" የጸጥታ ችግር አለባቸው የሚባሉ የአማራ ፣የኦሮሚያ እና የትግራይ ክልል አካባቢዎች ላይ ከችግሩ በፊት የተተከሉ የኔትወርክ ማማዎች ላይ አንዲት እቃ አልተነካብንም "- ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ፍቃዱን በተረከበ በአራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ በአገሪቱ ዙሪያ ያሉት የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቹ ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱን ይፋ አድርጓል።
የግል የቴሌኮም አቅራቡ ድርጅት የሆነው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት የአራተኛ ትውልድ ኔትወርክ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ ከግማሽ በላይ ለሚሆነው ተደራሽ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን ለዚህም ከመቶ ሃምሳ በላይ በሆኑ ከተሞች 3,141 የኔትወርከ ማማዎችን መገንባቱን ገልጿል።
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቺፍ ኤክስተርናል አፌርስ ኦፊሰር አቶ አንዷለም አድማስ "ሳፋሪኮም የመጠንከር የመወዳደር እና ቀና ብሎ የመጓዝ ሂደት ላይ" ነው ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
አቶ አንዷለም አድማስ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብም ምን አሉ ?
" 10 ሚሊየን ንቁ(Active) ደንበኞች ማለት ባለፉት ዘጠና ቀናት ውስጥ የደወለ ወይም መልእክት የተቀበለ ማለት ነው።
ባለፉት 90 ቀናት ካልደወለ ወይም ካርድ ካልሞላ ከእኛ ዳታ ቤዝ ውስጥ ይወጣል ከደወለ ወይም ካርድ ከሞላ ወደ ዳታ ቤዛችን ይገባል ስለዚህ 10 ሚሊየን ንቁ ደንበኛ ስንል ገንዘብ የምናገኝበት ትክክለኛ ደንበኛችን ማለት ነው።
3141 ታወሮች በጣራ ላይ እና ግሪን ፊልድ ላይ አሉን የተወሰኑ ሳይቶችን ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ ነው የምንጠቀመው ለዚህም ኢትዮ ቴሌኮም ጥሩ ገቢ ያገኛል።
ዋና ዋና የሚባሉ ከተሞች አዳርሰናል ከዚህ በኋላ ወደ ሌሎች ከተሞችም እንዳረሳለን ለዚህም ከ 1.5 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ኢንቨስት እናደርጋለን።
በአሁኑ ሰአት ከኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የ Fiber መቆረጥ አለ እሱ መፍትሄ በሚሰጥ መልኩ እየተሰራ ነው።
በመላ ሃጋሪቱ ነው የምንንቀሳቀሰው እቃዎች ተጭነው ነው የሚሄዱት በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ እንደማንኛውም ሰው እክል ሊገጥመን ይችላል ነገር ግን የተጋነነ ነገር አለ ብዬ አላስብም።
የጸጥታ ችግር አለባቸው የሚባሉ የአማራ ፣የኦሮሚያ እና የትግራይ ክልል አካባቢዎች ላይ ከችግሩ በፊት የተተከሉ የኔትወርክ ማማዎች ላይ አንዲት እቃ አልተነካብንም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ የአገልግሎት ፍቃዱን በተረከበ በአራት ዓመታት ጊዜ ውስጥ በአገሪቱ ዙሪያ ያሉት የ90 ቀናት ንቁ ደንበኞቹ ቁጥር 10 ሚሊዮን መድረሱን ይፋ አድርጓል።
የግል የቴሌኮም አቅራቡ ድርጅት የሆነው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት የአራተኛ ትውልድ ኔትወርክ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ውስጥ ከግማሽ በላይ ለሚሆነው ተደራሽ ማድረጉን የገለጸ ሲሆን ለዚህም ከመቶ ሃምሳ በላይ በሆኑ ከተሞች 3,141 የኔትወርከ ማማዎችን መገንባቱን ገልጿል።
የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቺፍ ኤክስተርናል አፌርስ ኦፊሰር አቶ አንዷለም አድማስ "ሳፋሪኮም የመጠንከር የመወዳደር እና ቀና ብሎ የመጓዝ ሂደት ላይ" ነው ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
አቶ አንዷለም አድማስ በዝርዝር በሰጡት ሃሳብም ምን አሉ ?
" 10 ሚሊየን ንቁ(Active) ደንበኞች ማለት ባለፉት ዘጠና ቀናት ውስጥ የደወለ ወይም መልእክት የተቀበለ ማለት ነው።
ባለፉት 90 ቀናት ካልደወለ ወይም ካርድ ካልሞላ ከእኛ ዳታ ቤዝ ውስጥ ይወጣል ከደወለ ወይም ካርድ ከሞላ ወደ ዳታ ቤዛችን ይገባል ስለዚህ 10 ሚሊየን ንቁ ደንበኛ ስንል ገንዘብ የምናገኝበት ትክክለኛ ደንበኛችን ማለት ነው።
3141 ታወሮች በጣራ ላይ እና ግሪን ፊልድ ላይ አሉን የተወሰኑ ሳይቶችን ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በጋራ ነው የምንጠቀመው ለዚህም ኢትዮ ቴሌኮም ጥሩ ገቢ ያገኛል።
ዋና ዋና የሚባሉ ከተሞች አዳርሰናል ከዚህ በኋላ ወደ ሌሎች ከተሞችም እንዳረሳለን ለዚህም ከ 1.5 ቢሊየን ዶላር በላይ ተጨማሪ ኢንቨስት እናደርጋለን።
በአሁኑ ሰአት ከኮሪደር ልማት ጋር በተገናኘ የ Fiber መቆረጥ አለ እሱ መፍትሄ በሚሰጥ መልኩ እየተሰራ ነው።
በመላ ሃጋሪቱ ነው የምንንቀሳቀሰው እቃዎች ተጭነው ነው የሚሄዱት በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ እንደማንኛውም ሰው እክል ሊገጥመን ይችላል ነገር ግን የተጋነነ ነገር አለ ብዬ አላስብም።
የጸጥታ ችግር አለባቸው የሚባሉ የአማራ ፣የኦሮሚያ እና የትግራይ ክልል አካባቢዎች ላይ ከችግሩ በፊት የተተከሉ የኔትወርክ ማማዎች ላይ አንዲት እቃ አልተነካብንም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
❤1.39K👏207😡41🙏32🥰19🕊15🤔11😱11😭11😢9💔3
TIKVAH-ETHIOPIA
“ የተገደሉት አባት ለ12 ዓመት በብትውና የኖሩ ነበሩ። ቀብራቸው ተፈጽሟል። ጥቃት በተከፈተበት ዋሻ አካባቢ የነበሩ ሰባት አባቶችን ወደ ገዳሙ አምጥተናል ” - ደብረ ከዋክብት ዝቋላ ገዳም በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ሸዋ ዞን ባለው ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ገዳም “የሸኔ ታጣቃዎች” ባህታውያን አባቶች በሚኖሩባቸው ዋሻዎች ተኩስ መክፈታቸውን ገዳሙ ማሳወቁ ይታወሳል። ይህን ተከትሎም፤…
" የግፍ አገዳደል ነው የተፈጸመው ፤ የሟቹን ወንድም ቤትም ታጣቂዎቹ አቃጥለውታል ፤ የአካባቢው ነዋሪም ወደ አጎራባች ቦታዎች ተፈናቅሏል " - የሟች የቅርብ ሰው
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የሰባት ልጆች አባት ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ በ "ሸኔ" በታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ግድያው አሰቃቂ መሆኑን፣ ሟች ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ከቤታቸው በታጣቂዎች እንደተገደሉ፣ ባለቤታቸውም በተመሳሳይ ከተገደሉ አመት ከስድስት ወራት እንዳስቆጠሩ፣ የ11 ዓመት ልጃቸውም በጥይት ተመትቶ ካህኑ በጥልቅ ሀዘን አንደነበሩ ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
አንድ የካህኑ የቅርብ ሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲናገሩ፣ " ካህኑን እጅግ በጣም አሰቃቂ በሆነ መንገድ ነው የገደሏቸው " ሲሉ በተሰበረ ልብ ገልጸዋል።
" አካላቸውን አፍሰን ነው ይዘን የመጣነው፤ ሰዎች በቄየው ሄደው ለቃቅመው ግማሽ አስከሬናቸው ግማሽ አካላቸው በሮቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እሁድ አርፏል፤ ግማሹን ደግሞ ትላንት ለቃቅመው ነው የቀበሩት። ለመናገርም ይዘገንናል " ሲሉም አክለዋል።
" ካህኑን ' እባካችሁ ቦታውን ለቃችሁ ወደ ከተማው ኑ ብንላቸውም ' ቤተክርስቲያኑን ለቅቄ አልሄድም የሆነው ይሁን ' ብለው ሳይመጡ ቀሩ " ብለው፣ " ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ/ም ቤተ ክርስቲያን ውለው ማታ ሲገቡ ጠላት ቀድሞ ቤታቸውን ምሽግ አድርጎ ጠብቆ ከምሽቱ 1 ሰዓት ገደማ ገደላቸው " ሲሉም ተናግረዋል።
" የሟች ወንድም ደውሎ መከላከያ እንዲደርስ አደረገ፣ ካህኑ ግን ተገድለው ተገኙ፣ የግፍ አገዳደል ነው " ያሉት እኝሁ አካል፣ የሟቹን ወንድም ቤትም ታጣቂዎቹ እንዳቃጠሉት፣ የአካባቢው ነዋሪም ወደ አጎራባች ቦታዎች መፈናቀሉን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል እናት ፓርቲ በሰሞነኛው የአማራ ክልል መቃ የተፈጸመው ግድያ እና በኦሮሚያ አርሲ ስለተፈፀመው ግድያ መግለጫ አውጥቷል።
" ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በምዕራብ ጎንደር ዞን ልዩ መቃ በታጣቂዎች እና በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች መካከል በተነሳ ግጭት መንገደኛና የእርዳታ ግብአት የጫኑ ተሽከርካሪዎች ላይ በደረሰ ድንገተኛ ተኩስ በርካታ ሹፌሮችና የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ከአካባቢው ምንጮች አረጋግጠናል " ያለው ፓርቲው " በአጠቃላይ በጥቃቱ አንድ መቶ በላይ ሰዎች እንደተገደሉና ከነዚህም ውስጥ አሥራ ስድስት የሚሆኑት ሾፌሮች መኾናቸውን ሰምተናል " ብሏል።
" ሁኔታው ከአእምሮ በላይ ነው፤ ሟቹ ከመብዛቱ የተነሳ አስከሬን በኤክስካቫተር ጭምር ሲነሳ ተመልክተናል ይላሉ እማኞች " ሲል ገልጿል።
" በሌላ በኩል ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑ ካህን ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ከምሽቱ 1፡30 አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላውቸውን ከአካባቢው ምንጮች ማረጋገጥ ችለናል " ብሏል።
" ያለፉትን 7 ዓመታት ኢትዮጵያ የንጹሃን ደም ጎርፍ ሆናለች ቢባል ከእውነይ የራቀ አይደለም " ያለው ፓርቲው " በተለይ የሃይማኖት አባቶችና ሾፌሮች ግድያ የቀን ተቀን ዜና ነው " ሲል ገልጿል።
" ሞቱንም ከማለባበስ በዘለለ ከእቁብም የሚቆጥረው የለም። የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዓይነት ተቋማት እንኳን በየቀኑ የሚፈሰውን የካህናትና ቤተሰባቸውን ደም ጽዋው ሞልቶ ሲፈስ ድምጽ አያሰሙም " ሲል ወቅሷል።
" ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብም የየቀኑ መረጃ ጠረጴዛው ላይ ደርሶት እያየ እንዳላየ ሆኗል። ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ይሄ ጉዳያቸው አይደለም " ሲል ገልጿል።
" ከተወሰኑ የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች በስተቀር አጠቃላይ ሚዲያው በፍርኃት ተሸብቦ እማኝ አናግሮ ማቅረብ ዳገት ሆኖበታል፡፡ የንጹሓን ደም ግን አሁንም በየቀኑ ይጣራል" ብሏል።
ፓርቲው " ጭፍጨፋውን በጽኑ እናወግዛለን ለሞቱት እረፍተ ነፍስን፣ ለሟች ቤተሰቦችና ለየአካባቢዎቹ ማኅበረሰብ ደግሞ መጽናናትን እንመኛለን " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የሰባት ልጆች አባት ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ በ "ሸኔ" በታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ግድያው አሰቃቂ መሆኑን፣ ሟች ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ከቤታቸው በታጣቂዎች እንደተገደሉ፣ ባለቤታቸውም በተመሳሳይ ከተገደሉ አመት ከስድስት ወራት እንዳስቆጠሩ፣ የ11 ዓመት ልጃቸውም በጥይት ተመትቶ ካህኑ በጥልቅ ሀዘን አንደነበሩ ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
አንድ የካህኑ የቅርብ ሰው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲናገሩ፣ " ካህኑን እጅግ በጣም አሰቃቂ በሆነ መንገድ ነው የገደሏቸው " ሲሉ በተሰበረ ልብ ገልጸዋል።
" አካላቸውን አፍሰን ነው ይዘን የመጣነው፤ ሰዎች በቄየው ሄደው ለቃቅመው ግማሽ አስከሬናቸው ግማሽ አካላቸው በሮቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እሁድ አርፏል፤ ግማሹን ደግሞ ትላንት ለቃቅመው ነው የቀበሩት። ለመናገርም ይዘገንናል " ሲሉም አክለዋል።
" ካህኑን ' እባካችሁ ቦታውን ለቃችሁ ወደ ከተማው ኑ ብንላቸውም ' ቤተክርስቲያኑን ለቅቄ አልሄድም የሆነው ይሁን ' ብለው ሳይመጡ ቀሩ " ብለው፣ " ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ/ም ቤተ ክርስቲያን ውለው ማታ ሲገቡ ጠላት ቀድሞ ቤታቸውን ምሽግ አድርጎ ጠብቆ ከምሽቱ 1 ሰዓት ገደማ ገደላቸው " ሲሉም ተናግረዋል።
" የሟች ወንድም ደውሎ መከላከያ እንዲደርስ አደረገ፣ ካህኑ ግን ተገድለው ተገኙ፣ የግፍ አገዳደል ነው " ያሉት እኝሁ አካል፣ የሟቹን ወንድም ቤትም ታጣቂዎቹ እንዳቃጠሉት፣ የአካባቢው ነዋሪም ወደ አጎራባች ቦታዎች መፈናቀሉን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።
በሌላ በኩል እናት ፓርቲ በሰሞነኛው የአማራ ክልል መቃ የተፈጸመው ግድያ እና በኦሮሚያ አርሲ ስለተፈፀመው ግድያ መግለጫ አውጥቷል።
" ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በምዕራብ ጎንደር ዞን ልዩ መቃ በታጣቂዎች እና በመንግሥት ፀጥታ ኃይሎች መካከል በተነሳ ግጭት መንገደኛና የእርዳታ ግብአት የጫኑ ተሽከርካሪዎች ላይ በደረሰ ድንገተኛ ተኩስ በርካታ ሹፌሮችና የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን ከአካባቢው ምንጮች አረጋግጠናል " ያለው ፓርቲው " በአጠቃላይ በጥቃቱ አንድ መቶ በላይ ሰዎች እንደተገደሉና ከነዚህም ውስጥ አሥራ ስድስት የሚሆኑት ሾፌሮች መኾናቸውን ሰምተናል " ብሏል።
" ሁኔታው ከአእምሮ በላይ ነው፤ ሟቹ ከመብዛቱ የተነሳ አስከሬን በኤክስካቫተር ጭምር ሲነሳ ተመልክተናል ይላሉ እማኞች " ሲል ገልጿል።
" በሌላ በኩል ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም በምሥራቅ አርሲ ሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑ ካህን ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ከምሽቱ 1፡30 አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላውቸውን ከአካባቢው ምንጮች ማረጋገጥ ችለናል " ብሏል።
" ያለፉትን 7 ዓመታት ኢትዮጵያ የንጹሃን ደም ጎርፍ ሆናለች ቢባል ከእውነይ የራቀ አይደለም " ያለው ፓርቲው " በተለይ የሃይማኖት አባቶችና ሾፌሮች ግድያ የቀን ተቀን ዜና ነው " ሲል ገልጿል።
" ሞቱንም ከማለባበስ በዘለለ ከእቁብም የሚቆጥረው የለም። የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዓይነት ተቋማት እንኳን በየቀኑ የሚፈሰውን የካህናትና ቤተሰባቸውን ደም ጽዋው ሞልቶ ሲፈስ ድምጽ አያሰሙም " ሲል ወቅሷል።
" ዓለምአቀፉ ማኅበረሰብም የየቀኑ መረጃ ጠረጴዛው ላይ ደርሶት እያየ እንዳላየ ሆኗል። ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ይሄ ጉዳያቸው አይደለም " ሲል ገልጿል።
" ከተወሰኑ የማኅበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች በስተቀር አጠቃላይ ሚዲያው በፍርኃት ተሸብቦ እማኝ አናግሮ ማቅረብ ዳገት ሆኖበታል፡፡ የንጹሓን ደም ግን አሁንም በየቀኑ ይጣራል" ብሏል።
ፓርቲው " ጭፍጨፋውን በጽኑ እናወግዛለን ለሞቱት እረፍተ ነፍስን፣ ለሟች ቤተሰቦችና ለየአካባቢዎቹ ማኅበረሰብ ደግሞ መጽናናትን እንመኛለን " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😭1.77K❤880😡116💔67😢28🙏19🕊16🤔15👏9🥰5😱3
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።
ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል " ብሏል።
" ብርቅዬ የክለባችን ተጫዋቾች በጨዋታ ሜዳ የገጠሙትን ሁሉንም ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉ የአደባባይ ምስጥር ነዉ " ሲል ገልጿል።
" ይሁን እንጂ ' የሊግ ካምፓኒ ያወጣውን የፋይናንስ ደንብ አላከበራችሁም ' በሚል በክለቡና በተጫዋቾች ላይ ቅጣት ተጥሎባቸዋል ቢባልም ክለቡ ያነሳዉ ዋንጫ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ በ48 ክለቦች መካከል የተደረገው መሆኑ ዕሙን ነው " ብሏል።
" የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የታገዱ ተጫዋቾችን አሰልፎ ከሆነ በጥሎ ማለፉ ያሸነፋቸው ክለቦች በሙሉ ፎርፌ አግኝተው ጉዳያቸው እንደገና መታየት አለበት እንደ ማለትም ይሆናል " ብሏል።
" እርስ በርስ የሚጣረሱ ሀሳቦችን በማገናኘት ውጤቱን ለመቀማት መሞከር ተገቢና ህግን የተከተለ ውሳኔ ነው ብለን አናምንም " ሲል ቦርዱ አሳውቋል።
" ፌዴሬሽኑ ዉሳኔውን ከህግጋቱ ጋር በማገናዘብ እንደገና እንዲያጠነዉ ቅሬታችንን እናሰማለን " ብሏል።
" ህዝባችን በፌደሬሽኑ ውሳኔ የተከፋ ቢሆንም የአፊኒ ባህል ያለው ታላቅ ህዝብ ስለሆነ ክስተቶችን በመረጋጋት መርምሮ በተገቢው እንዲያጠነውና ሂደቱን በትዕግሥት እንዲጠባበቅ በአክብሮት እየጠይቃል " ሲል ገልጿል።
" የተነፈግነው ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ጉዳዩን እስከ ፊፋ ገላጋይ ፍርድ ቤት ድረስ በይግባኝ ወስደን ለጉዳዩ ተገቢው እልባት እስኪሰጥ ድረስ የክለቡ ቦርድ ቁርጠኛ መሆኑን እናረጋግጣለን " ሲል አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ።
የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል።
ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል " ብሏል።
" ብርቅዬ የክለባችን ተጫዋቾች በጨዋታ ሜዳ የገጠሙትን ሁሉንም ከጨዋታ ብልጫ ጋር በማሸነፍ የ2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዋንጫ ማሸነፉ የአደባባይ ምስጥር ነዉ " ሲል ገልጿል።
" ይሁን እንጂ ' የሊግ ካምፓኒ ያወጣውን የፋይናንስ ደንብ አላከበራችሁም ' በሚል በክለቡና በተጫዋቾች ላይ ቅጣት ተጥሎባቸዋል ቢባልም ክለቡ ያነሳዉ ዋንጫ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ በ48 ክለቦች መካከል የተደረገው መሆኑ ዕሙን ነው " ብሏል።
" የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የታገዱ ተጫዋቾችን አሰልፎ ከሆነ በጥሎ ማለፉ ያሸነፋቸው ክለቦች በሙሉ ፎርፌ አግኝተው ጉዳያቸው እንደገና መታየት አለበት እንደ ማለትም ይሆናል " ብሏል።
" እርስ በርስ የሚጣረሱ ሀሳቦችን በማገናኘት ውጤቱን ለመቀማት መሞከር ተገቢና ህግን የተከተለ ውሳኔ ነው ብለን አናምንም " ሲል ቦርዱ አሳውቋል።
" ፌዴሬሽኑ ዉሳኔውን ከህግጋቱ ጋር በማገናዘብ እንደገና እንዲያጠነዉ ቅሬታችንን እናሰማለን " ብሏል።
" ህዝባችን በፌደሬሽኑ ውሳኔ የተከፋ ቢሆንም የአፊኒ ባህል ያለው ታላቅ ህዝብ ስለሆነ ክስተቶችን በመረጋጋት መርምሮ በተገቢው እንዲያጠነውና ሂደቱን በትዕግሥት እንዲጠባበቅ በአክብሮት እየጠይቃል " ሲል ገልጿል።
" የተነፈግነው ፍትህ እስኪረጋገጥ ድረስ ጉዳዩን እስከ ፊፋ ገላጋይ ፍርድ ቤት ድረስ በይግባኝ ወስደን ለጉዳዩ ተገቢው እልባት እስኪሰጥ ድረስ የክለቡ ቦርድ ቁርጠኛ መሆኑን እናረጋግጣለን " ሲል አሳውቋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
❤1.11K🤔144👏77😭48😡47🙏31🕊23😢10😱8💔6🥰1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል። ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል…
" ተክሰናል ፤ ሕዝቡ በልዩ ልዩ መንገዶች ደስታዉን እየገለፀ ነዉ " - የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ
ዛሬ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያስተላለፈዉን ዉሳኔ ተከትሎ የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ " የኢትዮጵያ ዋንጫን " ለወላይታ ዲቻ ይመልሳል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድንም በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ #ኢትዮጵያን የሚወክል ይሆናል።
ይህን የፌደሬሽኑን ዉሳኔ ተከትሎ የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች በአደባባይ ደስታቸዉን የገለፁ ሲሆን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላላ ከበደን ጨምሮ የክልሉና የወላይታ ዞን አመራሮች " የእንኳን ደስ ያላችሁ " መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገርናቸው የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ " ዉሳኔዉ በእግር ኳሱ ዘርፍ ተስፋ ሰጪና ለወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድን ደጋፊዎች ትልቅ ደስታን የፈጠረ ተገቢ ዉሳኔ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ተክሰናል " ያሉት ስራ አስኪያጁ " የዉሳኔዉን አፈጻጸም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በሚያስቀሚጠዉ ዕቅድ መሰረት ተፈፃሚ እናደርጋለን " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
ዛሬ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን ያስተላለፈዉን ዉሳኔ ተከትሎ የሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ " የኢትዮጵያ ዋንጫን " ለወላይታ ዲቻ ይመልሳል ወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድንም በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ #ኢትዮጵያን የሚወክል ይሆናል።
ይህን የፌደሬሽኑን ዉሳኔ ተከትሎ የወላይታ ዲቻ ደጋፊዎች በአደባባይ ደስታቸዉን የገለፁ ሲሆን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጥላላ ከበደን ጨምሮ የክልሉና የወላይታ ዞን አመራሮች " የእንኳን ደስ ያላችሁ " መልዕክት አስተላልፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገርናቸው የወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ክለብ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ሆሲሶ " ዉሳኔዉ በእግር ኳሱ ዘርፍ ተስፋ ሰጪና ለወላይታ ዲቻ እግር ኳስ ቡድን ደጋፊዎች ትልቅ ደስታን የፈጠረ ተገቢ ዉሳኔ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።
" ተክሰናል " ያሉት ስራ አስኪያጁ " የዉሳኔዉን አፈጻጸም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌደሬሽን በሚያስቀሚጠዉ ዕቅድ መሰረት ተፈፃሚ እናደርጋለን " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
❤1.52K😱173😡143🤔78👏56😭39🕊33🙏28🥰27💔11😢5
#SafaricomEthiopia
🤙🏽ከሳፋሪኮም ወደ የቴሌ የሚያስደውሉ የድምፅ ጥቅሎች በመጠቀም ከ07 ➡️ 09 መስመር በእጥፍ ጉርሻ በሽ በሽ ብለን እንደዋወል! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
🤙🏽ከሳፋሪኮም ወደ የቴሌ የሚያስደውሉ የድምፅ ጥቅሎች በመጠቀም ከ07 ➡️ 09 መስመር በእጥፍ ጉርሻ በሽ በሽ ብለን እንደዋወል! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
5❤143😡10🙏7🕊1
ዋሪት ፈርኒቸር
የመኖሪያ እና የስራ ቦታዎን ዛሬውኑ ይቀይሩ!
🛋የሪክላይነር ሶፋ ከምቾት ባለፈ የሚሰጠውን ጥቅም!
ጤናማ የደም ግፊትን እና የደም ዝውውርን ይደግፋሉ፣
አቀማመጥን ያሻሽላሉ፣ በተጨማሪም ለጭንቀት እፎይታ፣ እንደ ህመም ማስታገሻ እንደሚረዳ ያውቁ ኖሯል?
እንግዲያውስ በአንድ ቦታ ምቾት፣ ጤና እና ምርታማ ወደሚሆኑበት
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
* ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: 0911210706 / 07
https://www.instagram.com/warytfurniture
https://www.tg-me.com/warytfurniture
https://www.tiktok.com/@warytzefurniture
የመኖሪያ እና የስራ ቦታዎን ዛሬውኑ ይቀይሩ!
🛋የሪክላይነር ሶፋ ከምቾት ባለፈ የሚሰጠውን ጥቅም!
ጤናማ የደም ግፊትን እና የደም ዝውውርን ይደግፋሉ፣
አቀማመጥን ያሻሽላሉ፣ በተጨማሪም ለጭንቀት እፎይታ፣ እንደ ህመም ማስታገሻ እንደሚረዳ ያውቁ ኖሯል?
እንግዲያውስ በአንድ ቦታ ምቾት፣ ጤና እና ምርታማ ወደሚሆኑበት
ወደ ማሳያ ክፍሎቻችን በመምጣት ይጎብኙን !
* 22 - ዋሪት ህንፃ
* ጉርድ ሾላ - ሴንቸሪ ሞል
* ለቡ - ቫርኔሮ ፊት ለፊት
* አዳማ - ሶረቲ ሞል
* ቡልቡላ- ልዑል ህንፃ ፊት ለፊት
* ወሎ ሰፈር- Ethiolife life real estate
ዋሪት ፈርኒቸር
ትክክለኛ ምርጫ!
ለተጨማሪ መረጃ: 0911210706 / 07
https://www.instagram.com/warytfurniture
https://www.tg-me.com/warytfurniture
https://www.tiktok.com/@warytzefurniture
❤141🙏11🤔4😢2😭2🥰1😡1
TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ መኪና አስቁመው 1 ሺሕ፣ 2 ሺሕ ብር የሚቀበሉ የወረዳ ታጣቂዎች አሉ። ከፍተኛ የገንዘብ ጥቅም ስላለ ቁሞ ካበቃ በኋላ ኬላው ተነስቶ ድንገት የሚፈትሹ አሉ " - ማኀበሩ ሕገ ወጥ በመሆናቸው እንዲነሱ ተደርገው የነበሩ ኬላዎች ተመልሰው በመዘርጋታቸው አሽከርካሪዎች በአንድ ኬላ ብቻ 2,000 ብር እየተጠየቁ በመሆኑ መማራቸውን አሽከርካሪዎቹና የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ…
" ኬላዎች ናቸው ሕገ ወጥ እንጂ ኬላዎችን ዘርግተው የሚሰበስቡ ግን የመንግስት ተቋማት ናቸው " - ጉምሩክ ኮሚሽን
ሹፌሮች በየአካባቢው ባሉ ሕገ ወጥ ኬላዎች ገንዘብ እየተጠየቁ መማረራቸውን፣ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበርም ድርጊቱ በክልሎችና ወረዳዎች እንደሚፈጸምና ጉዳዩን በቅጡ መቆጣጠር እንዳተቻለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ጭምር ገልጸዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽን በበኩሉ፣ የ11 ወራት ሪፓርቱን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት የጉዳዩን አሳሳቢነትና በጥናት ጭምር መዳሰሱን ተናግሯል።
ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዘወው ጫኔ፣ "ሕገ ወጥ ኬላዎች ከሀገር በሚወጡና በሀገር በሚገቡ እቃዎች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በንግድ ስርዓቱ፣ በሎጂስቲክ፣ ከዋጋ ንረትም ጋር ጉልህ ሚና የሚጫወቱ አሉታዊ ተፅዕኖ አላቸው" ሲሉ ተደምጠዋል።
አክለው፣ "በጥናት የተረጋገጠ ስለሆነ ነው በዚህ ደረጀ የምናነሳው። ይሄ የክልልና ከተማ አስተዳደሮችን የሚመለከት ነው" ብለው፣ በሚያዚያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ትራንስፓርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ሆነው ስለድርጊቱ በክልሎች ጥናት እንዳደረጉ ተናግረዋል።
ድርጊቱ እንዴት እንደሚፈጸም፣ ምን ያክል ሕገወጥ ኬላዎች እንዳሉ፣ የኬላዎቹ ስያሜ ጭምር በተመለከተ ጥናት መደረጉን፣ ከዚህ በፊት ኬላዎች እንዲነሱ አቅጣጫ እንደተሰጠ ገልጸው፣ "የተነሱ አሉ፤ አዲስ የተጨመሩም አሉ" ብለዋል።
ጥናቱ እስከተጠናበት ጊዜ 237 ሕገወጥ ኬላዎች እንዳሉ ጠቅሰው፣ "በሕግ የቀመጠው ኬላን ማቋቋም የጉምሩክ ስልጣን ነው፤ ክልሎች ግን በተለያየ ምክንያት እነዚህን ኬላዎች አቋቁመው ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው" ሲሉም ተደምጠዋል።
"ኬላዎች ናቸው ሕገወጥ እንጂ ኬላዎችን ዘርግተው ግብር የሚሰበስቡት ግን የመንግስት ተቋማት ናቸው" ያሉት አቶ አዘዘው ፣ ይህም "በክልል ፓሊስ፣ በሚሊሻ መዋቅሮች፣ በአንዳንድ ቦታ በመንግስት የተቋቋሙ የሥራ እድል ፈጠራ፣ የወረዳ ግብረ ኃይል በሚል ጨምር" እንደሚፈጸም ተናግረዋል።
ችግሩን ለመቅረፍ ኮሚሽኑ ብቻ ሳይሆን በመንግስት ደረጃ መፈጸም እንዳለበት፣ በጉዳዩ ዙሪያ የተጠናው ጥናት ለመንግስት እንደቀረበ ጠቅሰው፣ "በ2018 ዓ/ም ችግሩ ይቀረፋል የሚል እምነት አለን" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopuiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ሹፌሮች በየአካባቢው ባሉ ሕገ ወጥ ኬላዎች ገንዘብ እየተጠየቁ መማረራቸውን፣ የኢትዮጵያ ከባድ መኪና አሽከርካሪዎች ማኀበርም ድርጊቱ በክልሎችና ወረዳዎች እንደሚፈጸምና ጉዳዩን በቅጡ መቆጣጠር እንዳተቻለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰሞኑን ጭምር ገልጸዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽን በበኩሉ፣ የ11 ወራት ሪፓርቱን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት የጉዳዩን አሳሳቢነትና በጥናት ጭምር መዳሰሱን ተናግሯል።
ምክትል ኮሚሽነር አቶ አዘወው ጫኔ፣ "ሕገ ወጥ ኬላዎች ከሀገር በሚወጡና በሀገር በሚገቡ እቃዎች ብቻ ሳይሆን በአጠቃላይ በንግድ ስርዓቱ፣ በሎጂስቲክ፣ ከዋጋ ንረትም ጋር ጉልህ ሚና የሚጫወቱ አሉታዊ ተፅዕኖ አላቸው" ሲሉ ተደምጠዋል።
አክለው፣ "በጥናት የተረጋገጠ ስለሆነ ነው በዚህ ደረጀ የምናነሳው። ይሄ የክልልና ከተማ አስተዳደሮችን የሚመለከት ነው" ብለው፣ በሚያዚያ ጉምሩክ ኮሚሽን፣ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር እና ትራንስፓርትና ሎጂስቲክ ሚኒስቴር ሆነው ስለድርጊቱ በክልሎች ጥናት እንዳደረጉ ተናግረዋል።
ድርጊቱ እንዴት እንደሚፈጸም፣ ምን ያክል ሕገወጥ ኬላዎች እንዳሉ፣ የኬላዎቹ ስያሜ ጭምር በተመለከተ ጥናት መደረጉን፣ ከዚህ በፊት ኬላዎች እንዲነሱ አቅጣጫ እንደተሰጠ ገልጸው፣ "የተነሱ አሉ፤ አዲስ የተጨመሩም አሉ" ብለዋል።
ጥናቱ እስከተጠናበት ጊዜ 237 ሕገወጥ ኬላዎች እንዳሉ ጠቅሰው፣ "በሕግ የቀመጠው ኬላን ማቋቋም የጉምሩክ ስልጣን ነው፤ ክልሎች ግን በተለያየ ምክንያት እነዚህን ኬላዎች አቋቁመው ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው" ሲሉም ተደምጠዋል።
"ኬላዎች ናቸው ሕገወጥ እንጂ ኬላዎችን ዘርግተው ግብር የሚሰበስቡት ግን የመንግስት ተቋማት ናቸው" ያሉት አቶ አዘዘው ፣ ይህም "በክልል ፓሊስ፣ በሚሊሻ መዋቅሮች፣ በአንዳንድ ቦታ በመንግስት የተቋቋሙ የሥራ እድል ፈጠራ፣ የወረዳ ግብረ ኃይል በሚል ጨምር" እንደሚፈጸም ተናግረዋል።
ችግሩን ለመቅረፍ ኮሚሽኑ ብቻ ሳይሆን በመንግስት ደረጃ መፈጸም እንዳለበት፣ በጉዳዩ ዙሪያ የተጠናው ጥናት ለመንግስት እንደቀረበ ጠቅሰው፣ "በ2018 ዓ/ም ችግሩ ይቀረፋል የሚል እምነት አለን" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopuiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤451😭58😡25👏15🤔13🕊10💔6😱3
በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይፋ ሆነ።
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል።
የፈተናው ውጤትም ይፋ ተደርጓል።
በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።
በ2017 ዓ.ም 79,034 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ተገልጿል።
Photo : AAEB
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል።
የፈተናው ውጤትም ይፋ ተደርጓል።
በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።
በ2017 ዓ.ም 79,034 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ተገልጿል።
Photo : AAEB
@tikvahethiopia
❤635👏68😡42🕊38😭35🙏29😢17🤔15💔15🥰10😱7
TIKVAH-ETHIOPIA
በመዲናዋ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይፋ ሆነ። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት የ2017 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የማለፊያ ውጤት 50% እንዲሆን በዛሬው እለት ወስነዋል። የፈተናው ውጤትም ይፋ ተደርጓል። በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሰረት በከተማ አስተዳደሩ የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ2015 የትምህርት ዘመን ጀምሮ እየተሰጠ ይገኛል።…
" ተማሪዎች ውጤታቸውን በ https://aa6.ministry.et/#/result
ወይም በ @emacs_ministry_result_qmt_bot ላይ መመልከት ይችላሉ " - ትምህርት ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 95 % ያህሉ 50% እና ከዛ በላይ በማምጣት ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
በ2017 ዓ.ም ፈተናውን ከወሰዱ 79,034 ተማሪዎች መካከል 75,085 ተማሪዎች ማለትም 95 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50% እና በላይ አስመዝግበው ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።
ዘንድሮው በከተማ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ1 እስከ 4 የሚሆኑት ከመንግስት ትምህርት ቤቶች መሆናቸው አመልክተዋል።
" በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መጥቷል " ሲሉ ገልጸዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ ተብሏል።
LINK ፦ https://aa6.ministry.et/#/result
Telegram Bot : @MinistryResultQMTBOT
@tikvahethiopia
ወይም በ @emacs_ministry_result_qmt_bot ላይ መመልከት ይችላሉ " - ትምህርት ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 95 % ያህሉ 50% እና ከዛ በላይ በማምጣት ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
በ2017 ዓ.ም ፈተናውን ከወሰዱ 79,034 ተማሪዎች መካከል 75,085 ተማሪዎች ማለትም 95 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50% እና በላይ አስመዝግበው ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።
ዘንድሮው በከተማ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ1 እስከ 4 የሚሆኑት ከመንግስት ትምህርት ቤቶች መሆናቸው አመልክተዋል።
" በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መጥቷል " ሲሉ ገልጸዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ ተብሏል።
LINK ፦ https://aa6.ministry.et/#/result
Telegram Bot : @MinistryResultQMTBOT
@tikvahethiopia
❤880🙏62😭43👏37🥰20🕊19😢13💔13😱12🤔1😡1