" በተፈጠረው እሳት አደጋ ሁለት ሰዎች ሞተዋል፤ አንዱ ሆስፒታል ገብቷል " - የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ
በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተፈጠረ በተባለ የፍንዳታ አደጋ በሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የክልሉ ጸጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ አህመድ በሰጡን ቃል፣ "ትላንት ሁለት ሰዓት አካባቢ በተፈጠረው እሳት አደጋ ሁለት ሰዎች ሞተዋል፤ አንዱ ሆስፒታል ገብቷል" ብለዋል።
የችግሩን መንስኤ ሲያስረዱም አቶ ሀሚድ፣ "የችግሩ መንስኤ ማሽኑ ላይ በተነሳው እሳት ምክንያት ነው፤ ማሽኑ ላይ እሳት/ ቃጠሎ ተነስቶ በዚያ የሚሰሩ ሰራተኞች ናቸው የተጎዱት" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋው መድረሱን ትላንት በሰሙበት ወቅት ሦስት ሰዎች ተጎድተው እንደነበር፣ አንዱ ሆስፒታል እንደገባ፣ ሁለቱ እንደሞቱ ነው የገለጹት።
የሀዋሳ ከተማ ጸጥታ መምሪያ በበኩሉ፣ ችግሩ ተፈጥሯል መባሉ ትክክል መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጾ፣ ተጨማሪ መረጃ ከፓሊስ እንዲጠየቅ ጠቁሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተፈጠረ በተባለ የፍንዳታ አደጋ በሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የክልሉ ጸጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ አህመድ በሰጡን ቃል፣ "ትላንት ሁለት ሰዓት አካባቢ በተፈጠረው እሳት አደጋ ሁለት ሰዎች ሞተዋል፤ አንዱ ሆስፒታል ገብቷል" ብለዋል።
የችግሩን መንስኤ ሲያስረዱም አቶ ሀሚድ፣ "የችግሩ መንስኤ ማሽኑ ላይ በተነሳው እሳት ምክንያት ነው፤ ማሽኑ ላይ እሳት/ ቃጠሎ ተነስቶ በዚያ የሚሰሩ ሰራተኞች ናቸው የተጎዱት" ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋው መድረሱን ትላንት በሰሙበት ወቅት ሦስት ሰዎች ተጎድተው እንደነበር፣ አንዱ ሆስፒታል እንደገባ፣ ሁለቱ እንደሞቱ ነው የገለጹት።
የሀዋሳ ከተማ ጸጥታ መምሪያ በበኩሉ፣ ችግሩ ተፈጥሯል መባሉ ትክክል መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጾ፣ ተጨማሪ መረጃ ከፓሊስ እንዲጠየቅ ጠቁሟል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤462😭240😢29💔23🕊16🙏11🥰8
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በእስራኤል እና በኢራን መካከል የተካሄደውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ወደ ሶስቱም ከተሞች ያቋረጥናቸውን በረራዎች በድጋሚ አስጀምረናል " - የኢትዮጵያ አየር መንገድ
በዛሬው ምሽት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፖርቶ ወደ ተሰኘች የፖርቹጋል ከተማ አዲስ በረራ ይጀምራል።
አየር መንገዱ የፖርቹጋል ሁለተኛ ትልቋ ከተማ ወደ ሆነችው ፖርቶ የሚያደርገው በረራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፓ ያሉትን የበረራ መዳረሻዎች ቁጥር 22 እንደሚያደርሰው ይፋ በማድረጊያ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አውሮፓ ከሚያደርጋቸው ጉዞዎች በሀገር ደረጃ ፖርቹጋል 17 ተኛዋ ሃገር ስትሆን ይህ በረራ ወደ ፖርቹጋል የተደረገ የመጀመሪያው በረራ መሆኑን ተነግሯል።
የአየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው አንድ ወር ጊዜ ወደ ወደ ዱባይ እና ቬትናም ተጨማሪ ሁለት መዳረሻዎችን ይፋ የሚያደርግ ይሆናል " ብለዋል።
በእስራኤል እና በኢራን መካከል ተቀስቅሶ የቆየውን ግጭት ተከትሎ አየር መንገዱ ወደ ቀጠናው የሚያደርገው ጉዞ ማቋረጡ ይታወሳል።
ተቋርጠው የቆዩት በረራዎች በድጋሚ መጀመራቸውን አቶ መስፍን ጣሰው አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ በዝርዝር ምን አሉ ?
" መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ አካባቢ ያሉ ሃገሮች ላይ ግጭት መኖሩን ተከትሎ የተወሰኑ ከተሞች በረራ አቋርጠን ነበር።
እስራኤል ውስጥ ወደ ቴልአቪቭ፣ ሊባኖስ ውስጥ ወደ ቤሩት እንዲሁም ዮርዳኖስ ውስጥ ወደ ኦማን ከተሞች ስናደርግ የነበረውን በረራዎች በጊዜያዊነት አቋርጠን ቆይተናል።
በእስራኤል እና በኢራን መካከል የተካሄደውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ወደ ሶስቱም ከተሞች ያቋረጥናቸውን በረራዎች በድጋሚ አስጀምረናል።
ተቋርጦ በቆየበት ወቅት መንገደኞች ወደዛ አካባቢ መጓጓዝ ያቆማሉ ስለዚህ መጠነኛ የተጓዦች መቀነስ ይታያል በረራ ላይ ሲታይ ግን ትልቅ ለውጥ የነበረው አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
በዛሬው ምሽት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ፖርቶ ወደ ተሰኘች የፖርቹጋል ከተማ አዲስ በረራ ይጀምራል።
አየር መንገዱ የፖርቹጋል ሁለተኛ ትልቋ ከተማ ወደ ሆነችው ፖርቶ የሚያደርገው በረራ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮፓ ያሉትን የበረራ መዳረሻዎች ቁጥር 22 እንደሚያደርሰው ይፋ በማድረጊያ ስነስርዓቱ ላይ ተገልጿል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ አውሮፓ ከሚያደርጋቸው ጉዞዎች በሀገር ደረጃ ፖርቹጋል 17 ተኛዋ ሃገር ስትሆን ይህ በረራ ወደ ፖርቹጋል የተደረገ የመጀመሪያው በረራ መሆኑን ተነግሯል።
የአየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው " የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመጪው አንድ ወር ጊዜ ወደ ወደ ዱባይ እና ቬትናም ተጨማሪ ሁለት መዳረሻዎችን ይፋ የሚያደርግ ይሆናል " ብለዋል።
በእስራኤል እና በኢራን መካከል ተቀስቅሶ የቆየውን ግጭት ተከትሎ አየር መንገዱ ወደ ቀጠናው የሚያደርገው ጉዞ ማቋረጡ ይታወሳል።
ተቋርጠው የቆዩት በረራዎች በድጋሚ መጀመራቸውን አቶ መስፍን ጣሰው አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ በዝርዝር ምን አሉ ?
" መካከለኛው ምስራቅ እና ገልፍ አካባቢ ያሉ ሃገሮች ላይ ግጭት መኖሩን ተከትሎ የተወሰኑ ከተሞች በረራ አቋርጠን ነበር።
እስራኤል ውስጥ ወደ ቴልአቪቭ፣ ሊባኖስ ውስጥ ወደ ቤሩት እንዲሁም ዮርዳኖስ ውስጥ ወደ ኦማን ከተሞች ስናደርግ የነበረውን በረራዎች በጊዜያዊነት አቋርጠን ቆይተናል።
በእስራኤል እና በኢራን መካከል የተካሄደውን የተኩስ አቁም ስምምነት ተከትሎ ወደ ሶስቱም ከተሞች ያቋረጥናቸውን በረራዎች በድጋሚ አስጀምረናል።
ተቋርጦ በቆየበት ወቅት መንገደኞች ወደዛ አካባቢ መጓጓዝ ያቆማሉ ስለዚህ መጠነኛ የተጓዦች መቀነስ ይታያል በረራ ላይ ሲታይ ግን ትልቅ ለውጥ የነበረው አይደለም " ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamily
@tikvahethiopia
❤832👏84🕊58🤔19😡19😭12🙏11😢10🥰8😱5
#HoPR🇪🇹
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስታቸውን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል።
በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን እንደሚያፀድቅ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጉባኤው ከጥዋት 2:30 ጀምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ይሰራጫል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስታቸውን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል።
በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀትን እንደሚያፀድቅ ከምክር ቤቱ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
ጉባኤው ከጥዋት 2:30 ጀምሮ በተለያዩ መገናኛ ብዙሃን በቀጥታ ይሰራጫል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😡885❤480😭41🙏24🤔23👏18🥰15💔15🕊12😱9😢3
TIKVAH-ETHIOPIA
" ትናንት የተሰጠውን የእንግሊዘኛ ትምህርት ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎች ሌሎች ትምህርት ፈተናዎችን ከወሰዱ በኋላ ይፈተናሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ትናንት በተሰጠው የመጀመሪያ ቀን ፈተናዎች ላይ የተወሰነ የኃይል እና የሲስተም መቆራረጥ አጋጥሞ እንደነበር የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናግረዋል። " ከሚመለከታቸው…
#NationalExam🇪🇹
ከሰኔ 23 እስከ 25/2017 ዓ/ም በበይነ መረብና በወረቀት ሲሰጥ የነበረው የአንደኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡
ፈተናውን በወረቀት 231,761 በበይነ መረብ 43,367 በድምሩ 275,128 ተፈታኞች ወስደዋል፡፡
የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ ላይ ፈተናውን በበይነ መረብ ሲወስዱ በተወሰኑ የፈተና ማዕከላት ላይ በተለያየ ምክንያት የእንግሊዘኛ ፈተና ያልወሰዱ ተፈታኞች አብዛኞቹ ነገ ሐሙስ ጥዋት ከሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ጋር ያልወሰዱት ፈተና የሚሰጣቸው እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በሁለተኛ ዙር ለመውሰድ ያልቻሉ ተፈታኞች ከሶስተኛውና ከአራተኛው ዙር ተፈታኞች ጋር እንደሚወስዱ አመልክቷል።
" ፈተናውን በተለያዩ ዙሮች መስጠት መቻላችን በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በተመደቡበት ዙር መፈተን ያልቻሉ ተፈታኞች በሌሎቹ ዙሮች ከሚፈተኑ ተፈታኞች ጋር መፈተን እንዲችሉ ዕድል ፈጥሯል " ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።
#EAES
@tikvahethiopia
ከሰኔ 23 እስከ 25/2017 ዓ/ም በበይነ መረብና በወረቀት ሲሰጥ የነበረው የአንደኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል፡፡
ፈተናውን በወረቀት 231,761 በበይነ መረብ 43,367 በድምሩ 275,128 ተፈታኞች ወስደዋል፡፡
የመጀመሪያ ቀን የመጀመሪያ ክፍለ ጊዜ ላይ ፈተናውን በበይነ መረብ ሲወስዱ በተወሰኑ የፈተና ማዕከላት ላይ በተለያየ ምክንያት የእንግሊዘኛ ፈተና ያልወሰዱ ተፈታኞች አብዛኞቹ ነገ ሐሙስ ጥዋት ከሁለተኛ ዙር ተፈታኞች ጋር ያልወሰዱት ፈተና የሚሰጣቸው እንደሆነ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በሁለተኛ ዙር ለመውሰድ ያልቻሉ ተፈታኞች ከሶስተኛውና ከአራተኛው ዙር ተፈታኞች ጋር እንደሚወስዱ አመልክቷል።
" ፈተናውን በተለያዩ ዙሮች መስጠት መቻላችን በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በተመደቡበት ዙር መፈተን ያልቻሉ ተፈታኞች በሌሎቹ ዙሮች ከሚፈተኑ ተፈታኞች ጋር መፈተን እንዲችሉ ዕድል ፈጥሯል " ሲል አገልግሎቱ ገልጿል።
#EAES
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤492🙏59😡27😭25🕊18🤔5🥰4😢3👏1
TIKVAH-ETHIOPIA
" በተፈጠረው እሳት አደጋ ሁለት ሰዎች ሞተዋል፤ አንዱ ሆስፒታል ገብቷል " - የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ በሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ተፈጠረ በተባለ የፍንዳታ አደጋ በሰዎች ላይ ሞትና የአካል ጉዳት መድረሱን የሲዳማ ክልል ጸጥታ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል። የክልሉ ጸጥታ ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሀሚድ አህመድ በሰጡን ቃል፣ "ትላንት ሁለት ሰዓት አካባቢ በተፈጠረው እሳት አደጋ…
" የውሃ ማሞቂያ ፈንድቶ ነው የሁለት ሰዎች ሕይወት ያልፈው " - የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ
➡️ " በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከአደጋው ጋር ተያይዞ የሚዘዋወሩት መረጃዎች የተሳሳቱ ናቸው !! "
የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ትናንት ጠዋት በፓርኩ ሼድ 40 የውሃ ማሞቂያ (ቦይሌር) ባለሙያ ሰራተኞች መደበኛ ስራቸውን እያከናወኑ ባሉበት ፈንድቶ የ62 እና 45 ዕድሜ ውስጥ ያሉ ሁለት ባለሙያዎች ሕይወታቸዉ ማለፉንና በሁሉት ሰራተኞች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ሁለቱም ባለሙያዎች ወንዶች ሲሆኑ ለረጅም ዓመታት በዘርፉ የሰሩና ልምድ ያላቸዉ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ማቴዎስ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ሰራተኞችም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምና ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
የአደጋውን ትክክለኛ መንስኤ እንዲያጣራ መርማሪ ቡድን መዋቀሩን የገለፁት የፓርኩ ስራ አስኪያጅ ከአደጋው ጋር ተያይዞ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች " ክስተቱ የእሳት አደጋ እንደሆነና መንስኤዉም ባለሙያዎች የልምድ ማነስ " ተደርጎ የሚሰራጩ መረጃዎች ፍፁም የተሳሳቱና ባለሙያዎችም የረጅም ዓመታት ማለትም ከ6 ዓመታት በላይ በዘርፉ ልምድ ያላቸው ስለመሆናቸው ተነግረዋል።
በዚህ ልክ በሰዉና በንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርስ የእሳት አደጋ ከዚህ ቀደም በፓርኩ ዉስጥ ተከስቶ እንደማያዉቅም አቶ ማቴዎስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
➡️ " በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ከአደጋው ጋር ተያይዞ የሚዘዋወሩት መረጃዎች የተሳሳቱ ናቸው !! "
የሀዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ስራ አስኪያጅ አቶ ማቴዎስ አሸናፊ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ትናንት ጠዋት በፓርኩ ሼድ 40 የውሃ ማሞቂያ (ቦይሌር) ባለሙያ ሰራተኞች መደበኛ ስራቸውን እያከናወኑ ባሉበት ፈንድቶ የ62 እና 45 ዕድሜ ውስጥ ያሉ ሁለት ባለሙያዎች ሕይወታቸዉ ማለፉንና በሁሉት ሰራተኞች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል።
ሕይወታቸዉ ያለፈዉ ሁለቱም ባለሙያዎች ወንዶች ሲሆኑ ለረጅም ዓመታት በዘርፉ የሰሩና ልምድ ያላቸዉ መሆናቸውን የገለፁት አቶ ማቴዎስ ጉዳት የደረሰባቸው ሁለት ሰራተኞችም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ኮምፕርሄንሲቪ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሕክምና ላይ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
የአደጋውን ትክክለኛ መንስኤ እንዲያጣራ መርማሪ ቡድን መዋቀሩን የገለፁት የፓርኩ ስራ አስኪያጅ ከአደጋው ጋር ተያይዞ በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች " ክስተቱ የእሳት አደጋ እንደሆነና መንስኤዉም ባለሙያዎች የልምድ ማነስ " ተደርጎ የሚሰራጩ መረጃዎች ፍፁም የተሳሳቱና ባለሙያዎችም የረጅም ዓመታት ማለትም ከ6 ዓመታት በላይ በዘርፉ ልምድ ያላቸው ስለመሆናቸው ተነግረዋል።
በዚህ ልክ በሰዉና በንብረት ላይ ጉዳት የሚያደርስ የእሳት አደጋ ከዚህ ቀደም በፓርኩ ዉስጥ ተከስቶ እንደማያዉቅም አቶ ማቴዎስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHawassa
@tikvahethiopia
❤860😭425😢56🙏43🕊36😡16👏13😱13🥰8
#DStvEthiopia
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
📣 ከእሁድ እስከ እሁድ አለንላችሁ!
❗️❗️ለአጭር ጊዜ የሚቆይ! ደንበኝነትዎን ከሰኔ 8 ጀምሮ ሲያራዝሙ ከፍ ወዳለው ፓኬጅ ከተጨማሪ ቻናሎች ጋር በስጦታ ያገኛሉ!!
አዲሱን እና የተሻሻለውን MyDStv መተግበሪያ ያውርዱ።
⬇️ https://mydstv.onelink.me/vGln/xepsjmo7
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው!
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
#ሁሉምያለውእኛጋርነው
📣 ከእሁድ እስከ እሁድ አለንላችሁ!
❗️❗️ለአጭር ጊዜ የሚቆይ! ደንበኝነትዎን ከሰኔ 8 ጀምሮ ሲያራዝሙ ከፍ ወዳለው ፓኬጅ ከተጨማሪ ቻናሎች ጋር በስጦታ ያገኛሉ!!
አዲሱን እና የተሻሻለውን MyDStv መተግበሪያ ያውርዱ።
⬇️ https://mydstv.onelink.me/vGln/xepsjmo7
ደንብና ሁኔታዎች ተፈፃሚነት አላቸው!
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #DStvEthiopia
❤153🙏5🥰4😱3😢3
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት
የሁለት ወር የልጆች የክረምት ስልጠና ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 5-18 ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ ነው።
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
የስልጠናዎቹ ዓይነት:
👉 Computer Programming and Website Development
👉 AI and Robotics
👉 Graphic Design, Video Editing and Animation
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Language and Basic Computer
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram
Tiktok
Linkedin
የሁለት ወር የልጆች የክረምት ስልጠና ሰኔ 30/2017 ዓ.ም ይጀመራል።
👉ስልጠናው ዕድሜያቸው ከ 5-18 ዓመት ላሉ ልጆች የሚሰጥ ነው።
👉 ልጆች ፕሮጀክቶች እየሰሩ የሚሰለጥኑበት
የስልጠናዎቹ ዓይነት:
👉 Computer Programming and Website Development
👉 AI and Robotics
👉 Graphic Design, Video Editing and Animation
👉 Art (Film Acting, Writing and Modeling)
👉 Painting, Drawing and Sculpture
👉 Language and Basic Computer
☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ፦ ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ እና ቁ.2 መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ
Telegram
Tiktok
❤112🙏6🤔5😡5😢2👏1
" ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 የሚሆኑ ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ " - ድርጅቱ
" ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ " የመብት ተሟጋች የተሰኘው ድርጅት፣ " የትግራይ ተወላጆች በአዲስ አበባ በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው " ሲል ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ስለእስሩ በተጨባጭ ያላችሁ መረጃ ምንድን ነው ? ብለን የጠየቅናቸው የድርጅቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ መብሪሂ ብርሃነ፣ " በባለፉት ሁለት፣ ሦስት ሳምንታት ያለየፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ያለበቂ ጥርጣሬ ሰዎች በማንነታቸው ብቻ እየታሰሩ ስለሆነ ይህን መሠረት አድረገን ክትትል ስናደርግ ቆይተናል " ብለዋል።
" ከክትትል ባለፈ ደግሞ ተጨባጭ ማስረጃ ካገኘን በኋላ እና ታስረው የወጡት፣ የታሳሪ ቤተሰቦችና ጓደኞችን ከጠየቅን በኋላ ሪፖርት አውጥተናል " ብለው፣ " ሰዎች ከሕግ ውጪ ሲታሰሩ ብቻ ሳይሆን ያለበቂ ጥርጣሬ ታስረው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ሲቀር ይሄ የዘፈቀደ እስር ነው " ሲሉ ወንጅለዋል።
" ሰዎች ሊታሰሩ ይችላሉ። ግን ሕግ ቢተላለፉ እንኳ ወደ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የሚቀርቡት ከ48 ሰዓታት በላይ ፓሊስ አስሮ ማቆየት አይችልም በወንጀል እንኳ የተጠረጠረውን። እነዚህ ግን የወንጀል ጥርጣሬም የላቸውም፣ ለምን እንደታሰሩም አይነገራቸውም " ነው ያሉት።
እስራቱ ከምን ጋር የተያያዘ እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " እስሮች በየጊዜው ይፈጸማሉ አሁን በትግራይ ተወላጆች ትኩረቱን አደረገ እንጂ፤ ከዚህ በፊትም ማንነት ተኮር እስሮች አሉ። ምክንያቱን አሳሪዎቹ ናቸው የሚያውቁት " ብለዋል።
" አንድ ሰው ከታሰረ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት እንጂ አንድ ቦታ አጎሮ ሳምንት፣ ሁለት ሳምንት ማቆየት ሕገ ወጥ ድርጊት ነው በወንጀልም ያስጠይቃል። በቁጥጥር ሥር የሚያውሏቸው ሰዎች 'እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ ከላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው' ነው የሚሉት " ብለዋል።
" ሰዎች በሕገ መግስቱ አንቀጽ 25 መሠረት በእኩልነት ነው መስተናገድ ያለባቸው " ያሉት ም/ዳይክተሩ፣ " የታሰሩ አንዳንድ ሰዎች ገንዘብ ከፍለው የወጡበት ሁኔታ አለ። ስለዚህ የሙስና ተግባራትም አለ ለማለት ያስችላል " ብለዋል።
በተጨባጭ ድርጅቱ ባለው መረጃ መሠረት ምን ያክል ሰዎች ታስረዋል ? የት ክፍለ ከተማስ ነው የታሰሩት ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረላቸው ጥያቄ፣ " በተጨባጭ በእያንዳንዱ ከተማ ምን ያህል ሰው እንደታሰረ መቁጠር ያስፈልጋል። ግን ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
" በመቶዎች ወይም እስከ 1000 ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን አጠቃላይ በቁጥጥር ሥር ውለው የተፈቱትና አሁንም በእስር ላይ ያሉት" ያሉት አቶ መብሪሂ፣ "ሰዎቹ የታሰሩት ቦሌ፣ ሲኤምሲ፣ ሾላ፣ ልደታ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ሰዎች ወንጀል ከሰሩ በሕግ አግባብ አይጠየቁ አንልም ነገር ግን በጅምላ እየተወሰዱ፣ አንዳንዴም ገንዘብ እየጠየቁ እየሆነ ያለ ተግባር ስለሆነ በማንም ተወላጅ ላይ ሊደረግ አይገባም። መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ ይስጥበት " ሲሉም አሳስበዋል።
ጉዳዩን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው አንድ ተቋም፣ ጉዳዩን እየተከታተለው መሆኑን የጠቆመ ሲሆን፣ ምላሽ ከሰጠ የምናቀርብ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" ቅድሚያ ለሰብዓዊ መብቶች ኢትዮጵያ " የመብት ተሟጋች የተሰኘው ድርጅት፣ " የትግራይ ተወላጆች በአዲስ አበባ በዘፈቀደ እየታሰሩ ነው " ሲል ለቲካቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ፡፡
ስለእስሩ በተጨባጭ ያላችሁ መረጃ ምንድን ነው ? ብለን የጠየቅናቸው የድርጅቱ ምክትል ዳይሬክተር አቶ መብሪሂ ብርሃነ፣ " በባለፉት ሁለት፣ ሦስት ሳምንታት ያለየፍርድ ቤት ትዕዛዝ፣ ያለበቂ ጥርጣሬ ሰዎች በማንነታቸው ብቻ እየታሰሩ ስለሆነ ይህን መሠረት አድረገን ክትትል ስናደርግ ቆይተናል " ብለዋል።
" ከክትትል ባለፈ ደግሞ ተጨባጭ ማስረጃ ካገኘን በኋላ እና ታስረው የወጡት፣ የታሳሪ ቤተሰቦችና ጓደኞችን ከጠየቅን በኋላ ሪፖርት አውጥተናል " ብለው፣ " ሰዎች ከሕግ ውጪ ሲታሰሩ ብቻ ሳይሆን ያለበቂ ጥርጣሬ ታስረው ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ሲቀር ይሄ የዘፈቀደ እስር ነው " ሲሉ ወንጅለዋል።
" ሰዎች ሊታሰሩ ይችላሉ። ግን ሕግ ቢተላለፉ እንኳ ወደ ፍርድ ቤት ነው እንጂ የሚቀርቡት ከ48 ሰዓታት በላይ ፓሊስ አስሮ ማቆየት አይችልም በወንጀል እንኳ የተጠረጠረውን። እነዚህ ግን የወንጀል ጥርጣሬም የላቸውም፣ ለምን እንደታሰሩም አይነገራቸውም " ነው ያሉት።
እስራቱ ከምን ጋር የተያያዘ እንደሆነ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ " እስሮች በየጊዜው ይፈጸማሉ አሁን በትግራይ ተወላጆች ትኩረቱን አደረገ እንጂ፤ ከዚህ በፊትም ማንነት ተኮር እስሮች አሉ። ምክንያቱን አሳሪዎቹ ናቸው የሚያውቁት " ብለዋል።
" አንድ ሰው ከታሰረ ፍርድ ቤት መቅረብ አለበት እንጂ አንድ ቦታ አጎሮ ሳምንት፣ ሁለት ሳምንት ማቆየት ሕገ ወጥ ድርጊት ነው በወንጀልም ያስጠይቃል። በቁጥጥር ሥር የሚያውሏቸው ሰዎች 'እኛ የምናውቀው ነገር የለም፤ ከላይ የመጣ ትዕዛዝ ነው' ነው የሚሉት " ብለዋል።
" ሰዎች በሕገ መግስቱ አንቀጽ 25 መሠረት በእኩልነት ነው መስተናገድ ያለባቸው " ያሉት ም/ዳይክተሩ፣ " የታሰሩ አንዳንድ ሰዎች ገንዘብ ከፍለው የወጡበት ሁኔታ አለ። ስለዚህ የሙስና ተግባራትም አለ ለማለት ያስችላል " ብለዋል።
በተጨባጭ ድርጅቱ ባለው መረጃ መሠረት ምን ያክል ሰዎች ታስረዋል ? የት ክፍለ ከተማስ ነው የታሰሩት ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ላቀረላቸው ጥያቄ፣ " በተጨባጭ በእያንዳንዱ ከተማ ምን ያህል ሰው እንደታሰረ መቁጠር ያስፈልጋል። ግን ለምሳሌ የካ ክፍለ ከተማ ወደ 100 ሰዎች መታሰራቸውን በማስረጃዎች አረጋግጠናል፤ ወደ ቦሌ ወደ 200 የሚሆኑ አሉ " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
" በመቶዎች ወይም እስከ 1000 ሊሆን ይችላል ብለን እንገምታለን አጠቃላይ በቁጥጥር ሥር ውለው የተፈቱትና አሁንም በእስር ላይ ያሉት" ያሉት አቶ መብሪሂ፣ "ሰዎቹ የታሰሩት ቦሌ፣ ሲኤምሲ፣ ሾላ፣ ልደታ እና ሌሎች ቦታዎች ላይ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።
" ሰዎች ወንጀል ከሰሩ በሕግ አግባብ አይጠየቁ አንልም ነገር ግን በጅምላ እየተወሰዱ፣ አንዳንዴም ገንዘብ እየጠየቁ እየሆነ ያለ ተግባር ስለሆነ በማንም ተወላጅ ላይ ሊደረግ አይገባም። መንግስት አስቸኳይ መፍትሄ ይስጥበት " ሲሉም አሳስበዋል።
ጉዳዩን በተመለከተ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምላሽ የጠየቀው አንድ ተቋም፣ ጉዳዩን እየተከታተለው መሆኑን የጠቆመ ሲሆን፣ ምላሽ ከሰጠ የምናቀርብ ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤439😭166🙏18😡15🤔14🕊12👏10😢10
" በጸጥታ ምክንያት የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ ያቋረጠባቸው ቦታዎች አሉ። ለምሳሌ ወረታ ደረቅ ወደብ " - ጠያቂዎች ስለባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት
የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ አገልግሎት ድርጅት በጸጥታው ምክንያት ወደ ወረታ ወደብ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ በማቋረጡ በባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽሕፈት ቤት ቅሬታ መኖሩን የሚመለከት ጥያቄ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ቀረበበት።
ጥያቄው የቀረበው ከሰሞኑን ኮሚሽኑ፣ የ11 ወራት ሪፓርቱን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።
በዚህም አንድ ጠያቂ፣ " በጸጥታ ምክንያት የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ ያቋረጠባቸው ቦታዎች አሉ። ለምሳሌ 'በወረታ ደረቅ ወደብ አካባቢ እንዳይሄዱ በመደረጉ በገቢያችን ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አመጡብን' የሚል ቅሬታ አለ በቅ/ጽ/ቤቱ። ኮሚሽኑ በዚህ ዙሪያ ምን እየሰራ ነው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
ሌላኛው ጠያቂም፣ ከወረታ ደረቅ ወደብ ጋር በተያያዘ የቅ/ጽሕፈት ቤቱ ቅሬታ ሲያስረዱ፣ "'ዩኒሞዳሉ (ግለሰቡ) ያስገባል፣ መልቲሞዳሉ (የመንግስቱ) ግን አቋርጧል። በተደጋጋሚ ብንጽፍም አድማጭ አልተገኘም። ይሄ በመሆኑ ገቢያችን ቀንሷል፤ አፈጻጻማችን ዝቅተኛ እንዲሆን አድርጎታል' የሚል ቅሬታ ስላለ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው?" ሲሉ ጠይቀዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽን፣ "በመስክ ጉብኝታችሁ ካያችኋቸው መካከል ባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽሕፈት ቤት በመልቲ ሞዳል የሚገቡ የእቃ ፍሰት መቀነስ ጋር የተነሳው እውነት ነው። የመልቲሞዳል ኦፕሬተሩ የመንግስት የባሕር የትራንስፓርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ድርጅት ነው" ሲል መልሷል።
"እቃ አገባብን በተመለከተ በክልሉ/በመስመሩ ያሉ የጸጥታ ችግሮች አልፎ፣ አልፎ የሚፈጸሙ ቢሆንም በሱ ስጋት መነሻ የመልቲሞዳል ሞደሉ እቃዎችን በፈለገው ደረጃ ቀደም ብሎ እንደነበረው ስሙዝሊ ለማማጓጓዝ ፍላጎት የለውም" ሲል አክሏል።
"በወደቡ የሚገባው የእቃ ፍሰት ከጸጥታ መነሻ በማድረግ የመልቲሞዳል ኦፕሬተሩ እቃ እያጓጓዘ አይደለም። ፍሰቱ የሚሻሻልበት ሁኔታ ይኖራል" ነው ያለው ኮሚሽኑ።
በሌላ በኩል ኮሚሽኑ፣ "የግብዓትና ሎጂስቱክስ ጉዳይ ቀለል ተደርጓል። ኤግሶስት አድርገናል ካገዛችሁን። 100 መኪና ይገዛልን ብለን ከጠየቅን ሁለት ዓመት አልፎታል። እስካሁን አልተገዛም። ዋጋ እየተከፈለ ሰው እየሞተ ነው፤ የጸጥታ ተቋማት ሰዎችም መዓት ነው የሚሞተው" ሲል ሪፓርት ባቀረበበት ወቅት ገልጿል።
ቋሚ ኮሚቴው በበኩሉ፣ ኮንትሮባንዲስቶችን ከመያዝ አኳያ በተደረገ ግምገማ፣ "መንግስት ያለው መኪና በጣም ደካማ፣ ችግር ያለበት፤ ኮንትሮባንዲስቶቹ የሚይዙት ደግሞ ዘመናዊ እንደሆነ በየጊዜው ሲነሳ ነበር" ብሎ፣ "ከመኪና ጋር ተያይዞ ሁልጊዜ አቅማችሁን እየተፈታተነ ያለ ነገር ስለሆነ ችግራችሁን በደንብ ብታስረዱን የኛ ቋሚ ኮሚቴም ለማገዝ ዝግጁ ነው" ብሏል።
"በዚህ ዘርፍ በሰው ሕይወት ጉዳት እየደረሰ እንዳለም እናውቃለን። እናንተም ራሳቸውን መስዋት ያደረጉ ሰዎችን ቤተሰቦች እየደገፋችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ተቋሙ ስራውን እየሰራ ባለበት የጠየቀው የመኪና ግዥ ምላሽ የማይሰጥበት ችግሩ ምንድን ነው?" ሲልም ኮሚሽኑን ጠይቋል።
ኮሚሽኑም፣ "ግዢ ሂደት ላይም ደርሰው አሸናፊ ከተለየ በኋላ ክረምት ላይ በተደረገ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጪ ምንዛሬ ፍሎቴሽኑ ላይ ትልቅ ኢምፓክት ስለነበረው አቅራቢዎቹ የማቅረብ ፍላጎት አልነበራቸውም" የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ አገልግሎት ድርጅት በጸጥታው ምክንያት ወደ ወረታ ወደብ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ በማቋረጡ በባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽሕፈት ቤት ቅሬታ መኖሩን የሚመለከት ጥያቄ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ቀረበበት።
ጥያቄው የቀረበው ከሰሞኑን ኮሚሽኑ፣ የ11 ወራት ሪፓርቱን በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ለፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።
በዚህም አንድ ጠያቂ፣ " በጸጥታ ምክንያት የባሕርና ትራንስፓርት ሎጂስቲክ ደረቅ ጭነት እንዳይጓጓዝ ያቋረጠባቸው ቦታዎች አሉ። ለምሳሌ 'በወረታ ደረቅ ወደብ አካባቢ እንዳይሄዱ በመደረጉ በገቢያችን ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አመጡብን' የሚል ቅሬታ አለ በቅ/ጽ/ቤቱ። ኮሚሽኑ በዚህ ዙሪያ ምን እየሰራ ነው ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
ሌላኛው ጠያቂም፣ ከወረታ ደረቅ ወደብ ጋር በተያያዘ የቅ/ጽሕፈት ቤቱ ቅሬታ ሲያስረዱ፣ "'ዩኒሞዳሉ (ግለሰቡ) ያስገባል፣ መልቲሞዳሉ (የመንግስቱ) ግን አቋርጧል። በተደጋጋሚ ብንጽፍም አድማጭ አልተገኘም። ይሄ በመሆኑ ገቢያችን ቀንሷል፤ አፈጻጻማችን ዝቅተኛ እንዲሆን አድርጎታል' የሚል ቅሬታ ስላለ የኮሚሽኑ ምላሽ ምንድን ነው?" ሲሉ ጠይቀዋል።
ጉምሩክ ኮሚሽን፣ "በመስክ ጉብኝታችሁ ካያችኋቸው መካከል ባሕር ዳር ጉምሩክ ቅ/ጽሕፈት ቤት በመልቲ ሞዳል የሚገቡ የእቃ ፍሰት መቀነስ ጋር የተነሳው እውነት ነው። የመልቲሞዳል ኦፕሬተሩ የመንግስት የባሕር የትራንስፓርትና ሎጂስቲክ አገልግሎት ድርጅት ነው" ሲል መልሷል።
"እቃ አገባብን በተመለከተ በክልሉ/በመስመሩ ያሉ የጸጥታ ችግሮች አልፎ፣ አልፎ የሚፈጸሙ ቢሆንም በሱ ስጋት መነሻ የመልቲሞዳል ሞደሉ እቃዎችን በፈለገው ደረጃ ቀደም ብሎ እንደነበረው ስሙዝሊ ለማማጓጓዝ ፍላጎት የለውም" ሲል አክሏል።
"በወደቡ የሚገባው የእቃ ፍሰት ከጸጥታ መነሻ በማድረግ የመልቲሞዳል ኦፕሬተሩ እቃ እያጓጓዘ አይደለም። ፍሰቱ የሚሻሻልበት ሁኔታ ይኖራል" ነው ያለው ኮሚሽኑ።
በሌላ በኩል ኮሚሽኑ፣ "የግብዓትና ሎጂስቱክስ ጉዳይ ቀለል ተደርጓል። ኤግሶስት አድርገናል ካገዛችሁን። 100 መኪና ይገዛልን ብለን ከጠየቅን ሁለት ዓመት አልፎታል። እስካሁን አልተገዛም። ዋጋ እየተከፈለ ሰው እየሞተ ነው፤ የጸጥታ ተቋማት ሰዎችም መዓት ነው የሚሞተው" ሲል ሪፓርት ባቀረበበት ወቅት ገልጿል።
ቋሚ ኮሚቴው በበኩሉ፣ ኮንትሮባንዲስቶችን ከመያዝ አኳያ በተደረገ ግምገማ፣ "መንግስት ያለው መኪና በጣም ደካማ፣ ችግር ያለበት፤ ኮንትሮባንዲስቶቹ የሚይዙት ደግሞ ዘመናዊ እንደሆነ በየጊዜው ሲነሳ ነበር" ብሎ፣ "ከመኪና ጋር ተያይዞ ሁልጊዜ አቅማችሁን እየተፈታተነ ያለ ነገር ስለሆነ ችግራችሁን በደንብ ብታስረዱን የኛ ቋሚ ኮሚቴም ለማገዝ ዝግጁ ነው" ብሏል።
"በዚህ ዘርፍ በሰው ሕይወት ጉዳት እየደረሰ እንዳለም እናውቃለን። እናንተም ራሳቸውን መስዋት ያደረጉ ሰዎችን ቤተሰቦች እየደገፋችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ተቋሙ ስራውን እየሰራ ባለበት የጠየቀው የመኪና ግዥ ምላሽ የማይሰጥበት ችግሩ ምንድን ነው?" ሲልም ኮሚሽኑን ጠይቋል።
ኮሚሽኑም፣ "ግዢ ሂደት ላይም ደርሰው አሸናፊ ከተለየ በኋላ ክረምት ላይ በተደረገ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የውጪ ምንዛሬ ፍሎቴሽኑ ላይ ትልቅ ኢምፓክት ስለነበረው አቅራቢዎቹ የማቅረብ ፍላጎት አልነበራቸውም" የሚል ምላሽ ሰጥቷል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤368🤔7😡7👏5🕊5😭5🥰4🙏3😢2
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ነገ ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተው ማብራሪያ ይሰጣሉ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የመንግስታቸውን የ2017 የዕቅድ አፈጻጸም አስመልክቶ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለሚነሱ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ይጠበቃል። በተጨማሪም የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፌዴራል መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት ረቂቅ…
#HoPR🇪🇹
" የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው ግንባር ቀደም ነው ! " - የምክር ቤት አባል
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተዋል።
የምክር ቤቱ አባላትም ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እያቀረቡ ይገኛሉ።
እስካሁን ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል ከኑሮ ውድነት፣ ከመንግሥት ሰራተኞች ፣ ጤና ባለሙያዎች እና መምህራን የደመወዝ ጭማሪ ጋር የተያያዘ ጥያቄ ይገኝበታል።
ጥያቄው የቀረበው በምክር ቤት አባሉ አቶ ግዛቸው አየለ ነው።
ምን አሉ ?
" የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።
በዚህ ምክንያት የጤና ባለሙያዎችን እና መምህራንን ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የመንግሥት ሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ እንዲደረግ ጥያቄ እያነሱ ይገኛሉ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የመንግሥት ሰራተኛን የኑሮ ደረጃ ከማሻሻል አኳያ በመንግሥት ምላሽ ዙሪያ ማብራሪያ ቢሰጥበት።
በተጨማሪ መንግሥት የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ እንዳለ ይታወቃል ይሁን እንጂ ካለው የቤት ፈላጊ ቁጥር ጋር ተነጻጽሮ ሲታይ ገና ብዙ ስራ ይጠይቃል። መንግሥት በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ በከተሞች የሚታየውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ምን እየሰራ ይገኛል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
የምክር ቤቱ ስብሰባ በብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል።
በተጨማሪ በምክር ቤቱ የዩትዩብ ገጽ መከታተል ይቻላል ፦ https://www.youtube.com/live/yLIns-2_vZM?feature=shared
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
" የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው ግንባር ቀደም ነው ! " - የምክር ቤት አባል
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ተገኝተዋል።
የምክር ቤቱ አባላትም ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ እያቀረቡ ይገኛሉ።
እስካሁን ከቀረቡ ጥያቄዎች መካከል ከኑሮ ውድነት፣ ከመንግሥት ሰራተኞች ፣ ጤና ባለሙያዎች እና መምህራን የደመወዝ ጭማሪ ጋር የተያያዘ ጥያቄ ይገኝበታል።
ጥያቄው የቀረበው በምክር ቤት አባሉ አቶ ግዛቸው አየለ ነው።
ምን አሉ ?
" የኑሮ ውድነት እና የዋጋ ግሽበት ከፍተኛ ጫና እያሳደረባቸው ካሉ የህብረተሰብ ክፍሎች የመንግሥት ሰራተኛው በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል።
በዚህ ምክንያት የጤና ባለሙያዎችን እና መምህራንን ጨምሮ የተለያዩ ዘርፎች የተሰማሩ የመንግሥት ሰራተኞች የደመወዝ ማሻሻያ እንዲደረግ ጥያቄ እያነሱ ይገኛሉ።
ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር የመንግሥት ሰራተኛን የኑሮ ደረጃ ከማሻሻል አኳያ በመንግሥት ምላሽ ዙሪያ ማብራሪያ ቢሰጥበት።
በተጨማሪ መንግሥት የዜጎችን የመኖሪያ ቤት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተለያዩ ስራዎችን እያከናወነ እንዳለ ይታወቃል ይሁን እንጂ ካለው የቤት ፈላጊ ቁጥር ጋር ተነጻጽሮ ሲታይ ገና ብዙ ስራ ይጠይቃል። መንግሥት በአጭር፣ በመካከለኛና በረጅም ጊዜ በከተሞች የሚታየውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ምን እየሰራ ይገኛል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።
የምክር ቤቱ ስብሰባ በብሔራዊ ቴሌቪዥን ቀጥታ እየተላለፈ ይገኛል።
በተጨማሪ በምክር ቤቱ የዩትዩብ ገጽ መከታተል ይቻላል ፦ https://www.youtube.com/live/yLIns-2_vZM?feature=shared
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤791🙏78😡52😭27🤔19👏11😱6😢6🥰3