TIKVAH-ETHIOPIA
" ፍትህ እንዲረጋገጥ እሻለሁ " - ወ/ሮ ፋንቱ ደምሴ ትላንት አርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ የተገደለበት 4ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 3ኛው ዓመት " የሃጫሉ አዋርድ " የሽልማት መርሃ ግብር በአዲስ አበባ ተካሂዷል። በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች እውቅና አግኝተዋል፡፡ በዚሁ መድረክ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ባለቤት እና…
ፎቶ ፦ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ 5ኛው የሙት ዓመት መታሰቢያ እና 4ኛው ዓመት " የሃጫሉ አዋርድ " የሽልማት መርሃ ግብር ዛሬ ምሽት በአዲስ አበባ ተካሂዷል።
በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች በመርሃግብሩ እውቅና አግኝተዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ፎቶ ክሬዲት ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን እና ኦኤምኤን
@tikvahethiopia
በኦሮሞ አርት ውስጥ በዓመቱ ጉልህ አሻራን ያኖሩ እና በተለያዩ ጊዜያት በአርቱ አስተዋጽኦ ያበረከቱ ግለሰቦች በመርሃግብሩ እውቅና አግኝተዋል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
ፎቶ ክሬዲት ፦ ሃጫሉ ሁንዴሳ ፋውንዴሽን እና ኦኤምኤን
@tikvahethiopia
❤750😡282😭69😢65🤔53🕊20🙏15👏13🥰8😱3
TIKVAH-ETHIOPIA
#NationalExam ዩኒቨርሲቲዎች ከፊታችን ሰኞ ጀምሮ የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚወስዱ ተፈታኞችን ዛሬ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም መቀበል ጀምረዋል፡፡ የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ ይታወቃል። በወጣው መርሐግብር መሰረት ሰኞ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ይጀምራል፡፡ ፈተናውን…
#NationalExam🇪🇹
ነገ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መሠጠት ይጀምራል።
ፈተናውን ለመውሰድ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ለገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችም ዛሬ የግንዛቤ ማስጨበጫ (Orientation) ሲሰጥ ውሏል።
ተፈታኞቹ በዩኒቨርሲቲዎቹ በሚኖራቸው ቆይታ ስለሚያገኙት አገልግሎቶች (ምግብ፣ መኝታ፣ ጤና...) እና ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጓል።
በተጨማሪም በፈተና ወቅት ስለሚከተሏቸው ህግና ደንቦች እንዲሁም ተያያዥ ስለሆኑ የፈተና ሂደቶችና አተገባበሮችን በሚመለከት ገለጻ ተሰጥቷቸዋል።
ነገ የሚጀመረው የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሚወስዱት ፈተና ይጀምራል።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
ነገ ሰኔ 23/2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መሠጠት ይጀምራል።
ፈተናውን ለመውሰድ ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ለገቡ የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎችም ዛሬ የግንዛቤ ማስጨበጫ (Orientation) ሲሰጥ ውሏል።
ተፈታኞቹ በዩኒቨርሲቲዎቹ በሚኖራቸው ቆይታ ስለሚያገኙት አገልግሎቶች (ምግብ፣ መኝታ፣ ጤና...) እና ሌሎች ቅድመ ሁኔታዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጓል።
በተጨማሪም በፈተና ወቅት ስለሚከተሏቸው ህግና ደንቦች እንዲሁም ተያያዥ ስለሆኑ የፈተና ሂደቶችና አተገባበሮችን በሚመለከት ገለጻ ተሰጥቷቸዋል።
ነገ የሚጀመረው የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በሚወስዱት ፈተና ይጀምራል።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤954🙏142🕊75😭48😢27😡22👏13😱8💔8
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
ሀገር አቀፉ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ተጀመረ።
የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ፈተናውን አስጀምረዋል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
የ2017 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና በዛሬው ዕለት ተጀምሯል።
የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ተጀምሯል።
የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ፣ የሚኒስቴሩ አማካሪ ሚኒስትር ዴኤታ ፕሮፌሰር ክንደያ ገ/ህይወት እንዲሁም የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ኢ/ር ነጋሽ ዋጌሾ በቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ተገኝተው ፈተናውን አስጀምረዋል።
ዘንድሮ በወረቀትና በበየነ መረብ ከ608 ሺ በላይ ተማሪዎች ፈተናቸውን ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
መረጃው የትምህርት ሚኒስቴር ነው።
@tikvahethiopia
❤1.11K🙏214😭140🕊86💔39🤔28👏23🥰22😱21😡17😢6
#SafaricomEthiopia
🤙🏽ከሳፋሪኮም ወደ የቴሌ የሚያስደውሉ የድምፅ ጥቅሎች በመጠቀም ከ07 ➡️ 09 መስመር በእጥፍ ጉርሻ በሽ በሽ ብለን እንደዋወል! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
🤙🏽ከሳፋሪኮም ወደ የቴሌ የሚያስደውሉ የድምፅ ጥቅሎች በመጠቀም ከ07 ➡️ 09 መስመር በእጥፍ ጉርሻ በሽ በሽ ብለን እንደዋወል! ከሳፋሪኮም ጋር በአብሮነት አንድ ወደፊት⚡️
#1Wedefit
#Furtheraheadtogether
❤175😡25🙏12🕊12👏11😭2
ኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ምን ውሳኔ አሳለፈ ?
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ ውይይት አካሂዶ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።
1. በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወስኗል።
ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ወሳኔ አሳልፏል።
" አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ብሏል።
ይህ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳብ ለብሔራዊ ባንክ ቦርድ ቀርቦ ጸድቋል።
ስለ ግምጃ ቤት ቦንድ ፦ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ በሚያስገድደው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ባንኮች መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ 2022 ጀምሮ ከአጠቃላይ ዓመታዊ ብድራቸው አምስት በመቶ የሚሆነውን ለዚህ የቦንድ ግዥ ሲያውሉ ቆይተዋል።
በዚህ መመሪያ መሠረት የገዙት ቦንድ የሚመለሰው (ለቦንድ ግዢ ያዋሉት ገንዘብ ተመላሽ የሚደረግላቸው) ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ ሲሆን ፣ ባንኮቹ መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ወር አንስቶ እ.ኤ.አ. እስከ ጁን 30 ቀን 2024 ድረስ የገዙት የቦንድ መጠን 94 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት ዕዳ መግለጫ ያመለክታል።
2. በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕቀባ የተመለከተ ውሳኔ ተላልፏል።
በአሁኑ ወቅት በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ጣሪያ እስከ መጪው መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲቀጠል ኮሚቴው ወስኗል።
" አሁን ላይ የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ እየተስተዋለ ቢሆንም ይህንን ማስቀጠል አስፈላጊ በመሆኑ በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕድገት ጣሪያ ባለበት እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ብሏል ኮሚቴው።
3. የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን (National Bank Rate) አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይ፣ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው ቋሚ የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት (standing deposit facility)፣ ለቋሚ የብድር አገልግሎት (standing lending facility) የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፣ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ በነበረበት እንዲቆይ ተወስኗል፡፡
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
#NBE #REPORTER
@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የገንዘብ ፖሊሲ ኮሚቴ ዛሬ ውይይት አካሂዶ የተለያዩ ውሳኔዎች አሳልፏል።
1. በሁሉም ንግድ ባንኮች ላይ የተጣለው አስገዳጅ የቦንድ ግዥ እንዲነሳ ወስኗል።
ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ (Treasury Bond) እንዲገዙ የሚያስገድደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ (MFAD/TRBO/001/2022) እንዲነሳ ወሳኔ አሳልፏል።
" አሁን ላይ የመንግሥት ገቢ የማሰባሰብ አቅም በእጅጉ በመሻሻሉ፣ እንዲሁም መንግሥት የበጀት ጉድለቱን ለሟሟላት የውጭና ገበያ መር የሆኑ የሀገር ውስጥ የመበደሪያ አማራጮችን እየተጠቀመ በመሆኑ በባንኮች ላይ ተጥሎ የቆየውን ይህ አስገዳጅ መመሪያ አሁን ላይ ማንሣቱ ተገቢ መሆኑን ኮሚቴው አምኖበታል" ብሏል።
ይህ የገንዘብ ፖሊሲ ምክረ ሐሳብ ለብሔራዊ ባንክ ቦርድ ቀርቦ ጸድቋል።
ስለ ግምጃ ቤት ቦንድ ፦ ሁሉም ንግድ ባንኮች የረጅም ጊዜ የግምጃ ቤት ቦንድ እንዲገዙ በሚያስገድደው የብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ባንኮች መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት እ.ኤ.አ. ከጃንዋሪ 2022 ጀምሮ ከአጠቃላይ ዓመታዊ ብድራቸው አምስት በመቶ የሚሆነውን ለዚህ የቦንድ ግዥ ሲያውሉ ቆይተዋል።
በዚህ መመሪያ መሠረት የገዙት ቦንድ የሚመለሰው (ለቦንድ ግዢ ያዋሉት ገንዘብ ተመላሽ የሚደረግላቸው) ከአምስት ዓመት ቆይታ በኋላ ሲሆን ፣ ባንኮቹ መመሪያው ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ወር አንስቶ እ.ኤ.አ. እስከ ጁን 30 ቀን 2024 ድረስ የገዙት የቦንድ መጠን 94 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር የመንግሥት ዕዳ መግለጫ ያመለክታል።
2. በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕቀባ የተመለከተ ውሳኔ ተላልፏል።
በአሁኑ ወቅት በባንኮች ዓመታዊ የብድር ዕድገት ላይ የተቀመጠው የ18 በመቶ ጣሪያ እስከ መጪው መስከረም 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲቀጠል ኮሚቴው ወስኗል።
" አሁን ላይ የዋጋ ግሽበት የመርገብ አዝማሚያ እየተስተዋለ ቢሆንም ይህንን ማስቀጠል አስፈላጊ በመሆኑ በባንኮች ላይ የተጣለው የብድር ዕድገት ጣሪያ ባለበት እንዲቆይ ማድረግ አስፈላጊ ነው " ብሏል ኮሚቴው።
3. የብሔራዊ ባንክ የፖሊሲ ተመን (National Bank Rate) አሁን ባለበት 15 በመቶ እንዲቆይ፣ብሔራዊ ባንክ ለሚሰጣቸው ቋሚ የተቀማጭ ሂሳብ አገልግሎት (standing deposit facility)፣ ለቋሚ የብድር አገልግሎት (standing lending facility) የሚከፈሉ የወለድ ተመኖች ባሉበት እንዲቀጥሉ፣ እንዲሁም ባንኮች በብሔራዊ ባንክ የሚያስቀምጡት የግዴታ መጠባበቂያ ምጣኔ በነበረበት እንዲቆይ ተወስኗል፡፡
(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)
#NBE #REPORTER
@tikvahethiopia
❤665😡67🙏31🤔8🕊8😱7😭4🥰2😢2💔1