TIKVAH-ETHIOPIA
" አንድ ሃገር ለመብረር ፈቃድ ያስፈልጋል ያንን ፈቃድ ጠይቀን ሲፈቀድልን ነው የምንበረው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ቬትናም የሚያደርገውን የመጀመሪያውን በረራ በዛሬው ዕለት ምሽት ያስጀምራል። አየር መንገዱ አፍሪካን ከ ኤዥያ ጋር ያገናኘው የዛሬ 52 አመት እ.ኤ.አ በ 1973 ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ቻይናዋ ከተማ ሻንጋይ በመብረር እንደነበር የአየር መንገዱ ዋና…
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚያስገነባው ግዙፉ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 2,500 አባወራዎች እንደሚነሱ መገለጹ ይታወሳል።
3,500 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈው አዲሱ የአየር ማረፊያ ስራ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አየር መንገዱ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአሁኑ ሰአት ለ2,500 አባውራዎች መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን እና በመስከረም ወር ለማስረከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ስለ አዲሱ አየር መንገድ እና በሃገር ውስጥ ያሉ መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰራ ስላለው ስራ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው እንደተጠናቀቀ ወደ ተሰራላቸው ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ይዘዋወራሉ ስራቸውንም በአዲስ መልክ ይጀምራሉ።
ቦታው ሲለቀቅልን የግንባታ ስራ እንጀምራለን የአየር መንገዱ ዲዛይንም በብዙ አድቫንስ አድርጓል እየቆራረጥን በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው የመጀመሪያውን ዙር ስራ ህዳር ውስጥ ለመጀመር እቅድ ይዘናል።
የሃገር ውስጥ በረራን ለማስፋት እና የአገልግሎት ጥራቱን ከፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ጥቂት አመታት በርካታ ስራ ሲሰራ ቆይቷል።
ከስራዎቹ መሃል ዛሬ ላይ ያሉን የአውሮፕላን ጣቢያዎች ማሻሻል ነው የአውሮፕላን መንደርደሪያው ጥሩ ካልሆነ እሱን በአዲስ መልክ መስራት።
መንገደኞች የሚስተናገዱባቸው ተርሚናሎችም አንዳንዶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና አሮጌ ፣ ወይም በቆርቆሮ የተሰሩ ነበሩ እነሱን እያፈረስን በዘመናዊ መንገድ እየሰራን ነው ሁሉንም በአንድ ጊዜ ስለማይቻል በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው።
ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ብቻ እንደ ጎዴ እና ጂንካ ያሉ 3 ተርሚናሎችን ሰርተን ስራ ላይ አውለናል።
አገልግሎቱን ለማስፋትም አዳዲስ ኤርፖርቶችን በመስራት ላይ እንገኛለን በአሁኑ ሰአት ስድስት ተርሚናሎች እየተሰሩ ይገኛሉ አንዳንዶቹ ለምረቃ ደርሰዋል።
ለምሳሌ ፦ ያቤሎ መንደርደሪያው አልቋል በሁለት ወር ውስጥ በረራ እምጀምራለን እሱ 23ኛው የሃገር ውስጥ መዳረሻችን ይሆናል ማለት ነው።
ነገሌ ቦረና፣ መቱ ፣ሚዛን አማን እና ደብረ ማርቆስም በመገንባት ላይ ናቸው በሚመጡት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚያስገነባው ግዙፉ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 2,500 አባወራዎች እንደሚነሱ መገለጹ ይታወሳል።
3,500 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈው አዲሱ የአየር ማረፊያ ስራ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አየር መንገዱ አሳውቋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው በአሁኑ ሰአት ለ2,500 አባውራዎች መኖሪያ ቤቶች እየተገነቡ መሆኑን እና በመስከረም ወር ለማስረከብ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ስለ አዲሱ አየር መንገድ እና በሃገር ውስጥ ያሉ መዳረሻዎችን ለማስፋት እየተሰራ ስላለው ስራ በዝርዝር ምን አሉ ?
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው እንደተጠናቀቀ ወደ ተሰራላቸው ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ይዘዋወራሉ ስራቸውንም በአዲስ መልክ ይጀምራሉ።
ቦታው ሲለቀቅልን የግንባታ ስራ እንጀምራለን የአየር መንገዱ ዲዛይንም በብዙ አድቫንስ አድርጓል እየቆራረጥን በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው የመጀመሪያውን ዙር ስራ ህዳር ውስጥ ለመጀመር እቅድ ይዘናል።
የሃገር ውስጥ በረራን ለማስፋት እና የአገልግሎት ጥራቱን ከፍ ለማድረግ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ባለፉት ጥቂት አመታት በርካታ ስራ ሲሰራ ቆይቷል።
ከስራዎቹ መሃል ዛሬ ላይ ያሉን የአውሮፕላን ጣቢያዎች ማሻሻል ነው የአውሮፕላን መንደርደሪያው ጥሩ ካልሆነ እሱን በአዲስ መልክ መስራት።
መንገደኞች የሚስተናገዱባቸው ተርሚናሎችም አንዳንዶቹ ደረጃቸውን ያልጠበቁ እና አሮጌ ፣ ወይም በቆርቆሮ የተሰሩ ነበሩ እነሱን እያፈረስን በዘመናዊ መንገድ እየሰራን ነው ሁሉንም በአንድ ጊዜ ስለማይቻል በቅደም ተከተል ነው የምንሰራው።
ባለፈው አንድ አመት ውስጥ ብቻ እንደ ጎዴ እና ጂንካ ያሉ 3 ተርሚናሎችን ሰርተን ስራ ላይ አውለናል።
አገልግሎቱን ለማስፋትም አዳዲስ ኤርፖርቶችን በመስራት ላይ እንገኛለን በአሁኑ ሰአት ስድስት ተርሚናሎች እየተሰሩ ይገኛሉ አንዳንዶቹ ለምረቃ ደርሰዋል።
ለምሳሌ ፦ ያቤሎ መንደርደሪያው አልቋል በሁለት ወር ውስጥ በረራ እምጀምራለን እሱ 23ኛው የሃገር ውስጥ መዳረሻችን ይሆናል ማለት ነው።
ነገሌ ቦረና፣ መቱ ፣ሚዛን አማን እና ደብረ ማርቆስም በመገንባት ላይ ናቸው በሚመጡት ወራት ውስጥ ይጠናቀቃሉ ተብሎ ይጠበቃል " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤1.36K😡153👏90🥰32😭31🙏28🕊18🤔16😢12💔2
TIKVAH-ETHIOPIA
" ካምፓኒዎቹን መቀመቅ የሚከት እብደት እንዲቆም የሚመለከተው አካል ሃላፊቱን ይወጣ " - አቶ በየነ ምክሩ አሁን ላይ በአዲስ አበባ የሚገኙትና የትእምት (EFFORT) ዋና ስራ አስፈፃሚ መሆናቸውን የሚናገሩት አቶ በየነ መክሩ ' ላዛ ትግርኛ ' ለተባለ የዩቱብ ሚድያ ቃለ መጠይቅ ሰጥተው ነበር። በዚህም " ህገ-ወጥ " ሲሉ የጠሩት የደብረፅን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) ህወሓት በትእምት ካምፓኒዎች ላይ ከፍተኛ…
#EFFORT
" ነባሩ ቦርድ ህጋዊ ነው ፤ በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " የሚል ውሳነ መሰጠቱ ተሰማ።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ታማኝ ምንጮች በላኩት መረጃ ነባሩ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር " ህገ-ወጥ የምክር ጉባኤ አካሂዶ ህገ-ያልተከተሉ አመራሮች መርጦ በተቋሙ ላይ የጀመረው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ይታገድልኝ " ሲል ለክልሉ የፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ተቀባይነት አግኝቷል።
" በስራ ላይ ያለው ህጋዊ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር ነኝ " የሚል አካል ለፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ምን ይመስላል ?
በአቶ ቴድሮስ ሓጎስ የሚመራው የትእምት ባለ አደራ ቦርድ አመራር " በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህገ-ወጥ ነው ፤ በጉባኤው የተመረጠ በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ በተቋሙ ላይ እያካሄደ የሚገኘው እንቅስቃሴም ህገ-ወጥ መሆኑ ተጣርቶ ይታገድልኝ " ሲል ለፍትህ ቢሮ አቤታቱ አቅርቧል።
ሦስት አጣሪ አባላት ያሉት ኮሚቴ በማቋቋም ላለፉት 10 ቀናት የቀረበለት አቤቱታ ሲመረምር የቆየው የፍትህ ቢሮ " በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ ህጋዊ አይደለም " በማለት በትእምት ላይ የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንዲያቆም የእግድ ውሳኔ ሰጥቷል።
" የትእምት ምክር ቤት ባለፈው የካቲት 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ መርጦኛል " በሚል በመንቀሳቀስ ላይ ያለውና የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ በየነ መክሩ ህጋዊ ርክክብ ባላካሄዱበት ሁኔታ በላያቸው ላይ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር በሚድያዎች እስከማስነገር የደረሰው በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራው አካል " ህጋዊ አይደለህም " የሚል የፍትህ ቢሮ ውሳኔ ያከብር ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለፈው መጋቢት 2017 ዓ.ም በተፈጠረው የፓለቲካ ቀውስ ምክንያት የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከትግራይ መውጣታቸው ተከትሎ የትእምት ኢንቨስትመንት ዋና ስራ አስፈፃሚና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ በየነ መክሩና አቶ ቴድሮስ ሓጎስ ከክልሉ ውጪ ናቸው።
የትእምት ዋና ስራ ስፈፃሚ በየነ መክሩ በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላዛ ትግርኛ ለተባለው ሚድያ ከአዲስ አበባ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው " ማለታቸው ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
" ነባሩ ቦርድ ህጋዊ ነው ፤ በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህጋዊ አይደለም " የሚል ውሳነ መሰጠቱ ተሰማ።
የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ታማኝ ምንጮች በላኩት መረጃ ነባሩ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር " ህገ-ወጥ የምክር ጉባኤ አካሂዶ ህገ-ያልተከተሉ አመራሮች መርጦ በተቋሙ ላይ የጀመረው ህገ-ወጥ እንቅስቃሴ ይታገድልኝ " ሲል ለክልሉ የፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ተቀባይነት አግኝቷል።
" በስራ ላይ ያለው ህጋዊ የትእምት ኢንቨስትመንት አመራር ነኝ " የሚል አካል ለፍትህ ቢሮ ያቀረበው ክስ ምን ይመስላል ?
በአቶ ቴድሮስ ሓጎስ የሚመራው የትእምት ባለ አደራ ቦርድ አመራር " በትእምት ስም የተካሄደው የምክር ቤት ጉባኤ ህገ-ወጥ ነው ፤ በጉባኤው የተመረጠ በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ በተቋሙ ላይ እያካሄደ የሚገኘው እንቅስቃሴም ህገ-ወጥ መሆኑ ተጣርቶ ይታገድልኝ " ሲል ለፍትህ ቢሮ አቤታቱ አቅርቧል።
ሦስት አጣሪ አባላት ያሉት ኮሚቴ በማቋቋም ላለፉት 10 ቀናት የቀረበለት አቤቱታ ሲመረምር የቆየው የፍትህ ቢሮ " በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራ ቦርድ ህጋዊ አይደለም " በማለት በትእምት ላይ የሚያደርገው እንቅስቃሴ እንዲያቆም የእግድ ውሳኔ ሰጥቷል።
" የትእምት ምክር ቤት ባለፈው የካቲት 2017 ዓ.ም ባካሄደው ጉባኤ መርጦኛል " በሚል በመንቀሳቀስ ላይ ያለውና የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ በየነ መክሩ ህጋዊ ርክክብ ባላካሄዱበት ሁኔታ በላያቸው ላይ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ለመቅጠር በሚድያዎች እስከማስነገር የደረሰው በኣብራሃም ተከስተ (ዶ/ር) የሚመራው አካል " ህጋዊ አይደለህም " የሚል የፍትህ ቢሮ ውሳኔ ያከብር ይሆን ? የብዙዎች ጥያቄ ነው።
ባለፈው መጋቢት 2017 ዓ.ም በተፈጠረው የፓለቲካ ቀውስ ምክንያት የቀድሞ ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ከትግራይ መውጣታቸው ተከትሎ የትእምት ኢንቨስትመንት ዋና ስራ አስፈፃሚና የባለ አደራ ቦርድ ሰብሳቢ አቶ በየነ መክሩና አቶ ቴድሮስ ሓጎስ ከክልሉ ውጪ ናቸው።
የትእምት ዋና ስራ ስፈፃሚ በየነ መክሩ በያዝነው ሳምንት መጀመሪያ ላዛ ትግርኛ ለተባለው ሚድያ ከአዲስ አበባ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ " ህገ-ወጥ ቡድኑ በሃይል ካስቀመጣቸው አመራሮች የተደረገ ርክክብ የለም ፤ ዋና ስራ አስፈፃሚና ቦርድ የነበረው ነው ያለው " ማለታቸው ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
@tikvahethiopia
❤262🕊12😡12🥰6👏5🤔5😭1
#ዙሪያ
ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ ያስችላቸዋል የተባለ ሲስተም ይፋ ተደርጓል።
ኢትዮ ቴሌኮም፣ ከዳሽን ባንክ እና ኤታ ሶሉሽንስ በአጋርነት በጋራ በመሆን የቀረበው "ዙሪያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲስተም በአስመጪና ላኪ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና ችርቻሮ ንግድ ዘርፍ ለተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን ያግዛቸዋል ተብሏል።
"ዙሪያ" የኢ.አር.ፒ (ERP)፣ የፒ.ኦ.ኤስ (POS) እና ካሽ ሬጂስተር (Cash Register) አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለመስጠት የሚያስችል የቢዝነስ አውቶሜሽ ሶሉሽን የያዘ ሲስተም ነው፡፡
መተግበሪያው የተለያየ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ የሚያስችል ነው።
"ዙሪያ" ሁሉንም የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ካርዶች መቀበል እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና እንደተሰጠው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ተገልጿል።
ይህ ሲስተም የሂሳብ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ነጋዴዎች የሚያንቀሳቅሱትን ሃብት ለማስተዳደር እና ማንኛውንም የክፍያ መረጃዎች በአንድ ያካተተ ደረሰኝ ለማግኘት ያስችላል ነው የተባለው፡፡
አገልግሎቱን ለማቅረብ ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌክላውድ (TeleCloud) መሠረተ ልማት በማቅረብ የተሳተፈ ሲሆን ለዚህ አገልግሎት የሚውለውን ማሽን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በማመቻቸት ዳሽን ባንክ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ ያስችላቸዋል የተባለ ሲስተም ይፋ ተደርጓል።
ኢትዮ ቴሌኮም፣ ከዳሽን ባንክ እና ኤታ ሶሉሽንስ በአጋርነት በጋራ በመሆን የቀረበው "ዙሪያ" የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲስተም በአስመጪና ላኪ፣ በማኑፋክቸሪንግ እና ችርቻሮ ንግድ ዘርፍ ለተሰማሩ ድርጅቶችና ተቋማት የአገልግሎት አሰጣጣቸውን ለማዘመን ያግዛቸዋል ተብሏል።
"ዙሪያ" የኢ.አር.ፒ (ERP)፣ የፒ.ኦ.ኤስ (POS) እና ካሽ ሬጂስተር (Cash Register) አገልግሎቶችን በአንድ ላይ ለመስጠት የሚያስችል የቢዝነስ አውቶሜሽ ሶሉሽን የያዘ ሲስተም ነው፡፡
መተግበሪያው የተለያየ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዜጎች ይዘዋቸው የምናያቸውን በርካታ ፖስ ማሽኖች በማስቀረት ወደ አንድ የተቀናጀ ስርአት እንዲገቡ የሚያስችል ነው።
"ዙሪያ" ሁሉንም የሀገር ውስጥና አለም አቀፍ ካርዶች መቀበል እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ኮሚሽን ዕውቅና እንደተሰጠው ይፋ በማድረጊያ ስነ ስርአቱ ላይ ተገልጿል።
ይህ ሲስተም የሂሳብ ምዝገባ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ነጋዴዎች የሚያንቀሳቅሱትን ሃብት ለማስተዳደር እና ማንኛውንም የክፍያ መረጃዎች በአንድ ያካተተ ደረሰኝ ለማግኘት ያስችላል ነው የተባለው፡፡
አገልግሎቱን ለማቅረብ ኢትዮ ቴሌኮም የቴሌክላውድ (TeleCloud) መሠረተ ልማት በማቅረብ የተሳተፈ ሲሆን ለዚህ አገልግሎት የሚውለውን ማሽን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት የውጭ ምንዛሬ አቅርቦት በማመቻቸት ዳሽን ባንክ አስተዋጽኦ ማድረጉን ተነግሯል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤540👏38😡38🕊32😭17🤔10🙏8🥰7😱6😢4
TIKVAH-ETHIOPIA
" የግፍ አገዳደል ነው የተፈጸመው ፤ የሟቹን ወንድም ቤትም ታጣቂዎቹ አቃጥለውታል ፤ የአካባቢው ነዋሪም ወደ አጎራባች ቦታዎች ተፈናቅሏል " - የሟች የቅርብ ሰው በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን ሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይና የሰባት ልጆች አባት ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ በ "ሸኔ" በታጣቂዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ። ግድያው አሰቃቂ…
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ሰዎች ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " - የወረዳው ቤተ ክህነት
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ የ"ሸኔ" ታጣቂ ቡድን በአንድ ቤተሰብ አባላት የግድያ እና እገታ ጥቃት መፈጸሙን የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ የሆነውን ሲያስረዳ፣ " ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ትላንት 3 ሰዓት ከሩብ ላይ ነው ጥቃቱ የተፈጸመው ዛሬ የሟች አባትና ልጅ ቀብር ተፈጽሟል። ካህንና ምዕመን ወንድማማቾች ታግተው ተወስደዋል፤ የተወሰዱትም የሟች ወንድም ናቸው " ሲል ተናግሯል።
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " ብሎ፣ ታጋች ካህን የሰኮራ ኪዳነ ምህረት አገልጋይ መሆናቸውን ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ፣ " ህዝቡ ሁሌም በልቅሶ ነው፤ ሁሌ መገደል ነው ማን ይደርስለታል " ሲልም በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚፈጸምን ጥቃት አስከፊነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
" ታጣቂ ቡድኑ 3 ሰዓት ይመጣል፤ ምሽት 11 ሰዓት ይመለሳል፤ በሌሊትም የፈለገውን ይፈጸሰማል" ብሎ " መንግስት የህዝቡ ድምጽ እንዲሰማና ህዝቡን እንዲጠብቅ አሳስቧል።
" መንግስት ቢደርስ ጥሩ ነው በወረዳው ከ2014 ዓ/ም ጀሞሮ ያለማቋረጥ ነው ግድያ እየተፈጸመ ያለው። ህዝቡ እየተፈናቀለ ነው፤ ተፈናቅሎም የሚገባበት የለም። ይህ የሆነው መንግስት ሃይ ባለማለቱ ነው " ሲልም ወቅሷል።
እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ በበዞኑ ሶኮራ ቀበሌ ሐምሌ 4/2017 ዓ/ም አባትና ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ገልጾ፣ " የሟች ወንድሞችና የአጥቢያው አገልጋይ ካህን ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወገኔ ጌታነህ ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን፣ የደረሱበት አልታወቀም " ሲል አስታውቋል።
" ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል በዞኑ በሁሉም አካባቢ በሚባል ደረጃ እየተንቀሳቀሰ ከፍተኛ ሰቆቃ የሚፈጽም ሲሆን፣ ከፌዴራሉም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በኩል ነገሩን ከማድበስበስ ያለፈ እስካሁን ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስዱ አልታየም። ይህም ለሌላ ጥርጣሬ የሚጋብዝ ነው " ብሏል።
" ፓርቲያችን ግድያውን በጽኑ ያወግዛል፤ ታፍነው የተወሰዱ ካህንና ወንድማቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ይጠይቃል " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በኦሮሚያ ክልል አርሲ ዞን ጀጁ ወረዳ ሶኮራ ቀበሌ የ"ሸኔ" ታጣቂ ቡድን በአንድ ቤተሰብ አባላት የግድያ እና እገታ ጥቃት መፈጸሙን የወረዳው ቤተ ክህነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ የሆነውን ሲያስረዳ፣ " ሁለት ሰዎች ተገድለዋል፤ ትላንት 3 ሰዓት ከሩብ ላይ ነው ጥቃቱ የተፈጸመው ዛሬ የሟች አባትና ልጅ ቀብር ተፈጽሟል። ካህንና ምዕመን ወንድማማቾች ታግተው ተወስደዋል፤ የተወሰዱትም የሟች ወንድም ናቸው " ሲል ተናግሯል።
" አንድ ካህንና ወንድሙ፤ ሁለት ናቸው ታግተው የተወሰዱት። አንድ አባት እስከ ልጃቸው ተገድለዋል " ብሎ፣ ታጋች ካህን የሰኮራ ኪዳነ ምህረት አገልጋይ መሆናቸውን ገልጿል።
ቤተ ክህነቱ፣ " ህዝቡ ሁሌም በልቅሶ ነው፤ ሁሌ መገደል ነው ማን ይደርስለታል " ሲልም በአካባቢው በተደጋጋሚ የሚፈጸምን ጥቃት አስከፊነት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድቷል።
" ታጣቂ ቡድኑ 3 ሰዓት ይመጣል፤ ምሽት 11 ሰዓት ይመለሳል፤ በሌሊትም የፈለገውን ይፈጸሰማል" ብሎ " መንግስት የህዝቡ ድምጽ እንዲሰማና ህዝቡን እንዲጠብቅ አሳስቧል።
" መንግስት ቢደርስ ጥሩ ነው በወረዳው ከ2014 ዓ/ም ጀሞሮ ያለማቋረጥ ነው ግድያ እየተፈጸመ ያለው። ህዝቡ እየተፈናቀለ ነው፤ ተፈናቅሎም የሚገባበት የለም። ይህ የሆነው መንግስት ሃይ ባለማለቱ ነው " ሲልም ወቅሷል።
እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ፣ በበዞኑ ሶኮራ ቀበሌ ሐምሌ 4/2017 ዓ/ም አባትና ልጅ በአሰቃቂ ሁኔታ እንደተገደሉ ገልጾ፣ " የሟች ወንድሞችና የአጥቢያው አገልጋይ ካህን ቄስ አድማሱ ጌታነህና ወገኔ ጌታነህ ታፍነው የተወሰዱ ሲሆን፣ የደረሱበት አልታወቀም " ሲል አስታውቋል።
" ራሱን የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ብሎ የሚጠራው ኃይል በዞኑ በሁሉም አካባቢ በሚባል ደረጃ እየተንቀሳቀሰ ከፍተኛ ሰቆቃ የሚፈጽም ሲሆን፣ ከፌዴራሉም ሆነ ከክልሉ መንግሥት በኩል ነገሩን ከማድበስበስ ያለፈ እስካሁን ይህ ነው የሚባል እርምጃ ሲወስዱ አልታየም። ይህም ለሌላ ጥርጣሬ የሚጋብዝ ነው " ብሏል።
" ፓርቲያችን ግድያውን በጽኑ ያወግዛል፤ ታፍነው የተወሰዱ ካህንና ወንድማቸው ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲለቀቁ ይጠይቃል " ሲል ገልጿል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😡281❤151😭104😢12🕊12🙏4👏3💔2🤔1
" ባለቤቴንና አምስት ልጆቼን ነው ያጣሁት " - ተጎጂ አባት
➡️ " ጥቃቱን ያደረሱት ጽንፈኛ የሚባሉ በዚሁ በወሰን አከባቢ ሸምቀው ያሉ ታጣቂዎች ናቸው ! " - የአካባቢው ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ቆንዳላ ቀበሌ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 14 ሰዎች ተገደሉ።
ጥቃቱ ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ሃምሌ 03 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት ነው የተፈጸመው።
የታጠቁ አካላት በመደዳው አንድ መንደር ላይ አነጣጥረው የዘፈቀደ ጥቃት ማድረሳቸው ነው የተገለጸው፡፡
ብርሃኑ ሸምሰዲን የተባሉ ተጎጂ በጥቃቱ ሙሉ የቤተሰቦቻቸውን አባል አጥተዋል፡፡
ባለቤታቸውን እና አምስት ልጆቻቸውን ድንገት ከቤት በወጡበት አጋጣሚ አልቀው ማግኘታቸውን ተናግረዋል። አደጋው ዱብ እዳ እንደሆነባቸው በደከመና በሚቆራረጥ ድምፅ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ተናግረዋል።
" ምሽት አንድ ሰዓት ተኩል አከባቢ ነው ስድስት የቤተሰቤ አባላት በሙሉ የጨረሱብኝ፡፡ የሁለት ዓመት ጨቅላ ህጻንና ባለቤቴን ጨምሮ ሶስት ወንድ ልጆቼን እና ሁለት ሴት ልጆቼ አልቀውብኛል " ብለዋል።
" የአምስት ዓመት፣ የ11 እና 12 ዓመት እንዲሁም የ14 ዓመት እድሜ ልጆች ናቸው ያለቁብኝ፡፡ ገዳዮች ከኔ የተለየ ቂም የላቸውም፤ #ጽንፈኛ የሚባሉ በአከባቢያችን የደቡብ ክልል አዋሳኝ አከባቢ ሸምቀው ያሉ መሆናቸው ብቻ ነው የተነገረን " ሲሉ አክለዋል።
" በመንደራችን በመደደው በተወሰደብን ድንገተኛው ጥቃት እንደ እኔ ሙሉ ቤተሰቦቻቸው አልቆባቸው ባይጎዱም እንደ እኔ ሁሉ ዉዶቻቸውን ያጡ አራት ቤቶች ግድም ጎረቤቶቼም አሉ " ብለዋል።
ጥቃቱ ድንገተኛና ምንም በማያውቁ ንጹሃን ላይ ያነጣጠረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ይህ ሁሉ አደጋ በመላው ቤተሰቦቻቸው ላይ የደረሰው እሳቸው ድንገት ለጉዳይ ወደ ጎረቤት ብቅ ባሉበት ሰዓት መሆኑን ገልጸዋል።
" ጥቃቱ የተፈጸመው ሁሉም በማታው ቤቱ ቁጭ ባለበት ሰዓት ነው፡፡ አንዳንዶቹ እራት እየበሉ ሌሎችም ቴሌቪዢን እየተመለከቱ ባሉበት ነው ድንገት ገብተውባቸው የጥይት እሩምታ በማዝነብ ህጻናት እና ሴት ሳይሉ ያገኙትን ሁሉ የገደሉዋቸው " ብለዋል።
" የተኩሱን ድምጽ ሰምቼ ከነበርኩበት ጎረቤት ቤት ልወጣ ስል በግድ አስቀመጡኝ፡፡ በኋላ ሮጬ ቤቴ ስደርስ ግን አንድም የተረፈልኝ የለም፤ ስድስት የቤተሰቤ አባላት በሙሉ አልቀው ጠበቁኝ " ሲሉ ሀዘናቸው መሪር መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ጥቃቱ የተፈጸመበት ቦታ የምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጋር በምታዋስን ቆንዳላ ቀበሌ ዳርጌ ከተማ ነው ያሉት የአይን እማኝየአከባቢው ነዋሪ፤ በተለይ ይህ ጥቃት የተፈጸመው በከተማዋ ዳር ላይ በሚገኙ መንደሮች ነው ብለዋል፡፡
ለደህንነታቸው ስባል ስማቸውን ሳይገልጹ አስተያየታቸውን ብቻ ያጋሩን እኚህ አስተያየት ሰጪ፤ " በሰዓቱ ሁላችንም በዚያችው ከተማ ውስጥ ነበርን፡፡ ጥቃቱ በደረሰበት በዚያ አከባቢ የከባባድ መሳሪያዎች ድምጽ ጨምር ስንሰማ ስለነበር ተኩሱ ሲቆም 2፡30 አከባቢ ወደ ቦታው ስናመራ ብዙ አስከሬን አገኘን " ብለዋል።
" የተጎዱትን ወደ ሆስፒታል ብንወስዳቸውም ሆስፒታልም ደርሰው ያለፉብን አሉ፡፡ አሁን ባጠቃላይ 14 ሰዎች ስሞቱ ሶስት ሰዎች በከባድ ሁኔታ ሆስፒታል እየታከሙ ይገኛሉ " ሲሉ ገልጸዋል።
" ሰላማዊ ሰዎች ላይ ነው በር እየከፈቱ እየገቡ የአንድ ዓመት ህጻን ጨምሮ አዛውንትና ሴት ሳይሉ ያገኙት ሁሉ ላይ ጥይት አርከፍክፈው የወጡት " ብለዋል፡፡
በወቅቱ የከተማዋን ጸጥታ የሚያስጠብቁ የፀጥታ አካላት በቦታው እንደሌሉ የገለጹት አስተያየት ሰጪው ነዋሪ ጥቃቱን ያደረሱ ታጣቂዎች ወደ 40 የሚጠጉ ናቸውም ብለዋል፡፡
" የፀጥታ መዋቅር በሰዓቱ ወደ ሌላ ስፍራ ተንቀሳቅሶ ነበር ነው የሚባለው፡፡ ይህን ክፍተት በመጠቀም ይመስላል ታጣቂዎቹ ዘልቀው ገብተው እንዲህ ያለ ዘግናኝ ጥቃት ያደረሱት፡፡ ጥቃቱን ያደረሱት ጽንፈኛ የሚባሉ በዚሁ በወሰን አከባቢ ሸምቀው ያሉ ሲሆን ከተማ ውስጥ ገብተው ጥቃቱን ያደረሱም በቁጥር ከ35 እስከ 40 እንደሚሆኑ ከጥቃቱ የተረፉ ነግረውናል፡፡ መሰል ድርጊቶች በዚህ ቀበሌና አከባቢው ተደጋግሞ የተፈጸመ ሲሆን አሁንም ልቆም አልቻለም " ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት ገልጸዋል፡፡
አከባቢው አሁን ተረጋግቶ እንደሆነ የተጠየቁት አስተያየት ሰጪው ነዋሪ፤ " ለአሁኑማ ምን መረጋጋት አለ፤ ሰው የሞተበትን ቀብሮ ሀዘን ተቀምጠዋል፡፡ የህግ አካላትም መጥተው ' ድርጊቱን የፈጸመውን አካል እያደንን ነው ' ብለዋል " ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
➡️ " ጥቃቱን ያደረሱት ጽንፈኛ የሚባሉ በዚሁ በወሰን አከባቢ ሸምቀው ያሉ ታጣቂዎች ናቸው ! " - የአካባቢው ነዋሪ
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳ ቆንዳላ ቀበሌ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት ቢያንስ 14 ሰዎች ተገደሉ።
ጥቃቱ ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ሃምሌ 03 ቀን 2017 ዓ.ም. ምሽት ነው የተፈጸመው።
የታጠቁ አካላት በመደዳው አንድ መንደር ላይ አነጣጥረው የዘፈቀደ ጥቃት ማድረሳቸው ነው የተገለጸው፡፡
ብርሃኑ ሸምሰዲን የተባሉ ተጎጂ በጥቃቱ ሙሉ የቤተሰቦቻቸውን አባል አጥተዋል፡፡
ባለቤታቸውን እና አምስት ልጆቻቸውን ድንገት ከቤት በወጡበት አጋጣሚ አልቀው ማግኘታቸውን ተናግረዋል። አደጋው ዱብ እዳ እንደሆነባቸው በደከመና በሚቆራረጥ ድምፅ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ተናግረዋል።
" ምሽት አንድ ሰዓት ተኩል አከባቢ ነው ስድስት የቤተሰቤ አባላት በሙሉ የጨረሱብኝ፡፡ የሁለት ዓመት ጨቅላ ህጻንና ባለቤቴን ጨምሮ ሶስት ወንድ ልጆቼን እና ሁለት ሴት ልጆቼ አልቀውብኛል " ብለዋል።
" የአምስት ዓመት፣ የ11 እና 12 ዓመት እንዲሁም የ14 ዓመት እድሜ ልጆች ናቸው ያለቁብኝ፡፡ ገዳዮች ከኔ የተለየ ቂም የላቸውም፤ #ጽንፈኛ የሚባሉ በአከባቢያችን የደቡብ ክልል አዋሳኝ አከባቢ ሸምቀው ያሉ መሆናቸው ብቻ ነው የተነገረን " ሲሉ አክለዋል።
" በመንደራችን በመደደው በተወሰደብን ድንገተኛው ጥቃት እንደ እኔ ሙሉ ቤተሰቦቻቸው አልቆባቸው ባይጎዱም እንደ እኔ ሁሉ ዉዶቻቸውን ያጡ አራት ቤቶች ግድም ጎረቤቶቼም አሉ " ብለዋል።
ጥቃቱ ድንገተኛና ምንም በማያውቁ ንጹሃን ላይ ያነጣጠረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ይህ ሁሉ አደጋ በመላው ቤተሰቦቻቸው ላይ የደረሰው እሳቸው ድንገት ለጉዳይ ወደ ጎረቤት ብቅ ባሉበት ሰዓት መሆኑን ገልጸዋል።
" ጥቃቱ የተፈጸመው ሁሉም በማታው ቤቱ ቁጭ ባለበት ሰዓት ነው፡፡ አንዳንዶቹ እራት እየበሉ ሌሎችም ቴሌቪዢን እየተመለከቱ ባሉበት ነው ድንገት ገብተውባቸው የጥይት እሩምታ በማዝነብ ህጻናት እና ሴት ሳይሉ ያገኙትን ሁሉ የገደሉዋቸው " ብለዋል።
" የተኩሱን ድምጽ ሰምቼ ከነበርኩበት ጎረቤት ቤት ልወጣ ስል በግድ አስቀመጡኝ፡፡ በኋላ ሮጬ ቤቴ ስደርስ ግን አንድም የተረፈልኝ የለም፤ ስድስት የቤተሰቤ አባላት በሙሉ አልቀው ጠበቁኝ " ሲሉ ሀዘናቸው መሪር መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
ጥቃቱ የተፈጸመበት ቦታ የምዕራብ ሸዋ ዞን ኖኖ ወረዳን ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ጋር በምታዋስን ቆንዳላ ቀበሌ ዳርጌ ከተማ ነው ያሉት የአይን እማኝየአከባቢው ነዋሪ፤ በተለይ ይህ ጥቃት የተፈጸመው በከተማዋ ዳር ላይ በሚገኙ መንደሮች ነው ብለዋል፡፡
ለደህንነታቸው ስባል ስማቸውን ሳይገልጹ አስተያየታቸውን ብቻ ያጋሩን እኚህ አስተያየት ሰጪ፤ " በሰዓቱ ሁላችንም በዚያችው ከተማ ውስጥ ነበርን፡፡ ጥቃቱ በደረሰበት በዚያ አከባቢ የከባባድ መሳሪያዎች ድምጽ ጨምር ስንሰማ ስለነበር ተኩሱ ሲቆም 2፡30 አከባቢ ወደ ቦታው ስናመራ ብዙ አስከሬን አገኘን " ብለዋል።
" የተጎዱትን ወደ ሆስፒታል ብንወስዳቸውም ሆስፒታልም ደርሰው ያለፉብን አሉ፡፡ አሁን ባጠቃላይ 14 ሰዎች ስሞቱ ሶስት ሰዎች በከባድ ሁኔታ ሆስፒታል እየታከሙ ይገኛሉ " ሲሉ ገልጸዋል።
" ሰላማዊ ሰዎች ላይ ነው በር እየከፈቱ እየገቡ የአንድ ዓመት ህጻን ጨምሮ አዛውንትና ሴት ሳይሉ ያገኙት ሁሉ ላይ ጥይት አርከፍክፈው የወጡት " ብለዋል፡፡
በወቅቱ የከተማዋን ጸጥታ የሚያስጠብቁ የፀጥታ አካላት በቦታው እንደሌሉ የገለጹት አስተያየት ሰጪው ነዋሪ ጥቃቱን ያደረሱ ታጣቂዎች ወደ 40 የሚጠጉ ናቸውም ብለዋል፡፡
" የፀጥታ መዋቅር በሰዓቱ ወደ ሌላ ስፍራ ተንቀሳቅሶ ነበር ነው የሚባለው፡፡ ይህን ክፍተት በመጠቀም ይመስላል ታጣቂዎቹ ዘልቀው ገብተው እንዲህ ያለ ዘግናኝ ጥቃት ያደረሱት፡፡ ጥቃቱን ያደረሱት ጽንፈኛ የሚባሉ በዚሁ በወሰን አከባቢ ሸምቀው ያሉ ሲሆን ከተማ ውስጥ ገብተው ጥቃቱን ያደረሱም በቁጥር ከ35 እስከ 40 እንደሚሆኑ ከጥቃቱ የተረፉ ነግረውናል፡፡ መሰል ድርጊቶች በዚህ ቀበሌና አከባቢው ተደጋግሞ የተፈጸመ ሲሆን አሁንም ልቆም አልቻለም " ሲሉ የችግሩን አሳሳቢነት ገልጸዋል፡፡
አከባቢው አሁን ተረጋግቶ እንደሆነ የተጠየቁት አስተያየት ሰጪው ነዋሪ፤ " ለአሁኑማ ምን መረጋጋት አለ፤ ሰው የሞተበትን ቀብሮ ሀዘን ተቀምጠዋል፡፡ የህግ አካላትም መጥተው ' ድርጊቱን የፈጸመውን አካል እያደንን ነው ' ብለዋል " ሲሉ ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።
መረጃው የዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ነው።
@tikvahethiopia
😭427❤216😡43💔20🕊6👏3🤔3🙏3🥰2
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጥቆማ (ለሚመለከተው አካል - አዲስ አበባ) " በሰውና መኪና ላይ ወድቆ ጉዳት እንዳይደርስ መፍትሄ ይፈለግለት ! " " ይህ በቪድዮው ላይ የምትመለከቱት የመብራት ኮንክሪት ፖል ታቹ ተበልቶ አልቆ ለመውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከጎኑ ትራንስፎርመርንም አለ። ቦታው ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር ነው ሲሆን ብዙ ሰው የሚመላለስበት…
#Update
አ/አ ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር የመብራት ኮንክሪት ፖል ለመውደቅ ጫፍ ላይ መድረሱን በመጠቆም መፍትሔ ይፈለግለት ሲሉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች መጠየቃቸው ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በደረሰው መረጃ መሰረት ይህንን ፖል የመቀየር ሥራ በምሽት እየተሰራ ይገኛል።
" ባለሞያዎቻችን አሁንም እዛው ሳይት ናቸው " ሲል ጥገናው ምሽቱን እየተከናወነ መሆኑን የገለጸልን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፥ ፖሉ ተበልቶ ሳይሆን በመኪና ተገጭቶ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር መረጃውን አጋርቶናል።
@eeuethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
አ/አ ከጋርመንት ወደ ጀሞ አንድ ሲኬድ መብራት ተሻግሮ (ቫርኔሮ የመኖሪያ መንደር አካባቢ) ዘመን ማደያ ጋር የመብራት ኮንክሪት ፖል ለመውደቅ ጫፍ ላይ መድረሱን በመጠቆም መፍትሔ ይፈለግለት ሲሉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦች መጠየቃቸው ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በደረሰው መረጃ መሰረት ይህንን ፖል የመቀየር ሥራ በምሽት እየተሰራ ይገኛል።
" ባለሞያዎቻችን አሁንም እዛው ሳይት ናቸው " ሲል ጥገናው ምሽቱን እየተከናወነ መሆኑን የገለጸልን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ፥ ፖሉ ተበልቶ ሳይሆን በመኪና ተገጭቶ ጉዳት ደርሶበት እንደነበር መረጃውን አጋርቶናል።
@eeuethiopia
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
2❤714👏429🙏66🤔15🕊10😢7🥰6😭6😡5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ሲዳማ ቡና ስፖርት ክለብ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴን ውሳኔ " ተገቢና ህግን ያልተከተለ ውሳኔ " ሲል ተቃወመ። የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፈዴሬሽን የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ዋንጫ ከሲዳማ ቡና ተነጥቆ ለወላይታ ዲቻ እንዲመለስ ሲል ውሳኔ አሳልፏል። ይህ ተከትሎ የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ቦርድ ውሳኔውን " ተገቢነት የለሌው ውሳኔ ነው። ውሳኔው እጅግ አሳዝኖናል…
" ቅሬታችንን ለዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት አስገብተናል " - የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ
የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ከኢትዮጵያ ዋንጫ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያስተላለፈዉን ዉሳኔ በመቃወም ለዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (CAS) የይግባኝ ደብዳቤ ማስገባቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ክለቡ ቅሬታዉን በየደረጃ ለፌዴሬሽኑም አስገብቶ ምላሽ ባለማግኘቱ ወደ ስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት ማለፉን የገልጿል።
ሲዳማ ቡና ከወላይታ ዲቻ ጋር ባደረጉት የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጫወታ የሲዳማ እግር ኳስ ክለብ 2ለ1 አሸንፎ ዋንጫዉን ቢያነሳም " ያለ አግባብ ተጫዋቾችን አሰልፏል " በሚል ፌዴሬሽኑ ቡድኑ የወሰደዉን ዋንጫ ለወላይታ ዲቻ ተመላሽ እንዲያደርግ የሚል ዉሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
የሲዳማ ቡና እግር ኳስ ክለብ ከኢትዮጵያ ዋንጫ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያስተላለፈዉን ዉሳኔ በመቃወም ለዓለም አቀፉ የስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት (CAS) የይግባኝ ደብዳቤ ማስገባቱን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቋል።
ክለቡ ቅሬታዉን በየደረጃ ለፌዴሬሽኑም አስገብቶ ምላሽ ባለማግኘቱ ወደ ስፖርት ገላጋይ ፍርድ ቤት ማለፉን የገልጿል።
ሲዳማ ቡና ከወላይታ ዲቻ ጋር ባደረጉት የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍፃሜ ጫወታ የሲዳማ እግር ኳስ ክለብ 2ለ1 አሸንፎ ዋንጫዉን ቢያነሳም " ያለ አግባብ ተጫዋቾችን አሰልፏል " በሚል ፌዴሬሽኑ ቡድኑ የወሰደዉን ዋንጫ ለወላይታ ዲቻ ተመላሽ እንዲያደርግ የሚል ዉሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
❤206🤔49🙏16👏13😢8😭7😡4🥰2💔2😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
" አካባቢው ላይ ያሉ ገበሬዎች ተነስተው የሚሰፍሩበት ቦታ ግንባታ በሰፊው እየተከናወነ ነው መስከረም ውስጥ ለማጠናቀቅ እየሰራን ነው " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቢሾፍቱ አቡሴራ አካባቢ አዲስ ለሚያስገነባው ግዙፉ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ 2,500 አባወራዎች እንደሚነሱ መገለጹ ይታወሳል። 3,500 ሔክታር መሬት ላይ የሚያርፈው አዲሱ የአየር ማረፊያ ስራ የቅድመ…
" በፈርንጆቹ 2026 ሁለት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ትናንሽ አውሮፕላኖች እናስመጣለን "-የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያዊ አየር መንገድ መጋቢት 17/2017 ዓም ላይ አርቸር አቪዬሽን ከተሰኘ አለም አቀፍ ተቋም ጋር ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አርቸር አቪዬሽን በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ለማዋል ሲሆን በመኪና ከ60-90 ደቂቃ የሚወስድ ጉዞን ወደ 10 ደቂቃ ዝቅ የሚያደርግ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር።
የዚህ ስምምነት ትግበራ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ጥያቄ አቅርቧል።
ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰጡት ምላሽ " በፈርንጂዎቹ 2026 ሁለት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ትናንሽ አውሮፕላኖች እናስመጣለን በዋነኛነት የቱሪስት መዳረሻዎች ላይ እንጠቀምባቸዋለን ብለን አቅደናል " ብለዋል።
የኢ-ኮሜርስ ንግድን ከማስፋፋት አኳያ አየር መንገዱ ከአለም አቀፎቹ አማዞን እና አሊባባ እንዲሁም ከሃገር ውስጡ " ዘመን ገበያ " ጋር በአጋርነት ለመስራት አስቧል ወይ ? ምን አይነት እንቅስቃሴዎችንስ እያደረገ ይገኛል ? የሚል ጥያቄ ያነሳንላቸው አቶ መስፍን ፤ አየር መንገዱ የተወሰነ እንቅስቃሴዎች እያደረገ እንደሚገኝ ነገር ግን ገና በሚባል ደረጃ ላይ ያለ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን በተጨማሪ ምን አሉ ?
"እኛ እስካሁን ድረስ ኢ-ኮሜርስን በአለም አቀፍ ደረጃ ለመስራት የሚያስችለንን ፋሲሊቲ ገንብተናል።
ይህ ፋስሊቲ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አካሉን ብቻ ነው የሚሰራው እኛ ኢ-ኮሜርስ ውስጥ አንገባም ኢ-ኮሜርስ ንግዱን የሚሰሩት ሌሎች ድርጅቶች ናቸው እኛ ትራንስፖርቱን ነው የምናቀላጥፈው።
ከመነሻው ማጠናቀቁን እና መዳረሻውን ላይ ደግሞ የመጨረሻውን ከሚያከፋፍሉ ድርጅቶች ጋር ተቀናጅተን ቦሌ ኤርፖርት ካርጎ ተርሚናላችንን ተጠቅመን ይህንን ለማሳለጥ ነው የምንሰራው የተወሰነ የተጀመረ ስራ አለ ነገር ግን ገና መሰራት ያለበት ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያዊ አየር መንገድ መጋቢት 17/2017 ዓም ላይ አርቸር አቪዬሽን ከተሰኘ አለም አቀፍ ተቋም ጋር ስምምነት መፈራረሙ ይታወሳል።
ስምምነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና አርቸር አቪዬሽን በኤሌክትሪክ የሚሰሩ አውሮፕላኖችን በአየር ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ ለማዋል ሲሆን በመኪና ከ60-90 ደቂቃ የሚወስድ ጉዞን ወደ 10 ደቂቃ ዝቅ የሚያደርግ እንደሆነ በወቅቱ ተገልጾ ነበር።
የዚህ ስምምነት ትግበራ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው ጥያቄ አቅርቧል።
ዋና ስራ አስፈጻሚ በሰጡት ምላሽ " በፈርንጂዎቹ 2026 ሁለት በኤሌክትሪክ የሚሰሩ ትናንሽ አውሮፕላኖች እናስመጣለን በዋነኛነት የቱሪስት መዳረሻዎች ላይ እንጠቀምባቸዋለን ብለን አቅደናል " ብለዋል።
የኢ-ኮሜርስ ንግድን ከማስፋፋት አኳያ አየር መንገዱ ከአለም አቀፎቹ አማዞን እና አሊባባ እንዲሁም ከሃገር ውስጡ " ዘመን ገበያ " ጋር በአጋርነት ለመስራት አስቧል ወይ ? ምን አይነት እንቅስቃሴዎችንስ እያደረገ ይገኛል ? የሚል ጥያቄ ያነሳንላቸው አቶ መስፍን ፤ አየር መንገዱ የተወሰነ እንቅስቃሴዎች እያደረገ እንደሚገኝ ነገር ግን ገና በሚባል ደረጃ ላይ ያለ መሆኑን ጠቁመዋል።
ዋና ስራ አስፈጻሚው አቶ መስፍን በተጨማሪ ምን አሉ ?
"እኛ እስካሁን ድረስ ኢ-ኮሜርስን በአለም አቀፍ ደረጃ ለመስራት የሚያስችለንን ፋሲሊቲ ገንብተናል።
ይህ ፋስሊቲ የትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ አካሉን ብቻ ነው የሚሰራው እኛ ኢ-ኮሜርስ ውስጥ አንገባም ኢ-ኮሜርስ ንግዱን የሚሰሩት ሌሎች ድርጅቶች ናቸው እኛ ትራንስፖርቱን ነው የምናቀላጥፈው።
ከመነሻው ማጠናቀቁን እና መዳረሻውን ላይ ደግሞ የመጨረሻውን ከሚያከፋፍሉ ድርጅቶች ጋር ተቀናጅተን ቦሌ ኤርፖርት ካርጎ ተርሚናላችንን ተጠቅመን ይህንን ለማሳለጥ ነው የምንሰራው የተወሰነ የተጀመረ ስራ አለ ነገር ግን ገና መሰራት ያለበት ነው " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
@tikvahethiopia
❤365😡70🤔23👏21🙏19😭12😱4🥰2