የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትርና ተጠሪ ተቋማት በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ያሳደሷቸዉን አቅመ ደካማ ቤቶችን አስረከቡ
ግሜ 5/2014 ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካዛንቺስ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ያሳደሷቸዉን የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታዉን በማጠናቀቅና ቁሳቁስ በማሟላት ያስረከበ ሲሆን የበአል መዋያ በግ በስጠታ አበርክቷል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት የክረምት በጎ ፈቃድ በጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ተጀምረዉ ወደ ስራ ከተቀየሩ ትልልቅ ሃሳቦችን አንዱ ነዉ፡፡ “ሀሳቡን ወደ መሬት አዉርደን በዚህ መንገድ ማገዛችን ከተባበርን ምን መስራት እንደምንችል ትምህርት ያገኘንበትና ሌሎች ትልልቅ ሃገራዊ የሆኑ ጉዳዮችን በትብብር መስራት እንደሚቻል ያሳየንበት ተግባር ነዉ” ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡
ለሚኒስቴር መ/ቤቱ 45 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችም በተመሳሳይ መልኩ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራ እያከናወኑ ነዉ ያሉት ሚኒስትሩ በቀጣይም ሌሎችን ተግባራትም አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት ለሰሩ፣ ለመሩና ለተባበሩ ሰዎችም በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸዉ “ከተባባርንና ጥቂት ነገር ካዋጣን የተሻለ ሃገር መፍጠር እንደምንችል ማሳያ ነዉ፡፡ ካለን ትንሽ ነገር ላይ ቀንሰን ለተወሰኑት መድረስ እንችላለን፡፡ ይህንንም በየአመቱ እየሰራን ከሄድን ዜጎችን የተሻለ ኑሮ ደረጃ እንዲደርሱና የተሻለ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንችላለን” ብለዋል፡፡
እኛ ኢትዮጵያዊያን በፍቅር ከተጋገዝን አሁን ያለብንን ችግር አይደለም ሌሎችን መጋፈጥና መሻገር እንደምንችል ያሳየ ነዉ ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታዉ፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል ረዲ በበኩላቸዉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሰራዉ ስራ የአቅመ ደካሞችን ቤት አፍርሶ ከብርድና ዝናብ መከላከል ከእገዛዉ ሁሉ ትልቅ እገዛ ነዉ ፡፡ይህም በአዲስ አመት መልካምነትን ያሳየንበት በጋራ የተባበርንበት ነዉ ብለዋል፡፡
የቤት እድሳት የተደረገላቸዉ ወ/ሮ እየሩሳሌም ወንድሙና ወ/ሮ አባይነሽ አለሙ ከዛሬ ነገ ፈረሰብን እያልን እንፈራና እንጨነቅ ነበር ፡፡ ፈጣሪ ይመስገን ይህን የመሰለ ቤት ስለተሰራልንና ሙሉ የቤት ቁሳቁስና እንዲሁም የበአል መዋያ ስለተሰጠን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሮች፣ የተጠሪ ተቋማት ሃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማዉና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡
ግሜ 5/2014 ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርና ተጠሪ ተቋማት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 ካዛንቺስ በክረምት በጎ ፈቃድ መርሃ ግብር ያሳደሷቸዉን የሁለት አቅመ ደካማ ቤቶችን ግንባታዉን በማጠናቀቅና ቁሳቁስ በማሟላት ያስረከበ ሲሆን የበአል መዋያ በግ በስጠታ አበርክቷል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዶ/ር ሳሙኤል ኡርቃቶ በርክክብ ስነስርዓቱ ላይ እንደተናገሩት የክረምት በጎ ፈቃድ በጠቅላይ ሚኒስቴር አቢይ አህመድ ተጀምረዉ ወደ ስራ ከተቀየሩ ትልልቅ ሃሳቦችን አንዱ ነዉ፡፡ “ሀሳቡን ወደ መሬት አዉርደን በዚህ መንገድ ማገዛችን ከተባበርን ምን መስራት እንደምንችል ትምህርት ያገኘንበትና ሌሎች ትልልቅ ሃገራዊ የሆኑ ጉዳዮችን በትብብር መስራት እንደሚቻል ያሳየንበት ተግባር ነዉ” ብለዋል ሚኒስትሩ፡፡
ለሚኒስቴር መ/ቤቱ 45 የመንግስት ዩኒቨርስቲዎችም በተመሳሳይ መልኩ የክረምት በጎ ፈቃድ ስራ እያከናወኑ ነዉ ያሉት ሚኒስትሩ በቀጣይም ሌሎችን ተግባራትም አጠናክረን እንቀጥላለን በማለት ለሰሩ፣ ለመሩና ለተባበሩ ሰዎችም በተቋሙ ስም ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸዉ “ከተባባርንና ጥቂት ነገር ካዋጣን የተሻለ ሃገር መፍጠር እንደምንችል ማሳያ ነዉ፡፡ ካለን ትንሽ ነገር ላይ ቀንሰን ለተወሰኑት መድረስ እንችላለን፡፡ ይህንንም በየአመቱ እየሰራን ከሄድን ዜጎችን የተሻለ ኑሮ ደረጃ እንዲደርሱና የተሻለ ኑሮ መምራት እንዲችሉ ማድረግ እንችላለን” ብለዋል፡፡
እኛ ኢትዮጵያዊያን በፍቅር ከተጋገዝን አሁን ያለብንን ችግር አይደለም ሌሎችን መጋፈጥና መሻገር እንደምንችል ያሳየ ነዉ ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታዉ፡፡
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስራ አስፈጻሚ አቶ ጀማል ረዲ በበኩላቸዉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሰራዉ ስራ የአቅመ ደካሞችን ቤት አፍርሶ ከብርድና ዝናብ መከላከል ከእገዛዉ ሁሉ ትልቅ እገዛ ነዉ ፡፡ይህም በአዲስ አመት መልካምነትን ያሳየንበት በጋራ የተባበርንበት ነዉ ብለዋል፡፡
የቤት እድሳት የተደረገላቸዉ ወ/ሮ እየሩሳሌም ወንድሙና ወ/ሮ አባይነሽ አለሙ ከዛሬ ነገ ፈረሰብን እያልን እንፈራና እንጨነቅ ነበር ፡፡ ፈጣሪ ይመስገን ይህን የመሰለ ቤት ስለተሰራልንና ሙሉ የቤት ቁሳቁስና እንዲሁም የበአል መዋያ ስለተሰጠን ደስ ብሎናል እናመሰግናለን ብለዋል፡፡
በርክክብ ስነ ስርአቱ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትሮች፣ የተጠሪ ተቋማት ሃላፊዎች፣ የክፍለ ከተማዉና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢዉ ነዋሪዎች ተገኝተዋል፡፡