ምርምሮች የምርምር የስነ ምግባር የተከተሉ እንዲሆኑ ለማስቻል እየተሰራ ነው
========================
(መስከረም 13/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከሐሮማያ ዪኒቨርስቲና ከአውሮፓና ታዳጊ ሃገራት የክሊኒካል ሙከራዎች ትብብር (EDCTP) ጋር በመተባበር የምርምር ስነምግባር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሐረማያ ዩኒቨርስቲ እየሰጠ ይገኛል፡፡
ፕ/ር አፈወርቅ ካሱ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ በበየነመረብ ባደረጉት መክፈቻ እንደተናገሩት ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ለምርምር ልዩ ትኩረት በመስጠት ፖሊሲና ስትራቴጂዎች አዘጋጅቶ እየሰራ ሲሆን እነዚህ ፖሊሲዎችና ስትራቴጅዎች ተጠቅመው የሃገራችንን የትምህርትና ስልጠና ምርምር ተቋማት ምርምሮች እያካሄዱ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
ይህ በምርምር ስነምግባር ዙሪያ የሚሰጠዉ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ዋና አላማ በሃገራችን ያሉንን የምርምር ስራዎች ያሉ እድሎችን ለማጠናከር እንዲሁም ተግዳሮቶች ተብለዉ የተለዩትን የተመራማሪ እጥረት ለማሳደግ፣ ወጣት ተመራመሪዎችን ለማበረታታት፣ የምርምር አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት፣ ትብብርና ትስስርን በተቋማትና ምርምር ማእከላት ለመፍጠር፣ ዘላቂነት፣ ጥራትና አግባብነት፣ የመሰረተ ልማትና በጀት ችግር ለመሻገር እንዲሁም የተሰሩ ምርምሮችን በአግብቡ እንዲሰራጩ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሳይንስና ምርምር ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር በበኩላቸዉ የምንሰራቸዉ ምርምሮች ስራዎች የምርምር ስነምግባርን መርህ የተከተሉ እና የምናሳትማቸው ጆርናሎች በትክክለኛ ዌብ ሳይት መሆኑን ማረጋገጥ አለብን ብለዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን አክለውም በሀገራችን በርካታ የምርምር ስነ ምግባር ችግሮች መኖራቸውን ገልጸው ይህም ከግለሰብ ጀምሮ ዩኒቨርስቲውን ፣ ፈንድ አድራጊውን ፣ ሃብትን፣ ጊዜና ገንዘብ በማባከን ሃገር ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራል ብለዋል፡፡
ይህንን ለመከላከል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጥራቱን የጠበቀ የምርምር ስራዎችና ጆርናሎች እንዲሰሩ የተለያዩ ህጎችና ሪፎርሞች አውጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ስልጠናዉ በሃገር ደረጃ ለ5ኛ ግዜ በሓሮማያ ዩኒቨርስቲ ለመጀመሪያ ግዜ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የምርምር ስነምግባር ዳይሬክተር ዶ/ር ዳኒኤል ታደሰ ናቸው።
በስልጠናው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጀኔራል ዳይሬክተሮች፣ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች፣ የሃሮማያ ክላስተር የሚገኙ የመንግስት ዪኒቨርስቲዎች (ድሬዳዋ ፣ ሐሮማያ ፣ ቀ/ዳሃር ሰመራ ፣ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሰቲዎች)፣ ከግል ዩኒቨርስቲዎች ዩኒቲ፣ አድማስ፣ ሃራምቤና ሪፍት ቫሊ ዩንቨርስቲዎች፣ የሃረሪ፣የድሬዳዋ ፣ የአፋር እና የሶማሊ የግብርና፣ አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር የምርምር ማእከሎች፣ ጤና ቢሮ፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡
========================
(መስከረም 13/2014ዓ.ም) የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከሐሮማያ ዪኒቨርስቲና ከአውሮፓና ታዳጊ ሃገራት የክሊኒካል ሙከራዎች ትብብር (EDCTP) ጋር በመተባበር የምርምር ስነምግባር የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና በሐረማያ ዩኒቨርስቲ እየሰጠ ይገኛል፡፡
ፕ/ር አፈወርቅ ካሱ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ዴኤታ በበየነመረብ ባደረጉት መክፈቻ እንደተናገሩት ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ለምርምር ልዩ ትኩረት በመስጠት ፖሊሲና ስትራቴጂዎች አዘጋጅቶ እየሰራ ሲሆን እነዚህ ፖሊሲዎችና ስትራቴጅዎች ተጠቅመው የሃገራችንን የትምህርትና ስልጠና ምርምር ተቋማት ምርምሮች እያካሄዱ ይገኛሉ ብለዋል፡፡
ይህ በምርምር ስነምግባር ዙሪያ የሚሰጠዉ የአቅም ማጎልበቻ ስልጠና ዋና አላማ በሃገራችን ያሉንን የምርምር ስራዎች ያሉ እድሎችን ለማጠናከር እንዲሁም ተግዳሮቶች ተብለዉ የተለዩትን የተመራማሪ እጥረት ለማሳደግ፣ ወጣት ተመራመሪዎችን ለማበረታታት፣ የምርምር አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት፣ ትብብርና ትስስርን በተቋማትና ምርምር ማእከላት ለመፍጠር፣ ዘላቂነት፣ ጥራትና አግባብነት፣ የመሰረተ ልማትና በጀት ችግር ለመሻገር እንዲሁም የተሰሩ ምርምሮችን በአግብቡ እንዲሰራጩ ለማድረግ ነው ብለዋል፡፡
የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሳይንስና ምርምር ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀኔራል ዶ/ር ሰለሞን ቢኖር በበኩላቸዉ የምንሰራቸዉ ምርምሮች ስራዎች የምርምር ስነምግባርን መርህ የተከተሉ እና የምናሳትማቸው ጆርናሎች በትክክለኛ ዌብ ሳይት መሆኑን ማረጋገጥ አለብን ብለዋል፡፡
ዶ/ር ሰለሞን አክለውም በሀገራችን በርካታ የምርምር ስነ ምግባር ችግሮች መኖራቸውን ገልጸው ይህም ከግለሰብ ጀምሮ ዩኒቨርስቲውን ፣ ፈንድ አድራጊውን ፣ ሃብትን፣ ጊዜና ገንዘብ በማባከን ሃገር ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራል ብለዋል፡፡
ይህንን ለመከላከል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ጥራቱን የጠበቀ የምርምር ስራዎችና ጆርናሎች እንዲሰሩ የተለያዩ ህጎችና ሪፎርሞች አውጥቶ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
ስልጠናዉ በሃገር ደረጃ ለ5ኛ ግዜ በሓሮማያ ዩኒቨርስቲ ለመጀመሪያ ግዜ እየተሰጠ መሆኑን የገለጹት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የምርምር ስነምግባር ዳይሬክተር ዶ/ር ዳኒኤል ታደሰ ናቸው።
በስልጠናው የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጀኔራል ዳይሬክተሮች፣ ዳይሬክተሮችና ባለሙያዎች፣ የሃሮማያ ክላስተር የሚገኙ የመንግስት ዪኒቨርስቲዎች (ድሬዳዋ ፣ ሐሮማያ ፣ ቀ/ዳሃር ሰመራ ፣ ኦዳ ቡልቱም ዩኒቨርሰቲዎች)፣ ከግል ዩኒቨርስቲዎች ዩኒቲ፣ አድማስ፣ ሃራምቤና ሪፍት ቫሊ ዩንቨርስቲዎች፣ የሃረሪ፣የድሬዳዋ ፣ የአፋር እና የሶማሊ የግብርና፣ አርብቶ አደርና ከፊል አርብቶ አደር የምርምር ማእከሎች፣ ጤና ቢሮ፣ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ተመራማሪዎችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ ይገኛል፡፡