18ኛው የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ተከብሮ ውሏል።
==============
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት 18ኛው የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ‘’ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ! ‘’ በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።
==============
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት 18ኛው የብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ‘’ሰንደቅ ዓላማችን ለኢትዮጵያ ታላቅ የከፍታ ዘመን ብሥራት፣ ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ሕዳሴ! ‘’ በሚል መሪ ቃል ተከብሯል።
❤7👍2
የታደሰ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ትጋት ሊገነባ እንደሚገባ ተገለፀ፡፡
======================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች "የታደሰ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና፣ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ትጋት!!! " በሚል መሪ ቃል የጋራ የምክክር መድረክ አካሄደዋል፡፡
ሰነዱን በማቅረብ መድረኩን የመሩት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ጂኦስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በማጉላት፣ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን በማጠናከር፣ ሉአላዊነቷ እና ብሔራዊ ጥቅሟ በማስከበር እና ተፅዕኖ ፈጣሪነቷን በማጎልበት የሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና የውስጥ ችግሮቻችንን ደረጃ በደረጃ በሰለጠነ መንገድ እየፈታን ሰላማችንን ማስጠበቅ ከቻልን ሀገራችን ወደ ብልፅግና ማማ ለማሸጋገር የሚያዳግተን ምንም ዓይነት ፈተናና እንቅፋት አይኖርም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር የአንድ ወገን ኃላፊነት ብቻም ሳይሆን የሁላችንም ኃላፊነት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና የታደሰ ዓለም አቀፋዊ ስትራቴጂካዊ ቁመናን ከማረጋገጥ አኳያ ከወንድም ጎረቤት ሀገራት ህዝቦች ጋር በአብሮ የማደግ መርህ በጋራ እንደምትሰራም አንስተዋል፡፡
በየዘርፉ የተቋማት ውጤታማና የማይናወጥ የተቋማት ግንባታ ሥራ የምንሠራበት፣ የልማት ትልሞቻችን ከማሳካት ጎን ለጎን እንደ አባቶቻችን በአርበኝነት ስሜት የኢትዮጵያን አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር በሀገራችንን እየተመዘገቡ ያሉ ሁለንተናዊ እድገቶችን ለማስቀጠል ሁሉም በተሰማራንበት ሥራ ላይ ውጤታማ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
======================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮችና ሰራተኞች "የታደሰ ጂኦስትራቴጂያዊ ቁመና፣ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የጋራ ትጋት!!! " በሚል መሪ ቃል የጋራ የምክክር መድረክ አካሄደዋል፡፡
ሰነዱን በማቅረብ መድረኩን የመሩት የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ባይሳ በዳዳ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቀንድ ያላትን ጂኦስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ በማጉላት፣ ዓለም አቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቷን በማጠናከር፣ ሉአላዊነቷ እና ብሔራዊ ጥቅሟ በማስከበር እና ተፅዕኖ ፈጣሪነቷን በማጎልበት የሀገራዊ ኢኮኖሚ እድገትን ማረጋገጥ እንደሚቻል አስገንዝበዋል፡፡
የኢትዮጵያን የግዛት አንድነት እና የውስጥ ችግሮቻችንን ደረጃ በደረጃ በሰለጠነ መንገድ እየፈታን ሰላማችንን ማስጠበቅ ከቻልን ሀገራችን ወደ ብልፅግና ማማ ለማሸጋገር የሚያዳግተን ምንም ዓይነት ፈተናና እንቅፋት አይኖርም ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምን ማስከበር የአንድ ወገን ኃላፊነት ብቻም ሳይሆን የሁላችንም ኃላፊነት ነው ያሉት ሚኒስትር ዴኤታው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅምና የታደሰ ዓለም አቀፋዊ ስትራቴጂካዊ ቁመናን ከማረጋገጥ አኳያ ከወንድም ጎረቤት ሀገራት ህዝቦች ጋር በአብሮ የማደግ መርህ በጋራ እንደምትሰራም አንስተዋል፡፡
በየዘርፉ የተቋማት ውጤታማና የማይናወጥ የተቋማት ግንባታ ሥራ የምንሠራበት፣ የልማት ትልሞቻችን ከማሳካት ጎን ለጎን እንደ አባቶቻችን በአርበኝነት ስሜት የኢትዮጵያን አንድነትና ብሔራዊ ጥቅም በማስከበር በሀገራችንን እየተመዘገቡ ያሉ ሁለንተናዊ እድገቶችን ለማስቀጠል ሁሉም በተሰማራንበት ሥራ ላይ ውጤታማ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ከኢትዮጵያ ጀርባ ላይ ያልወረደው የሁለንተናዊ እድገት መሰናክልና እንቅፋት የሆነው የባዕድ ጣልቃ ገብነት አባዜን ለማስወገድ ሁሉም የድርሻውን ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን ተሳታፊዎች ጠቁመዋል፡፡
በመድረኩ የብሔራዊ ጥቅም ምንነት እና ጂኦስትራቴጂክ ቁመና፣ የኢኮኖሚ ብልፅግና፣ ፖለቲካዊ አቅምና ተፅዕኖ ፈጣሪነት፣ ሉዓላዊነት፣ የግዛት አንድነትን፣ የባህር በር ጉዳይ፣ ሰላምና ጸጥታን ማረጋገጥ፣ ከፖለቲካ ሀይሎች ጋር ሰላማዊ አማራጭ መከተል፣ የባህል ነፃነት፣ የህዝቦች ማህበራዊ ልማትና ዋስትና የሚሉ ሀሳቦች ተዳሰዋል።
በመድረኩ የብሔራዊ ጥቅም ምንነት እና ጂኦስትራቴጂክ ቁመና፣ የኢኮኖሚ ብልፅግና፣ ፖለቲካዊ አቅምና ተፅዕኖ ፈጣሪነት፣ ሉዓላዊነት፣ የግዛት አንድነትን፣ የባህር በር ጉዳይ፣ ሰላምና ጸጥታን ማረጋገጥ፣ ከፖለቲካ ሀይሎች ጋር ሰላማዊ አማራጭ መከተል፣ የባህል ነፃነት፣ የህዝቦች ማህበራዊ ልማትና ዋስትና የሚሉ ሀሳቦች ተዳሰዋል።
የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ግንዛቤ ለተቋም ዓላማ ስኬት መረጋገጥ ሚናው የላቀ እንደሆነ ተገለፀ።
==================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር ለመካከለኛ አመራሮች የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር የኦዲት ስራ አስፈፃሚ አቶ አሻግሬ አለሙ የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የጠራ ግንዛቤ መፍጠር ለተቋማዊ ውጤታማነት ያለውን ሚና አስረድተዋል።
ተቋማት ሳያውቁ ከሚሰሯቸው የኦዲት ግኝቶች ለመታደግ በዘርፉ ላይ ያሉ መመሪያና ደንቦች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ለሁለም የሚበጅ መሆኑን ገልፀዋል።
ኦዲት የሀገራዊ ኢኮኖሚ ውጤታማነትን የሚጨምር ነው ያሉት ስራ አስፈፃሚው ተቋማት በዘርፉ ላይ የግንዛቤ አቅምን በመፍጠር የሀገራዊ ብሎም የተቋሙን የአሰራር ስርዓት በማሳለጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ምቹ ስነምህዳር ይፈጥራል ብለዋል።
የኦዲት ስራ ጫናን ለመቀነስ እየተተገበረ ያለው የዲጂታል አገልግሎት ከሚያመጣው ታምራዊ ለውጥ ባሻገር የኦዲት ህግና ደንብ ዙሪያ የተቋም የሰው ሀይል ልማት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በቀጣይ የፋይናሻል ኦዲት የማይሸፍናቸውን ስራዎች በግብ ተኮር የሆነው የክዋኔ ኦዲትን ተግባራዊ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
በመድረኩ ሁሉም ሰራተኛ የመንግስትን ያሰራር ስርዓቶችን ጠንቅቆ በማወቅ የተመደበበትን ስራ በውጤታማነት ለማከናወን የሚያግዘውን የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ዕውቀት የሚያገኝበትን ዕድል በየጊዜው መፈጠር እንዳለበት ተሳታፊዎች አንስተዋል።
==================
የኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር ለመካከለኛ አመራሮች የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል።
በኢኖቬሽንና ቴክኖሊጂ ሚኒስቴር የኦዲት ስራ አስፈፃሚ አቶ አሻግሬ አለሙ የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ላይ የጠራ ግንዛቤ መፍጠር ለተቋማዊ ውጤታማነት ያለውን ሚና አስረድተዋል።
ተቋማት ሳያውቁ ከሚሰሯቸው የኦዲት ግኝቶች ለመታደግ በዘርፉ ላይ ያሉ መመሪያና ደንቦች ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠቱ ለሁለም የሚበጅ መሆኑን ገልፀዋል።
ኦዲት የሀገራዊ ኢኮኖሚ ውጤታማነትን የሚጨምር ነው ያሉት ስራ አስፈፃሚው ተቋማት በዘርፉ ላይ የግንዛቤ አቅምን በመፍጠር የሀገራዊ ብሎም የተቋሙን የአሰራር ስርዓት በማሳለጥ የሚፈለገውን ውጤት ለማስመዝገብ ምቹ ስነምህዳር ይፈጥራል ብለዋል።
የኦዲት ስራ ጫናን ለመቀነስ እየተተገበረ ያለው የዲጂታል አገልግሎት ከሚያመጣው ታምራዊ ለውጥ ባሻገር የኦዲት ህግና ደንብ ዙሪያ የተቋም የሰው ሀይል ልማት ላይ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በቀጣይ የፋይናሻል ኦዲት የማይሸፍናቸውን ስራዎች በግብ ተኮር የሆነው የክዋኔ ኦዲትን ተግባራዊ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።
በመድረኩ ሁሉም ሰራተኛ የመንግስትን ያሰራር ስርዓቶችን ጠንቅቆ በማወቅ የተመደበበትን ስራ በውጤታማነት ለማከናወን የሚያግዘውን የፋይናንስና የክዋኔ ኦዲት ዕውቀት የሚያገኝበትን ዕድል በየጊዜው መፈጠር እንዳለበት ተሳታፊዎች አንስተዋል።
👍3❤1