" ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " - አቶ በየነ ምክሩ
አሁን ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙትና የትእምት (EFFORT) ዋና ስራ አስፈፃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ በየነ መክሩ ' ላዛ ትግርኛ ' ለተባለ የዩቱብ ሚድያ ቃለ መጠይቅ ሰጥተው ነበር።
በዚህም " ህገ-ወጥ " ሲሉ የጠሩት የደብረፅን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ ከፍተኛ አደጋ እንዲያንዣብብ እየተንቀሳቀሰ ነው በማለት ከሰዋል።
መጋቢት 2017 ዓ.ም በትግራይ በወቅቱ በነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ላይ በተከሰተው ከፍተኛ የፓለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መውጣታቸው የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው የሳቸውንና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ቴድሮስ ሓጎስ የሚጠቀሙበት ማህተም ከህግ አገባብ ውጪ በማስቀረፅ " ህገ-ወጡ ቡድን " አደገኛ ተግባራት በመፈፀም ላይ ይገኛል ብለዋል።
" ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ ቦርድና የባለ አደራ ቦርድ በስራ እያለ ቡድኑ የራሱ ህገ-ወጥ ቦርድና የባለ አደራ ቦርድ በመሰየም ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር ማስታወቅያ በማስነገር ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ በየነ " ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት ይህንን መሰል እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " ብለዋል።
" የቡድኑ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ካምፓኒዎቹ ከስራ ውጭ እንዳያደርግ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ተከታታይ ምክክሮች እያካሄድን ነው " ያሉ ሲሆን " ጉዳዩ በህግ-ማእቀፍ እንዲታይ በክልሉ ፍትህ ቢሮ ክስ መመስርተናል " ሲሉ አስታውቀዋል።
ይህን ሳይሳካ ከቀረ ግን የፌደራል መንግስት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ በጦርነቱ ጊዜ ያስቀመጠው እግድ መልሶ ለማየት የሚገደድበት ሁኔታ ዝግ አይደለም ብለዋል።
በተጨማሪ ምን አሉ ?
- " የትእምት 60 በመቶ ሃብት በጦርነቱ ወድሟል ፤ መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ አርጅቷል ፤ ትራንስ ኢትዮጵያ ከነበሩት 500 መኪኖች አሮጌ 100 መኪኖች ብቻ ነው የቀሩት ፤ አልመዳ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ በአውሮፕላን ቦንብ ሙሉ በሙሉ ወድመዋል። "
- " የፌደራል መንግስት ከጥቅምት 2013 እስከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም በትእምት ካምፓኒዎች ላይ አኖሮት የነበረው እግድ ለጊዜው ሲያነሳ ካምፓኒዎቹ ከህወሓት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው መስራት እንዳለባቸው ቅድመ ማስጠንቀቂያ ስጥቶ ነው ያስረከበን። "
- " የፌደራል መንግስት በትእምት ካምፓኒዎች ያስቀመጠው እግድ ሙሉ በሙሉ ባለነሳበት ሁኔታ ሆነን ከፓለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው እንዲያንሰራሩ ስንሰራ ነበር፤ ህገወጡ የህወሓት ቡድን ከካምፓኒዎቹ ላይ እጁ የማያነሳ ከሆነ የፌደራል መንግስት እግድ ሊቀጥል ይችላል። "
- " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው። "
ትእምት ኢንቨስትመንት በስሩ 15 ካምፓኒዎች እንዳሉት ይታወቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
አሁን ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙትና የትእምት (EFFORT) ዋና ስራ አስፈፃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ በየነ መክሩ ' ላዛ ትግርኛ ' ለተባለ የዩቱብ ሚድያ ቃለ መጠይቅ ሰጥተው ነበር።
በዚህም " ህገ-ወጥ " ሲሉ የጠሩት የደብረፅን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ ከፍተኛ አደጋ እንዲያንዣብብ እየተንቀሳቀሰ ነው በማለት ከሰዋል።
መጋቢት 2017 ዓ.ም በትግራይ በወቅቱ በነበረው ጊዚያዊ አስተዳደር ላይ በተከሰተው ከፍተኛ የፓለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ወደ አዲስ አበባ መውጣታቸው የተናገሩት ዋና ስራ አስፈፃሚው የሳቸውንና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ ቴድሮስ ሓጎስ የሚጠቀሙበት ማህተም ከህግ አገባብ ውጪ በማስቀረፅ " ህገ-ወጡ ቡድን " አደገኛ ተግባራት በመፈፀም ላይ ይገኛል ብለዋል።
" ዋና ስራ አስፈፃሚ ፣ ቦርድና የባለ አደራ ቦርድ በስራ እያለ ቡድኑ የራሱ ህገ-ወጥ ቦርድና የባለ አደራ ቦርድ በመሰየም ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር ማስታወቅያ በማስነገር ላይ ይገኛል ሲሉ ተናግረዋል።
አቶ በየነ " ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት ይህንን መሰል እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " ብለዋል።
" የቡድኑ ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ካምፓኒዎቹ ከስራ ውጭ እንዳያደርግ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ተከታታይ ምክክሮች እያካሄድን ነው " ያሉ ሲሆን " ጉዳዩ በህግ-ማእቀፍ እንዲታይ በክልሉ ፍትህ ቢሮ ክስ መመስርተናል " ሲሉ አስታውቀዋል።
ይህን ሳይሳካ ከቀረ ግን የፌደራል መንግስት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ በጦርነቱ ጊዜ ያስቀመጠው እግድ መልሶ ለማየት የሚገደድበት ሁኔታ ዝግ አይደለም ብለዋል።
በተጨማሪ ምን አሉ ?
- " የትእምት 60 በመቶ ሃብት በጦርነቱ ወድሟል ፤ መሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ አርጅቷል ፤ ትራንስ ኢትዮጵያ ከነበሩት 500 መኪኖች አሮጌ 100 መኪኖች ብቻ ነው የቀሩት ፤ አልመዳ የጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ በአውሮፕላን ቦንብ ሙሉ በሙሉ ወድመዋል። "
- " የፌደራል መንግስት ከጥቅምት 2013 እስከ ጥቅምት 2015 ዓ.ም በትእምት ካምፓኒዎች ላይ አኖሮት የነበረው እግድ ለጊዜው ሲያነሳ ካምፓኒዎቹ ከህወሓት ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው መስራት እንዳለባቸው ቅድመ ማስጠንቀቂያ ስጥቶ ነው ያስረከበን። "
- " የፌደራል መንግስት በትእምት ካምፓኒዎች ያስቀመጠው እግድ ሙሉ በሙሉ ባለነሳበት ሁኔታ ሆነን ከፓለቲካ ጣልቃ ገብነት ነፃ ሆነው እንዲያንሰራሩ ስንሰራ ነበር፤ ህገወጡ የህወሓት ቡድን ከካምፓኒዎቹ ላይ እጁ የማያነሳ ከሆነ የፌደራል መንግስት እግድ ሊቀጥል ይችላል። "
- " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው። "
ትእምት ኢንቨስትመንት በስሩ 15 ካምፓኒዎች እንዳሉት ይታወቃል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤780🤔57🕊33😡20🥰17😭14🙏7😢6😱4
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" መንግስት ሁሉን አቀፍ እና አካታች ፖለቲካዊ ውይይት ማድረግ አለበት " - የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ)
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ ከአምስት አመት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አካሄደ።
በዚህ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የኦነግ በማዕከላዊ ኮሚቴ ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ ምን አለ ?
- መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ሁሉን አቀፍ ፖለቲካዊ ውይይት ያድርግ፤
- የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ ውስጥ ካሉ አካላት ጋር በመነጋገር ችግሮች ይፍታ፤
- የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ እና ነፃ እንዲሆን ይሁን ሲል መጠየቁን አቶ ለሚ ተናግረዋል ።
ፓርቲው ላለፉት አምስት አመታት በየደረጃው ያሉ አመራሮቹና አባላቶቹ በመታሰራቸው እንዲሁም ከዋናው ጅምሮ በዞን እና ወረዳዎች ያሉት ጽህፈት ቤቶቹ በመዘጋታቸው የፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ማሳለፉን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አስታውሰዋል።
በፓርቲው በውስጥ የገጠሙትን ችግሮች እና ክፍተቶች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ በቅርቡ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ኮሚቴ መዋቀሩንም አቶ ለሚ ገልፀዋል።
ፓርቲው በሀምሳ አመት የትግል ጉዞው ያስመዘገባቸው ድሎች እና ድክመቶች በዚህ ጉባኤው ይገመግማል ያሉት አቶ ለሚ የወደፊት የሰላማዊ ትግል አቅጣጫ ያስቀምጣል ብለዋል።
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ በቀጣይ ጉባኤው እያደረገ ያለው ሰላማዊ ትግል ፀንቶ እንደሚቀጥል የተናገሩት አቶ ለሚ " መንግስት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ዴሞክራሲን መለማመድ አስፈላጊ መሆኑን እንዲገነዘብ ከወዲሁ እናሳስባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ፎቶ፦ ፋይል
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte
@tikvahethiopia
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ ከአምስት አመት ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አካሄደ።
በዚህ ስብሰባ የተለያዩ ውሳኔዎችን ማሳለፉን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለሚ ገመቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
የኦነግ በማዕከላዊ ኮሚቴ ሰሞኑን ባካሄደው ስብሰባ ምን አለ ?
- መንግስት በሀገሪቱ ውስጥ ሰላምና መረጋጋት እንዲመጣ ሁሉን አቀፍ ፖለቲካዊ ውይይት ያድርግ፤
- የትጥቅ ትግል እንቅስቃሴ ውስጥ ካሉ አካላት ጋር በመነጋገር ችግሮች ይፍታ፤
- የፖለቲካ ምህዳሩ እንዲሰፋ እና ነፃ እንዲሆን ይሁን ሲል መጠየቁን አቶ ለሚ ተናግረዋል ።
ፓርቲው ላለፉት አምስት አመታት በየደረጃው ያሉ አመራሮቹና አባላቶቹ በመታሰራቸው እንዲሁም ከዋናው ጅምሮ በዞን እና ወረዳዎች ያሉት ጽህፈት ቤቶቹ በመዘጋታቸው የፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ለማድረግ አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ማሳለፉን የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አስታውሰዋል።
በፓርቲው በውስጥ የገጠሙትን ችግሮች እና ክፍተቶች ላይ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ለማሳለፍ በቅርቡ ጠቅላላ ጉባኤ ለማድረግ ኮሚቴ መዋቀሩንም አቶ ለሚ ገልፀዋል።
ፓርቲው በሀምሳ አመት የትግል ጉዞው ያስመዘገባቸው ድሎች እና ድክመቶች በዚህ ጉባኤው ይገመግማል ያሉት አቶ ለሚ የወደፊት የሰላማዊ ትግል አቅጣጫ ያስቀምጣል ብለዋል።
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ በቀጣይ ጉባኤው እያደረገ ያለው ሰላማዊ ትግል ፀንቶ እንደሚቀጥል የተናገሩት አቶ ለሚ " መንግስት የፖለቲካ ምህዳሩን በማስፋት ዴሞክራሲን መለማመድ አስፈላጊ መሆኑን እንዲገነዘብ ከወዲሁ እናሳስባለን " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
ፎቶ፦ ፋይል
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ነቀምቴ
#TikvahEthiopiaFamliyNekemte
@tikvahethiopia
❤566😡153🕊35🤔24👏11🙏8🥰7😱4😢4
#AddisAbaba
ሽንኩርት ፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች #ከቫት ነጻ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።
ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።
በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።
በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።
ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
ሽንኩርት ፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች #ከቫት ነጻ እንደሆኑ የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው " ማህበረሰቡ ዕለት በዕለት የሚሸምታቸው ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ ተደርገዋል " ሲል ገልጿል።
ከሰሞኑን ለቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች በወረደው ሰርኩላር ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች የአትክልት ምርቶች ከቫት ውጭ መደረጋቸውን አመላክቷል።
በሰርኩላሩ ላይ " የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ 1341/2016 አንቀፅ 10 እና አዋጅን ለማስፈፀም በወጣው ደንብ ቁጥር 570/2017 ዓ.ም መሰረት ያልተዘጋጁ እንደ ሽንኩርት፣ ድንችና ሌሎች አትክልቶች ያሉ ምርቶች ወደሀገር ውስጥ ሲገቡም ሆነ በሀገር ውስጥ ተመርተው ለግብይት ሲቀርቡ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ መደረጋቸውን ተደንግጓል " በሚል ተቀምጧል።
በዚህም መሰረት ያልተዘጋጁ የአትክልት ምርቶች የሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች ብቻ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የተደረጉ መሆናቸው ታውቆ ከሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ አጠቃቀም ጋር በተያያዘ ተገቢው ክትትል በማድረግ እንዲፈፀም አዟል።
ይሁንና በአዋጁ ከታክስ ነፃ ከተደረጉ ውጪ የፍራፍሬ ምርቶች በሚያቀርቡ ግብር ከፋዮች የቫት አሰራሩ የሚቀጥል መሆኑን በመግለፅ ተገቢው ክትትል እንዲደረግ ቢሮው አሳስቧል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
❤1.89K🙏220👏108🤔74😡54🕊24😱18😢18🥰17😭16
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
የሁለት ወር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy) የክረምት
ስልጠና የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://www.tg-me.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
የሁለት ወር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy) የክረምት
ስልጠና የፊታችን ሰኞ ሐምሌ 07/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram: https://www.tg-me.com/sagetraininginstitute
Tiktok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
Linkedin: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute
❤179😭5😡5🙏3🕊3
" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " - የዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን
በአራት ክልሎች ኢንደሚክ የሚባሉትን ጨምሮ ወደ 54 የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳትን በውጪ ዜጎች እየታደኑ በዶላር እየተሸጡ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።
በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ባለሙያ አቶ ፋንታዬ ነጋሽ በሰጡን ገለጻ፣ ለምሳሌ " አንድ ኒያላ 15 ሺሕ ዶላር ነው የሚሸጠው፤ ይሄ ይበቃል? አይበቃም? የሚለው ገና እየታየ ነው በሕግ፤ አልጸደቀም እንጂ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድረስ ገብቷል ረቂቁ። ዋጋው በቂ አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ እንዲህ አይነት በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳት መታደናቸው ልክ አይደለም የሚሉ ቁጣዎች እየተሰነዘሩ ነው፤ ለዚህ ትችት ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? ሲል አቶ ፋንታዬን ጠይቋል።
" ኢንደሚክ እንስሳት ይታደናሉ፤ ያም ደግሞ ዝም ብሎ በዘፈቀደ ሂዶ ማደን ሳይሆን ሳይንሳዊ በሚሆን መንገድ ተጠንቶ፤ ተቆጥረው ይህን ያክል ቢገደል ተብሎ በሚሰጥ ኮታ መሠረት ነው። የእንስሳቱን የመኖር ህልውና ምንም አደጋ ላይ በማይጥል መልኩ ተጠንቶ ነው ያ የሚደረገው፤ ያም ሲደረግ ደግሞ ከፌደራል፣ ከክልል የተውጣጡ ባለሙያዎች አጥንተው ሳይንሳዊ የሆነ ሪሰርች ቀርቦ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ሁሉም የየራሳቸው ዋጋና ኮታ አላቸው። ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " ብለዋል ባለሙያው።
ይህ የሚሆነው አንድ እንስሳ ምን ያህል ቢገደል ነው የእንስሳቱን ቁጥር የማይጎዳው? ተብሎ ቀንዱ ተለክቶ እድሜው ታውቆ እንደሆነ አስረድተው፣ "ለምሳሌ ኒያላን ከ29.5 ኢንቺ በታች ቱሪስቶች በስህተት እንኳ ከገደሉ የእንስሳውን እጥፍ ነው የሚከፍሉት። ማንኛውንም ሴት እንስሳ ቢገድሉ ደግሞ የዋጋውን እጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋል " በማለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በሌሎች ሀገራት የሌሉ ኢትዮጵያ ብቻ የምትታወቅባቸው ብርቅዬ እንስሳት እየታደኑ የሚሸጡ ከሆነ በአንድ ወቅት ህልውናቸው ሊጠፋ ስለሚችል ጭራሹንም መጠሪያ ማጣትን አያስከትልም ወይ? ከጠፉ ደግሞ የቱሪስት ፍሰት አይኖርምና ከሚገደሉ ይልቅ በቱሪስት የሚያስገኙት ገቢ አይሻልም ወይ? በሚል ለሚነሳው ስጋት ምላሽ እንዲሰጡም አቶ ፋንታዬን ጠይቀናቸዋል።
ምን መለሱ?
" ያልከው ስጋት ምናልባት ስፓርታዊ ሃንቲንግ ምንድን ነው? ብለው በትክክል ካለመረዳት የመጣ ነው። መስጋታቸው ምንም ሊደንቅ አይገባም፤ ግን ደግሞ ሳይንሱን ቢያውቁት ግልጽ ይሆንላቸዋል።
ሲቀጥል እንስሳቱ የሚታደኑት ፓርክ ላይ አይደለም። ይልቁንም ለእነርሱ ተብሎ የተከለለ የአደን ቀበሌ አለ፤ ከፓርኮቻችን ቢያንስ 5 ኪሎ ሜትር የራቀ ቦታ እንጂ ብሔራዊ ፓርኮች ውስጥ አደን አይፈቀድም። ነገር ግን ዓለም አቀፍ ህግ በሚፈቅደው መልኩ የአደን ቀበሌ ተብሎ ይቋቋልማል፤ እዚያ አደን ቀበሌ ላይ ነው ኮታ የሚሰጠው።
ኒያላ ብቻ ሳይሆን ወደ 54 እንስሳትን እናሳድናለን፤ አንድ ቱሪስት ደግሞ ኒያላ ብቻ ብሎ አይመጣም። ሌሎች እንስሳትን (የምኒልክ ድኩላ፣ ተራ ድኩላ፣ የቆላ አጋዘን...) አብሮ ይገዛል። ሁሉም በሳይንሳዊ መንገድ ተጠንተው ኮታ ተሰጥቷቸው ነው የሚታደኑት " ብለዋል።
በዚሁ አደንም ከፍተኛ ገቢ እንደሚገኝ፣ 85 በመቶው ገቢ እንስሳው ለታደነበት ክልል፣ 15 በመቶው ለፌደራል መንግስት እንደሚገባ፣ አደኑ በኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሶማሌና አፋር ክልሎች እንደሚከናወን፣ የታደኑትን እንስሳትን ትክክለኛ ቁጥር ለጊዜው ባያስታውሱም በዚህ ዓመት ወደ 177 ሚሊዮን ብር ገቢ እንደተገኘ ገልዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በአራት ክልሎች ኢንደሚክ የሚባሉትን ጨምሮ ወደ 54 የኢትዮጵያ ብርቅዬ የዱር እንስሳትን በውጪ ዜጎች እየታደኑ በዶላር እየተሸጡ መሆኑን የኢትዮጵያ የዱር እንስሳት ባለስልጣን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገረ።
በባለስልጣኑ የዱር እንስሳት አጠቃቀም ባለሙያ አቶ ፋንታዬ ነጋሽ በሰጡን ገለጻ፣ ለምሳሌ " አንድ ኒያላ 15 ሺሕ ዶላር ነው የሚሸጠው፤ ይሄ ይበቃል? አይበቃም? የሚለው ገና እየታየ ነው በሕግ፤ አልጸደቀም እንጂ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ድረስ ገብቷል ረቂቁ። ዋጋው በቂ አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ እንዲህ አይነት በኢትዮጵያ ብቻ የሚገኙ ብርቅዬ እንስሳት መታደናቸው ልክ አይደለም የሚሉ ቁጣዎች እየተሰነዘሩ ነው፤ ለዚህ ትችት ያላችሁ ምላሽ ምንድን ነው ? ሲል አቶ ፋንታዬን ጠይቋል።
" ኢንደሚክ እንስሳት ይታደናሉ፤ ያም ደግሞ ዝም ብሎ በዘፈቀደ ሂዶ ማደን ሳይሆን ሳይንሳዊ በሚሆን መንገድ ተጠንቶ፤ ተቆጥረው ይህን ያክል ቢገደል ተብሎ በሚሰጥ ኮታ መሠረት ነው። የእንስሳቱን የመኖር ህልውና ምንም አደጋ ላይ በማይጥል መልኩ ተጠንቶ ነው ያ የሚደረገው፤ ያም ሲደረግ ደግሞ ከፌደራል፣ ከክልል የተውጣጡ ባለሙያዎች አጥንተው ሳይንሳዊ የሆነ ሪሰርች ቀርቦ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።
" ወደ 54 እንስሳት ነው የምናሳድነው፤ ሁሉም የየራሳቸው ዋጋና ኮታ አላቸው። ኢንደሚክ የሆኑ ለምሳሌ ጭላዳ ዝንጀሮንም፣ የምኒልክ ድኩላንም እናሳድናለን " ብለዋል ባለሙያው።
ይህ የሚሆነው አንድ እንስሳ ምን ያህል ቢገደል ነው የእንስሳቱን ቁጥር የማይጎዳው? ተብሎ ቀንዱ ተለክቶ እድሜው ታውቆ እንደሆነ አስረድተው፣ "ለምሳሌ ኒያላን ከ29.5 ኢንቺ በታች ቱሪስቶች በስህተት እንኳ ከገደሉ የእንስሳውን እጥፍ ነው የሚከፍሉት። ማንኛውንም ሴት እንስሳ ቢገድሉ ደግሞ የዋጋውን እጥፍ እንዲከፍሉ ይደረጋል " በማለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።
በሌሎች ሀገራት የሌሉ ኢትዮጵያ ብቻ የምትታወቅባቸው ብርቅዬ እንስሳት እየታደኑ የሚሸጡ ከሆነ በአንድ ወቅት ህልውናቸው ሊጠፋ ስለሚችል ጭራሹንም መጠሪያ ማጣትን አያስከትልም ወይ? ከጠፉ ደግሞ የቱሪስት ፍሰት አይኖርምና ከሚገደሉ ይልቅ በቱሪስት የሚያስገኙት ገቢ አይሻልም ወይ? በሚል ለሚነሳው ስጋት ምላሽ እንዲሰጡም አቶ ፋንታዬን ጠይቀናቸዋል።
ምን መለሱ?
" ያልከው ስጋት ምናልባት ስፓርታዊ ሃንቲንግ ምንድን ነው? ብለው በትክክል ካለመረዳት የመጣ ነው። መስጋታቸው ምንም ሊደንቅ አይገባም፤ ግን ደግሞ ሳይንሱን ቢያውቁት ግልጽ ይሆንላቸዋል።
ሲቀጥል እንስሳቱ የሚታደኑት ፓርክ ላይ አይደለም። ይልቁንም ለእነርሱ ተብሎ የተከለለ የአደን ቀበሌ አለ፤ ከፓርኮቻችን ቢያንስ 5 ኪሎ ሜትር የራቀ ቦታ እንጂ ብሔራዊ ፓርኮች ውስጥ አደን አይፈቀድም። ነገር ግን ዓለም አቀፍ ህግ በሚፈቅደው መልኩ የአደን ቀበሌ ተብሎ ይቋቋልማል፤ እዚያ አደን ቀበሌ ላይ ነው ኮታ የሚሰጠው።
ኒያላ ብቻ ሳይሆን ወደ 54 እንስሳትን እናሳድናለን፤ አንድ ቱሪስት ደግሞ ኒያላ ብቻ ብሎ አይመጣም። ሌሎች እንስሳትን (የምኒልክ ድኩላ፣ ተራ ድኩላ፣ የቆላ አጋዘን...) አብሮ ይገዛል። ሁሉም በሳይንሳዊ መንገድ ተጠንተው ኮታ ተሰጥቷቸው ነው የሚታደኑት " ብለዋል።
በዚሁ አደንም ከፍተኛ ገቢ እንደሚገኝ፣ 85 በመቶው ገቢ እንስሳው ለታደነበት ክልል፣ 15 በመቶው ለፌደራል መንግስት እንደሚገባ፣ አደኑ በኦሮሚያ፣ ደቡብ፣ ሶማሌና አፋር ክልሎች እንደሚከናወን፣ የታደኑትን እንስሳትን ትክክለኛ ቁጥር ለጊዜው ባያስታውሱም በዚህ ዓመት ወደ 177 ሚሊዮን ብር ገቢ እንደተገኘ ገልዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😡867❤551😭38💔21🤔20🙏10🕊9👏8🥰6😱5
ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።
ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ለቀናት ህመም ላይ እንደነበረ የተነገረ ሲሆን ሀምሌ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ጋዜጠኛው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከጋዜጠኝነት እስከ የዜናና ወቅታዊ መረጃ ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።
በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን " #የሚዲያ_ዳሰሳ " በሚል ርእስ ሲያቀርበው በነበረው ትንታኔ በአድማጭ ተመልካቾች ዘንድ ይታወሳል።
ወደ አሜሪካ በመሄድም በPhD ተመርቋል።
ከትምህርቱ ጎን ለጎንም እስከ ህልፈቱ ድረስ TBS በተባለው የትግርኛ ቴሌቪዥን በአማርኛና በትግርኛ ቋንቋዎች ወቅታዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ሲያቀርብ ነበር።
በ1963 ዓ/ም በትግራይ ውቕሮ ከተማ የተወለደው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጋዜጠኝነትን ኮሙዩኒኬሽንን ክፍል በዲግሪ ተመርቋል። በጋዜጠኝነት ሙያ ለረጅም አመታት ሰርቷል።
መረጃው የቲቢኤስ ቴሌቪዥን ነው።
@tikvahethiopia
ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ለቀናት ህመም ላይ እንደነበረ የተነገረ ሲሆን ሀምሌ 2 ቀን 2017 ዓ/ም በአሜሪካ ሲያትል ከተማ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።
ጋዜጠኛው በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከጋዜጠኝነት እስከ የዜናና ወቅታዊ መረጃ ዳይሬክተር በመሆን አገልግሏል።
በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን " #የሚዲያ_ዳሰሳ " በሚል ርእስ ሲያቀርበው በነበረው ትንታኔ በአድማጭ ተመልካቾች ዘንድ ይታወሳል።
ወደ አሜሪካ በመሄድም በPhD ተመርቋል።
ከትምህርቱ ጎን ለጎንም እስከ ህልፈቱ ድረስ TBS በተባለው የትግርኛ ቴሌቪዥን በአማርኛና በትግርኛ ቋንቋዎች ወቅታዊና የመዝናኛ ፕሮግራሞች ሲያቀርብ ነበር።
በ1963 ዓ/ም በትግራይ ውቕሮ ከተማ የተወለደው ጋዜጠኛ ታደሰ ሚዛን ከአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የጋዜጠኝነትን ኮሙዩኒኬሽንን ክፍል በዲግሪ ተመርቋል። በጋዜጠኝነት ሙያ ለረጅም አመታት ሰርቷል።
መረጃው የቲቢኤስ ቴሌቪዥን ነው።
@tikvahethiopia
😭1.19K❤507😢124🕊78💔53🙏47😱10🤔8🥰7👏6😡2
#Houthis
የየመን ሁቲዎች በጉዞ ላይ የነበረ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ከፈጸሙ እና መርከቡ ቀይ ባህር ውስጥ ከሰጠመ በኋላ 6 መርከበኞች መትረፋቸውን እና ቢያንስ 3 ሌሎች ሰዎች መሞታቸውን የአውሮፓ የባህር ኃይል ተልዕኮ አስታወቀ።
የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልበው እና በግሪክ የሚንቀሳቀሰው 'ኤተርኒቲ ሲ' የተባለው የጭነት መርከብ 25 ሠራተኞችን ይዞ እየተጓዘ ነበር።
መርከቡ ሰኞ ዕለት ከትንሽ ጀልባዎች በተተኮሱ የሮኬት ቦምቦች ከተመታ በኋላ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በዚህም የመንቀሳቀስ አቅሙን እንዳጣ የእንግሊዝ የባሕር ንግድ ሥራዎች ኤጀንሲ (UKMTO) ገልጿል።
ጥቃቱ ማክሰኞ ዕለትም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን መርከበኞቹን የማዳን ሥራ የተጀመረው ሌሊት ላይ ነው።
በኢራን የሚደገፉት ሁቲዎች፤ ኤተርኒቲ ሲ ላይ ጥቃት የፈጸሙት ወደ እስራኤል እየተጓዘ ስለነበረ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ቁጥራቸው ያልታወቀ ሠራተኞችንም " ደህንነቱ ወደ የተጠበቀ ቦታ " እንደወሰዱ ተናግረዋል።
በየመን የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሁቲዎች " በሕይወት የተረፉ የቡድን አባላትን አፍነው መውሰዳቸውን " ገልጾ፤ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ አቅርቧል።
የፊሊፒንስ ባለስልጣናት ከቡድኑ አባላት ውስጥ 21 ያህሉ ዜጎቻቸው እንደሆኑ ተናግረዋል።
ከቀሪዎቹ መካከል አንዱ የሩስያ ዜግነት ያለው እንደሆነ እና በጥቃቱ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት እግሩን እንዳጣም ተገልጿል።
ሁቲዎች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህንን ዓይነቱን ጥቃት ሲፈጽሙ ይህ ሁለተኛቸው ነው።
ቡድኑ እሁድ ዕለት 'ማሲክ ሲስ' በተባለ ሌላ የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልብ የግሪክ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።
የእሁዱን ጥቃት የፈጸሙት መርከቡ፤ " በተወረረው የፍልስጤም ግዛት ውስጥ በሚገኙ ወደቦች ላይ የተጣለውን የጉዞ ክልከላ የጣሰ ኩባንያ ንብረት በመሆኑ " ነው ብለዋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
የየመን ሁቲዎች በጉዞ ላይ የነበረ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ከፈጸሙ እና መርከቡ ቀይ ባህር ውስጥ ከሰጠመ በኋላ 6 መርከበኞች መትረፋቸውን እና ቢያንስ 3 ሌሎች ሰዎች መሞታቸውን የአውሮፓ የባህር ኃይል ተልዕኮ አስታወቀ።
የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልበው እና በግሪክ የሚንቀሳቀሰው 'ኤተርኒቲ ሲ' የተባለው የጭነት መርከብ 25 ሠራተኞችን ይዞ እየተጓዘ ነበር።
መርከቡ ሰኞ ዕለት ከትንሽ ጀልባዎች በተተኮሱ የሮኬት ቦምቦች ከተመታ በኋላ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት ሲሆን በዚህም የመንቀሳቀስ አቅሙን እንዳጣ የእንግሊዝ የባሕር ንግድ ሥራዎች ኤጀንሲ (UKMTO) ገልጿል።
ጥቃቱ ማክሰኞ ዕለትም ቀጥሎ የዋለ ሲሆን መርከበኞቹን የማዳን ሥራ የተጀመረው ሌሊት ላይ ነው።
በኢራን የሚደገፉት ሁቲዎች፤ ኤተርኒቲ ሲ ላይ ጥቃት የፈጸሙት ወደ እስራኤል እየተጓዘ ስለነበረ እንደሆነ አስታውቀዋል።
ቁጥራቸው ያልታወቀ ሠራተኞችንም " ደህንነቱ ወደ የተጠበቀ ቦታ " እንደወሰዱ ተናግረዋል።
በየመን የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ሁቲዎች " በሕይወት የተረፉ የቡድን አባላትን አፍነው መውሰዳቸውን " ገልጾ፤ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጥሪ አቅርቧል።
የፊሊፒንስ ባለስልጣናት ከቡድኑ አባላት ውስጥ 21 ያህሉ ዜጎቻቸው እንደሆኑ ተናግረዋል።
ከቀሪዎቹ መካከል አንዱ የሩስያ ዜግነት ያለው እንደሆነ እና በጥቃቱ በደረሰበት ከፍተኛ ጉዳት እግሩን እንዳጣም ተገልጿል።
ሁቲዎች በአንድ ሳምንት ጊዜ ውስጥ ይህንን ዓይነቱን ጥቃት ሲፈጽሙ ይህ ሁለተኛቸው ነው።
ቡድኑ እሁድ ዕለት 'ማሲክ ሲስ' በተባለ ሌላ የላይቤሪያን ባንዲራ የሚያውለበልብ የግሪክ የጭነት መርከብ ላይ ጥቃት ፈጽመዋል።
የእሁዱን ጥቃት የፈጸሙት መርከቡ፤ " በተወረረው የፍልስጤም ግዛት ውስጥ በሚገኙ ወደቦች ላይ የተጣለውን የጉዞ ክልከላ የጣሰ ኩባንያ ንብረት በመሆኑ " ነው ብለዋል።
መረጃው የቢቢሲ ነው።
@tikvahethiopia
❤893😭125👏65😡52🕊37😢14🤔7🙏7🥰5😱4💔3
#USA #VISA
" የቪዛው የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር አጥሯል ፤ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትም ተከልክሏል " - ኤምባሲው
የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታውቋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ኤምባሲው ገልጿል።
በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ " ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ " እንደሚኖረው አስታውቋል።
ኤምባሲው ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውስጥ ይካተታል።
እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።
አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።
በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ትላንት ይፋ አድርጓል። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።
#USEmbassyAddisAbaba #BBCAmharic
@tikvahethiopia
" የቪዛው የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር አጥሯል ፤ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትም ተከልክሏል " - ኤምባሲው
የአሜሪካ ኤምባሲ ለኢትዮጵያውያን የሚሰጠው ቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን አስታውቋል።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ስደተኛ ባልሆኑ የቪዛ አመልካቾች ላይ ባደረገው የፖሊሲ ለውጥ ምክንያት ውሳኔው መተላለፉን ኤምባሲው ገልጿል።
በአዲሱ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፖሊሲ መሠረት፤ " ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለኢትዮጵውያን የሚሰጠው ቪዛ ለአንድ ጊዜ ብቻ የሚያገለግል እና የሦስት ወር ቆይታ " እንደሚኖረው አስታውቋል።
ኤምባሲው ከሐምሌ 1/2017 ዓ.ም. በፊት የተሰጡ ቪዛዎች ባሉበት እንደሚቀጥሉ ገልጿል።
ለንግድ እና ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን የሚያገኙት ቪዛ "B1" እና "B2" በሚለው ምድብ ውስጥ ይካተታል።
እስካሁን በነበረው አሰራር በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገቡ ተጓዦች የሚያገኙት ቪዛ ለሁለት ዓመት የሚቆይ ነበር። በተጨማሪም የቪዛው የቆይታ ጊዜ እስከሚጠናቀቅ ድረስ በተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ እንዲገቡ ያስችል ነበር።
አሁን ይፋ የተደረገው ፖሊሲ የቪዛውን የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ከማሳጠር በተጨማሪ በአንድ ቪዛ ተደጋጋሚ ወደ አገሪቱ መግባትን ከልክሏል።
በአዲሱ ፖሊሲ ቪዛ የሚያገኙ ተጓዦች የቆይታ ጊዜ ባይጠናቀቅም እንኳ ከአሜሪካ ከወጡ በኋላ በዚያው ቪዛ ተመልሰው መግባት አይችሉም።
የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተለያዩ አፍሪካ አገራትን ቪዛ የቆይታ ጊዜን ወደ ሦስት ወራት ማሳጠሩን ትላንት ይፋ አድርጓል። ይህ ውሳኔ ከተላለፈባቸው ሀገራት መካከል ናይጄርያ እና ጋና ይገኙበታል።
#USEmbassyAddisAbaba #BBCAmharic
@tikvahethiopia
❤981😭397😡105🤔60👏37😢36🙏26🕊19😱12🥰11
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል " - አምባሳደር ነብያት ጌታቸው
ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ኢትዮጵያውያና የሌላ አገር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆዩ ቅጣት እንደሚከተላቸው የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ይህን ያሉት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።
በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአሜሪካ መንግስት የቪዛና አገልንሎትና ኢምግሬሽን ጉዳዮችን በሚመለከት አዳዲስ አሰራሮችንና አካሄዶችን ይፋ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዜጎች ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
"በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል" ሲሉ ተናግረዋል።
"ወደፊትም ለትምህርትም ሆነ ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የመጓዝ እድል ያላቸው ዜጎች እነኝህን የተቀመጡ የቪዛ ቆይታ ጊዜዎች ካላከበሩ ለተለያዩ ችግሮች ሊጋለጡ የሚችሉ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ እንደረግ ማሳሰብ እንፈልጋለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ወደ አሜሪካ ለመጓዝ፣ ቪዛ ለማግኘት ለአሜሪካ ኤምባሲ ማመልከቻ የሚያስገቡ ከመንግስትም ሆነ ከግል ተቋማት የሚመነጩ ሰነዶች ትክክል ስለመሆናቸው እያረጋገጡ እንዲሆን አሳስበዋል።
በአጠቃላይ የአሜሪካ መንግስት የቪዛ አገልግሎትን የኢምግሬሽን ጉዳዮችን የሚያወጣቸውን አዳዲስ አሰራሮች በመከታተል ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አምባሳደሩ፣ "ከአሜሪካም ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን" ሲሉም ተናግረዋል።
አምባሳደር ነብያት፣ "ይህ አሰራር የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ያልያዙትን ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ይጨምራል" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ከአሜሪካ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጡ የአሜሪካ ቪዛ የያዙ ኢትዮጵያውያና የሌላ አገር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ከቆዩ ቅጣት እንደሚከተላቸው የኢትዮጵያ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሚኒስቴሩ ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ይህን ያሉት ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው።
በዚህም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአሜሪካ መንግስት የቪዛና አገልንሎትና ኢምግሬሽን ጉዳዮችን በሚመለከት አዳዲስ አሰራሮችንና አካሄዶችን ይፋ እያደረገ መሆኑን ጠቅሰው ለዜጎች ማሳሰቢያ ሰጥተዋል።
"በተማሪነትም ሆነ በቱሪስት ቪዛ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ ዜጎቻችን ከተፈቀደላቸው የቪዛ ቆይታ ጊዜ በላይ በአሜሪካ መቆየት በአሁኑ ወቅት ተቀባይነት የሌለውና ከፍተኛ ተጠያቂነት የሚያስከትል መሆኑን መገንዘብ ያሻል" ሲሉ ተናግረዋል።
"ወደፊትም ለትምህርትም ሆነ ለጉብኝት ወደ አሜሪካ የመጓዝ እድል ያላቸው ዜጎች እነኝህን የተቀመጡ የቪዛ ቆይታ ጊዜዎች ካላከበሩ ለተለያዩ ችግሮች ሊጋለጡ የሚችሉ በመሆኑ ተገቢውን ጥንቃቄ እንደረግ ማሳሰብ እንፈልጋለን" ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ወደ አሜሪካ ለመጓዝ፣ ቪዛ ለማግኘት ለአሜሪካ ኤምባሲ ማመልከቻ የሚያስገቡ ከመንግስትም ሆነ ከግል ተቋማት የሚመነጩ ሰነዶች ትክክል ስለመሆናቸው እያረጋገጡ እንዲሆን አሳስበዋል።
በአጠቃላይ የአሜሪካ መንግስት የቪዛ አገልግሎትን የኢምግሬሽን ጉዳዮችን የሚያወጣቸውን አዳዲስ አሰራሮች በመከታተል ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት አስገንዝበዋል።
አምባሳደሩ፣ "ከአሜሪካም ወደ ኢትዮጵያ ጉዞ የሚያደርጉ የአሜሪካ ፓስፓርት የያዙ ኢትዮጵያውያን፣ የሌሎች ዜግነት ያላቸው ግለሰቦች የኢትዮጵያን ቪዛ ለማግኘት ወደ አገራችን ሲመጡ ከተፈቀደላቸው የቆይታ ጊዜ በላይ በሀገራችን ሕግ መሠረት ቅጣት የሚያስከትል በመሆኑ ተገቢው ጥንቃቄ እንዲደረግ ለማሳሰብ እንወዳለን" ሲሉም ተናግረዋል።
አምባሳደር ነብያት፣ "ይህ አሰራር የትውልድ ኢትዮጵያዊ መታወቂያ ካርድ ያልያዙትን ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ይጨምራል" ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvaEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.31K😡191🤔62👏56😭31🕊27💔19🥰17😢17🙏11😱4