲታጠን....
ጥቅምትና ኅዳር - ታኅሣሥና ጥር - መጋቢት ሚያዝያም - ፈክተው
ይውላሉ፣
ቤተ ክርስቲያን ሆይ - ክረምትሽ አለፈ - በጋ ነው እያሉ።
@Mgetem
@Mgetem
@Solasc
👍8
Forwarded from የorthodox መዝሙር ብቻ
ሥላሴን አመስግኑ
ሥላሴን አመስግኑ (፪)
የምድር ፍጥረታት ዘምሩ እልል በሉ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
ምስጋና ይገባል ከምንም በፊት
ዓለማትን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ
ምስጋና ይገባል ከጠዋት እስከ ማታ
አዝ = = = = =
ኪሩቤል ሱራፌል የሚያመሰግኑት
መላእክት በሰማይ የሚዘምሩለት
እኛም የአዳም ልጆች እንዘምራለን
በሰማይም በምድር እንጠራሃለን
አዝ = = = = = =
ብራብ በሥላሴ እጠግባለሁኝ
ብጠማም በአምላኬ እረካለሁኝ
ሥላሴ አምባዬ ክብሬ ናቸውና
ሁሌ ይመሩኛል በህይወት ጎዳና
💞 @yeorthodoxmezmur 💟
💘 @yeorthodoxmezmur 💓
💖 @yeorthodoxmezmur 💝
ሥላሴን አመስግኑ (፪)
የምድር ፍጥረታት ዘምሩ እልል በሉ
በስመአብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
ምስጋና ይገባል ከምንም በፊት
ዓለማትን ሁሉ ለፈጠረ ጌታ
ምስጋና ይገባል ከጠዋት እስከ ማታ
አዝ = = = = =
ኪሩቤል ሱራፌል የሚያመሰግኑት
መላእክት በሰማይ የሚዘምሩለት
እኛም የአዳም ልጆች እንዘምራለን
በሰማይም በምድር እንጠራሃለን
አዝ = = = = = =
ብራብ በሥላሴ እጠግባለሁኝ
ብጠማም በአምላኬ እረካለሁኝ
ሥላሴ አምባዬ ክብሬ ናቸውና
ሁሌ ይመሩኛል በህይወት ጎዳና
💞 @yeorthodoxmezmur 💟
💘 @yeorthodoxmezmur 💓
💖 @yeorthodoxmezmur 💝
👍2❤1
Forwarded from የorthodox መዝሙር ብቻ
ብዙ ልጆች አሉት ለስሙ ምስክር
በዙሪያዉ ያሉት አብቅቷል ለክብር
ስለ ፍጹም ምልጃዉ የኔ ግን ይለያል
መልኩ ሚካኤል ስለዉ ደስ ይለኛል
አዝ
ከመላእክት ክብሩ ከፍ ከፍ ብሎ
በአምላክ የተሾመ ዘንዶዉንም ጥሎ
አሳዳጊየ ነዉ ሆኖ እናት አባቴ
ሚካኤል ባለበት ይሸሻል ጠላቴ
አዝ
ከሚታየዉ ሁሉ ልቤ ከሚፈራዉ
ካላየሁት ነገር ጠላት ከሰወረዉ
ያድነኛል ፈጥኖ ከመንገዴ ወቶ
ሚካኤል ሀያሉ ክንፎቹን ዘርግቶ
አዝ
በባህራን ታሪክ በነ ጠናፊኖስ
በአፎሚያ መትረፍ በነዱረታዎስ
በነብዪ ዳንኤል የጭፍን ሰምና
የሚካኤል ስራ ይቀጥላል ገና
አዝ
በጉዞ የረዳችሁ በባህር በየብሱ
ፈጥኖ ደርሶላችሁ እንባን ስታፈሱ
ስለታችሁ ሰምሯል ቁሙ በዝማሬ
በሚካኤል ምልጃ የቆማችሁ ዛሬ
አዝ
ክብር ለሚገባዉ ክብርን እንሰጣለን
ንጉስ ለወደደዉ እንሰግድለታለን
እንኳን ለሚካኤል ለሚቆም ጌታ ፊት
ክብርን እንሰጥ የለ ለምድር ሹማምት
💟 @yeorthodoxmezmur
💖 @yeorthodoxmezmur
💘 @yeorthodoxmezmur
በዙሪያዉ ያሉት አብቅቷል ለክብር
ስለ ፍጹም ምልጃዉ የኔ ግን ይለያል
መልኩ ሚካኤል ስለዉ ደስ ይለኛል
አዝ
ከመላእክት ክብሩ ከፍ ከፍ ብሎ
በአምላክ የተሾመ ዘንዶዉንም ጥሎ
አሳዳጊየ ነዉ ሆኖ እናት አባቴ
ሚካኤል ባለበት ይሸሻል ጠላቴ
አዝ
ከሚታየዉ ሁሉ ልቤ ከሚፈራዉ
ካላየሁት ነገር ጠላት ከሰወረዉ
ያድነኛል ፈጥኖ ከመንገዴ ወቶ
ሚካኤል ሀያሉ ክንፎቹን ዘርግቶ
አዝ
በባህራን ታሪክ በነ ጠናፊኖስ
በአፎሚያ መትረፍ በነዱረታዎስ
በነብዪ ዳንኤል የጭፍን ሰምና
የሚካኤል ስራ ይቀጥላል ገና
አዝ
በጉዞ የረዳችሁ በባህር በየብሱ
ፈጥኖ ደርሶላችሁ እንባን ስታፈሱ
ስለታችሁ ሰምሯል ቁሙ በዝማሬ
በሚካኤል ምልጃ የቆማችሁ ዛሬ
አዝ
ክብር ለሚገባዉ ክብርን እንሰጣለን
ንጉስ ለወደደዉ እንሰግድለታለን
እንኳን ለሚካኤል ለሚቆም ጌታ ፊት
ክብርን እንሰጥ የለ ለምድር ሹማምት
💟 @yeorthodoxmezmur
💖 @yeorthodoxmezmur
💘 @yeorthodoxmezmur
❤2👍2
መራራ ሕይወቴ
መራራ ሕይወቴ ጣፈጠ በማርያም
ማዘን ስደት ይቅር እስከ ዘለዓለም
ተፈውሷልና በእመቤታችን
የመሪባ ውኃ ተባረከልን
በእግዝእትነ ማርያም እንድናለን
አዝ.........
ሀገሪቱ መልካም ኑሮዋ መራራ
በስደት አለቀ ወገኔ በተራ
ሽማግሌ እንዲጦር ህፃናት እንዲያድጉ
ኤልሳዕን የሚተካ አባት ሰው ፈልጉ
ማሰሮ አምጡ ጨውም ጨምራችሁ
ሞት አንዳይነግስ በመካከላችሁ
ማረን እንበል ኤሎሄ ብለን
እንዋደድ እንዲሰምርልን
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሉሽ
ኢትዮጵያን እንባዋን አብሽ
አዝ.........
ታለቅሳለች እና እማማ ኢትዮጵያ
የወላዶች መካን አርገዋት ልጆቿ
ዓለሙም ንብረቱም ሁሉም ያልፋልና
ይበቃናል እንበል በቀና ልቦና
የህፃናት ድምፅ ተሰማ በራማ
ስለሆነች ምድሪቱ አኬልዳማ
የዘገየ ቢመስል እግዚአብሔር
ቀድሞ ይፈርዳል ሳሉ በምድር
የአቤል ደም ፀባኦት ደረሰ
ቃየልስ ወዴት ገሰገሰ
ለአዛኝቷ ሁሉ ይሆናልና
ንገሯት በጽኑ ልመና
አዝ........
አኔ የኬፋ ነኝ የአጵሎስ አትበሉ
የተለያየ መንግስት አይጸናም እንዲሉ
የኢትዮጵያ ልጆች አንድ ነን ሁላችን
ልዩነት እናጥፋ ከመካከላችን
ስንዴ መሃል እንክርዳድ አንዝራ
ተደምስሷል የዲያበሎስ ሴራ
በአስጨናቂዎች እጅ አትጣለን
ፍረድልን እናነባለን
ለልጁ አባት ይገደዋልና
አምላክ ሆይ ተመልከተን ናና
ስለማርያም ብለን ለምነን
አልፈናል ያን ክፉ ዘመን
አዝ...........
ሀገርን አይተውም ያለ አንዳች ጻድቅ
ስውሩም ይታያል አይሆንም ድብቅ
የአባቶቼ እርስት ስሟ ቶኔቶር
ገበዟ ጊዮርጊስ ነው አሥራት የድንግል
ዳሯን እሳት መሃሏን ገነት
ለእኛም ይስጠን ፍቅር አንድነት
የተሰዓቱ ቅዱሳን መሸሻ
ኖላዊ ኄር ጠባቂሽ ነው ጋሻ
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሉሽ
ኢትዮጵያን እንባዋን አብሽ
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሉሽ
ሀገሬን እንባዋን አብሽ
🙏 @yeorthodoxmezmur🙏
🙏 @yeorthodoxmezmur🙏
🙏 @yeorthodoxmezmur🙏
መራራ ሕይወቴ ጣፈጠ በማርያም
ማዘን ስደት ይቅር እስከ ዘለዓለም
ተፈውሷልና በእመቤታችን
የመሪባ ውኃ ተባረከልን
በእግዝእትነ ማርያም እንድናለን
አዝ.........
ሀገሪቱ መልካም ኑሮዋ መራራ
በስደት አለቀ ወገኔ በተራ
ሽማግሌ እንዲጦር ህፃናት እንዲያድጉ
ኤልሳዕን የሚተካ አባት ሰው ፈልጉ
ማሰሮ አምጡ ጨውም ጨምራችሁ
ሞት አንዳይነግስ በመካከላችሁ
ማረን እንበል ኤሎሄ ብለን
እንዋደድ እንዲሰምርልን
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሉሽ
ኢትዮጵያን እንባዋን አብሽ
አዝ.........
ታለቅሳለች እና እማማ ኢትዮጵያ
የወላዶች መካን አርገዋት ልጆቿ
ዓለሙም ንብረቱም ሁሉም ያልፋልና
ይበቃናል እንበል በቀና ልቦና
የህፃናት ድምፅ ተሰማ በራማ
ስለሆነች ምድሪቱ አኬልዳማ
የዘገየ ቢመስል እግዚአብሔር
ቀድሞ ይፈርዳል ሳሉ በምድር
የአቤል ደም ፀባኦት ደረሰ
ቃየልስ ወዴት ገሰገሰ
ለአዛኝቷ ሁሉ ይሆናልና
ንገሯት በጽኑ ልመና
አዝ........
አኔ የኬፋ ነኝ የአጵሎስ አትበሉ
የተለያየ መንግስት አይጸናም እንዲሉ
የኢትዮጵያ ልጆች አንድ ነን ሁላችን
ልዩነት እናጥፋ ከመካከላችን
ስንዴ መሃል እንክርዳድ አንዝራ
ተደምስሷል የዲያበሎስ ሴራ
በአስጨናቂዎች እጅ አትጣለን
ፍረድልን እናነባለን
ለልጁ አባት ይገደዋልና
አምላክ ሆይ ተመልከተን ናና
ስለማርያም ብለን ለምነን
አልፈናል ያን ክፉ ዘመን
አዝ...........
ሀገርን አይተውም ያለ አንዳች ጻድቅ
ስውሩም ይታያል አይሆንም ድብቅ
የአባቶቼ እርስት ስሟ ቶኔቶር
ገበዟ ጊዮርጊስ ነው አሥራት የድንግል
ዳሯን እሳት መሃሏን ገነት
ለእኛም ይስጠን ፍቅር አንድነት
የተሰዓቱ ቅዱሳን መሸሻ
ኖላዊ ኄር ጠባቂሽ ነው ጋሻ
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሉሽ
ኢትዮጵያን እንባዋን አብሽ
ትውልድ ሁሉ ብፅዕት የሚሉሽ
ሀገሬን እንባዋን አብሽ
🙏 @yeorthodoxmezmur🙏
🙏 @yeorthodoxmezmur🙏
🙏 @yeorthodoxmezmur🙏
👍5
#እስከዛው_ተኝቼ_ልክረም
@Mgetem
ጌታ ሆይ!
በምድር በዚች ዓለም ላይ - ጥቂት ቀናትን መክረሜ፣
አሳዝኖህ አዝነህልኝ - ከጨመርክልኝ ዕድሜ፣
የአቤሜሌክን እንጂ - የማቱሳላን አልሻም፣
ከ60 ዓመታት እንቅልፍ የ9 ምዕት ኑሮ አልመርጥም፡፡
እንደማቱሳላ ኖሬ - ከድህነት ከምታገል - መከራ ችግርን ከማይ፣
በጎዶሎዋ ምድር - ሳይሞላልኝ ከምሰቃይ፣
60 ዓመት ላንቀላፋ - ዘመነ እንቅልፍ ስጠኝ ከላይ፡፡
ለተዳከመው ገላዬ - ኑሮ ላዛለው አካሌ፣
ልትጨምርልኝ ከዳዳህ - ለዕጣ ፈንታ ለዕድሌ፣
የእንቅልፍ ዕድሜን እንጂ - ቀን አልሻም የመከራ፣
መተኛት እንጂ መቅበዝበዝ -ይቅርብኝ ጌታ አደራ፡፡
እንደ ፃድቁ አቤሜሌክ - ኢትዮጵያዊ ነኝና፣
እንደው የዘር ሆኖብኝ - መተኛት ያምረኛልና፣
እንዳልሠራ እንድጋደም፣
ጥፋቷን መድማቷን ከማይ - የሀገሬን ርሃብ ጥም፣
ሲመቻት ብቻ ቀስቅሰኝ እስከዛው ተኝቼ ልክረም፣
እንዳንቀላፋ እንዳልደክም፣
ዘመነ እንቅልፍን ስጠኝ - ዕድሜ አድለኸኝ ልጋደም፣
መቼስ ስስት አያውቅህም፡፡
©ዘሕሊና
፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨
(- አቤሜሌክ የኢየሩሳሌምን ጥፋት እንዳያይ 66 ዓመት በተዐምር
እንዲተኛ የተደረገ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ /ትንቢተ ኤርሚያስ/
- ማቱሳላ 969 ዓመታትን የኖረ፣ በዕድሜ የሰውን ዘር ኹሉ የሚበልጥ
ነው፡፡ /ኦሪት ዘፍጥረት/
- የአቤሜሌክ 66 ዓመት መተኛት 60 መባሉ፣ የማቱሳላም 969 ዓመት
ዕድሜ 9 ምዕት/9 መቶ/ መባሉ አጠጋግቶ መቁጠር የአባቶች ልማድ
በመኾኑ ነው - 318ቱን ሊቃውንት ሠለስቱ ምዕት፣ 72ቱን ሊቃናትን
ሰባው ሊቃናት እንዲል፤)
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
@Mgetem
@Mgetem
@solasc
@Mgetem
ጌታ ሆይ!
በምድር በዚች ዓለም ላይ - ጥቂት ቀናትን መክረሜ፣
አሳዝኖህ አዝነህልኝ - ከጨመርክልኝ ዕድሜ፣
የአቤሜሌክን እንጂ - የማቱሳላን አልሻም፣
ከ60 ዓመታት እንቅልፍ የ9 ምዕት ኑሮ አልመርጥም፡፡
እንደማቱሳላ ኖሬ - ከድህነት ከምታገል - መከራ ችግርን ከማይ፣
በጎዶሎዋ ምድር - ሳይሞላልኝ ከምሰቃይ፣
60 ዓመት ላንቀላፋ - ዘመነ እንቅልፍ ስጠኝ ከላይ፡፡
ለተዳከመው ገላዬ - ኑሮ ላዛለው አካሌ፣
ልትጨምርልኝ ከዳዳህ - ለዕጣ ፈንታ ለዕድሌ፣
የእንቅልፍ ዕድሜን እንጂ - ቀን አልሻም የመከራ፣
መተኛት እንጂ መቅበዝበዝ -ይቅርብኝ ጌታ አደራ፡፡
እንደ ፃድቁ አቤሜሌክ - ኢትዮጵያዊ ነኝና፣
እንደው የዘር ሆኖብኝ - መተኛት ያምረኛልና፣
እንዳልሠራ እንድጋደም፣
ጥፋቷን መድማቷን ከማይ - የሀገሬን ርሃብ ጥም፣
ሲመቻት ብቻ ቀስቅሰኝ እስከዛው ተኝቼ ልክረም፣
እንዳንቀላፋ እንዳልደክም፣
ዘመነ እንቅልፍን ስጠኝ - ዕድሜ አድለኸኝ ልጋደም፣
መቼስ ስስት አያውቅህም፡፡
©ዘሕሊና
፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨ ፨፨፨
(- አቤሜሌክ የኢየሩሳሌምን ጥፋት እንዳያይ 66 ዓመት በተዐምር
እንዲተኛ የተደረገ ኢትዮጵያዊ ነው፡፡ /ትንቢተ ኤርሚያስ/
- ማቱሳላ 969 ዓመታትን የኖረ፣ በዕድሜ የሰውን ዘር ኹሉ የሚበልጥ
ነው፡፡ /ኦሪት ዘፍጥረት/
- የአቤሜሌክ 66 ዓመት መተኛት 60 መባሉ፣ የማቱሳላም 969 ዓመት
ዕድሜ 9 ምዕት/9 መቶ/ መባሉ አጠጋግቶ መቁጠር የአባቶች ልማድ
በመኾኑ ነው - 318ቱን ሊቃውንት ሠለስቱ ምዕት፣ 72ቱን ሊቃናትን
ሰባው ሊቃናት እንዲል፤)
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
@Mgetem
@Mgetem
@solasc
👍4