Telegram Web Link
💥 ጌታችን ጌትነቱን ገልጦበታል። የአብ ድምፅ ተሰምቶበታልና ታቦር ተራራ ቅዱስ ነው። ቅዱስ ጴጥሮስም በመልእክቱ "ከገናናው ክብር፦ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይኽ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ከእግዚአብሔር አብ ክብርንና ምስጋናን ተቀብሎአልና፤ እኛም በቅዱሱ ተራራ ከእርሱ ጋር ሳለን ይኽን ድምፅ ከሰማይ ሲወርድ ሰማን።" በማለት ገልጦታል (2ኛ ጴጥ 1:17-18)

❖ ሌላው ሙሉሙሉ ዳቦ መጋገሩ በትውፊት እንደምንረዳው ጌታ ብርሃኑን ሲገልጽ ብርሃኑ እስከ አርሞንኤም ተራራ ድረስ ያበራ ስለነበር እረኞች ሌሊቱ ኹሉ ቀን መስሏቸው እዛው ስለዋሉ ቤተሰቦቻቸው “ኅብስት” ይዘውላቸው ኼደዋልና የዚያ ምሳሌ እንደኾነ በአበው ትውፊት ይነገራል፡፡

💥[በደብረ ታቦር ላይ ብርሃኑን የገለጠው አምላካችን ክርስቶስ ምስጋና ይግባው]፡፡
[መልካም በዓል]
መጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ (በድጋሚ የተለጠፈ)
98👍18🥰3
"ሰላም ለዕርገተ ሥጋኪ"
👉 ኀሙስ ነሐሴ 16 ጠዋት በምሥራቀ ፀሐይ ቀበና መድኀኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን አይቀርም።
💥 የአምላክን እናት የዕርገቷን በዓል በበዓለ ንግሥና 8ኛው የአመቤታችንን ጉባኤ በታላቅ ድምቀት የምናስብ ሲኾን፦
በዕለቱም፦ 
💥 ሥርዐተ ቅዳሴ
💥 ጠዋት 3 ሰዓት ታቦተ ኪዳነ ምሕረት እጅግ በታላቅ ድምቀት ታጅባ ትወጣለች።
💥 የገነት አበባ የተባለች የአምላክ እናት ዕርገቷን በማሰብ የከበረ ሥዕሏ በካህናት በዲያቆናት ታጅቦ በ10,000 አበባዎች፤ መለከት እየተነፋ ነጋሪት እየተጎሰመ በታላቅ ድምቀት ይወጣል።
💥 ሊቃውንት ያሬዳዊ ዝማሬን ያሰማሉ።
💥 ብዙ ሕሙማን የተፈወሱበት በግብጽ ፓርት ሳይድ የእመቤታችን ቤተ ክርስቲያን ካለችው ከቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ላይ የሚፈሰው ፈዋሽ ወዝ ለመጡት ኹሉ በነጻ ይሰጣል። "ሰላም ለሥዕልኪ ሐፈ ማሕየዌ በጼዴንያ ወግብጽ ዘአውሐዘት በኢሕሳዌ" (በጼዴንያና በግብጽ ፈዋሽ ወዝን ያፈሰሰች ሥዕልሽ ሰላምታ ይገባል) (መልክአ ሥዕል)
💥  በመኾኑም በዚኽ ታላቅ በዓል የአምላክ እናት ልትባርኮት ጠርታዎታለችና በጠዋቱ እንዳይቀሩ።
👉 የቤተ ክርስቲያኑ አድራሻ ከ4 ኪሎ ወደ ቀበና አደባባይ ሲመጡ ማደያው ጋር ከመድረሶት በፊት።
91👍33👎1
37 አልፋ 73 የመጽሐፍ ምረቃ በሜክሲኮ ገነት ሆቴል አዳራሽ

የመጋቤ ሐዲስ ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ 28ኛ መጽሐፍ ይመረቃል

👉 እሑድ ጳጉሜን 3 ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ

👉 ተመራማሪዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦች፣ የኪነ ጥበብ ሰዎችና ክቡራን እንግዶች ይታደሙበታል።

👉 በዚኽ ድንቅ የጥበብ መርሐ ግብር አይቀርም

👉 የመጽሐፉ ዳሰሳ
በዶክተር ጌትነት ፈለቀ (አስትሮፊዚዚስት)
በዶክተር ሔኖክ ሙሉጌታ (የሳይበር ሳይንቲስት)
23👍14🔥1
2025/07/08 19:32:38
Back to Top
HTML Embed Code: